label
class label
4 classes
headline
stringlengths
17
80
text
stringlengths
1
16.8k
headline_text
stringlengths
28
16.8k
url
stringlengths
36
49
5sports
የስፖርት ኮከቦች እና የንግድ ምልክቶቻቸው- ከቦልት እስከ ክርስቲያኖ ሮናልዶ
የአትሌቲክሱ ዓለም ኮከብ እና ፈጣኑ ሰው ዩሴን ቦልት ከውድድር በፊት እና በኋላ የሚያሳየውን ታዋቂ የሆነውን ምልክት ለንግድ ምልክትነት ለመጠቀም ጥያቄ በማቅረብ ላይ ይገኛል። እሱ ብቻ ግን አይደለም የሚለይበትን ምልክት የሚያሳይ ኮከብ። የአሜሪካ የፓተንት እና የንግድ ምልክት ቢሮ እንደገለጸው ቦልት ታዋቂውን ምልክቱን በንግድ ምልክትነት ለማስመዝገብ ማመልከቻውን ነሐሴ 2014 ዓ.ም. መጀመሪያ ላይ አስገብቷል። መቀመጫቸውን ዋሽንግተን ያደረጉት የንግድ ምልክት ጠበቃው ጆሽ ገርበን “አንድ እጁ ታጥፎ ወደ ጭንቅላቱ ሲጠቆም ሌላኛው እጁ በተመሳሳይ አቅጣጫ ወደ ላይ ከፍ ብሎ  እንደሚዘረጋ” ያሳያል ብለዋል። ቦልት ይህን የሚያደርገው ዝነኛ የድል አድራጊነቱን የሚያሳየውን አርማ የንግድ ምልክት በማድረግ ልብሶችን እና የፋሽን ዕቃዎችን ለመሸጥ በማሰቡ ነው። ታዋቂዋ የአሜሪካ የሴቶች ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች ሜጋን ራፒኖ ጎል ካስቆጠረች በኋላ ደስታዋን በምትገልጽበት የተለየ መንገድ ትታወቃለች። ከአሜሪካ የሴቶች ብሔራዊ ቡድን ጋር የዓለም ዋንጫ እና የኦሎምፒክ ወርቅ አሸናፊ ለመሆን የበቃችው ሜጋን እጆቿን ዘርግታ በምታሳየው ፈገግታ ወይም እርካታ ትለያለች። እአአ በ2019 በፊፋ ኮከብ ተጫዋች ለመሆን የበቃችው ተጫዋቿ ቀላል እና በአድናቂዎች የተወደደ የደስታ አገላለጽ ነው ያላት። ሞ ፋራህ የበርካታ የኦሎምፒክ፣ የዓለም እና የአውሮፓ የረዥም ርቀት ሩጫዎች ሻምፒዮን ነው።  ብዙዎችም "የእንግሊዝ የምንግዜም ታላቅ አትሌት" እያሉ ይጠሩታል። ውድድሮችን ሲያሸንፍ "ሞቦት" በማሳየት በጣም ታዋቂ ነው። የሁለቱን አጅቹን ጣቶች በማገናኘት የጭንቅላቱ አናት ላይ በማድረግ የስሙ መነሻ የሆነውን ‘M’ የእንግሊዘኛ ፊደል ይሠራል። ታዋቂው ፖርቹጋላዊ የማንቸስተር ዩናይትድ አጥቂ ጎል ካስቆጠረ በኋላ ደስታውን የሚገልጽበት መንገድ አዘጋጅቷል። ይሮጥና ይዘላል፣ አየር ላይ እያለ ይዞርና እጆቹን ወደ ጎን እየወረወረ “ሲ” እያለ ይጮሃል። “ሲ” በፖርቹጋል ቋንቋ አዎ እንደማለት ነው። ደቡብ ኮሪያዊው የእግር ኳስ ኮከብ ሶን ሄንግ-ሚን በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ለሚሳተፈው ቶተንሃም ሆትስፐርስ ይጫወታል። አጥቂው ጎል ካስቆጠረ በኋላ ደስታውን የሚገልጽበት የራሱን ልዩ ምልክት አዘጋጅቷል። አውራ እና ጠቋሚ ጣቶቹን በማገናኘት ያንን ቅጽበት ለመቅረጽ የሚረዳውን ካሜራን የሚወክል ቅርጽ ይሠራል። ስለእነዚህ ምልክተቶች ምን ያስባሉ? ቦልት ዝነኛ ምልክት ያለው ብቸኛው ሰው ባይሆንም በዓለም ዙሪያ በጣም ታዋቂው ነው ማለት ግን ይቻላል። የንግድ ምልክት ማመልከቻው ከተሳካ ደግሞ ምናልባት የበለጠ ዕውቅና ያገኛል።
የስፖርት ኮከቦች እና የንግድ ምልክቶቻቸው- ከቦልት እስከ ክርስቲያኖ ሮናልዶ የአትሌቲክሱ ዓለም ኮከብ እና ፈጣኑ ሰው ዩሴን ቦልት ከውድድር በፊት እና በኋላ የሚያሳየውን ታዋቂ የሆነውን ምልክት ለንግድ ምልክትነት ለመጠቀም ጥያቄ በማቅረብ ላይ ይገኛል። እሱ ብቻ ግን አይደለም የሚለይበትን ምልክት የሚያሳይ ኮከብ። የአሜሪካ የፓተንት እና የንግድ ምልክት ቢሮ እንደገለጸው ቦልት ታዋቂውን ምልክቱን በንግድ ምልክትነት ለማስመዝገብ ማመልከቻውን ነሐሴ 2014 ዓ.ም. መጀመሪያ ላይ አስገብቷል። መቀመጫቸውን ዋሽንግተን ያደረጉት የንግድ ምልክት ጠበቃው ጆሽ ገርበን “አንድ እጁ ታጥፎ ወደ ጭንቅላቱ ሲጠቆም ሌላኛው እጁ በተመሳሳይ አቅጣጫ ወደ ላይ ከፍ ብሎ  እንደሚዘረጋ” ያሳያል ብለዋል። ቦልት ይህን የሚያደርገው ዝነኛ የድል አድራጊነቱን የሚያሳየውን አርማ የንግድ ምልክት በማድረግ ልብሶችን እና የፋሽን ዕቃዎችን ለመሸጥ በማሰቡ ነው። ታዋቂዋ የአሜሪካ የሴቶች ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች ሜጋን ራፒኖ ጎል ካስቆጠረች በኋላ ደስታዋን በምትገልጽበት የተለየ መንገድ ትታወቃለች። ከአሜሪካ የሴቶች ብሔራዊ ቡድን ጋር የዓለም ዋንጫ እና የኦሎምፒክ ወርቅ አሸናፊ ለመሆን የበቃችው ሜጋን እጆቿን ዘርግታ በምታሳየው ፈገግታ ወይም እርካታ ትለያለች። እአአ በ2019 በፊፋ ኮከብ ተጫዋች ለመሆን የበቃችው ተጫዋቿ ቀላል እና በአድናቂዎች የተወደደ የደስታ አገላለጽ ነው ያላት። ሞ ፋራህ የበርካታ የኦሎምፒክ፣ የዓለም እና የአውሮፓ የረዥም ርቀት ሩጫዎች ሻምፒዮን ነው።  ብዙዎችም "የእንግሊዝ የምንግዜም ታላቅ አትሌት" እያሉ ይጠሩታል። ውድድሮችን ሲያሸንፍ "ሞቦት" በማሳየት በጣም ታዋቂ ነው። የሁለቱን አጅቹን ጣቶች በማገናኘት የጭንቅላቱ አናት ላይ በማድረግ የስሙ መነሻ የሆነውን ‘M’ የእንግሊዘኛ ፊደል ይሠራል። ታዋቂው ፖርቹጋላዊ የማንቸስተር ዩናይትድ አጥቂ ጎል ካስቆጠረ በኋላ ደስታውን የሚገልጽበት መንገድ አዘጋጅቷል። ይሮጥና ይዘላል፣ አየር ላይ እያለ ይዞርና እጆቹን ወደ ጎን እየወረወረ “ሲ” እያለ ይጮሃል። “ሲ” በፖርቹጋል ቋንቋ አዎ እንደማለት ነው። ደቡብ ኮሪያዊው የእግር ኳስ ኮከብ ሶን ሄንግ-ሚን በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ለሚሳተፈው ቶተንሃም ሆትስፐርስ ይጫወታል። አጥቂው ጎል ካስቆጠረ በኋላ ደስታውን የሚገልጽበት የራሱን ልዩ ምልክት አዘጋጅቷል። አውራ እና ጠቋሚ ጣቶቹን በማገናኘት ያንን ቅጽበት ለመቅረጽ የሚረዳውን ካሜራን የሚወክል ቅርጽ ይሠራል። ስለእነዚህ ምልክተቶች ምን ያስባሉ? ቦልት ዝነኛ ምልክት ያለው ብቸኛው ሰው ባይሆንም በዓለም ዙሪያ በጣም ታዋቂው ነው ማለት ግን ይቻላል። የንግድ ምልክት ማመልከቻው ከተሳካ ደግሞ ምናልባት የበለጠ ዕውቅና ያገኛል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/ceknk30j2xxo
5sports
እግር ኳስ፡ ዩናይትድ፣ አርሴናል፣ ቼልሲ . . . ምን አስበዋል?
የስፖርት ጋዜጦች ስለ እግር ኳስ ምን እያሉ ነው? በሚቀጥለው ጥር የሚከፈተው የዝውውር መስኮትስ ምን ያሳየን ይሆን?ዋና ዋናዎቹን በዚሀች አጭር ዘገባ እንዳስሳለን። አላንድ፡ የቦሩሲያ ዶርትመንዱ አጥቂ ኧርሊንግ ብራውት አላንድ ፈላጊው በዝቷል። አሁን ደግሞ ቼልሲዎች ተጫዋቹን ለማስፈረም ዕቅድ እንዳላቸው እየተነገረ ነው። ነገር ግን ማንቸስተር ሲቲዎች ተጫዋቹ የእኛ ነው እያሉ ነው። ይህን የዘገበው '90 ሚኒት' ጋዜጣ ነው። ቼልሲ አላንድንና የዌስትሃሙን ዴክሌን ራይስ ለማስፈረም ሰባት ተጫዋቾቹን ሊሸጥ እንደሚችል ስካይ ስፖርት ዘግቧል። ባርክሌይ፣ አሎንሶ፣ ሩዲገር፣ ክሪስቴንሰን፣ ጆርጊንሆ፣ ድሪንክዎተርና ሞሰስ ለገበያ ሊቀርቡ እንደሚችሉ ተነግሯል። በሌላ በኩል ማንቸስተር ዩናይትድም አላንድን ማስፈረም ይፈልጋል። ነገር ግን የተጫዋቹ ወኪል የሆነው ሚኖ ራዮላ ከዩናትድ ጋር ያለው ግንኙነት ሰላማዊ ስላልሆነ ችግር ሊፈጥር ይችላል እየተባለ ነው ይላል ሚረር ባወጣው ዘገባ። ዩናይትድ አላንድን ማስፈረም ካልቻለ ፊቱን ወደ ኤቨርተኑን ዶሞኒክ ካልቨርት-ሌዊን ሊያዞር ይችላል። ሩዲገር፡ ቼልሲ ሊሸጣቸው ካሰባቸው ተጫዋቾች መካከል የሆነው ጀርመናዊው አንቶኒዮ ሩዲገር በፓሪስ ሴይንት ዠርሜይን ይፈለጋል። ይህን ያተመው የፈረንሳዩ 'ለ ፓሪዚያ' ነው። ሊቨርፑል፡ ቀያዮቹ የሪያል ማድሪዱን ብራዚላዊ ተከላካይ ኤደር ሚሊቶን ለማስፈረም አቅደዋል። አርጀንቲናዊው የ34 ዓመት ተጫዋች እዝቄል ጋሬይም በሊቨርፑሎች እየተፈለገ ነው። ይህን ዜና ያሰማው የስፔኑ ቶዶፊቻሄስ ነው። አርሴናል፡ የመድፈኞቹ አሠልጣኝ ማይክል አርቴታ የሪያል ማድሪዱን ብራዚላዊ አጥቂ ቪኒሺዬስ ጁኒዬርን ወደ ኤሜሬትስ ለማምጣት አቅደዋል። የ22 ዓመቱ አጥቂ ወደ ኤሜሬትስ በሚቀጥለው ጥር ወር በውሰት ሊመጣ ይችላል ተብሏል። አርቴታ ከወጣቱ አጥቂ በተጨማሪ የ28 ዓመቱን ስፔናዊ አማካይ ኢስኮ፤ ይፈልገዋል። ነገር ግን ተጫዋቹ ወደ ዩቬንቱስ መሄድን ይመርጣል - 'የደይሊ ስታር' እንደዘገበው። ባርሴሎና፡ የካታሎኑ ክለብ የአርሴናሉን ተከላካይ ሹከርዳን መስጣፊን ይፈልገዋል ይላል 'ስፖክስ' ጋዜጣ። የ28 ዓመቱ ሙስጣፊ ከአርሴናል ጋር ያለው ውል እየተገባደደ ነው። ጆንስ፡ የደርቢ ካውንቲ አሠልጣኝ የሆነው ዋይኒ ሩኒ የቀድሞ የቡድን አጋሩ ፊል ጆንስን ማስፈረም ይሻል። እንደ 'ሜትሮ' ዘገባ ከሆነ በማንቸስተር ዩናይትድ ቤት ዕድል ያጣው ጆንስ በዌስትብሮምም ይፈለጋል። የአውሮፓ እግር ኳስ የዝውውር መስኮት በሚቀጥለው የፈረንጆቹ ጥር ወር ይከፈታል። ማን ወደ የት ይሄዳል? ጊዜ ይፈታዋል።
እግር ኳስ፡ ዩናይትድ፣ አርሴናል፣ ቼልሲ . . . ምን አስበዋል? የስፖርት ጋዜጦች ስለ እግር ኳስ ምን እያሉ ነው? በሚቀጥለው ጥር የሚከፈተው የዝውውር መስኮትስ ምን ያሳየን ይሆን?ዋና ዋናዎቹን በዚሀች አጭር ዘገባ እንዳስሳለን። አላንድ፡ የቦሩሲያ ዶርትመንዱ አጥቂ ኧርሊንግ ብራውት አላንድ ፈላጊው በዝቷል። አሁን ደግሞ ቼልሲዎች ተጫዋቹን ለማስፈረም ዕቅድ እንዳላቸው እየተነገረ ነው። ነገር ግን ማንቸስተር ሲቲዎች ተጫዋቹ የእኛ ነው እያሉ ነው። ይህን የዘገበው '90 ሚኒት' ጋዜጣ ነው። ቼልሲ አላንድንና የዌስትሃሙን ዴክሌን ራይስ ለማስፈረም ሰባት ተጫዋቾቹን ሊሸጥ እንደሚችል ስካይ ስፖርት ዘግቧል። ባርክሌይ፣ አሎንሶ፣ ሩዲገር፣ ክሪስቴንሰን፣ ጆርጊንሆ፣ ድሪንክዎተርና ሞሰስ ለገበያ ሊቀርቡ እንደሚችሉ ተነግሯል። በሌላ በኩል ማንቸስተር ዩናይትድም አላንድን ማስፈረም ይፈልጋል። ነገር ግን የተጫዋቹ ወኪል የሆነው ሚኖ ራዮላ ከዩናትድ ጋር ያለው ግንኙነት ሰላማዊ ስላልሆነ ችግር ሊፈጥር ይችላል እየተባለ ነው ይላል ሚረር ባወጣው ዘገባ። ዩናይትድ አላንድን ማስፈረም ካልቻለ ፊቱን ወደ ኤቨርተኑን ዶሞኒክ ካልቨርት-ሌዊን ሊያዞር ይችላል። ሩዲገር፡ ቼልሲ ሊሸጣቸው ካሰባቸው ተጫዋቾች መካከል የሆነው ጀርመናዊው አንቶኒዮ ሩዲገር በፓሪስ ሴይንት ዠርሜይን ይፈለጋል። ይህን ያተመው የፈረንሳዩ 'ለ ፓሪዚያ' ነው። ሊቨርፑል፡ ቀያዮቹ የሪያል ማድሪዱን ብራዚላዊ ተከላካይ ኤደር ሚሊቶን ለማስፈረም አቅደዋል። አርጀንቲናዊው የ34 ዓመት ተጫዋች እዝቄል ጋሬይም በሊቨርፑሎች እየተፈለገ ነው። ይህን ዜና ያሰማው የስፔኑ ቶዶፊቻሄስ ነው። አርሴናል፡ የመድፈኞቹ አሠልጣኝ ማይክል አርቴታ የሪያል ማድሪዱን ብራዚላዊ አጥቂ ቪኒሺዬስ ጁኒዬርን ወደ ኤሜሬትስ ለማምጣት አቅደዋል። የ22 ዓመቱ አጥቂ ወደ ኤሜሬትስ በሚቀጥለው ጥር ወር በውሰት ሊመጣ ይችላል ተብሏል። አርቴታ ከወጣቱ አጥቂ በተጨማሪ የ28 ዓመቱን ስፔናዊ አማካይ ኢስኮ፤ ይፈልገዋል። ነገር ግን ተጫዋቹ ወደ ዩቬንቱስ መሄድን ይመርጣል - 'የደይሊ ስታር' እንደዘገበው። ባርሴሎና፡ የካታሎኑ ክለብ የአርሴናሉን ተከላካይ ሹከርዳን መስጣፊን ይፈልገዋል ይላል 'ስፖክስ' ጋዜጣ። የ28 ዓመቱ ሙስጣፊ ከአርሴናል ጋር ያለው ውል እየተገባደደ ነው። ጆንስ፡ የደርቢ ካውንቲ አሠልጣኝ የሆነው ዋይኒ ሩኒ የቀድሞ የቡድን አጋሩ ፊል ጆንስን ማስፈረም ይሻል። እንደ 'ሜትሮ' ዘገባ ከሆነ በማንቸስተር ዩናይትድ ቤት ዕድል ያጣው ጆንስ በዌስትብሮምም ይፈለጋል። የአውሮፓ እግር ኳስ የዝውውር መስኮት በሚቀጥለው የፈረንጆቹ ጥር ወር ይከፈታል። ማን ወደ የት ይሄዳል? ጊዜ ይፈታዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-55435608
0business
ዓለምን ካስጨነቃት የዋጋ ንረት ተጠቃሚዎቹ እነማን ናቸው?
ከኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ተጽእኖ ሳያገግም የዩክሬን እና ሩሲያ ጦርነት የገጠመው የዓለም ምጣኔ ሃብት ከቀውስ አዙሪት ውስጥ አልወጣም። የነዳጅ እና የምግብ ምርቶች የዋጋ ንረት በመላው ዓለም በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት ከባድ አድርጎታል። ታዲያ ዓለም በዋጋ ንረት በምትጨነቅበት በአሁኑ ወቅት በተለየ ሁኔታ ትርፍ እያጋበሱ ተጠቃሚ የሚሆኑ ዘርፎች አሉ። እነዚህ ከዋጋ ንረት የሚያተርፉ ድርጅቶች የትኞቹ ናቸው?
ዓለምን ካስጨነቃት የዋጋ ንረት ተጠቃሚዎቹ እነማን ናቸው? ከኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ተጽእኖ ሳያገግም የዩክሬን እና ሩሲያ ጦርነት የገጠመው የዓለም ምጣኔ ሃብት ከቀውስ አዙሪት ውስጥ አልወጣም። የነዳጅ እና የምግብ ምርቶች የዋጋ ንረት በመላው ዓለም በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት ከባድ አድርጎታል። ታዲያ ዓለም በዋጋ ንረት በምትጨነቅበት በአሁኑ ወቅት በተለየ ሁኔታ ትርፍ እያጋበሱ ተጠቃሚ የሚሆኑ ዘርፎች አሉ። እነዚህ ከዋጋ ንረት የሚያተርፉ ድርጅቶች የትኞቹ ናቸው?
https://www.bbc.com/amharic/articles/crgj31l8mzzo
2health
ኮሮናቫይረስ፡ በቫይረሱ የሞቱት የሮማኒያው ከንቲባ በምርጫ አሸነፉ
በኮሮናቫይረስ የሞቱት የሮማኒያው ከንቲባ በቅርቡ የተደረገውን ምርጫ በከፍተኛ ድምፅ አሸንፈዋል። 64 በመቶ የመራጮችንም ድምፅ ማግኘት ችለዋል። በደቡባዊቷ ሮማኒያ በምትገኘው ግዛት ዴቬሴሉ ከንቲባ የነበሩት ኢዮን አሊማን ለሶስተኛ ጊዜም አሸንፈዋል። ከሁለት ሳምንታት በፊት በመዲናዋ ቡካሬስት ህይወታቸው ያለፈው የቀድሞው ከንቲባ ስም ከተመራጮች ዝርዝር ውስጥ ነበር። የተመራጮች ዝርዝር ቀድሞ በመታተሙ ስማቸውን ማስወገድ እንዳልተቻለም ባለስልጣናቱ አስታውቀዋል። በዚህም ምክንያት የሞተ ሰው ከንቲባ ሆኖ እንደተመረጠም ተገልጿል። ሌላ ምርጫ እንደሚደረግም ባለስልጣናቱ ለሮይተርስ የተናገሩ ሲሆን በርካታ የግዛቲቷ ነዋሪዎች የቀድሞ ከንቲባቸውን ቀብር በመጎብኘት ሃዘናቸውን በመግለፅ ላይ ናቸው። በርካታ የመንደሪቷ ሰዎችም በመካነ መቃብሩ ተሰባስበው መታየታቸውን በማህበራዊ ሚዲያ የተጋሩ ቪዲዮዎች አሳይተዋል። "ይህ የአንተ ድል ነው" ሲል አንድ ግለሰብ ሲናገር ተሰምቷል። "እውነተኛ ከንቲባችን ነበር" በማለት ሌላ ግለሰብ ለአካባቢው የቴሌቪዥን ጣቢያ መናገሯን ሮይተርስ ዘግቧል። "ሁሉንም የግዛቲቷን ነዋሪ በእኩል አይን ያይ የነበረ፤ ህግንም ያከብር ነበር። እንደሱ አይነት ከንቲባ መቼም አይኖረንም" ግለሰቧ ማለቷንም ሮይተርስ አስነብቧል። የቀድሞ የባህር ኃይል አባል የነበሩት ኢዮን የግራ ክንፍ የሚያዘመው የሶሺያል ዲሞክራት ፓርቲ (ፒኤስዲ) አባል ነበሩ፤ በትናንትናው ዕለትም 57 አመታቸው ይሆን ነበር። በከንቲባነታቸው በህዝባቸው በከፍተኛ ሁኔታ መወደዳቸውም በፓርቲያቸው ዘንድ ጥሩ ስም አስገኝቶላቸዋል። ፓርቲያቸው በአሁኑ በተደረገው አገራዊ ምርጫ በተለያዩ ከተሞችና የምክር ቤቶች መቀመጫቸውን ለቀኝ ክንፍ አክራሪው ዩኤስ አር ፕላስ አሊያስና የአገሪቱን የመንግሥት ስልጣን በበላይነት ለተቆጣጠረው ሴንትሪስት ሊበራል አጥተዋል። በበርካታ የአውሮፓ ህብረት አባል አገራት የፍትህ ስርአቱ እንዲሻሻልና የሰፈነው ሙስና እንዲቆም የሚጠይቁ ከፍተኛ የተቃውሞ ሰልፎችን ተከትሎም ነው ፒኤስዲ በርካታ መቀመጫዎችን በፖርላመንት በድምፅ እንዲያጣ የተደረገው። የቀድሞ ከንቲባው ኢዮን ከሞቱ በኋላ በምርጫ ማሸነፍ በአገሪቷ የመጀመሪያው ክስተት አይደለም በጎሮጎሳውያኑ 2008 ኔኩላይ ኢቫስኩ የተባሉት ከንቲባም በጉበት በሽታ ከሞቱ በኋላ የቮይነስቲ ግዛት ከንቲባ ሆነዋል።
ኮሮናቫይረስ፡ በቫይረሱ የሞቱት የሮማኒያው ከንቲባ በምርጫ አሸነፉ በኮሮናቫይረስ የሞቱት የሮማኒያው ከንቲባ በቅርቡ የተደረገውን ምርጫ በከፍተኛ ድምፅ አሸንፈዋል። 64 በመቶ የመራጮችንም ድምፅ ማግኘት ችለዋል። በደቡባዊቷ ሮማኒያ በምትገኘው ግዛት ዴቬሴሉ ከንቲባ የነበሩት ኢዮን አሊማን ለሶስተኛ ጊዜም አሸንፈዋል። ከሁለት ሳምንታት በፊት በመዲናዋ ቡካሬስት ህይወታቸው ያለፈው የቀድሞው ከንቲባ ስም ከተመራጮች ዝርዝር ውስጥ ነበር። የተመራጮች ዝርዝር ቀድሞ በመታተሙ ስማቸውን ማስወገድ እንዳልተቻለም ባለስልጣናቱ አስታውቀዋል። በዚህም ምክንያት የሞተ ሰው ከንቲባ ሆኖ እንደተመረጠም ተገልጿል። ሌላ ምርጫ እንደሚደረግም ባለስልጣናቱ ለሮይተርስ የተናገሩ ሲሆን በርካታ የግዛቲቷ ነዋሪዎች የቀድሞ ከንቲባቸውን ቀብር በመጎብኘት ሃዘናቸውን በመግለፅ ላይ ናቸው። በርካታ የመንደሪቷ ሰዎችም በመካነ መቃብሩ ተሰባስበው መታየታቸውን በማህበራዊ ሚዲያ የተጋሩ ቪዲዮዎች አሳይተዋል። "ይህ የአንተ ድል ነው" ሲል አንድ ግለሰብ ሲናገር ተሰምቷል። "እውነተኛ ከንቲባችን ነበር" በማለት ሌላ ግለሰብ ለአካባቢው የቴሌቪዥን ጣቢያ መናገሯን ሮይተርስ ዘግቧል። "ሁሉንም የግዛቲቷን ነዋሪ በእኩል አይን ያይ የነበረ፤ ህግንም ያከብር ነበር። እንደሱ አይነት ከንቲባ መቼም አይኖረንም" ግለሰቧ ማለቷንም ሮይተርስ አስነብቧል። የቀድሞ የባህር ኃይል አባል የነበሩት ኢዮን የግራ ክንፍ የሚያዘመው የሶሺያል ዲሞክራት ፓርቲ (ፒኤስዲ) አባል ነበሩ፤ በትናንትናው ዕለትም 57 አመታቸው ይሆን ነበር። በከንቲባነታቸው በህዝባቸው በከፍተኛ ሁኔታ መወደዳቸውም በፓርቲያቸው ዘንድ ጥሩ ስም አስገኝቶላቸዋል። ፓርቲያቸው በአሁኑ በተደረገው አገራዊ ምርጫ በተለያዩ ከተሞችና የምክር ቤቶች መቀመጫቸውን ለቀኝ ክንፍ አክራሪው ዩኤስ አር ፕላስ አሊያስና የአገሪቱን የመንግሥት ስልጣን በበላይነት ለተቆጣጠረው ሴንትሪስት ሊበራል አጥተዋል። በበርካታ የአውሮፓ ህብረት አባል አገራት የፍትህ ስርአቱ እንዲሻሻልና የሰፈነው ሙስና እንዲቆም የሚጠይቁ ከፍተኛ የተቃውሞ ሰልፎችን ተከትሎም ነው ፒኤስዲ በርካታ መቀመጫዎችን በፖርላመንት በድምፅ እንዲያጣ የተደረገው። የቀድሞ ከንቲባው ኢዮን ከሞቱ በኋላ በምርጫ ማሸነፍ በአገሪቷ የመጀመሪያው ክስተት አይደለም በጎሮጎሳውያኑ 2008 ኔኩላይ ኢቫስኩ የተባሉት ከንቲባም በጉበት በሽታ ከሞቱ በኋላ የቮይነስቲ ግዛት ከንቲባ ሆነዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-54336166
2health
ኮሮናቫይረስ፡ አውሮፕላኖች እንዴት ነው በፀረ- ተህዋሲያን የሚፀዱት?
የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መከሰቱን ተከትሎ ቀጥ ብሎ የነበረውን የአለም የንግድ እንቅስቃሴን ለመመለስ በርካታ ጥረቶች እየተደረገ ነው። በተለያዩ አገራትም የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት ጥለዋቸው የነበሩ መመሪያዎችን እያላሉ ይገኛሉ። የወረርሽኝ ስርጭቱን ለመግታት አገራት አስተላልፈዋቸው ከነበሩ መመሪያዎች መካከል ዓለም አቀፍ በረራዎችን ማቆም፣ አየር ማረፊያዎቻቸውንና ድንበሮቻቸውን መዝጋት ይገኙበታል። በዚህም የተነሳ በርካታ የኢንዱስትሪ ዘርፎች በከፍተኛ ሁኔታ የተጎዱ ሲሆን በተለይም የአየር ትራንስፖርት ዘርፉ እንዲሽመደመድ ምክንያት ሆኗል። ከሰሞኑ አገራቱ ዘግተዋቸው የነበሩ ድንበሮቻቸውን ከፍተዋል፤ አለም አቀፍ አየር መንገዶቹም በረራዎችን ጀምረዋል። የአለም አቀፉ አቪየሽን ድርጅት የአየር ትራንስፖርቱ ዘርፍ እንዲያንሰራራና ተጓዦችም ደህንነታቸቸው በተጠበቀ መልኩ እንዲጓዙ ለማድረግ እንደ መመሪያነት የሚያገለግል አንድ ሰነድ አውጥቷል። በዚህም መመሪያ ውስጥ ከተካተቱት ጉዳዮች መካከል አውሮፕላኖች በምን መንገድ በፀረ- ተህዋሲያን መፀዳት እንዳለባቸውና የፅዳት ድግግሞሽንም ይመለከታል። እንዲሁ ከላይ ከላይ ሲታይ የአየር በረራና አካላዊ ርቀትን መጠበቅ የሚጣጣሙ አይመስሉም ። ነገር ግን ተቆጣጣሪ አካላት የተለያዩ ፕሮቶኮሎችን በማውጣት አስፈላጊ የሚባሉ የፅዳት መመሪያዎችን ለመተግበር ቀን ተሌት ደፋ ቀና በማለት ላይ ናቸው። ለአየር በረራዎች በዋነኝነት የሚያስፈልገው ፈጣንና፣ በቅልጥፍና የተሞላ ውጤታማ ፀረ- ተህዋሲያን የፅዳት ስርዓት መዘርጋት ነው። ከዚህም ጋር ተያይዞ ፍቃድ ያላቸው የፀረ- ተህዋሲያን ፅዳት በሚታዩና፣ ተደራሽ በሆኑ አካላት ላይ ጨርቅን እንዲሁም ተንቀሳቃሽ መርጫን በመጠቀም ማፅዳት ተግባራዊ እየተደረጉ ይገኛሉ። ነገር ግን ሁለቱም የማፅጃ መንገዶች በሰዎች አማካኝነት የሚካዱ ከመሆናቸው አንፃር ውጤታማነታቸውን የሚቀንስ ሲሆን መደረስ የማይችሉ የአውሮፕላኑ አካላትም ላይ ክፍተትን ይፈጥራሉ ተብሏል። ኦክስጅንና ኦዞን በሌላ መልኩ "አቶሚክ ኦክስጅንን" እንደ ፀረ-ተህዋሲያነት በመጠቅም አካባቢን ለማፅዳት ተጀምሯል። ከዚህም በተጨማሪ አምቡላንሶችን ለማፅዳት የሚጠቀሙበትን ፀረ ተህዋሲያንንም ለአውሮፕላን የውስጥ ክፍል ለማፅዳት እየታሰበበት ነው። ነገር ግን እነዚህ ማፅጃዎች ባላቸው የንጥረ ነገር በተለይም 'ኦክሳይድ' ባለው ባህርይ የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶች ላይ ጉዳት ሊፈጥሩ ይችሉ ይሆን በሚለው ስምምነት ላይ አልተደረሰም። መቶ በመቶ ውጤታማ የፀረ ተህዋሲያን ማፅጃ በሌለበት ሁኔታ ሌላኛው አማራጭ "የኦዞን" ንጥረ ነገሮችን መጠቀም ነው። በአሁኑ ወቅት ኦዞን በአውሮፕላን አካላት ላይ አገልግሎት ላይ ባይውልም በመጠጥ ቤቶችና በተለያዩ የንግድ ተቋማት ላይ በፀረ-ተህዋሲያን ማፅጃነት እያገለገለ ይገኛል። አካባቢውን የኦዞን ንጥረ ነገሮችን በመርጨት ውጤታማ የሆነ ፅዳትን ማግኘት ይቻላል። ነገር ግን ይህ ንጥረ ነገር በከፍተኛ መጠን ሲሆን ለሰዎች ጎጅ በመሆኑ ባለሙያን በመጠቀም መንገደኞች በሌሉበት ሁኔታ ሊረጭ ይገባል። ነገር ግን አሁንም ቢሆን ኦዞን ላይ ያለው ዋነኛ ጥያቄም የኦክሳይድ ንጥረ ነገር መጠኑ ነው፤ 'በአውሮፕላን የውስጥ አካልና የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ላይ ያለው ተፅእኖ ላይ መስማማት አልተቻለም። 'አየኖችና የአልትራቫዮሌት ጨረር ' በላብራቶሪ ውስጥ ተሞክሮ ውጤታማ የሆነው ከከባቢ አየር የሚለቀቀውን የውሃ ትነት ውስጥ የኦክስጅንና ሃይድሮጅን ንጥረ ነገሮችን ለይቶ በማውጣት ፀረ ተህዋሲያንን መፍጠር ነው። ይህ የፀረ ተህዋሲያን ማፅጃ መንገድ በጣም አድካሚና ለሁለት ሰዓታት ያህልም የሚወስድ ጊዜን ይፈጃል። ሆኖም ይሄ መንገድ በከፍተኛ ሁኔታ ውጤታማና መቶ በመቶ የሚተማመኑበት ነው። ከዚህም በተጨማሪ ፀረ ተህዋሲያኑ ቀላልና ተንቀሳቃሽ በሆነ መልኩ ትልልቅ የአውሮፕላን አካሎችን ማፅዳት ቢቻልም ለማፅዳት ግን ረዘም ያለ ጊዜ መውሰድ ያስፈልጋል። ሌላኛው ደግሞ ሲ የሚባለው የአልትራቫዮሌት ጨረር ሲሆን ይህ ጨረር ሳርስ የተባለውን የኮሮናቫይረስ አይነት ማጥፋት ይችላል። ለዚያም ነው ከፍተኛ ወጪ የሌላቸው ጨረሮች የአውሮፕላን አካላትን ለማፅዳት እየተነደፉ እንዲሁም እየተመረቱ ያሉት። ይህንም ተከትሎ በገበያው ላይ የነዚህ ጨረሮች ፍላጎት በመጨመሩ ምክንያት የአልትራቫዮሌት ጨረሮችን የሚያመርቱ ኩባንያዎች ምርታቸው በሚቀጥሉት አራት አመታት በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጨምርም ግምታቸውን አስቀምጠዋል። በርካታ አማራጮች በርካታ የፀረ ተህዋሲያን ማፅጃ አማራጮች ከመኖራቸው አንፃር በተለያየ ሂደትም ላይ ናቸው። አሁንም ቢሆን የትኛው የበለጠ ተስማሚ እንደሆነም እስካሁንም አይታወቅም። የትኛው የፀረ ተህዋሲያን ስርአት የበለጠ ውጤታማ እንደሚሆን መለየት ከተቻለ በኋላ ምን ያህል ጊዜም ይወስዳል የሚለውን ማየት አስፈላጊ እንደሆነም እየተነገረ ነው። የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ አሁንም ስጋት ሆኖ ባለበት ወቅት በርካታ አየር መንገዶች በረራ መጀመራቸው ጋር ተያይዞ ቫይረሱ እንዳይሰራጭ የማድረግ ከፍተኛ ኃላፊነትና ሸክም ተጥሏባቸዋል። የአውሮፕላኑ ሰራተኞች፣ መንገደኞችን ደህንነት በሚያስጠብቅ መልኩ አውሮፕላኖቹ በፀረ ተህዋሲያን መፀዳትም ግዴታ ነው። እነዚህ የፀረ ተህዋሲያን ማፅጃ ዘዴዎች ቫይረሱን መግታት ብቻ ሳይሆን የአየር መንገድ ኃላፊዎችም ሆነ ተቆጣጣሪዎች የሚያስወጣቸውን ዋጋና እንዲሁም ቀልጣፋና ውጤታማ በሆነ መንገድ መፅዳት የሚችሉበትን ሁኔታ መገምገም ይጠበቅባቸዋል። በአንድ መልኩ የአየር ትራንስፖርቱ ወደቀደመ ሁኔታ እንዲመለሱ ግፊት እያደረጉ ሲሆን በሌላ መልኩ በዚህ ወረርሽኝ መካከል የተጓዦች ደህንነት በተጠበቀ መልኩ አገልግሎታቸውን መመለስና በወረርሽኙ ምክንያት ያጡትን ገቢ ለማግኘትም አጣጥመው መሄድ ይጠበቅባቸዋል። በተለይም አውሮፕላኖቹ የሚፀዱበትን ደረጃና ያለውን የስጋት መጠንን መቀነስና፤ የሚፀዳበትን ጊዜ አጣጥመው መሄድም ይጠበቅባቸዋል። የመንገደኞችን ጤንትና ደህንነት ቅድሚያ በመስጠትም አየር መንገዶቹ እነዚህን ተግባራት እንዲያከናውኑም አለም አቀፉ አቪየሽንም መመሪያ ሰጥቷል። ከአለም አቀፉ አቪየሽን ቡድንና፣ የትራንስፖርት ዘርፍ ተመራማሪዎች የተውጣጡ ግለሰቦችም ውጤታማ የሆኑትን የፀረ ተህዋሲያን የማፅጃ ዘዴዎችንም ለመቀየስ ከፍተኛ ምርምሮችን እያደረጉም ነው፤ የተለያዩ መመሪያዎችንም በማውጣትም ላይ ይገኛሉ።
ኮሮናቫይረስ፡ አውሮፕላኖች እንዴት ነው በፀረ- ተህዋሲያን የሚፀዱት? የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መከሰቱን ተከትሎ ቀጥ ብሎ የነበረውን የአለም የንግድ እንቅስቃሴን ለመመለስ በርካታ ጥረቶች እየተደረገ ነው። በተለያዩ አገራትም የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት ጥለዋቸው የነበሩ መመሪያዎችን እያላሉ ይገኛሉ። የወረርሽኝ ስርጭቱን ለመግታት አገራት አስተላልፈዋቸው ከነበሩ መመሪያዎች መካከል ዓለም አቀፍ በረራዎችን ማቆም፣ አየር ማረፊያዎቻቸውንና ድንበሮቻቸውን መዝጋት ይገኙበታል። በዚህም የተነሳ በርካታ የኢንዱስትሪ ዘርፎች በከፍተኛ ሁኔታ የተጎዱ ሲሆን በተለይም የአየር ትራንስፖርት ዘርፉ እንዲሽመደመድ ምክንያት ሆኗል። ከሰሞኑ አገራቱ ዘግተዋቸው የነበሩ ድንበሮቻቸውን ከፍተዋል፤ አለም አቀፍ አየር መንገዶቹም በረራዎችን ጀምረዋል። የአለም አቀፉ አቪየሽን ድርጅት የአየር ትራንስፖርቱ ዘርፍ እንዲያንሰራራና ተጓዦችም ደህንነታቸቸው በተጠበቀ መልኩ እንዲጓዙ ለማድረግ እንደ መመሪያነት የሚያገለግል አንድ ሰነድ አውጥቷል። በዚህም መመሪያ ውስጥ ከተካተቱት ጉዳዮች መካከል አውሮፕላኖች በምን መንገድ በፀረ- ተህዋሲያን መፀዳት እንዳለባቸውና የፅዳት ድግግሞሽንም ይመለከታል። እንዲሁ ከላይ ከላይ ሲታይ የአየር በረራና አካላዊ ርቀትን መጠበቅ የሚጣጣሙ አይመስሉም ። ነገር ግን ተቆጣጣሪ አካላት የተለያዩ ፕሮቶኮሎችን በማውጣት አስፈላጊ የሚባሉ የፅዳት መመሪያዎችን ለመተግበር ቀን ተሌት ደፋ ቀና በማለት ላይ ናቸው። ለአየር በረራዎች በዋነኝነት የሚያስፈልገው ፈጣንና፣ በቅልጥፍና የተሞላ ውጤታማ ፀረ- ተህዋሲያን የፅዳት ስርዓት መዘርጋት ነው። ከዚህም ጋር ተያይዞ ፍቃድ ያላቸው የፀረ- ተህዋሲያን ፅዳት በሚታዩና፣ ተደራሽ በሆኑ አካላት ላይ ጨርቅን እንዲሁም ተንቀሳቃሽ መርጫን በመጠቀም ማፅዳት ተግባራዊ እየተደረጉ ይገኛሉ። ነገር ግን ሁለቱም የማፅጃ መንገዶች በሰዎች አማካኝነት የሚካዱ ከመሆናቸው አንፃር ውጤታማነታቸውን የሚቀንስ ሲሆን መደረስ የማይችሉ የአውሮፕላኑ አካላትም ላይ ክፍተትን ይፈጥራሉ ተብሏል። ኦክስጅንና ኦዞን በሌላ መልኩ "አቶሚክ ኦክስጅንን" እንደ ፀረ-ተህዋሲያነት በመጠቅም አካባቢን ለማፅዳት ተጀምሯል። ከዚህም በተጨማሪ አምቡላንሶችን ለማፅዳት የሚጠቀሙበትን ፀረ ተህዋሲያንንም ለአውሮፕላን የውስጥ ክፍል ለማፅዳት እየታሰበበት ነው። ነገር ግን እነዚህ ማፅጃዎች ባላቸው የንጥረ ነገር በተለይም 'ኦክሳይድ' ባለው ባህርይ የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶች ላይ ጉዳት ሊፈጥሩ ይችሉ ይሆን በሚለው ስምምነት ላይ አልተደረሰም። መቶ በመቶ ውጤታማ የፀረ ተህዋሲያን ማፅጃ በሌለበት ሁኔታ ሌላኛው አማራጭ "የኦዞን" ንጥረ ነገሮችን መጠቀም ነው። በአሁኑ ወቅት ኦዞን በአውሮፕላን አካላት ላይ አገልግሎት ላይ ባይውልም በመጠጥ ቤቶችና በተለያዩ የንግድ ተቋማት ላይ በፀረ-ተህዋሲያን ማፅጃነት እያገለገለ ይገኛል። አካባቢውን የኦዞን ንጥረ ነገሮችን በመርጨት ውጤታማ የሆነ ፅዳትን ማግኘት ይቻላል። ነገር ግን ይህ ንጥረ ነገር በከፍተኛ መጠን ሲሆን ለሰዎች ጎጅ በመሆኑ ባለሙያን በመጠቀም መንገደኞች በሌሉበት ሁኔታ ሊረጭ ይገባል። ነገር ግን አሁንም ቢሆን ኦዞን ላይ ያለው ዋነኛ ጥያቄም የኦክሳይድ ንጥረ ነገር መጠኑ ነው፤ 'በአውሮፕላን የውስጥ አካልና የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ላይ ያለው ተፅእኖ ላይ መስማማት አልተቻለም። 'አየኖችና የአልትራቫዮሌት ጨረር ' በላብራቶሪ ውስጥ ተሞክሮ ውጤታማ የሆነው ከከባቢ አየር የሚለቀቀውን የውሃ ትነት ውስጥ የኦክስጅንና ሃይድሮጅን ንጥረ ነገሮችን ለይቶ በማውጣት ፀረ ተህዋሲያንን መፍጠር ነው። ይህ የፀረ ተህዋሲያን ማፅጃ መንገድ በጣም አድካሚና ለሁለት ሰዓታት ያህልም የሚወስድ ጊዜን ይፈጃል። ሆኖም ይሄ መንገድ በከፍተኛ ሁኔታ ውጤታማና መቶ በመቶ የሚተማመኑበት ነው። ከዚህም በተጨማሪ ፀረ ተህዋሲያኑ ቀላልና ተንቀሳቃሽ በሆነ መልኩ ትልልቅ የአውሮፕላን አካሎችን ማፅዳት ቢቻልም ለማፅዳት ግን ረዘም ያለ ጊዜ መውሰድ ያስፈልጋል። ሌላኛው ደግሞ ሲ የሚባለው የአልትራቫዮሌት ጨረር ሲሆን ይህ ጨረር ሳርስ የተባለውን የኮሮናቫይረስ አይነት ማጥፋት ይችላል። ለዚያም ነው ከፍተኛ ወጪ የሌላቸው ጨረሮች የአውሮፕላን አካላትን ለማፅዳት እየተነደፉ እንዲሁም እየተመረቱ ያሉት። ይህንም ተከትሎ በገበያው ላይ የነዚህ ጨረሮች ፍላጎት በመጨመሩ ምክንያት የአልትራቫዮሌት ጨረሮችን የሚያመርቱ ኩባንያዎች ምርታቸው በሚቀጥሉት አራት አመታት በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጨምርም ግምታቸውን አስቀምጠዋል። በርካታ አማራጮች በርካታ የፀረ ተህዋሲያን ማፅጃ አማራጮች ከመኖራቸው አንፃር በተለያየ ሂደትም ላይ ናቸው። አሁንም ቢሆን የትኛው የበለጠ ተስማሚ እንደሆነም እስካሁንም አይታወቅም። የትኛው የፀረ ተህዋሲያን ስርአት የበለጠ ውጤታማ እንደሚሆን መለየት ከተቻለ በኋላ ምን ያህል ጊዜም ይወስዳል የሚለውን ማየት አስፈላጊ እንደሆነም እየተነገረ ነው። የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ አሁንም ስጋት ሆኖ ባለበት ወቅት በርካታ አየር መንገዶች በረራ መጀመራቸው ጋር ተያይዞ ቫይረሱ እንዳይሰራጭ የማድረግ ከፍተኛ ኃላፊነትና ሸክም ተጥሏባቸዋል። የአውሮፕላኑ ሰራተኞች፣ መንገደኞችን ደህንነት በሚያስጠብቅ መልኩ አውሮፕላኖቹ በፀረ ተህዋሲያን መፀዳትም ግዴታ ነው። እነዚህ የፀረ ተህዋሲያን ማፅጃ ዘዴዎች ቫይረሱን መግታት ብቻ ሳይሆን የአየር መንገድ ኃላፊዎችም ሆነ ተቆጣጣሪዎች የሚያስወጣቸውን ዋጋና እንዲሁም ቀልጣፋና ውጤታማ በሆነ መንገድ መፅዳት የሚችሉበትን ሁኔታ መገምገም ይጠበቅባቸዋል። በአንድ መልኩ የአየር ትራንስፖርቱ ወደቀደመ ሁኔታ እንዲመለሱ ግፊት እያደረጉ ሲሆን በሌላ መልኩ በዚህ ወረርሽኝ መካከል የተጓዦች ደህንነት በተጠበቀ መልኩ አገልግሎታቸውን መመለስና በወረርሽኙ ምክንያት ያጡትን ገቢ ለማግኘትም አጣጥመው መሄድ ይጠበቅባቸዋል። በተለይም አውሮፕላኖቹ የሚፀዱበትን ደረጃና ያለውን የስጋት መጠንን መቀነስና፤ የሚፀዳበትን ጊዜ አጣጥመው መሄድም ይጠበቅባቸዋል። የመንገደኞችን ጤንትና ደህንነት ቅድሚያ በመስጠትም አየር መንገዶቹ እነዚህን ተግባራት እንዲያከናውኑም አለም አቀፉ አቪየሽንም መመሪያ ሰጥቷል። ከአለም አቀፉ አቪየሽን ቡድንና፣ የትራንስፖርት ዘርፍ ተመራማሪዎች የተውጣጡ ግለሰቦችም ውጤታማ የሆኑትን የፀረ ተህዋሲያን የማፅጃ ዘዴዎችንም ለመቀየስ ከፍተኛ ምርምሮችን እያደረጉም ነው፤ የተለያዩ መመሪያዎችንም በማውጣትም ላይ ይገኛሉ።
https://www.bbc.com/amharic/53627279
3politics
ቤኒቶ ሙሶሊኒ ላይ የተኮሰችው አየርላንዳዊት
ጊዜው በፈረንጆቹ ሚያዝያ 7 1926 ነበር። ቦታው ደግሞ የጣልያኗ መዲና ሮም። የሃገሬው ሰው በ20ኛው ክፍለ ዘመን ከነበሩ ኃያላን መካከል አንዱ የነበረውን ግለሰብ ለማየት ተኮልኩሏል። አንዲት አየርላንዳዊት ሴት ግን በሰውዬው ወሬ ብዙም አልተማረከችም። ዓላማዋ ሌላ ነበር። ድንገት የተኩስ ድምፅ ተሰማ። ሰው ወዲያ ወዲህ ተበታተነ። ለተሰበሰበው ሰው መልዕክቱን ሲያስተላልፍ የነበረው ቤኒቶ ሙሴሊኒም ወደኋላ ተዘረጋ። ጥይቷ የፈለቀችው ከአየርላንዳዊቷ ሴት አፈሙዝ ነበር። ዒላማዋን አልሳተችም። የሙሶሊኒን አፍንጫ ቦረሸችው። ሙሶሊኒ ግን አልሞተም። የጣልያኑ መሪ ከተቃጣበት የግድያ ሙከራ መትረፍ ቻለ። አውሮፓውያን በ20ኛው ክፍለ ዘመን ፋሺስታዊነትን ለመከላከል ከፈፀሟቸው ድርጊቶች መካከል የቫዮሌት ጊብሰን ድርጊት ሁሌም ይነሳል። ሙሶሊኒን ለመግደል ጥረት ካደረጉ አራት ሰዎች መካከል የተሻለ ሙከራ ያደረገችው እሷ ናት። አየርላንዳዊቷ ሙሶሊኒን ለመግደል ሙከራ ካደረገች እነሆ መቶ ዓመት ሊደፍን ጥቂት ዓመታት ይቀሩታል። ይህን ለማሰብ ደብሊን ውስጥ መታሰቢያ እንዲቆምላት ሥራዎች ተጀምረዋል። ቫዮሌት ሙሶሊኒ ላይ ሶስት ጥይቶች ተኩሳለች። አራተኛውን ልትለቀው ስትል ግን ሽጉጧ ነከሰ። ይሄኔ የሙሶሊኒ ጠባቂዎች የከበቧት። የከተማዋ ፖሊስ ጣልቃ ገብቶ በቁጥጥር ሥር ባያውሏት ኖሮ የጠባቂዎቹ ጡጫ ሲሳይ ትሆን ነበር። ጣልያን ውስጥ ታሥራ ከቆች በኋላ ወደ እንግሊዝ እንድትሄድ ተደረገ። ይህ የሆነው ጣልያን ውስጥ የፍርድ ሂደቱ ቢካሄድ ውርደት ይሆናል በሚል ነው ይባላል። ቫዮሌት እንግሊዝ ውስጥ ባለው የቅዱስ አንድሩ የአእምሮ ሕሙማን መታከሚያ ማዕከል ገብታ በስተመጨረሻ በፈረንጆቹ 1956 ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች። ከእንግሊዛዊ አየርላንዳዊ ከበርቴ ቤተሰብ የተወለደችው ቫዮሌት ክዊን ቪክቶሪያ ውስጥ ነበር የምትኖረው። አሁን የደብሊን ከተማ በስሟ መታሰቢያ እንዲቆም ረቂቅ አፅድቆ ወደ ሥራ ገብቷል። የከተማዋ አስተዳደር የሴትዬዋ ድርጊት በታሪክ መዝገብ ብዙም ባለመዘገቡ የሠራችውን 'ፀረ-ፋሺስት' ሥራ የሚዘክር መታሰቢያ ሊቆምላት ይገባል ብሏል። "የብሪታኒያ መንግሥትና ቤተሰቦቿ የሷን ድርጊት እንደ 'እብድ ሰው' ተግባር ሳይሆን እንደ ፖለቲካ ሊያዩት ይገባል" ይላል ረቂቁ። በጀግንነቷ ምክንያት የተሰቃየችው ረቂቁን ለደብሊን ከተማ ምክር ቤት ያቀረቡት ገለልተኛው የከተማው ምክር ቤት አባል ማኒክስ ፍሊን "ቫዮሌት ጊብሰን በአየርላንድና እንግሊዝ መንግሥታት የተረሳች ናት" ሲሉ ይከራከራሉ። "ልክ እንደበርካታ ሴቶች እጅግ ድፍረት የተሞላበት ድርጊት ብትፈፅምም ተገፍታለች" ሲሉ ለቢቢሲ ሰሜን አየርላንድ ጣቢያ ይናገራሉ። "ቫዮሌት ጊብሰን የሠራችው ሥራ የሚያሳፍር ነው' 'እብድ ናት' በማለት እንድትደበቅ ተደርጋለች።" የቫዮሌት ቤተሰቦች ለመታሠቢያ ኃውልቱ ፈቀድ ሰጥተዋል። በሚቀጥሉት ሳምንታትም ረቂቁ ፀድቆ ወደ ሥራ እንደሚገባ ይጠበቃል። መታሰቢያ በልጅነቷ ያደገችበት ደብሊን ውስጥ የሚገኘው የሜሪዬን አደባባይ እንዲሆንም ሐሳብ ቀርቧል። ደብዳቤ ለቸርችል የቫዮሌት ታሪክ ወደ አደባባይ ብቅ ያለው በፈረንጆቹ 2014 አርቲኢ የተሰኘው ራድዮ ጣቢያ በሠራው ዘጋቢ ቅንብር ምክንያት ነው። ዘገባው 'ሙሶሊኒ ላይ የተኮሰችው ሴት' ከተሰኘው መፅሐፍ ላይ የተወሰደ ነው። ታሪኳ ላይ እንደተመዘገበው ቫዮሌት ከቅዱስ አንድሩ ሆስፒታል እንድትለቀቅ በወቅቱ ለነበሩ ኃያላን መሪዎች ደብዳቤ ፅፋ ነበር። ከእነዚህ መካከል የአሁኗ የእንግሊዝ ንግሥት ኤሊዛቤት ይገኙበታል። ሌላኛው ደብዳቤ የተላከው በወቅቱ የእንግሊዝ መሪ ለነበሩት ዊንስተን ቸርችል ነበር። ቸርችል በደብሊን ከተማ ባደጉ ወቅት ከቫዮሌት ጋር እውቅና ሳይኖራቸው አይቀርም ይላል ታሪኳን የሚዘግበው መፅሐፍ። ለዊንስተን ቸርችል የተፃፈው ደብዳቤ አሁንም አለ። ነገር ግን በወቅቱ ደብዳቤው ለቸርችል ሊደርስ አልቻለም። የራድዮ ዘገባው አዘጋጆች ወደ ጣልያን ሄደው በሠሩት ጥናት መሠረት ሙሶሊኒ ላይ ከተሞከሩ ግድያዎች መካከል ብዙ መረጃ የተሰበሰበው በቫዮሌት ዙሪያ ነው። "ይህን ድርጊት የፈፀመው ወንድ ቢሆን ኖሮ ይሄን ሃውልት ወይም ሌላ መታሰቢያ ተሠርቶለት ነበር። እሷ ሴት ስለነበረች ታሠረች። እኛ ታሪኩን ለሕዝብ ይፋ በማድረጋችን ደስተኞች ነን" ይላሉ የዘገባው አዘጋጆች። ቤኒቶ ሙሶሊኒ ማነው? የሙሶሊኒ ብሔራዊ ፋሺስት ፓርቲ ጣልያን ውስጥ ወደ ሥልጣን የመጣው ከአንደኛው ዓለም ጦርነት በኋላ ነው። 'ብላክሸርትስ' በተሰኙ ታጣቂዎች የሚደገፈው ፖርቲ ተቀናቃኞችን በኃይል ያስፈራራ ነበር። ፋሺስቱ ፓርቲ በ1920ዎቹ ሥልጣን ከያዘ በኋላ ዴሞክራሲያዊ የሚባሉ ተቋማትን አፈራረሰ። ሙሶሊኒ የጣልያን አምባገነናዊ መሪ ሆነው የተሾሙት በፈረንጆቹ 1925 ነበር። ሙሶሊኒ በስፔን የእርስ በርስ ጦርነት ወቅት የጁኔራል ፍራንቺስኮ ፍራንኮ ደጋፊ ነበር። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ደግሞ የአዶልፍ ሂትለር ቀኝ እጅ ነበር። ሙሶሊኒ የሂትለርን አንዳንድ ፖሊሲዎች ወስዶ በ1938 የጣልያኑ አይሁዳዊያን ሙሉ በሙሉ መብታቸው እንዲገፈፍ አድርጎ ነበር። በአይሁዶች ጅምላ ጭፍጨፋ [ሆሎኮስት] ወቅት ከ7 ሺህ 500 በላይ የጣልያን አይሁዶች እንደተገደሉ ይታመናል። ኢትዮጵያ በጣልያን ለሁለተኛ ጊዜ የተወረረችው በሙሶሊኒ አምባገነናዊ ሥርዓት ወቅት ነበር። ሙሶሊኒ ከምዕራባዊያን ጦር ለማምለጥ ሲሞክር በጣሊያን ነፃ አውጭዎች ተይዞ የተገደለው በፈረንጆቹ 1945 ነው።
ቤኒቶ ሙሶሊኒ ላይ የተኮሰችው አየርላንዳዊት ጊዜው በፈረንጆቹ ሚያዝያ 7 1926 ነበር። ቦታው ደግሞ የጣልያኗ መዲና ሮም። የሃገሬው ሰው በ20ኛው ክፍለ ዘመን ከነበሩ ኃያላን መካከል አንዱ የነበረውን ግለሰብ ለማየት ተኮልኩሏል። አንዲት አየርላንዳዊት ሴት ግን በሰውዬው ወሬ ብዙም አልተማረከችም። ዓላማዋ ሌላ ነበር። ድንገት የተኩስ ድምፅ ተሰማ። ሰው ወዲያ ወዲህ ተበታተነ። ለተሰበሰበው ሰው መልዕክቱን ሲያስተላልፍ የነበረው ቤኒቶ ሙሴሊኒም ወደኋላ ተዘረጋ። ጥይቷ የፈለቀችው ከአየርላንዳዊቷ ሴት አፈሙዝ ነበር። ዒላማዋን አልሳተችም። የሙሶሊኒን አፍንጫ ቦረሸችው። ሙሶሊኒ ግን አልሞተም። የጣልያኑ መሪ ከተቃጣበት የግድያ ሙከራ መትረፍ ቻለ። አውሮፓውያን በ20ኛው ክፍለ ዘመን ፋሺስታዊነትን ለመከላከል ከፈፀሟቸው ድርጊቶች መካከል የቫዮሌት ጊብሰን ድርጊት ሁሌም ይነሳል። ሙሶሊኒን ለመግደል ጥረት ካደረጉ አራት ሰዎች መካከል የተሻለ ሙከራ ያደረገችው እሷ ናት። አየርላንዳዊቷ ሙሶሊኒን ለመግደል ሙከራ ካደረገች እነሆ መቶ ዓመት ሊደፍን ጥቂት ዓመታት ይቀሩታል። ይህን ለማሰብ ደብሊን ውስጥ መታሰቢያ እንዲቆምላት ሥራዎች ተጀምረዋል። ቫዮሌት ሙሶሊኒ ላይ ሶስት ጥይቶች ተኩሳለች። አራተኛውን ልትለቀው ስትል ግን ሽጉጧ ነከሰ። ይሄኔ የሙሶሊኒ ጠባቂዎች የከበቧት። የከተማዋ ፖሊስ ጣልቃ ገብቶ በቁጥጥር ሥር ባያውሏት ኖሮ የጠባቂዎቹ ጡጫ ሲሳይ ትሆን ነበር። ጣልያን ውስጥ ታሥራ ከቆች በኋላ ወደ እንግሊዝ እንድትሄድ ተደረገ። ይህ የሆነው ጣልያን ውስጥ የፍርድ ሂደቱ ቢካሄድ ውርደት ይሆናል በሚል ነው ይባላል። ቫዮሌት እንግሊዝ ውስጥ ባለው የቅዱስ አንድሩ የአእምሮ ሕሙማን መታከሚያ ማዕከል ገብታ በስተመጨረሻ በፈረንጆቹ 1956 ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች። ከእንግሊዛዊ አየርላንዳዊ ከበርቴ ቤተሰብ የተወለደችው ቫዮሌት ክዊን ቪክቶሪያ ውስጥ ነበር የምትኖረው። አሁን የደብሊን ከተማ በስሟ መታሰቢያ እንዲቆም ረቂቅ አፅድቆ ወደ ሥራ ገብቷል። የከተማዋ አስተዳደር የሴትዬዋ ድርጊት በታሪክ መዝገብ ብዙም ባለመዘገቡ የሠራችውን 'ፀረ-ፋሺስት' ሥራ የሚዘክር መታሰቢያ ሊቆምላት ይገባል ብሏል። "የብሪታኒያ መንግሥትና ቤተሰቦቿ የሷን ድርጊት እንደ 'እብድ ሰው' ተግባር ሳይሆን እንደ ፖለቲካ ሊያዩት ይገባል" ይላል ረቂቁ። በጀግንነቷ ምክንያት የተሰቃየችው ረቂቁን ለደብሊን ከተማ ምክር ቤት ያቀረቡት ገለልተኛው የከተማው ምክር ቤት አባል ማኒክስ ፍሊን "ቫዮሌት ጊብሰን በአየርላንድና እንግሊዝ መንግሥታት የተረሳች ናት" ሲሉ ይከራከራሉ። "ልክ እንደበርካታ ሴቶች እጅግ ድፍረት የተሞላበት ድርጊት ብትፈፅምም ተገፍታለች" ሲሉ ለቢቢሲ ሰሜን አየርላንድ ጣቢያ ይናገራሉ። "ቫዮሌት ጊብሰን የሠራችው ሥራ የሚያሳፍር ነው' 'እብድ ናት' በማለት እንድትደበቅ ተደርጋለች።" የቫዮሌት ቤተሰቦች ለመታሠቢያ ኃውልቱ ፈቀድ ሰጥተዋል። በሚቀጥሉት ሳምንታትም ረቂቁ ፀድቆ ወደ ሥራ እንደሚገባ ይጠበቃል። መታሰቢያ በልጅነቷ ያደገችበት ደብሊን ውስጥ የሚገኘው የሜሪዬን አደባባይ እንዲሆንም ሐሳብ ቀርቧል። ደብዳቤ ለቸርችል የቫዮሌት ታሪክ ወደ አደባባይ ብቅ ያለው በፈረንጆቹ 2014 አርቲኢ የተሰኘው ራድዮ ጣቢያ በሠራው ዘጋቢ ቅንብር ምክንያት ነው። ዘገባው 'ሙሶሊኒ ላይ የተኮሰችው ሴት' ከተሰኘው መፅሐፍ ላይ የተወሰደ ነው። ታሪኳ ላይ እንደተመዘገበው ቫዮሌት ከቅዱስ አንድሩ ሆስፒታል እንድትለቀቅ በወቅቱ ለነበሩ ኃያላን መሪዎች ደብዳቤ ፅፋ ነበር። ከእነዚህ መካከል የአሁኗ የእንግሊዝ ንግሥት ኤሊዛቤት ይገኙበታል። ሌላኛው ደብዳቤ የተላከው በወቅቱ የእንግሊዝ መሪ ለነበሩት ዊንስተን ቸርችል ነበር። ቸርችል በደብሊን ከተማ ባደጉ ወቅት ከቫዮሌት ጋር እውቅና ሳይኖራቸው አይቀርም ይላል ታሪኳን የሚዘግበው መፅሐፍ። ለዊንስተን ቸርችል የተፃፈው ደብዳቤ አሁንም አለ። ነገር ግን በወቅቱ ደብዳቤው ለቸርችል ሊደርስ አልቻለም። የራድዮ ዘገባው አዘጋጆች ወደ ጣልያን ሄደው በሠሩት ጥናት መሠረት ሙሶሊኒ ላይ ከተሞከሩ ግድያዎች መካከል ብዙ መረጃ የተሰበሰበው በቫዮሌት ዙሪያ ነው። "ይህን ድርጊት የፈፀመው ወንድ ቢሆን ኖሮ ይሄን ሃውልት ወይም ሌላ መታሰቢያ ተሠርቶለት ነበር። እሷ ሴት ስለነበረች ታሠረች። እኛ ታሪኩን ለሕዝብ ይፋ በማድረጋችን ደስተኞች ነን" ይላሉ የዘገባው አዘጋጆች። ቤኒቶ ሙሶሊኒ ማነው? የሙሶሊኒ ብሔራዊ ፋሺስት ፓርቲ ጣልያን ውስጥ ወደ ሥልጣን የመጣው ከአንደኛው ዓለም ጦርነት በኋላ ነው። 'ብላክሸርትስ' በተሰኙ ታጣቂዎች የሚደገፈው ፖርቲ ተቀናቃኞችን በኃይል ያስፈራራ ነበር። ፋሺስቱ ፓርቲ በ1920ዎቹ ሥልጣን ከያዘ በኋላ ዴሞክራሲያዊ የሚባሉ ተቋማትን አፈራረሰ። ሙሶሊኒ የጣልያን አምባገነናዊ መሪ ሆነው የተሾሙት በፈረንጆቹ 1925 ነበር። ሙሶሊኒ በስፔን የእርስ በርስ ጦርነት ወቅት የጁኔራል ፍራንቺስኮ ፍራንኮ ደጋፊ ነበር። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ደግሞ የአዶልፍ ሂትለር ቀኝ እጅ ነበር። ሙሶሊኒ የሂትለርን አንዳንድ ፖሊሲዎች ወስዶ በ1938 የጣልያኑ አይሁዳዊያን ሙሉ በሙሉ መብታቸው እንዲገፈፍ አድርጎ ነበር። በአይሁዶች ጅምላ ጭፍጨፋ [ሆሎኮስት] ወቅት ከ7 ሺህ 500 በላይ የጣልያን አይሁዶች እንደተገደሉ ይታመናል። ኢትዮጵያ በጣልያን ለሁለተኛ ጊዜ የተወረረችው በሙሶሊኒ አምባገነናዊ ሥርዓት ወቅት ነበር። ሙሶሊኒ ከምዕራባዊያን ጦር ለማምለጥ ሲሞክር በጣሊያን ነፃ አውጭዎች ተይዞ የተገደለው በፈረንጆቹ 1945 ነው።
