id
stringlengths
8
14
url
stringlengths
36
42
title
stringlengths
8
90
summary
stringlengths
6
505
text
stringlengths
133
19.2k
news-52932157
https://www.bbc.com/amharic/news-52932157
ጊኒ ቢሳው፡ የገዛ ጄኔራሎቿ አደገኛ እጽ የሚነግዱባት አገር
ባለፈው ጥር ወር በአንድ ጀምበር በተደረገ አሰሳ የተገኘው ነገር አስደንጋጭ ነበር።
ሃያ መርሴዲስ ቤንዝ ቅንጡ መኪኖች፣ በባንክ የተደበቀ 3 ሚሊዮን ዶላር፣ 90 ሺህ ዶላር የሚያወጣ ውስኪና ወይን። ነገር ግን ከሁሉ የሚያስደነግጠው ይህ አይደለም። 1 ነጥብ 8 ቶን የሚመዝን ኮኬንይን መገኘቱ ነው አነጋጋሪ የሆነው። ይህ ፍርድ ቤት ይፋ ያደረገው መረጃ ነው። በጊኒ ቢሳው በኩል ወደ አሜሪካና አውሮፓ የሚሾልከው የአደገኛ እጽ መጠን አስደንጋጭ እየሆነ መጥቷል። ማቆሙም ፈተና ሆኗል። ባለፈው ወር በተደረገው ልዩ ዘመቻ የተያዙት 12 አደገኛ የእጽ አስተላላፊዎች የጊኒ ዜጎች ብቻ አልነበሩም። ፖርቹጋሎች፣ የሜክሲኮና ኮሎምቢያ ሰዎችም ነበሩበት። ይህ በዚያች አገር ያለው የእጽ ዝውውር ምን ያህል ዓለም አቀፋዊ ትስስር እንዳለው አመልካች ሆኗል። ከተከሳሾቹ መካከል ሁለቱ በሌሉበት ተፈርዶባቸዋል። ጊኒ ቢሳው በወንጀለኞቹ ላይ የወሰደችው እርምጃ ተደንቆላታል። ሆኖም የዚያች አገር እንጀራ፣ የዚያች ትንሽ አገር ፖለቲካና ምጣኔ ሀብት ኮኬንይን እንዳይሆን ስጋት አለ። 'ጄኔራሎቹ ኮኬይን ይነግዳሉ' አንቶኒ ማዛቶሊ በጊኒ ቢሳዎ የተባበሩት መነግሥታት ድርጅት የአገሪቱን የጸረ አደገኛ እጽ ዘመቻ ይመራሉ። "ይህ ሰሞኑን ይፋ የተደረገው የአደገኛ እጽ መረብን የመበጣጠስ እርምጃ እንደ መጀመሪያ ስኬት ቀላል ግምት የምንሰጠው አይሆንም። ስምንት ዓመት የፈጀ ጉዳይ ነው። ጊኒ ቢሳውን በቀጣይነት ከአደገኛ እጽ የማስተላለፊያ ወደብነት ነጻ ለማድረግ አንድ እርምጃ ነው" ብለዋል። ጊኒ ቢሳው ለማስተላለፊያነት የተመቸ መለክአ ምድራዊ አቀማመጥ ነው ያላት። ከብራዚል፣ ከኮሎምቢያ፣ ከቬንዝዌላ፣ ከኢኳዶርና ከፔሩ ወደ ስፔን፣ ፈረንሳይ እና ጣሊያን መጠኑ ከፍ ያለ ኮኬይን ለማሸጋገር እንደ ጊኒ የሚመች አገር የለም። ይህቺ የቀድሞው የፖርቱጋል ቅኝ ግዛት ጊኒ ቢሳው በአሜሪካና በተባበሩት መንግሥታትም ጭምር የአደገኛ እጽ ወደብ በሚል ተሰይማ ነበር። "ናርኮስቴት" ይሏታል። መዋቅሩ ሁሉ በአደገኛ እጽ ሰንሰለት የተተበተበ አገር እንደማለት ነው። በአፍሪካ እንዲህ ዓይነት ስም የተሰጣት ብቸኛዋ አገር ጊኒ ቢሳው ናት። የጊኒ ቢሳዎ ደሴቶች የእጽ ማስተላለፊያ አመቺ ቦታዎች ናቸው ይባላል ይህ ስም የዛሬ 10 ዓመት ነበር ለጊኒ ከአሜሪካና ከተባበሩት መንግሥታት ጭምር የተሰጣት። አሁን ግን ነገሮችን ለመቆጣጠርና ስሟን ለማደስ የተጀመሩ ሙከራዎች አሉ። ይህ በእንዲህ እንዳለ በዚያች አገር ባለፈው የካቲት በተደረገ አጨቃጫቂ ምርጫ ኡማሩ ሲሶኮ አሸንፈዋል። የእርሳቸው ወደ ሥልጣን መምጣት አደገኛ እጽ ዝውውር ላይ የተከፈተውን ጦርነት ቀዝቃዛ ውሃ እንዳይቸልስበት ተፈርቷል። ፍርሃቱ ያለ ምክንያት አልመጣም። ምንም እንኳ አዲሱ ፕሬዝዳንት በአደገኛ እጽ የዝውውር ሰንሰለት እጃቸው እንዳለበት የሚያሳይ ተጨባጭ መረጃ ባይኖርም ዋና ዋና የጦር ጄኔራሎች ለእርሳቸው ድጋፍ መስጠታቸው ምናልባት በእጽ ዝውውር የሚታሙት እነዚያው የጦር መሪዎች ንግዱን በአዲስ መልክ እንዳያጧጡፉት ተሰግቷል። በተለይ ባለፈው በመፈንቅለ መንግሥት ሥልጣን ይዘው የነበሩት ኢታማዡር ሹሙ አንቶኒዮ ኢንጃይ ለአዲሱ ፕሬዝዳንት ድጋፍ መስጠታቸው አዲስ ጥርጣሬን ፈጥሯል። ኢታማዡር ሹሙ የእጽ ዝውውሩ ላይ እስከ አንገታቸው ተዘፍቀዋል ተብለው ይታማሉ። ጄኔራል ኢንጃይ ግን ክሱን ያስተባብላሉ። ጊኒና ኮኬይን ጊኒ ቢሳዎ ከፖርቱጋል የቅኝ አገዛዝ ቀንበር ነጸ የወጣቸው በ1970ዎቹ መጀመርያ ነበር። ከዚያ በኋላ 9 መፈንቅለ መንግሥት አስተናግዳለች። ይህም በመሆኑ የዚያች አገር ተቋማት ልፍስፍስ ሆነው ቆይተዋል። የተቋማቱ መልፈስፈስ ደግሞ የእጽ ዝውውሩ እንዲሳለጥ የተመቻቸ ሁኔታን ፈጥሯል። ጊኒ ቢሳዎ የምዕራብ አፍሪካ አገር ናት። የሕዝብ ብዛቷ አንድ ሚሊዮን ተኩል ሲሆን ፖርቹጊዝ እና ክሪዮሎ የሚባል ቋንቋ ተናጋሪዎች ናቸው። አደገኛ እጽ ሲራራ ነጋዴዎች ጊኒን በጣም ይወዷታል፤ ከደቡብ አሜሪካ ተጭኖ ወደ አውሮፓ ለማድረስ ምቹ ወደብ ሆና ትታያቸዋለችና። ከሕዝቧ 70 ከመቶ የሚሆነው የቀን ገቢው ከ2 ዶላር ያነሰ ነው። "በዚያች አገር ተቋማት ባለመገንባታቸው እጽ አስተላላፊዎች ማንኛውንም ባለሥልጣን በሙስና እንዲያባብሉ አግዟቸዋል" ይላሉ የተባበሩት መንግሥታት የአካባቢው ጸረ እጽ ግብረ ኃይል መሪ ማዜቴሊ። "በዚህ ሂደት ጥቂት ጄኔራሎች ይበለጽጋሉ። የሚደማው ግን ሰፊው የአገሬው ሕዝብ ነው።" የቀድሞው የባሕር ኃይል አዛዥ ቡቦ ና ቹቶ በአስተላላፊነት ከተጠረጠሩ ከፍተኛ ባለሥልጣናት አንዱ ናቸው። ሰውየው በርካታ መፈንቅለ መንግሥት ሙከራዎችን ያደረጉ ሲሆን ተሳክቶላቸው ግን አያውቅም። አሜሪካ እኚህን ጄኔራል "የእጽ ጌታ" የሚል ቅጽል ሰጥታቸዋለች። 2013 ላይ በወታደሮቻቸው እገዛ በልዩ ጥበብ ነበር በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ የተደረጉት። የቀድሞው ኢታማዡር ሹሙ ጄኔራል ኢንጃይን 'የኮኬይን መፈንቅለ መንግሥት' በሚባለው ስልጣን ላይ ወጥተው ነበር ጄኔራሉ ወደ አሜሪካ ለሚዘዋወር እጽ ድጋፍ በመስጠት ክስ ተመስርቶባቸው 4 ዓመት እስር ተበይኖባቸዋል። ለመርማሪዎች ተባባሪ ስለነበሩና መልካም ባህሪን ስላሳዩ በሚል የእስር ዘመናቸው አጭር እንዲሆን ተደርጓል። አሁን ወደ ኑሯቸው ተመልሰው ድምጽ አጥፍተው እዚያው ጊኒ ውስጥ ናቸው። ሰውየው የተያዙበት መንገድ ፊልም የሚመስል ነበር። በቁጥጥር ሥር ለማዋል የተፈለገው ኢታማዡር ሹሙ ጄኔራል ኢንጃይን ነበር። ለኚሁ ኢታማዦር ሹም የእጽ ነጋዴዎች ሊያነጋግሯቸው እንደሚፈልጉና ወደ ወደብ በአስቸኳይ እንዲመጡ መልዕክት ይደረግላቸዋል። ኢታማዦር ሹሙ ነገሩ ጥርጣሬ ይፈጥርባቸውና የባሕር ኃይል አዛዡን ይልኳቸዋል። እኚህ አዛዥ ወደ ድንበር ሄደው የተባሉትን የእጽ ነጋዴዎች ሲጠብቁ የአሜሪካ ሰላዮች ያጠመዱላቸው ወጥመድ ውስጥ ይወድቃሉ። በቁጥጥር ሥር የዋሉትም ያን ጊዜ ነበር። የጊኒ 'እስር ቤቶች' ጊኒ ቢሳው 10 እስር ቤቶች አሏት። ነገር ግን እስር ቤቶቿ እጅግ የተጎሳቆሉ ናቸው። ፖሊሶችም አንድ እስረኛ ሊያመልጥ ቢል ለማስቆም የሚያስችል የጥበቃ መሳሪያ እንኳ በበቂ ሁኔታ የሌላቸው