text
stringlengths
414
53.2k
አቶ ፈለቀ አጥናፌ ይባላሉ የ76 አመት የዕድሜ ባለፀጋ ናቸው፡፡ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 አዲሱ አደይ አበባ ስቴድየም አካባቢ ነዋሪ ናቸው፡፡ ስታዲየሙ ውስጥ በሚመሸጉ ሌቦች በደረሰባቸው ጉዳት ከአገር ውስጥ እስከ ውጪ ሆስፒታሎች ተመላልሰው ህክምና ተከታትለው አሁን መጠነኛ ለውጥ ማሳየታቸውን ይናገራሉ፡፡ ከ30 አመት በላይ ኖረዋል፡፡ ክፉ ደጉን ባየንበት እንቅስቃሴያችን ሁሉ በፍርሀት በሰቆቃ ሆነ፣ ሰላምና አጣን፤የመኖር ዋስትናችን ተነጠቀ ብለዋል፡፡ ወደ ሰፈሩ ስንመጣ ቦታው ባዶ ስለነበር የምንፈራው ጅብ ነበር፣ አሁን ደግሞ ያኔ ጅቡን ከምንፈራው በላይ የምንፈራው ሰው ነው ይላሉ:: ከውጪ የመጣች ዘመዳቸው ፤ ሀገር ቤት የገባች ቀን መዘረፏን የነገሩን አቶ ፈለቀ፤ እኔንም በቃ ገለነዋል ብለው የወሰዱብኝን ሞባይል ይዘው የዘመዴንም የልጆቿንም ፓስፖርት የያዘውን ቦርሳ ይዘው የገቡት ወደ ስታዲየም ነው ብለዋል፡፡ በአካባቢው የጭፈራና የሺሻ ቤቶች እንቅልፍ ማጣታችን ሳያንስ የማያልቀው ስታዲየም ለሌቦቹ መመሸጊያ በመሆን የመኖር ዋስትናችን ነጠቀን ሲሉ ምሬታቸውን ገልፀዋል፡፡ ሌላው በአካባቢው ባለ አራት ወለል ያለው ህንጻ ቤት ሰርተው እያከራዩ የሚኖሩት አቶ መሰከረ ረታ፤ በአካባቢው በተንሰራፋው ሌብነት ምክንያት ፤ተከራዮች ዘራፊዎቹን ፈርተው በመልቀቃቸው ቤቴ ከተከራየ 1 አመት ከ 6 ወር አለፈው ብለውናል፡፡ግዙፎቹ የቻይና ቴሌኮም ኩባንያዎች ሁዋዌና ዜድ ቲ ኢ ፤ ቤቴን ተከራይተውት ነበር ያሉ ሲሆን ሁለቱም በዘረፋ ተሰላችተው ለቀው ሄደዋል ብለዋል፡፡ በአካባቢው ወደ ሚገኘው ቻይና ሬስቶራንት የሚመጡ የውጪ ዜጎችን መዝረፍ ብቻ ሳይሆን ተሰብስበው ይደበድባሉ ብለዋል፡፡የአካባቢው ነዋሪዎች፣ስራቸው በዚያው አካባቢ የሆነ እንዲሁም በአዲሱ አደይ አበባ ስቴዲየም አካባቢ ሲያልፉ የተዘረፉ ሰዎች ብሶታቸውን ለጣቢያችን ያጋሩን ሲሆን ሁሉም ወንጀለኞቹ ከዘረፉን በኋላ ወደ ስታዲየም ነው የሚገቡት ብለዋል፡፡ ከጓደኛዋ ጋር በቅርቡ ወደ ገባንበት በአካባቢው ወደ ሚገኘው ቢሮዬ እየሄድኩ ነበር የምትለው ደግሞ መስከረም ነች፡፡ ሁለት ሆነው መጥተው ስልኬን በግድ ታግለው ተቀበሉኝ ፤ ጓደኛዬ በዣንጥላዋ ለመከላከል ሞከረች፣ ግን አልተሳካም ስትል በቁጭት ተናግራለች፡፡ በጣም የገረመኝ ትላለች መስከረም፤ በጣም የገረመኝ ፤ ከሰረቁን በኋላ ምንም እዳልተፈጠረ፣ የራሳቸውን ንብረት ተቀብለው እንደሚሄዱ ሁሉ ዘና ብለው ነው ወደ ስታዲየም የገቡት ያለች ሲሆን በጣም ብዙ ሰው የሆነውን እያየ ዝም ማለቱ ለራሳቸው ደህንነት በመስጋታቸው እንደሆነ ነግራናለች፡፡ በአዲሱ ስታዲየም አካባቢ እያለፈ የነበረው ናሆም ደግሞ በመንገድ መዘጋጋት ምክንያት መኪናው ውስጥ ተቀምጦ ረዘም ላለ ጊዜ መንቀሰቀስ ባለመቻሉ አዲስ አይፎን ስልኩ የሌቦች ሲሳይ መሆኑን በሀዘኔታ አጫውቶናል፡፡ አንድ ልጅ መጣና የመኪናውን ስፖኪዮ በሀይል መቶ አጠፈው፤ እኔ በንዴት ጦፌ ትኩረቴን ወደሱ በማድረግ ምን መሆኑ እንደሆነ ስጠይቀው፤ለካ ጓደኛው ክፍት በነበረው በሌላኛው የመኪናው መስኮት ስልኬን ይዞ እየሮጠ ነበር ብሏል፡፡ተከትየው ወደ ገባበት ስታዲየም ልገባ ስል ፤ አብደህ ካልሆነ እንዳታደርገው፣ ተደብድበህ ሌላ እቃም አስረክበህ ነው የምትወጣው አሉኝ ፣ ስለዚህ ስልኬን አስረክቤ ተመለስኩ ብሎናል፡፡ ስሟን መጥቀስ ያልፈለገችው በአካባቢው ተወልዳ እንዳደገች ያነገረችን ወጣት ደግሞ ፤ ሁልጊዜም የአካባቢው ሰዎች ሌቦች እየተከተሉሽ ነው፣ ተጠንቀቂ ስለሚሉኝና በሌሎች ላይ የሚደርሰውን ዝርፊያ ስለማውቅ በጣም ነበረ የምጠነቀቀው ያለች ሲሆን የስራ ሰርቪስ ልይዝ ከቤት በወጣሁበት አንድ ጠዋት ግን የሌሎቹ ክፉ ዕጣ እኔ ላይም ደርሷል ብላናለች፡፡ መሬት ላይ በጭንቅላቴ ፈጥፍጦኝ ቦርሳዬን ይዞ አላልቅ ወዳለው አደይ አበባ ስታዲየም ገባ ብለለች፡፡ ሆስፒታል በመሄድ ጭቅላቴ ላይ የደረሰው ጉዳት የከፋ እንዳልነበረ ባውቅም ከዚያ በኋላ ኑሮዬ ሁላ የፍርሀትና የሰቆቃ ሆነ ስትል ህግና መንግስት ባለበት ሀገር መሀል ከተማ ላይ በጭንቀት መኖሯ እንደሚያንገበግባት ነግራናለች፡፡ሰፈሩ እኮ የለየለት የውንብድና ሰፈር ሆኗል የሚሉት እነዚህ ሰዎች ስታድየሙ መቼ ነው የሚያልቀው? እንዴት ስቴዲየሙስ የሌቦች መመሸጊያ ሲሆን መንግስት ዝም ብሎ ያያል? ሲሉ ትዝብታቸውንና ጉዳታቸውን አጋርተውናል፡፡ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 በተለምዶ ሀያ አምስቱ አፓርትማ ተብሎ በሚታወቀው መንደር ውስጥ የሚኖሩ 450 እና ከዚያ በላይ የሆኑ አባወራዎች ለስፖርት ኮሚሽን፣ ለወረዳ፣ ለክፍለ ከተማ እና ለከተማ አስተዳደሩ ስቃያቸው እንዲቆምላቸው ተደጋጋሚ አቤቱታ አስምተዋል፡፡ ነዋሪዎቹ ለጣቢያችን እንተናገሩት በነዚህ ወንበዴዎች ምክንያት ሴቶች ይደፈራሉ፣ህፃናት ወንዶች ላይ ጥቃት ይደርሳል፣የውጪ ዜጎች ሳይቀር ይደበደባሉ፣ እስከ ሞት አደጋ የደረሰበትም አለ ሲሉ ነግረውናል፡፡በመኖርያ ቤቶች ላይ በተገጠሙ ካሜራዎች ዝርፍያ ሲፈፀም የተቀረፁ ቪዲዮዎች ነዋሪዎቹ ለጣቢያችን የላኩ ሲሆን ሌቦቹ ለመዝረፍ ከአደይ አበባ ስታዲየም ሲወጡ፣ ከነጠቁ በኋላ ደግሞ ወደ ስታዲየሙ ሮጠው ሲገቡ ቪዲዮው ያሳያል፡፡ በስፖርት ኮሚሽን የስፖርት ፋኩልቲ ዳይሬክተር አቶ አስመራ ግዛው ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት ፤ እኛም ተቸግረናል፣ ጥበቃ እየተደበደበ የሳይቱ ዕቃ እየዘተረፈ ነው ፣ ነዋሪዎቹ ለኛ ደብዳቤ ፅፈዋል፣ እኛ ደግሞ ክፍለ ከተማ ደብዳቤ ፅፈናል ብለዋል፡፡ዋናው ችግር የሆነብን በህገ ወጥ መንግድ በቦታው ሸራና ላስቲክ ወጥረው የሚኖሩት ናቸው ያሉ ሲሆን ከተፈቀደ በር ውጪ መስጊድ አለ፣ በመስጊዱ በኩል ደግሞ ፤ ሌላ በር አለ፣ በዚያ በኩል ነው የሚገቡት እሱን ለመቆጣጠር ደግሞ በፍርድ ቤት ሂደት ላይ ያለው መስጊድ ሌላ ምትክ ቦታ ማግኘት አለበት ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ፕሮጀክቱ ሳይጀመር ጀምሮ ባለፈው ሳምንት ፤ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት እስከተደረገው የምክር ቤት ጉባኤ ድረስ ይሄን ጉዳይ ሺህ ጊዜ ጠይቀናል ፤ ያሉ ሲሆን ክፍለ ከተማው ለመስጊዱ ምትክ ቦታ እፈልጋለሁ ብሏል ሲሉ የነገሩን ሲሆን ፖሊስ ያኔ ህገ ወጥ ሰፋሪዎችን አጸዳለሁ ብሏል ብለውናል፡፡ ስታዲየሙ በፕሮግራሙ መሰረት እየተሰራ ነው የሚሉት አቶ አስመራ አንደኛው ምዕራፍ አልቆ ሁለተኛው የማጠቃለያ ምዕራፍ ተጀምሯል፤ የሚመለከተው ክፍል ህገ ወጥ ሰፋሪዎቹን ካላነሳልንና ለመስጊዱም ሌላ ምትክ ቦታ ካልሰጠ ግን ነዋሪው ላይ ብቻ ሳይሆን ፕሮጀክቱ ላይም ከፍተኛ አሉታዊ ተፅዕኖ ያሳድራል ሲሉ አሳስበዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ኮሚሽን ጋር ሄደን ስለ ጉዳዩ ጠይቀናቸዋል፡፡ የተለየ ትኩረት ሰጥተን የምነከታተከውና የምንጠበቀው ቦታ ነው ሲሉ ነግረውናል፡፡ በኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ኮማንደር ፋሲካ ፋንታ በህገ ወጥ መንገድ ሸራና ላስቲክ ወጥረው የሚኖሩት ካልተነሱ ችግሩ ዘላቂ መፍትሄ አያገኝም ያሉ ሲሆን የሚመለከተው አካል ይሄን እንዲያደርግ አሳስበዋል፡፡ በአካባቢው የሚገኙ ጭፈራና ሺሻ ቤቶች ለችግሩ መበርከት ሌላ ምክንያት እንደሆኑም ገልፀዋል፡፡ ከወንጀለኞቹ ጋር ቀጥታ ግንኙነት ያላቸው ከነዚሁ ዲስኮ ቤቶች የሚወጡ ረጅም እጅ ያላቸው ሰዎች ጥቂት አይደሉም ብለዋል፡፡በቋሚነት ከተመደቡ ፖሊሶች በተጨማሪ ቦታው አደገኛ በመሆኑ ምክንያት በየትኛውም የአዲስ አበባ ክፍል ያላደረግነውን በቋሚነት ፓትሮል መኪና እየተሸከረከረ እንዲጠብቅ መድበናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ እስከ ሰበር ሰሚ ችሎት ድረስ ሄዶ መፍትሄ ያላገኘው መስጊድና የአየር ካርታ ጭምር አለን በማለት ከቦታው አንነሳም የሚሉ ሕገ ወጥ ሰፋሪዎቹን የሚመለከተው ክፍል መፍትሄ ካላበጀላቸው ግን የአካባቢው ችግር ዘላቂ መፍትሄ አያገኝም ብለዋል፡፡ ተለዋዋጭ ባህሪ ያውን በከተማዋ የተንሰራፋውን ስርቆት ለመቀነስ በግጭትና በተለያዩ ምክንያቶች ወደ መዲናዋ የሚፈልሱት ወጣቶች ላይ እልባት መሰጠት አለበት የሚሉት ኮማንደር ፋሲካ ህዝቡም የስርቆት ወንጀል ሲፈጸምበት አንዴ አመልክቶ ምላሽ ካላገኘ ወደ በላይ አካል ሄዶ ጉዳዩን የማስፈፀም ልምድ ማዳበር አለበት ሲሉ ምክራቸው ለግሰዋል፡፡ በስቴዲየሙ ዙርያ በህገ ወጥ መንገድ ስለሚኖሩት፣ስለሚነግዱትና፣ ምትክ ቦታ ይፈልግለታል ስለተባለው መስጊድ ልንጠይቅ ወደ ቦሌ ክፍለ ከተማ ያደረግነው ተደጋጋሚ ሙከራ አልተሳካም፡፡
የመለስ ዜናዊ አስተሳሰብና ምግባር ሕዝብን በተለይም ፖለቲከኞችን በተራራቀ ተቃራኒ ጫፍ እንዳቆሙ መሞታቸዉ የኢትዮጵያን ፖለቲካ በበጎ ወይም በመጥፎ፥ ወይም በሁለቱም መሐል-ክፉኛ መንካቱ እንደማይቀር ያኔ ተብሎ ነበር። አሁንም አልቀረም። የቀድሞዉ ጠቅላይ ሚንስትር ተሸኙ። ሁለት ሺሕ አራትም ተሰናበተ። እና አዲስ ዓመት። ሁለት ሺሕ አምስት። ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ርዕሠ-ሊቃና ጳጳሳት እና፥ በአቶ መለስ ዜናዊ ሞት ማግስት የባተዉ ሁለት ሺሕ አምስት ካዲስ መሪ፥ ካዲስ ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ሹመት ጋር አዲስ ተስፋ አጭሮም ነበር። ዓመቱ ዛሬ-አርጅቶ ሊሰናበት ሁለት ቀን ቀረዉ። የዓመቱን የኢትዮጵያ አበይት ፖለቲካዊ ክንዉኖች እየጠቃቀስን፥ ተስፋዉ መጠዉለግ-መፅደቁን፥ ላፍታ እንቃኛለን። አብራችሁኝ ቆዩ። መለስ በተቀበሩ በሳምቱ ሁለት ሺሕ አምስት እንደ አዲስ ዓመት ሲብት ሁለት የስዊድን ጋዜጠኞችን ጨምሮ በሺሕ የሚቆጠሩ እስረኞች በምሕረት መፈታታቸዉን የኢትዮጵያ መንግሥት ማወጁ፥ የአዲሱ ዓመት አዳዲስ መሪዎች አሮጌዉን ከፋፋይ መርሕ ከአሮጌዉ ዓመት ጋር ለማሰናበት ፍንጭ ማሳየታቸዉ መስሎ ነበር። ከእስረኞቹ የመፈታት ዜና በተጨማሪ የኢትዮጵያ መንግሥት ከኦጋዴን ብሔራዊ ነፃዉጪ ግንባር (ኦብነግ) ጋር ለመደራደር መወሰኑን አስታዉቆም ነበር።ኦብነግ የመለስ ዜናዊ መንግሥት ለረጅም ጊዜ ባሽባሪነት የወነጀለዉ፥ ከሁለት ሺሕ ሁለት ጀምሮ ደግሞ ከአልቃኢዳ፥ ከአልሸባብ፥ እና ከሁለት ሐገር በቀል ድርጅቶች ጋር በሕግ-በአሸባሪነት የፈረጀዉ ቡድን ነዉ። በዚሕም ሰበብ በመለስ ሞት ማግሥት አዳዲሶቹ መሪዎች ከኦብነግ ጋር ለመደራደር መስማማታቸዉን ሲያስታዉቁ፥ ለኢትዮጵያ ፖለቲካ አዲስ ተስፋ ማጫሩ አልቀረም። በአዲሱ ዓመት ዋዜማ ናይሮቢ ኬንያ ዉስጥ በኢትዮጵያ መከላከያ ሚንስትር ሲራጅ ፈርጌሳና በኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አዉጪ ግንባር የዉጪ ግንኙነት ሐላፊ በአብዱረሕማን መሕዲ መካካል የተደረገዉ ድርድር እንዲደረግ የወሰኑት አቶ መለስ ዜናዊ ከመሞታቸዉ በፊት መሆኑ ሲነገር ግን ተስፋዉ የአዲሱ ዓመት ፀጋ፥ የአዲሶቹ መሪዎችም ብልሕነት እንዳልሆነ ግልፅ ሆነ። እስረኞቹ የተለቀቁትም በመለስ ዉሳኔ እንደነበር ተነግሯል። የሁለቱ ወገኖች ተደራዳሪዎች በድርድሩ ሥነ-ሥርዓታዊ ጉዳዮች ተስማምተዉ፥ ለመስክረም ማብቂያ ለሁለተኛ ዙር ድርድር ለመገናኘት ተቀጣጥረዉ ነበር። መንግሥት አማፂዉ ቡድን ሕገ-መንግሥቱን ካልተቀበለ አልደራደርም በማለቱ፥ አማፂዉ ቡድን ቅድመ ሁኔታዉን ባለመቀበሉ ቀጠሮዉ-በቀጠሮ ቀረ። ተስፋዉም ቢያንስ ለዚሕ ዓመት ተጨናጎለ። ተስፋ የማይቆርጠዉ ወይም ተስፋ ላለመቁረጥ፥ ተስፋ የሚያደርገዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሌላ ተስፋ የሚያደርግበት ሰበብ ምክንያት አላጣም። የአዲሱ መሪዉ ቃል ዋናዉ ነበር። የአቶ መለስ ዜናዊ ሞት ከታወጀበት ጊዜ ጀምሮ የጠቅላይ ሚንስትርነቱን ሥልጣን በጊዚያዊነት የያዙት ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ሐይለ ማርያም ደሳለኝ የጠቅላይ ሚንስትርነትቱን ሥልጣን በይፋ ተረከቡ። መስከረም አስር። አዲሱ ጠቅላይ ሚንስትር ኋላ እንዳሉት የዚያን ቀን ያደረጉትን ንግግር ፍሬ ሐሰብ ከማርቀቅ በስተቀር ንግግሩን የፃፉት ሌሎች ናቸዉ። ንግግሩን እንደ ኦጋዴኑ ድርድር ሟቹ ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ የወሰኑት ወይም ፅፈዉ የተዉት ነዉ ማለት ግን አይቻልም።የንግግሩ ይዘት፥ ቃሉም ብዙ አዲስ አይደለም። ግን የአዲሱ ጠቅላይ ሚንስትር ነዉ። የሐይለ ማርያም ደሳለኝ። ሁሉም ተባለ። የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ጥሪ፥ የነፃ ጋዜጠኞች አቤቱታ፥ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ስሞታ፥ የሙስሊሞች ጩኸትም ቀጠለ። ታሕሳስ መባቻ። የአል-ጀዚራዋ ጋዜጠኛ አዲሱን የጠቅላይ ሚንስትር ጠየቀች። «ሙስሊሞችን በተመለከተ በቀጠለዉ የተቃዉሞ ሠልፍ ምክንያት (እና በሌላም ምክንያት) በሐገሪቱ ዉስጥ ብዙ ችግሮች አሉባችሁ። በሺ የሚቆጠሩ ሰዎች ታስረዋል። ብዙዎቹ እንደሚሉት መንግሥት አህባሽ የተሰኘዉን የእስልምና (ሐራጥቃ) በሕዝቡ ላይ በሐይል ጭናችኋል፥ መንግሥት ሐይማኖቱን በሐይል ባዲስ መልክ ለመቅረፅ ጠንካራ እርምጃ ወስዷል ይላሉ። ጠንካራ እርምጃ ነዉ።» ጠቅላይ ሚንስትሩ መለሱ። «እንደሚመስለኝ ይሕ የአናሳዎች ድምፅ ነዉ። የአብዛኞቹ ድምፅ አይደለም። የአብዛኞቹ ሙስሊሞች ጥያቄ የራሳቸዉ የአስተዳደር ሥርዓት እንዲኖራቸዉ ነዉ። መንግሥት በነሱ የአስተዳደር ሥርዓት ዉስጥ የሚያገባዉ የለም። ለሐይማኖት ያልወገነ መንግሥት ነዉ ያለዉ።ሕገ-መንግሥቱም መንግሥት በሐይማኖታዊ ጉዳይ ጣልቃ እንደማይገባ ይደነግጋል።» ጥር ማብቂያ። ጠቅላይ ሚንስትር ሐይለ ማርያም ደሳለኝ «በሐይማኖታዊ ጉዳይ ጣልቃ አይገባም ያሉት መንግሥት የሚቆጣጠረዉ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጉዳያቸዉ በፍርድ ቤት የሚታይ የሙስሊም መሪዎችን በአሸባሪነት የሚወነጅለዉን ፊልም አሰራጨ። ርዕስ፥ ጅሐዳዊ ሐረካት። ጠቅላይ ሚንስትር ሐይለ ማርያም ለአል-ጀዚራ ቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት ቃለ ምልልስ በፖለቲካ ምክንያት የታሠረ አንድም ሰዉ እንደሌለ ተናግረዉ ነበር። ጥር ማብቂያ። ዓለም አቀፉ የሠብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ሑዩማን ራይትስ ዋች ባወጣዉ ዘገባዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ከጥር ሁለት ሺሕ አራት እስከ ታሕሳስ ሁለት ሺሕ አምስት በነበረዉ አንድ ዓመት ብቻ ሰላሳ የተቃዋሚ ፓርቲ ፖለቲከኞች እና ጋዜጠኞች በአወዛጋቢዉ የፀረ-ሽብር ሕግ ተወንጅለዉ እስራት ተበይኖባቸዋል። የቀድሞዉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ርዕሠ-ሊቃነ ጳጳሳት ከሞቱበት እስከ ዓመቱ አጋማሽ ድረስ የዉጪ እና የሐገር ዉስጥ በሚል ለሁለት የተከፈሉት የሐይማኖት አባቶች ይታረቃሉ የሚል ተስፋ አሳድሮ ነበር። ድርድር፥ ዉይይትም ነበር። የካቲት-ሁሉም ቀረ። የሐገር ዉስጡ ሲኖዶስ የዉጪዉን ጥያቄ ዉድቅ አድርጎ ርዕሠ-ሊቃነ ጳጳሳት ሾመ። ሚያዚያ፥ ምርጫና ጉብኝት ነዉ። መስከረም ላይ ጠቅላይ ሚንስትሩ ቃል ገብተዉ ነበር። ሚያዚያ ላይ ሠላሳ ሦስት ተቃዋሚ ፓርቲዎች ምርጫ ቦርድን ጨምሮ ከመንግሥትና ከገዢዉ ፓርቲ ይደርስብናል ያሉት ጫና እንዲቃለልላቸዉ ያቀረቡት ጥያቄ ዉድቅ ሆነብን በሚል ከአካባቢያዊና ከከተሞች አስተዳድር ምርጫ እራሳቸዉን አገለሉ። ገዢዉ ፓርቲ እና ተባባሪዎቹ ብቻቸዉን ተወዳድረዉ አሸነፉ። ጠ/ሚ/ር ሐይለ ማርያም ደሳለኝ ከአዉሮጳ ሕብረትና ከፈረንሳይ ባለሥልጣናት ጋር ለመነጋገር ብራስልስን፥ ሽትራስቡርግንና ፓሪስን የጎበኙትም ሚያዚያ አጋማሽ ነበር። ግንቦት፥ የአፍሪቃ መሪዎች የአፍሪቃ ሕብረት የተመሠረተበትን ሐምሳኛ ዓመት አዲስ አበባ ዉስጥ በደማቅ ሥነ-ሥርዓት አከበሩ። መሪዎቹ በተሰናበቱ በሳምንቱ ሰማያዊ ፓርቲ የጠራዉ የተቃዉሞ ሠልፍ አዲስ አበባ ዉስጥ ተደረገ። ከ1997 ወዲህ ሕዝብ፥ መንግሥትን በመቃወም አደባባይ ሲወጣ የመጀመሪያዉ ነበር። ግንቦት ሃያ-አምስት። በወሩ አንድነት ለፍትሕና ለዲሞክራሲ የጠራዉ ሠላማዊ የተቃዉሞ ሠልፍ ጎንደርና ደሴ ዉስጥ ተደረገ። የአደባባይ ተቃዉሞ ሠልፍ የማድረጉ ጥረት፥ ሙከራ፥ ዝግጅትም ቀጥሏል። የዚያኑ ያክል ተቃዋሚ ፖለቲከኞች እንደሚሉት በአባሎቻቸዉና በደጋፊዎቻቸዉ ላይ መንግሥት የሚፈፅመዉ እስራት እንግልትም አላባራም። ግንቦትና ሰኔ፥-የኢትዮጵያንና የግብፅን የቃላት እንኪያ ሰላንታ እንዳሰሙን-ሐምሌ ተካቸዉ። የአዉሮጳ ምክር ቤት የሰብአዊ መብት ጉዳይ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ ባርባራ ሎኽቢኸር የመሩት የመልዕክተኞች ቡድን ኢትዮጵያን ጎብኝቶ ነበር። ሐምሌ – ቡድኑ ከመንግሥትና ከተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ጋር ከተነጋገረ በኋላ እስረኞችን ለመጎብኘት ጠይቆ ተፈቅዶለት ነበር። ቃሊቲ ሲደርስ «ማን ፈቀደልህ» ተባለ። የዘንድሮዉ ሐምሌ ለሙስሊሞች የቅዱስ ረመዳን ወር ነበር። የድምጻችን ይሰማ የመስጊዱ ተቃዉሞ ጩኸታቸዉ ግን አላባራም። በተቃዉሞዉ ሰበብ ከፀጥታ አስከባሪዎች የሚደርስባቸዉ ወከባ እስራት ዘረፋና ግፍም ብሶ ቀጥሏል። ለኮፈሌ፥ ለኢዶ፥ ለዋቤ፥ ለቆሬ ከተሞች ደግሞ የዘንድሮዉ ረመዳን የአሳዝኝ ግድያ ወርም ነበር። ሐምሌ ማብቂያ ፀጥታ አስከባሪዎች በተሰበሰቡ ሙስሊሞች ላይ በከፈቱት ተኩስ ሲያንስ አስር ሲበዛ ሃያ-ስድስት ሰላማዊ ሰዎች ገድለዋል። ኢድ-አልፊጥር የፌስታ፥ ደስታ፥ ታላቅ ዕለት ነዉ።የአዲስ አበባ ሙስሊሞች የዘንድሮዉን ረመዳን የፈጠሩት፥ ኢድን ያከበሩት የከብት፥ የበግ፥ የዶሮ ደም አፍስሰዉ ሳይሆን በፖሊስ ቆመጥ የራሳቸዉን ደም አዝርተዉ ነበር። ሁለት ጋዜጠኞችም ታስረዉ ነበር። ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት የጋዜጠኞቹን መታሰር አዉግዟል። በዓለም ላይ በሸሪዓ ሕግ የሚገዙ ሁለት ሐገራት አሉ። ኢራንና ሳዑዲ አረቢያ። ጠቅላይ ሚንስትር ሐይለማርያም ደሳለኝ በኢድ አልፊጥር ማግሥት እንዳሉት ደግሞ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ኢትዮጵያን በሸሪዓ ሕግ የምትገዛ ሦስተኛ ሐገር ለማድረግ ይጥራሉ። ዘንድሮ- ሦስት ሚንስትሮች የተሻሩ፥ ከሦስቱ አንዱ ከተከታዮቻቸዉ በሙስና የታሰሩበት፥ አዳዲስ ሚንስትሮች የተሾሙበት፥ ኢትዮጵያ ባለ-ሦስት ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ካቢኔ የሰየመችበትም ዓመት ነዉ። ዓመቱ በርካታ የህወሃት ቁልፍ ሰዎች እና የደኅንነት አመራሮች እንዲሁም አይነኬ ባለሃብቶች ከሥልጣናቸው እየተነቀሉ ሌሎችን ሲያጉሩበት በነበረው እስርቤት የተወረወሩበት ነው፡፡ የሙስናው መዘዝ ተመዝዞ መጨረሻው የት እንደሚደርስና ወደየት አቅጣጫ እንደሚነጉድ መጪው ዓመት ብዙ ያሳየናል፡፡ ዋናዎቹን የሙስና ሻርኮችንም ይደርስባቸው ይሆን ወይም አልፏቸው ይሄድ ይሁን አዲሱ ዓመት ያሳየናል፡፡(ምንጭ፡ የጀርመን ድምጽ ሬዲዮ፤ ዘገባው ለጋዜጣችን እንዲመች ሆኖ ለመታረሙ ኃላፊነቱን እንወስዳለን)