https://www.bbc.com/amharic/news-56145284
0business
ኮሮናቫይረስና የነዳጅ ዘይት ምን አገናኛቸው?
ኮሮናቫይረስ የማይነካው ነገር እንደሌለ እየታየ ነው። በየሰበብ አስባቡ እያሻቀበ የነበረውን ነዳጅ ዘይትን ሊነካው ዳርዳር እያለ ነው። በሽታው አሳሳቢ ደረጃ ላይ በደረሰበት በአሁኑ ጊዜ የዓለማችን ትልልቆቹ የነዳጅ አምራች አገራት በሽታው ካስከተለው ችግር ለመቋቋም በሚያደርጉት ጥረት ውስጥ ምርታቸው ሊቀንስ ይችላል እየተባለ ነው። የነዳጅ ዋጋን ለመደገፍ እርምጃ እንዲወሰድ እየተጠየቀ ባለበት በአሁኑ ወቅት የነዳጅ አምራች አገራት ማህበር የሆነው ኦፔክ እና አጋሮቹ በዚህ ሳምንት ስብሰባ እንደሚቀመጡ እየተጠበቀ ነው። • ኮሮናቫይረስ፡ ኢትዮጵያዊያን ተማሪዎች በቻይና • አባቱ በኮሮናቫይረስ የተጠረጠረው አካል ጉዳተኛ ታዳጊ ሞተ በጥር ወር መጀመሪያ ላይ የነዳጅ ዋጋ በዓመት ውስጥ ከታየው ከፍ ብሎ በ20 በመቶ ካሻቀበ በኋላ አሽቆልቁሎ ዝቅተኛው ዋጋው ላይ ይገኛል። ስለምን ይህ የቫይረስ ወረርሽኝ እንዲህ ያለው ከፍተኛ ተጽእኖን በዓለም አቀፉ የኃይል ገበያ ላይ ሊያስከትል ቻለ? የቻይናዊያን አዲስ ዓመት የበዓል ጊዜ በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍል በበሽታው ምክንያት በመራዘሙና የጉዞ እገዳ በመደረጉ ፋብሪካዎች፣ ቢሮዎችና መደብሮች ዝግ ሆነው ይገኛሉ። ይህም ማለት አስከ 14 ሚሊዮን በርሜሎችን በቀን ውስጥ የምትጠቀመውና የዓለማችን ትልቋ የድፍድፍ ነዳጅ ገዢ አገር የሆነችው ቻይና ማሽኖቿን ለማንቀሳቀስ፣ ለተሽከርካሪዎችና ለኤሌክትሪክ ኃይል ወትሮ ከምትፈልገው ነዳጅ ዘይት በእጅጉ የቀነሰውን እንድትጠቀም አድርጓታል። በወረርሽኙ ምክንያት በርካታ አየር መንገዶች ወደ ቻይና የሚያደርጓቸውን በረራዎች በማቋረጣቸው የተነሳና በቻይና ውስጥ ባለው የጉዞ እገዳ ሳቢያ በረራዎች በመቀነሳቸው ለአውሮፕላን ነዳጅ ያለው ፍላጎት በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሰዋል ተብሎ ይታሰባል። • ኮሮናቫይረስ፡ ምን ያህል አሳሳቢ ነው? • ካሜሮናዊው በኮሮናቫይረስ በመያዝ የመጀመሪያው አፍሪካዊ ሆነ ብሉምበርግ በዚህ ሳምንት እንደዘገበው የቻይና ዕለታዊ የድፍድፍ ነዳጅ ፍጆታ በ20 በመቶ ቀንሷል። ይህም ማለት ብሪታኒያና ጣሊያን በአንድ ላይ በቀን የሚያስፈልጋቸውን ነው። በዚህም ሳቢያ በቻይና መንግሥት የሚተዳደረው የእስያ አህጉር ትልቁ የነዳጅ ማጣሪያ ሲኖፔክ በየቀኑ የሚያጣራውን የድፍድፍ ነዳጅ መጠን በ600 ሺህ በርሜሎች ቀንሷል። ይህም ከሥራው 12 በመቶው አቁሟል ማለት ሲሆን ከ10 ዓመታት በላይ ባለው ጊዜ ውስጥ ከፍተኛው ቅናሽ ነው። በነዳጅ ዘይት ላይ የታየው ከፍተኛ ቅናሽ የኃይል ኢንዱስትሪውን በከፍተኛ ደረጃ እንዳሳሰበው የዘርፉ ባለሙያዎች እየተናገሩ ነው። በነዳጅ ፍላጎት ላይ የተከሰተው ከፍተኛ ቅናሽ በቻይና ውስጥ የተከሰተውን የሥራ መቀዛቀዝን የሚያሳይ ግልጽ ምልክት ነው። በተጨማሪም ባለፉት 30 ዓመታት ውስጥ ቻይናን ካጋጠማት የኢኮኖሚ ዕድገት መቀነስ ክስተት ውስጥ ዝቅተኛው ማጋጠሙ ደግሞ የነዳጅ ፍጆታዋን የበለጠ ይቀንሰዋል ተብሏል። የተባሉት በቻይና የሳይንስ አካዳሚ ውስጥ ተመራማሪ የሆኑነት ዣንግ ሚንግ እንደሚሉት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በዓመቱ መጀመሪያ ላይ ባሉት ሦስት ወራት የአገሪቱን ዓመታዊ የኢኮኖሚ ዕድገት ከ5 በመቶ በታች ሊያወርደው ይችላል። • "ኮሮናቫይረስ በአሜሪካ የሥራ ዕድልን ሊያሳድግ ይችላል" ያደጉት አገራት እድገታቸውን ለማጠናከር ትግል በሚያደርጉበት ጊዜ ቻይና የዓለማችን ሁለተኛዋ ግዙፍ ኢኮኖሚና ለዓለም የኢኮኖሚ ዕድገት አንቀሳቃሽ ሞተር ናት። የዓለም ገንዘብ ድርጅት ዳይሬክተር የሆኑት ክሪስታሊና ጆርጂዮቫ ባዚህ ሳምንት እንዳሉት ወረርሽኙ ቢያንስ ለአጭር ጊዜ የዓለም ኢኮኖሚ ዕድገትን ያቀዛቅዘዋል፤ ነገር ግን የወደፊቱን ለመናገር አሁን ጊዜው ገና እንደሆነም አመልክተዋል። እያሽቆለቆለ ያለውን የነዳጅ ዋጋ ለማሳደግ ታላላቆቹ የዓለም ነዳጅ ዘይት አምራቾች ለገበያ የሚያቀርቡትን ምርት በከፍተኛ መጠን ለመቀነስ በሚያደርጉት ስብሰባ ላይ እንደሚወያዩ እየተነገረ ነው። የኮሮናቫይረስ ክስተት ለነዳጅ የለውን ፍላጎት እንዲቀንስ በማድረጉ ምክንያት የነዳጅ አምራችና ላኪ አገራት ማኅበር የሆነው ኦፔክ አባል የሆነችው ኢራን ሰኞ ዕለት እየወደቀ ያለውን የነዳጅ ዋጋ ለመደገፍ እርምጃዎች እንዲወሰዱ በይፋ ጠይቃለች። የኦፔክ አባል አገራትና ሩሲያ በዚህ ሳምንት ያደርጉታል ተብሎ በሚጠበቀው ስብሰባ ላይ በቀን ለገበያ ከሚያርቡት የነዳጅ ምርት ከ500 ሺህ እስከ 1 ሚሊዮን በርሜል የሚደርሰውን ለመቀነስ ይወያያሉ ተብሏል።
ኮሮናቫይረስና የነዳጅ ዘይት ምን አገናኛቸው? ኮሮናቫይረስ የማይነካው ነገር እንደሌለ እየታየ ነው። በየሰበብ አስባቡ እያሻቀበ የነበረውን ነዳጅ ዘይትን ሊነካው ዳርዳር እያለ ነው። በሽታው አሳሳቢ ደረጃ ላይ በደረሰበት በአሁኑ ጊዜ የዓለማችን ትልልቆቹ የነዳጅ አምራች አገራት በሽታው ካስከተለው ችግር ለመቋቋም በሚያደርጉት ጥረት ውስጥ ምርታቸው ሊቀንስ ይችላል እየተባለ ነው። የነዳጅ ዋጋን ለመደገፍ እርምጃ እንዲወሰድ እየተጠየቀ ባለበት በአሁኑ ወቅት የነዳጅ አምራች አገራት ማህበር የሆነው ኦፔክ እና አጋሮቹ በዚህ ሳምንት ስብሰባ እንደሚቀመጡ እየተጠበቀ ነው። • ኮሮናቫይረስ፡ ኢትዮጵያዊያን ተማሪዎች በቻይና • አባቱ በኮሮናቫይረስ የተጠረጠረው አካል ጉዳተኛ ታዳጊ ሞተ በጥር ወር መጀመሪያ ላይ የነዳጅ ዋጋ በዓመት ውስጥ ከታየው ከፍ ብሎ በ20 በመቶ ካሻቀበ በኋላ አሽቆልቁሎ ዝቅተኛው ዋጋው ላይ ይገኛል። ስለምን ይህ የቫይረስ ወረርሽኝ እንዲህ ያለው ከፍተኛ ተጽእኖን በዓለም አቀፉ የኃይል ገበያ ላይ ሊያስከትል ቻለ? የቻይናዊያን አዲስ ዓመት የበዓል ጊዜ በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍል በበሽታው ምክንያት በመራዘሙና የጉዞ እገዳ በመደረጉ ፋብሪካዎች፣ ቢሮዎችና መደብሮች ዝግ ሆነው ይገኛሉ። ይህም ማለት አስከ 14 ሚሊዮን በርሜሎችን በቀን ውስጥ የምትጠቀመውና የዓለማችን ትልቋ የድፍድፍ ነዳጅ ገዢ አገር የሆነችው ቻይና ማሽኖቿን ለማንቀሳቀስ፣ ለተሽከርካሪዎችና ለኤሌክትሪክ ኃይል ወትሮ ከምትፈልገው ነዳጅ ዘይት በእጅጉ የቀነሰውን እንድትጠቀም አድርጓታል። በወረርሽኙ ምክንያት በርካታ አየር መንገዶች ወደ ቻይና የሚያደርጓቸውን በረራዎች በማቋረጣቸው የተነሳና በቻይና ውስጥ ባለው የጉዞ እገዳ ሳቢያ በረራዎች በመቀነሳቸው ለአውሮፕላን ነዳጅ ያለው ፍላጎት በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሰዋል ተብሎ ይታሰባል። • ኮሮናቫይረስ፡ ምን ያህል አሳሳቢ ነው? • ካሜሮናዊው በኮሮናቫይረስ በመያዝ የመጀመሪያው አፍሪካዊ ሆነ ብሉምበርግ በዚህ ሳምንት እንደዘገበው የቻይና ዕለታዊ የድፍድፍ ነዳጅ ፍጆታ በ20 በመቶ ቀንሷል። ይህም ማለት ብሪታኒያና ጣሊያን በአንድ ላይ በቀን የሚያስፈልጋቸውን ነው። በዚህም ሳቢያ በቻይና መንግሥት የሚተዳደረው የእስያ አህጉር ትልቁ የነዳጅ ማጣሪያ ሲኖፔክ በየቀኑ የሚያጣራውን የድፍድፍ ነዳጅ መጠን በ600 ሺህ በርሜሎች ቀንሷል። ይህም ከሥራው 12 በመቶው አቁሟል ማለት ሲሆን ከ10 ዓመታት በላይ ባለው ጊዜ ውስጥ ከፍተኛው ቅናሽ ነው። በነዳጅ ዘይት ላይ የታየው ከፍተኛ ቅናሽ የኃይል ኢንዱስትሪውን በከፍተኛ ደረጃ እንዳሳሰበው የዘርፉ ባለሙያዎች እየተናገሩ ነው። በነዳጅ ፍላጎት ላይ የተከሰተው ከፍተኛ ቅናሽ በቻይና ውስጥ የተከሰተውን የሥራ መቀዛቀዝን የሚያሳይ ግልጽ ምልክት ነው። በተጨማሪም ባለፉት 30 ዓመታት ውስጥ ቻይናን ካጋጠማት የኢኮኖሚ ዕድገት መቀነስ ክስተት ውስጥ ዝቅተኛው ማጋጠሙ ደግሞ የነዳጅ ፍጆታዋን የበለጠ ይቀንሰዋል ተብሏል። የተባሉት በቻይና የሳይንስ አካዳሚ ውስጥ ተመራማሪ የሆኑነት ዣንግ ሚንግ እንደሚሉት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በዓመቱ መጀመሪያ ላይ ባሉት ሦስት ወራት የአገሪቱን ዓመታዊ የኢኮኖሚ ዕድገት ከ5 በመቶ በታች ሊያወርደው ይችላል። • "ኮሮናቫይረስ በአሜሪካ የሥራ ዕድልን ሊያሳድግ ይችላል" ያደጉት አገራት እድገታቸውን ለማጠናከር ትግል በሚያደርጉበት ጊዜ ቻይና የዓለማችን ሁለተኛዋ ግዙፍ ኢኮኖሚና ለዓለም የኢኮኖሚ ዕድገት አንቀሳቃሽ ሞተር ናት። የዓለም ገንዘብ ድርጅት ዳይሬክተር የሆኑት ክሪስታሊና ጆርጂዮቫ ባዚህ ሳምንት እንዳሉት ወረርሽኙ ቢያንስ ለአጭር ጊዜ የዓለም ኢኮኖሚ ዕድገትን ያቀዛቅዘዋል፤ ነገር ግን የወደፊቱን ለመናገር አሁን ጊዜው ገና እንደሆነም አመልክተዋል። እያሽቆለቆለ ያለውን የነዳጅ ዋጋ ለማሳደግ ታላላቆቹ የዓለም ነዳጅ ዘይት አምራቾች ለገበያ የሚያቀርቡትን ምርት በከፍተኛ መጠን ለመቀነስ በሚያደርጉት ስብሰባ ላይ እንደሚወያዩ እየተነገረ ነው። የኮሮናቫይረስ ክስተት ለነዳጅ የለውን ፍላጎት እንዲቀንስ በማድረጉ ምክንያት የነዳጅ አምራችና ላኪ አገራት ማኅበር የሆነው ኦፔክ አባል የሆነችው ኢራን ሰኞ ዕለት እየወደቀ ያለውን የነዳጅ ዋጋ ለመደገፍ እርምጃዎች እንዲወሰዱ በይፋ ጠይቃለች። የኦፔክ አባል አገራትና ሩሲያ በዚህ ሳምንት ያደርጉታል ተብሎ በሚጠበቀው ስብሰባ ላይ በቀን ለገበያ ከሚያርቡት የነዳጅ ምርት ከ500 ሺህ እስከ 1 ሚሊዮን በርሜል የሚደርሰውን ለመቀነስ ይወያያሉ ተብሏል።
https://www.bbc.com/amharic/news-51368390
5sports
በርካታ ኢትዮጵያውያን የሚጠበቁበት የቤልግሬዱ የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና
ሰርቢያ ቤልግሬድ ውስጥ ዛሬ ከመጋቢት 9 ተጀምሮ አስከ 11/2014 ዓ.ም በሚቆየው የዓለም የቤት ውስጥ የአትሌቲክስ ሻምፒዮና አፍሪካዊያን አትሌቶች ሜዳሊያ ያገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል። ኬንያዊው አትሌት ፈርዲናንድ ኦሙርዋ ኦማንያላ ከእነዚህ መካከል አንዱ ሲሆን የዩሴይን ቦልትን የ100 ሜትር የዓለም ክብረወሰን መስበር እንደሚችል ተናግሯል። ኬንያዊው አትሌት በሰርቢያው ሻምፒዮና ውድድሩን 60 ሜትር ይጀምራል። የ26 ዓመቱ አትሌት በ9.77 በሆነ ሰከንድ የአፍሪካን የ100 ሜትር ክብረወሰን በእጁ አስገብቷል። በአጭር ርቀት መሻሻል ካሳየ የቦልትን ክብረ ወሰን (9.58 ሰከንድ) ለመስበር እንደሚረዳው ያምናል። "ምንም የማይቻል ነገር የለም ብዬ አምናለሁ። የዓለም ክብረ ወሰን የሚሳካ ነገር ነው" ሲል ኦማንያላ ለቢቢሲ ስፖርት አፍሪካ ተናግሯል። "ይህን ክብረ ወሰን መስበር የሚችል ሰው ካለ እኔ ነኝ ብዬ አምናለሁ።'' "የአፍሪካን ክብረ ወሰን ተመልከቱ። ሩጫ ስጀምር ሰዎች በቅርቡ አይሰበርም ብለው አስበው ነበር። ይህን ግን ባለፈው ዓመት አሳክቻለሁ።'' ይህም የኦማንያላ ክብረወሰን የምንጊዜም ፈታኝ ሰዓቶች ስምንተኛው አድርጎታል። ይህን ግን ያሳካው የ14 ወራት የአበረታች መድኃኒት እገዳ በ2017 ከተጣለበት በኋላ ነው። መድኃኒቱ የተገኘበት በውስጡ ስቴሮይድ አለበት ያለውን የህመም ማስታገሻ ከወሰደ በኋላ መሆኑን ጠቅሶ "በሁኔታው ተጎድቻለሁ" ብሏል። ሻምፒዮን ለመሆን ጣሊያናዊውን የ100 ሜትር የኦሊምፒክ ሻምፒዮን ማርሴል ጃኮብስን እና የወቅቱን የቤት ውስጥ ሻምፒዮን አሜሪካዊውን ክርስቲያን ኮልማንን ማሸነፍ ይኖርበታል። በቤልግሬድ የሚወዳደሩ ሌሎች አፍሪካውያንስ? በ2022ቱ የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ከ137 አገራት የተውጣጡ 680 አትሌቶች ይሳተፋሉ። ውድድሩ ከመጋቢት 9 እስከ 11/2014 ሰርኒያ ቤልግሬድ ውስጥ ይካሄዳል። ስድስቱ ተጠባቂ አፍሪካዊያን ሰለሞን ባረጋ (ኢትዮጵያ) - የ22 ዓመቱ አትሌት የ10,000 ሜትር የኦሊምፒክ ሻምፒዮን ነው። በ2018 በዓለም የቤት ውስጥ ውድድር በ3000 ሜትር ያገኘውን የብር ሜዳሊያ ለማሻሻል ይወዳደራል። ለሜቻ ግርማ (ኢትዮጵያ) - በ3000 ሜትር መሰናክል የዓለም እና የኦሊምፒክ የብር ሜዳሊያ አሸናፊ ነው። የ21 ዓመቱ አትሌት የ3000 ሜትር አሸናፊ ለመሆን ከሰለሞን ጋር ይፎካከራል። ሳሙኤል ተፈራ (ኢትዮጵያ) - የ1500ሜ የዓለም የቤት ውስጥ ክብረ ወሰን ባለቤት ሲሆን በ2018 በርሚንግሃም ላይ ያገኘውን የወርቅ ሜዳሊያ ለማስጠበቅ ይወዳደራል። ጉዳፍ ፀጋይ (ኢትዮጵያ) - የ5,000 ሜትር የኦሊምፒክ እና የ1500 ሜትር የዓለም ሻምፒዮና የነሐስ ሜዳሊያ አሸናፊዋ 24 ዓመቷ አትሌት በ1500 ሜትር ትጠበቃለች። ኢሴ ብሩሜ (ናይጄሪያ) - የኦሊምፒክ እና የዓለም ሻምፒዮና የነሐስ ሜዳሊያ አሸናፊዋ የ26 ዓመቷ አትሌት፣ የአፍሪካ ሻምፒዮን ናት። በሴቶች የአግድሞሽ ዝላይ ውድድር ትሳተፋለች። ሃሊማ ናካዪ (ኡጋንዳ) - የ27 ዓመቷ አትሌት በ2019 ዶሃ ላይ ባስመዘገበችው የ800 ሜትር የዓለም ሻምፒዮና ወርቅ ላይ ተጨማሪ ድል ለማስመዝገብ ትፎካከራለች። ያሲር ትሪኪ (አልጄሪያ) - ባለሦስትዮሽ ዝላይ (ትሪፕል ጃምፕ) በ16.95 ሜትር በመዝለል ከወቅቱ የዓለም ምርጥ 5ቱ ውስጥ ተካቷል።
በርካታ ኢትዮጵያውያን የሚጠበቁበት የቤልግሬዱ የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ሰርቢያ ቤልግሬድ ውስጥ ዛሬ ከመጋቢት 9 ተጀምሮ አስከ 11/2014 ዓ.ም በሚቆየው የዓለም የቤት ውስጥ የአትሌቲክስ ሻምፒዮና አፍሪካዊያን አትሌቶች ሜዳሊያ ያገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል። ኬንያዊው አትሌት ፈርዲናንድ ኦሙርዋ ኦማንያላ ከእነዚህ መካከል አንዱ ሲሆን የዩሴይን ቦልትን የ100 ሜትር የዓለም ክብረወሰን መስበር እንደሚችል ተናግሯል። ኬንያዊው አትሌት በሰርቢያው ሻምፒዮና ውድድሩን 60 ሜትር ይጀምራል። የ26 ዓመቱ አትሌት በ9.77 በሆነ ሰከንድ የአፍሪካን የ100 ሜትር ክብረወሰን በእጁ አስገብቷል። በአጭር ርቀት መሻሻል ካሳየ የቦልትን ክብረ ወሰን (9.58 ሰከንድ) ለመስበር እንደሚረዳው ያምናል። "ምንም የማይቻል ነገር የለም ብዬ አምናለሁ። የዓለም ክብረ ወሰን የሚሳካ ነገር ነው" ሲል ኦማንያላ ለቢቢሲ ስፖርት አፍሪካ ተናግሯል። "ይህን ክብረ ወሰን መስበር የሚችል ሰው ካለ እኔ ነኝ ብዬ አምናለሁ።'' "የአፍሪካን ክብረ ወሰን ተመልከቱ። ሩጫ ስጀምር ሰዎች በቅርቡ አይሰበርም ብለው አስበው ነበር። ይህን ግን ባለፈው ዓመት አሳክቻለሁ።'' ይህም የኦማንያላ ክብረወሰን የምንጊዜም ፈታኝ ሰዓቶች ስምንተኛው አድርጎታል። ይህን ግን ያሳካው የ14 ወራት የአበረታች መድኃኒት እገዳ በ2017 ከተጣለበት በኋላ ነው። መድኃኒቱ የተገኘበት በውስጡ ስቴሮይድ አለበት ያለውን የህመም ማስታገሻ ከወሰደ በኋላ መሆኑን ጠቅሶ "በሁኔታው ተጎድቻለሁ" ብሏል። ሻምፒዮን ለመሆን ጣሊያናዊውን የ100 ሜትር የኦሊምፒክ ሻምፒዮን ማርሴል ጃኮብስን እና የወቅቱን የቤት ውስጥ ሻምፒዮን አሜሪካዊውን ክርስቲያን ኮልማንን ማሸነፍ ይኖርበታል። በቤልግሬድ የሚወዳደሩ ሌሎች አፍሪካውያንስ? በ2022ቱ የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ከ137 አገራት የተውጣጡ 680 አትሌቶች ይሳተፋሉ። ውድድሩ ከመጋቢት 9 እስከ 11/2014 ሰርኒያ ቤልግሬድ ውስጥ ይካሄዳል። ስድስቱ ተጠባቂ አፍሪካዊያን ሰለሞን ባረጋ (ኢትዮጵያ) - የ22 ዓመቱ አትሌት የ10,000 ሜትር የኦሊምፒክ ሻምፒዮን ነው። በ2018 በዓለም የቤት ውስጥ ውድድር በ3000 ሜትር ያገኘውን የብር ሜዳሊያ ለማሻሻል ይወዳደራል። ለሜቻ ግርማ (ኢትዮጵያ) - በ3000 ሜትር መሰናክል የዓለም እና የኦሊምፒክ የብር ሜዳሊያ አሸናፊ ነው። የ21 ዓመቱ አትሌት የ3000 ሜትር አሸናፊ ለመሆን ከሰለሞን ጋር ይፎካከራል። ሳሙኤል ተፈራ (ኢትዮጵያ) - የ1500ሜ የዓለም የቤት ውስጥ ክብረ ወሰን ባለቤት ሲሆን በ2018 በርሚንግሃም ላይ ያገኘውን የወርቅ ሜዳሊያ ለማስጠበቅ ይወዳደራል። ጉዳፍ ፀጋይ (ኢትዮጵያ) - የ5,000 ሜትር የኦሊምፒክ እና የ1500 ሜትር የዓለም ሻምፒዮና የነሐስ ሜዳሊያ አሸናፊዋ 24 ዓመቷ አትሌት በ1500 ሜትር ትጠበቃለች። ኢሴ ብሩሜ (ናይጄሪያ) - የኦሊምፒክ እና የዓለም ሻምፒዮና የነሐስ ሜዳሊያ አሸናፊዋ የ26 ዓመቷ አትሌት፣ የአፍሪካ ሻምፒዮን ናት። በሴቶች የአግድሞሽ ዝላይ ውድድር ትሳተፋለች። ሃሊማ ናካዪ (ኡጋንዳ) - የ27 ዓመቷ አትሌት በ2019 ዶሃ ላይ ባስመዘገበችው የ800 ሜትር የዓለም ሻምፒዮና ወርቅ ላይ ተጨማሪ ድል ለማስመዝገብ ትፎካከራለች። ያሲር ትሪኪ (አልጄሪያ) - ባለሦስትዮሽ ዝላይ (ትሪፕል ጃምፕ) በ16.95 ሜትር በመዝለል ከወቅቱ የዓለም ምርጥ 5ቱ ውስጥ ተካቷል።
https://www.bbc.com/amharic/news-60788088
3politics
ምርጫ 2013፡ የምርጫ ውጤት በምርጫ ክልል ደረጃ ረቡዕና ሐሙስ ይገለጻል ተባለ
ሰኞ ዕለት የተካሄደው ምርጫ ውጤት በምርጫ ክልል ደረጃ ረቡዕና ሐሙስ ይፋ እንደሚደረግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ አስታወቀ። ቆጠራ በተጠናቀቀባቸው ምርጫ ጣቢዎች ውጤቶች ከማክሰኞ ንጋት ጀምሮ ይፋ ሲደረጉ የቆዩ ሲሆን፤ የምርጫ ጣቢያ ውጤቶች ወደ ምርጫ ክልሎች ከተላኩ በኋላ "ነገ [ረቡእ] እና ከነገ ወዲያ [ሐሙስ] የምርጫ ክልል ውጤት ይፋ ይደረጋል" ሲሉ የቦርዱ የኮምዩኒኬሽን አማካሪ ሶሊያና ሽመልስ ተናግረዋል። የምርጫ ክልል ውጤቶች ደግሞ ከመላው አገሪቱ ወደ ማዕከል ገብተው አስፈላጊው ማጣራት ከተካሄደ በኋላ ቦርዱ አጠቃላይ ውጤቱን ይፋ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማክሰኞ ከሰዓት በበኋላ በሰጠው መግለጫ እስከ ቀጣይ 10 ቀናት ድረስ ቢያንስ ጊዜያዊ የሆነ የአጠቃላይ የምርጫ ውጤት ይፋ አድርጋለሁ ብሏል። ከዚህ ባሻገር የተለያዩ ግለሰቦች የምርጫ ጣቢያ ውጤቶችን በመያዝ የመጨረሻ ውጤት በማስመሰል ይፋ ከማድረግ ተግራባቸው እንዲቆጠቡ ቦርዱ ጠይቋል። የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ኮምዩኒኬሽን አማካሪ ሶሊያና ሽመልስ በርካታ አክቲቪስቶች እና ማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ከአንድ ምርጫ ጣቢያ የተገኘ ውጤን መሠረት በማድረግ 'የዚህ ምርጫ ክልል አሸናፊ እከሌ ነው' እያሉ ሲውጁ ተመልክተናል ብለዋል። የምርጫ ውጤቶችን ይፋ ማድረግ የሚችለው ምርጫ ቦርድ ብቻ መሆኑን ያስታወሱት ሶሊያና፤ መሰል ተግባራት "ተቀባይነት የሌለው እና ወንጀል ጭምር ነው" ብለዋል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምን ያክል ሰዎች ድምጽ ለመስጥት ወጡ የሚለው አሃዝ እስካሁን እንደሌለው በመጥቀስ በርካታ ቁጥር ያለው ሰው ግን ድምጽ ለመስጥ መውጣቱን መገንዘቡ ተገልጿል። "በከተማም በገጠርም በርካታ ሕዝብ ድምጽ ለመስጥት ወጥቷል። ይህም በጣም አስደሳች ነበር" ብለዋል የቦርዱ የኮምዩኒኬሽን አማካሪ ሶሊያና ሽመልስ። ሰኞ ሰኔ 14/2013 ዓ.ም በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍሎች በተካሄደው ምርጫ የተሰጡትን ድምጾች በመቁጠር ከማክሰኞ ጠዋት ጀምሮ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ ውጤቶች ይፋ እየተደረጉ ሲሆን በበርካታ ቦታዎች ውጤቶች ታውቀዋል። ከዚህ ባሻገር በተለያዩ አካባቢዎች ባጋጠሙ መስተጓጎሎች ሰኞ ዕለት ድምጽ ሳይሰጥባቸው በቀሩ አካባቢዎች ዛሬ ማክሰኞ ዕለት መራጮች ድምጽ ሰሰጡ ውለዋል። ከምርጫው ጋር በተያያዘ ወደ ኢትዮጵያ ከገቡ በኋላ በሆቴል ክፍላቸው ውስጥ ሕይወታቸው አልፎ ስለተገኙት አሜሪካዊ ግለሰብን በተመለከተም ቦርዱ ክስተቱን ከፖሊስ መስማቱን ተናግረዋል። "ግለሰቡ በሆቴል ክፍላቸው ሕይወታቸው አልፎ መገኘቱን ሰምተናል። ሆቴል ክፍላቸው ወድቀው ነው የተገኙት። እጅግ አሳዛኝ አጋጣሚ ነው" ካሉ በኋላ የግለሰቡ አሟሟት ከምርጫው ጋር የተገናኘ አለመሆኑን ተናግረዋል። ሶሊያና ግለሰቡ ዓለም አቀፍ የምርጫ ታዛቢ አለመሆናቸውን ጠቅሰው በእንግድነት ከምርጫ ቦርድ ባጅ ወስደው እንደነበረ ተናግረዋል። "የመታዘብ ሥራን የሚሰሩ አልነበሩም። ለእንግዶች የሚሰጥ ባጅ ነው የወሰዱት። ከካርተር ሴንተር ለመታዘብ የመጣ የለም" ብለዋል። ባለፈው ዓመት ሊካሄድ ታስቦ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ወደዚህ ዓመት ተሸጋግሮ በሁለት ዙሮች ምርጫው እንዲካሄድ በተወሰነው መሰረት የመጀመሪያው ዙር ምርጫ ሰኞ ሰኔ 14/2013 ዓ.ም ተካሂዷል። ሁለተኛው ዙር ምርጫ በሶማሌና በሐረሪ ክልሎች እንዲሁም በሌሎች አንዳንድ አካባቢዎች ከሁለት ወራት በኋላ ጳጉሜ 01/2013 ዓ.ም ይካሄዳል።