ናቸው። ይህን ያሉት የቀድሞው የፍትሕ ሚኒስትር ሩት ሞንቴሪዮ ናቸው። ለምሳሌ መግቢያው ላይ የተጠቀሰው ወንጀል የተጠርጣሪዎቹ ክስ ሊታይ የነበረው በጊኒ ቢሳዎ ዋና ከተማ ቢሳዎ አልነረበረም። በዚያው በተያዙበት ከተማ ቢሶሮ ውስጥ ነበር። ነገር ግን በቢሶሮ ከተማ ተጠርጣሪን ወደ እስር ቤት የሚወስድ መኪና እንኳ ባለመኖሩ ወደ ዋና ከተማው እንዲመጡ ተደረገዋል። "እስር ቤት የለንም፤ እስረኛ ማጓጓዠ የለንም፣ ተቋማት የሉንም፣ እስረኛ ላምልጥ ቢል እንኳ ማስቆም አንችልም። ይህ ሁሉ ተደማምሮ እኛ ለአደገኛ እጽ ማስተላለፊያነት የተመቸን አድርጎናል" ይላሉ የቀድሞው የአገሪቱ የፍትሕ ሚኒስትር ሩት ሞንቴሪዮ። ከዚህም በተጨማሪ በዚያች አገር ከአደገኛ እጽ ዝውውር የሚገኘው ገንዘብ የአልቃይዳ ርዝራዦችን መደጎሚያነት እየዋለ ነው። መስከረም ላይ ከዋና ከተማዋ አቅራቢያ የተያዘው ኮኬይን ለምሳሌ ባለፈው ወር የተየዘ 900 ኪሎ ግራም የሚመዝን የጭነት መኪና የጫነው ዓሳ እንደሆነ ነበር የሚታወቀው። ሆኖም ውስጡ ኮኬይን ተሞልቶ ነበር። የጭነት መኪናው ሊያመራ የነበረው ሰሜን መግረብ በረሃ ለሚነስቀሳቀሱ አሸባሪ ቡድኖች ነበር። በጊኒ የአደገኛ እጽ ገንዘብ የምርጫ ቅስቀሳ ይደረግበታል። ለምሳሌ ብራይማ ሳይድ ባ አደገኛ እጽ አዘዋዋሪ ነው። እስከዛሬም አልተያዘውም። ሁለት ዜግነት አለው። ፖርቱጋላዊና ጊኒያዊ ነው። በጋምቢያ በጊኒና በማሊ እንደሚዘዋወር ይገመታል። ይህ የሚያሳየው ንግዱ የአካባቢውን አገራት እንደሚያዳርስ ነው። ሌላው ተጠርጣሪ ሪካርዶ ነው። ሪካርዶ የኮሎምቢያም የሜክሲኮም ዜግነት አለው። አልተያዘም። ምናልባት በደቡብ አሜሪካ እንደሚዘዋወር ይገመታል። ተጠርጣሪዎቹ ፖለቲካዉን ጭምር ይዘውሩታል። ከእጽ ዝውውር የሚገኘው ገንዘብ መልሶ ለምርጫ ቅስቀሳ ይውላል። ለፓርላማ ምርጫ የየድርሻቸውን ይቀራመቱታል። በዚያው ሌላ በእጽ የናወዘ፣ በእጽ የሚዘወር ሥርዓት ይመሰረታል። ጊኒን "ናርኮስቴት" ያሰኛትም ሌላ ሳይሆን ይኸው ነው"
54581101
https://www.bbc.com/amharic/54581101
በትግራይ እና በፌደራል መንግሥት መካከል ያለውን ፍጥጫ ለመፍታት ምን መደረግ አለበት?