“ወይኔ ልጄ፣ እጅ እግሬ ልጄ፣ ወይኔ ልጄ፣ ወዴት ነህ ልጄ፣ የት ላግኝህ ልጄ? እምኑ ጋር ነህ? ልጄ … ልጄ … ልጄ … ልጄ …” ጥቁር ቦርሳቸውን በወገባቸው ተሸክመው፣ ቂሊንጦ እስር ቤት ደጅ የሚያነቡ እናት ለቅሶ!! ሁሉም ያነባሉ። ሁሉም ያለቀሳሉ፣ የሚሰማ ግን የለም። እንደውም “ዘወር በሉ” እየተባሉ ይደገንባቸዋል። “ሊታረሙ በህግ ከለላ ስር ሆነዋል” የተባሉ ወገኖች “ተረሽነዋል” የሚለው አስተሳሰብ እየጠነከረ መጥቷል። ለቤተሰቦቻቸው እንደምን ተቆጥረው ይሁን? ይህ ሁሉ የጭካኔ ግፍ ወዴት ይመራን ይሆን? የብዙዎች ጥያቄና ስጋት ነው። በየሰዓቱ የሚወጡት መረጃዎች ደግሞ ስጋቱን የሚያግሉና ቁጣን የሚቀሰቅሱ ሆነዋል። የህወሃት ሹሞችም “የሆነው ነገር ሁሉ የተከሰተው በዕቅድ አይደለም” ይላሉ፡፡ በአልሞት ባይ ተጋዳነት የሚውተረተረው ህወሃት አሁንም አለሁ ቢልም የቂሊንጦ ጉዳይ ማቆሚያ ላጣው ፈተናው ተጨማሪ ነዳጅ ሆኗል፡፡ ይህ አገራዊ ሃዘን ምናልባትም ህወሃት የራሱን ማክተሚያ እያጣደፈ ነው የሚሉ አሉ፡፡ የታሳሪ ቤተሰቦች “እስከ አርብ ጠብቁ” ተብለዋል – ከአርብ በፊትስ ምን ታስቧል? “ህወሃት አብቅቶለታል” በማለት እየተናገሩ ያሉት ምዕራባውያን በተለይም አሜሪካ በህወሃት ላይ ያላትን አቋም ጠበቅ እያደረገች መጥታለች፡፡ ፊት እየዞረባቸው እንደሆነ የተገነዘቡት እነ አባይ ጸሃዬ ጌቶቻቸው ዘንድ ቀርበው በሚችሉት ቋንቋ ኦሮሞና አማራ ተባብረውብናል፤ ሰግተናል በማለት ለሦስት ሳምንት ያህል እየተመላለሱ ቢለምኑም እንደ ቀድሞው የጌቶቻቸውን ይሁንታ ሊያገኙ አልቻሉም። ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ እንደሚሉት ህወሃት የሚመዘው የማደናገሪያ ካርታ ስላለቀበት ትዕዛዝ እንዲቀበል እየተገደደ ነው። ከእውነታው በተገላቢጦሽ የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) አገር እየገዛ እንደሆነ ለማሳመን ቢጥርም አልተሳካለትም። የአገሪቱ በርካታው አካባቢዎች ከቁጥጥሩ ውጪ ሆኗል፡፡ በከመረው እርምና ባፈሰሰው የንጹሃን ደም ህዝብ ፊት ነስቶታል። ሁኔታውን በውል የተረዱት ጌቶቹም እንደቀድሞው ሊጠጋገኑት ከመሞከር ይልቅ ፊታቸውን አዙረውበታል፤ ባደባባይ ሊለዩት ጫፍ ላይ ናቸው። በዚሁ መነሻ እንደ ዱሮው ስብሰባ አይጠራም፤ አይጋበዝም፤ አይፈለግም፡፡ በጎረቤት አገራት በሚካሄዱ ስብሰባዎች እንኳን “አትፈለግም” ተብሏል፡፡ ዥጉርጉር ሚዲያዎች “መንግሥት” እያሉ የሌለውን ወግና ማዕረግ የሰጡት ህወሃት ከትክክለኛ ማንነቱ ጋር የሚመጣጠን ተግባር ላይ የተጠመደውም ለዚሁ እንደሆነ ብዙዎች እየመሰከሩ ነው። የሌለውን ስብዕና ተጎናጽፎ እመራዋለሁ የሚለው ህዝብ ላይ ጦርነት የሚያውጅ የወንበዴ ቡድን፣ እየዋለ ሲያድር ማንነቱና ለመንግስትነት ወግ ሊበቃ የማይገባው እንደነበር ያረጋገጠው የመለስ ህወሃት፣ የህዝብ ተቃውሞን በጸጋ ተቀበሎ ከማስተናገድ ይልቅ የመረጠው መንገድ እርቃኑን ያወጣው ሲሆን፣ ሰሞኑንን የረሸናቸው ወገኖች ጉዳይ ይህንኑ አውሬነቱን ያመላከተ እንደሆን በውጪም ሆነ ባገር ውስጥ ስምምነት አለ። ባለፈው ቅዳሜ የበርካታ ወገኖችን ህይወት የቀጠፈው የቂሊንጦ እስር ቤት ቃጠሎ፣ በውስጡ ሌላ እሣት ፈጥሮበታል፡፡ “አንድ ሰው ሞተ” ሲል ጀምሮ 23 የደረሰው የሟቾች ቁጥር እጅግ በርካታዎች እንደሞቱ በውል የሚያረጋግጥ ሆኗል፡፡ በራሱ በህወሃት/ኢህአዴግ ሁለት ዜጎች በጥይት ተመትተው መሞታቸው መናገሩ ምን ያህሉ በጥይት ተመትተው ይሆን የሚል ጥያቄ ፈጥሯል፡፡ በ1998 ዓም ላይ “የኦነግ አባላት ናችሁ” በሚል ታስረው የነበሩና “ከቃሊቲ ሊያመልጡ ሲሉ ሰባት ታራሚዎች ተገደሉ” ያለው ህወሃት በኋላ ግን ከ160 የሚበልጡ ታራሚዎች በተተኮሰባቸው ጥይት በግፍ ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡ ቢታሰሩም ድምጻቸው ያልታሰረውና የህወሃትን የመኖር ዋስትና አደጋ ላይ የጣሉት እነ በቀለ ገርባ የታሰሩበት ቂሊንጦስ? እንዴት ሆኖ ይሆን? አንድ እናት እዚያው ቂሊንጦ ደጅ “ወይኔ ልጄ፣ እጅ እግሬ ልጄ፣ ወይኔ ልጄ፣ ወዴት ነህ ልጄ፣ የት ላግኝህ ልጄ? እምኑ ጋር ነህ? ልጄ … ልጄ … ልጄ … ልጄ …” እያሉ ያነቡ ነበር። የእናት አንጀት!! ከእሣቱ በፊት 45 ደቂቃ የወሰደ የቀለጠ የተኩስ ድምጽ መሰማቱ፣ እሣት አደጋ መከላከያ እሣቱን ለማጥፋት በቦታው የተገኘበት ሰዓት፣ እሳቱ የተነሳበት ቦታ የት እንደሆነ በውል አለመነገሩና በህወሃት/ኢህአዴግ ሹሞችና አፍቃሪዎች የሚነገረው የተምታታ መሆኑ፣ እሣቱን ያስነሳው ምን እንደሆነና ያስነሳው ማን እንደሆነ ከህወሃት በኩል የሚጣረስ መረጃ መሰጠቱ፣ ሐኪሞች የሟቾች ቁጥር 60 እንደሆነ መናገራቸውና የግለሰቦቹን ማንነታቸውን እንዳይለዩ በአስከሬን ላይ ቁጥር እንዲጠቀሙ መታዘዛቸው … ከዚህ አልፎ ደግሞ ከአገዛዙ የሚሰጠው መረጃ እርስበርሱ የሚጋጭ መሆኑ በህወሃት ውስጥ የተፈጠረውን ሁኔታ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ሆኗል፡፡ በዚህ ጉዳይ ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ የሰብዓዊ መብት ድርጅት ከፍተኛ አመራር “ይህ ሁኔታ በራሱ የሟቾቹን ማንነት ለመደበቅ ሆን ተብሎ እየተቀናበረ ያለ ሤራ እንዳለ አመላካች ነው” ብለዋል፡፡ ቪኦኤ ያነጋገራቸው ቤተሰቦች “እስከ አርብ ጠብቁ” መባላቸውን ተናግረዋል፡፡ ከአርብ በፊትስ የታሰበው ነገር ምን ይሆን? በቂሊንጦ የተሰዉትን ስም ህወሃት ይፋ እንዲያደርግ ምዕራባውያን ፖለቲከኞችና እና ሚዲያው አስጨንቀው መያዛቸው ጎልጉል ያገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ ከዚህ አንጻር በተደጋጋሚ የእስረኞቹ ማንነት እንዲናገሩ ጥያቄው ከቀረበባቸው ከፍተኛ የህወሃት ባለሥልጣናት መካከል አንዱ የማውቀው ነገር የለኝም፤ ሆኖም ግን የተከሰተው ነገር ሁሉ በዕቅድ የተደረገ አይደለም፤ ሆን ተብሎ የተከናወነ ድርጊት አይደለም በማለት ማስተባቤ መስጠታቸው የሟቾቹን ማንነት ከፍተኛ ጥርጣሬ ላይ የጣለ አድርጎታል፡፡ የተከሰተው ቃጠሎ ነው፤ የፈረሰና የተቆለለ ክምር የለም፤ ከፍርስራሽ ውስጥ ሰዎችን የማውጣት ሥራ አይደረግ፤ … የሞቱት ሰዎች ማንነት በቃጠሎው አልጠፋ፤ ታዲያ ለምን ይሆን ቤተሰብ እንዲህ የሚንገላታው? “እናቶች ልጆቻቸውን ፍለጋ ወገባቸውን በመቀነት አስረው በጉልበታቸው እየሄዱ” እንደሆነ ትላንት የተሰራጨው የቪኦኤ ዘገባ ላይ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ የወጣቶች ክፍል ኃላፊ አቶ ጉርሜሳ አያና ባለቤት ወ/ሮ ዐይናለም ደበላ ተናግረዋል፡፡ እርሳቸውም እንደሌሎቹ የባለቤታቸውን መኖር በተመለከተ እስከ አርብ ጠብቁ ተብለው ጭንቅ ውስጥ ናቸው፡፡ ከእነዚህ ወገኖች ሌላ ህወሃት በግፍ በሚገዛት ኢትዮጵያ እጅግ በርካታ ዜጎች በየቀኑ እየተገደሉ፣ እየተሰወሩ፣ እየተሰቃዩ፣ … ይገኛሉ፡፡ መኖራቸው የማይታወቅ፣ የሚጮህላቸው ወገን የሌላቸው፣ የሚዲያ ሽፋን የማያገኙ፣ … የእነዚህስ ቤተሰቦችና ወገኖች እስከመቼ ይሆን የሚጠብቁት? “ልጅን ያህል ነገር ያለበትን ሳላውቅ እንዴት ዝም ልበል?” ያሉትን የዮናታን ተስፋዬን እናት ወ/ሮ ሙጪት ተካን ጨምሮ የአቶ በቀለ ገርባ ባለቤት ወ/ሮ ሃና እና ልጃቸው ወ/ት ቦንቱ በቀለ፣ የአቶ ደጀኔ ጣፋ ባለቤት ወ/ሮ አሰለፈች ሙላትና የመኢአድ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ አሰጋ አሰፋ ልጅ ወ/ት ህይወት አሰፋ ቤተሰቦቻቸው ያሉበትን ሁኔታ አለማወቃቸው ጭንቀት ውስጥ እንደከተታቸው ለአሜሪካ ድምፅ መግለፃቸው ይታወሳል፡፡ በግፍ መታሰራቸው፣ በየቀኑ ግፍ መቀበላቸው፣ መንገላታቸው ሳያንስ አሁን ደግሞ “ንገሩን” እያሉ የሲቃ ድምጽ እያሰሙ ነው፡፡ ቀን አልፎ ቀን እየተተካ መሄዱ በራሱ የግፉዓኑን በሕይወት መኖር ጥርጣሬ ላይ እየጣለው መጥቷል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ቃጠሎው የዓለምአቀፉን ሚዲያ ትኩረት መሳቡ በህወሃት ላይ ከፍተኛ ጫና እያመጣ ነው፡፡ “አብቅቶልሃል” ባሉት አንጋሾቹ ዘንድ ይህ ዓይነቱ አካሄድ ብዙም የሚወደድ ባለመሆኑ ህወሃትን ውጥረት ውስጥ ከቶታል። ዜጎችን በግፍ እየጨፈጨፈ ያለው ህወሃት ከአንጋሾቹ ጋር ፍጥጫ ውስጥ በመግባቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚታየው ነገር “ስሉሱ” የዞረ መሆኑን የሚያመካልት ሆንዋል። እየተገደሉ ያሉትን ዜጎች በተመለከተ ለተባበሩት መንግሥታት መርማሪ ቡድን ህወሃት/ኢህአዴግ በሩን መክፈት እንዳለበት አክርረው የተናገሩት ሳማንታ ፓወር ህወሃት ዜጎችን እየፈጀ መሆኑን ሲናገሩ በዲፕሎማሲያዊ ቋንቋ የጸጥታ ኃይላት “ከልክ ያለፈ ኃይል” መጠቀማቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡ የሁልጊዜ የፖለቲካ ወዳጅ ከሌላት አሜሪካ እንዲህ ያለ የከረረ ነገር መስማት የማይወደው ህወሃት በቂሊንጦ ጉዳይ ውሳኔውን ይፋ ለማድረግ መስማማት አቅቶታል፡፡ ይህም ከአንጋሾቹና ከዓለምአቀፍ ሚዲያ ከሚመጣው ተጽዕኖ ጋር ተዳምሮ ኅልውናውን የሚፈትንበት ሰዓት ላይ አድርሶታል፡፡ “እስከ አርብ ጠብቁ” ብሏል! ሰሞኑን የቀድሞው የበረሃ ጓድ እና የድል ተካፋይ ታምራት ላይኔ ከኤስቢኤስ ሬዲዮ ጋር በሁለት ክፍል ባደረጉት ቃለምልልስ የቀድሞ ጓዶቻቸው ምን ማድረግ እንዳለባቸው በርካታ ምክር ሰጥተዋል፡፡ የወቅቱን የሕዝቡ ጥያቄ “በምን ዓይነት መልኩ እንፍታው በሚለው ጥያቄ ላይ የኢህአዴግ መሪ አካላት (ህወሃትን ማለታቸው ነው) ወታደራዊውና ሲቪል መሪዎች በጉዳዩ ላይ አንድ ቁመና ይዘው የማይገኙበት ሁኔታ ይፈጥራል፤ … ቅራኔው ስለተባባሰ በዚህ እንሂድ ወይስ በዚያ እንሂድ በሚለው ጉዳይ ላይ” የማይቀር ክፍፍል እንደሚከሰት ተናግረው ነበር፡፡ የቂሊንጦ ሟቾችን በተመለከተስ? የሟቾችን ማንነት ይፋ ከማድረግ ጋር የተፈጠረ ነገር ይኖር ይሆን? ስምምነት ወይስ መለያየት? ከአርብ በፊት የታሰበውስ ምንድነው? አንዳንድ “ታማኝ ጋዜጠኞች” በፌስቡክ ገጻቸው “የሟቾች ስም ዝርዝር ሃሙስ ይለጠፋል” እያሉ ነው። የሰው ልጅ ሞት እንደ ኮንዶሚኒየም ወይም እንደ ትምህርት ፈተና ውጤት ወይም “ስማቸው ይለጠፋል” ማለት ሰብዕና የሌለው ህወሃት ራሱ የሚመልሰው እንኳን አይደለም፡፡ ውዶቻቸው የሞቱባቸውና ያልሞቱባቸው እንደ ሎተሪ ዕጣ ነገ ስማቸው ሲለጠፍ ያያሉ፤ ለመሆኑ የህወሃት ግፍና የጭከና መጠን የሚለካበት ገደብ ይኖር ይሆን? ጉዳዩ የታዋቂ ፖለቲከኞች ጉዳይ ስለሆነ ብቻ አይደለም፤ የማንም ህይወትስ ቢሆን እንዴት “የስም ዝርዝር ይለጠፋል” ይባላል? በተመሳሳይ የቂሊንጦ እስር ቤት የተፈጸመውን አሳዛኝ ትራጀዲ አዲስ ስታንዳርድ (addis standard) ሲዘግብ “እስረኞች ሲረሸኑ አየሁ” ያለ እማኝ ጠቅሶ ጽፏል። ቃጠሎው ሲደርስ በቂሊንጦ እስር ቤት ጥበቃ ላይ የነበረ የዓይን እማኝ ጠቅሶ የሚሰቀጥጥ መረጃ ያስነበበው አዲስ ስታንዳርድ እስረኞች ላይ ጥይት መርከፈከፉን አርጋግጧል። እንደ ዘገባው ከሆነ የጥበቃ ሰራተኛው ማንነቱ እንዳይጠቀስ ጠይቆ፣ ቂሊንጦ እስር ቤት ሰራተኛ መሆኑንን የሚያረጋግጥ የስራ መታወቂያውን አያይዞ ነው እልቂቱን በኢሜይል ያጋለጠው። የዓይን ምስክሩ እንዳለው እሳቱ እንደተነሳ 5 እስረኞች ከሁለት ማማ ላይ በተቀመጡ ጠባቂዎች ተገድለዋል። እሳቱን ለማጥፋት ሲረባረቡ የነበሩ እስረኞች ላይ የጥይት እሩምታ ሲወርድባቸውም ተመልክቷል። የ18 እስረኞች አስከሬን ከእስር ቤቱ ሲወጣ ማየቱን የተናገረው የዓይን እማኝ፣ ሁሉም በጥይት መገደላቸውንና እሳት የሚባል ነገር እንዳልነካቸው ያየውን መስክሯል። የእማኙ ገለጻ በቂሊንጦ እስር ቤት ታሳሪዎች “በጅምላ ተጨፍጭፈዋል” የሚለውን ዜና ያጠናክረዋል። በፋሽስት የሚመሰለው ህወሃት “ለማምለጥ የሞከሩ” ሲል የጠራቸው ሁለት እስረኞች በጥይት መገደላቸውን፣ 21 ደግሞ እሳትና ጭስ ተባብረው እንደገደሏቸው የፋሽስት ልሳን የሆነው ራዲዮ ፋና መዘገቡ አይዘነጋም። “የእርም ሽንት፣ የባንዳ ዘር ፍሬ” የሚባለው ፋና የፊታችን ዓርብ ውይም ሐሙስ ደግሞ ምን እንደሚል ይጠበቃል። ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡
ክርስቶስ በደረሰበት ከፍተኛ ድብደባ ምክንያት በመድከሙ፥ ሮማውያን ስምዖን መስቀሉን ተሸክሞ ክርስቶስ ከሁለት ወንበዴዎች ጋር ወደሚሰቀልበት ከከተማ ወጣ ያለ ስፍራ እንዲያደርስ አስገደዱት። ብዙውን ጊዜ ወንጀለኞች ወንጀላቸው የተዘረዘረበት ጨርቅ ከአንገታቸው ላይ ይደረግና መስቀሉን ተሸክመው ወደሚሰቀሉበት ስፍራ እንዲወሰዱ ይገደዱ ነበር። ማርቆስ መስቀሉን የተሸከመው ስምዖን፥ የአሌክለንድሮስና የሩፎስ አባት እንደነበር ገልጾአል። ጳውሎስም በሮሜ 18፡13 ሩፎስን ስለሚጠቅስ፥ እነዚህ ሰዎች ምናልባትም በሮም የሚኖሩ ክርስቲያኖች ሳይሆኑ አይቀሩም። ስቅላት እጅግ አስከፊ የግድያ ዘዴ በመሆኑ፥ ባሮችና ከፍተኛ ወንጀል የሚፈጽሙ ሰዎች ወይም አማፅያን ብቻ በዚህ ዓይነት ይገደሉ ነበር። የአይሁድ መሪዎች ለክርስቶስ በነበራቸው ከፍተኛ ጥላቻ ምክንያት ለዚህ ቅጣት ዳረጉት። በእጆቹና በእግሮቹ ላይ ምስማሮችን ቸነከሩባቸው። በዚህ ዓይነት ስቅላት የሚቀጡ ሰዎች ነፍሳቸው እስኪወጣ ድረስ በአብዛኛው ከሁለት እስከ ሦስት ቀናት ይሠቃዩ ነበር። የተሰቀለው ሰው ቶሎ እንዲሞት ለማድረግ፥ አንዳንድ ጊዜ ወታደርች ቅልጥሙን ይሰብሩ ነበር። ክርስቶስን የሰቀሉት ወታደሮች የክርስቶስን ልብስ ተከፋፈሉ። ከሦስት ሰዓት ጀምሮ እስከሞተበት ዘጠኝ ሰዓት ድረስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ዋለ። ክርስቶስ ከሚቀበለው ሥጋዊ ሥቃይ በላይ ሰዎች በቃላት ይዘልፉት ነበር። ከሁሉም በላይ፥ ክርስቶስ የዓለምን ኃጢአት በመሸከሙ ምክንያት እግዚአብሔር አብ ከእርሱ ጋር የነበረውን ኅብረት አቋረጠ። ክርስቶስ በታላቅ ድምፅ ጮኾ መሞቱ፥ ክርስቶስ ነፍሱን እንደ ሰጠ ያመለክታል። ብዙውን ጊዜ የስቅላት ቅጣት የሚፈጽምባቸው ሰዎች እየተዳከሙ ሄደው ራሳቸውን ይስቱና በዚያው ያርፋሉ። በዚህ ጊዜ ማርቆስ ስለ ክርስቶስ አንድ መልካም ቃል ብቻ ተናግሯል። ክርስቶስ በሚሞትበት ጊዜ አይሁዶች ምን እየሆነ እንዳለ ወይም ክርስቶስ የተለየ ሰው መሆኑን አልተገነዘቡም ነበር። ነገር ግን ቀደም ሲል ብዙ ሰዎች ሲሰቀሉ የተመለከተው የሮም ወታደር፥ ክርስቶስ የተለየና የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ተገነዘበ። የአርማቲያሱ ዮሴፍ ጲላጦስ የክርስቶስን አስከሬን እንዲሰጠው በጠየቀ ጊዜ፥ ጲላጦስ ክርስቶስ ቶሎ በመሞቱ ተደነቀ። የመቶ አለቃው ክርስቶስ መሞቱን ካረጋገጠ በኋላ፥ ዮሴፍ የክርስቶስን አስከሬን ለመውሰድ ፈቃድ አገኘና በራሱ መቃብር ውስጥ ወስዶ ቀበረው። በመጨረሻም፥ ከዮሴፍና ኒቆዲሞስ በተጨማሪ ለክርስቶስ ትኩረት ሰጥተው የቆዩ ሦስት ብቸኛ ሰዎች ነበሩ። እነርሱም ከክርስቶስ ጋር የኖሩ ሴቶች ሲሆኑ ክርስቶስ ሰባት አጋንንት ያወጣላት መግደላዊት ማርያም፥ የታናሹ ያዕቆብና የዮሳ እናት የሆነችው ማርያም፥ የዮሐንስና ያዕቆብ እናት የሆነችው ሰሎሜ ከእርሱ ጋር ቆዩ። አሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት ከሸሹ በኋላ፥ እነዚህ ሴቶች ጌታቸው ሊሞትና ሲቀበር ለማየት እዚያው ቆዩ። የውይይት ጥያቄ፡- ብዙውን ጊዜ ወንዶች ከሴቶች በላይ ደፋሮች እንደሆኑ ይነገራል። በዚህ ጊዜ ግን ሴቶች ከወንዶች በላይ ደፍረው የተገኙት ለምን ይመስልሃል? ይህ እነዚህ ሦስት ሴቶች ለክርስቶስ ስለነበራቸው የእምነት ጥልቀት ምን ያስተምራል? መጀመሪያ የማርቆስን ወንጌል ያነበቡ ብዙ ሰዎች ከፍተኛ ስደት ደርሶባቸዋል። አንዳንዶች በእንስሳት ቆዳ ተሸፍነው ለዱር አራዊት ተጥለዋል። ሌሎች ዘይት ተርከፍክፎባቸው በስታዲዮም እንደ ጧፍ እየነደዱ ብርሃን እንዲሰጡ ተደርገዋል። ከወታደሮች ወይም ከአናብስት ጋር ለመታገል የተገደዱም ነበሩ። አንዳንዶች እንደ ክርስቶስ ተሰቅለዋል። ነገር ግን ስደቱ ምንም ያህል ከባድ ቢሆንም፥ ጌታቸው ክርስቶስ በስቅላት እንደ ሞተ በመገንዘብ ይጽናኑ ነበር። የእርሱ ሞት ለአሟሟታቸው አርአያ ነበር። ጳውሎስ በኋላ እንደገለጸው፥ ክርስቲያኖች መከራ በመቀበልና በመሠዋት ለቤተ ክርስቲያን የጎደለውን ይፈጽማሉ (ቆላ. 1፡24)። (ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ.አይ.ኤም ከታተመውና የአዲስ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር አገልግሎታቸውን ይባርክ፡፡)