ምርጫ 2013፡ የምርጫ ውጤት በምርጫ ክልል ደረጃ ረቡዕና ሐሙስ ይገለጻል ተባለ ሰኞ ዕለት የተካሄደው ምርጫ ውጤት በምርጫ ክልል ደረጃ ረቡዕና ሐሙስ ይፋ እንደሚደረግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ አስታወቀ። ቆጠራ በተጠናቀቀባቸው ምርጫ ጣቢዎች ውጤቶች ከማክሰኞ ንጋት ጀምሮ ይፋ ሲደረጉ የቆዩ ሲሆን፤ የምርጫ ጣቢያ ውጤቶች ወደ ምርጫ ክልሎች ከተላኩ በኋላ "ነገ [ረቡእ] እና ከነገ ወዲያ [ሐሙስ] የምርጫ ክልል ውጤት ይፋ ይደረጋል" ሲሉ የቦርዱ የኮምዩኒኬሽን አማካሪ ሶሊያና ሽመልስ ተናግረዋል። የምርጫ ክልል ውጤቶች ደግሞ ከመላው አገሪቱ ወደ ማዕከል ገብተው አስፈላጊው ማጣራት ከተካሄደ በኋላ ቦርዱ አጠቃላይ ውጤቱን ይፋ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማክሰኞ ከሰዓት በበኋላ በሰጠው መግለጫ እስከ ቀጣይ 10 ቀናት ድረስ ቢያንስ ጊዜያዊ የሆነ የአጠቃላይ የምርጫ ውጤት ይፋ አድርጋለሁ ብሏል። ከዚህ ባሻገር የተለያዩ ግለሰቦች የምርጫ ጣቢያ ውጤቶችን በመያዝ የመጨረሻ ውጤት በማስመሰል ይፋ ከማድረግ ተግራባቸው እንዲቆጠቡ ቦርዱ ጠይቋል። የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ኮምዩኒኬሽን አማካሪ ሶሊያና ሽመልስ በርካታ አክቲቪስቶች እና ማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ከአንድ ምርጫ ጣቢያ የተገኘ ውጤን መሠረት በማድረግ 'የዚህ ምርጫ ክልል አሸናፊ እከሌ ነው' እያሉ ሲውጁ ተመልክተናል ብለዋል። የምርጫ ውጤቶችን ይፋ ማድረግ የሚችለው ምርጫ ቦርድ ብቻ መሆኑን ያስታወሱት ሶሊያና፤ መሰል ተግባራት "ተቀባይነት የሌለው እና ወንጀል ጭምር ነው" ብለዋል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምን ያክል ሰዎች ድምጽ ለመስጥት ወጡ የሚለው አሃዝ እስካሁን እንደሌለው በመጥቀስ በርካታ ቁጥር ያለው ሰው ግን ድምጽ ለመስጥ መውጣቱን መገንዘቡ ተገልጿል። "በከተማም በገጠርም በርካታ ሕዝብ ድምጽ ለመስጥት ወጥቷል። ይህም በጣም አስደሳች ነበር" ብለዋል የቦርዱ የኮምዩኒኬሽን አማካሪ ሶሊያና ሽመልስ። ሰኞ ሰኔ 14/2013 ዓ.ም በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍሎች በተካሄደው ምርጫ የተሰጡትን ድምጾች በመቁጠር ከማክሰኞ ጠዋት ጀምሮ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ ውጤቶች ይፋ እየተደረጉ ሲሆን በበርካታ ቦታዎች ውጤቶች ታውቀዋል። ከዚህ ባሻገር በተለያዩ አካባቢዎች ባጋጠሙ መስተጓጎሎች ሰኞ ዕለት ድምጽ ሳይሰጥባቸው በቀሩ አካባቢዎች ዛሬ ማክሰኞ ዕለት መራጮች ድምጽ ሰሰጡ ውለዋል። ከምርጫው ጋር በተያያዘ ወደ ኢትዮጵያ ከገቡ በኋላ በሆቴል ክፍላቸው ውስጥ ሕይወታቸው አልፎ ስለተገኙት አሜሪካዊ ግለሰብን በተመለከተም ቦርዱ ክስተቱን ከፖሊስ መስማቱን ተናግረዋል። "ግለሰቡ በሆቴል ክፍላቸው ሕይወታቸው አልፎ መገኘቱን ሰምተናል። ሆቴል ክፍላቸው ወድቀው ነው የተገኙት። እጅግ አሳዛኝ አጋጣሚ ነው" ካሉ በኋላ የግለሰቡ አሟሟት ከምርጫው ጋር የተገናኘ አለመሆኑን ተናግረዋል። ሶሊያና ግለሰቡ ዓለም አቀፍ የምርጫ ታዛቢ አለመሆናቸውን ጠቅሰው በእንግድነት ከምርጫ ቦርድ ባጅ ወስደው እንደነበረ ተናግረዋል። "የመታዘብ ሥራን የሚሰሩ አልነበሩም። ለእንግዶች የሚሰጥ ባጅ ነው የወሰዱት። ከካርተር ሴንተር ለመታዘብ የመጣ የለም" ብለዋል። ባለፈው ዓመት ሊካሄድ ታስቦ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ወደዚህ ዓመት ተሸጋግሮ በሁለት ዙሮች ምርጫው እንዲካሄድ በተወሰነው መሰረት የመጀመሪያው ዙር ምርጫ ሰኞ ሰኔ 14/2013 ዓ.ም ተካሂዷል። ሁለተኛው ዙር ምርጫ በሶማሌና በሐረሪ ክልሎች እንዲሁም በሌሎች አንዳንድ አካባቢዎች ከሁለት ወራት በኋላ ጳጉሜ 01/2013 ዓ.ም ይካሄዳል።
https://www.bbc.com/amharic/news-57554222
2health
በኒው ዚላንድ ሰዎች በፍቃዳቸው እንዲሞቱ የሚደነግግ ሕግ ሊወጣ ነው
በኒው ዚላንድ በጠና የታመሙ ሰዎች በፍቃዳቸው እንዲሞቱ የሚደነግግ ሕግ ሊወጣ ነው። ባለፈው ወር በተካሄደ ሕዝበ ውሳኔ 65.2% መራጮች የፍቃድ ሞትን ደግፈዋል። ዩትኔዝያ ወይም የፈቃድ ሞት በጠና የታመሙ ወይም ከስድስት ወር በላይ እንደማይኖሩ የተነገራቸው ሰዎች በህክምና እርዳታ ሕይወታቸው እንዲያልፍ የሚደረግበት ሂደት ነው። ሕጉ በቀጣዩ ዓመት ጥቅምት ወር ጸድቆ ይተገበራል ተብሎ ይጠበቃል። ኒው ዚላንድ ሕጉን ካጸደቀች የፈቃድ ሞት ከሚተገበርባቸው ጥቂት አገሮች አንዷ ትሆናለች። ዩትኔዝያ ከተፈቀደባቸው አገሮች ኔዘርላንድ እና ካናዳ ይጠቀሳሉ። ኒው ዚላንዳውያን ባለፈው ወር መሪያቸውን ሲመርጡ ስለ ፈቃድ ሞት እና ዕጸ ፋርስ ሕዝበ ውሳኔ አድርገዋል። ዕጸ ፋርስን ለመዝናኛ መጠቀም ሕጋዊ እንዲሆን ድምጽ የሰጡት 46.1% ብቻ ሲሆኑ፤ 53.1% ተቃውመዋል። የፈቃድ ሞትን ጠቅላይ ሚንስትር ጀሲንዳ አርደን እንዲሁም ተቀናቃኛቸው ጁዲት ኮሊንስም ይደግፉታል። ሕዝቡም ሕጋዊ ይሁን ብሎ እንደሚመርጥ ይጠበቅ ነበር። ባለቤቱ የሞተችበት ማት ቪከርስ "ርህራሄ እና ደግነት አሸንፈዋል። በጠና የታመሙ ኒው ዚላንዳውያን ሕይወታቸውን ማሳለፍ ስለሚችሉ ደስ ብሎኛል" ሲል የተሰማውን ገልጿል። ጠበቃ የነበረችው ባለቤቱ የአንጎል እጢ ሲገኝባት በፈቃዷ ለመሞት ክስ ብትመሠረትም ሳታሸንፍ በጠና ታማ ከአምስት ዓመታት በፊት ሞታለች። "ባለቤቴ መሞት አትሻም ነበር። ማንም ሰው መሞት አይፈልግም። ነገር ግን መኖር የምርጫ ጉዳይ ነው። ስቃይ እየበረታ ሲሄድ መሞት አንዱ ምርጫ መሆን አለበት" ብሏል። አንድ ሰው በፈቃዱ ለመሞት በጠና የታመመ ወይም ከስድስት ወር በላይ እንደማይኖር የተረጋገጠ መሆን አለበት። ሰውነቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተዳከመ እንደሄደና ውሳኔው ላይ ለመድረስ በቂ መረጃ እንዳለው ማረጋገጥም ተገቢ ነው። ሂደቱ የሚመራው በዶክተር ወይም በነርስ ነው። አንድ ሰው እድሜው ስለገፋ፣ የአእምሮ ህመም ስላለበት ወይም የአካል ጉዳት ስላለበት የፍቃድ ሞት ሕግን መተግበር አይችልም። ሕጉን የሚቃወሙ ሰዎች "እንድንኖር እንጂ እንድንሞት አትርዱን" ሲሉ ምክር ቤት ሄደው ተቃውሞ አሰምተዋል። ሕጉ ለማኅበረሰቡ አስጊ እንደሆነ እና ራስን ማጥፋትን ለመግታት ከወጣ መርህ ጋር እንደሚቃረን ይናገራሉ። ሌላው መከራከሪያ ነጥብ በጠና የታመሙ ሰዎች የቤተሰብ ሸክም ላለመሆን ብለው በፈቃዳቸው ሊሞቱ ይችላሉ የሚለው ነው። ዩትኔዝያን አጥብቆ ሲተች የነበረ ቡድን "የኒው ዚላንድ ዜጎች የተሳሳተ ሕግ እንዲጸድቅ ድምጽ በመስጠታቸው አዝነናል" ሲል መግለጫ አውጥቷል። የፈቃድ ሞትን ሕጋዊ ያደረጉ አገሮች የኒው ዚላንድን ሕዝበ ውሳኔ በቅርበት ሲከታተሉ ነበር። ከነዚህ መካከል ቤልጄም፣ ካናዳ፣ ኮሎምቢያ፣ ሉግዘምበርግ እና ኔዘርላንድስ ይጠቀሳሉ። በኔዘርላንድስ በህክምና ታግዞ ራስን ማጥፋት ይቻላል። በአሜሪካ ያሉ ብዙ ግዛቶች እና የአውስትራሊያዋ ቪክቶሪያ በህክምና የታገዘ ሞትን ፈቅደዋል።
በኒው ዚላንድ ሰዎች በፍቃዳቸው እንዲሞቱ የሚደነግግ ሕግ ሊወጣ ነው በኒው ዚላንድ በጠና የታመሙ ሰዎች በፍቃዳቸው እንዲሞቱ የሚደነግግ ሕግ ሊወጣ ነው። ባለፈው ወር በተካሄደ ሕዝበ ውሳኔ 65.2% መራጮች የፍቃድ ሞትን ደግፈዋል። ዩትኔዝያ ወይም የፈቃድ ሞት በጠና የታመሙ ወይም ከስድስት ወር በላይ እንደማይኖሩ የተነገራቸው ሰዎች በህክምና እርዳታ ሕይወታቸው እንዲያልፍ የሚደረግበት ሂደት ነው። ሕጉ በቀጣዩ ዓመት ጥቅምት ወር ጸድቆ ይተገበራል ተብሎ ይጠበቃል። ኒው ዚላንድ ሕጉን ካጸደቀች የፈቃድ ሞት ከሚተገበርባቸው ጥቂት አገሮች አንዷ ትሆናለች። ዩትኔዝያ ከተፈቀደባቸው አገሮች ኔዘርላንድ እና ካናዳ ይጠቀሳሉ። ኒው ዚላንዳውያን ባለፈው ወር መሪያቸውን ሲመርጡ ስለ ፈቃድ ሞት እና ዕጸ ፋርስ ሕዝበ ውሳኔ አድርገዋል። ዕጸ ፋርስን ለመዝናኛ መጠቀም ሕጋዊ እንዲሆን ድምጽ የሰጡት 46.1% ብቻ ሲሆኑ፤ 53.1% ተቃውመዋል። የፈቃድ ሞትን ጠቅላይ ሚንስትር ጀሲንዳ አርደን እንዲሁም ተቀናቃኛቸው ጁዲት ኮሊንስም ይደግፉታል። ሕዝቡም ሕጋዊ ይሁን ብሎ እንደሚመርጥ ይጠበቅ ነበር። ባለቤቱ የሞተችበት ማት ቪከርስ "ርህራሄ እና ደግነት አሸንፈዋል። በጠና የታመሙ ኒው ዚላንዳውያን ሕይወታቸውን ማሳለፍ ስለሚችሉ ደስ ብሎኛል" ሲል የተሰማውን ገልጿል። ጠበቃ የነበረችው ባለቤቱ የአንጎል እጢ ሲገኝባት በፈቃዷ ለመሞት ክስ ብትመሠረትም ሳታሸንፍ በጠና ታማ ከአምስት ዓመታት በፊት ሞታለች። "ባለቤቴ መሞት አትሻም ነበር። ማንም ሰው መሞት አይፈልግም። ነገር ግን መኖር የምርጫ ጉዳይ ነው። ስቃይ እየበረታ ሲሄድ መሞት አንዱ ምርጫ መሆን አለበት" ብሏል። አንድ ሰው በፈቃዱ ለመሞት በጠና የታመመ ወይም ከስድስት ወር በላይ እንደማይኖር የተረጋገጠ መሆን አለበት። ሰውነቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተዳከመ እንደሄደና ውሳኔው ላይ ለመድረስ በቂ መረጃ እንዳለው ማረጋገጥም ተገቢ ነው። ሂደቱ የሚመራው በዶክተር ወይም በነርስ ነው። አንድ ሰው እድሜው ስለገፋ፣ የአእምሮ ህመም ስላለበት ወይም የአካል ጉዳት ስላለበት የፍቃድ ሞት ሕግን መተግበር አይችልም። ሕጉን የሚቃወሙ ሰዎች "እንድንኖር እንጂ እንድንሞት አትርዱን" ሲሉ ምክር ቤት ሄደው ተቃውሞ አሰምተዋል። ሕጉ ለማኅበረሰቡ አስጊ እንደሆነ እና ራስን ማጥፋትን ለመግታት ከወጣ መርህ ጋር እንደሚቃረን ይናገራሉ። ሌላው መከራከሪያ ነጥብ በጠና የታመሙ ሰዎች የቤተሰብ ሸክም ላለመሆን ብለው በፈቃዳቸው ሊሞቱ ይችላሉ የሚለው ነው። ዩትኔዝያን አጥብቆ ሲተች የነበረ ቡድን "የኒው ዚላንድ ዜጎች የተሳሳተ ሕግ እንዲጸድቅ ድምጽ በመስጠታቸው አዝነናል" ሲል መግለጫ አውጥቷል። የፈቃድ ሞትን ሕጋዊ ያደረጉ አገሮች የኒው ዚላንድን ሕዝበ ውሳኔ በቅርበት ሲከታተሉ ነበር። ከነዚህ መካከል ቤልጄም፣ ካናዳ፣ ኮሎምቢያ፣ ሉግዘምበርግ እና ኔዘርላንድስ ይጠቀሳሉ። በኔዘርላንድስ በህክምና ታግዞ ራስን ማጥፋት ይቻላል። በአሜሪካ ያሉ ብዙ ግዛቶች እና የአውስትራሊያዋ ቪክቶሪያ በህክምና የታገዘ ሞትን ፈቅደዋል።
https://www.bbc.com/amharic/54744271
0business
"የቻይናና የአሜሪካ ቀዝቃዛው ጦርነት ከኮሮናቫይረስ በላይ ለዓለም ያሰጋል"
በመጪዎቹ ዓመታት በአሜሪካና በቻይና መካከል ሊከሰት የሚችለው ቀዝቃዛ ጦርነት ዓለምን ከኮሮናቫይረስ በላይ ሊያስጨንቅ እንደሚገባ ዕውቁ የምጣኔ ሀብት ሊቅ ጄፍሪ ሳክስ ተናገሩ። የኮሎምቢያው ዩኒቨርስቲ ዕውቅ ፕሮፌሰር ጄፍ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ዓለም ወደ አንዳች መደነቃቀፍ እያመራች ነው፤ መሪ አልባም ሆናለች ብለዋል። እንዲሁም የዓለም ሁኔታ መልክ ባልያዘበት ሁኔታ በሁለቱ የዓለም ኃያላን መካከል ያለው ቁርሾና ቅራኔ እየባሰ ከሄደ ሁኔታዎችን ያባብሳል፤ ጦሱም ለተቀረው ዓለም ይተርፋል ብለዋል። እኚህ ፕሮፌሰር ለዚህ ሁሉ ተጠያቂዋ አሜሪካና አመራሯ ነው ብለዋል። • አገራዊ መድረክ ማዘጋጀት እንጂ ከህወሓት ጋር በድብቅ የሚደረግ ውይይትን አንቀበልም፡ ደብረፅዮን (ዶ/ር) • "አባላቶቻችን በአካባቢው ይህን የደንብ ልብስ መልበስ ካቆሙ ስድስት ወራት አልፈዋል" የኦሮሚያ ፖሊስ አሁን ያለው የአሜሪካ አመራር ከትብብር ይልቅ ክፍፍልን የሚያፋፍም ነው ሲሉም ለቢቢሲ ተናግረዋል። "አመራሩ አዲስ ቀዝቃዛ ጦርነት ከቻይና ጋር ለመፍጠር እየሞከረ ነው። ይህ ከሆነ ደግሞ ዓለምን ዳግም ወደ ሰላም ለመመለስ በጣም ይቸገራል" ብለዋል ፕሮፌሰሩ። የፕሮፌሰር ጄፍሪ ሳክስ አስተያየት የመጣው ሰሞኑን ቻይናና አሜሪካ ከምጣኔ ሀብት ጦርነት ጋር ብቻም ሳይሆን ፖለቲካዊ መቆራቆዝ ውስጥ እየገቡ ስለመሆኑ ምልክቶች መታየታቸውን ተከትሎ ነው። በያዝነው ሳምንት ለምሳሌ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ በቻይና ባለሥልጣናት ላይ ማዕቀብ የሚጥለው ሰነድ ላይ ይፈርማሉ ተብሏል። ማዕቀቡን የሚጥሉት በዢንጂያንግ ግዛት የቻይና ሙስሊሞችን ለርዕዮተ ዓለም ጥምቀት ማጎርያ ውስጥ መከተታቸውን ተከትሎ ነው። ያም ሆኖ የዶናልድ ትራምፕ የቀድሞው የደኅንነት አማካሪ ሰሞኑን ለአንባቢዎች ያደርሱታል በተባለው አዲስ መጽሐፋቸው እንደጠቀሱት፤ ፕሬዝዳንቱ ቻይና ይህንን የሙስሊሞች ማጎርያ እንድትገነባ አበረታተው ነበር። ዶናልድ ትራምፕ ከሰሞኑ ከዎልስትሪት ጆርናል ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ቻይና ኮሮናቫይረስን ለዓለም ያቀበለችውና ብሎም ያሰራጨችው ሆን ብላ የአሜሪካንን ምጣኔ ሀብት ለማንኮታኮት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የቻይናና የአሜሪካንን የኢኮኖሚ ጦርነት ካመላከቱ ነገሮች አንዱ አሜሪካ በቻይናው ግዙፍ የቴሌኮም ኩባንያ ሁዋዌ ላይ የጣለችው እቀባ ነው። አሜሪካ እንደምትለው ሁዋዌ የደንበኞችን መረጃ ለመሰለል የተቋቋመ ነው። ቻይና ይህንን ክስ ታስተባብላለች። የቀድሞው የዶናልድ ትራምፕ ከፍተኛ የደኅንነት አማካሪ ጆን ቦልተን አዲስ በጻፉት መጽሐፍ እንዳጋለጡት ከሆነ ዶናልድ ትራምፕ ህዋዌ ላይ እቀባ ያደረጉት በድጋሚ የመመረጥ ዕድላቸውን ለማስፋት ብቻ ነው። • ትራምፕ እንዳይታተም ባሉት መጽሐፍ ይፋ የሚደረጉ 6 ምስጢሮች • በህዳሴው ግድብ ዙሪያ የሚደረገው ድርድር፡ የግብፅ ፍላጎትና የኢትዮጵያ ውሳኔ ፕሮፌሰር ጄፍሪ ሳክስም በዚህ የቦልተን ሐሳብ ይስማማሉ። ሁዋዌን ትራምፕ ያገዱት የምርም የደኅንነት ጉዳይ አሳስቧቸው ሊሆን አይችልም። "አሜሪካ በ5ጂ የሞባይል ቴክኖሎጂ ተቀድማለች። ሁዋዌ ደግሞ የዓለምን የገበያ ድርሻ ተቀራምቶታል፤ ይህ ነው አሜሪካንን የረበሻት" ይላሉ። ከቻይና ጋር ፍጥጫ ላይ ያለችው አገር አሜሪካ ብቻ አይደለችም። ቻይና ባለፈው ሳምንት ከሕንድ ጋር የድንበር ግጭት ውስጥ ገብታ 20 የሕንድ ወታደሮችን መገደላቸው አይዘነጋም። ይህ በእንዲህ እናዳለ ቻይና በፓኪስታን፣ በምያንማር፣ በሲሪሊንካና በኔፓል በርካታ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን እያገዘች ነው። እነዚህ አገራት ደግሞ የሕንድ ጎረቤቶች ናቸው። ሕንድ ቻይና የአካባቢው ተጽእኖ ፈጣሪ አገር የመሆኗን ጉዳይ ማስቆም ትፈልጋለች። ፕሮፌሰር ሳክስ እንደሚያምኑት ቻይና በአካባቢው አገራት ላይ የትብብር መንፈስ ካሳየች ነገሮች የተሻሉ ይሆናሉ። ቻይና እድሏ ያለው በእጇ ነው። ቻይና ተባባሪ ከሆነች፣ በዲፕሎማሲ ችግሮችን ለመፍታት ከፈለገችና የትብብር መንፈስ ካሳየች ጉልበት ያላት አገር ስለሆነች ብዙ ነገር መቀየር ትችላለች፤ የእሲያ አህጉርም የተሻለ መጻኢ እድል ይኖረዋል።
"የቻይናና የአሜሪካ ቀዝቃዛው ጦርነት ከኮሮናቫይረስ በላይ ለዓለም ያሰጋል" በመጪዎቹ ዓመታት በአሜሪካና በቻይና መካከል ሊከሰት የሚችለው ቀዝቃዛ ጦርነት ዓለምን ከኮሮናቫይረስ በላይ ሊያስጨንቅ እንደሚገባ ዕውቁ የምጣኔ ሀብት ሊቅ ጄፍሪ ሳክስ ተናገሩ። የኮሎምቢያው ዩኒቨርስቲ ዕውቅ ፕሮፌሰር ጄፍ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ዓለም ወደ አንዳች መደነቃቀፍ እያመራች ነው፤ መሪ አልባም ሆናለች ብለዋል። እንዲሁም የዓለም ሁኔታ መልክ ባልያዘበት ሁኔታ በሁለቱ የዓለም ኃያላን መካከል ያለው ቁርሾና ቅራኔ እየባሰ ከሄደ ሁኔታዎችን ያባብሳል፤ ጦሱም ለተቀረው ዓለም ይተርፋል ብለዋል። እኚህ ፕሮፌሰር ለዚህ ሁሉ ተጠያቂዋ አሜሪካና አመራሯ ነው ብለዋል። • አገራዊ መድረክ ማዘጋጀት እንጂ ከህወሓት ጋር በድብቅ የሚደረግ ውይይትን አንቀበልም፡ ደብረፅዮን (ዶ/ር) • "አባላቶቻችን በአካባቢው ይህን የደንብ ልብስ መልበስ ካቆሙ ስድስት ወራት አልፈዋል" የኦሮሚያ ፖሊስ አሁን ያለው የአሜሪካ አመራር ከትብብር ይልቅ ክፍፍልን የሚያፋፍም ነው ሲሉም ለቢቢሲ ተናግረዋል። "አመራሩ አዲስ ቀዝቃዛ ጦርነት ከቻይና ጋር ለመፍጠር እየሞከረ ነው። ይህ ከሆነ ደግሞ ዓለምን ዳግም ወደ ሰላም ለመመለስ በጣም ይቸገራል" ብለዋል ፕሮፌሰሩ። የፕሮፌሰር ጄፍሪ ሳክስ አስተያየት የመጣው ሰሞኑን ቻይናና አሜሪካ ከምጣኔ ሀብት ጦርነት ጋር ብቻም ሳይሆን ፖለቲካዊ መቆራቆዝ ውስጥ እየገቡ ስለመሆኑ ምልክቶች መታየታቸውን ተከትሎ ነው። በያዝነው ሳምንት ለምሳሌ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ በቻይና ባለሥልጣናት ላይ ማዕቀብ የሚጥለው ሰነድ ላይ ይፈርማሉ ተብሏል። ማዕቀቡን የሚጥሉት በዢንጂያንግ ግዛት የቻይና ሙስሊሞችን ለርዕዮተ ዓለም ጥምቀት ማጎርያ ውስጥ መከተታቸውን ተከትሎ ነው። ያም ሆኖ የዶናልድ ትራምፕ የቀድሞው የደኅንነት አማካሪ ሰሞኑን ለአንባቢዎች ያደርሱታል በተባለው አዲስ መጽሐፋቸው እንደጠቀሱት፤ ፕሬዝዳንቱ ቻይና ይህንን የሙስሊሞች ማጎርያ እንድትገነባ አበረታተው ነበር። ዶናልድ ትራምፕ ከሰሞኑ ከዎልስትሪት ጆርናል ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ቻይና ኮሮናቫይረስን ለዓለም ያቀበለችውና ብሎም ያሰራጨችው ሆን ብላ የአሜሪካንን ምጣኔ ሀብት ለማንኮታኮት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የቻይናና የአሜሪካንን የኢኮኖሚ ጦርነት ካመላከቱ ነገሮች አንዱ አሜሪካ በቻይናው ግዙፍ የቴሌኮም ኩባንያ ሁዋዌ ላይ የጣለችው እቀባ ነው። አሜሪካ እንደምትለው ሁዋዌ የደንበኞችን መረጃ ለመሰለል የተቋቋመ ነው። ቻይና ይህንን ክስ ታስተባብላለች። የቀድሞው የዶናልድ ትራምፕ ከፍተኛ የደኅንነት አማካሪ ጆን ቦልተን አዲስ በጻፉት መጽሐፍ እንዳጋለጡት ከሆነ ዶናልድ ትራምፕ ህዋዌ ላይ እቀባ ያደረጉት በድጋሚ የመመረጥ ዕድላቸውን ለማስፋት ብቻ ነው። • ትራምፕ እንዳይታተም ባሉት መጽሐፍ ይፋ የሚደረጉ 6 ምስጢሮች • በህዳሴው ግድብ ዙሪያ የሚደረገው ድርድር፡ የግብፅ ፍላጎትና የኢትዮጵያ ውሳኔ ፕሮፌሰር ጄፍሪ ሳክስም በዚህ የቦልተን ሐሳብ ይስማማሉ። ሁዋዌን ትራምፕ ያገዱት የምርም የደኅንነት ጉዳይ አሳስቧቸው ሊሆን አይችልም። "አሜሪካ በ5ጂ የሞባይል ቴክኖሎጂ ተቀድማለች። ሁዋዌ ደግሞ የዓለምን የገበያ ድርሻ ተቀራምቶታል፤ ይህ ነው አሜሪካንን የረበሻት" ይላሉ። ከቻይና ጋር ፍጥጫ ላይ ያለችው አገር አሜሪካ ብቻ አይደለችም። ቻይና ባለፈው ሳምንት ከሕንድ ጋር የድንበር ግጭት ውስጥ ገብታ 20 የሕንድ ወታደሮችን መገደላቸው አይዘነጋም። ይህ በእንዲህ እናዳለ ቻይና በፓኪስታን፣ በምያንማር፣ በሲሪሊንካና በኔፓል በርካታ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን እያገዘች ነው። እነዚህ አገራት ደግሞ የሕንድ ጎረቤቶች ናቸው። ሕንድ ቻይና የአካባቢው ተጽእኖ ፈጣሪ አገር የመሆኗን ጉዳይ ማስቆም ትፈልጋለች። ፕሮፌሰር ሳክስ እንደሚያምኑት ቻይና በአካባቢው አገራት ላይ የትብብር መንፈስ ካሳየች ነገሮች የተሻሉ ይሆናሉ። ቻይና እድሏ ያለው በእጇ ነው። ቻይና ተባባሪ ከሆነች፣ በዲፕሎማሲ ችግሮችን ለመፍታት ከፈለገችና የትብብር መንፈስ ካሳየች ጉልበት ያላት አገር ስለሆነች ብዙ ነገር መቀየር ትችላለች፤ የእሲያ አህጉርም የተሻለ መጻኢ እድል ይኖረዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-53135326
2health
በኮሮና የተያዙ ሰዎች በድባቴ እና የመርሳት በሽታ የመጠቃት እድላቸው እንደሚጨምር ጥናት አመለከተ
ባለፈው ስድስት ወራት ውስጥ የኮሮናቫይረስ የያዛቸው ሰዎች በድባቴ፣ የመርሳት በሽታ፣ ስትሮክ እና በሳይኮሲስ ህመሞች የመጠቃት እድላቸው ከፍተኛ መሆኑን በኦክስፎርድ ተመራማሪዎች የተሰራ ጥናት አመላከተ። ከእነዚህ ውስጥ አንድ ሶስተኛው ቀድመው የነበሩባቸው የስነ ልቦና እና የነርቭ ችግሮች ያገረሽባቸዋል ወይም እንደ አዲስ ሕመሞቹ ያጠቋቸዋል ሲል ጥናቱ አመልክቷል። በቫይረሱ ተይዘው ሆስፒታል የገቡ ወይም በፅኑ ህሙማን ማቆያ ከነበሩ ደግሞ የመያዝ እድላቸው የበለጠ ይሰፋል ሲል ጥናቱ አመላክቷል። እነዚህ ጫናዎችም ጭንቀትን በማስከተል ወይም ቫይረሱ አዕምሮ ላይ በሚያስከትለው ቀጥተኛ ጫና ላይ ሊመሰረት እንደሚችልም አክሏል። እንግሊዛዊያን ሳይንቲስቶቹ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ በአሜሪካ የኮሮናቫይረስ ተጠቂዎችን የኤሌክትሮኒክ መረጃ በመመልከት እና በተለይም 14 ለሚሆኑ የስነ-ልቦና እና የነርቭ ችግሮች የመጋለጥ እድሎችን መርምረዋል። ከእነዚህም መካከል የአዕምሮ ውስጥ የደም መፍሰስ፣ ስትሮክ፣ ፓርኪንሰን፣ የመርሳት በሽታ፣ ሳይኮሲስ፣ የስሜት መቃወስ እና የጭንቀት ችግሮች ይገኙበታል፡፡ በጣም መታመምን ወይም ወደ ሆስፒታል መወሰድ ከሚያስከትለው የጭንቀት ጫና የተነሳ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች ለጭንቀት እና የስሜት መቃወስ መዳረግ በተደጋጋሚ የታዩባቸው ችግሮች ናቸው ሲል ገልጿል። እንደ ስትሮክ እና የመርሳት በሽታ ያሉት ደግሞ ቫይረሱ በራሱ በሚያስከትለው አካላዊ ጉዳት ላይ ተመስርተው የሚከሰቱ ወይም ሰውነታችን ለቫይረሱ በሚሰጠው ምላሽ ምክንያት ሊከሰቱ ይችላሉ ሲልም አስረድቷል። ጥናቱ የኮሮናቫይረስ በቀጥታ ለፓርኪንሰን ወይም ለጊላይን-ባሬ ሲንድሮም የማጋለጥ እድሉን አላረጋገጠም። ምርምሩ ሁለት በጉንፋን የተያዙ ሰዎችን የያዙ ቡድኖችን በኮሮናቫይረስ ከተያዙት ጋር በማነፃፀር የተሰራ ሲሆን፣ ጥናቱን ያካሄዱት የኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ ተመራማሪዎች ኮሮና ከሌሎች የመተንፈሻ ህመሞች በበለጠ ከአዕምሮ ጉዳቶች ጋር እንደሚያያዝ ገልፀዋል። ቫይረሱ ወደ አዕምሮ ውስጥ እንደሚገባ እና ጉዳቶችን እንደሚያደርስ የሚያሳዩ ማስረጃዎች ተገኝተዋል ሲሉ ከተመራማሪዎቹ አንዱ የሆኑት የኦክስፎርዱ የኑሮሎጂ ፕሮፌሰር መሱድ ሃሰን አብራርተዋል፡፡ ከቀጥተኛ ጉዳቶችም ባሻገር የደም መርጋትን በማስከተሉ እና ይህም ስትሮክን ሊያመጣ እንደሚችል አክለዋል፡፡ በአጠቃላይም ሰውነታችን ቫይረሱን ለመከላከል ሲል የሚያደርገው ግብ ግብ አእምሮን ሊጎዳ ይችላል ሲሉም ገልፀዋል፡፡
በኮሮና የተያዙ ሰዎች በድባቴ እና የመርሳት በሽታ የመጠቃት እድላቸው እንደሚጨምር ጥናት አመለከተ ባለፈው ስድስት ወራት ውስጥ የኮሮናቫይረስ የያዛቸው ሰዎች በድባቴ፣ የመርሳት በሽታ፣ ስትሮክ እና በሳይኮሲስ ህመሞች የመጠቃት እድላቸው ከፍተኛ መሆኑን በኦክስፎርድ ተመራማሪዎች የተሰራ ጥናት አመላከተ። ከእነዚህ ውስጥ አንድ ሶስተኛው ቀድመው የነበሩባቸው የስነ ልቦና እና የነርቭ ችግሮች ያገረሽባቸዋል ወይም እንደ አዲስ ሕመሞቹ ያጠቋቸዋል ሲል ጥናቱ አመልክቷል። በቫይረሱ ተይዘው ሆስፒታል የገቡ ወይም በፅኑ ህሙማን ማቆያ ከነበሩ ደግሞ የመያዝ እድላቸው የበለጠ ይሰፋል ሲል ጥናቱ አመላክቷል። እነዚህ ጫናዎችም ጭንቀትን በማስከተል ወይም ቫይረሱ አዕምሮ ላይ በሚያስከትለው ቀጥተኛ ጫና ላይ ሊመሰረት እንደሚችልም አክሏል። እንግሊዛዊያን ሳይንቲስቶቹ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ በአሜሪካ የኮሮናቫይረስ ተጠቂዎችን የኤሌክትሮኒክ መረጃ በመመልከት እና በተለይም 14 ለሚሆኑ የስነ-ልቦና እና የነርቭ ችግሮች የመጋለጥ እድሎችን መርምረዋል። ከእነዚህም መካከል የአዕምሮ ውስጥ የደም መፍሰስ፣ ስትሮክ፣ ፓርኪንሰን፣ የመርሳት በሽታ፣ ሳይኮሲስ፣ የስሜት መቃወስ እና የጭንቀት ችግሮች ይገኙበታል፡፡ በጣም መታመምን ወይም ወደ ሆስፒታል መወሰድ ከሚያስከትለው የጭንቀት ጫና የተነሳ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች ለጭንቀት እና የስሜት መቃወስ መዳረግ በተደጋጋሚ የታዩባቸው ችግሮች ናቸው ሲል ገልጿል። እንደ ስትሮክ እና የመርሳት በሽታ ያሉት ደግሞ ቫይረሱ በራሱ በሚያስከትለው አካላዊ ጉዳት ላይ ተመስርተው የሚከሰቱ ወይም ሰውነታችን ለቫይረሱ በሚሰጠው ምላሽ ምክንያት ሊከሰቱ ይችላሉ ሲልም አስረድቷል። ጥናቱ የኮሮናቫይረስ በቀጥታ ለፓርኪንሰን ወይም ለጊላይን-ባሬ ሲንድሮም የማጋለጥ እድሉን አላረጋገጠም። ምርምሩ ሁለት በጉንፋን የተያዙ ሰዎችን የያዙ ቡድኖችን በኮሮናቫይረስ ከተያዙት ጋር በማነፃፀር የተሰራ ሲሆን፣ ጥናቱን ያካሄዱት የኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ ተመራማሪዎች ኮሮና ከሌሎች የመተንፈሻ ህመሞች በበለጠ ከአዕምሮ ጉዳቶች ጋር እንደሚያያዝ ገልፀዋል። ቫይረሱ ወደ አዕምሮ ውስጥ እንደሚገባ እና ጉዳቶችን እንደሚያደርስ የሚያሳዩ ማስረጃዎች ተገኝተዋል ሲሉ ከተመራማሪዎቹ አንዱ የሆኑት የኦክስፎርዱ የኑሮሎጂ ፕሮፌሰር መሱድ ሃሰን አብራርተዋል፡፡ ከቀጥተኛ ጉዳቶችም ባሻገር የደም መርጋትን በማስከተሉ እና ይህም ስትሮክን ሊያመጣ እንደሚችል አክለዋል፡፡ በአጠቃላይም ሰውነታችን ቫይረሱን ለመከላከል ሲል የሚያደርገው ግብ ግብ አእምሮን ሊጎዳ ይችላል ሲሉም ገልፀዋል፡፡
https://www.bbc.com/amharic/news-56664358
5sports
ለአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ከሁሉ ቀድመው ካሜሮን የገቡት ዋሊያዎች
በኮሮናቫይረስ ምክንያት በአንድ ዓመት የዘገየው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አሁንም በወረርሽኙ ስጋት ውስጥ ሆኖ በመጪው ወር ጥር 01/2014 ዓ.ም ካሜሩን ውስጥ መካሄድ ይጀምራል። በዚሁ ውድድር መሳተፋቸውን ያረጋገጡት ዋልያዎቹም ባለፈው ሳምንት እሁድ ከሁሉም የአፍሪካ አገራት ቀድመው ካሜሩን በመድረስ ዝግጅታቸውን ጀምረዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪው ጌታነህ ከበደን ጨምሮ 25 ተጫዋቾች በቡድኑ ውስጥ የተካተቱ ሲሆን፣ ካፍ ካስቀመጠው ገደብ በተጨማሪ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ሦስት ተጫዋቾች እንዲካተቱ ተደርጓ። ታኅሣሥ 14/ 2014 ይፋ ከተደረገው የብሔራዊ ቡድኑ 25 ተጫዋቾች ዝርዝር ከዚህ ቀደም በተጠባባቂነት ተይዘው የነበሩት ሱራፌል ዳኛቸው፣ ፍሬው ጌታሁን እና ይሁን እንደሻው ብሔራዊ ቡድኑን ተቀላቅለው ዋሊያዎቹ 28 ተጫዋቾችን በመያዝ ወደ ካሜሩን አቅንተዋል። የኢትዮጵያ የወንዶች ብሔራዊ ቡድን ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈው ከ8 ዓመታት በፊት ደቡብ አፍሪካ ባስተናገደችው ውድድር ላይ ነበር። ባለፈው እሁድ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፍያ የተነሳው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ልዑክ በቀዳሚነት የካሜሩን ሁለተኛ ከተማ ወደሆነችው ዱዋላ ደርሶ ለአንድ ሰዓት ከቆየ በኋላ ወደ ዋና ከተማዋ ያውንዴ ደርሷል። ብሔራዊ ቡድኑ ያውንዴ አየር ማረፊያ እንደደረሰ የኮቪድ-19 ምርመራን ያደረገ ሲሆን በመቀጠል ወደ ሆቴል ዴ ዴፕዩቴ አምርቶ ማረፊያውን ማድረጉን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን መረጃ ያሳያል። ብሔራዊ ቡድኑ እስካሁን ቀላል እና ጠንከር ያሉ አራት ልምምዶችን አከናውኗል። በዋሊያዎቹ ከሁሉ ቀድመው ለምን ወደ ካሜሩን ሄዱ? የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋና ፀሐፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን እንደሚሉት የመጀመሪያ እቅድ ተደርጎ የነበረው በመካከለኛው ምሥራቅ ከሚገኙ አገራት መካከል በአንዱ ውስጥ ዝግጅት ለማድረግ ነበር። "ከሳዑዲ አረቢያ እግር ኳስ ማኅበር ጋር ንግግሮች ነበሩ። እንዲያውም ሙሉ ወጪያችንን ሸፍነው እነሱ ጋር ሄደን እንድንዘጋጅ ተነጋግረን ነበር።" ነገር ግን የኮሮናቫይረስ ስርጭትን ተከትሎ የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት የጉዞ እግዳዎችን ከጣለባቸው አገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ በመሆኗ ሀሳቡ ሳይሳካ እንደቀረ ኃላፊው ለቢቢሲ ገልጸዋል። የሳዑዲ አረቢያ እግር ኳስ ፌደሬሽንም ቢሆን በተፈጠረው ነገር ማዘኑን እንደገለጸና ይቅርታ እንደመጠየቀም ኃላፊው አመልክተዋል። የመጀመሪያው እቅድ አለመሳካቱን ተከትሎ ደግሞ ፌደሬሽኑ ወደ ሁለተኛ እቅዱ ፊቱን ለማዞር ተገዷል። ይህም ደግሞ ወደ ምዕራብ አፍሪካ አገራት በመሄድ ልምምድ ማካሄድ ነበር። በስተመጨረሻም ወደ አዘጋጇ አገር ካሜሩን በመሄድ ልምምድ ለማድረግ ውሳኔ ላይ ተደርሷል። በተጨማሪም ብሔራዊ ቡድኑ ቀድሞ ወደ ካሜሩን ማቅናቱ የአገሪቱን የአየር ጸባይ ለመልመድ ይእንደሚረዳ የገለጹት አቶ ባሕሩ፣ የአፍሪካ ዋንጫ ዘንድሮ እንዳይካሄድ ከተለያዩ ወገኖች ግፊት ይደረግ ስለነበረ ያን በመቃወም ውድድሩ በተያዘለት ጊዜ እንዲከናወን ኢትዮጵያ ያላትን ድጋፍ ለማሳየት መሆኑን ጠቅሰዋል። ፊፋንና የአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበርን ጨምሮ አንዳንድ የእግር ኳስ ማኅበራት የወረርሽኙን ስርጨት ተከትሎ የአፍሪካ ዋንጫ በዚህ ጊዜ መካሄድ የለበትም የሚል አስተያየት ሲሰጡ እንደነበር ዋና ፀሐፊው ተናግረዋል። "እኛ ደግሞ የፓንአፍሪካኒዝም ጀማሪዎች እንዲሁም የካፍ መስራች እንደመሆናችን ይሄ ውድድር በተያዘለት ጊዜ በካሜሩን እንደሚካሄድ ማረጋገጫ ለመስጠትና ይህንን መልዕክት ለማስተላለፍ ነው ቀድመን ወደ ካሜሩን ለማቅናት የወሰንነው።" ኦሚክሮን የተባለው አዲሱን የኮቪድ-19 ዝርያ በስፋት መሰራጨትን ተከትሎ በርካቶች ውድድሩ ላይካሄድ ይችላል በሚል ስጋታቸውን ቢገልጹም፣ የየካሜሩን መንግሥት እና የእግር ኳስ ማኅበሩ እንዲሁም የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ግን ጨዋታው በወጣለት መረሃ ግብር መሠረት እንደሚከናወን አረጋግጠዋል። ነገር ግን በካሜሩን በሚካሄደው የአፍሪካ እግር ኳስ ዋንጫ ላይ መታደም የሚችሉት የኮቪድ-19 ክትባትን ሙሉ ለሙሉ የወሰዱ እና ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸው የተረጋገጠ ደጋፊዎች ብቻ እንደሚሆኑ አዘጋጆቹ ገልጸዋል። የካሜሩን ቆይታና ዝግጅት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሁን የሚገኘው የፊፋ ወኪል በሆነ ኤጀንት አማካይነት በተመቻቸ የስልጠና ካምፕ አገልግሎት መስጫ ውስጥ ነው። ይህ የስልጠና አገልግሎት መስጫ ካምፕ ሆቴል፣ መስተንግዶ፣ የስልጠና ቦታና ሌሎች አስፈላጊ ነገሮችን ሁሉ ያሟላ እንደሆነ አቶ ባህሩ ይገልጻሉ። "አሁን ብሔራዊ ቡድኑ ያለበት ቦታ ሁሉንም ፍላጎታቸውን የሚያሟላ ነው። አሁን ላይም ተጫዋቾቹ አስፈላጊውን ስልጠናና ዝግጅት በዚህ ማዕከል እያደረጉ ነው'' ሲሉ ዋሊያዎቹ ለውድድሩ አስፋለጊውን ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን አመልክተዋል። በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ዝግጅት ያውንዴ ከከተመ ሳምንት ሊሆነው ተቃርቧል። በቆይታውም መደበኛ ልምምድ በማድረግ ከሳምንት ለሚጀመረው ውድድር እየተዘጋጀ ነው። ከዚሁ ጋር ተያይዞም ከዋሊያዎቹ ቀጥሎ ካሜሩን ከደረሰው የሱዳን ብሔራዊ ቡድን ጋር ሐሙስ ዕለት የአቋም መፈተሻ ጨዋታ አድርጓል። በምድብ 'መ' ከግብፅ፣ ከናይጄሪያ እና ከጊኒ ቢሳዎ ጋር ከተደለደለችው ሱዳን ጋር በተደረገው የአቋም መለኪያ ጨዋታው አማኑኤል ገ/ሚካኤል ሁለት፣ ሽመልስ በቀለ ደግሞ አንድ ግቦችን አስቆጥረው ዋሊያዎቹ 3 ለ 2 በሆነ ውጤት ለማሸነፍ ችለዋል። ዋሊያዎቹ በካሜሩን በሚኖራቸው ቆይታ አጠቃላይ ወጪያቸውን የኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ገንዘብ መድቦ እንደሚሸፍን የፌደሬሽኑ ዋና ፀሐፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን ለቢቢሲ ገልጸዋል። የአፍሪካ አህጉር ትንቁ የእግር ኳስ ውድድር በሆነው ጨዋታ ላይ ኢትዮጵያን ወክሎ ለሚቀርበው ቡድን የሚያስፈልገውን ገንዘብ ፌዴሬሽኑ ከመንግሥት አግኝቷል። "ለዚህ ውድድር 51 ሚሊየን ብር እንዲመድብ ጠይቀን 35 ሚሊየን ብር ጸድቆልናል። በዚህ ገንዘብ ነው ብሔራዊ ቡድኑ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው። በዚህ አጋጣሚ መንግሥት ላደረገው ነገር በሙሉ ፌዴሬሽኑ ያመስግናል'' ብለዋል አቶ ባሕሩ። ከዋሊያዎቹ ምን እንጠብቅ? የአፍሪካ እግር ኳስ ውድድር መስራች የሆነችው ኢትዮጵያ ከውድድሩ ርቃ ከመቆየቷ በተጨማሪ ከአንድ ጊዜ በላይ የጎላ ውጤትን ሳታስመዘገብ ቆይታለች። በዚህ 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የሚሳታፈው ቡድን ግን ይህንን ታሪክ የመቀየር ከፍ ያለ ፍላጎት አለው። ለዚህም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ከዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋሊያዎቹ በምድብ ጨዋታዎች ጥሩ ውጤት አስመዝግበው ከምድባቸው ማለፍን በቀዳሚነት የሚጠበቅ ውጤት እንደሆነ አቶ ባህሩ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ በምድብ አንድ ከአዘጋጇ ካሜሩን፣ ከቡርኪና ፋሶ እና ኬፕ ቬርድ ጋር ተደልድሏል። በዚህ ሂደትም ዋሊያዎቹ ከምድባቸው ወደቀጣይ ዙር ማለፍን የመጀመሪያ ግብ ከመሆኑ ጎን ለጎን "በስፖርት ዲፐሎማሲው ዘርም ሌሎች ኃላፊነቶችን እንመዲወስዱም" አቶ ባሕሩ ጠቅሰው "ኢትዮጵያን ለዓለም ሕዝብ በደንብ ማስተዋወቅና ማሳየት እንፈልጋለን። በዚህ ትልቅ አጋጣሚ አንድነታችንን ለመላው ዓለም በደንብ አድርገን እናሳያለን" ብለዋል። በተጨማሪም ካሜሩን ውስጥ 20 የሚደርሱ የኢትዮጵያውያን ስብስቦች እንደሚገኙ የገለጹት አቶ ባህሩ እነዚህን ኢትዮጵያውያን በማሰባብ ለብሔራዊ ቡድኑ ድጋፍ እንዲያደርጉ፣ እንዲሁም ከ500 በላይ የሚሆኑ ደጋፊዎች ከኢትዮጵያ ወደ ካሜሩን ለመጓዝ እየተዘጋጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። የዋሊያዎቹ ስብስብ ግብ ጠባቂዎች፡ ተክለማርያም ሻንቆ ከሲዳማ ቡና፣ ፋሲል ገብረሚካኤል ከባሕር ዳር ከተማ፣ ጀማል ጣሰው ከአዳማ ከተማ እንዲሁም ፍሬው ጌታሁን ከድሬዳዋ ከተማ ናቸው። ተከላካዮች፡ አስራት ቱንጆ ከኢትዮጵያ ቡና፣ ሱሌማን ሐሚድ ከቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ረመዳን የሱፍ ከወልቂጤ ከተማ፣ ደስታ ዮሐንስ ከአዳማ ከተማ፣ አስቻለው ታመነ ከፋሲል ከነማ፣ ያሬድ ባየህ ከፋሲል ከነማ፣ ምኞት ደበበ ከቅዱስ ጊዮርጊስ እና መናፍ አወል ከባሕር ዳር ከተማ። አማካዮች፡ አማኑኤል ዮሐንስ ከኢትዮጵያ ቡና፣ ጋቶች ፓኖም ከቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ሽመልስ በቀለ ከአል ጎውና፣ መስዑድ መሐመድ ከጅማ አባጅፋር፣ ሱራፌል ዳኛቸው ከፋሲል ከነማ፣ ፍጹም ዓለሙ ከባሕር ዳር ከተማ፣ ፍሬው ሰለሞን ከሲዳማ ቡና፣ በዛብህ መላዮ ከፋሲል ከነማ እንዲሁም ይሁን እንደሻው ከፋሲል ከነማ። አጥቂዎች፡ አቡበክር ናስር ከኢትዮጵያ ቡና፣ ጌታን ከበደ ከወልቂጤ ከተማ፣ አማኑኤል ገ/ሚካኤል ከቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ሽመክት ጉግሳ ከፋሲል ከነማ፣ ሙጂብ ቃሲም ከጄይኒስ ስፖርቲቭ ዲ ካቢሌ፣ መስፍን ታደሰ ከሐዋሳ ከተማ እንዲሁም ዳዋ ሁጤሳ ከአዳማ ከተማ ተመርጠዋል። ዋሊያዎቹ በካሜሩን ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ዋንጫ የደረሰችው ከዘጠኝ ዓመታት ቆይታ በኋላ ነው። በ1962 (እአአ) የአህጉሪቱን ትልቁን ዋንጫ ያነሱት ዋሊያዎቹ በአፍሪካ ዋንጫ ሲሳተፉ ይህኛው ለ11ኛ ጊዜ ነው። በዓለም እግር ኳስ 137ኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ በአሠልጣኝ ውበቱ አባተና በአምበሉ ጌታነህ ከበደ እየተመራች ወደ ያውንዴ አቅንታለች። ይህ የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ለአሠልጣኝ ውበቱ አባቱና ለቡድኑ አባላት ከአፍሪካ ዋንጫ መሥራቾች አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ ያላትን ተሰጥዖ የሚያሳዩበት መድረክ እንደሚሆን ይገመታል። ውበቱ ለዓይን ገዥ የሆነውን ኳስ እግር ላይ ሳይቆዩ እየተቀባበሉ መጫወትን የሚመርጥ አሠልጣኝ ነው። የመሃል ሜዳው ሞተር ሽመልስ በቀለና አጥቂው ጌታነህ ከበደ ከወጣቱ የኢትዮጵያ ቡና አጥቂ አቡበከር ናስር ጋር በመጣመር ለተቀናቃኞቻቸው አደጋ ሊሆኑ ይችላሉ። ውበቱ በሚመርጠው የ4-3-3 አሠላለፍ ማለትም 4 የኋላ ደጀን ሦስት አማካዮችና ሦስት አጥቂዎች ተመርቶ ወደ ሜዳ እንደሚገባ ይገመታል። ብሔራዊ ቡድኗን በውበቱ አባተ እያጠናከረች ያለችው ኢትዮጵያ ወደ ዙር 16 መሻገር እንደ ትልቅ ውጤት ቢታይ የሚገርም አይሆንም። አልፎም ብሔራዊ ቡድናቸው በአፍሪካ ትልቁ ውድድር ሲሳተፍ ማየት ለጓጉ ኢትዮጵያዊያን ይህ ትልቅ ዕድል ነው።
ለአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ከሁሉ ቀድመው ካሜሮን የገቡት ዋሊያዎች በኮሮናቫይረስ ምክንያት በአንድ ዓመት የዘገየው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አሁንም በወረርሽኙ ስጋት ውስጥ ሆኖ በመጪው ወር ጥር 01/2014 ዓ.ም ካሜሩን ውስጥ መካሄድ ይጀምራል። በዚሁ ውድድር መሳተፋቸውን ያረጋገጡት ዋልያዎቹም ባለፈው ሳምንት እሁድ ከሁሉም የአፍሪካ አገራት ቀድመው ካሜሩን በመድረስ ዝግጅታቸውን ጀምረዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪው ጌታነህ ከበደን ጨምሮ 25 ተጫዋቾች በቡድኑ ውስጥ የተካተቱ ሲሆን፣ ካፍ ካስቀመጠው ገደብ በተጨማሪ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ሦስት ተጫዋቾች እንዲካተቱ ተደርጓ። ታኅሣሥ 14/ 2014 ይፋ ከተደረገው የብሔራዊ ቡድኑ 25 ተጫዋቾች ዝርዝር ከዚህ ቀደም በተጠባባቂነት ተይዘው የነበሩት ሱራፌል ዳኛቸው፣ ፍሬው ጌታሁን እና ይሁን እንደሻው ብሔራዊ ቡድኑን ተቀላቅለው ዋሊያዎቹ 28 ተጫዋቾችን በመያዝ ወደ ካሜሩን አቅንተዋል። የኢትዮጵያ የወንዶች ብሔራዊ ቡድን ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈው ከ8 ዓመታት በፊት ደቡብ አፍሪካ ባስተናገደችው ውድድር ላይ ነበር። ባለፈው እሁድ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፍያ የተነሳው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ልዑክ በቀዳሚነት የካሜሩን ሁለተኛ ከተማ ወደሆነችው ዱዋላ ደርሶ ለአንድ ሰዓት ከቆየ በኋላ ወደ ዋና ከተማዋ ያውንዴ ደርሷል። ብሔራዊ ቡድኑ ያውንዴ አየር ማረፊያ እንደደረሰ የኮቪድ-19 ምርመራን ያደረገ ሲሆን በመቀጠል ወደ ሆቴል ዴ ዴፕዩቴ አምርቶ ማረፊያውን ማድረጉን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን መረጃ ያሳያል። ብሔራዊ ቡድኑ እስካሁን ቀላል እና ጠንከር ያሉ አራት ልምምዶችን አከናውኗል። በዋሊያዎቹ ከሁሉ ቀድመው ለምን ወደ ካሜሩን ሄዱ? የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋና ፀሐፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን እንደሚሉት የመጀመሪያ እቅድ ተደርጎ የነበረው በመካከለኛው ምሥራቅ ከሚገኙ አገራት መካከል በአንዱ ውስጥ ዝግጅት ለማድረግ ነበር። "ከሳዑዲ አረቢያ እግር ኳስ ማኅበር ጋር ንግግሮች ነበሩ። እንዲያውም ሙሉ ወጪያችንን ሸፍነው እነሱ ጋር ሄደን እንድንዘጋጅ ተነጋግረን ነበር።" ነገር ግን የኮሮናቫይረስ ስርጭትን ተከትሎ የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት የጉዞ እግዳዎችን ከጣለባቸው አገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ በመሆኗ ሀሳቡ ሳይሳካ እንደቀረ ኃላፊው ለቢቢሲ ገልጸዋል። የሳዑዲ አረቢያ እግር ኳስ ፌደሬሽንም ቢሆን በተፈጠረው ነገር ማዘኑን እንደገለጸና ይቅርታ እንደመጠየቀም ኃላፊው አመልክተዋል። የመጀመሪያው እቅድ አለመሳካቱን ተከትሎ ደግሞ ፌደሬሽኑ ወደ ሁለተኛ እቅዱ ፊቱን ለማዞር ተገዷል። ይህም ደግሞ ወደ ምዕራብ አፍሪካ አገራት በመሄድ ልምምድ ማካሄድ ነበር። በስተመጨረሻም ወደ አዘጋጇ አገር ካሜሩን በመሄድ ልምምድ ለማድረግ ውሳኔ ላይ ተደርሷል። በተጨማሪም ብሔራዊ ቡድኑ ቀድሞ ወደ ካሜሩን ማቅናቱ የአገሪቱን የአየር ጸባይ ለመልመድ ይእንደሚረዳ የገለጹት አቶ ባሕሩ፣ የአፍሪካ ዋንጫ ዘንድሮ እንዳይካሄድ ከተለያዩ ወገኖች ግፊት ይደረግ ስለነበረ ያን በመቃወም ውድድሩ በተያዘለት ጊዜ እንዲከናወን ኢትዮጵያ ያላትን ድጋፍ ለማሳየት መሆኑን ጠቅሰዋል። ፊፋንና የአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበርን ጨምሮ አንዳንድ የእግር ኳስ ማኅበራት የወረርሽኙን ስርጨት ተከትሎ የአፍሪካ ዋንጫ በዚህ ጊዜ መካሄድ የለበትም የሚል አስተያየት ሲሰጡ እንደነበር ዋና ፀሐፊው ተናግረዋል። "እኛ ደግሞ የፓንአፍሪካኒዝም ጀማሪዎች እንዲሁም የካፍ መስራች እንደመሆናችን ይሄ ውድድር በተያዘለት ጊዜ በካሜሩን እንደሚካሄድ ማረጋገጫ ለመስጠትና ይህንን መልዕክት ለማስተላለፍ ነው ቀድመን ወደ ካሜሩን ለማቅናት የወሰንነው።" ኦሚክሮን የተባለው አዲሱን የኮቪድ-19 ዝርያ በስፋት መሰራጨትን ተከትሎ በርካቶች ውድድሩ ላይካሄድ ይችላል በሚል ስጋታቸውን ቢገልጹም፣ የየካሜሩን መንግሥት እና የእግር ኳስ ማኅበሩ እንዲሁም የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ግን ጨዋታው በወጣለት መረሃ ግብር መሠረት እንደሚከናወን አረጋግጠዋል። ነገር ግን በካሜሩን በሚካሄደው የአፍሪካ እግር ኳስ ዋንጫ ላይ መታደም የሚችሉት የኮቪድ-19 ክትባትን ሙሉ ለሙሉ የወሰዱ እና ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸው የተረጋገጠ ደጋፊዎች ብቻ እንደሚሆኑ አዘጋጆቹ ገልጸዋል። የካሜሩን ቆይታና ዝግጅት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሁን የሚገኘው የፊፋ ወኪል በሆነ ኤጀንት አማካይነት በተመቻቸ የስልጠና ካምፕ አገልግሎት መስጫ ውስጥ ነው። ይህ የስልጠና አገልግሎት መስጫ ካምፕ ሆቴል፣ መስተንግዶ፣ የስልጠና ቦታና ሌሎች አስፈላጊ ነገሮችን ሁሉ ያሟላ እንደሆነ አቶ ባህሩ ይገልጻሉ። "አሁን ብሔራዊ ቡድኑ ያለበት ቦታ ሁሉንም ፍላጎታቸውን የሚያሟላ ነው። አሁን ላይም ተጫዋቾቹ አስፈላጊውን ስልጠናና ዝግጅት በዚህ ማዕከል እያደረጉ ነው'' ሲሉ ዋሊያዎቹ ለውድድሩ አስፋለጊውን ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን አመልክተዋል። በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ዝግጅት ያውንዴ ከከተመ ሳምንት ሊሆነው ተቃርቧል። በቆይታውም መደበኛ ልምምድ በማድረግ ከሳምንት ለሚጀመረው ውድድር እየተዘጋጀ ነው። ከዚሁ ጋር ተያይዞም ከዋሊያዎቹ ቀጥሎ ካሜሩን ከደረሰው የሱዳን ብሔራዊ ቡድን ጋር ሐሙስ ዕለት የአቋም መፈተሻ ጨዋታ አድርጓል። በምድብ 'መ' ከግብፅ፣ ከናይጄሪያ እና ከጊኒ ቢሳዎ ጋር ከተደለደለችው ሱዳን ጋር በተደረገው የአቋም መለኪያ ጨዋታው አማኑኤል ገ/ሚካኤል ሁለት፣ ሽመልስ በቀለ ደግሞ አንድ ግቦችን አስቆጥረው ዋሊያዎቹ 3 ለ 2 በሆነ ውጤት ለማሸነፍ ችለዋል። ዋሊያዎቹ በካሜሩን በሚኖራቸው ቆይታ አጠቃላይ ወጪያቸውን የኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ገንዘብ መድቦ እንደሚሸፍን የፌደሬሽኑ ዋና ፀሐፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን ለቢቢሲ ገልጸዋል። የአፍሪካ አህጉር ትንቁ የእግር ኳስ ውድድር በሆነው ጨዋታ ላይ ኢትዮጵያን ወክሎ ለሚቀርበው ቡድን የሚያስፈልገውን ገንዘብ ፌዴሬሽኑ ከመንግሥት አግኝቷል። "ለዚህ ውድድር 51 ሚሊየን ብር እንዲመድብ ጠይቀን 35 ሚሊየን ብር ጸድቆልናል። በዚህ ገንዘብ ነው ብሔራዊ ቡድኑ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው። በዚህ አጋጣሚ መንግሥት ላደረገው ነገር በሙሉ ፌዴሬሽኑ ያመስግናል'' ብለዋል አቶ ባሕሩ። ከዋሊያዎቹ ምን እንጠብቅ? የአፍሪካ እግር ኳስ ውድድር መስራች የሆነችው ኢትዮጵያ ከውድድሩ ርቃ ከመቆየቷ በተጨማሪ ከአንድ ጊዜ በላይ የጎላ ውጤትን ሳታስመዘገብ ቆይታለች። በዚህ 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የሚሳታፈው ቡድን ግን ይህንን ታሪክ የመቀየር ከፍ ያለ ፍላጎት አለው። ለዚህም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ከዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋሊያዎቹ በምድብ ጨዋታዎች ጥሩ ውጤት አስመዝግበው ከምድባቸው ማለፍን በቀዳሚነት የሚጠበቅ ውጤት እንደሆነ አቶ ባህሩ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ በምድብ አንድ ከአዘጋጇ ካሜሩን፣ ከቡርኪና ፋሶ እና ኬፕ ቬርድ ጋር ተደልድሏል። በዚህ ሂደትም ዋሊያዎቹ ከምድባቸው ወደቀጣይ ዙር ማለፍን የመጀመሪያ ግብ ከመሆኑ ጎን ለጎን "በስፖርት ዲፐሎማሲው ዘርም ሌሎች ኃላፊነቶችን እንመዲወስዱም" አቶ ባሕሩ ጠቅሰው "ኢትዮጵያን ለዓለም ሕዝብ በደንብ ማስተዋወቅና ማሳየት እንፈልጋለን። በዚህ ትልቅ አጋጣሚ አንድነታችንን ለመላው ዓለም በደንብ አድርገን እናሳያለን" ብለዋል። በተጨማሪም ካሜሩን ውስጥ 20 የሚደርሱ የኢትዮጵያውያን ስብስቦች እንደሚገኙ የገለጹት አቶ ባህሩ እነዚህን ኢትዮጵያውያን በማሰባብ ለብሔራዊ ቡድኑ ድጋፍ እንዲያደርጉ፣ እንዲሁም ከ500 በላይ የሚሆኑ ደጋፊዎች ከኢትዮጵያ ወደ ካሜሩን ለመጓዝ እየተዘጋጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። የዋሊያዎቹ ስብስብ ግብ ጠባቂዎች፡ ተክለማርያም ሻንቆ ከሲዳማ ቡና፣ ፋሲል ገብረሚካኤል ከባሕር ዳር ከተማ፣ ጀማል ጣሰው ከአዳማ ከተማ እንዲሁም ፍሬው ጌታሁን ከድሬዳዋ ከተማ ናቸው። ተከላካዮች፡ አስራት ቱንጆ ከኢትዮጵያ ቡና፣ ሱሌማን ሐሚድ ከቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ረመዳን የሱፍ ከወልቂጤ ከተማ፣ ደስታ ዮሐንስ ከአዳማ ከተማ፣ አስቻለው ታመነ ከፋሲል ከነማ፣ ያሬድ ባየህ ከፋሲል ከነማ፣ ምኞት ደበበ ከቅዱስ ጊዮርጊስ እና መናፍ አወል ከባሕር ዳር ከተማ። አማካዮች፡ አማኑኤል ዮሐንስ ከኢትዮጵያ ቡና፣ ጋቶች ፓኖም ከቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ሽመልስ በቀለ ከአል ጎውና፣ መስዑድ መሐመድ ከጅማ አባጅፋር፣ ሱራፌል ዳኛቸው ከፋሲል ከነማ፣ ፍጹም ዓለሙ ከባሕር ዳር ከተማ፣ ፍሬው ሰለሞን ከሲዳማ ቡና፣ በዛብህ መላዮ ከፋሲል ከነማ እንዲሁም ይሁን እንደሻው ከፋሲል ከነማ። አጥቂዎች፡ አቡበክር ናስር ከኢትዮጵያ ቡና፣ ጌታን ከበደ ከወልቂጤ ከተማ፣ አማኑኤል ገ/ሚካኤል ከቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ሽመክት ጉግሳ ከፋሲል ከነማ፣ ሙጂብ ቃሲም ከጄይኒስ ስፖርቲቭ ዲ ካቢሌ፣ መስፍን ታደሰ ከሐዋሳ ከተማ እንዲሁም ዳዋ ሁጤሳ ከአዳማ ከተማ ተመርጠዋል። ዋሊያዎቹ በካሜሩን ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ዋንጫ የደረሰችው ከዘጠኝ ዓመታት ቆይታ በኋላ ነው። በ1962 (እአአ) የአህጉሪቱን ትልቁን ዋንጫ ያነሱት ዋሊያዎቹ በአፍሪካ ዋንጫ ሲሳተፉ ይህኛው ለ11ኛ ጊዜ ነው። በዓለም እግር ኳስ 137ኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ በአሠልጣኝ ውበቱ አባተና በአምበሉ ጌታነህ ከበደ እየተመራች ወደ ያውንዴ አቅንታለች። ይህ የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ለአሠልጣኝ ውበቱ አባቱና ለቡድኑ አባላት ከአፍሪካ ዋንጫ መሥራቾች አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ ያላትን ተሰጥዖ የሚያሳዩበት መድረክ እንደሚሆን ይገመታል። ውበቱ ለዓይን ገዥ የሆነውን ኳስ እግር ላይ ሳይቆዩ እየተቀባበሉ መጫወትን የሚመርጥ አሠልጣኝ ነው። የመሃል ሜዳው ሞተር ሽመልስ በቀለና አጥቂው ጌታነህ ከበደ ከወጣቱ የኢትዮጵያ ቡና አጥቂ አቡበከር ናስር ጋር በመጣመር ለተቀናቃኞቻቸው አደጋ ሊሆኑ ይችላሉ። ውበቱ በሚመርጠው የ4-3-3 አሠላለፍ ማለትም 4 የኋላ ደጀን ሦስት አማካዮችና ሦስት አጥቂዎች ተመርቶ ወደ ሜዳ እንደሚገባ ይገመታል። ብሔራዊ ቡድኗን በውበቱ አባተ እያጠናከረች ያለችው ኢትዮጵያ ወደ ዙር 16 መሻገር እንደ ትልቅ ውጤት ቢታይ የሚገርም አይሆንም። አልፎም ብሔራዊ ቡድናቸው በአፍሪካ ትልቁ ውድድር ሲሳተፍ ማየት ለጓጉ ኢትዮጵያዊያን ይህ ትልቅ ዕድል ነው።
https://www.bbc.com/amharic/news-59840259
2health
የተከተቡ ሰዎች ለምን በድጋሚ ኮሮናቫይረስ ይይዛቸዋል?
ኮቪድ የሰው ልጅን የሙጥኝ እንዳለ አለ። አሜሪካ፣ ፈረንሳይ፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ አርጀንቲና፣ ብራዚል እና ሌሎም አገራት ውስጥ ኦሚክሮን ተመልሶ እያመሳቸው ነው። በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የሆስፒታል አልጋን እየያዙ ነው። ከእነዚህ የሚበዙት የተከተቡ ናቸው። ታዲያ መከተብ ከተህዋሲው ካልተከላከለ ምንድነው ፋይዳው? እርግጥ ነው ተከተቡ በተባሉ ሰዎች የሚታይ የጎንዮሽ ጉዳት ዝቅተኛ ነው። ብዙ ሰዎች በድኅረ ክትባት ጊዜ ከትኩሳት፣ ከራስ ምታት፣ ከክንድ መለስተኛ ሕመም፣ ከድካምና ከማቅለሽለሽ የከፋ ስሜት አይሰማቸውም። በክትባቱ ታይተዋል የሚባሉት አናፊላክሲስ፣ ቶምቦሲስ፣ ሚዮካርዲቲስ (የልብ አካባቢ መለብለብ) ወዘተ እጅግ ቁጥሩ ባነሱ ተከታቢ ሰዎች ዘንድ ብቻ ነው የተስተዋሉት። አሁን ድፍን ዓለም እየጠየቀ ያለው ጥያቄ ግን አንድ ነው። መከተብ ከተህዋሲው መያዝ ካላዳነ ምንድነው ፋይዳው? የሚል። ቢቢሲ ከሕጻናት ሕክምና አዋቂና የተላላፊ በሽታዎች አጥኚ ሬናቶ ክፎሪ ጋር በዚህ ጉዳይ ላይ ቆይታ አድርጎ ነበር። እሳቸው እንደሚሉት ከሆነ በመጀመሪያው ምዕራፍ ላይ እነ ፋይዘር እና አስትራዜኒካ እንዲሁም ጆንሰን ኤንድ ጆንሰን ክትባታቸውን ሲያበለጽጉ ግብ የነበረው ተህዋሲው ሰዎችን ለከፋ የጤና ችግር እንዳይዳርጋቸው፣ ሲከፋ ደግሞ ለሞት እንዳያበቃቸው እንጂ ተህዋሲው እንዳይዛቸው ለማድረግ አልነበረም። ሐኪሙ ይህ ግባቸው ተሳክቷል ብለው ያምናሉ። "ክትባቶቹ እጅግ ለከፋው የጤና ችግር አጋላጭ ሁኔታ በቂና አስተማማኝ ምላሽ ይሰጣሉ። ቀላልና መለስተኛ ለሆኑ የተህዋሲው ምልክቶች ደግሞ ክትባቶቹ እምብዛምም ናቸው።" እንደ ሐኪሙ ማብራሪያ መጀመሪያውኑም እኮ ክትባቶቹ ሥሪታቸው ወረርሽኙን ማቆም ወይም ሰው በተህዋሲው መልሶ እንዳይያዝ ማድረግ አልነበረም ይላሉ። "ዋናው የክትባቶቹ ተልዕኮ አንድ ነው። ተህዋሲው ሰውነትን ለከፋ አደጋ ብሎም ለሞት እንዳያበቃ ጉዳቱን መቀነስ ነበር፤ ይህም ስኬታማ ነው" ይላሉ። እንደ ምሳሌ የሚያቀርቡት በተለምዶ የጉንፋን ማስታገሻ የምንለው ክትባትን ነው። ያ ክትባት ለዘመናት ሲሰጥ ነው የተኖረው። አንድም ጊዜ ግን ጉንፋኑን ለማጥፋት ተብሎ አግልግሎት ላይ አልዋለም። ሰዎች በጉንፋን የተነሳ ወደከፋ ደዌ እንዳይወደቁ ማገዝ ነው ተግባሩ። ይህ ክትባት ኢንፍሌዌንዛን ለማጥፋት አልተመረተም። ነገር ግን ልጆች፣ ነፍሰጡሮች፣ ሽማግሌዎች እና ገመምተኞች ይህ የኢንፍሌውዛ ተህዋሲዊ ችግር ውስጥ እንዳይጥላቸው ያደርጋቸዋል። የኮቪድ-19 ክትባትም ተመሳሳይ ነው። ወረርሽኝ የማቆም ተልዕኮ የለውም ይላሉ። የኮቪድ-19 ክትባቶች ምን ያህል ሞትን ታድገዋል የሚለውን ብንመለከት ይህን የሐኪሙን ሙግት የሚደግፍ ሆኖ እናገኘዋለን። የኮመንዌልዝ ፈንድ ባወጣው አንድ ሰነድ ላይ እንደተመላከተው ኮሮናቫይረስ ክትባቶች ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት ብቻ አንድ ሚሊዮን ሞትን ተከላክሏል። ነገር ግን 10 ሚሊዮን ሰዎች ደግሞ ሆስፒታል እንዳይገቡና አልጋ እንዳይዙ የሆኑት ክትባት በመውሰዳቸው ነው። ይህ አሐዝ የአሜሪካንን ሕዝብ ብቻ ግምት ውስጥ ያስገባ ነው። የዓለም ጤና ድርጅትና የአውሮፓ የተላላፊ በሽታ ቁጥጥጥር ማዕከል እንደሚገምቱት ደግሞ ግማሽ ሚሊዮን የሚሆኑ ዕድሜያቸው ከ60 ዓመት በላይ የሆኑ፣ በ33 የአውሮፓ አገራት የሚኖሩ ዜጎች ክትባቱ ከሞት ታድጓቸዋል። ይህ በሌላ አነጋገር ሲገለጽ እነዚህ ሰዎች ክትባቱን በወቅቱ ባይከተቡ ኖሮ የመሞት ዕድላቸው ሰፊ ነበር። ከእነዚህ መካከል ምናልባትም በርካታ ሰዎች ተህዋሲው መልሶ አልያዛቸውም ባይባልም፣ ለከፋ ጉዳት እንዳያደርሳቸው የሆነው ግን በመከተባቸውና በመከተባቸው ብቻ ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተከተቡ ሰዎች ለምን በተህዋሲው በብዛት መያዝ ጀመሩ? ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሙሉ ክትባት የወሰዱ ሰዎች ሳይቀር በኦሚክሮን እየተያዙ እንደሆነ የሚስተባበል ጉዳይ አይደለም። ይህ በሦስት ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ይገመታል። በተለይ በምዕራቡ ዓለም ገና እና አዲስ ዓመት ክብረ በዓል ላይ በርካታ ሰዎች በጋራ ብዙ ተቀራርበዋል። ይህ መቀራረብ ተህዋሲው እንደልብ እንዲዛመት ሳያስችለው አልቀረም። ሁለተኛው ምክንያት ክትባቱ ለተቀረው ዓለም ከተሰራጨ ከዓመት በኋላ ተመራማሪዎች የደረሱበት አንድ ፍንትው ያለ ሐቅ ቢኖር፣ ክትባቱ አንድ ጊዜ ተወስዶ በቃ ከዚህ ወዲያ እምብዛም አያስፈልግም የሚባል እንዳልሆነ ነው። "በጊዜ ሂደት የክትባቱ የመከላከል አቅም እንደሚወርድ ደርሰንበታል። አቅሙ የመውረዱ ፍጥነት ደግሞ ከተከታቢው ዕድሜና የተፈጥሮ ሁኔታ ጋር የተያያዘ ነው" ይላሉ ሐኪም ክፎሪ። ይህም ሐቅ ነው ሦስተኛ ዙር የማጠናከሪያ ክትባት ዘመቻ እንዲከፈት ምክንያት የሆነው። ይህ ዘመቻ በቅድሚያ ዕድሜያቸው ለገፋ ብቻ ታስቦ የነበረ ቢሆንም ሌሎች ሰዎችም ቢወስዱት ጥቅም እንጂ ጉዳት እንደሌለው ተደርሶበታል። ያም ሆኖ አሁንም የተከተቡ ሰዎች በተህዋሲው እየተያዙ ነው ያሉት። በዚህ ጉዳይ ላይ ሐኪሙ የሚሉት ይህንን ነው። "ነገሩ እንደ ኢንፍሌዎንዛ ክትባት ነው። ከዚህ ሁኔታ ጋር፣ ከሐቁ ጋር ተስማምተን መኖር መቀጠል ነው የሚኖርብን። ሌላ ነገር የለም።" መልካሙ ነገር ተከትበው ሳለ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በመጣው ልውጥ የኮሮናቫይረስ ምክንያት ወደ ሆስፒታል የሚመጡ ሰዎች ቁጥር እዚህ ግባ የሚባል አለመሆኑ ነው። ይህም የሚያሳየው ክትባቱ ይነስም ይብዛ ሥራውን እየሠራ መሆኑን ነው። ይህን ሐቅ ለማስረዳት ኒውዮርክ ከተማን እንደ ማሳያ መውሰድ ብቻ በቂ ነው። በታኅሣሥ ወር ወደ ሆስፒታል የሚመጡ ሰዎች እና የሟቾች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ አሻቀበ። ከእነዚህ ውስጥ እጅግ የበዙት ክትባት ያልወሰዱ ናቸው። ክትባት የወሰዱ ሰዎች ግን በተህዋሲው ቢያዙም ለሆስፒታል የሚያበቃ ችግር ላይ አልወደቁም። የዩናይትድ ኪንግደም ጤና ቢሮም ቢሆን ከዚህ የተለየ ድምዳሜ ላይ አልደረሰም። የኬምብሪጅ ዩኒቨርስቲ ባወጣው አንድ የጥናት አሐዝ አንድ ሙሉ ጠብታ የተከተበ ሰው በኦሚክሮን ቢያዝ ወደ ሆስፒታል የማይመጣበት ዕድል 81 ከመቶ በላይ ነው። ሐኪሙ የመጨረሻ መልዕክታቸው ይህ ነው። "ብከተብም ባልከተብም ያው በቫይረሱ መያዜ አይቀርምና ቢቀርብኝስ የሚሉት ሰዎች ፍጹም የተሳሳቱ ናቸው። እውነት ነው፣ የተከተበም ያልተከተበም በተህዋሲው ሊያዝ ይችላል። ነገር ግን ውጤታቸው አንድ አይደለም። የተከተቡት በቤታቸው ያልፉታል፤ ያልተከተቡት ግን ይሞታሉ።"
የተከተቡ ሰዎች ለምን በድጋሚ ኮሮናቫይረስ ይይዛቸዋል? ኮቪድ የሰው ልጅን የሙጥኝ እንዳለ አለ። አሜሪካ፣ ፈረንሳይ፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ አርጀንቲና፣ ብራዚል እና ሌሎም አገራት ውስጥ ኦሚክሮን ተመልሶ እያመሳቸው ነው። በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የሆስፒታል አልጋን እየያዙ ነው። ከእነዚህ የሚበዙት የተከተቡ ናቸው። ታዲያ መከተብ ከተህዋሲው ካልተከላከለ ምንድነው ፋይዳው? እርግጥ ነው ተከተቡ በተባሉ ሰዎች የሚታይ የጎንዮሽ ጉዳት ዝቅተኛ ነው። ብዙ ሰዎች በድኅረ ክትባት ጊዜ ከትኩሳት፣ ከራስ ምታት፣ ከክንድ መለስተኛ ሕመም፣ ከድካምና ከማቅለሽለሽ የከፋ ስሜት አይሰማቸውም። በክትባቱ ታይተዋል የሚባሉት አናፊላክሲስ፣ ቶምቦሲስ፣ ሚዮካርዲቲስ (የልብ አካባቢ መለብለብ) ወዘተ እጅግ ቁጥሩ ባነሱ ተከታቢ ሰዎች ዘንድ ብቻ ነው የተስተዋሉት። አሁን ድፍን ዓለም እየጠየቀ ያለው ጥያቄ ግን አንድ ነው። መከተብ ከተህዋሲው መያዝ ካላዳነ ምንድነው ፋይዳው? የሚል። ቢቢሲ ከሕጻናት ሕክምና አዋቂና የተላላፊ በሽታዎች አጥኚ ሬናቶ ክፎሪ ጋር በዚህ ጉዳይ ላይ ቆይታ አድርጎ ነበር። እሳቸው እንደሚሉት ከሆነ በመጀመሪያው ምዕራፍ ላይ እነ ፋይዘር እና አስትራዜኒካ እንዲሁም ጆንሰን ኤንድ ጆንሰን ክትባታቸውን ሲያበለጽጉ ግብ የነበረው ተህዋሲው ሰዎችን ለከፋ የጤና ችግር እንዳይዳርጋቸው፣ ሲከፋ ደግሞ ለሞት እንዳያበቃቸው እንጂ ተህዋሲው እንዳይዛቸው ለማድረግ አልነበረም። ሐኪሙ ይህ ግባቸው ተሳክቷል ብለው ያምናሉ። "ክትባቶቹ እጅግ ለከፋው የጤና ችግር አጋላጭ ሁኔታ በቂና አስተማማኝ ምላሽ ይሰጣሉ። ቀላልና መለስተኛ ለሆኑ የተህዋሲው ምልክቶች ደግሞ ክትባቶቹ እምብዛምም ናቸው።" እንደ ሐኪሙ ማብራሪያ መጀመሪያውኑም እኮ ክትባቶቹ ሥሪታቸው ወረርሽኙን ማቆም ወይም ሰው በተህዋሲው መልሶ እንዳይያዝ ማድረግ አልነበረም ይላሉ። "ዋናው የክትባቶቹ ተልዕኮ አንድ ነው። ተህዋሲው ሰውነትን ለከፋ አደጋ ብሎም ለሞት እንዳያበቃ ጉዳቱን መቀነስ ነበር፤ ይህም ስኬታማ ነው" ይላሉ። እንደ ምሳሌ የሚያቀርቡት በተለምዶ የጉንፋን ማስታገሻ የምንለው ክትባትን ነው። ያ ክትባት ለዘመናት ሲሰጥ ነው የተኖረው። አንድም ጊዜ ግን ጉንፋኑን ለማጥፋት ተብሎ አግልግሎት ላይ አልዋለም። ሰዎች በጉንፋን የተነሳ ወደከፋ ደዌ እንዳይወደቁ ማገዝ ነው ተግባሩ። ይህ ክትባት ኢንፍሌዌንዛን ለማጥፋት አልተመረተም። ነገር ግን ልጆች፣ ነፍሰጡሮች፣ ሽማግሌዎች እና ገመምተኞች ይህ የኢንፍሌውዛ ተህዋሲዊ ችግር ውስጥ እንዳይጥላቸው ያደርጋቸዋል። የኮቪድ-19 ክትባትም ተመሳሳይ ነው። ወረርሽኝ የማቆም ተልዕኮ የለውም ይላሉ። የኮቪድ-19 ክትባቶች ምን ያህል ሞትን ታድገዋል የሚለውን ብንመለከት ይህን የሐኪሙን ሙግት የሚደግፍ ሆኖ እናገኘዋለን። የኮመንዌልዝ ፈንድ ባወጣው አንድ ሰነድ ላይ እንደተመላከተው ኮሮናቫይረስ ክትባቶች ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት ብቻ አንድ ሚሊዮን ሞትን ተከላክሏል። ነገር ግን 10 ሚሊዮን ሰዎች ደግሞ ሆስፒታል እንዳይገቡና አልጋ እንዳይዙ የሆኑት ክትባት በመውሰዳቸው ነው። ይህ አሐዝ የአሜሪካንን ሕዝብ ብቻ ግምት ውስጥ ያስገባ ነው። የዓለም ጤና ድርጅትና የአውሮፓ የተላላፊ በሽታ ቁጥጥጥር ማዕከል እንደሚገምቱት ደግሞ ግማሽ ሚሊዮን የሚሆኑ ዕድሜያቸው ከ60 ዓመት በላይ የሆኑ፣ በ33 የአውሮፓ አገራት የሚኖሩ ዜጎች ክትባቱ ከሞት ታድጓቸዋል። ይህ በሌላ አነጋገር ሲገለጽ እነዚህ ሰዎች ክትባቱን በወቅቱ ባይከተቡ ኖሮ የመሞት ዕድላቸው ሰፊ ነበር። ከእነዚህ መካከል ምናልባትም በርካታ ሰዎች ተህዋሲው መልሶ አልያዛቸውም ባይባልም፣ ለከፋ ጉዳት እንዳያደርሳቸው የሆነው ግን በመከተባቸውና በመከተባቸው ብቻ ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተከተቡ ሰዎች ለምን በተህዋሲው በብዛት መያዝ ጀመሩ? ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሙሉ ክትባት የወሰዱ ሰዎች ሳይቀር በኦሚክሮን እየተያዙ እንደሆነ የሚስተባበል ጉዳይ አይደለም። ይህ በሦስት ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ይገመታል። በተለይ በምዕራቡ ዓለም ገና እና አዲስ ዓመት ክብረ በዓል ላይ በርካታ ሰዎች በጋራ ብዙ ተቀራርበዋል። ይህ መቀራረብ ተህዋሲው እንደልብ እንዲዛመት ሳያስችለው አልቀረም። ሁለተኛው ምክንያት ክትባቱ ለተቀረው ዓለም ከተሰራጨ ከዓመት በኋላ ተመራማሪዎች የደረሱበት አንድ ፍንትው ያለ ሐቅ ቢኖር፣ ክትባቱ አንድ ጊዜ ተወስዶ በቃ ከዚህ ወዲያ እምብዛም አያስፈልግም የሚባል እንዳልሆነ ነው። "በጊዜ ሂደት የክትባቱ የመከላከል አቅም እንደሚወርድ ደርሰንበታል። አቅሙ የመውረዱ ፍጥነት ደግሞ ከተከታቢው ዕድሜና የተፈጥሮ ሁኔታ ጋር የተያያዘ ነው" ይላሉ ሐኪም ክፎሪ። ይህም ሐቅ ነው ሦስተኛ ዙር የማጠናከሪያ ክትባት ዘመቻ እንዲከፈት ምክንያት የሆነው። ይህ ዘመቻ በቅድሚያ ዕድሜያቸው ለገፋ ብቻ ታስቦ የነበረ ቢሆንም ሌሎች ሰዎችም ቢወስዱት ጥቅም እንጂ ጉዳት እንደሌለው ተደርሶበታል። ያም ሆኖ አሁንም የተከተቡ ሰዎች በተህዋሲው እየተያዙ ነው ያሉት። በዚህ ጉዳይ ላይ ሐኪሙ የሚሉት ይህንን ነው። "ነገሩ እንደ ኢንፍሌዎንዛ ክትባት ነው። ከዚህ ሁኔታ ጋር፣ ከሐቁ ጋር ተስማምተን መኖር መቀጠል ነው የሚኖርብን። ሌላ ነገር የለም።" መልካሙ ነገር ተከትበው ሳለ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በመጣው ልውጥ የኮሮናቫይረስ ምክንያት ወደ ሆስፒታል የሚመጡ ሰዎች ቁጥር እዚህ ግባ የሚባል አለመሆኑ ነው። ይህም የሚያሳየው ክትባቱ ይነስም ይብዛ ሥራውን እየሠራ መሆኑን ነው። ይህን ሐቅ ለማስረዳት ኒውዮርክ ከተማን እንደ ማሳያ መውሰድ ብቻ በቂ ነው። በታኅሣሥ ወር ወደ ሆስፒታል የሚመጡ ሰዎች እና የሟቾች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ አሻቀበ። ከእነዚህ ውስጥ እጅግ የበዙት ክትባት ያልወሰዱ ናቸው። ክትባት የወሰዱ ሰዎች ግን በተህዋሲው ቢያዙም ለሆስፒታል የሚያበቃ ችግር ላይ አልወደቁም። የዩናይትድ ኪንግደም ጤና ቢሮም ቢሆን ከዚህ የተለየ ድምዳሜ ላይ አልደረሰም። የኬምብሪጅ ዩኒቨርስቲ ባወጣው አንድ የጥናት አሐዝ አንድ ሙሉ ጠብታ የተከተበ ሰው በኦሚክሮን ቢያዝ ወደ ሆስፒታል የማይመጣበት ዕድል 81 ከመቶ በላይ ነው። ሐኪሙ የመጨረሻ መልዕክታቸው ይህ ነው። "ብከተብም ባልከተብም ያው በቫይረሱ መያዜ አይቀርምና ቢቀርብኝስ የሚሉት ሰዎች ፍጹም የተሳሳቱ ናቸው። እውነት ነው፣ የተከተበም ያልተከተበም በተህዋሲው ሊያዝ ይችላል። ነገር ግን ውጤታቸው አንድ አይደለም። የተከተቡት በቤታቸው ያልፉታል፤ ያልተከተቡት ግን ይሞታሉ።"