በትግራይ ክልልና በፌደራል መንግሥቱ መካከል ያለው ግነኙነት ከጊዜ ወደጊዜ እየሻከረ መጥቷል።
(ከግራ ወደ ቀኝ) ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና፣ አቶ አሉላ ሃይሉ፣ አቶ አዳነ ታደሰ፣ አቶ ናትናኤል ፈለቀ በሁለቱ አካላት መካከል ያለው አለመግባባትም አንዳቸው ሌላኛቸውን "ሕገ ወጥ" እስከ ማለት ያደረሰ እና የእርስ በእርስ ግንኙነታቸውንም ማቋረጣቸውን በይፋ እስከ መግለጽ አድርሷቸዋል። ባለፈው ዓመት ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው አገራዊ ምርጫ በኮሮናቫይረስ ወረርሽን ምክንያት ሲራዘም፣ የትግራይ ክልል የራሱን ክልላዊ ምርጫ ማካሄዱ ይታወሳል። የፌዴሬሽን ምክር ቤትም ምርጫው ከመከናወኔ በፊት ምርጫው ቢካሄድም ሕገ-ወጥ ነው ሲል ቆይቶ፣ ምርጫው ተደርጎ ውጤቱ ይፋ ከሆነ በኋላ ደግሞ ምርጫው እንዳልተደረገ የሚቆጠርና ተፈጻሚነት የማይኖረው ይሆናል ሲል አስታውቋል። በዚህ ብቻ ሳያበቃም የፌደራል መንግሥት የትግራይ ክልል ሕዝብ የልማትና መሠረታዊ አገልግሎቶች ፍላጎት ላይ በማተኮር የከተማ እና የቀበሌ አስተዳደርን ጨምሮ በክልሉ ከሚገኙ ሕጋዊ ተቋማት ጋር ብቻ ግንኙነት እንዲያደረግ ወስኗል። የትግራይ ክልል በበኩሉ ውሳኔውን ቅቡልነት የሌለው በማለት ምክር ቤቱ ሥልጣኑን ከሕገ መንግሥቱ ውጪ፣ የሕገ መንግሥት ትርጉም በመስጠት ያራዘመ ስለሆነ፤ ሕገ መንግሥታዊ መሠረት የለውም ብሏል። ይህ የሁለቱ አካላት ፍጥጫ እንዴት ይፈታ? የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ሚናስ ምን መሆን አለበት ስንል የተለያዩ ፓርቲ አመራሮችን አነጋግረናል። ውይይት ውይይት ውይይት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና "አደገኛ ወደ ሆነ ፍጥጫ ውስጥ ገብተዋል" በማለት ሁሉም አካላት ከገቡበት አለመግባባት ተመልሰው ወደ ድርድር እንዲገቡ እንደሚጠብቁ ይናገራሉ። የፖለቲካ ልዩነቶች በድርድር መፈታት አለባቸው የሚሉት ፕሮፌሰሩ የትግራይ ክልል መንግሥትን እና የፌደራል መንግሥቱን ፍጥጫ ለመፍታትም "መፍትሔው ድርድር ብቻ ነው" ይላሉ። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ናትናኤል ፈለቀ ሕወሓትና የፌደራል መንግሥቱ የገቡት እሰጥ አገባ "አደጋ ይጋርጣል" ሲሉ ከፕሮፌሰር መረራ ሃሳብ ጋር ይስማማሉ። አክለውም በኢትዮጵያ ውስጥ የለውጥ ሂደቱ ተጀመረ ከተባለበት ጊዜ አንስቶ ሕወሓት በበላይነት ያስተዳድረው ከነበረው የፌደራል መንግሥት መገለሉን፤ በኋላም ላይ ብልጽግና ሲመሰረት ከፌደራል ሚና ወጥቶ ክልሉን ብቻ ወደ ማስተዳደር መቀየሩን አስታውሰው፤ በጊዜ ሂደት ሕወሓት እየወሰዳቸው የመጣቸው ውሳኔዎች ራሱን የሚነጥልና ከአገራዊ የለውጥ ሂደቱ ራሱን የሚያስወጣ ሂደት ተከትሏል ይላሉ። የኢዜማው አቶ ናትናኤል፣ የፌደራል መንግሥቱንና የትግራይ ክልልን የሚያስተዳድሩት አካላት ያላቸው አለመግባባት የትግራይ ክልል ሕዝብ ላይ አደጋ ሊጋርጥ የሚችል ይመስላል በማለት፣ ጉዳዩን "በውይይት ለመፍታት የሚያስችሉ በሮች እየተዘጉ ከዚያ ውጪ ያሉ አማራጮችን ለማየት የሚያስገድዱ ይመስላሉ" ሲል ይገለፁታል። የፌደራል መንግሥቱን ከማንም በላይ ሊያሳስበው የሚገባው ሕግ የማስከበር፣ የዜጎችን ደህንንት የማስከበር ነው በማለትም ጉዳዩ ከዚህ በላይ ሳይባባስ ወደ ውይይት ሁለቱ ወገኖች የሚመጡበትን ሁኔታ የማመቻቸት የበለጠ ኃላፊነት ያለበት መሆኑን ይገልጻሉ። ኢዜማም የፌደራል መንግሥቱ ያንን ማድረግ አለበት ሲል አንደሚያምን የገለፁት አቶ ናትናኤል፤ የሚወሰዱ እርምጃዎች በሙሉ ሕወሓትን ወደ ጠረጴዛ እንዲመጣ የሚጋብዙ አለበለዚያም የሚያስገድዱ መሆን አለባቸው ይላሉ። የፌደራል መንግሥቱ የሚወስዳቸው እርምጃዎች የትግራይን ሕዝብ ደህንነት አደጋ ውስጥ የሚጥል መሆን እንደሌለበትም አቶ ናትናኤል ጨምረው ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) ፕሬዚዳንት አቶ አዳነ ታደሰ በበኩላቸው በአገሪቱ ውስጥ የተለያዩ የፖለቲካ ችግሮች ቢኖሩም አገሪቱ ሕልውና ላይ ተጨባጭ አደጋ ጋርጦ ያለው በሕወሓት እና በብልጽግና፣ በፌደራል መንግሥቱና በትግራይ ክልል መንግሥት መካከል ያለው ፍጥጫ ነው ብለው እንደሚያምኑ ይናገራሉ። ፓርቲያቸው ከባለፈው ዓመት ጥር ወር ጀምሮ ይህንን በመገንዘብ አቋሙን ሲገልጽ እንደነበር በማስታወስም፣ ሁለቱን ወገኖች ለማቀራረብ በሚደረግ ማንኛውም ተሳትፎ ውስጥ የፓርቲያቸው ሚና የሚያስፈልግ ከሆነ ለመሳተፍ ዝግጁ መሆኑንም ማስታወቁን ይገልጻሉ። ከፌደራል መንግሥት ወገን ክልሉን "የመግፋት"፤ ከትግራይ ክልል ወገን ደግሞ "ሆን ተብሎ ችግሮቹን የማስፋት አዝማሚያ" የሚታይ መሆኑንም በመጥቀስ ይህ ለአገር ትልቅ ስጋት መሆኑን ይገልጻሉ። አቶ ታደሰ ሁለቱ አካላት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ተቀራርበው ችግሩን ለመፍታት ጥረት ማድረግ አለባቸው ሲሉ ይገልጻሉ። ኃላፊነት ያለባቸው የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎችም ቢሆኑ የችግሩን አደገኛነት ተረድተው ለመፍታት ጥረት ማድረግ እንዳለባቸው ያስታውሳሉ። 