እናፍቃለሁ… የውዳሴ እና የምስጋና ግጥም የምጽፍለት መሪና ስርዓት እንድናገኝ። እኩል ተወዳድሬ የምሰራበትና፣ በታማኝነት “ይኸው ይሄን ያህል ገቢ አገኘሁ። ተመኑን ቁረጥና አገሪቷን አቅናበት፣ ሕዝቡን አንቃበት።” ብዬ የምገብርለት ስርዓት፥ ካፌ ቆጥቤ በሰጠሁት ብር ዱላና መሳሪያ ገዝቶ፤ በጠራራ ፀሐይ በ“ለምን አየሁህ” ደምፉ፣ ሕዝብ የሚደበድብበት ወግ የሚቀርበት ቀን ይናፍቀኛል። በሰላም ወጥቶ መግባት፣ በስርዓት መኗኗሩ፤ …ማንበብና መጻፍ መቻሌን ማማረር፣ ማየትና መስማቴን መራገም የማቆምበት ቀን፤ …በገዛ መኝታ ቤቴ ስነቃ፣ በገዛ አገሬ ጎዳናዎች ስራመድ እንግዳነት የማይሰማኝ፤ …በነጻነት ስሜት፣ የነጻነትና የፍቅር ግጥሞችን ብቻ የምጽፍበት ቀን ይናፍቀኛል። ጥበቃዬ ከዳር ደርሶ፣ መገናኘትን ማንቆላጰስና፣ የሰው ልጆችንና መኖርን ማወደስ እናፍቃለሁ። ያረገዘች በሰላምና በጤና የምትገላገልበት፣ የተወለደ የሚያድግበት፣ ያደገም የነፍሱን መሻት የሚከውንበት፣ ሰው ተምሮ የሚያገለግልበት፣ በስተርጅናም በክብር ቆይቶ በደስታ የሚሰናበትበት ኑሮ እናፍቃለሁ። ፅዱና አረንጓዴ አዲስ አበባና ሌሎች ክፍላተ አገራት… ተመጥኖ በተሰጣት ቀንና ማታ ለ13 ወራት በጸሐይ አሸብርቃ፣ መስከረም ሲጠባ አደይ አበባና የመስቀል ወፍ የሚያጌጡባት ዘረኝነት ያላጠቃት ኢትዮጵያ ትናፍቀኛለች። ወጣቶች በተስፋ መቁረጥ የማይኖሩባት፣ እናቶች ለልመና የማይወጡባት፣ ህጻናት በየጎዳናው የማይበተኑባት አገሬ ትናፍቀኛለች። ይገርመኛል፥ “መጽሐፎችህ ጨለምተኞች ናቸው” ሲሉኝ፤ “ግጥሞችህ፣ እንዲሁም ፌስቡክ ላይ የምትለጥፋቸው ጽሁፎች ጨለምተኞች ናቸው።” ሲሉኝ። ኑሮዬን የሚያውቁት ይመስል ቀለምና የብርሃን ዓይነት ሲመርጡለት ሳይ ይገርመኛል። “እንዲህ አጠቋሩረኸው ስታበቃ “የብርሃን” ማለትህ ሽሙጥ ነው?” ይሉኛል፤ …ብርሃን መውደዴን፣ ብርሃን መናፈቄን ሳያውቁ። ሀሳቤን መግለጼን እንጂ፥ መንጻት፣ መጥቆራቸውንስ አውቃለሁ? ብርሃንን መተረክስ አይቀልም? ደግሞ “ጆ ሁለቱንም መጽሐፍቶችህን በ3 ዓመታት ልዩነት ልክ ግንቦት 8 ያደረግከው ለምንድን ነው?” ተብዬ ለብዙኛ ጊዜ ተጠየቅኩኝ። ባጋጣሚዎች ሳልመልሰው ያልፋል። ምክንያቴን የልደት ቀኗ ግንቦት 8 ለሆነችው ወዳጄ Kal Kidan ብቻ ነበር ነግሬያት የማውቀው። “የ1981 ዓመተ ምህረቱ መፈንቅለ መንግስት ናፋቂ ሆነህ ነው እንዴ?” ብሎ ያስፈገገኝም አለ። ዛሬ ላውራው እስኪ… “ብርሃን ብርሃን” ማለቴ፣ መጽሐፎቼን ግንቦት 8 ለማስመረቅ መፈለጌም፥ በግንቦት 7 ቀን፣ 1997 ቁጭት የተደባለቀበት ትዝታ ነው። ብርሃን ናፍቄ ነበር። ‘ምርጫው ለውጥ ያመጣልናል፣ ከዴሞክራሲ ጋርም ያስተቃቅፈናል’ ብዬ፣ በከፍተኛ መጓጓት እና መቁነጥነጥ ውስጥ ሆኜ ነበር ደርሶ ማለፉን የምጠብቀው። ሰው ለመምረጥ እንደዚያ ይስገበገባል?? (ዴሞክራሲ ግን ለምን የማናውቀው ቦታ የሄደብንና መምጫውን የማናውቅ ዘመድ ይመስለኛል?) የግንቦት7 ማግስት…ግንቦት 8ን ለብስራት ነበር ያለምኳት፤ ለለውጥ እና ለነጻነት ግጥሞች ነበር ተስፋ ያደረግኳት፤ ለመተቃቀፍና በደስታ እንባ ለመራጨት ነበር ያሰብኳት። የብርሃን ነዶዎች ዙሪያዬን እየከበቡ ያቃዡኝ ነበረ። በኑሮዬ ጣሪያ ቀዳዳዎች ሾልከው ሾልከው ወለል ላይ የቆሙ የብርሃን በትሮች፥ የተስፋ ምርኩዝ ሆነውኝ ያጽናኑኝ ነበረ። እንደ“ይቺን ብላ! ዶሮ ማታ”… ‘ሲነጋ ባህሩ ይከፈልልንና ተሻግረን አገራችን እንገባለን።’ እል ነበር ለራሴ። ፍትህ ተከብሮ፣ ሰዎች ዋጋ እንደተከፈለባቸው በክብር ሲኖሩ እየታየኝ ብቻዬን ያስወራኝ እንደነበረ የትናንት ያህል ትዝ ይለኛል። እኩል፥ ልቀላቀል የምችለው ከሙስና የፀዳ የሥራ ዓለምና መመረቄም ይናፍቁኝ ነበር። በልቤ፥ የምጽፋቸውን የደስታ ግጥሞች እያሰብኩ በቀብድ ‘poegasm’ ላይ ደርሼ አውቃለሁ። …ይናፍቁኛል እነዚያ ጊዜያት! ወደው የማያገኙትን ሰው ሲጠብቁ፥ ቁርጡ ቀን ባያልፍ ያስሸልላል። የወዳጅ ዘመድ “አይዞህ”… “እየጠበቅኩ ነው” የማለት ማጽናናት ጫፍ ላይም አይደርስም። ሲነጋ ግን እንዳይሆኑት ሆኖ ዛሬም ድረስ “እህህ” እያስባለን ያለ ነገር ተከሰተ። ጭራሽ 5 ዓመት ተቆጥሮ ጉድ አፍርቶና ጎምርቶ “100% ተመርጠናል” ብለው አረፉት። ይኸው ቀን ጠብቆ የታፈኑ ድምጾች በየቦታው ስርዓቱን ሲያወግዙ ተሰሙ። ምላሹም “እንካ ቅመስ” ሆነ። በጸሐይ ደም የትም ፈሰሰ። እስሩም ድብደባውም በገፍ ሆነ። ሆኖም፥ “ኧከሌ ታሰረ” ሲባል፥ “አርፎ አይቀመጥም ነበር።” ይሉ የነበሩ ሰዎች ዐይናቸው ተገለጸ። “እነ ኧከሌ በጸረ ሽብር አዋጁ ክስ ተመሰረተባቸው” ሲባል “የሆነ ነገር ሳያኖርማ…” ይሉ የነበሩ ሰዎች ከእውነታው ጋር ተፋጠጡ። “ፖለቲካና ኤሌክትሪክ በሩቁ” የሚሉ ወዳጆች፥ በግድ ዙሪያቸው ስለሚከናወነው ነገር ማወቅ፣ መጠየቅና ምሬትን መግለጽ ጀመሩ። የጭቆና መብዛት፥ የግዱን የነዋሪዎችን ዐይን ይገላልጣል። ይኼ እንደ ጥሩ ጭላንጭል ኾኖ ያጽናናል እንጂ፥ የተደረገብን ነገር፣ ለመናገር ያከብዳል። ዝም ለማለትም ይጨንቃል። መናፈቅ ግን አይከለከልም! …ዛሬም ብዙ ብዙ ነገር እናፍቃለሁ! ጊዜና ባለጊዜ አልፈው፥ እንደምርጫ 97 ተስገብግቤ ቀበሌ ሄጄ የምመርጥበት ሰልፍና፣ በልቤ ስዬው እንደነበረው ዓይነት የምርጫ ማግስት እናፍቃለሁ! አንሙትማ! Rate this: Posted on August 15, 2016 September 1, 2016 Categories UncategorizedTags EthiopiaLeave a comment on ብርሃን፣ ግንቦት 8 እና ናፍቆት…
ብሰንኪ ለበዳ ኮቪድ19ን ኵናትን ንክልተ ዓመታት ኣብ ወረዳ ዋጃ ኣላማጣ ተቛሪፁ ዝነበረ ከይዲ ምምሃር ምስትምሃር ምጅማሩ እቲ ወረዳ ኣፍሊጡ።ድሕሪ ሰላሳ ዓመታት ንፈለማ ግዜ ብቋንቋ ኣምሓርኛ ትምህርቲ ከምዝጀመረ ተፈሊጡ። ይኹን እምበር ክምሃሩ ካብ ዝግብኦም ተማሃሮ 10 ሚእታዊት ጥራይ ይመሃሩ ምህላዎም ተገሊጹ። ሓላፊ ማሕበራዊ ዘፈር ግዚያዊ ምምሕዳር ዋጃ ኣላማጣ ኣቶ ሙሉጌታ ኣስማማው ምምሃር ምስትምሃር ኣብዚ ሰሙን ክቕፅል ምስተገበረ ብ ቋንቋ አደ ናይ ምምሃር ሕቶ ብዝተወሰነ ደረጃ ተመሊሱ ኣሎ ኢሎም። ተወካሊ ሓላፊ ቤት ፅሕፈት ትምህርቲ ወረዳ ራያ ኣላማጣ ኣቶ ተካ ንጋቱ ኣብቲ ወረዳ ክምሃሩ ዝግብኦም ልዕሊ 19,000 ተማሃሮ እንተኾኑ እውን ኣብ ሓደ ካልኣይ ደረጃ ቤት ትምህርትን 14 ቀዳማይ ደረጃ ኣብያተ ትምህርቲ ይመሃሩ ዘለው 1,140 ተማሃሮ እዮም ኢሎም። ዕለታዊ ፈነወ ድምጺ ኣመሪካ 08/12/2022 ፈነወ ትግርኛ ሓሙስ ፈነወ ትግርኛ ብናይ`ዚ መዓልቲ ዓበይቲ ዜና ይጅምር ። ካብ ኤርትራን ኢትዮጵያን ዝረኽቦም ቃለ-መጠይቓትን ሰሙናዊ መደባትን ድማ የስዕብ ። ሰሙናዊ መደባት ሓሙስ፡ መንእሰያት/ ጥዕና
በኢትዮጲያ የውስጥ ጉዳይ ላይ በመግባት የዕጅ መጠምዘዝ ስራ ለመስራት በሚሞክሩ ተቋማት እና የታላቁ ህዳሴ ግድብ ስራ እንዲስተጓጎል በሚሰሩ አካላት ላይ ተቃውሞ ለማሰማት ሰላማዊ ሰልፍ ይደረጋል ተብሏል፡፡ የሰላማዊ ሰልፉ ዋነኛ አላማ የኢትዮጲያ ህዝብ በሀብቱ ለመጠቀም የማንንም ፈቃድ የማይሻ እና በዚህ ጉዳይ ላይ የማይደራደር መሆኑን ለዓለም ህዝብ ለማሳወቅ ነው ተብሏል፡፡ ስለ ኢትዮጲያ ትክክለኛ መረጃ ለዓለም እንዳይደርስ በሚሰሩ ሀገራት እና አለምአቀፍ ሚዲያዎች ላይ ተቃውሞ ለማሰማት ህዝባዊ ሰልፍ ለማዘጋጀት ዝግጅታቸውን ማጠናቀቃቸውን አስተባባሪ ኮሚቴዎች ዛሬ በሰጡት መግለጫ ላይ አሳዉቀዋል፡፡ በመሆኑም መላ የሃገሪቱ ህዝብ እና የኢትዮጲያ ወዳጅ የሖኑ የውጭ ሀገር ዜጎች እና ተቋማት ህዝባዊ ሰልፍ በሚከናወንበት እለት አጋርነታቸውን እንዲያሳዩ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ የፊታችን መጋቢት 19 የሚደረገ ሲሆን በመስቀል አደባባይ ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ ይካሄዳል ተብሏል፡፡ የሰላማዊ ሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴዎች እንደተናገሩት፣ ህዝባዊ ሰልፉን ለማድረግ የሚመለከታቸው አካላት ፈቃድ እንዲሰጣቸው ከሳምንት በፊት ያቀረቡ ሲሆን፣ ተቋሙ ተቀብሏቸው የራሱን ዝግጅት እያደረገ ይገኛል ሲሉ ኮሚቴዎቹ ገልፀዋል፡፡
በጁላይ 6፣ የማሰብ ችሎታ ያለው ብጁ የቦርድ ጨዋታ ፈጠራ መድረክ “CubyFun” በቅርቡ ከፕሮፌሰር ጋኦ ቢንግኪያንግ እና ከቻይና የብልጽግና ካፒታል ጋር ከሌሎች ባለሀብቶች ወደ 10 ሚሊዮን ዩዋን የሚጠጋ የገንዘብ ድጋፍ መልአክ አግኝቷል።አብዛኛው የተቀበለው ፈንድ ለምርት ልማት እና ለሰርጥ ማስፋፊያ የሚውል ነው። በአሁኑ ጊዜ የቴክኖሎጂ እድገቶች በዋነኛነት በምናባዊ ጨዋታዎች እና በሞባይል ጨዋታዎች ውስጥ የተካተቱ ናቸው።ነገር ግን፣ ለአዲስ የቦርድ ጨዋታ፣ ከመስመር ውጭ ጨዋታ አይነት አሁንም ብዙ ቦታ አለ፣ እና ለብዙ አመታት ባህላዊ ሆኖ ይቆያል።ይህ ፈጣን የማህበራዊ ጨዋታ ከቴክኖሎጂ እና ብልህነት ጋር መቀላቀል እንዳለበት ግልጽ ነው።በዚህ ምክንያት የሼንዘን ኩባንያ CubyFun እራሱን ያዳበረ የማሰብ ችሎታ ያለው የቦርድ ጨዋታ አስተናጋጅ ምርት JOYO ን ለመክፈት እና በባህላዊው የቦርድ ጨዋታ ላይ አስተዋይ የሆነ መስተጋብር ለመፍጠር እየሞከረ ህጻናትን እና ወጣቶችን ከስክሪኑ በማራቅ እና ፊትን እንዲመሩ ያስችላቸዋል። - ፊት ለፊት መስተጋብር.በተጨማሪም CubyFun በ iPad APP መልክ የቦርድ ጨዋታ ፈጠራ መድረክን POLY በተሳካ ሁኔታ ጀምሯል፣ በዚህም ተራ ተጠቃሚዎች የራሳቸውን ብልህ ብጁ የቦርድ ጨዋታ መፍጠር ይችላሉ። የCubyFun መስራች ሱ ጓንዋ እንዳብራሩት የማሰብ ችሎታ ያለው የቦርድ ጨዋታ አስተናጋጅ ምርት ከመስመር ውጭ ጨዋታዎች መቀየሪያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።በአስተናጋጁ ውስጥ ከፍተኛ ትክክለኛነትን እና ምስላዊ ማወቂያን እና ሌሎች ዳሳሾችን በማዘጋጀት ከመስመር ውጭ የማሰብ ችሎታ ያለው መስተጋብር ለማግኘት የተጫዋቹን የተግባር አቀማመጥ፣ የምልክት ዳኝነት እና አስተዋይ ዳኛ ለይቶ ማወቅ ይችላል። የCubyFun ዋና አባላት በዋናነት ከዲጄ-ኢኖቬሽንስ የመጡ ናቸው።መስራቹ እና ዋና ስራ አስፈፃሚው ሱ ጓንዋ በአንድ ወቅት ለ Evernote ፣ Sinovation Ventures እና DJ-Innovations ሰርተዋል ፣ በ RobomasterS1 ፣ Spark Drone ፣ Mavic drone ፣ Osmo handheld gimbal እና ሌሎች ምርቶች ምርምር እና ልማት ላይ ተሳትፈዋል። የዚህ ዙር ባለሀብት የሆነው የቻይና ብልጽግና ካፒታል ቡድን፣ “ከአስደናቂ የፈጠራ እና የፈጠራ ችሎታው ጋር፣ የኩቢፈን ቡድን ፕሮጀክቱን ለመጀመሪያ ጊዜ ስንገናኝ በጣም አስደነቀን።ከዲጂአይ የመጣው መስራች ቡድን በርካታ የማሰብ ችሎታ ያላቸውን የሃርድዌር እና የሶፍትዌር ምርቶችን በማዘጋጀት ጥሩ ውጤት በማስመዝገብ ተሳትፏል።እራስን የመማር እና የመድገም ችሎታ ያለው ቡድን የፈጠራ እና የማሰብ ችሎታ ያላቸውን ምርቶች በመፍጠር የራሱን የምርት ስም መገንባት ሊቀጥል ይችላል ብለን እናምናለን።
የዩክሬን ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ የዩክሬን እና የራሽያ ሀይሎች በሲቪሮዶኔትስክ ለሚገኘው እያንዳንዷ ስንዝር መሬት እየተዋጉ መሆናቸውን ገልፀው፣ ዩክሬን ዘመናዊ የሚሳይል መቃወሚያ ሥርዓት ያስፈልጋታል ሲሉ ዓለም አቀፍ አጋሮችን ተማፅነዋል። ዘለንስኪ ምሽቱን በቪዲዮ ባስተላለፉት መልዕክት የሩሲያ ቁልፍ ኢላማ አለመቀየሩን እና በሲቪሮዶኔትስክ ምዕራብ እና ደቡብ ምዕራብ ወደሚገኙት ሊሲቻንስክ፣ ባከሙት እና ስሎቭያንስክ ከተሞች እየገፉ በሆኑን ተናግረዋል። የዘለንስኪ አማካሪ ሚኻይሎ ፖዶሊያክ ሰኞ እለት ባስተላለፉት የትዊተር መልዕክት "ጦርነቱን ለማስቆም ከፍተኛ የጦር መሳሪያዎች ያስፍለጉናል" በማለት የሚያስፍለጉዋቸውን የመሳሪያ አይነቶች እና ብዛት በዝርዝር አስፍረዋል። የመከላከያ ሚኒስትር ወኪሎች ረቡዕ እለት በብራስልስ ስብሰባ እንደሚያካሂዱ በመግለፅም ውሳኔያቸውን እንደሚጠባበቁ አስታውቀዋል። በሁለቱም ወገኖች በኩል እየደረሰ ያለውን ጉዳት ማረጋገጥ ባይቻልም በሩሲያ በኩል የሟቾች ቁጥር ከ40 ሺህ እንደሚበልጥ ዘለንስኪ በዚህ ወር ገልፀው ነበር። የእንግሊዝ መከላከያ ሚኒስቴር በቅርብ ቀናት በሲቪሮዶኔትስክ እየተደረገ ያለው ውጊያ የሚያስቆጣ መሆኑን በመግለፅ ሩሲያ ወንዝ አቋራጭ ውጊያዎችን የማካሄድ አቅሟ በቀጣይ ጦርነቱ ላይ ትልቅ ሚና የሚጫወት ይሆናል ብለዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የዩናይትድ ስቴትስ የመከላከያ ሚኒስቴር ሎይድ ኦስቲን በኔቶ ዋና መቀመጫ ስብሰባ እያካሄዱ ሲሆን ባለፈው ግንቦት ወር በድህረገፅ አማካኝነት የተካሄደውን የኔቶ ስብሰባ ተከትሎ ዩክሬን በጦር ሜዳ የሚያካሂደውን እንቅስቃሴ አጠናክራ እንድትቀጥል ከዩክሬን ጋር ያለንን ጥምረት የበለጠ ለማስፋት እየጣርን ነው ብለዋል። ሩሲያ በአሁኑ ወቅት 97 ከመቶ የሚሆነውን የሉሃንስክ ግዛት መቆጣጠሯን ብታስታውቅም አብዛኛውን የዶምባስ ምስራቃዊ ክፍል ለመቆጣጠር በምታደርገው ጥረት የኢንዱስትሪ ማዕከል የሆነችው ሲቮሮዶኔትስክ ትልቅ ሚና ይኖራታል።
[ክፍል አራት] – የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ለማ መገርሳ ባለፈው ሳምንት ነሐሴ 10/2009 በአዳማ ከተማ በተካሄደው የክልሉ የካቢኔ የዞንና የወረዳ አመራሮች የ2009 ዓመት አፈፃፀም እና የ2010 ዓመት እቅድ የግምገማና የውይይት መድረክ ላይ ያደረጉት ንግግር፡፡ (ከአፋን ኦሮሞ ወደ አማርኛ በHornAffairs የተተረጎመ) ድርጅታችንን ጠንካራ፣ የህዝቡን ጥያቄ መመለስ የሚችል፣ ብቁ እና በህዝቡ ዘንድ legitimacy ያለው ማድረግ አለብን፡፡ ስለዚህ ጠንክረን፤ ደከመን ሰለቸን ሳንል መስራት አለብን፡፡ ሞራሉ ተነሳስቶ፣ ተስፋን ሰንቆ፣ እውቅና የሰጠን፣ recognize ያደረገንን ህዝብ ልብ መስበር የለብንም፡፡ ትናንት እንደተናቅነው፣ ትናንት ህዝቡ አቆሽሾን እንደጠላን፣ ወደዚያ መመለስ የለብንም፡፡ እውነቴን የምላችሁ፤ ይሀ ህዝብ ብዙ ቀልቦናል፡፡ ብዙ ተሸክሞናል፡፡ ይሀ ህዝብ ባለፉት 25 ዓመታት ቀለበን፣ ቀለበን፣ ግን OPDO ማለት “ቢቀለብ ቢቀለብ የማያድግ ልጅ” ሆኖ ነው የቆየው፡፡ ይሀ ህዝብ ቢቀልበን ቢቀልበን ማደግ ያልቻልነው እኛ ነን፡፡ ከአሁን በኋላ ከዓመት እስከ ዓመት እየተቀለበ የማያድግ ልጅ መሆን የለብንም፡፡ ድርጅታችን ህዝቡ በሚፈልገው ደረጃ ማደግ መቻል አለበት፡፡ ህዝቡ በሚፈልገው ደረጃ vigilant ሆኖ፡ bold ሆኖ ወጥቶ፣ ለዚህ ህዝብ መብት ታግሎ የህዝቡን ጥቅም ማረጋገጥ መቻል አለበት፡፡ ድርጅታችን የዚህ ህዝብ ፍላጎት እና ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ መቻል አለበት፡፡ መንግስታችንን ጠንካራ ማድረግ አለብን፡፡ ድርጅታችንንም ጠንካራ ማድረግ አለብን፡፡ ሊጠነክር የሚችለው ደግሞ በሁላችን ትግል ነው፡፡ ዛሬ ህዝቡ ጥሩ certificate ሰጥቶናል፡፡ ይሀን እውቅና የሰጠንን ህዝብ መዋረድ የለብንም፡፡ ዛሬ ህዝቡ የመጨረሻ እድል ሰጥቶናል፡፡ በታሪካችን ሰጥቶን የማያውቀውን እውቅና ሰጥቶናል፡፡ እኔ’ምላችሁ ነገር ቢኖር፤ በዚህ ትግል ውስጥ የምንቸገር ሰዎች ካለን፤ ገንዘብ የምንፈልግ ሰዎች ያለን እንደሆነ አስራሩ አለ፡፡ እናግዛችኋለን፣ ውጡና በጥቃቅን እና አነስተኛ ተደራጁ፡፡ እናግዛቿለን፣ ቃል እገባላቿለሁ፡፡ ማገዝ እንችላለን፡፡ ግን እሱ ራሱ መታገዝ የሚችለው ይህ ስርዓት ሲኖር ነው፡፡ ስለዚህ ማንም ወሬ በኩንታል እያመረተ ሊረብሸን አይገባም፡፡ አላማችን አንድ እና አንድ ነው፡፡ ለዚህ ህዝብ መታገል፡፡ እያንዳንዳቹ ወደዚህ ትግል ስትገቡ ለምን ዓላማ እንደሆነ ተመልሳችሁ እራሳችሁን ጠይቁ፡፡ እኔ ወደዚህ ትግል የገባሁት ለኦሮሞ ህዝብ ለመታገል ነው፡፡ የኦሮሞን ህዝብ ፍላጎትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ነው ወደ ትግሉ የገባሁት፡፡ ለምን? ፍላጎቴ እና ጥቅሜ የሚረጋገጠው፡ የኦሮሞ ህዝብ ፍላጎትና ተጠቃሚነት ሲረጋገጥ ስለሆነ፡፡ ይሀ ማለት ሌላውን መጥላት ማለት አይደለም፡፡ ይሀ ማለት ሌላው ላይ መዛት ማለት አይደለም፡፡ This is a logic. ይሀን መቀበል አቅቶት deny ማድረግ የሚፈልግ አለ፡፡ ከዚህ ህዝብ interest የሚበልጥብን ሌላ ግብ ሊኖረን አይችልም፡፡ ይሀን ማድረግ ካቃተን ትግሉን መልቀቅ ነው ያለብን፤ ህዝቡ ለራሱ ይታገል፡፡ አለበለዚያ bold ሆነን ህዝቡ በሚፈልገው ደረጃ በመገኘት በሀቀኝነት፣ በቅንነት፣ ቆራጥ ሆነን፣ ለቆምንለት ዓላማ ከልብ መታገል ነው ያለብን፡፡ አሁን አምኖን ከጎናችን የቆመውን ህዝብ ይዘን ጠንክረን መለወጥ መቻል አለብን፡፡ ከዚህ በፊት በህዝባችን ዘንድ እንደተናቅነው፡ ታሪካችንን ማበላሸት የለብንም፡፡ ለዚህ ትግል ዋጋ አስከከፈልን ድረስ ታሪካችንን ማበላሸት የለብንም፡፡ ጠንካራ ድርጅት መሆን ጀምረናል፡፡ ጠንካራ መንግስት መሆን ጀምረናል፡፡ ግን ፈፅሞ በቂ አይደለም፡፡ ገና ጅምር ላይ ነን፡፡ ድል ተቀዳጅተናል? አዎ! የነበረው አስከፊ ሁኔታን በመቀልበስ ድል ተቀዳጅተናል፡፡ መስራት ጀምረናል፡፡ ህዝቡ ከሚጠብቀው አንፃር ግን ገና ስራ አልጀመርንም፡፡ ስለዚህ ሁሉም ከክልል እስከ ቀበሌ ድረስ ሁሉም አመራር ስኬት ላይ ለመድረስ ከልብ በመናበብ፣ ከላይ እስከ ታች አንድ ቋንቋ በመናገር፣ ለጋራ ዓላማ ተሰልፎ በጋራ መታገል አለበት፡፡ ምን ይመጣል እያላችሁ ከሹመት ቦታ በመነሳት ስጋት የተለያየ illusion ውስጥ የገባችሁ አካላት፤ ሹመት ከሆነ የምትፈልጉት የሹመት ቦታ በቂ አለ፡፡ አያልቅም፡፡ እየሰራን ካለነው አኳያ ስራው ከዚህ በላይ ሃይል እየጠየቀ ነው ያለው፡፡ ግን useless የሆነ ሰው፣ ችግር መፍታት የማይችል ሰው፣ ውስጣችን ሆኖ ሊበጠብጠን አይችልም፡፡ ከስራው ይልቅ እሱ ራሱ የቤት ስራ ሆኖብን ጊዜ ልናቃጥልበት አይገባም፡፡ እንዴት ሞራላችን እንደተነካ፣ እንዴት ድርጅታችን በህዝቡ ዘንድ እንደቆሸሸ፣ እንዴት እንደተናቀ ሁላችሁም ታውቁታላችሁ፡፡ We have to change. ይሀን ታሪክ መቀየር አለብን፡፡ ይህን ታሪክ የምንቀይረው