https://www.bbc.com/amharic/news-59925005
3politics
ኡጋንዳ ከሙዚቀኛው ተቃዋሚ ጋር ግንኙነት ያላቸው የዩቲዩብ ቻናሎች እንዲታገዱ ጠየቀች
የኡጋንዳ መንግሥት ከታዋቂው ሙዚቀኛና ተቃዋሚ ቦቢ ዋይን ግንኙነት ያላቸው የዩቲዩብ ቻናሎች እንዲታገዱ ጠይቋል። በኡጋንዳ የኮሚዩኒኬሽን ዘርፉን በዋነኝነት የሚቆጣጠረው አካል አስራ አራት የዩቲየብ ቻናሎች እንዲዘጉ ጠይቋል። ተቆጣጣሪው አካል ደብዳቤውን የፃፈው የዩቲዩብ ባለቤት ለሆነው ጉግል ሲሆን በባለፈው ወር ከደረስው ነውጥም ጋር ግንኙነት ያላቸውና ለ50 ሰዎችም መሞት ተጠያቂ ናቸው ያላቸው እንደሆነም አስፍሯል። በአገሪቱ ውስጥ ዋነኛ ተቃዋሚ የሚባለው ሮበርት ካያጉላንይ ወይም ቦቢ ዋይን እስር ተከትሎም በመዲናዋም ካምፓላም ሆነ በዋነኞቹ ከተሞች ነውጥ ተከስቷል። ሙዚቀኛው ቦቢ ዋይን የኮሮናቫይረስ መመሪያዎችን ጥሷል በሚልም ነው ለእስር የተዳረገው። እንዲታገዱ የተወሰኑት የዩቲዩብ ቻናሎች ከሙዚቀኛው ጋር ግንኙነት አላቸው ቢባልም የኡጋንዳ ኮሚዩኒኬሽን የህግ ጉዳዮች ኃላፊ በበኩላቸው "የአጋጣሚ ጉዳይ ነው" ማለታቸውን ብሉምበርግ ዘግቧል። ኮሚሽኑ ለጉግል በፃፈው ደብዳቤ የዩቲብ ቻናሎቹን ነውጡን ለማነሳሳት ተጠቅመውበታል፤ ከህግ ውጭ ያላቸውንም ይዘቶች አሳይተዋል በማለትም ዴይሊ ሞኒተር ጋዜጣ ፅፏል። ኡጋንዳ በጥር ወር ምርጫዋን ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ናት። አገሪቷን ከሶስት አስርት አመታት በላይ የመሯት ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪንም በምርጫው ይወዳደራሉ።
ኡጋንዳ ከሙዚቀኛው ተቃዋሚ ጋር ግንኙነት ያላቸው የዩቲዩብ ቻናሎች እንዲታገዱ ጠየቀች የኡጋንዳ መንግሥት ከታዋቂው ሙዚቀኛና ተቃዋሚ ቦቢ ዋይን ግንኙነት ያላቸው የዩቲዩብ ቻናሎች እንዲታገዱ ጠይቋል። በኡጋንዳ የኮሚዩኒኬሽን ዘርፉን በዋነኝነት የሚቆጣጠረው አካል አስራ አራት የዩቲየብ ቻናሎች እንዲዘጉ ጠይቋል። ተቆጣጣሪው አካል ደብዳቤውን የፃፈው የዩቲዩብ ባለቤት ለሆነው ጉግል ሲሆን በባለፈው ወር ከደረስው ነውጥም ጋር ግንኙነት ያላቸውና ለ50 ሰዎችም መሞት ተጠያቂ ናቸው ያላቸው እንደሆነም አስፍሯል። በአገሪቱ ውስጥ ዋነኛ ተቃዋሚ የሚባለው ሮበርት ካያጉላንይ ወይም ቦቢ ዋይን እስር ተከትሎም በመዲናዋም ካምፓላም ሆነ በዋነኞቹ ከተሞች ነውጥ ተከስቷል። ሙዚቀኛው ቦቢ ዋይን የኮሮናቫይረስ መመሪያዎችን ጥሷል በሚልም ነው ለእስር የተዳረገው። እንዲታገዱ የተወሰኑት የዩቲዩብ ቻናሎች ከሙዚቀኛው ጋር ግንኙነት አላቸው ቢባልም የኡጋንዳ ኮሚዩኒኬሽን የህግ ጉዳዮች ኃላፊ በበኩላቸው "የአጋጣሚ ጉዳይ ነው" ማለታቸውን ብሉምበርግ ዘግቧል። ኮሚሽኑ ለጉግል በፃፈው ደብዳቤ የዩቲብ ቻናሎቹን ነውጡን ለማነሳሳት ተጠቅመውበታል፤ ከህግ ውጭ ያላቸውንም ይዘቶች አሳይተዋል በማለትም ዴይሊ ሞኒተር ጋዜጣ ፅፏል። ኡጋንዳ በጥር ወር ምርጫዋን ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ናት። አገሪቷን ከሶስት አስርት አመታት በላይ የመሯት ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪንም በምርጫው ይወዳደራሉ።
https://www.bbc.com/amharic/news-55329580
5sports
እግር ኳስ፡ አምስት ቁልፍ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች በኮሮናቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ
ኢትዮጵያ ጥቅምት ወር መጨረሻ ላይ ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ውድድር ከኒጀር ጋር ለምታደርገው የደርሶ መልስ ጨዋታ ተጠርተው ከነበሩት ተጫዋቾች መካከል አምስት ቁልፍ ተጫዋቾች ኮቪድ-19 እንደተገኘባቸው ተነገረ። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን ለቢቢሲ እንዳረጋገጡት ለብሔራዊ ቡድኑ ተጠርተው ከነበሩት 36 ተጫዋቾች መካከል ለቡድኑ ወሳኝ የሆኑት አምስት ተጫዋቾች በተደረገላቸው ምርመራ የኮሮናቫይረስ ተገኝቶባቸዋል። አቶ ባህሩ ለውድድሩ 41 ተጫዋቾች መጠራታቸውን አስታውሰው፣ አምስቱ በተለያየ ምክንያት ቡድኑን አለመቀላቀላቸውን አመልክተዋል። ከአምስቱ መካከል ሁለቱ በአሁን ሰዓት በውጭ አገር በሙከራና በመጫወት ላይ የሚገኙ ተጫዋቾች ናቸው ብለዋል። ኃላፊው አክለውም ሁለት ተጫዋቾች ዘግይተው ቡድኑን መቀላቀላቸውን ገልፀው፤ አንደኛው ደግሞ ከዚህ ቀደም በነበረበት ጉዳት ምክንያት ቡድኑን መቀላለቀል ያልቸለ መሆኑን ተናግረዋል። ለእግር ኳስ ቡድኑ አባላት የኮቪድ-19 ምርመራ ከመደረጉ በፊት የልብ ምርመራን ጨምሮ አጠቃላይ የጤና ምርመራ መደረጉን የተናገሩት ኃላፊው፤ የኮቪድ-19 ምርመራውም ለሁሉም መሰጠቱን ገልጸዋል። በዚህም መሠረት ለብሔራዊ ቡድኑ ለተጠሩት ለአጠቃላዩ 36 ተጫዋቾች የኮሮናቫይረስ ምርመራ ተደርጎ አምስት ተጫዋቾች ላይ ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል ብለዋል አቶ ባሕሩ። ቫይረሱ ከተገኘባቸው ተጫዋቾች ጋር ንክኪ አላቸው የተባሉትን የመለየት ሥራ እየተሰራም መሆኑን ጨምረው አመልክተዋል። እነዚህ ቫይረሱ የተገኘባቸው አምስት ተጫዋቾች በአሁኑ ጊዜ በሆቴል ራሳቸውን ለይተው እንዲቆዩ መደረጉን በመግለጽ፣ ልምምድ እየሰሩ በቶሎ እንዲያገግሙ ፌዴሬሽኑ የተቻለውን ሁሉ እያደረገ መሆን አብራርተዋል። የአምስቱ ተጫዋቾች ውጤት እንደተሰማ በቡድኑ አባላት መካከል ድንጋጤ ተፈጥሮ የነበረ ቢሆንም ከኅብረተሰብ ጤና ኢንስትትዩት የመጡ ባለሙያዎች ሙያዊ ምክር እንደሰጧቸውም ተገልጿል። እነዚህ በኮቪድ-19 የተያዙ አምስት ተጫዋቾች ለለይቶ ማቆያነት ፈቃድ ወደ ተሰጣቸው ሆቴሎች ዛሬ፣ ሰኞ፣ እንደሚዛወሩም ኃፊው አክለው ተናግረዋል። አምስቱ ተጫዋቾች በቡድኑ ውስጥ ቁልፍ ሚና እንደነበራቸው ያስታወሱት አቶ ባሕሩ በቡድኑ ላይ የሥነ ልቦና ጫና ቢኖረውም ቶሎ አገግመው ወደ ቡድኑ እንዲቀላቀሉ ይደረጋል ብለዋል። ተጫዋቾቹ ከ14 ቀን ለይቶ ማቆያ በኋላ ለጨዋታው ይደርሳሉ ተብሎ እንደሚገመት ተናግረው፣ እነዚህን ተጫዋቾች ወደ ቡድኑ የመቀላቀል ውሳኔ ግን የአሰልጣኙ መሆኑን አስረድተዋል። ቀሪ የቡድኑ አባላትን ከኮሮናቫይረስ ለመጠበቅ የተለያዩ የጥንቃቄ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑንም አብራርተዋል። ኢትዮጵያ ከኒጀር ጋር የሚኖራት ጨዋታ የሚካሄደው ጥቅምት 30/2013 ዓ.ም መሆኑ ኃላፊው ጨምረው ገልፀዋል። በተያያዘ ዜና ከኮሮናቫይረስ ስጋት ጋር በተያያዘ ተቆርጠው የቆዩት ከፍተኛ ሊግ፣ አንደኛ ሊግና የሴቶች ፕሪሚየር ሊግን ኅዳር አጋማሽ ላይ ለመጀመር የእግር ስ ፌዴሬሽኑ አቅዶ ለቡድኖች ማሳወቁንና እነርሱም ዝግጅት ማድረጋቸውን አክለው ተናግረዋል። ውድድሮቹ የሚካሄዱት በዝግ ስታዲየም መሆኑን ገልፀው በሂደት አማራጮች እየታዩ ደጋፊዎች የሚገቡበት ሁኔታ ይፈቀዳል ብለው እንደሚያስቡ ለቢቢሲ አቶ ባሕሩ ጥላሁን ተናግረዋል።
እግር ኳስ፡ አምስት ቁልፍ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች በኮሮናቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ ኢትዮጵያ ጥቅምት ወር መጨረሻ ላይ ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ውድድር ከኒጀር ጋር ለምታደርገው የደርሶ መልስ ጨዋታ ተጠርተው ከነበሩት ተጫዋቾች መካከል አምስት ቁልፍ ተጫዋቾች ኮቪድ-19 እንደተገኘባቸው ተነገረ። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን ለቢቢሲ እንዳረጋገጡት ለብሔራዊ ቡድኑ ተጠርተው ከነበሩት 36 ተጫዋቾች መካከል ለቡድኑ ወሳኝ የሆኑት አምስት ተጫዋቾች በተደረገላቸው ምርመራ የኮሮናቫይረስ ተገኝቶባቸዋል። አቶ ባህሩ ለውድድሩ 41 ተጫዋቾች መጠራታቸውን አስታውሰው፣ አምስቱ በተለያየ ምክንያት ቡድኑን አለመቀላቀላቸውን አመልክተዋል። ከአምስቱ መካከል ሁለቱ በአሁን ሰዓት በውጭ አገር በሙከራና በመጫወት ላይ የሚገኙ ተጫዋቾች ናቸው ብለዋል። ኃላፊው አክለውም ሁለት ተጫዋቾች ዘግይተው ቡድኑን መቀላቀላቸውን ገልፀው፤ አንደኛው ደግሞ ከዚህ ቀደም በነበረበት ጉዳት ምክንያት ቡድኑን መቀላለቀል ያልቸለ መሆኑን ተናግረዋል። ለእግር ኳስ ቡድኑ አባላት የኮቪድ-19 ምርመራ ከመደረጉ በፊት የልብ ምርመራን ጨምሮ አጠቃላይ የጤና ምርመራ መደረጉን የተናገሩት ኃላፊው፤ የኮቪድ-19 ምርመራውም ለሁሉም መሰጠቱን ገልጸዋል። በዚህም መሠረት ለብሔራዊ ቡድኑ ለተጠሩት ለአጠቃላዩ 36 ተጫዋቾች የኮሮናቫይረስ ምርመራ ተደርጎ አምስት ተጫዋቾች ላይ ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል ብለዋል አቶ ባሕሩ። ቫይረሱ ከተገኘባቸው ተጫዋቾች ጋር ንክኪ አላቸው የተባሉትን የመለየት ሥራ እየተሰራም መሆኑን ጨምረው አመልክተዋል። እነዚህ ቫይረሱ የተገኘባቸው አምስት ተጫዋቾች በአሁኑ ጊዜ በሆቴል ራሳቸውን ለይተው እንዲቆዩ መደረጉን በመግለጽ፣ ልምምድ እየሰሩ በቶሎ እንዲያገግሙ ፌዴሬሽኑ የተቻለውን ሁሉ እያደረገ መሆን አብራርተዋል። የአምስቱ ተጫዋቾች ውጤት እንደተሰማ በቡድኑ አባላት መካከል ድንጋጤ ተፈጥሮ የነበረ ቢሆንም ከኅብረተሰብ ጤና ኢንስትትዩት የመጡ ባለሙያዎች ሙያዊ ምክር እንደሰጧቸውም ተገልጿል። እነዚህ በኮቪድ-19 የተያዙ አምስት ተጫዋቾች ለለይቶ ማቆያነት ፈቃድ ወደ ተሰጣቸው ሆቴሎች ዛሬ፣ ሰኞ፣ እንደሚዛወሩም ኃፊው አክለው ተናግረዋል። አምስቱ ተጫዋቾች በቡድኑ ውስጥ ቁልፍ ሚና እንደነበራቸው ያስታወሱት አቶ ባሕሩ በቡድኑ ላይ የሥነ ልቦና ጫና ቢኖረውም ቶሎ አገግመው ወደ ቡድኑ እንዲቀላቀሉ ይደረጋል ብለዋል። ተጫዋቾቹ ከ14 ቀን ለይቶ ማቆያ በኋላ ለጨዋታው ይደርሳሉ ተብሎ እንደሚገመት ተናግረው፣ እነዚህን ተጫዋቾች ወደ ቡድኑ የመቀላቀል ውሳኔ ግን የአሰልጣኙ መሆኑን አስረድተዋል። ቀሪ የቡድኑ አባላትን ከኮሮናቫይረስ ለመጠበቅ የተለያዩ የጥንቃቄ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑንም አብራርተዋል። ኢትዮጵያ ከኒጀር ጋር የሚኖራት ጨዋታ የሚካሄደው ጥቅምት 30/2013 ዓ.ም መሆኑ ኃላፊው ጨምረው ገልፀዋል። በተያያዘ ዜና ከኮሮናቫይረስ ስጋት ጋር በተያያዘ ተቆርጠው የቆዩት ከፍተኛ ሊግ፣ አንደኛ ሊግና የሴቶች ፕሪሚየር ሊግን ኅዳር አጋማሽ ላይ ለመጀመር የእግር ስ ፌዴሬሽኑ አቅዶ ለቡድኖች ማሳወቁንና እነርሱም ዝግጅት ማድረጋቸውን አክለው ተናግረዋል። ውድድሮቹ የሚካሄዱት በዝግ ስታዲየም መሆኑን ገልፀው በሂደት አማራጮች እየታዩ ደጋፊዎች የሚገቡበት ሁኔታ ይፈቀዳል ብለው እንደሚያስቡ ለቢቢሲ አቶ ባሕሩ ጥላሁን ተናግረዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-54417243
2health
ኮሮናቫይረስ፡ በኦክስጂን እጥረት በርካቶች በሚሞቱባት ሕንድ ሆስፒታል ላይ በተነሳ እሳት 13 ህሙማን ሞቱ
ዛሬ አርብ በሕንዷ ከተማ ሙምባይ አቅራቢያ ባለ ኮቪድ-19 ህክምና ሆስፒታል ላይ በተነሳ ቢያንስ 13 ሰዎች መሞታቸው ተነገረ። አርብ ጠዋት የተቀሰቀሰው እሳት ለበርካቶች ሞት ምክንያት ከሆነ በኋላ በቁጥጥር ሰር የዋለ ሲሆን ከአደጋው ተረፉት ህሙማን በአቅራቢያ ወደሚገኝ ሆስፒታል ተዘዋውረዋል። በርካታ ሰዎች በወረርሽኙ እየተያዙባት ባለችው ሕንድ በዛሬው ዕለት ብቻ 332,730 ሰዎች ላይ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሲሆን ይህም በዓለም በአንድ ቀን የተመዘገበው የህሙማን ቁጥር ነው ተብሏል። በበሽታው ሰበብ ህይወታቸው ሚያልፍ ሰዎች አሃዝም እጅግ ከፍተኛ ሲሆን ባለፉት 24 ሰዓታት 2,263 ሰዎች መሞታቸው ተገልጿል። በሕንድ ለሁለተኛ ጊዜ የተከሰተውን የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ተከትሎ በዋና ከተማዋ ኒው ደልሂ ያሉ ሆስፒታሎች ከፍተኛ የኦክስጂን እጥረት አጋጥሟቸዋል። በዚህም ኦክስጂን በመጠባበቅ ላይ የነበሩ ታማሚዎች ህይወት እያለፈ መሆኑን እና በሕንድ ምርጥ የተባለ የጤና መሰረተ ልማት ባያላት ኒው ደልሂ ከተማ ለጽኑ ህሙማን የሚሆኑ አልጋዎች ሞልተዋል ተብሏል። እስከ አሁን ድረስ 16 ሚሊዮን ዜጎቿ በኮሮናቫይረስ መያዛቸውን ሕንድ አረጋግጣለች። ትናንት ሐሙስ ይፋ የተደረገው የ24 ሰዓታት የምርመራ ውጤት ብቻ ከ314 ሺህ በላይ ሰዎች በአንድ ቀን በወረርሽኙ መያዛቸውን እና ከሁለት ሺህ በላይ ሰዎች መሞታቸውን ያሳያል። የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስቴር ናሬንድራ ሞዲም በቫይረሱ ከባድ ጉዳት ከደረሰባቸው ግዛቶች መሪዎች እና ከኦክስጂን አምራቾች ጋር ዛሬ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል። ከኒው ደልሂ ውጪ ጉጃራት፣ ኡታር ፕራዴሽ እና ሃርያና የተሰኙት ግዛቶች ተመሳሳይ የኦክስጂን እጥረት ገጥሟቸዋል። ግዛቶች የኦክስጂን መያዣ ጋኖች ወደ ሌሎች ግዛቶች እንዳይዘዋወሩ በማገድ ላይ ሲሆኑ፤ የተወሰኑ ተቋማት ምርቶቻቸውን ማከማቸት መጀመራቸውን የደልሂ ቴሌቪዥን ዘግቧል። በኮቪድ-19 ተይዞ በህክምና ላይ ያለው የሕንድ ፖለቲከኛ ሳውራህ ባራድዋጅ በትዊተር ገጹ የተገጠመለት ኦክስጂን ሊያልቅ የቀረው ሦስት ሰዓታት ብቻ መሆኑን አጋርቶ ነበር። "ብዙ ሰዎች በኦክስጅን ላይ ጥገኛ ሆነው ነው ያሉት። የተገጠመላቸው ኦክስጂን ሲጠናቀቅ ህይወታቸው ያልፋል። ይህ ጊዜ በጋራ ተባብረን የምንሰራበት ነው" ሲል ተማፅኗል። በበሽታው ምክንያት የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ከፍተኛ በመሆኑ በሕንድ ባህል መሰረት የሞቱ ሰዎች አስከሬንን ለማቃጠል ከፍተኛ ወረፋ መኖሩን ቤተሰቦች ገልጸዋል። አንድ ሐኪም በሆስፒታ ውስጥ ተራ የሚጠብቁ በርካታ አስከሬኖች መኖራቸውንም ገልጿል።
ኮሮናቫይረስ፡ በኦክስጂን እጥረት በርካቶች በሚሞቱባት ሕንድ ሆስፒታል ላይ በተነሳ እሳት 13 ህሙማን ሞቱ ዛሬ አርብ በሕንዷ ከተማ ሙምባይ አቅራቢያ ባለ ኮቪድ-19 ህክምና ሆስፒታል ላይ በተነሳ ቢያንስ 13 ሰዎች መሞታቸው ተነገረ። አርብ ጠዋት የተቀሰቀሰው እሳት ለበርካቶች ሞት ምክንያት ከሆነ በኋላ በቁጥጥር ሰር የዋለ ሲሆን ከአደጋው ተረፉት ህሙማን በአቅራቢያ ወደሚገኝ ሆስፒታል ተዘዋውረዋል። በርካታ ሰዎች በወረርሽኙ እየተያዙባት ባለችው ሕንድ በዛሬው ዕለት ብቻ 332,730 ሰዎች ላይ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሲሆን ይህም በዓለም በአንድ ቀን የተመዘገበው የህሙማን ቁጥር ነው ተብሏል። በበሽታው ሰበብ ህይወታቸው ሚያልፍ ሰዎች አሃዝም እጅግ ከፍተኛ ሲሆን ባለፉት 24 ሰዓታት 2,263 ሰዎች መሞታቸው ተገልጿል። በሕንድ ለሁለተኛ ጊዜ የተከሰተውን የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ተከትሎ በዋና ከተማዋ ኒው ደልሂ ያሉ ሆስፒታሎች ከፍተኛ የኦክስጂን እጥረት አጋጥሟቸዋል። በዚህም ኦክስጂን በመጠባበቅ ላይ የነበሩ ታማሚዎች ህይወት እያለፈ መሆኑን እና በሕንድ ምርጥ የተባለ የጤና መሰረተ ልማት ባያላት ኒው ደልሂ ከተማ ለጽኑ ህሙማን የሚሆኑ አልጋዎች ሞልተዋል ተብሏል። እስከ አሁን ድረስ 16 ሚሊዮን ዜጎቿ በኮሮናቫይረስ መያዛቸውን ሕንድ አረጋግጣለች። ትናንት ሐሙስ ይፋ የተደረገው የ24 ሰዓታት የምርመራ ውጤት ብቻ ከ314 ሺህ በላይ ሰዎች በአንድ ቀን በወረርሽኙ መያዛቸውን እና ከሁለት ሺህ በላይ ሰዎች መሞታቸውን ያሳያል። የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስቴር ናሬንድራ ሞዲም በቫይረሱ ከባድ ጉዳት ከደረሰባቸው ግዛቶች መሪዎች እና ከኦክስጂን አምራቾች ጋር ዛሬ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል። ከኒው ደልሂ ውጪ ጉጃራት፣ ኡታር ፕራዴሽ እና ሃርያና የተሰኙት ግዛቶች ተመሳሳይ የኦክስጂን እጥረት ገጥሟቸዋል። ግዛቶች የኦክስጂን መያዣ ጋኖች ወደ ሌሎች ግዛቶች እንዳይዘዋወሩ በማገድ ላይ ሲሆኑ፤ የተወሰኑ ተቋማት ምርቶቻቸውን ማከማቸት መጀመራቸውን የደልሂ ቴሌቪዥን ዘግቧል። በኮቪድ-19 ተይዞ በህክምና ላይ ያለው የሕንድ ፖለቲከኛ ሳውራህ ባራድዋጅ በትዊተር ገጹ የተገጠመለት ኦክስጂን ሊያልቅ የቀረው ሦስት ሰዓታት ብቻ መሆኑን አጋርቶ ነበር። "ብዙ ሰዎች በኦክስጅን ላይ ጥገኛ ሆነው ነው ያሉት። የተገጠመላቸው ኦክስጂን ሲጠናቀቅ ህይወታቸው ያልፋል። ይህ ጊዜ በጋራ ተባብረን የምንሰራበት ነው" ሲል ተማፅኗል። በበሽታው ምክንያት የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ከፍተኛ በመሆኑ በሕንድ ባህል መሰረት የሞቱ ሰዎች አስከሬንን ለማቃጠል ከፍተኛ ወረፋ መኖሩን ቤተሰቦች ገልጸዋል። አንድ ሐኪም በሆስፒታ ውስጥ ተራ የሚጠብቁ በርካታ አስከሬኖች መኖራቸውንም ገልጿል።
https://www.bbc.com/amharic/news-56827449
5sports
የጀርመን ቡንደስሊጋ ቡድኖች ለ'ብላክ ላይቭስ ማተር' ያላቸውን ድጋፍ አሳዩ
የጀርመን ቡንደስሊጋ የእግር ኳስ ቡድኖች ለ'ብላክ ላይቭስ ማተር' እንቅስቃሴ ያላቸውን ድጋፍ በትናንትናው ዕለት በተለያዩ ተቃውሞዎች አሳይተዋል። የብሮሲያ ዶርትሙንድና ሄርታ በርሊን ተጫዋቾች በሲግናል ኢዱና ፓርክ በመገኘት ሜዳውን በመክበብም በጉልበታቸው ተንበርክከው ነበር። የዶርትሙንድ ተጫዋቾች ከውድድሩ በፊት ሲያሟሙቁ "ፍትህ ከሌለ ሰላም የለም" እንዲሁም "ተባብረን እንቁም" የሚሉ መልእክቶች በተፃፈባቸው ማሊያዎች (ካናቴራዎች) ነው። የባየር ሙኒክ ተወዳዳሪዎች "ለዘረኝነት ቀይ ካርድ" የሚል ማሊያ (ካናቴራ) ለብሰው የነበረ ሲሆን፤ በዛኑ ዕለት ባየር ሌቨርኩሰንን 4 ለ2 በሆነ ውጤት ረትተዋል። የቡንደስሊጋ ቡድኑ አመራሮችም እንዲሁም የቡድኑ አባላት በጨዋታዎች ላይ 'ብላክ ላይቭስ ማተር' የሚል ፅሁፍ ያለበት እጃቸው ላይ አጥልቀው ነበር ተብሏል። የሜይንዝ ቡድን አጥቂ ካሜሮናዊው ፒየር ኩንዴ ከኤይንትራችት ፍራንክፈርት ጋር ባደረጉት ጨዋታም ላይ ጎል ካስቆጠረ በኋላ በጉልበቱ ተንበርክኳል። በግጥሚያው ቡድኑ 2 ለ0 ረትቷል። በዚህ ሳምንትም ታዋቂዎቹ የስፖርት ሰዎች ሴረና ዊልያምስ፣ ፓውል ፖግባና ሊውስ ሃሚልተን በአሜሪካ በጥቁሮች ላይ የሚፈፀመውን የፖሊስ ጭካኔ አስመልክቶ ድምፃቸውን አሰምተዋል። ባለፈው ሳምንት በሚኒያፖሊስ ጥቁር አሜሪካዊው ጆርጅ ፍሎይድ እጁ ከኋላ እንደተጠፈረ ከመሬት ላይ ተጣብቆ ነጭ ፖሊስ አንገቱን በጉልበቱ ለዘጠኝ ደቂቃ ተጭኖት ህይወቱ ማለፉን ተከትሎ በበርካታ ግዛቶች ተቃውሞች ተቀጣጥለዋል።
የጀርመን ቡንደስሊጋ ቡድኖች ለ'ብላክ ላይቭስ ማተር' ያላቸውን ድጋፍ አሳዩ የጀርመን ቡንደስሊጋ የእግር ኳስ ቡድኖች ለ'ብላክ ላይቭስ ማተር' እንቅስቃሴ ያላቸውን ድጋፍ በትናንትናው ዕለት በተለያዩ ተቃውሞዎች አሳይተዋል። የብሮሲያ ዶርትሙንድና ሄርታ በርሊን ተጫዋቾች በሲግናል ኢዱና ፓርክ በመገኘት ሜዳውን በመክበብም በጉልበታቸው ተንበርክከው ነበር። የዶርትሙንድ ተጫዋቾች ከውድድሩ በፊት ሲያሟሙቁ "ፍትህ ከሌለ ሰላም የለም" እንዲሁም "ተባብረን እንቁም" የሚሉ መልእክቶች በተፃፈባቸው ማሊያዎች (ካናቴራዎች) ነው። የባየር ሙኒክ ተወዳዳሪዎች "ለዘረኝነት ቀይ ካርድ" የሚል ማሊያ (ካናቴራ) ለብሰው የነበረ ሲሆን፤ በዛኑ ዕለት ባየር ሌቨርኩሰንን 4 ለ2 በሆነ ውጤት ረትተዋል። የቡንደስሊጋ ቡድኑ አመራሮችም እንዲሁም የቡድኑ አባላት በጨዋታዎች ላይ 'ብላክ ላይቭስ ማተር' የሚል ፅሁፍ ያለበት እጃቸው ላይ አጥልቀው ነበር ተብሏል። የሜይንዝ ቡድን አጥቂ ካሜሮናዊው ፒየር ኩንዴ ከኤይንትራችት ፍራንክፈርት ጋር ባደረጉት ጨዋታም ላይ ጎል ካስቆጠረ በኋላ በጉልበቱ ተንበርክኳል። በግጥሚያው ቡድኑ 2 ለ0 ረትቷል። በዚህ ሳምንትም ታዋቂዎቹ የስፖርት ሰዎች ሴረና ዊልያምስ፣ ፓውል ፖግባና ሊውስ ሃሚልተን በአሜሪካ በጥቁሮች ላይ የሚፈፀመውን የፖሊስ ጭካኔ አስመልክቶ ድምፃቸውን አሰምተዋል። ባለፈው ሳምንት በሚኒያፖሊስ ጥቁር አሜሪካዊው ጆርጅ ፍሎይድ እጁ ከኋላ እንደተጠፈረ ከመሬት ላይ ተጣብቆ ነጭ ፖሊስ አንገቱን በጉልበቱ ለዘጠኝ ደቂቃ ተጭኖት ህይወቱ ማለፉን ተከትሎ በበርካታ ግዛቶች ተቃውሞች ተቀጣጥለዋል።
https://www.bbc.com/amharic/news-52954511