6ኛው ሃገራዊ ምርጫ መራዘሙ ትክክል እንዳልሆነና ትግራይ ክልላዊ ምርጫ በማካሄድ መንግስት ማቋቋም መቻሏ ህጋዊነት እንዳለው የሚገልጸው የሳልሳይ ወያነ ትግራይ (ሳወት) ምክትል ሊቀመንበር አቶ አሉላ ሃይሉ በብልጽግናና ህወሓት መካከል ያለው "አደገኛ አለመግባባት" ግን በአስቸኳይ መፈታት እንዳለበት ያምናል። ፓርቲዎቹ ችግራቸውን በራሳቸው መንገድ መፍታት እንዳለባቸው የሚናገረው አሉላ ይህንን ማድረግ ካልቻሉ ግን በህጋዊ መንገድ መፈታት እንደሚኖርበት የፓርቲያቸው ሳወት አቋም መሆኑን ይገልጻ። የፌደሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ እና የሕወሓት አቋም የፌዴሬሽን ምክር ቤት ከሕገመንግሥት አጣሪ ጉባኤ የቀረበለትን ውሳኔ በመንተራስ አገራዊ ምርጫውንም ሆነ የመንግሥትን ስልጣን ለማራዘም መወሰኑ ይታወሳል። ከዚህ በተጨማሪም ምክር ቤቱ የትግራይ ክልል መንግሥት ያካሄደው ምርጫ ተፈጻሚነት የሌለው፣ የማይጸና እና እንደተደረገ የማይቆጠር በማለት፣ ከክልሉ መንግሥት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት እንደማይኖር በማስታወቅ፣ ከታችኛው መዋቅሮች ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት እንደሚደረግ ወስኗል። ሕውሃትም ተመሳሳይ አቋም አንጸባርቋል። ይህንን በማስመልከትም የኦፌኮው ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ፤ የፌደራል መንግሥቱ እና የትግራይ ክልል መንግሥት አንዳቸው አንዳቸውን በመወንጀልና "ሕገ-ወጥ" በማለት ግንኙነት ማቋረጣቸው ተገቢ አለመሆኑን ይገልጻሉ። የፌደራል መንግሥት ከወረዳና ቀበሌ አስተዳደሮች ጋር ግንኙነቱን አደርጋለሁ ማለቱ በምን መልኩ ተግባራዊ ይሆናል የሚለው ለፕሮፌሰሩ መመለስ ያለበት ነጥብ ነው። በእርሳቸው እምነት በበላይነት ክልሉን የሚያስተዳድረው አካል የታችኛው መዋቅሩንም የማደራጀት ኃላፊነት ያለበት በመሆኑ፣ የፌደራል መንግሥቱ፣ ሕወሓትን አልፎ ከታችኛው መዋቅር ጋር ምን ምን እንደሚሰራ መታወቅ እንዳለበት በማንሳት፣ ወደ ስራ ለመተርጎምም ቀላል ይሆናል የሚል እምነት እንደሌላቸው ገልፀዋል። ሕዝቡን የሚያስተዳድር እንዲሁም ሌሎች ጉዳዮችን የሚያሟላው አካል የተለያዩ መሆናቸው ለአፈጻጸም አስቸጋሪ እንደሚያደርገውም ያነሳሉ። ፕሮፌሰር መረራ አክለውም እነዚህ ሁለት አካላት ዋነኛ የፖለቲካ ችግራቸውን እስካልፈቱ ድረስ በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ አብሮ መጓዝ እንደሚከብዳቸውንም ግምታቸውን ያስቀምጣሉ። የኢዜማ ሕዝብ ግንኙነት የሆኑት አቶ ናትናኤል በበኩላቸው ሕወሓት ቀደም ብሎ ከመስከረም 30 በኋላ መንግሥት የለም የሚል ቅስቀሳ እና ንግግሮች በተደጋጋሚ ሲያደርግ እንደነር በማስታወስ፣ ቅስቀሳውም ሆነ ውሳኔው "አደገኛ ሁኔታ ውስጥ የሚከተን ነው የሚሆነው" ብለዋል። "ይህ አደገኛ ቅስቀሳ እንደ አገር አደገኛ ሁኔታ ውስጥ እንደሚከተን አድርገን ነው ያየነው" የሚሉት የኢዜማው አቶ ናትናኤል የፌዴሩሽን ምክር ቤቱ ከትግራይ የክልል መንግሥት በታች ካሉ መዋቅሮች ጋር ግንኙነት ለማድረግ መወሰኑ አግባብነት ያለው ነው ብለን ነው የምንወስደው