ደግሞ ወሬኛ እና ሌባን አቅፈን አይደለም፡፡ ሌብነት ነው በህዝቡ እንድንጠላ እያደረገን ያለው፡፡ ይሀን ከውስጣችን መጥረግ አለብን፡፡ ለቅመን ማስወገድ አለብን፡፡ ወዲህ ወዲያ ማየት የለብንም፡፡ ጠንከረን መስራት አለብን፡፡ እኔ ስለኦሮሞ ህዝብ ጥቅም ስለተናገርኩ የሚከፋው ሰው ካለ፤ መክፋት አይደለም ወደ ፈለገ ይገለባበጥ፡፡ ማህበር ለመጠጣት ወይም ፀበል ለመጠጣት አይደለም እኔ ወደዚህ ትግል የተቀላቀልኩት፡፡ ለዚህ ህዝብ ታግለናል እስካልን ድረስ፤ We have to protect the interest of this people. ለዚህ መስራት ነው፡፡ እኛ ይሀን ስንሰራ ስንቱ ነው ይሀ አይሆንም ያለን! ከውጭ ብቻ አይደለም እኮ! እዚህ እኛው ውስጥ ሆኖ ስንት ሴራና ደባ እኛ ላይ ለመስራት ሌተ’ቀን የሚተጋ ስንቱ አለ? ይሀን በትግላችን clear ማድረግ አለብን፡፡ ይሀ ድርጅትና መንግስት ህዝቡ አለኝታዬ ነው የሚለው መሆን አለበት፡፡ ደግመን ደጋግመን እየተናገርን ነው፡፡ ህዝቡን እንስማ፡፡ ከህዝቡ ጋራ ሆነን ህዝቡ የሚፈልገውን እንስራ፡፡ ሌላ ነገር አይደለም እንስራ እያልን ያለነው፡፡ Rocket science እንፍጠር እየተፈላሰፍን ከአቅማችን በላይ እንንጠራራ አይደለም እያለን አይደለም፡፡ ይሀ አይነት ፍላጎት የለንም፡፡ ለዚህ ህዝብ እንስራ ነው እያልን ያለነው፡፡ በየትኛውም ደረጃና በየትኛውም ቦታ ለዚህ ህዝብ ፍላጎትና ተጠቃሚነት እንቁም ነው እያልን ያለነው፡፡ ጠንክረን እንስራ ነው እያልን ያለነው፡፡ 25 ሙሉ ያልተሰራበትን የፊንፊኔ ልዩ ጥቅም ለማረጋገጥ ስንሰራ ማነው አይሆንም ያለን? የኦሮሞ ህዝብ ተጠቃሚነት ”አይ አይሆንም” ያለን ማነው? የተፋለመን ማነው? ይሀን ነው እያልን ያለነው፡፡ ጠንክረን መስራት አለብን፡፡ ሌላ አማራጭ የለንም፡፡ የሞተ ኦህዴድ ለኢህአዴግም አይጠቅምም፡፡ የተኮላሸ ኦህዴድ ለሀገሪቷም አይጠቅምም፡፡ ለሀገሪቷም ቢሆን ጠንካራ ኦህዴድ ነው የሚጠቅመው፡፡ ይህ ድርጅት ጠንክሯል እያለ ስጋት የሚሰማው ሰው ካለ ተሳስቷል፡፡ ይሀ ድርጅት ከጠነከረ ነው፣ የኦሮሚያ ክልል መንግስት ከጠነከረ ነው፣ ሀገሪቷም ሀገር የምትሆነውና የምትጠቀመውም፡፡ ሀገሪቷም የምትጠነክረው ያኔ ነው፡፡ ሌላውም ይሀን ማወቅ አለበት፡፡ ለዚህ ህዝብ ተጠቃሚነት ስለሰራን ብቻ በመጥፎ አይን መታየት የለብንም፡፡ ግን ደግሞ የፈለገ ሰው አይኑ መቅላት አይደለም ደሙ ይደፍርስ እንጂ፤ እኛ ነን በቀዳሚነት ለዚህ ህዝብ ጥቅም መታገል ያለብን፤ የዚህን ህዝብ ጥቅም ማሰጠበቅ ያለብን፡፡ ስለዚህ እንደ አመራር በአንድነት ጠንክረን በመስራት፣ ዳግም እድል ለሰጠን ህዝብ ውጤት ማሳየት አለብን፡፡ ከሰራን ደግሞ እንችላለን፡፡ ህዝቡ ይሰማናል፡፡ ትንሽዬ ሰርተን ላሳየነውም ይመሰክራል፡፡ ሌላው መታወቅ ያለበት ደግሞ፤ ይሀ ድርጅት ወድቆ አይወድቅም፡፡ የፈለገ እየዞረ ወሬ ይሸጣታል እንጂ፤ የፈለገ የሚያኖረው መስሎት በህዝብ እየነገደ ይኖራታል እንጂ፤ ይሀ ድርጅት ጠንካራ ህዝባዊ መሰረት አለው፡፡ ለመታገል 4 ሚሊዬን አይደለም 400 ሰው ይበቃል፡፡ የፈለገ ወደፈለገበት ቦታ መሄድ ይችላል፡፡ በትግል ሂደቱ ዋጋ ከፍለንበታል፡፡ ለዚህ ህዝብ ጥቅም ብለን ታመንበት፣ ተሰቃይተንበት፣ ህይወት አጥተንበታል፡፡ ስለፈለገ ማንም ሊያደናቅፈን አይችልም፡፡ ወዲያ ወዲህ ማለት ትተን ይህን ህዝብ፣ ይሀን ድርጅት፣ ይሀን መንግስት፣ በአግባቡ መምራት አለብን፡፡ በአግባቡ ለመምራት ደግሞ ሌቦችን፣ ወረኞችን፣ ውሸታሞችን፣ የሌብነት ሱስ ያለባቸው ሌቦችን፣ ፍርፋሪ ለቃቃሚዎችን፣ ከውስጣችን መጥረግ አለብን፡፡ አለበለዚያ የቆሸሸውን አቅፈን ህዝቡ እኛን ሊሆን አይችልም፡፡ ይህን ለማድረግ ደግሞ በምሬት እንታገላለን፡፡ እኛ የምንፈልገው የህዝባችን ከኛ ጎን መሰለፍ ነው፡፡ የፈለገ ወደ ፈለገው ይሂድ፡፡ ህዝባችን ከኛ ጋራ ከሆነ መስራት እንችላለን፡፡
ጉዳያችን - GUDAYACHN: ሰበር ዜና - ግንቦት 7 ንቅናቄ ''ልዩ መግለጫና ተግባሪዊ የመጀመሪያ እርከን የትግል ጥሪ'' በሚል ርዕስ ስር አዲስ የትግል ጥሪ አስተላለፈ።ጥሪው የመን፣እንግሊዝ እና ኢህአዴግ/ወያኔ ላይ ያነጣጠረ ነው ጉዳያችን - በጉዳያችን ሚድያ፣ኮምኒኬሽን እና ምክር አገልግሎት የሚዘጋጅ ሲሆን ከ2003 ዓም ጀምሮ በድረ-ገፅ ላይ የነበረ በአሁኑ ጊዜ ከአንድ ሚልዮን በላይ ጎብኚዎች ያሉት ገፅ ነው። Gudayachn is prepared by Gudayachn Multimedia, Communication and Consultant Organization. It has been online since 2011. Currently, Gudayachn is being visited by over One-million readers from all over the world. ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages Sunday, July 6, 2014 ሰበር ዜና - ግንቦት 7 ንቅናቄ ''ልዩ መግለጫና ተግባሪዊ የመጀመሪያ እርከን የትግል ጥሪ'' በሚል ርዕስ ስር አዲስ የትግል ጥሪ አስተላለፈ።ጥሪው የመን፣እንግሊዝ እና ኢህአዴግ/ወያኔ ላይ ያነጣጠረ ነው የመንን በተመለከተ የየመን መንግሥት የዓለም ዓቀፍ ህግም ሆነ የየመን የራሷን ህግ በመተላለፍ መሪያችንን ለእርድ አሳልፎ ሰጥቶብናል። ከመጀመሪያው ጀምሮ ለየመን መንግሥት የተደረገው ተማጽኖ ሰሚ ጆሮ አላገኘም። እስካሁንም ድረስ የየመን መንግሥት አቶ አንዳርጋቸውን ማሠሩና ለወያኔ አሳልፎ መስጠቱ በይፋ አላመነም። እኛ ባለን መረጃ መሠረት በአይሮፕላን ማረፊያው ከማገት ጀምሮ በልዩ በረራ ወደ ኢትዮጵያ እስከ መላክ ድረስ ያለውን የውንብድና ሥራ በየመን በኩል ሆኖ የሠራው ቀጥታ ተጠሪነቱ ለየመን ፕሬዚዳንት የሆነው የስለላ ድርጅት ነው። በዚህም ሳቢያ የየመን መንግሥት ሊቀለበስ የማይችል እና በቀላሉ የማይፋቅ ታሪካዊ ስህተት ፈጽሟል። የየመን መንግሥትና ሕዝብ ይህን እንዲያውቁት ማድረግ ወቅቱ የሚጠይቀው የተግባር እንቅስቃሴ አካል ነው። የመንን በተመለከተ የሚቀጥለው ሳምንት ዘመቻችን ግብ ቁጣችንን የየመን ፕሬዚዳንት እና የየመን መንግሥት ብቻ ሳይሆን የየመን ሕዝብም እንዲያውቅ ማድረግ ነው። የሚከተሉት ተግባራት ለአብነት ያህል ተጠቅሰዋል። ለየመን ፕሬዚዳንት አዲስ መረር ያለ ደብዳቤ ተጽፎ በፋክስና በኢሜል በየመን መንግሥታዊ መሥሪያ ቤቶችና ኤምባሲዎች አድራሻዎች መላክ። በመልዕክት መጨናነቅ ከሚገባቸው የየመን ተቋማት አንዱ አዲስ አበባ የሚገኘው የየመን ኤምባሲ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ ሆናችሁ በዘመቻው የምትሳተፉ ጥንቃቄ እንዳይለያችሁ እናሳስባለን፤ የኢንተርኔትና የፋክስ መልክቶችን ስትልኩ ራስን ለጉዳት በማያጋልጥ መንገድ መደረግ ይኖርበታል። የየመን ኤምባሲዎችን ሥራ ማወክ በሚችሉ ሰልፎችና ተቃውሞዎች ማጨናነቅ። የፕሬዚዳንቱን ፎቶና የአገሪቱን ባንዲራ ማቃጠል። ይህ በውጭ አገራት ብቻ መደረግ ያለበት ነው። በውጭ አገራት በየከተሞች ለሚገኙ የየመን ኮሚኒቲዎች ደብዳቤ መፃፍና መንግሥታቸውን እንዲቃወሙ መገፋፋት፤ ይህንን ካላደረጉ ግን ከመንግሥታቸው ጎን ተሰልፈው በኢትዮጵያ ላይ ጦርነት እንዳወጁ የምንቆጥረው መሆኑን በማያሻማ መንገድ መንገር፤ በየመን አየር መንገድና በማናቸው የየመን የንግድ ድርጅቶችና ቢዝነሶች ላይ እቀባ ማድረግ፤ በቢዝነሶቻቸው ላይ አሉታዊ ቅስቀሳ ማድረግ። ይህ ተግባር በኢትዮጵያም ከኢትዮጵያ ውጭም በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን መተግበር የሚኖርበት አቢይ ተግባር ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የየመን ቢዝነሶችን መርጦ ምርቶቻቸው እና አገልግሎቶቻቸው እንዲጠሉ ማድረግ። ከእንግዲህ በየመን ገንዘብ የተሠራ ወይም ከየመን የመጣ ብስኩትም ይሁን ሲጃራ የወገናች ደም የነካው እቃ ነው። ብርታኒያን በተመለከተ የእንግሊዝ መንግሥት ማድረግ የነበረበትን እና ማድረግ ይችል የነበረውን ሁሉ አድርጓል ብለን አናምንም። እርምጃው ፈጣን አልነበረም፤ አሁንም አይደለም። ስለሆነም እንግሊዝን በተመለከተ የዘመቻችን ግብ የእንግሊዝ መንግሥት ለጉዳዩ ትኩረት በመንፈጉ መክሰስ እና ከአሁን በኋላም ተገቢውን ትኩረት ሰጥቶ እንዲከታተለውና መሪያችን እንዲያስፈታ መወትወት ነው። የሚከተሉት ተግባራት ለአብነት ተዘርዝረዋል። የእንግሊዝ መንግሥትን በህግ መክሰስ (ይህ በንቅናቄው ጽ/ቤት የሚሠራ ሲሆን ዝርዝሩ ወደፊት ይገለፃል)፤ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አዲስ ደብዳቤ ጽፎ በፋክስና በኢሜል ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና ለኤምባሲዎች በብዛት መላክ። አንዱ ትኩረት የሚደረግበት ኤምባሲ አዲስ አበባ የሚገኘው የእንግሊዝ ኤምባሲ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ በዘመቻው የሚሳተፉ ወገኖች አስፈላጊው ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል። በለንደን በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደጃፍ፤ በሌሎች አገሮች ደግሞ በእንግሊዝ ኤምባሲዎች ቁጣ የተቀላቀለበት የተቃውሞ ሰልፎችን ማካሄድ። ወያኔን በተመለከተ ወያኔን በተመለከተ የሚደረጉ ትግሎች በሙሉ ወያኔን ከስልጣን ማስወገድን ያነጣጠሩ መሆን ይኖርባቸዋል። ወያኔም ለመጣል ትልቁን ድርሻ የሚያበረክተው ሕይወታቸውን ለመስጠት የቆረጡ፡ ከቁም ውርደትና ባርነት ለነጻነትና ለፍትህ ከወያኔ ጋር ጉረሮ ለጉረሮ እየተናነቁ እየጣሉ ለመውደቅ ፤ መስዋእት ለመሆን በወሰኑ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችንና የህዝብ ሃይሎች የሚያደርጉት ተግባራዊ እንቅስቅሴ ነው ፤ እንቀላቀላቸው። በተለያዩ ምክንያቶች ወሳኙን ትግል መቀላቀል የማይችሉ ወገኖቻችን በያሉበት ሆነው ከወያኔ የስለላ መረብ ተጠነቅቀው ራሳቸውን በቡድን ያደራጁ፤ ይህንኑ የሚያግዙ ተግባራት ለመፈጸም ራሳቸውን ያዘጋጁ። እነዚህ ተግባራት ወያኔን በገቡበት እየገቡ በማሳፈር ፤እረፍት በመንሳት፤ የፈፀሟቸውን ወንጀሎች በአደባባይ በመናገር እንዲሸማቀቁ በማድረግ፤ ማንነታቸው ለሸሪኮቻቸው ወይም ለሥራ ባልደረቦቻቸው በመንገር ወዳጅ በማሳጣት፣ ንግዶቻቸውን ኩባንያዎቻቸው እንዲከስሩ በማድረግ የፋናንስ አቅማቸው በማዳከም ረገድ የሚኖራቸው አስተዋጽኦ ቀላል እንዳልሆነ ሊታወቅ ይገባል። ከዚህ አኳያ ሊደረጉ ከሚገቡ ተግባራት የሚከተሉት በምሳሌነት ተዘርዝረዋል። በምዕራቡ ዓለም በተለያዩ ሽፋኖች ተሰግስገው ያሉት እና የሚመላለሱ ወንጀለኞች የወያኔ ሹማምንትና ደጋፊዎችን ለፍርድ ለማቅረብ መደራጀትና እንደየሀገሩ ሁኔታ አግባብ ያላቸውን የህግ መሳሪያዎች መጠቀም፤ በመላው ዓለም የወያኔ ኤምባሲዎችና የኮንሱላር ጽ/ቤቶች ሥራ መሥራት የማይችሉበት ሁኔታ መፍጠር፤ በመላው ዓለም የወያኔ አባላትና ደጋፊዎችን ከያሉበት (ከሰፈር፣ በዩኒቨርስቲዎች፣ በንግድ የተሰማሩ ..) በማደን ማስነወር፣ ማግለል፣ ማዋረድ፤ ከእነሱ ጋር አንዳችም የንግድም ፡ የሥራ ፤ የማኅበራዊ ትብብርና ግንኙነት አለማድረግ፤ ፊት መንሳት ፤ በሥራዎቻቸው ላይ አሉታዊ ቅስቀሳዎችን ማካሄድ። የወያኔ አባላትንና ደጋፊዎችን በሁሉም ዓይነት ግንኙት ማግለል፡ አለመተባበር በኢትዮጵያም ውስጥ በስፋት በሥራ ላይ መዋል ይኖርበታል። በማናቸውም የዓለም ክፍል ለሥራ ወይም ለሽርሽር የሚዘዋወሩ ከፍተኛ የወያኔ ሲቪል፣ የወታደራዊና የደህነት ባለሥልጣኖችና የጦር መኮንኖችን እየተከታተሉ ማሸማቀቅ፣ ማስነወር፣ መውጫ መግቢያ ማሳጣት፤ በየትኛውም የዓለም ክፍል ተቀባይነት እንደሌላቸው በሕዝብ ላይ ለፈጸሙት ወንጀሎች ሁሉ የሕዝብ ቁጣ ዒላማ እንዲሆኑ እንደልባቸው መፏላል እንዳይችሉ ማድረግ። በኢትዮጵያ ውስጥ ሕዝብ ራሱ በቡድን አደራጅቶ ለወያኔ ታጣቂዎች ጥቃት ሳያጋልጡ አድብቶና አስልቶ ተመሳሳይ ድርጊቶች መፈፀም የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ በወያኔ አገዛዝ የሚመሩ እንዲሁም በወያኔ ኤፈርት ስር ያሉ ኩባንያዎች፤ቢዝነሶች ላይ እቅባ ማድረግ፤ የሸቀጥና የአገልግሎታቸው ተጠቃሚ አለመሆን፤ በእነሱ ላይ አሉታዊ ቅስቀሳ ማድረግ፤ በልዩ ልዩ መንገዶች ሥራቸውን ማጨናገፍ ማደናቀፍ፤ አሻጥሮችን በተደራጀ መልክ፣ በጥናትና በብልሃት ተግባራዊ ማድረግ። ይህ በኢትዮጵያም በመላው ዓለም በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ተግባሪዊ መደረግ ይኖርበታል። በዌስተር ዩኒየን፣ በመኒ ግራም እንዲሁም በአሜሪካ፣ በአውሮፓ፤ በመካከለኛው ምሥራቅ በወያኔ ደጋፊዎች በመሠርቱዋቸው ልዩ ልዩ የገንዘብ ላኪ ድርጅቶች በኩል ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ አለመላክ፤ በየአካባቢው አማራጭ የገንዘብ መላኪያ መንገዶችን መፈለግ፤ እነዚህ በሌሉባቸው አካባቢዎች የፈጠራ ችሎታን በመጠቀም ገንዘብ ለዘመድ አዝማድ በወያኔ በኩል ሳይላክ የሚደርስበትን ሁኔታ መፍጠር፤ የወያኔን የፋሽታዊ አገዛዝ አንዱና ዋነኛ ምሰሶ የሆነውን የውጭ ምንዛሪ የማድረቂያ ዘዴዎችን ሁሉ በመፈለግ ተግባሪዊ በማድርግ የወያኔን በዘረኝነትና በዘረፋ የተገነባ የገንዘብና የኢኮኖሚ አቅም ማዳከም፤ መቦርቦር፤ መናድ። ከወያኔ ጋር የሚሠሩ የውጭ አገር ድርጅቶች ከወያኔ ጋር ያ ያላቸውን ሽርክና እንዲያቋርጡ መወትወት፤ አልሰማ ካሉ በቢዝነሳቸው ላይ አሉታዊ ቅስቀሳ ማካሄድ። (የእነዚህን ዝርዝሮች በተከታታይ ይገልጻሉ) የምዕራብ አገራት ዩኒቨርስቲዎች ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን ግኑኝነት እንዲመረምሩ ማሳሰብ። በተለይ ደግሞ ሳያስተምሩ ለወያኔ ሹማምንቶች ዲግሪ የሚያድሉ ዩኒቨርስቲዎችና ኮሌጆችን ማስጠንቀቅ፤ ተግባሮቻቸውን ለተማሪዎቻቸው ጭምር መንገር (ለምሳሌ University of Greenwich ከ International Leadership Institute ጋር ያለውን ግኑኝነት እንዲሰርዝ፣ እስከዛሬ የሰጣቸውንም የማስትሬት ዲግሪዎች እንዲመረመር የሚጠይቅ ደብዳቤ ጽፎ በብዛት በፋክስ መላክ፤ ተመሳሳይ ደብዳቤ Open University እና ከወያኔ ጋር ተሻርከው ለሚሠሩ ዩኒቨርስቲና ኮሌጆች መላክ) ይህ ዘመቻ ለጊዜው በወያኔ ላይ ያነጣጠረ ቢሆንም፣ የሕዝቡን የነፃነትና የፍትህ ጥረት የሚያደናቅፉ የሀገር ውስጥም ሆነ የውጭ አገር ዜጎች በሆኑ ቱጆሮችና ከወያኔ ጋር የተያያዙ የንግድ ቤቶችና ኩባንያዎች የዘመቻው ዒላማ ሊሆኑ ይችላሉ። (ዝርዝራቸውን በተከታታይ እናወጣለን) በመጨረሻም የወጣቱ የማያልቅ የፈጠራ ችሎታ ከላይ በዝርዝሩ ውስጥ ያልተካተቱ ሆኖም ግን ውጤታማ የሆኑ የተቃውሞ መግለጫ ዘዴዎች ያፈልቃል ብለን እናምናለን። ስለሆነም ዘመቻውን በየአካባቢው በሚገኝ ሀሳብና ፈጠራ ማዳበር ይቻላል። ይህ ዘመቻ ወያኔ ከስልጣን እስኪባረር ድረስ በየጊዜ እየከረረ መሄድ እንዳለበት ታሳቢ አድርጎ መነሳት ይኖርበታል። ስለሆነም በየጊዜው አዳዲስ ነጥቦችን ተግባሪዊ የትግል ስልቶችን እንጨምራለን። ለመላው የአትዮጵያ ሕዝብ፣ በመላው ዓለም የምትገኙ ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ሁሉ፣ ለሁሉም የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ሁሉ በኅብረት በጋራ ሆነን፤ ትከሻ ገጥመን ለተግባሪዊ ትግል በቁርጠኝነት እንድንነሳ ጥሪያችንን እናቀርባለን ። ይህ ዘመቻ ወያኔን ከስልጣን ለማባረር ምድር ላይ ከምናደርገው የመረረ ትግል ጋር ሲቀናጅ የሚፈለገውን ውጤት ስለሚያስገኝ ለነፃነቱ ግድ ያለው ዜጋ ሁሉ በሙሉ ኃይሉና አቅሙ ተሳትፎ እንዲያደርግ ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አገራዊ ጥሪ ያቀርባል። በመስዋዕትነት ድልን እንቀዳጃለን !!! ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!! ምንጭ -http://www.ginbot7.org/2014/07/06/ከግንቦት-7:-የፍትህ፣-የነፃነትና-የዲሞክ/ By ጌታቸው በቀለ ዳምጠው / Getachew Bekele Damtew Getachew Bekele Damtew at July 06, 2014 Email ThisBlogThis!Share to TwitterShare to FacebookShare to Pinterest No comments: Post a Comment Newer Post Older Post Home Subscribe to: Post Comments (Atom) የዋጋ ንረት ጉዳይ የፀጥታ አና የሀገር ደህንነት ጉዳይ ነው። የኢትዮጵያ የዋጋ ንረትን ለማቃለል መንግስት መከለስ ያለበት ቁልፍ የፖሊሲ ጉዳይ። ========= ጉዳያችን ልዩ ========= አይኢም ኤፍ የዋጋ ግሽበትን (ንረትን) ሲተረጉም ''በተወሰነ ጊዜ ውስጥ የሚለካ አጠቃላይ የዋጋ ንረት ሲሆን ይህ የዋጋ ንረት አጠቃላይ ሀገራዊ የኑሮ ውድነትን ... የ ኤርትራ ጉዳይ ና የ ሃያ አንደኛው ክ/ዘመን ልጆች አስተሳሰብ በ ካርታ ጫወጣ ጎበዝ አደለሁም። ግን ጆከር የተባለች ካርታ መኖሯን አውቃለሁ።ጆከር ካርታ በ ሁሉም ቦታ ስለምትገባ በ ካርታ ጫወታ ጆከር የደረሰው ሰው የማሸነፍ እድል ስላለው ፊቱ በ ፈገግታ ይሞላል። የ አትዮጵ... A Loud and Clear Lesson – For Ethiopia and the World ዓለም እና ኢትዮጵያ (ከምዕራቡ ዓለም የሰሞኑ የሽብርተኛው ህወሃትን መደገፍ) ትልቅ ትምሕርት ይውሰዱ! በሚል የእንግሊዙ ጸሓፊ ዛሬ ያወጣው ሙሉ ጽሑፍ በርካታ ጉዳዮችን ይዳስሳል። Without US support — milita... ጌታቸው ረዳ ''ክው'' ብሏል።በትግሪኛ የሰጠው መግለጫ።ምን ይዟል? ጌታቸው ረዳ በከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ ========= ጉዳያችን ምጥን ========= ጌታቸው ረዳ በትግርኛ ማምሻውን መግለጫ ሰጥቷል። ጋዜጠኞቹ ይችን ምሽት ጌታቸው አጠገብ መቀመጥ እንዳስጨነቃቸው ከጠያቂዎቹ መርበትበት ለ...
“ከሰማይ በታች እኛን የሚያሸንፍ ምድራዊ ሃይል የለም” በሚል እብሪት ልባቸው ያበጠው ህወሃታዊያን የራሳቸው ና የህዝቡ የዘመናት አጋራቸውን የሰሜን ዕዝ የሰራዊት አባላትን የወለደችውን እንደምትበላ ድመት በተኛበት በአሰቃቂ ሁኔታ ረሸኑ ፡፡ የሀገርን ክብር በሚያዋርድ መልኩ የክብር ልብሱን አስወልቀው ከክልላችን ውጡ ብለው ወደ ባዕድ ሃገር አሰደዱት ፣ ሴት ወታደሮችን ጡት እንዳልቆረጡና ከሰብዓዊ ፍጡር የማይጠበቅ የማይጠበቅ እየፈጸሙባቸውና እያሰቃዩ እንዳልገደሉ ፣ ሬሳቸው ላይ እምበር ተጋዳላይ እንዳልጨፋሩ ፣ በተኙበት አፍነው ይዘው አሰልፈው በሲኖትራክ እንዳልጨፈለቁ ፣ ከፍተኛ ጀነራል መኮንኖችን ጨምሮ በርካታ አባላትን አግተው ያለ ምግብ ውሃ በእግር እያሰጓዙ እንዳላሰቃዩ በዚህም በርሃብና በጥም በርካቶች እንዲሞቱ እንዳላደረጉ ፣ ማይካድራ ላይ ታሪክ ይቅር የማይለው የዘር ማጥፋት እንዳልፋፀሙ ሁሉ ፣ በንቀትና በትዕቢት ተነፋፍተው በደንጎላ ኮሎኔል ማራኪ የውሸትና ባረጀ ባፋጀ ስልት የጀመሩት ጦርነት ፣ በቆራጥ ኢትዮጵያዊያን መስዋዕትነት ድባቅ ሲመቱ ፣ የጦርነት ሊቆች ነን ባዮች ግብዞቹም በለኮሱት እሳት ሲፈጁ ዲጅታል ወያኔዎች ሌላ ዘፋን ይዘው ብቅ አሉና አለምን ማደናገር ጀመሩ። ትግራይ ውስጥ ሰብአዊ መብት እየተጣሰ ነው ፣ ሴቶች እየተደፈሩ ነው ፣ ንብረት በኤርትራ ወታደሮች እየተዘረፈ ነው ፣ የኢትዮጵያ መንግስት የትግራይ ህዝብን በርሃብ እየቀጣ ነው ፣ የሃገር ሉአላዊነት ተደፍሯል… የሚሉና ፣ ምድር ላይ ካለው እውነት የሚጣረሱ ክሶችን በሶሻል ሚዲያና በውጭ ሃገር የመገናኛ አውታሮች የሃሰት ፕሮፖጋንዳቸውን ማናፋሱን ተያይዘውታል። ምክኒያቱም ዛሬ ትግራይ ውስጥ ስለተፈፀመውና መቸም ከልባችን ከማይጠፋው ግፍና መከራ ከጨፈጨፋቸው ወታደሮች ህይወት ይልቅ ጦርነቱ ያስከተለው ማህበራዊ ቀውስ እንጅ ፣ የቀውሱ ጠንሳሽና ፈፃሚ የሆነውን ህወሃት የፈፀመው አሰቃቂ ግፍ በህወሃት ጀሌዎች ዘንድ ይሁን በአለም አቀፍ ሚዲያዎችም ሲወገዝም ሲወቀስም አንሰማም። ትግራይ ውስጥ በግፍ የተጨፈጨፉትን የሰሜን ዕዝ አባላትን ክብር የጠበቁት ልብስና የእግዜር ውሃ ያቀመሱት ኤርትራዊያን ወታደሮችና እናቶች ናቸው ወይስ… ? የህወሃታዊያን ሌላው ድንቁርና የባዕድ ሃገር ኤርትራ የኢትዮጵያን ሉአላዊነት ተዳፍራ ወታደሮቿን ትግራይ ውስጥ አስገብታለች የሚል ክስ ነው አስገብታለች አላስገባችም የሚለውን እውነት ለመንግስት እንተወውና ፣ አስገብታ ቢሆንስ እንደ ህወሃትና ባንዳዎች ክህደትና ሴራ ቢሆን ኖሮ ዛሬ ኢትዮጵያ ከሶሪያም የባሰች የፈረሰ ሃገር ትሆን እንደነበር ግልፅ ነው ፡፡ ከራሱ ሃገር እንደባዕድ ተቆጥሮ የሗሊት ታስሮ ከተገደለው ፣ ጡታቸው ተቆርጦ ተሰቃይተው ከሞቱት ፣ በድንጋይ እየተወገረ ልብሱ ሳይቀር እየተዘረፈ ከገዛ ሀገሩ ለተባረረው ሰራዊታችን ከለላ የሆነው ፣ ዛሬ ህወሃታዊያን ባዕድ ሃገር የሚሏት ኤርትራ አልነበረችምን ? እውነት እንነጋገር ከተባለ በወቅቱ ጁንታዎቹ ሰራዊታችንን ከሃገራችን ውጡ ብለው ሲያባርሩ የተቀበለው የኤርትራ ህዝብ ነው ባዕድ ወይስ ህወሃታዊያን? ትግራይ ውስጥ በግፍ የተጨፈጨፉትን የሰሜን ዕዝ አባላትን ክብር የጠበቁት ልብስና የእግዜር ውሃ ያቀመሱት ኤርትራዊያን ወታደሮችና እናቶች ናቸው ወይስ… ? እኔም ይሄን እላለሁ ፣ ህወሃታውያን ሆይ በጦር ሜዳ ላይ ያጣችሁትን ድልና ላይመለሱ ያሸለቡትን አለቆቻችሁን በፌስቡክና በዮቲዮብ ጋጋታ ላትመልሱት ፣ በውሸት ጫጫታና አስፖልት ላይ በመንከባለል የሚፈታ የትግራይ ህዝብ ችግር የለም ፡፡ መጀመሪያ አጎቶቻቹሁ የፈፀሙትን ወራዳ ተግባር አውግዙ ፡፡ በናንተ ዘመዶችና ሃሺሻም ታጣቂዎች የተጨፈጨፉ ወታደሮችን ህይወት አስቡ ፡፡ ሃገራችን የገባችበት ቅርቃር የሽማግሌ ህወሃታዊያን ሴራ መሆኑን እመኑ ፡፡ የኤርትራ ወታደሮች ሉአላዊነትን ተዳፍረው ትግራይ ውስጥ ገብተዋል ከማለታችሁ በፊት ዳር ድንበር ጠባቂ ወታደሮችን ከጀርባቸው የወጋውን ከሃዲ በአደባባይ ባንዳ በሉት፡፡ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን የካደውን የበደለውን የህወሃት የጥፋት ሃይል እናንተን እንደማይወክል በተግባር አሳዩ ፡፡ ያኔ የናንተ ህመም የሁሉም ኢትዮጵያዊ ህመም ይሆናል። ሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሰራዊታችንን በመደገፍ የጁንታውን ግብአተ መሬት እንዳፋጠነው ሁሉ ፣ አሁን ደግሞ የዲጅታል ወያኔን የውሽት ፕሮፖጋንዳ በሃገራችንና በሰራዊታችን ላይ የተከፈተውን ዘመቻ እያጋለጥን በጁንታው የተፈፀሙ ግፎችን አጉልቶ ማውጣት ይጠበቅበናል።
ይህም አደረጃጀትና አሰራርን በማዘመን ተደራሽ፣ ቀልጣፋ፣ ግልጽና ጤናማ የውጭ ማስታወቂያ እንዲኖር እንዲሁም ኢንዱስትሪው ሰፊ የንግድ፣ የኢንቨስትመንት እና የሥራ እድል እንዲፈጥር ለማድረግ ያግዛል ነዉ የተባለዉ። ይህ ደንብ በቢል ቦርድ፣ በማስታወቂያ ሰሌዳ፣ በኤሌክትሮኒክ ስክሪን ወይም በተንቀሳቃሽ ምስል የሚሰራጭ፣ እንዲሁም በሕንጻ፣ በግድግዳ፣ በጣራ፣ በማናቸውም ስትራክቸር ወይም በትራንስፖርት ተሽከርካሪ፣ በተንሳፋፊ ፊኛ ወይም መሰል ነገር ላይ የሚሳል፣ የሚፃፍ፣ የሚለጠፍ፣ የሚተከል ማስታወቂያን ይመለከታል ነው የተባለው። በሌላ በኩል በተንጠልጣይ ነገር፣ በፖስተር፣ በስቲከር፣ በተባዛ በራሪ ወረቀት፣ በብሮሸር፣ ሊፍሌት፣ ፍላየር የሚሰራጭ፣ በድምጽ ካሴት፣ በድምፅ ማጉያ መሳሪያ የሚሰራጭንም ያጠቃልላል። ሆኖም የመንገድ አቅጣጫ ጠቋሚ፣ የትራፊክና የአውቶቡስ ፌርማታ ምልክትን፣ የመንገድ ስምን ወይም ቁጥርንና መሰል የሕዝብ አገልግሎት መረጃ ሰጪ ምልክቶችን አይጨምርም ተብሏል። ማንኛውም በምስል፣ በቅርጽና በድምፅ፣ በምስል የሚተላለፉ የውጭ ማስታወቂያዎች የፌደራል መንግስትና የከተማ አስተዳደሩን ህጎች፣ የህዝቡን ባህል፣ እምነት፣ ቋንቋና እሴቶች የማክበር ግዴታ አለባቸው መባሉን ኢትዮ ኤፍኤም ከባለስልጣኑ ሰምቷል። እንዲሁም ማንኛውም የውጭ ማስታወቂያ ከመሰራጨቱ በፊት በባለሥልጣኑ እና በሚመለከተው አካል የሚያወጣውን የብቃትና የጥራት ደረጃ መመሪያ የሚያሟላ የውጭ ማስታወቂያ መሆን አለበት ነው የተባለው። በማንኛውም ሁኔታ የውጭ ማስታወቂያ ማሰራጨት የሚቻለው በአዲስ አበባ ግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ፈቃድ ብቻ መሆኑንም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ያደረሰን መረጃ ያመላክታል፡፡
“የአምስት ዓመት ልጄን በስልክ አግኝቻት ነበር፡፡ እርሷም ‹ማሚ እባክሽ የወርቅ ሜዳሊያውያን አሸንፊ› ስትል ጠየቀችኝ፡፡ ቃል ገብቼላት ነበር፤ ቃሏን በመጠበቄ ኮርቻለሁ በቃ፣ ዛሬ እንደገና የተወለድሁ ያህል ከፍተኛ ደስታ ተሰምቶኛል፤” ይህን ቃል መሠረት ደፋር ከ2004 የአቴንስ ኦሊምፒክ በኋላ ሁለተኛውን የኦሊምፒክ ወርቅ በ5‚000 ሜትር ለንደን ላይ ካሸነፈች በኋላ ለዜና ሰዎች የተናገረችው ነው፡፡ ከፍተኛ ፉክክር የነበረበትን ውድድር ተቀናቃኟን ኬንያዊት ቪቪያን ቼሪዮትንና የቤጂንግ ኦሊምፒክ አሸናፊዋና የዘንድሮው የ10‚000 ሜትር ባለወርቅ ጥሩነሽ ዲባባን አስከትላ በ15 ደቂቃ 04.25 ሰከንድ በሆነ ጊዜ በማሸነፍ የወርቅ ሜዳሊያውን አግኝታለች፡፡ ዛሬ መጠናቀቂያው ላይ የደረሰው 30ኛው የለንደን ኦሊምፒክ የኢትዮጵያ ሴት አትሌቶችን አይበገሬነት አሳይቷል፡፡ በ56 ዓመት ታሪክ ውስጥ በአንድ ኦሊምፒክ ሦስት ሴት አትሌቶች ሦስት ወርቅ በማግኘት ታሪክ ሠርተው ድሉን አድምቀውታል፡፡ ሦስተኛውን ወርቅ ባለፈው ዓርብ ምሽት በ5‚000 ሜትር በኢትዮጵያውያትና በኬንያውያት መካከል በነበረው ከፍተኛ ፉክክር ድሉን የጨበጠችው መሠረት ደፋር ናት፡፡ መሠረት ደፋር በኦሊምፒክ 5‚000 ሜትር ሁለት የወርቅ ሜዳሊያዎችና አንድ ነሐስን ጨምሮ ሦስት ሜዳሊያዎችን በማግኘት ብቸኛዋ አትሌት ሆናለች፡፡ ደራርቱ ቱሉም በተመሳሳይ በ10‚000 ሜትር በባርሴሎናና በሲዲኒ ኦሊምፒኮች ሁለት የወርቅና በአቴንስ ኦሊምፒክ አንድ የነሐስ ሜዳሊያዎች አግኝታለች፡፡ “ሁለተኛውን ወርቅ ከስምንት ዓመት በኋላ ማግኘቴ ልዩ እመርታ ነው፤ ዛሬ ዳግም እንደተወለድኩ ነው የምቆጥረው፤” ያለችው መሠረት፣ የድሉን መስመር አልፋ እንደገባች ከጉያዋ ውስጥ ድንግል ማርያም ከልጇ ጋር ያለችበትን ምስል እያሳየች ስትስም ታይታለች፡፡ “ድሉን ዛሬ ስለሰጠኝ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፤ እጅግ በጣም ተደስቻለሁ፣ ይህ ለእኔ ታላቅ ነው፤” ማለቷን የኢንተርናሽናል አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማኅበር ድረ ገጽ አስፍሯል፡፡ ዝግ ብሎ የተጀመረውን የ5,000 ሜትር ሩጫ ብሪታንያዊቷና ጣሊያናዊቷ የመጀመርያውን ሦስት ሺሕ ሜትር እየተፈራረቁ የመሩት ቢሆንም አልዘለቁበትም፡፡ ኬንያውያቷ ቼሪዮት፣ ኪፒዮጎና ኪሲዎት ወደፊት ማምራት መጀመራቸውን ያስተዋለችው ጥሩነሽ ቀዳሚነቱን ይዛ ዙሩን ስታከረው መሠረትም ተከትላታለች፡፡ አራቱን ዙር ያፈጠነችው ጥሩነሽ ለኢትዮጵያ ስኬት በሩን ከፍታለች፡፡ 100 ሜትር ላይ ማለፍ የጀመረችው መሠረት በድንቅ አፈጻጸም አንደኛ ስትሆን ሦስተኛ ላይ የነበረችው ኬንያዊቷ ቼሩዮት ጥሩነሽን አልፋ ሁለተኛ ሆናለች፡፡ ውድድሩ የምሥራቅ አፍሪካውያት የበላይነት የታየበትና ሦስት ኢትዮጵያውያትና ሦስት ኬንያውያት ተፈራርቀው የገቡበት ነው፡፡ የመሠረት ድል የኢትዮጵያን የኦሊምፒክ 5‚000 ሜትር የበላይነት ለ12 ዓመታት እንዲዘልቅ ያደረገ ነው፡፡ በ10‚000 ሜትር ሩጫ በወርቅነሽ ኪዳኔ የታየው የቡድን ሥራ በ5‚000 ሜትር ላይ በጥሩነሽ ዲባባ መቀጠሉ ታይቷል፡፡ “400 ሜትር ከቀረ ቼሪዮት አስቸጋሪ ነች፡፡ እንዳታመልጠን አራት ዙር ሲቀረው ወጣሁ፤” በማለት ለዜና ሰዎች የተናገረችው ጥሩነሽ፣ “ወርቁን እኔም አገኘሁት መሠረት ዋናው ለአገር መሆኑ ነው፤” ብላለች፡፡ በ5‚000 ሜትር በተጠባባቂነት ተይዛ የነበረችው ጥሩነሽ በርቀቱ እንደምትወዳደር በተነገረ ጊዜ እንደ ቤጂንጉ ሁሉ ድርብ ድልን ታስመዘግባለች የሚሉ ቁጥራቸው ቀላል አልነበረም፡፡ ዓርብ ምሽት ውድድሩ ሊያበቃ 100 ሜትር አካባቢ እስከቀረውና መሠረት እስካለፈቻት ድረስ ትመራ ነበር፡፡ ኢትዮጵያ ሦስተኛውን ወርቅ በመሠረት በኩል እንድታገኝ ያከናወነችው የቡድን ሥራ በአስደሳችነቱ ሲወሳ ሌላዋ አትሌት ገለቴ ቡርቃ አምስተኛ ሆናለች፡፡ ለባህሬን የሮጡት ትውልደ ኢትዮጵያውያቱ ሽታዬ እሸቴና ጠጂቱ ዳባ 10ኛ እና 12ኛ ሆነው አጠናቀዋል፡፡ መሠረት የድሉን መስመር እንዳለፈች የተፈጠረባት ደስታ ሲቃና እንባ የተሞላ ነበር፡፡ ከቤጂንግ በኋላ የዓመታት ጥረቷ ለወርቅ በመብቃቱ እፎይታን ፈጥሮላታል፡፡ በሦስት ኦሊምፒያዶች ሦስት ሜዳሊያዎች ያገኘችውና እ.ኤ.አ በ2007 የዓለም ምርጥ አትሌት ተብላ የተመረጠችው መሠረት ወደፊት ማራቶን ለመሮጥ ሐሳቡ አላት፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት ፊላዴልቪያ ላይ ግማሽ ማራቶን ሩጣ በ67 ደቂቃ 45 ሰከንድ ማጠናቀቋ ይታወሳል፡፡ የሴቶች 5‚000 ሜትር ለመጀመርያ ጊዜ ለውድድር የቀረበው በአትላንታ ኦሊምፒክ (1996) ሲሆን፣ በወቅቱ ያሸነፈችው ቻይናዊቷ ዋንግ ጁኒያ ስትሆን ኬንያዊቷ ፓውሊን ኮንጋ ሁለተኛ ወጥታ ነበር፡፡ ኢትዮጵያን በ5‚000 ሜትር የመጀመሪያ የሜዳሊያ ባለቤት ያደረገችው ሲድኒ ኦሊምፒክ (2000) የተካፈለችው ጌጤ ዋሚ ስትሆን ሦስተኛ ወጥታ ነሐስ አግኝታለች፡፡ አየለች ወርቁና ወርቅነሽ ኪዳኔ አራተኛና ሰባተኛ ሆነው ማጠናቀቃቸው ይታወሳል፡፡ ከመሠረት ወርቃማ ድል ግማሽ ሰዓት በኋላ በተካሔደው የሴቶች 1‚500 ሜትር ፍፃሜ በከፍተኛ ደረጃ ለወርቅ ተጠብቃ የነበረችው አበባ አረጋዊ ባልተገመተ ሁኔታ አምስተኛ ሆና አጠናቃለች፡፡ ከሦስት ዓመት ወዲህ የተከሰተችውና በዳይመንድ ሊግ በርቀቱ እየመራች ያለችው አበባ፣ የመጀመርያውንና የግማሽ ፍፃሜ ማጣርያዎችን በብቃት በአንደኛነት ማሸነፏ ብዙዎች ድሉን ለእርሷ ሰጥተው ነበር፡፡ ቢያንስ ከሜዳሊያው ተርታ እንደማትርቅም ገምተው ነበር፡፡ መሐመድ አማን በ800 ሜትር ያጋጠመውን ዓይነት ሽንፈት አስተናግዳለች፡፡ ከመነሻው መጨረሻ ላይ የነበረችው አበባ ወደ መሀል ስትገባ መደነቃቀፉ የፈጠረባት ጫና በውጤቷ ላይ ተፅዕኖ ማሳደሩ አልቀረም፡፡ ከልምድ ማነስ፣ መውጣት በሚገባት ጊዜ ያለመውጣትና በሥነ ልቦና አለመዘጋጀት ከሥልጠና ችግር የመጣ መሆኑ ለውጤቱ መጥፋት እንደምክንያት እየተቆጠረ ነው፡፡ ውድድሩን ቱርካዊቱ አልሲ ካኪር አልናቴኪን በ4 ደቂቃ 10፡23 ሰከንድ ስታሸንፍ፣ ሌላዋ የአገሯ ዜጋ ጋምዜ ቡሉት ሁለተኛ፣ ለባህሬን የሮጠችው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ መርያም ዩሱፍ ጀማል ደግሞ ሦስተኛ ሆናለች፡፡ ትናንትና ምሽት የወንዶች 5‚000 ሜትር ሩጫ የተካሄደ ሲሆን፣ ማተሚያ ቤት ቀድመን በመግባታችን ውጤቱን አልያዝንም እንጂ ኢትዮጵያ በወጣቶቹ ደጀን ገብረ መስቀል፣ ሐጎስ ገብረ ሕይወትና የኔው አላምረው ተወክላለች፡፡ ሐምሌ 20 ቀን የተጀመረው 30ኛው ኦሊምፒያድ ከ17 ቀናት በኋላ የሚያከትመው ዛሬ ከእኩለ ቀን በኋላ በሚደረገው የማራቶን ውድድር ይሆናል፡፡ በወንዶች ማራቶን የወርቅ ሜዳሊያ ካገኘች ሁለት ኦሊምፒያዶች ያሳለፈችው ኢትዮጵያ የአበበ ቢቂላን፣ የማሞ ወልዴን፣ የገዛኸኝ አበራን ድል የሚያስቀጥልላት አትሌት ከዲኖ ስፍር፣ ከአየለ አብሽሮና ከጌቱ ፈለቀ መካከል ማን ይሆን? ኢትዮጵያ እስከ ትናንት ድረስ በጥሩነሽ ዲባባ ወርቅና ነሐስ፣ በቲኪ ገላና ወርቅ፣ በመሠረት ደፋር ወርቅ፣ በሶፍያ አሰፋና በታሪኩ በቀለ ነሐሶች 22ኛ ደረጃ ላይ ትገኝ ነበር፡፡
‹‹እኔ ያደግሁት ውጭ አገር ነው፡፡ የትም ዓለም ላይ 13 ወር የለም፡፡ ፒራሚድ ሲታይ ግብፅ ነው፡፡ አይፈልታወር ሲታይ ፈረንሣይ ነው፡፡ የነፃነት ሐውልት ሲታይ አሜሪካ አለ፡፡ እኛ የምንታወቅበት የለንም ነበር፡፡ ሁሉ ነገር ከዘር፣ ከሃይማኖት ጋር የተያያዘ ነበር፡፡ ሳላውቀው አንድ ወቅት ላይ የ13 ወር ደመወዝ ይሰጠን ብዬ ጠየቅሁ፡፡ ወዲያው ይህንን ሐሳብ ወደ ቱሪስት መሳቢያነት መቀየር እንደሚቻል አሰብኩ፡፡ ሌላው ሁሉ ከዘር ከሃይማኖት ጋር የሚያያዝ ነበር፡፡ ላሊበላን ባደርግ ኢትዮጵያ በሙሉ ክርስቲያን ባለመሆኑ ችግር ነበረበት፡፡ የአሥራ ሦስት ወር ፀሐይ ግን ከምንም ነገር ጋር አይገናኝም፡፡ ምንም የፖለቲካና የሃይማኖት ንክኪ የለውም፡፡ አሁን ከዚያ የበለጠ ከተገኘ ደግሞ ቶሎ መተካት ነው፡፡ ምንም ችግር የለበትም፡፡›› በማለት በአንድ ወቅት ከሪፖርተር ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ የተናገሩት አቶ ሀብተሥላሴ ታፈሰ በኢትዮጵያ የቱሪዝም ኢንዱስትሪ መሥራች፣ የአሥራ ሦስት ወራት ፀጋ (13 Months of Sunshine) በሚል መጠሪያ የአገሪቱ ቱሪዝም ለዘመናት ሲያስተዋውቅ የኖረውን መለያ የፈጠሩና በዘርፉ በርካታ ሥራዎችን ያስተዋወቁ፣ የተገበሩ የቱሪዝም አባት ናቸው፡፡ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ይህንን ውለታቸውን ቆጥሮ ዕውቅና በመስጠት ለመጀመሪያ ጊዜ ሽልማት አበርክቶላቸዋል፡፡ ሰሞኑንም ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ እጅ ለሁለተኛ ጊዜ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ በቱሪዝም መስክና በተያያዥ ጉዳዮች ላይ ሔኖክ ያሬድና ብርሃኑ ፈቃደ ከጥቂት ዓመታት በፊት አነጋግረዋቸው ነበር፡፡ ይኸው ቃለ ምልልስ ለትውስታ ይሆን ዘንድ እንዲህ ቀርቧል፡፡ ሪፖርተር፡- በዘርፉ በጠቅላላው ኢትዮጵያን ለምን ያህል ጊዜ አገልግለዋል? አቶ ሀብተሥላሴ፡- ከመጀመሪያው እ.ኤ.አ. ከ1954 ጀምሮ አገልግያለሁ፡፡ ያኔ ከውጭ አገር ወደ ኢትዮጵያ እንደመጣሁ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ውስጥ እሠራ ነበር፡፡ ከዚያ በግድ ይህንን ሥራ [ቱሪዝምን] እንድሠራ አዘዙኝ፡፡ ገባሁበት፡፡ ከባድ ሥራ ነው፡፡ ያን ጊዜ ካሜራ ወደ ኢትዮጵያ አይገባም ነበር፡፡ ሲገባም ጉምሩክ ይይዘዋል፡፡ ፈቃድ ከማስታወቂያ ሚኒስቴር ማውጣትም ያስፈልግ ነበር፡፡ በዚህ ሰበብ ሁለት ጊዜ ታስሬያለሁ፡፡ ፎቶግራፍ ለምን ታነሳለህ ብለው ነው ያሰሩኝ፡፡ ያን ጊዜ ፎቶግራፍ የሚያነሳ ሰው ሰላይ ተደርጐ ይታሰብ ስለነበር ነው፡፡ ሪፖርተር፡- በቱሪዝም ሙያዎ ኢትዮጵያን ምን ያህል ያውቋታል? አቶ ሀብተሥላሴ፡- ያልደረስኩበት ቦታ የለም፡፡ በእግር፣ በፈረስ፣ በግመል፣ በሄሊኮፕተር፣ በአውሮፕላን ሁሉ ተዘዋውሬ ከ100 በላይ ሰው ያልረገጣቸው የኤርትራ ደሴቶችን አይቻለሁ፡፡ ትልቅ ሀብት ናቸው፡፡ ቢያውቁበት በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ መሰብሰብ ይችሉ ነበር፡፡ በጋምቤላ በኩል ጂካው ድረስ ሄጃለሁ፡፡ የደቡብ ሱዳን ጠረፍ ነው፡፡ በኤርትራ በኩል ቤንአመር ድረስ ወዳለው የጠረፍ ቦታ ደርሻለሁ፡፡ ቤንሻንጉልን በሙሉ እስከ ሱዳን ድረስ አዳርሻለሁ፡፡ መሥራት ካስፈለገ ማየት፣ ማወቅ ግድ ይሆናል፡፡ ካየን፣ ካወቅን በኋላ ማውራት ይቻላል፡፡ ሪፖርተር፡- በእነዚህ ሁሉ ጊዜያት እርስዎ ብዙ ሠርተዋል፡፡ ከሠሯቸው መካከል አሁንም ድረስ የሚታወቀው ኢትዮጵያ የአሥራ ሦስት ወር ፀጋ የሚለው አገሪቱ መጠሪያ ነው፡፡ ይህ የኢትዮጵያ መለያ ለብዙ ጊዜ ያገለገለ ነው፡፡ አሁን መቀየር አለበት የሚሉ አሉ፡፡ ይቀየር ቢባል ምን ይሰማዎታል? አቶ ሀብተሥላሴ፡- ሁልጊዜ አንድ ነገር ሲፈጠርና የሚበልጠው ሲገኝ ያንን ማየቱ ተገቢ ነው፡፡ በአንድ ወቅት ምክትል አፈንጉሥ ገብረ ወልድ ፎቅ ቤት ሠርተው ነበር፡፡ ያን ጊዜ በንጉሡ ዘመን የመንግሥት ግልበጣ ሙከራ ነበር፡፡ መንግሥቱ ንዋይ ደግሞ ጠንሳሽና የእኛም ዘመድ ነበር፡፡ ሰውየው ሰማይ ጠቀስ ፎቅ ሠርተሃል ተብለው ታሰሩ፡፡ ይህ ከሆነማ አፍርሱት ሲሏቸው የለም አንተን ነው የምናፈርሰው ብለው ገደሏዋቸው፡፡ አሁን ደግሞ በተገላቢጦሽ ሰማይ ጠቀስ ፎቅ እንዲሠራ ነው የሚፈለገው፡፡ ሪፖርተር፡- የአሥራ ሦስት ወር የፀሐይ ፀጋን እንዴት መረጡት? አቶ ሀብተሥላሴ፡- እኔ ያደግሁት ውጭ አገር ነው፡፡ የትም ዓለም ላይ 13 ወር የለም፡፡ ፒራሚድ ሲታይ ግብፅ ነው፡፡ አይፈልታወር ሲታይ ፈረንሣይ ነው፡፡ የነፃነት ሐውልት ሲታይ አሜሪካ አለ፡፡ እኛ የምንታወቅበት የለንም ነበር፡፡ ሁሉ ነገር ከዘር፣ ከሃይማኖት ጋር የተያያዘ ነበር፡፡ ሳላውቀው አንድ ወቅት ላይ የ13 ወር ደመወዝ ይሰጠን ብዬ ጠየቅሁ፡፡ ወዲያው ይህንን ሐሳብ ወደ ቱሪስት መሳቢያነት መቀየር እንደሚቻል አሰብኩ፡፡ ሌላው ሁሉ ከዘር ከሃይማኖት ጋር የሚያያዝ ነበር፡፡ ላሊበላን ባደርግ ኢትዮጵያ በሙሉ ክርስቲያን ባለመሆኑ ችግር ነበረበት፡፡ የአሥራ ሦስት ወር ፀሐይ ግን ከምንም ነገር ጋር አይገናኝም፡፡ ምንም የፖለቲካና የሃይማኖት ንክኪ የለውም፡፡ አሁን ከዚያ የበለጠ ከተገኘ ደግሞ ቶሎ መተካት ነው፡፡ ምንም ችግር የለበትም፡፡ ሪፖርተር፡- ዛሬም ድረስ መሥራት የሚፈልጓቸው ብዙ ጉዳዮች አሉ፡፡ አቶ ሀብተሥላሴ፡- መርዳት ነው የምፈልገው፡፡ መሥራት ያለባቸው የተመደቡት ሰዎች ናቸው፡፡ እነርሱን ለመርዳት ዝግጁ ነኝ፡፡ አምስት ያህል ፕሮጀክቶች አሉኝ፡፡ ፍልውኃን በአግባቡ አልተጠቀምንበትም፡፡ ወንዶገነትና ሶደሬ አካባቢ ጥቅም ላይ ውሏል፡፡ ነገር ግን ከ3,000 በላይ ፍልውኃ በየቦታው አለን፡፡ ያ የማያልቅ፣ ከወርቅና ከከበረ ድንጋይ ሁሉ የበለጠ ሀብት ነው፡፡ ነገር ግን አልተሠራበትም፡፡ እኔጋ ጥናቱ አለ፡፡ ዩኔስኮ ውኃውን ጨምሮ ያገኘው ጉዳይ አለ፡፡ ጥናቱ በእጄ ስላለ ለመንግሥት እሰጣለሁ፡፡ ይሠሩበታል ብዬ አስባለሁ፡፡ አሁን ቱሪስቶች ያሉት እዚሁ ከጐናችን ነው፡፡ ዱባይ፣ ኤምሬቶች አሉ፡፡ ድሮ ዓረብ ድሃ ነው፡፡ አሁን ዓለምን የያዙ እነሱ ናቸው፡፡ ፍልውኃ አረንጓዴያማ መስክ ይወዳሉና አቅሙ ላላቸው ባለሀብቶች መስጠት ከተቻለ ሰው ይመጣል፡፡ ከዱባይ አዲስ አበባ የሦስት ሰዓት በረራ ብቻ ነው የሚያስፈልገው፡፡ ከአውሮፓና ከአሜሪካ ሰው ይመጣል ብሎ መጠበቅ ከባድ እየሆነ ነው፡፡ ቀውስ ላይ ናቸው፡፡ የቅርብ አገሮች ግን መምጣት የሚችሉበት አቅም አላቸው፡፡ በግብፅ ለሁለት ዓመት ቆይቻለሁ፡፡ አባቴ አምባሳደር ነበሩና በዚያ ኖረናል፡፡ በጣም ቃጠሎ ነው፣ ሲበዛ ሞቃት ነው፡፡ በክረምት ብቻ ወደ አሌክሳንድርያ እንሄድ ነበር፡፡ አሁንም በጣም ሞቃት ነው፡፡ ሪፖርተር፡- እርስዎ የአሥራ ሦስት ወር ፀጋ ብለው ነበር ብዙ ፀጋ አለን ማለት ነው? አቶ ሀብተሥላሴ፡- ደመወዝ የለውማ፡፡ የአሥራ ሦስት ወር ደመወዝ አይከፈልበትም፡፡ ሪፖርተር፡- እንደ ኬንያ ያሉት አገሮች ግን የዱር እንስሳት ሀብት ብቻ እያላቸው ነገር ግን ብዙ የተጠቀሙበት ሁኔታ አለ፤ አቶ ሀብተሥላሴ፡- እነሱ ስላሠሩ ነዋ፡፡ እኛ አንሠራም፡፡ አንዱ ሲሠራ አሥሩ ወደኋላ ይጐትታል፡፡ ምቀኝነት አለ፡፡ የሐበሻ ፀባይ አብሮ መሥራት ስለሌለው መድረስ ያለብን ቦታ አልደረስንም፡፡ ሪፖርተር፡- አየር በዕቃ ሞልተው ለመሸጥ የሞከሩበት ጊዜ እንደነበር ይነገራልና ስለእርሱ ቢነግሩን? አቶ ሀብተሥላሴ፡- የኢትዮጵያ አየር የትም ዓለም ላይ አይገኝም፡፡ አንድ ጊዜ ንጉሡ ጋር ገባሁና አየር ይሸጣል አልኳቸው፡፡ ገንዘብ ሚኒስትሩ መጡና ምን ይለፈልፋል ብለው አጣጣሉኝ፡፡ አጋጣሚ ሆኖ እ.