Dataset Card for [Dataset Name]

Dataset Summary

MasakhaNEWS is the largest publicly available dataset for news topic classification in 16 languages widely spoken in Africa.

The train/validation/test sets are available for all the 16 languages.

Supported Tasks and Leaderboards

[More Information Needed]

  • news topic classification: categorize news articles into new topics e.g business, sport sor politics.

Languages

There are 16 languages available :

  • Amharic (amh)
  • English (eng)
  • French (fra)
  • Hausa (hau)
  • Igbo (ibo)
  • Lingala (lin)
  • Luganda (lug)
  • Oromo (orm)
  • Nigerian Pidgin (pcm)
  • Rundi (run)
  • chShona (sna)
  • Somali (som)
  • Kiswahili (swą)
  • Tigrinya (tir)
  • isiXhosa (xho)
  • Yorùbá (yor)

Dataset Structure

Data Instances

The examples look like this for Yorùbá:

from datasets import load_dataset
data = load_dataset('masakhane/masakhanews', 'yor') 

# Please, specify the language code

# A data point example is below:

{
'label': 0, 
'headline': "'The barriers to entry have gone - go for it now'", 
'text': "j Lalvani, CEO of Vitabiotics and former Dragons' Den star, shares his business advice for our CEO Secrets series.\nProduced, filmed and edited by Dougal Shaw", 
'headline_text': "'The barriers to entry have gone - go for it now' j Lalvani, CEO of Vitabiotics and former Dragons' Den star, shares his business advice for our CEO Secrets series.\nProduced, filmed and edited by Dougal Shaw", 
'url': '/news/business-61880859'
}

Data Fields

  • label: news topic id
  • headline: news title/headline
  • text: news body
  • headline_text: concatenation of headline and news body
  • url: website address

The news topics correspond to this list:

"business", "entertainment", "health", "politics", "religion", "sports", "technology"

Data Splits

For all languages, there are three splits.

The original splits were named train, dev and test and they correspond to the train, validation and test splits.

The splits have the following sizes :

Language train validation test
Amharic 1311 188 376
English 3309 472 948
French 1476 211 422
Hausa 2219 317 637
Igbo 1356 194 390
Lingala 608 87 175
Luganda 771 110 223
Oromo 1015 145 292
Nigerian-Pidgin 1060 152 305
Rundi 1117 159 322
chiShona 1288 185 369
Somali 1021 148 294
Kiswahili 1658 237 476
Tigrinya 947 137 272
isiXhosa 1032 147 297
Yoruba 1433 206 411

Dataset Creation

Curation Rationale

The dataset was introduced to introduce new resources to 20 languages that were under-served for natural language processing.

[More Information Needed]

Source Data

The source of the data is from the news domain, details can be found here ****

Initial Data Collection and Normalization

The articles were word-tokenized, information on the exact pre-processing pipeline is unavailable.

Who are the source language producers?

The source language was produced by journalists and writers employed by the news agency and newspaper mentioned above.

Annotations

Annotation process

Details can be found here **

Who are the annotators?

Annotators were recruited from Masakhane

Personal and Sensitive Information

The data is sourced from newspaper source and only contains mentions of public figures or individuals

Considerations for Using the Data

Social Impact of Dataset

[More Information Needed]

Discussion of Biases

[More Information Needed]

Other Known Limitations

Users should keep in mind that the dataset only contains news text, which might limit the applicability of the developed systems to other domains.

Additional Information

Dataset Curators

Licensing Information

The licensing status of the data is CC 4.0 Non-Commercial

Citation Information

Provide the BibTex-formatted reference for the dataset. For example:

@article{Adelani2023MasakhaNEWS,
  title={MasakhaNEWS: News Topic Classification for African languages},
  author={David Ifeoluwa Adelani and  Marek Masiak and  Israel Abebe Azime and  Jesujoba Oluwadara Alabi and  Atnafu Lambebo Tonja and  Christine Mwase and  Odunayo Ogundepo and  Bonaventure F. P. Dossou and  Akintunde Oladipo and  Doreen Nixdorf and  Chris Chinenye Emezue and  Sana Sabah al-azzawi and  Blessing K. Sibanda and  Davis David and  Lolwethu Ndolela and  Jonathan Mukiibi and  Tunde Oluwaseyi Ajayi and  Tatiana Moteu Ngoli and  Brian Odhiambo and  Abraham Toluwase Owodunni and  Nnaemeka C. Obiefuna and  Shamsuddeen Hassan Muhammad and  Saheed Salahudeen Abdullahi and  Mesay Gemeda Yigezu and  Tajuddeen Gwadabe and  Idris Abdulmumin and  Mahlet Taye Bame and  Oluwabusayo Olufunke Awoyomi and  Iyanuoluwa Shode and  Tolulope Anu Adelani and  Habiba Abdulganiy Kailani and  Abdul-Hakeem Omotayo and  Adetola Adeeko and  Afolabi Abeeb and  Anuoluwapo Aremu and  Olanrewaju Samuel and  Clemencia Siro and  Wangari Kimotho and  Onyekachi Raphael Ogbu and  Chinedu E. Mbonu and  Chiamaka I. Chukwuneke and  Samuel Fanijo and  Jessica Ojo and  Oyinkansola F. Awosan and  Tadesse Kebede Guge and  Sakayo Toadoum Sari and  Pamela Nyatsine and  Freedmore Sidume and  Oreen Yousuf and  Mardiyyah Oduwole and  Ussen Kimanuka and  Kanda Patrick Tshinu and  Thina Diko and  Siyanda Nxakama and   Abdulmejid Tuni Johar and  Sinodos Gebre and  Muhidin Mohamed and  Shafie Abdi Mohamed and  Fuad Mire Hassan and  Moges Ahmed Mehamed and  Evrard Ngabire and  and Pontus Stenetorp},
  journal={ArXiv},
  year={2023},
  volume={}
}

Contributions

Thanks to @dadelani for adding this dataset.

Downloads last month
2,834
Edit dataset card