ኤ.አ. በ1970 በኦሳካ ኤግዚቢሽን ነበርና ወደ ቶኪዮ ዞር ዞር ብዬ ለማየት ሄድኩ፡፡ አንድ ቦታ ላይ የፊጂ ተራሮች የሚል ጽሑፍ ያለበት ቆርቆሮ አየሁ፡፡ ሳነሳው ባዶ ነው፡፡ ውስጡ ያለው የፊጂ አየር ብቻ ነው፡፡ ሰው ገዝቶ በአፍንጫው መማግ ብቻ ነው፡፡ ይህንን ገዛሁና ወደ ንጉሡ አመጣሁት፡፡ ስጦታ አምጥቼሎታለሁ አልኩና ሰጠኋቸው፡፡ አንስተው ሲያዩ ምንም የሌለው መስሏቸው ምን ትቀልዳለህ አሉኝ፡፡ አየር ይሸጣል ያልኩዎትኮ ይኼ ነው፤ ገዝቼ መጣሁ አልኳቸው፡፡ ገንዘብ ሚኒስትሩን ጠሩና ታስታውሳለህ ያልከውን ይኸውልህ አየር ይሸጣል አሏቸው፡፡ ይኼንን አሁንም ማድረግ ይቻላል፡፡ አየር በዕቃ ሞልቶ እንዲማግ ማድረግና መሸጥ ይቻላል፡፡ ውኃ በፕላስቲክ እየተሸጠ እኮ ነው፡፡ ሰው ግን አያምንም፣ አይቀበልም፡፡ አገሪቱን ያጠቃት በምቀኝነት፣ በዘር፣ በሃይማኖት መከፋፈላችን ነው፡፡ አንድ ሆነን ካልሠራን ከባድ ነው፡፡ አሁን ብዙ ለውጥ መጥቷል፡፡ ከሞት የተመለስኩ ያህል የሚሰማኝ ጊዜ አለ፡፡ ሴቱ ሁሉ እንደ ልቡ ነው፡፡ ወደ ዱባይ ወደ መሳሰሉት አገሮች ሲሄዱ፣ ሲሠሩ የሚታዩ ቆነጃጅቶች ብዙ አሉ፡፡ በእኛ ጊዜ እንዲህ አይታሰብም፡፡ ብዙ ለውጥ አለ፡፡ የሰው አስተሳሰብ ተቀይሯል፡፡ ሪፖርተር፡- አንድ ኒውዝላንዳዊ ሚሊየነር ኢትዮጵያን በሄሊኮፕተር ጐብኝቶ መደነቁን ሲናገሩ ነበርና ስለእርሱ ቢገልጹልን? አቶ ሀብተሥላሴ፡- ፓይለቱ የሰውየው ልጅ ባል ነው፡፡ ሰውየው ደግሞ ባለሄሊኮፕተር ነው፡፡ የእርሱ አስጎብኚ ከእኔ ጋር የሚሠራ ነውና ተዟዙሮ አይቶ እኔን ማየት ፈለገና እራት ጋበዘኝ፡፡ ተኝታችኋል አለኝ፡፡ በሄሊኮፕተር እየተዘዋወርን ከ125 በላይ አገሮች አይተናል እንደ ኢትዮጵያ የሚሆን ግን አላየንም አለኝ፡፡ ሰውየው የምንም ፍላጎት የላቸውም፡፡ ለጥቅም ብለው ነው እንዳይባል አገራቸው ኤምባሲ እንኳ እዚህ የላትም፡፡ ሰውየው ደግሞ እጅግ ባለጠጋ ናቸው፡፡ ቢሊየነር በመሆናቸው ለጉብኝት ብቻ ነው የመጡት፡፡ ያዩትን አይተው ተኝታችኋል አሉኝ፡፡ ሪፖርተር፡- የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሽልማት ሲሰጥዎ፣ በሕይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሽልማት ተጠራሁ ብለዋል፡፡ ለምንድን ነው ከዚህ በፊት ይህን ሁሉ ሠርተው ያልተሸለሙት? አቶ ሀብተሥላሴ፡- ምቀኞች ስለሆንን፡፡ ሁሌም ሲጠሩኝ ለአንድ ወቀሳ ነው፡፡ ቤተክህነት ተጠርቼ በቴሌቪዥን ለምን እንዲህ ተናገርህ እባላለሁ፣ የአገር ውስጥ ገቢ ይጠሩኝና እወቀሳለሁ፡፡ ያን ጊዜ ከቀረጥ ነፃ ሱቅ ከፍተን ነበር፡፡ የእኛ ቢሮ ከመንግሥት ቢሮዎች ሁሉ ሀብታም የሚባለው ነበር፡፡ ያን ጊዜ ቱሪዝም በጀት 220 ሺሕ ብር ስለነበር በዚህ በጀት እንዴት አገርን ማሳደግ ይቻላል እያልሁ ከጃንሆይ ጋር እጨቃጨቅ ነበር፡፡ አንድ ጊዜ ቁልፉን ይዤ ሄድኩና ጃንሆይ ይኼንን መሥሪያ ቤት ለሒሳብ ሹም ይስጡት ደመወዝ ከመክፈል ውጪ ሌላ ሥራ መሥራት አልቻልኩም አልኳቸው፡፡ የዲውቱ ፍሪ ፈቃድ ስጡኝ ብዬ ጃንሆይን ጠየቅሁ፡፡ ኋላ ላይ ገንዘብ ሚኒስትሩ መጡና እኛ ኮንትሮባንድ መቆጣጠር አቅቶናል፣ ሀብተሥላሴ ደግሞ አናታችን ላይ ኮንትሮባንድ ለመፍጠር ይፈልጋል አሉኝ፡፡ ንጉሡም ሥራህ መቆጣጠር ነው እንጂ ሥራ አይሥራ ነው የምትለው ወይስ መቆጣጠር አልችልም ነው? ብለው ጠየቋቸውና ተፈቀደልኝ፡፡ ሥራው ሊጀመር ሲል ደግሞ ገንዘብ ስለጠፋ የአባቴን ካርታ ወስጄ ለአንድ እብድ ሰጠሁና 5,000 ዶላር ተበደርኩ፡፡ በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ማግኘት ተቻለን፡፡ በአንድ ወቅት ከመላው ኢትዮጵያ የእኛ መሥሪያ ቤት ነበር ሀብታም የነበረው፡፡ አንድ ሚኒስትር ሲሾም በጊዜው እንዲነግድ አይፈቀድለትም ነበር፡፡ ለእኛ ተፈቅዶ ነበርና ብዙ ገንዘብ አስገብተናል፡፡ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ሕንፃ ተሠርቶ ሥራ ሲጀምር የእኛ መኪኖች ነበሩ የሚያገለግሉት፡፡ 46 ያህል ነበሩን፡፡ እኔ እንደ ሾፌር፣ እንደ አስጐብኚ፣ እንደ ፎቶግራፍ አንሺ እየሆንኩ ሠርቻለሁ፡፡ በኋላ ምቀኛ በዛና የዲውቲ ፍሪ ገንዘብ ወደ መንግሥት ይግባ አሉ፡፡ ያ አሠራር ዛሬ ቆይቶ ቢሆን ኖሮ አሥር ሚሊዮን ሰዎች በተሰማሩበት ነበር፡፡ ሪፖርተር፡- በጊዜው ሴቶችን ፎቶግራፍ ያነሱ ነበርና ከንጉሡ ዘንድ የገጠመዎት ጉዳይ አለ ይባላል፤ አቶ ሀብተሥላሴ፡- አዎ፡፡ አንዲት የጋምቤላ ሴት ፎቶግራፍ አንስቼ ነበር፡፡ ሴትየዋ ጡቷ ቆንጆ ነበርና አንስቼ ፖስተሩ ከመታተሙ በፊት ናሙናውን ለንጉሡ አስገብቼ ጠረጴዛ ላይ እደረድር ነበር፡፡ ንጉሡ መጥተው ሲያዩ ይኼ ምንድን ነው አሉና ጠየቁኝ፣ አይ ቱሪስቶች እንዲህ ማየት ይወዳሉ ስላቸው፣ አንተም ትወዳለህ ይባላል አሉኝ፡፡ በኋላ ታትሞ ሲወጣ ሳንሱር ይደረግ ነበር ራቁት እያሳየ ነው ብለው ንጉሡ ጋር መልሰው ይዘው መጡ፡፡ ንጉሡም አይተናል አሉና መለሷቸው፡፡ ከዚያ በኋላ የቱንም ነገር ከመሥራቴ በፊት ቀድሜ ለንጉሡ ስለማሳይ አይተናል እያሉ ሚኒስትሮችን ይመልሷቸው ነበር፡፡ ብዙ መሥራት አንወድም፡፡ ስንሠራ ደግሞ ምቀኛው ወደኋላ የሚጐትት ነው፡፡ ሪፖርተር፡- እርስዎ ለባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር እሰጣለሁ ካሏቸው ፕሮጀክቶች አንዱ አንድ ብር ቢያንስ በአንድ ዶላር መመንዘር የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡ ይኼ አስማት አይደለም ሲሉም ሰምተናልና እንዴት ነው ይኼ የሚሆነው? አቶ ሀብተሥላሴ፡- ይኼ አስማት አይደለም፡፡ እንዴት እንደሆን የምንነግረው ግን ለሚኒስትሩ ነው፡፡ እሳቸው ከተስማሙ በኋላ የእሳቸው ፕሮጀክት ይሁን፡፡ አሁን መናገሩ ጊዜው አይደለም፡፡
የካሜራ ሞጁል, እኛ እናውቃለን እንደ ካሜራዎች ወይም ውጫዊ በይነ የተለያዩ ቅርጾች, ነገር ግን የውስጥ ሞጁሎች በመሠረቱ ሌንሶች, ቤዝ, ማጣሪያዎች, ዳሳሾች, DSP (አይኤስፒ ጨምሮ), PCB substrates, ወዘተ ያቀፈ ነው እንደ ውጫዊ በይነ የተለያዩ መሠረት. የምርቱ የትግበራ ሁኔታዎች ፣ የተለያዩ የበይነገጽ ዓይነቶች አሉ።ለ DSP ክፍል ተመሳሳይ ነው.እንደ ተለያዩ የመተግበሪያ ሁኔታዎች፣ የተለያዩ የአጠቃቀም ዘዴዎች እና የተለያዩ የማስኬጃ መስፈርቶች፣ አንዳንዶቹ በቀጥታ በሴንሰሩ ውስጥ የተካተቱ ሲሆን አንዳንዶቹ ደግሞ በቀጥታ ዳሳሹ ውስጥ ይካተታሉ።ለማቀነባበር ውጫዊ የተወሰነ ቺፕ ያስፈልጋል። መነፅርብርሃንን ወደ ምስል ዳሳሽ የሚያፈስ መሳሪያ ነው።ዘመናዊ ሌንሶች ብዙውን ጊዜ የበርካታ ሌንሶች ቡድን ናቸው.ሌንስ በተለያዩ ቁሳቁሶች መሰረት በመስታወት እና በፕላስቲክ የተከፋፈለ ነው የምስል ዳሳሽበተለምዶ ሴንሰር በመባል የሚታወቀው የካሜራ ሞጁል ዋና አካል ነው።በዋናነት ሁለት ዓይነት የCMOS ምስል ዳሳሾች እና የሲሲዲ ምስል ዳሳሾች አሉ።ላይ ላይ በመቶዎች ወይም በአስር ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ፎቲዲዮዮዶች አሉ።የኦፕቲካል ምልክቱ ወደ ኤሌክትሪክ ምልክት ይቀየራል, ጥራቱ በቀጥታ የ CCM አፈፃፀም ላይ ተጽዕኖ ያሳድራል. የ IR ማጣሪያ ተግባር በሰው ዓይን የማይታየውን አልትራቫዮሌት እና ኢንፍራሬድ ብርሃንን በማጣራት ያልተፈለገ ብርሃንን ማንጸባረቅ፣የቀለም ቀረጻ ተጽእኖን ለመከላከል ቆሻሻዎችን ማስወገድ እና የጠፋ ብርሃንን መቀነስ ነው።650NM፣850NM፣940Nm አለን። መሠረት የየካሜራ ሞጁልየካሜራውን ኦፕቲካል ኤለመንቶችን ከዋናው ፕሮሰሰር ጋር የማገናኘት ሃላፊነት ያለው የታተመ የወረዳ ሰሌዳ (ፒሲቢ) ወይም ተጣጣፊ የወረዳ ሰሌዳ (ኤፍፒሲ/ኤፍሲቢ) ነው። ሮንጉዋ፣ እ.ኤ.አአምራችበ R&D ፣ በማበጀት ፣ በማምረት ፣ በካሜራ ሞጁሎች ፣ በዩኤስቢ ካሜራ ሞጁሎች ፣ ሌንሶች እና ሌሎች ምርቶች ሽያጭ እና አገልግሎት ላይ ያተኮረ ። እኛን ለማግኘት ከፈለጉ እባክዎን
በየትግራይ ክልል ያለውን ሁኔታ “አሰቃቂ” ነው በማለት የገለጹት ዶ/ር ቴድሮስ፤ “6 ሚልየን የሚሆነው የክልሉ ህዝብ ለ500 ቀናት ያክል ከውጭው ዓለም ጋር እንዳይገናኝ ተደርጎ እንደተዘጋበት ነው” ብለዋል። “ከታህሳስ ወር አጋማሽ ጀምሮ ምንም አይነት እርዳታ አልደረሰም” ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ፤ በዓለም ጤና ድርጅት በተደረገ ግምገማ መሰረት የክልሉ ሶስት አራተኛ የጤና ተቋማት መውደማቸውም በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል። ባለፈው የካቲት ወር ለ300 ሺህ ሰዎች የሚበቃ 33.3 ሜትሪክ ቶን መድሃኒት እና የህክምና ቁሳቁሶች ወደ ትግራይ ማስገባት ቢቻልም፤ ይህ በክልሉ ላለው ችግር ምላሽ ለመስጠት ከሚያስፈልገው 2 ሺህ 200 ሜትሪክ ቶን እንጻር እጅግ ዝቅተኛ ነው ብለዋል። እስካሁን ወደ ክልሉ የገባው አጠቃላይ የህክምና እርዳታ መጠን 117 ሜትሪክ ቶን (ከ1 በመቶ ያነሰ) ብቻ መሆኑንም ጭምር ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል። አሁን ባለው ሁኔታ 46 ሺህ የሚሆኑ በደማቸው ኤች.አይ.ቪ ያላቸው ሰዎች እንዲሁም የካንሰር፣ስኳር፣ቲቢ እና ተጓዳኝ በሽታ ታማሚዎች ህክምና ማግኘት የሚችሉበት ሁኔታ የለም ብለዋል። ዶ/ር ቴድሮስ በንግግራው አክለውም፤ “አዎ፣ እኔ የትግራይ ተወላጅ ነኝ፤ ይህ ችግር እኔን፣ ቤተሰቤን እና ጓደኞቼን በግል ይነካል” ነገር ግን እኔ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር በመሆኔ ጤና አደጋ ላይ በወደቀበት ቦታ ሁሉ ጤናን የመጠበቅ እና የማስተዋወቅ ግዴታ አለብኝ ፤እናም በዓለም ላይ እጅግ የከፋ የጤና ቀውስ ያለው በትግራይ ነው” ሲሉም ተደምጧል። ዶ/ር ቴድሮስ በዓፋር እና አማራ ክልል ያለው የሰብዓዊ ቀውስ ሁኔታ ከጊዜ ወደ እየተባባሰ መምጣቱንም ተናግረዋል። በሁለቱም ክልሎች የመጠሊያ፣ ምግብ እና ህክምና ድጋፍ የሚሹ በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መኖራቸውን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ተፈናቃዮች ለመርዳት የተለያዩ ስራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውንም አስታውቀዋል። የሰሜን ኢትዮጵያው ትግራይ ክልል "ስልታዊ" እገዳ ተጥሎበት ነበር-ዶ/ር ቴድሮስ ሆኖም ግን በአማራ ክልል እና በአፋር ክልል በነበረው ጦርነት ስለወደሙ የጤና ተቋማት ከመናገር ተቆጥበዋል። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ በሰጡት መግለጫቸው የዶ/ር ቴድሮስ መግለጫን በማስመለከት ምላሽ ሰጥተዋል። በምላሻቸውም “ዋና ዳይሬክተሩ እንደ ትግራይ ሁሉ በህወሐት ምክንያት በአማራና በአፋር የወደሙትን የጤና ተቋማት ጉዳይ ሊያሳስባቸው ይገባል” ብለዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ከዚህ ቀደም ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ከተጣለባቸው ሃላፊነት ውጪ በሽብርተኝነት ለተፈረጀው ህወሃት ያደላ የፖለቲካ ውግንና አሳይተዋል በሚል፤ ለዓለም ጤና ድርጅት መርማሪ ቦርድ የ‘ይመርመርልኝ’ ጥያቄ እስከማቅረብ ደርሷል። የድርጅቱ መርማሪ ቦርድ “ይህ እጅግ ውስብስብና ፖለቲካዊ መልክ ያለው እና ከኮሚቴው የአሰራር ሂደት ውጭ የሆነም ጉዳይ ነው” የሚል ምላሽ እንደሰጠም የሚታወስ ነው።
የናሙና ጊዜ ከ5-7 ቀናት አካባቢ / የጅምላ ማዘዣ ጊዜ ከ10-25 ቀናት አካባቢ በተለያዩ ምርቶች እና ቴክኒኮች (ዝርዝሮች እባክዎን ያነጋግሩን እኛ የበለጠ ለመጋራት እንረዳለን) / በተለያዩ ቻናል ላይ የተመሠረተ የማጓጓዣ ጊዜ (የተለመደ ብሔራዊ ፈጣን ከ5-7 ቀናት አካባቢ ፣ በፍላጎትዎ መሰረት እዚህ ብዙ ወጪ ለመቆጠብ የተሻለውን እንዲመርጡ ተጨማሪ ቻናል እናካፍልዎታለን) ለዋና ሸማችዎ ስለመላክ በተለምዶፓኬጁን ወደ ደንበኞቻችን አድራሻ እንልካለን እና ጥቅሉን ወደ ደንበኛ ደንበኛዎ እንድንልክ ከፈለጉ ለመላክ እንረዳዎታለን።ወይም ከእርስዎ እና ከጓደኞችዎ የተሰበሰበው ትዕዛዝ፣እኛ እንዲሁ ለእያንዳንዱ ሰው ለመላክ እና የማጓጓዣ ወጪን በተናጠል ለማስላት ልንረዳዎ እንችላለን። ስለ ታክስ ወጪ ብዙውን ጊዜ የ EXW ዋጋን ያለግብር ወጪ ወይም በደንበኛ የመርከብ ጥያቄ መሰረት እንጠቅሳለን ፣ከታክስ ወጪ ጋር የመርከብ አማራጭን እናቀርባለን።ነገር ግን የ EXW ዋጋን ለአንዳንድ ደንበኞች ስንጠቅስ በምክንያት የታክስ ወጪን የምንቆጣጠርበት መንገድ የለንም::የተለያዩ ሀገር ፕሮሊሲሲ፣ ነገር ግን ማጓጓዣን ስናዘጋጅ ብጁ እሴት ስራ በዚህ ክፍል ላይ ያለውን ወጪ ለመቆጠብ በተቻለ መጠን ዝቅተኛ ለመስራት መርዳት እንችላለን። ከእኛ ጋር መስራት ይፈልጋሉ? አግኙን OEM & ODM ማተሚያ አምራች, በደንበኞች ተግዳሮቶች እና ግፊቶች ላይ እናተኩራለን, ለደንበኞች በጣም ተወዳዳሪ የሆነ የህትመት ምርት መፍትሄዎችን መስጠቱን እንቀጥላለን.በደንበኞች የሚታመን አቅራቢ እና በሠራተኞች የሚታወቅ የሥራ ልማት ቦታ ይሁኑ።
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 6፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኮሮናቫይረስ (ኮቪድ 19) ወረርሽኝ ስርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠርና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ የወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተፈጻሚነት ለማረጋገጥ ዝግጁ መሆናቸውን ፍርድ ቤቶች ገለጹ። መንግስት የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ስርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠርና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ወደ ስራ ገብቷል። አዋጁን ተከትሎ የወጣው የማስፈፀሚያ ደንቡ በአራት ዋና ዋና ከፍሎች ክልከላን በማስቀመጥ፤ ግደታዎችን […] Source: ፍርድ ቤቶች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ተፈጻሚነት ለማረጋገጥ ዝግጁ መሆናቸውን ገለጹ – Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C ፍርድ ቤቶች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ተፈጻሚነት ለማረጋገጥ ዝግጁ መሆናቸውን ገለጹ አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 6፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኮሮናቫይረስ (ኮቪድ 19) ወረርሽኝ ስርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠርና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ የወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተፈጻሚነት ለማረጋገጥ ዝግጁ መሆናቸውን ፍርድ ቤቶች ገለጹ። መንግስት የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ስርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠርና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ወደ ስራ ገብቷል። አዋጁን ተከትሎ የወጣው የማስፈፀሚያ ደንቡ በአራት ዋና ዋና ከፍሎች ክልከላን በማስቀመጥ፤ ግደታዎችን በመጣል፤ የአስፈፃሚ አካላትን ክንውን በመዘርዘር ልዩ ልዩ ድንጋጌዎችን አስቀምጧል፡፡ በዚህም የፌደራል ከፍተኛ እና የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶችም መደበኛ የወንጀል ዳኝነት አስራር ስርዓትን ለጊዜው በማቆም በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መሰረት ስራቸውን እንዲያከናውኑም ተደንግጓል። በተለይም በአስቸካይ ጊዜ አዋጁ ድንጋጌዎች በተቋማትና ድርጅቶች ሲጣሱ ግለሰቦችም አዋጁን ሲተላለፉ ፍርድ ቤቶቹ በህግ ተጠያቂ ያደርጋሉ። የአስቸካይ ጊዜ አዋጁ አስፈጻሚ ከሆኑት መካከል ፍርድ ቤቶች ለአዋጁ ተፈጻሚነት ያላቸውን ዝግጁነት ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ገልጸዋል። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ብርሃነ መስቀል፥ መንግስት የዜጎቹን ህልውና ለመጠበቅ ያወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተፈጻሚ እንዲሆን በቅድሚያ ሁሉም ዜጋ የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ ይገባል ብለዋል። ይሁንና ይህ አዋጅ ተፈጻሚ እንዳይሆን የሚቀሳቀሱ በተለይም አዋጁን ተላልፈው የተገኙ ሰዎችን በህግ በተቀመጠው የቅጣት አወሳሰን መሰረት በዳኝነት አካሉ ፈጣን እልባት ለመስጠት በፍርድ ቤቶች በኩል ዝግጁነት እንዳለ አረጋግጠዋል። በተለይም የአስቸካይ ጊዜ አዋጁን ተከትሎ በፍርድ ቤቶች ተረኛ ችሎቶችን በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲደራጁ በማድረግ በአዋጁ አተገባበር ዙሪያ የሚገጥሙ መተላለፎችን በህግ መሰረተ ተፈፃሚ ለማድረግ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ፉአድ ኪያር አህመድ በበኩላቸው፥ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል ፍርድ ቤቶች ከመጋቢት 10 ጀምሮ በከፊል የተዘጉና በተረኛ ችሎት ለውሳኔ የደረሱ እና ውዝፍ መዛግብት ላይ ውሳኔዎችን እየሰጡ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ለአስቸኳይ አዋጁ ተፈጻሚነት ግን ፍርድ ቤቱ ዝግጁ ነው ያሉት አቶ ፉአድ፥ የህግ እልባት የሚሹ ጉዳዮች ሲያጋጥሙም በተረኛ ችሎት በመመልከት አፋጣኝ እልባት ለመስጠት ቁርጠኝነት መኖሩንም ተናግረዋል።
የ1960ዎቹ የኢትዮጵያ አብዮት ንቅናቄ አንዱ ፍንካች፣ በትግራይ እና በኤርትራ የሽምቅ ወታደራዊ ባህሪ ይዞ የቀጠለው ትግል መሆኑ እሙን ነው። በርግጥ የትግራይ ዐመጽና ተቃውሞ መሪዎቹ ከሚሉትም ባለፈ፤ የመነሻ ምክንያቱ ሰፊና መዋቅራዊ ፍላጎት እንደነበረው አይዘነጋም። በዚህ ዐውድ፣ የዛሬዎቹ የወያኔ መሪዎችን እና የትግራይ ልሂቃንን ተጣራሽ አቋምና ፖሊሲዎች በአጭሩ እንመለከታለን። በትብብርና የቅራኔ ታሪክ የቆመው የወያኔ ፖሊሲ ወያኔ አንድን አጋር ድርጅት ወይም ስብስብ ለወታደራዊም ሆነ ለፖለቲካዊ ፍላጎቱ ተጠቅሞ መጣልን ‹መርህ› በሚል የዳቦ ስም እንደሚያቆላምጠው ልብ ይሏል። እንዲህ ዐይነቱን ኀቡዕ ምንፍቅና የተጫነው “ግንኙነት”ም፣ ከበርካታ ድርጅቶች ጋር እንዳደረገው ሁሉ፤ ከኤርትራ ዐማጺያንም ጋር ሲዳከም ትብብርን፣ ሲጠናከር ቅራኔን የተከተለ “ወዳጅነት” ፈጥሮ ነበር። በተለይ በትግሉ መጀመሪያ አካባቢ በአስመራ ዩኒቨርሲቲ የነበሩ የትግራይ ተወላጆች፣ ከኤርትራው ነፃ አውጪ ጀብሓ የድጋፍ ቃል እንዲገባላቸው ብዙ ጥረዋል። በኋላ ምንም እንኳ ጀብሓን ጥለው ሻዕቢያ ላይ ቢንጠላጠሉም። ይህን በተመለከተ ጆን ያንግ “The Tigray and Eritrean Peoples Liberation Fronts;- A History of Tensions and Pragmatism” (1996) የሚል ርዕስ በሰጠው ጽሑፉ ሻዕቢያ፣ ለወያኔ ድጋፍ የማድረግና የማጠናከር ውሳኔ ላይ የደረሰው፣ የነፃነት ጥያቄውን መቀበሉን መሰረት በማድረግ እንደነበረ አስረግጧል። በቀጣይነትም የወያኔ የጦር አዛዥ ስዬ አብርሃን ጨምሮ፤ ዘጠኝ አባላት ያሉት የአመራር ቡድን፣ በኤርትራ ለሦስት ወራት ስልጠናዎችን ወስዶ ተመልሷል። አስመራ በነበሩ የትግራይ ተማሪዎች የድጋፍ ቃል ሲጠየቅ የነበረው ጀብሓም፣ ትግራይ በነበረው የመንግሥት ወታደራዊ ማዕከላት ላይ ከሰነዘራቸው ጥቃቶች፣ ወያኔ የውጊያ ልምድ ማግኘቱ አይካድም። ይህም፣ በጀብሓ እና ወያኔ መሃል በጎ ወታደራዊ ትብብር እንዲፈጥር ያስቻለ ነበር። በተለይ ደርግ በ1968 ዓ.ም (በፈረንጆቹ 1976) የኤርትራ ዐማጺያኖችን ለመምታት “ራዛ ኦፕሬሽን” የተሰኘ ዘመቻ ባወጀበት ወቅት፣ ወታደራዊ ትብብሩን ሻዕቢያም ተቀላቅሎት፣ ዘመቻውን አክሸፈውታል።
እግዚአብሒር ንኣዳም ንሔዋንን ካብ ኣርባዕተ ባሕርያት ፈጢሩ ብመንፈስ ቅዱስ ቀዲሱ ኣኽቢሩ ብዘይካ ሓንቲ ኦም በለሰ ኵሉ ወንኑ ብልዑ ስተዩ ኢሉ ኣብ ገነት ኣቐመጦም፡ ነታ ኦም እቲኣ’ውን ነፊግሎም ኣይኰነን እንታይ ደኣ ናቱ ገዛእነትን ናታቶም ተገዛኢነትን ንኽፈልጡ ንመጻኢ’ውን ሥርዕት ጾም ንኽምህሮም እዩ።(ዘፍ.2፡6-7) ሸውዓተ ዓመት ትእዛዙ ሓሊዎም ብውሉድነት ጸኒዖም ክነብሩ ኸለዉ ብድሕሪኡ ግን ናይ ከይሲ ምኽሪ ሰሚዖም ፤ ኣምላኽነት ተመንዮም ትእዛዙ ኣፍረሱ፤ ካብ’ታ ኣይትብልዑ ዝበሎም ኦም በሊዖም፤ ኣብ ልዕሊ ሞተ ሥጋ ሞተ ነፍስ ተፈርዶም፤ “ሞት ግን ካብ ኣዳም ክሳብ ሙሴ ኣብኣቶም ከም’ቲ ናይ ኣዳም ትእዛዝ ብምጥሓስ ኃጢኣት ኣብ ዝገብሩን ዘይገብሩን ነጊሡ ነበረ’’። (ሮሜ .5፡14) ብድኅሪ’ዚ ጽቡቕን፤ ክፉእን ፤ ነዊሕን ፤ ሐጺርን ፤ ቀይሕን ፤ ጸሊምን፤ ምግቡ እንተ በላዕካዮ ደዌ ሥጋ ፍልጸት ፤ቅርጸት ፤ መንፋሕቲ ፤ ቅርጥማት፡ ደዌ ነፍሲ ኸኣ ዝሙት፤ ኃጢኣት ኣብ ዝነግሠሉ ናብ’ዚ ዓለም’ዚ ሰደዶም “ወተሰዱ ውስተ ምድረ ሕማም ወኣራያ ሕሱም ወኃሣር ወሲሳየ ኃዘን” ከም ዘበለ። (መቅ.ወንጌል) ነገር ግን ኣብ ጐድኒ ቁጥዓኡ ምሕረቱ ከም ዘሎ ፈሊጦም ተጣዒሶም ሚእቲ ዓመት ንስሓ ኣትዮም በኸዩ፤ “ወኮኑ ውስተ ኃዘን ምእተ ዓመት”፡ ብፍጥረቱ ጨኪኑ ዘይጭክን ጐይታ ንስሓኦም ርእዩ ተቐቢሉ ብኽያትቶም ሰሚዑ። “በሐሙስ ዕለት ወበመንፈቃ ለዕለት እትወለድ እምወለተ ወለትከ፤ ወእከውን ሕፃን በእንቲኣከ፤ ወእድህከ ውስተ ምርህብከ፤ ወእትቤዘወከ በመስቀልየ፡” ድሕሪ ሓሙሽተ መዓልትን ፈረቓ መዓልትን ካብ ጓል ጓልካ ተወሊደ ምእንታኻ ሕፃን ኰይነ ኣብ ጐላጒልካ ፍሑኽ ፍሑኽ ኢለ ብመስቀለይ ክብጀወካ እየ ክምዝበለ።(ቀሌምንጦስ) እቲ ተስፋ ንደቁ ነጊርዎም ነበረ፣ ደቁ ኸኣ ትንቢት እናተነበዩ ሱባዔ እናቘጸሩ ከም’ቲ ዳዊት ዝበሎ። “አንሥእ ኃይለከ ፈኑ እዴከ” ኃይልኻ ዝተባህለ ወልድ ብሥጋ ሰዲድካ ኣድሕነና። (መዝ.144፡7)እናበሉ እቲ ተስፋ እቲ እናተጸበዩ በብተራ ሓለፉ፡ ሓሙሽተ መዓልቲ ፈረቓን ዝበሎ ግን ብእግዚአብሔር ኣቋጻጽራ ሰዓት 5500(ሐሙሽተ ሽሐን ሓሙሽተ ምእቲን ዓመት) እዩ ዝነበረ። (መዝ.90፡4 ፡ 2ይጴጥ.3፡8) እቲ ዝተባህለ ዓመት ምስ ኣኸለ። ዝተዛረቦ ዘይርስዕ ዝህቦ ተስፋ ዘይከልእ እግዚአብሔር ሓደ ሰዓት ወይ ደቒቕ ከየሕለፈ ካብ ቅድስት ድንግል ማርያም፤ ካብ ሥጋኣ ሥጋ፤ ካብ ነፍሳ ነፍሲ ወሲዱ፤ ብዘመነ ዮሐንስ ብዕሥራን ትሽዓተን መጋቢት፤ ብሣልሳይ ሰዓት ፤ ብዕለተ እሁድ ተፀንሰ፡ ድሕሪ ትሽዓተ ወርሕን ሓሙሽተ መዓልትን ብዘመን ማቴዎስ ዕሥራን ትሽዕተን ታሕሣስ ሠሉስ መዓልቲ፤ ፍርቂ ለይቲ ተወልደ። ብዳሕራይ ዘመን ካብ ሠለስተ ኣካላት ሓደ መጀመርታ ዘይብሉ ናይ እግዚአብሔር ቃል ማንም ከየገደዶ ብናቱን ብናይ ኣብኡን ብመንፈስ ቅዱስን ፍቓድ ሰብ ኮነ፤ ኣብ ሰማይ ካብ ዘለው መላእኽቲ ሰብ ከም ዝኾነ ምንም ኣይፈለጡን፤ ካብ ኣቦን ካብ ኣደን ዝተወልደት ካብ ቅድስት ድንግል ማርያም ሐደረ፤ ሥጋ ዘይብሉ ንሱ ሥጋ ተዋሒዱ ከም ሰብ ትሽዓተ ወርኂን ሓሙሽተ መዓልትን ብጐይትነቱ ኰሎ ኣብ ማኅፀና ተወሰነ፤ ትሽዓተ ወርኂን ሓሙሽተ መዓልትን ምስ ተፈጸመ፣ ዝውለደሉ መዓልቲ ምስኣኸለ ክምርመር ብዘይከኣል ተግባር ብሕቱም ድንግልና ተወልደ፤ ማኅተመ ድንግልናኣ’ውን ኣይተለወጠን ማኅተመ ድንግልናኣ ከይተለወጠ ደኣ ተወልደ። (ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ሃይማኖተ ኣበው 212 ገጽ) ክሳብ እዛ መዓልቲ እዚኣ ጽቡቕ ተግባር ዝገበሩ ቅዱሳን ሓዋርያት ሰማዕታት ኵሎም ከም ዘኣመንዎም እምነት ከምኡ ኢና ንኣምን፤ “ቃል ሥጋ ኮነ” መናፍቃን ከም ዝብልዎ ኣብ (ዕሩቅ ብእሲ) ተራ ሰብ ኣይሓደረን። ብናቱ ፍቓድ፤ ብናይ ኣብኡን፤ ብናይ መንፈስ ቅዱስን ድልየት ካብ ቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋ ወሲዱ ተዋሃሃደ፤ ከም’ቲ ዝተጻሕፈ ኵሉ ዝፈጠረ ኣምላኽ ናይ ኣብ ኣካልዊ ቓል ፍጹም ሰብ ኰይነ ተወልደ።(ገላ.4፡4) ዝተባህለ ነስተውዕል እግዚኣብሔር ካባና ባሕርይ ዝተዋሃሃዶ ተዋሕዶ ንእሽቶ ክብሪ ኣይምሰለና፤ እዚ ንመላእኽቲ እኳ ኣይተገብረን፤ ናይ መላእኽቲ ባሕርይ ኣይተወሓሃደቶን ዝተዋሃሃደቶስ ናትና ባሕርይ እያ ንሱ’ውን ንባሕርይና ደኣ ተውሃዳ ንምንታየይ ኣይበለን። (ቅዱስ ዮሐንስ ኣፈወርቂ ሃይማኖተ ኣበው ገጽ 219፡21) ካብ ሠለስተ ኣካላት መን እዩ ዝተወልደልና እንተ ተባህለ እግዚአብሔር ወልድ እዩ፤ ስለምንታይ አብን ፤ መንፈስ ቅዱስን ተወሊዶም እንተ ዝብሃልከ ናይ ባሕርይ ስሞምን ተግባሮምን ምተፋለሰ ነይሩ። ከም’ዚ ከይከውን ግና እግዚኣብሔር ወልድ ብናይ ባሕርይ ስሙን ብናይ ባሕርይ ግብሩን ንምጽዋዕ ብሥምረቱን ድልየቱን ብጀካ ኃጢኣት ፍጹም ሰብ ኰይኑ ተወልደ። “ወአኮ አብ ዘኃደረ ውስተ ከርሠ ድንግል ለተሰብአ፤ ከመ ኢይበል መኑሂ ይትፋለሰ ስመ አብ ወመንፈስ ቅዱስ ለከዊነ ስመ ወልድ፤ ኣላ ውእቱ ወልድ በፈቃደ አቡሁ ወበሥምረተ መንፈስ ቅዱስ ተሠገወ እስመ አሐቲ ፈቃደ ዘሥሉስ ቅዱስ” ። ማንም ሰብ ስም አብን መንፈስ ቅዱስን፤ ናብ ስም ወልድ ንምዃን ተቐያሪ እዩ ንኸይበሃል፤ ኣቦ፥ ሰብ ንምዃን ኣብ ማኅፀን ድንግል ኣይሐደረን፤ እንታይ ደኣ ፍቓድ ቅድስት ሥላሴ ሓደ ስለ ዝኾነ ወልድ ብፍቓድ አብን፤ ብሥምረት መንፈስ ቅዱስን እዩ ሥጋ ዝተወሃሃደ። ይብል። (ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ) ከም’ዚ ሰለ ዝተባህለ ግን አብ ንምጽናዕ፤ ወልድ ሥጋ ንምውህሃድ፣ መንፈስ ቅዱስ ከኣ ንምንጻሕ ፤ ኣብ ከርሢ እግዝእትነ ማርያም ኃደሩ ንብል ነኣምን’ውን። መንፈስ ቅዱስ ንእግዝእትነ ማርያም ኣንጺሕዋ ይብል ካብ ምንታይ ኣንጺሕዋ ማለት እዩ እንተ ተባህለ ካብ ናይ ኣንስቲ ልማድ፤ ካብ ዘርእን፤ ርኳቤን “ውእቱ ንጹሕ እምሠለስቱ ግብራት ዘውእቶሙ ዘርእ፤ ውሩካቤ፤ ወሰስሎተ ድንግልና፤ እለ ሥሩዓን በእጓለ እመ ሕያው ወእሙራን ቦሙ”። ንሱ ኻብ’ቶም ኣብ ደቂ ሰባት ዘለዉ ፍሉጣትን ሥሩዓት ዝኾኑ ሠለስተ ተግባራት ዘርእን ፤ ሩካቤን ንጹሕ እዩ ይብል ። (ስኑትዮ ዝእስክንድርያ) ነገር ግን እዚ ዀሉ ኣብ እግዝእትነ ማርያም ኔሩ ኣይኮነን ንሳስ ናይ ኣዳም ኃጢኣት ዘይረኽባ ንጽሕቲ ባሕርይ እያ፡ “ወኢረኵሰት በምንትኒ እምዘፈጠራ ድንግል ብኅሊናሃ ወድንግል በሥጋሃ” ይብላ፡ (ሃይማኖት ኣበው)። እዚ ዝተብህለ ናይ ደቂ ኣዳም ሥርዓት ንኽይበጽሓ ካብ ትፍጠር ጀሚሩ ቀዲስዋ ኣካላዊ ቃል ጐይታና ኢየሱስ ክርስቶስ ንምውላድ ኣብቂዕዋ ንማለት እዩ፡ “ መንፈስ ቅዱስ አንጽሐ ለማርያም ወረሰያ ድሉተ ለተወክፎ ቃል አብ” ከም ዝበለ፡ (ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ) ቅዱስ ገብርኤል መልኣኸ ክትፀንሲ ኢኺ፤ ወዲ’ውን ክትወልዲ ኢኺ ምስ በላ ንሳ’ውን ከም’ቲ ዝበልካኒ ይኵነለይ ምስ በለቶ፣ ክምርመር ብዘይከኣል ተግባር ብዘይውሱን ኣካል ቅድሚ ዓለም ዝነበረን ዘሎን ንዘልዓለም ዝነብርን ኣካላዊ ቃል ብምልኣትን ብጐይትነትን ካብ አብን መንፈስ ቅዱሱን ሓድነት ከይተፈለየ፤ ብድንግልና ጸኒዓ ካብ ዝነበረትን ዘላን ንዘለዓለም’ውን ትነብርን ካብ ኣዴና ቅድስት ደንግል እግዝእትነ ማርያም ብናይ መንፈስ ቅዱስ ግብሪ ናይ ዕለት ፅንሲ ኾነ፡ “ነሥአ ሥጋ እንዘ ምሉእ በኵለሄ እንዘ ኢየዐርቅ እመንበረ ስብሐቲሁ ፤ ውስተ ማኅፀነ ድንግል ኅደረ ሥጋ ኮነ ወተወልደ” ኣብ ኵሉ ምሉእ ኰሎ ሥጋ ንምልባስ ኣብ ማኅፅን ተወሰነ፤ ካብ ናይ ሥልጣኑ መንበር ከይለቐቐ ኣብ ማኅፀን ድንግል ሓደረ፤ ሥጋ ለቢሱ ኸኣ ተወልደ ይብል፡ (ያሬዳዊ መዝሙር(ድጓ)) ናይ ዕለት ፅንሲ ኮይኑ ዝተቈጽረሉ ምሥጢር ግን ዝፈልጦን ዝምርምሮን የለን፤ ንሱ ብዝፈልጦ እዩ ኣካላዊ ቃል ሰብ ዝኾነ። “ወአሜሃ ሥጋሁ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ተሥዕለ በጥንተ ኣካል እንዘ ይትወሐድ ምስለ ቃል”። ሽዑ ሥጋ ጐይታና ኢየሱስ ክርስቶስ ምስ ኣካላዊ ቃል ብምውሕሃድ ብጥንታዊ ኣካል ኣዳም ተፈጥረ ይብል ። (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቒ) በቲ ጊዜ እቲ ሥጋ ምስ ቃል ተወሃሃደ ሓደ ኣካል ሓደ ባሕርይ ኾነ “ወረሰዮ ምስሌሁ አሐደ ህላዌ ወአሕደ ሥምረተ ወአሐደ አካለ ዘእግዚአብሔር ቃል’’ (ቅዱስ ጎርርዮስ ዘኑሲሰ)። ስለ’ዚ መለኮት ምስ ሥጋ ብምውህሃድ ሰብ ኣምላኽ ኮነ ፤ ሥጋ ምስ መለኮት ብምውህሃድ ከኣ ኣምላኽ ሰብ ኮነ፤ ረቂቕ ዝነበረ መለኮት ምስ ሥጋ ብምውህሃድ ግዙፍ ዝድህሰስ ኾነ፤ ግዙፍ ሥጋ ምስ መለኮት ብምውህሃድ ረቂቕ ኮነ ፤ ወሰን ዘይነብሮ መለኮት ብሥጋ ውሱን ኮነ፤ ውሱን ዝነበረ ሥጋ ብመለኮት ዘይውሱን ኣብ ኵሉ ምሉእ ኮነ ፡ ወልድ አብ ብመለኮቱ ወልደ ማርያም ብትስብእቱ፥፡ ክልተ ልደት ብምውህሃድ ኸበረ፤ ሥጋ ምስ መለኮት ብምውህሃድ ባሕርያዊ ወዲ እግዚአብሔር ኮነ። “ወይደልወነ ንእመን ከም ቦቱ ለወልደ እግዚአብሔር ክልኤቱ ልደታት ቀዳሜ ልደት እምእግዚአብሔር አብ ፤ እምቅድመ ኵሉ መዋዕል ፤ ወዳግም ልደት እምእግዝእትነ ድንግል ማርያም በድኃሪ መዋዕል”፡ ንወዲ እግዚአብሔር ክልተ ልደት ከም ዘለዎ ክንኣምን ይግበኣና እዩ፤ ቀዳማይ ልደት ቅድሚ ዓለም ወዲ እግዚአብሔር አብ ምዃኑ፤ ካልኣይ ልደት ከኣ ዳሕራይ ጊዜ ካብ እግዚእትነ ማርያም ምውላዱ ከም ዝበለ። (ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ) “ወለእመኒ ቃል ሥጋ ኮነ ፤ እመቦ ዘሰገደ ለቃል ናሁ ሰገደ ለሥጋ፤ ወዘሂ ሰገደ ለሥጋ ሰገደ ለእግዚአብሔር ቃል፤ ወከማሁ መላእክትኒ ይትለኣኩ ለአርአያ ሥጋ፤ ወየአምሩ ከመ እግዚኦሙ ውእቱ ወይሰግዱ ሎቱ፡”። ቃል ምስ ሥጋ ብምውህሃዱ ንቓል ዝሰገደ እነሆ ንሥጋ ሰገደ’ውን ንእግዚአብሔር ቃል ሰገደ፤ መላኣኽቲ’ውን ከምኡ ንብሥጋ ዝተገልጸ ይለኣኹ፤ ጐይትኦም ምዃኑ ፈሊጦም ከኣ ይሰግድሉ ይብል። (ሃይማኖተ ኣበው) “ወሶቦሂ ሰቀሉ ኣይሁድ ሥጋሁ ፤ ሰቀሉ ኪያሁ፤ ወአልቦ እም ውስተ መጻሕፍት ፍልጠት ማእከለ ቃል ወሥጋሁ አላ አሐዱ ህላዌ ፤ ወአሐዱ ገጽ ፤ ወአሐዱ ግብር ውእቱ ፤ ኵለንታሁ አምላክ ወውእቱ ኵለንታሁ ብእሲ ወአሐዱ ግብር ዘመለኮት ወዘትስብእት ኅብሩ”። ኣይሁድ ንሥጋኡ ምስ ሰቐሉ ፤ ንቓል’ውን ሰቀሉ፤ ብመጻሕፍቲ ወገን ኣብ ማእከል ቃልን ሥጋኡን ፍልልይ የለን፤ እንታይ ደኣ ሓደ ባሕርይ ፤ ሓደ ግብርን፤ ብዅለንተናኡ ፍጹም ኣምላኽ ፍጹም ሰብን እዩ ይብል። (ሃይማኖተ ኣበው) ቃል ሥጋ ኮነ ብኸመይ ነገር ወላዲተ ኣምላኽ ተባሂላ፤ ሥጋ ድማ ቃል ከይኮነ ብኸመይ ነገር ናብ ባሕርያዊ ወዱ ኾነ፤ ንመላእኽቲ’ውን ጎይትኦም ንምንታይ ተባህለ፡ ወላዲተ ኣምላኽ ኢልና እናምን እምበር ብኸም’ዚ ዝበለ ተዋህዶ እዩ። ኣምላኽ ሰብ ከይኮነ ወዲ ኣዳም ድኂኑ ክብሃል ኣይከኣልን፤ ሰብ’ውን ኣምላኽ ከይኮነ ምእንቲ ደቂ ኣዳም ሓሚሙ ፤ ተሰቒሉ ሞይቱ ክብሃል ኣይከኣልን፤ ዓርቢ መዓልቲ ተሰቒሉ መሥዋዕቲ ዝኾነ ናይ ጐይታና ሥጋን ደምን እዩ፤ ማለት ናይ ኣምላኽ ሥጋን ደምን እንተ ዘይኮይኑ ናይ መን ጻድቕ ፤ ወይ ሰማዕት ሥጋን ደምን እዩ መሥዋዕት ኮይኑ ንዘልዓለም ክሳብ ዕለተ ምጽኣት ወሀቢ ሕይወትን ድኅነትን ኮይኑ ዝነብር። ብኸም’ዚ ዝበለ ናይ ተዋህዶ ምሥጢር ናይ እሳት ብሐይን ኣካልን ተለዊጡ ኃፂን ከይኮነ ፤ ከምኡ ኸኣ ናይ ብርሃን ባሕርይ ተለዊጡ ዕንቍ ከይኮነ፤ በተዕቅቦ ሓደ ኣካል ሓደ ባሕርይ ከም ዝኸውን ከምኡ ድማ መለኮት ምስ ትስብእት፤ ትስብእት ምስ መለኮት ብምውህሃድ ፤ ካብ ክልተ ኣካል ፤ ሓደ ኣካል ፤ ካብ ክልተ ባሕርይ ሓደ ባሕርይ ኮነ። “ወይትሜሰል ወልድ በዕንቈ ባሕርይ እንተ ይእቲ በአማን ኵለንታሃ ብርሃን ፣ ወይትሜሰል ሥጋሁ በሥጋሃ ፤ ወብርሃና በመለኮቱ። ባስልዮስ”፡ በአይ ኣምሳል ይትሜሰል መለኮት በትስብእት ፤ ይቤ ይመስል እሳተ በሕፂን ብንያሚ” ወልድ በታ ብዅለትናኣ ብርሃን ዝዀነት ዕንቈ ባሕርይ ይምሰል ፤ ሥጋኡ ብሥጋኡ ብርሃና ብመለኮቱ ይምሰል ይብል፡ (ቅዱስ ባስልዩስ ዘኣንጾኪያ) ሓፂን ጸሊም ከሎ ምስ እሳት ብምውህሃዱ ይበርህ ደኣ እምበር ኣይጽልምን፤ እቲ ሓፂን ዝፍለ እንተ ኮነ ፤ መለኮት ግን ካብ ትስብእት ተፈልዩ ኣይብሃልን ይብል። “ናሁ ድንግል ትፅንስ ወትወልድ ወልደ” እንሆ ድንግል ክትፅንስ ወዲ’ውን ክትወልድ እያ።(ኢሳ።7፡14) ጐይታና ኢየሱስ ክርስቶስ ካብ እግዚእትነ ማርያም ብኅቱም ድንግልና ምውላዱ ብኸመይ እዩ፧ ንዝብል ንምሳሌ ካብ ዐይኒ ብርሃን ካብ ግንባር ድማ ረሓጽ ብኅቱሙ ከም ዝርከብ፤ ከምኡ ኸኣ ጎይታና ኢየሱስ ክርስቶስ ማኅተመ ድንግልናኣ ከይፈትሐ ብኅቱም ድንግልና ተወልደ። “ተወልደ እም ድንግል እንዘ ኅቱም ድንግልናሃ፤ ከመ ልደተ ንጻሬ አዕይንት፤ ወከመ ልደተ ሐፍ እም ገጽ፤ ወከመ ልደተ መልክዕ እመጽሔት” ከም ዝበለ። (ቅዱስ ያዕቆብ ዘእልበረዲ) ከምኡ ድማ ናይ ፀሐይ ነጸብራቕ ምስ ማይ ተዋሀሂዱ ዕንቈ ባሐርይ ከም ዝወልድ፤ ኣካላዊ ቃል ክርስቶስ ከኣ ምስ ደም ድንግልናኣ ተዋሃሂዱ ብዘይ ዘርኢ ተፀኒሱ ብኅቱም ድንግልናኣ ተወልደ፡ “ወዝኩ ዕንቈ ባሕርይ አኮ በተራክቦ ዘይፀነስ ወይትወልድ፤ ባሕቱ ይትወልድ በተዋሕዶተ መብረቅ ወማይ፡ ወከማሁ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ተፅንሰ ዘእንበለ ትድምርተ ሥጋ፤ ወኮነ እመንፈስ ቅዱስ ተፅንሶቱ ለእግዚአብሔር ቃል ሥጋ ኮነ” ከም ዝበለ። (ቅዱስ ኤፍሬም.ኣፍ.በረከት) ካብ አብን መንፈስ ቅዱስን ሓድነት ከይተፈለየ፤ ኣብ ኵሉ ምሉእ ከሎ ሥጋ ምዃኑ ከመይ እዩ፧ እንተ ተባሀለ ናይ ዐይኒ ብርሃን ካብ ክበብ ዓይኑ ከይተፈለየ ፤ ምስ ብርሃነ ፅሐይ ተዋሃሂዱ ምሉእ ኰይኑ ከም ዝርኢ፤ ከምኡ ድማ ጐይታና ብመለኮታዊ ባህርዩ ኣብ ኵሉ ምሉእ ከሎ ኽምርምር ብዘይከኣል ምሥጢር ከም ቅጽበት ዓይኒ ሰብ ኮነ ፤ ዘይፍለን ዘይምርመርን ዘይፍለጥን ተዋህዶ ኮነ። “ወመጽአ እንዘ ኢይትፈልጥ እምሕፅነ አቡሁ፤ ሰማያትኒ ወምድር ምሉአን እምኔሁ”። ካብ ናይ ባሕርይ ኣቡኡ ካብ አብ፤ ካብ ናይ ባሕርይ ሕይወቱ ካብ መንፈስ ቅዱስ ሓድነት ከይተፈለ ፤ ሰብ ኮነ ፤ ሰብ ድኅሪ ምዃኑ ድማ ሰማይን ምድርን ብእኡ ምሉኣት እዮም ማለት ኣብኣቶም ብምልኣት ህልዊ እዩ። ( ቅዱስ ዮሓንስ. ዘኣንጾኪያ) “አንተ ውእቱ አምላክ ዘበአማን ፤ ወአንተ ሰብእ ፍጹም ዝእንበለ ሕፅት፤ ወአንተ ውእቱ ዘትነብር ዲበ መንበረ ስብሐቲከ ፤ ወአንተ ዲበ ዕፀ መስቀል” ሓቀኛ ባሕርያዊ ኣምላኽ ንስኻ ኢኻ፤ (ሕፀፅ) ጉድለት ዘይብልካ’ውን ፍጹም ሰብ ኢኻ፡ ኣብ ልዕሊ መስቀል ምእንቲ ኃጢኣትና ዝተሰቐል ካ’ውን ንስኻ ኢኻ። ኣብ ናይ ጐይትነትካ መንበር እትነብር’ውን ንስኻ ኢኻ። (ቅዱስ ዮሓንስ ኣፈወርቒ ብድርሳነ ቶማስ) ካብ ብዝኅ ብውኅዱ ምሥጢረ ሥጋዌ እዚ እዩ፡
አጋር ሀገሮች የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ የኢኮኖሚ ፖሊሲን የሚንቅፉ ቢሆንም ፕሬዚዳንቱ በመጪው የቡድን ሰባት ጉባዔ ላይ በአቋማቸው እንደሚፀኑ ከዋና የኢኮኖሚ አማካሪዎቻቸው አንዱ ትላንት ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። ዋሺንግተን ዲሲ — አጋር ሀገሮች የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ የኢኮኖሚ ፖሊሲን የሚንቅፉ ቢሆንም ፕሬዚዳንቱ በመጪው የቡድን ሰባት ጉባዔ ላይ በአቋማቸው እንደሚፀኑ ከዋና የኢኮኖሚ አማካሪዎቻቸው አንዱ ትላንት ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። “ፕሬዚዳንቱ እነዚህ ከባድ ጉዳዮች አያስጨቋቸውም። ምን ጊዜም ቢሆን በዩናይትድ ስቴትስና በቡድን ሰባት አባል ሀገሮች መካከል ስለሆነ ነገር ውጥረት አለና” ሲሉ የብሄራዊ ኢኮኖሚ ካውንስል ሥራ አስኪያጅ ላሪ ኩድሎው አስገንዝበዋል። ኩድሎው በዋይት ኃውስ ቤተመንግሥት በተደረገው ጋዜጣዊ ጉባዔ ይህን ያሉት የቡድን ሰባት ጉባዔን የሚያስተናግዱት የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ጃስቲን ትሩዶና የጀርመን ቻንስለር አንጌላ መርከል ነገና ቅዳሜ በማካሄደው ጉባዔ ላይ ከባድ ውይይት እንደሚደረግ ከገለፁ በኋላ ነው።
ድርጅቱ ጥሪውን ያቀረበው ድርጊቱን የፈጸሙት በክልሉ የሚገኙና ራሳቸውን የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ብለው የሚጠሩ፣ መንግስት ደግሞ “ሸኔ” ብሎ የሚገልጻቸው ታጣቂዎች ናቸው ሲሉ የተናገሩትን በአካባቢው የሚገኙ የዓይን እማኞችን ጠቅሶ ነው። ሁከት እየተባባሰ በመጣበት የምዕራብ ወለጋ አካባቢ ሰኔ አስራ አንድ ቀን በአማራ ተወላጆች ላይ ለተፈጸመው ጭፍጨፋ መንግስት “ሸኔ” ብሎ የሚጠራውና ራሱን ደግሞ የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ብሎ የሚገልጸውን ቡድን ተጠያቂ ሲያደርግ፥ ታጣቂው በበኩሉ ከመንግስት ጋር ያበሩ ሚሊሺያዎችን ተጠያቂ ያደርጋል። አምነስቲ ኢንተርናሽናል ያነጋገራቸው ዘጠኝ የዓይን እማኞች እንደሚሉት የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት በቶሌ ቀበሌ ላይ ጥቃት መሰንዘር የጀመረው ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ ነበር። ገና የመጀመሪያው ጥይት እንደተተኮሰ ነዋሪዎቹ ለአካባቢው ባለስልጣናት ቢያሳውቁም፣ የመንግስት ሃይሎች የደረሱት ጥቃቱ ከተጠናቀቀ ከሰዓታት በኋላ መሆኑን እማኞቹ ለአምነስቲ ተናግረዋል። አጥቂዎቹ የአማራ ተወላጆችን በጅምላ እንደጨፈጨፉ፣ ንብረት እንደዘረፋና ቤቶችን እንዳቃጠሉ ተናግረዋል። የሰብዓዊ መብት ድርጅቱ ይህንን ድርጊት በሳተላይት ምስሎች ማረጋገጡን ገልጿል። ምስሎቹ እሳት በአካባቢው እንደነበር ያሳያሉ ብሏል አምነስቲ። ዲፕሮሰ ሙቼና የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ ሃላፊ ሲሆኑ፣ “ይህ በቶሌ በተጠርጣሪው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት የተፈጸመው ሰቅጣጭ ግድያ ፈጻሚዎቹ ለሰው ህይወት ግድ እንደሌላቸው ማሳያ ነው። ይህ የሴቶችንንና የህጻናትን ህይወት የቀጠፈ ጭቃኔ የተሞላበት ጭፍጨፋ በገለልተኛ ወገን በሚገባ መመርመር አለበት” ብለዋል። የአምነስቲ መግለጫ የወጣው ባለፈው ወር የተመድ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር ምሼል ባቼሌት የኢትዮጵያ መንግስት በቶሌ የተፈጸመውን ግድያ በተመለከተ “ፈጣን፣ ገለልተኛና ጥልቀት ያለው” ምርመራ እንዲያደርግ ጥሪ ማድረጋቸውን ተከትሎ ነው። የ64 ዓመቱ ሁሴን ለአምነስቲ እንደተናገሩት 22 ልጆችና የልጅ ልጃቸውን በጥቃቱ ተነጥቀዋል። “በአንድ ቦታ ብቻ 42 ሰዎች ገደሉ። ከነዚህ ውስጥ አንድ ወንድ አዋቂ ብቻ ነው የነበረው፣ ሌሎቹ ሴቶችና ህጻናት ናቸው” ናቸው ብለዋል ሁሴን። ሌላኛው የዓይን እማኝ ደግሞ፣ “የአንድ ጎረቤቴን ቤት፣ ቤተሰቡ ልጆቹና የልጅ ልጆቹ ውስጡ እያሉ በእሳት አጋይተውታል። አንዷ የሰባት ወር እርጉዝ ስትሆን ከሁለት ልጆቿ ጋር ነበረች። ከሰል እስኪሆኑ ስለተቃጠሉ እዛው ግቢ ውስጥ ቀበርናቸው” ሲሉ ለአምነስቲ ተናግረዋል። የዓይን እማኞቹን ከበቀል ለመከላከል አምነስቲ እውነተኛ ስማቸውን በሚስጥር ይዟል። የሟቾቹን ቁጥር በተመለከተ እስከአሁን ኦፊሴላዊ ቁጥር ባይቀመጥም፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ቃል አቀባይ ቢልለሌ ስዩም ባለፈው ወር በሰጡት መግለጫ 338 ሰለባዎች መለየታቸውን ተናግረዋል። አንድ የአካባቢው ባለስልጣን ቢያንስ 450 ሰዎች መገደላቸውን ለአምነስቲ ተናግረዋል። የዓይን እማኞቹ እንዳሉት አጥቂዎቹ በለበሱት መለዮ፣ በተሰሩት “ለየት ያለ ረጅም ሹሩባ” እና በሚጠቀሙት የኦሮምኛ ቋንቋ መሰረት የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት አባል መሆናቸውን መለየት እንደቻሉ ተናግረዋል። አጥቂዎቹ በተጨማሪም ቤቶችን ሲያቃጥሉ፥ ከብቶችን፣ ግንዘብና ሌሎች ንብረቶችን ከመንደርተኛው ዘርፈዋል። ባለስልጣናት “መንገድ በመዘጋቱ መድረስ አልቻልንም” ማለታቸውን የአምነስቲ መግለጫ ጠቅሷል። ባለስልጣናት በተጨማሪም በአማራ ተወላጆች ላይ ለተፈጸሙት በርካታ ጥቃቶች “ሸኔ” ብለው የሚጠሩት የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊትን ተጠያቂ ያደርጋሉ። ከ2010 ጀምሮ ከፌዴራል መንግስቱ ጋር ሲዋጋ የሰነበተው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት፥ በሰሜን ኢትዮጵያ ከመንግስትና ሌሎች ሃይሎች ጋር ጦርነት ውስጥ ከነበረው ህወሃት ጋር ባለፈው ዓመት የትግል አጋርነት በማወጁ ትኩረት አግኝቷል።
ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲና የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) በሀገሪቱ ፍትህና ዴሞክራሲ እንዲሰፍን በጥምረት ለመስራት ያስችላል ያሉትን የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል። ትብብሩ በቀጣይ በአገሪቱ እንዲፈጠርና እንዲጎለብት የሚፈለገው የአገራዊ በጎ ሀይሎች ጥምረት መሰረት እንዲሆን ያለመ መሆኑም ተገልጿል። በመጪው አገራዊ ምርጫ የመራጮች የጋራ ፍላጎትና ራዕይ ለማሳካት ፓርቲዎቹ በጋራ ለመስራት በማሰብ የተመሰረ የፖለቲካ ትብብር መሆኑንም ነው ፓርቲዎቹ የገለፁት። በአገሪቱም ሆነ በዜጎች ላይ የተጋረጡ ፈተናዎች እንዳሉ የገለጹት ፓርቲዎቹ፣ ይህንን ከመቼውም ጊዜ በላይ በትብብር ለመታገል በቁርጠኝነት እንደሚሰሩና ትብብሩ ከምርጫው በኋላም እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። (ኢቢሲ) የባልደራስ መሪና በአሁኑ ጊዜ በእሥር ላይ የሚገኙት አቶ እስክንድር ነጋ ከአማራ ድርጅቶች በተለይ ከአብን ጋር ምሥጢራዊ ግንኙነት አላቸው እየተባ ሲነገር ቆይቷል። እርሳቸው ግን በጎጥ እንደማያምኑ የተናገሩ ቢሆንም በሕብረብሔራዊነት ነው የተደራጀሁት ከሚለው መአህድ ጋር ይሠሩ እንደነበር ራሳቸው መናገራቸው ይታወሳል። የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ እና የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ ትብብርን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ የሀገራችን ህዝብ ለዘመናት በተጫኑበት ኢዲሞክራሲያዊና አምባገነን አገዛዞች የተነሳ፣ በነጻነት እጦት፣በስቃይ እና በመከራ ኑሮውን እንዲገፋ ተደርጓል። ጭቆናን አስወግዶ የሚፈልገውን ፍትህ እና እኩልነት እውን ለማድረግ ከፍትኛ ዋጋ መክፈሉም እሙን ነው። ይሁንና የሃገራችን የለውጥ ፍላጎት እና እንቅስቃሴ ጅማሮው ሳይሳካ፣ ለቀጣዩ ዴሞክራሲያዊ ትግል ተስፋ ሊሆን የሚችል መሰረታዊ የትርክትና የመዋቅር ክለሳ እንኳ ሳይደረግ አምባገነንነትና ዘረኝነት የእጅ ለውጥ ብቻ እያደረጉ የሚፈራረቁባት ሆናለች። በዚህ ሁሉ ፈተና ውስጥ ያለፈው ህዝባችን አሁንም ዲሞክራሲን፣ እኩልነትንና ዘላቂ ሰላምን በመሻት ለነጻነት የሚያደርገውን ትግል አጠንክሮ እንደቀጠለ ይገኛል። የዚህ አይነት መልክና ይዘት ተላብሶ የተደራጀው የተፎካካሪ ሀይል ለሰርጎ ገቦች የተጋለጠ፣ በተፈጥሮው ደካማና ተሰባሪ ከመሆኑም በላይ የአምባገነኑን ስርአት ራዕይ አቀንቃኝ እስከመሆን ደርሶ እንደነበር ይታወሳል። በተጨማሪ የተቃውሞው ጎራ እርስ በርሱ በፍረጃና በሴራ መጠላለፍ ምክንያት በቁርሾ እንዲሞላ በማድረግ የጋራ ሀገራዊ ስምሪት መውሰድ እንዳይችል አድርጎት ቆይቷል። በዚህ ሂደት ውስጥ አምባገነኖችን በጋራ መታገል ጥረት ከማድረግ ወርደው በመናኛ ፍላጎቶችና በጥቃቅን ልዩነቶች ዙሪያ ታጥረው ሲሻኮቱ በመካከል የባከነው ጊዜ እና የሰው ህይወት የሚያስቆጭ ነው። የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) ሀገራችንን ለድሜ ልክ ዝቅታ የዳረጋት የጥላቻ ትርክት፣ ትርክቱን መሰረት አድርገው የተደነገጉ ህግጋትና የተዘረጉ መዋቅሮች ተከልሰው መላ ኢትዬጵያውያን በእኩልነት፣ በወንድማማችነት፣ በፍትህና በሰላም የሚተዳደሩነት ዘላቂ ስርአት በማስፈን በተለምዶ “መንታ ቅኝት” ያለው የትግል እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል። የአብን ስትራቴጂክ ግብ መላውን ኢትዬጵያዊ የፍትሀዊ አማካኝ ተጠቃሚ በማድረግ ሁሉንም አሸናፊ የሚያደርግ የፖለቲካ ማእቀፍ እንዲፈጠር ሲሆን የድርሻውን ለማበርከት አበክሮ እየሰራ ያለ ንቅናቄ ነው። ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ /ባልደራስ/ ደግሞ የኢትዬጵያዊ ህብር አይነተኛ መገለጫ የሆነችውን የአድስ አበባ ከተማ ህዝብ ከከፋፋይና ከጥላቻ ፖለቲካ ነፃ ለማድረግና ህዝቡ ራሱን በራሱ የማስተዳደር መብቱ እንዲረጋገጥ ለማስቻል በሚል የተደራጀ ስለመሆኑ በሰፊው የሚታወቅ ነው። አዲስ አበባ ከተማ የኗሪዎቿ መሆኗን ለማረጋገጥ የሚያደርጉት የጋራ ትግል መነሻ ዴሞክራሲን፣ ነፃነትን፣ ፍትህንና እኩልነትን በማስፈን ላይ የተመሰረተ ሲሆን አንዳች ቅቡልነት ያለው መርህ ወይም ምክንያት ማጣቀስ የማይችሉ ሀይሎች ከተማዋ የአንድ ንጥል ብሄር ንብረት መሆኗን በይፋ በመግለፅ የማታገያ አጀንዳ በማድረግ ህዝቡ በነሱ ፍቃድና ይሁንታ መኖር እንዳለበት አድርገው ያወጁት ያልተገራ ፍላጎት የጋረጠበትን የህልውና ስጋት መቀረፍ እንዳለበት አብንና ባልደራስ የጋራ ፖለቲካዊ አቋም ወሰደዋል። የሀገራችን ኢትዬጵያ መድናና የመላ ህዝቧ ሰላማዊ መኖሪያ ሆና ዘመናትን የተሻገረችው አዲስ አበባ መደበኛና ነባር ምልከታ ሊቸራት ሲገባ ከልቦለድ የመነጨ የዘረኞች “የልዩ ጥቅም”ቀንበር ጊዜ በረዘመ ቁጥር የህግና የፖለቲካ ቋጠሮው እየጠበቀ መምጣቱና ይዘቱ “በኦሮሚያ ክልል አስተዳደርና በአዲስ አበባ መስተዳደር ስምምነት” እንደሚወሰን በተሻሻለው ቻርተር መደንገጉ ከተማዋንና ህዝቧን ከአንድ ወገን በተሰባሰበ የፖለቲካ ሀይል ይሁንታ፣ ፍፁም ቁጥጥርና ጥበቃ ስር ለማዋል የተወሰነ መሆኑን ያሳያል። አብንና ባልደራስ ይሄን አምባገነናዊ፣ ፍትህ አልቦ፣ ዘረኛ፣ አግላይና በመጨረሻም የግጭትና የብሄራዊ ደህንነት አደጋ የሆነ አፍራሽ እንቅስቃሴ በጋራ ተሰልፈው ለመታገል ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ትብብሩ በቀጣይ እንዲፈጠርና እንዲጎለብት ለምንፈልገው የሀገራዊ በጎ ሀይሎች ጥምረት እርሾ ሆኖ እንዲያገለግል የታለመ ነው። አስቻይነት የሌለውና በህግ የተደነገገው የጊዜ ገደብ ጉዳይ በነባራዊ ተግዳሮቶች ምክንያት የተፈጠረ መሆኑን በማረጋገጥ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ተመሳሳይ አንድምታ ያላቸውን ጉዳዬች ባስተናገደበት ሁኔታ ትብብሩ ለህጋዊ እውቅና ሲቀርብ በመፍቀድና በመመዝገብ እንዲያፀድቀው የሚቀርብ ይሆናል። በዚህ መነሻነት ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን እውን ለማድረግ ለሚደረገው ትግል በመጪው ሃገራዊ ምርጫ የመራጮችን የጋራ ፍላጎትና ራዕይ ለማሳካት የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ/አብን/ እና ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ /ባልደራስ/ በጋራ የምንሰራበት የፖለቲካ ትብብር ፈጥረን ለመስራት መወሰናችንን ለመላው ሀገር ወዳድ ኢትዬጵያውያን፣ ለመላው አማራ ህዝብና ለአድስ አበባ ህዝብ ስናበስር በታላቅ ደስታ ነው። ሌሎች ፓርቲዎችን ጨምሮ በሁለቱ ፓርቲ አመራሮች መሃከል ለወራት ሲካሄድ የነበረው ረጂምና አድካሚ ድርድር ፍሬ አፍርቶ መጪውን ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ የአብን እና የባልደራስ ትብብር አሸናፊ ሆኖ መውጣት የሚያስችላቸውን የጋራ ስልቶች ቀይሰው በይፋ መንቀሳቀስ ጀምረዋል። የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ/አብን/ እና ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ/ባልደራስ/ አጠቃላይ የኢትዬጵያ ህዝብ፣ የአማራ ህዝብ እና የአዲስ አበባ ከተማ ኗሪ ህዝብ በበደል ውስጥ አምጠው የወለዷቸው የቁርጥ ቀን ልጆቹ እንደመሆናቸው መጠን በተባባረ ክንድ በህዝባችን ላይ የተጫነውን የመከራ ቀንበር እንዲወርድ ከመቸውም ግዜ በላይ በጋራ ትብብር ለመታገል በቁርጠኝነት ተሰልፈዋል፡፡ አብን በጽንፈኞች የተሳሳተ ትርክት መነሻነት በአማራ ህዝብ ላይ በተከታታይ የሚደርሰው ግፍ ድምጽ በመሆን በመጀመሪያው ረድፍ ሆኖ ትግሉን እየመራ ይገኛል። አብን የሀገራችን ኢትዬጵያን ደህንነት ለማረጋገጥና ህልውናዋን ለማስቀጠል አንድ ወሳኝ አምድ የሆነው የአማራ ህዝብ በልዩ ሁኔታ ተፈርጆ የሚጠቃበትን የፅንፈኞች ስሁት ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ለመግታት የሚያስችል ልዩ ማዕቀፍ ሆኖ የተደራጀ ሲሆን ታሪካዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ስሪቱ በኢትዬጵያዊነት፣ ምልከታውም በወንድማማችነት፣ በፍትህና በዴሞክራሲ የተቃኘ ስለመሆኑ ውሎ ያደረ ጉዳይ ነው። ከላይ በሰፊው እንደተመላከተው ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ በአዲስ አበባ ከተማ ህዝብ ላይ የተጋረጡ የህልውና አደጋዎችን ለመከላከል፣ የከተማዋ ህዝብም ራሱ በዴሞክራሲያዊ መንገድ በመረጣቸው እንደራሴዎቹ የመተዳደር መብቱን ለማስከበር ባሚያደርገው እልህ አስጨራሽ ትግል ውስጥ በብቃትና በንቃት በነሳተፍ አያሌ መስዋዕትነቶችን በመክፈል የቀጠለ መሆኑን ራሱ ህዝቡ በተግባር ኖሮ ያረጋገጠው ሀቅ ነው። ከላይ በተጠቀሱት መሰረታዊ ሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ ግቦች ዙሪያ ሁለቱ ድርጅቶች በፅኑ የሚጋሯቸውን አቋሞች መሰረት በማድረግ ቀጣይ ለሚደረገው ጠንካራና የተቀናጀ የህዝብ ትግል ወሳኝ የማታገያ አጀንዳ እንዲሆኑ ስምምነት ላይ ደርሰዋል። በሃገር አቀፍ ደረጃ ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው ምርጫ መላው የሀገራችን ህዝብ፣ በተለይም የአማራ ህዝብና የአዲስ አበባ ህዝብ የተደቀነባቸውን የህልውና አደጋ በትብብር ከመታገል ውጭ ሌላ ተጨባጭ የመፍትሄ አማራጭ እንደሌለ መተማመን ላይ ደርሰዋል። ከዚህ ቀደም በጋራ አብረውን ለመስራት ንግግር ጀምረው ሳለ በተለያዩ ምክንያቶች በትብብሩ ለመዝለቅ ያልቻሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሁንም ጊዜው አለመርፈዱን ተገንዝበው በጎ ፍላጎት ካሳዩን ከግማሽ መንገድ ባላይ ተጉዘን ለመቀበል ዝግጁ መሆናችንን በዚህ አጋጣሚ ለማረጋገጥ እንወዳለን። የፈጠርነው ትብብር አርአያ መሆን የሚችልና ከትላንት ለተሻለ አዲስ የፖለቲካ ባህል ማሳያ ፈር ቀዳጅ እንደመሆኑ ከምርጫ በኃላም ትብብሩ ጎልብቶ፤ የሀገራችንን ህዝብ ለዘመናት የቆየ የፍትህ ትግል ዳር ለማድረስ እንዲሁም የመላው ኢትዬጵያዊ የሆነችውን የአዲስ አበባ ከተማን ዓለም አቀፍነት የሚመጥን አመራር ለመስጠት ለመፍጠር ከወዲሁ አብረን መቆም ጀምረናል። አብንና ባልደራስ የአዲስ አበባ ህዝብ ራስን በራስ የማስተዳደር ዴሞክራሲያዊ መብት አክብረው ከሚቀበሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ትብብር በመፍጠር የከተማዋ ህዝብ በፌደራል መንግስቱ ውስጥ ተወክሎ እንደሁሉም ህዝብ ጥቅሙን ለማስጠበቅ የሚያደርገውን ትግል የማሳለጥ ሚና እንደሚኖረው ለማሳወቅ እንወዳለን። አዲስ አበባ በሁሉም ኢትዮጵያውያን ጥረት የተገነባች፣የአፍሪካ የዲፕሎማሲ ዋና ከተማ ብትሆንም፣ ከቅርብ ግዜ ወዲህ የተነሱ ተረኞች ከተማይቷን በልዩ ጥቅም ስም የአንድ ቋንቋ ተናጋሪ ብቸኛ ንብረት ለማድረግ የሚደረገው እንቅስቃሴ በጋራ አጥብቀን እናወግዛለን። በከተማይቱ እና ነዋሪዎቿ ላይ የተደቀነውን ይህ አደጋ ለመከላከል ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ/ ባልደራስ/ በዋነኛነት እያካሄደ ያለውን ትግል አብን የሚያድንቅ እና በሙሉ ልብ ከጎኑ እንደሚሰለፍ ቃል ይገባል። በአንጻሩም ባልደራስ ፓርቲ በጽንፈኞች ሴራ ኢላማ እንዲሆን በተደረገው የአማራ ህዝብ ላይ የሚደርሰውን ግፍ እና በደል ለማስቀረት በቁርጠኝነት አብን ለሚያደርገው ትግል ክብርና እውቅና እንደሚሰጥ ለመግለፅ እንወዳለን፡፡ ከላይ ለመግለጽ እንደተሞከረው ስምምነታችን የተበላሸውን የሀገራችንን ፖለቲካ ባሕል በማስተካከል፣ በውይይትና በሰጥቶ መቀበል መርህ ለሕዝብ ጥቅም ሲባል አብሮ መቆም እንደሚገባ ከማሳየት ባሻገር፣ ሌሎች ለተመሳሳይ አላማ ያነገቡ ፓርቲዎችም ይህን ፈለግ ተከትለው የትብብሩ አካል እንዲሆኑ ፅኑ ፍላጎት አለን። በመጨረሻም በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች ጽንፈኛ ሃይሎች በሚፈጽሟቸው የሽብር ድርጊቶች ምክንያት እየደረሰ ያለውን ሞት፣የአካል ጉዳት፣መፈናቀል እና የንብረት ውድመት ለማስቆም በየእርከኑ ያሉ የፌደራል እና የክልል መንግስታት ሃላፊዎች ተግተው እንዲሰሩ ጥሪ እናቀርባለን። በተለይ ችግሩ ተባብሶ በሚገኝባቸው የኦሮሚያ፣ የቤንሻንጉል እና አንዳንድ የደቡብ ክልል አካባቢዎች የሚገኙ የመንግስት አስተዳደርና የፀጥታ አካላት ችግሩን የሚመጥን ሀላፊነት በመውሰድ ንፁሀንን ከጥቃት እንዲከላከሉና ወንጀለኞችን ለህግ እንዲያቅርቡ በአፅንኦት እንጠይቃለን። መሰረተ ቢስ በሆነ ክስ ተወንጅለው ለእስር የተዳረጉትንና የመምረጥና መመረጥ መብታቸውን የተነፈጉ የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ አመራሮች በአስቸኳይ እንዲፈቱ እናሳስባለን። ትህነግ በለኮሰው ጦርነት በትግራይ ክልል ህግ ለማስከበር እየተካሄደ ባለው ዘመቻ የንጹሃን ዜጎቻችንን ደህንነት እና የሰብዓዊ መብት እንዳይጣስ ልዩ ትኩረት እንዲደረግና የሰብአዊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ለማሳሰብ እንወዳለን።
ናይ ዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ ኣውሮፓ ካብ ናይ ናዚ ወራር ነፃ ንምውፃእ ኣሽሓት ሓይልታት ጥምረት ኣብ ወሰን ማይ ኖርማንዲ ብውግእ ዝተሰውእሉን D-Day ብዝብል ስም ኣብ ዝፍለጥን ዝኽሪ ኵናት መበል 70 ዓመት ተሳቲፎም። ሎማዕንቲ ዓርቢ 29 ግንቦት 2006 ዓ/ም ወይ 6 ሰነ 2014 ሰማያት ብጡሽ ተሸፊኑ ነፈርቲ ውግእ ኣብ ሰማይ እናተገለባበጣ መሬት የንቅጥቅጣ።እንተኾነ እቲ ናይ ሎማዕንቲ ጡሽ ንኽብሪ እቶም ስውኣት ዝተተኮሱ 21 መዳፍዕ ዝፈጠርዎ እዩ።እተን ዝበራ ዘለዋ ነፈርቲ እውን F-15 ዝዓይነተን ነፈርቲ ውግእ ኮይነን ንዝኽሪ መስዋእቲ ኣሽሓት ወታደራት ዩናይትድ ስቴትስን ሓይልታት ጥምረትን እየን ምርኢት ዘርእያ ዘለዋ። ፕሬዝዳንት ኦባማ ብርክት ዝበሉ ካብ ናይ ኵናት D-Day ዝተረፉ ወታደራት ነበርን ካልኦትን ኣብዝተሳተፉሉ ስነስርዓት ኣብ ዘስዕዎ መደረ ድፋዕ ዴሞክራሲ ክብሉ ፀዊዖምዎ።ኣሜሪካ ዝወነነቶ ሓርነት፣ማዕርነት፣ነፃነትን ተፈጥራዊ ክብሪ ኩሎም ደቂ ሰባትን ኣብዚ ወሰን ባሕሪ ብደም ተፃሒፉ፤ንዘልኣለም እውን ክነብር እዩ ኢሎም። ብዛዕባ ሰላም ንኽንፈልጥ ምእንታ እዞም ወታደራት እዚኦም ኵናት ተዋጎኦም ዝበሉ ንሶም ብምስዓብ ‘’ንሕና ብነፃነት ንኽንነብርን ብድሕሪኦም ክንዋግእ ከምዘይብልና ተስፋ ብምግባርን ንሳቶም ተዋጊኦም።ክብርን ምስጋናን ይብፅሓዮም ‘’ኢሎም። ልዕሊ 160 ሽሕ ሓይልታት ጥምረት ካብዚኦም እቶም 73 ሽሕ ኣሜሪካዊያን እዮም፤ሓይልታት ናዚ ጀርመን ብኸቢድ ዓሪዶምሉ ንዝበሩ መስመር ድፋዕ ወሰን ማይ ንምስባር ግዙፍ መጥቓዕቲ ፈኒዮም።ድሕሪ ክልተ ኣዋርሕ ሓይልታት ጥምረት ንፓሪስ ሓራ ብምውፃእ ከም ውፅኢት ኣብ ምሉእ ኣውሮፓ ንናዚ ስዒሮምዎ። ፕሬዝዳንት ኦባማ ድሕሪ እቲ መደረ ናይ ብሪታኒያ ንግስቲ ኤልሳቤትን መራሕቲ ኣውሮፓን ኣብ ተሳተፍሉ ካሊእ ስነስርዓት ተኻፊሎም።ናይ ሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እውን ካብቶም መራሕቲ ሓደ ነይሮም። ፕሬዝዳንት ኦባማ ሩሲያ ኣብ ልዕሊ ዩክሬይን ብዝወሰደቶ ስጉምትታት ንፕሬዝዳንት ፑቲን ንምግላል ብዙሕ ሓይሎም ዘጥፍእሉ ናይ ኣውሮፓ መገሽኦም ናብ ምጥቕላል ገፁ እዩ።ክልቲኦም መራሕቲ ኣብ ኖርማንዲ ንምርኻብ ዝኾነ ይኹን ወግዓዊ መደብ ኣይነበሮምን።ግን ኣካል እቲ ስነስርዓት ዝኾነ ብናይ ፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኣብዝተዳለወ እንግዶት ድራድ ንብርክት ዝበሉ ደቓይቕ ጎናዊ ዝርርብ ንምክክያድ ዕድል ረኺቦም።
የአቡዳቢ ልዑል አልጋ ወራሽ እና የአረብ ኤሚሬቶች ጦር ኃይል ምክትል ጠቅላይ አዛዥ ሼክ መሃመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ከአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒዮ ብሊንከን ጋር ተወያዩ፡፡ ልዑል አልጋ ወራሹ እና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በሞሮኮ ራባት ነው የተወያዩት፡፡ የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነትን ጨምሮ በየመን ስለሚንቀሳቀሱት የሃውሲ አማጽያን እንዲሁም በተለያዩ ቀጣናዊ የጸጥታና ደህንነት ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውን የኤሚሬት ዜና አገልግሎት (ዋም) ዘግቧል፡፡ በውይይቱ የኤሚሬት የውጭ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር ሼክ አብዱላህ ቢን ዛይድ አል ናህያንን ጨምሮ ሌሎች ባለስልጣናት ተገኝተዋል፡፡ ብሊንከን የሃገራቱን ትብብር የበለጠ ያጠነክራል ያሉትን ፍሬያማ ውይይት ከሼክ መሃመድ ጋር ማድጋቸውን በይፋዊ የማህበረሰብ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡ ውይይቱን አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡት የብሊንከን ቃል አቀባይ ኔድ ፕራይስም ኤሚሬት የሃውሲ አማጽያን ከየመን ከሚፈጽሙባት ጥቃት ራሷን ለመከላከል የምታደርገውን ጥረት አሜሪካ በቁርጠኝነት እንደምትደግፍ ተናግረዋል፡፡ ኤሚሬት የየመን ችግር በዲፕሎማሲያዊ መንገዶች ብቻ ሰላማዊ መፍትሔዎችን ሊያገኝ ይገባል ማለቷንም አድንቀዋል፡፡ ብሊንከን እና ሼክ አብዱላህ ቢን ዛይድ ከሰሞኑ እስራኤል ነበሩ፡፡ ወደ ራባት ከማቅናታቸውም በፊት እስራኤል ከአራት የአረብ ሃገራት ጎረቤቶቿ ጋር ባዘጋጀችው የኔጌቭ ጉባዔ ላይ ተሳትፈዋል፡፡ ኤሚሬት እና እስራኤል የአብርሃም ስምምነትን በመፈረም ለዓመታት ሻክሮ የቆየ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ለማለስለስ መስማማታቸው ይታወሳል፡፡ በዚህም ሃገራቱ ኤምባሲዎቻቸውን ከፍተው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ማድረግ ጀምረዋል፡፡
README.md exists but content is empty. Use the Edit dataset card button to edit it.
Downloads last month
3
Edit dataset card