ብለዋል። ውሳኔው ግን ምን ያህል ሁለቱን ወገኖች የሚያቀራርብና ወደ ውይይት ያመጣል የሚለው ላይ አሁንም ስጋት እንዳላቸው ከመግለጽ አልተቆጠቡም። ስለዚህ ሕወሓትን ወደ ውይይት ጠረጴዛ ለማምጣት ምን መደረግ አለበት የሚለው በሚገባ መታሰብ እንዳለበት ይገልጻሉ። የኢዴፓው አቶ አዳነ በበኩላቸው ሕወሓት ምርጫ አድርጎ ስልጣኑን ያራዘመበት መንገድ ፍፁም ተገቢ ያልሆነ እና ሕገ-መንግስታዊ ነው ብለው እንደማያምኑ ይናገራሉ። በሌላ በኩል ደግሞ የፌደራል መንግሥቱም ሥልጣኑን ያራዘመበት መንገድም ሕገ ወጥና ሕገ መንግሥታዊ ያልሆነ መሆኑን ይገልጻሉ። ከዚህ አንጻር በፌደሬሽን ምክር ቤት እና በትግራይ ክልል መካከል የሚካሄዱ ሕጋዊ የሚመስሉ ምልልሶች ተገቢ አለመሆናቸውን ይጠቅሳሉ። ከዚህ ይልቅ "ሕጉን ወደ ጎን ትቶ፣ በዚያ ሰበብ ሕዝብ ማደናገሩን ትቶ፣ ፖለቲካዊ መፍትሄ መስጠት" እንደሚያሻቸው ይናገራሉ። ብልጽግናና ሕወሓት በጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብለው ችግሮቻቸውን መፍታት አለባቸው በማለትም፣ "እነርሱ በያዙት የፖለቲካ ጨዋታ አገር ይፈርሳል" በማለት ፖለቲካዊ ውሳኔ ለመስጠት የሚያስችል ድርድርና ውይይት ማድረግ እነደሚያስፈልግ ይገልጻሉ። የተቃዋሚ ፓርቲዎች ሚና የሳወት ሊቀመንበር አቶ አሉላ ሃይሉ እንደሚለው ተቃዋሚ ፓርቲዎች ብልጽግናን እና ህወሓትን በማስታረቅ የሚፈለገውን መግባባት ለመፍጠር የሚያስችላቸው ዕድል ሊኖር አይችልም። "የነበረው የኢህወዴግ ስርዓት በወቅቱ ሲፈጠሩ የነበሩት ተቃዋሚ ፓርቲዎች ደካማ እንዲሆኑ ያደርግ ነበር። አንዳንድ ጠንካራ የሚባሉ ከተፈጠሩም በገዢው ግንባር የሚታፈኑበት ሁኔታ ነው የነበረው። ስለዚህ አሁንም የመሰማት ወይም የመደመጥ ዕድል ያገኛሉ ብዬ አላስብም" በማለት ምክንያቱን ያስቀምጣል። በተጨማሪም በብልጽግናና ህወሐት መካከል "የስልጣን ሽኩቻ" ስላለ ሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎች በመሃል ገብተው መፍትሔ ሊያመጡ እንደማይችሉና ተሰሚነት እንደማይኖራቸው በትግራይ ውጥስ ያለውን የፖለቲካ ሁኔታ በምሳሌነት በመጥቀስ ያስረዳል። ፕሮፌሰር መረራ ፓርቲያቸው ብሔራዊ እርቅ እና ብሔራዊ መግባባት እንደሚያስፈልግ ላለፉት ሁለት ዓመታት ሲናገር መቆየቱን ያስታውሳሉ። ብሔራዊ እርቁና መግባባቱ በማህበረሰብ፣ በፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በመንግሥትና ተቃዋሚዎች መካከል እስካልተፈጠረ ድረስ የኢትዮጵያ እጣ ፈንታ አስቸጋሪ እንደሚሆን ፓርቲያቸው እንደሚያምን ፕሮፌሰሩ ገልፀዋል። አክለውም ለትግራይም ሆነ ለቀሪው ኢትዮጵያ ፍትሃዊ የሆነና በብሔራዊ መግባባት ላይ የተመሰረተ ምርጫ ማካሄድ አስፈላጊ መሆኑን ይናገራሉ። አቶ ናትናኤል በበኩላቸው ፓርቲዎች በጋራ የፈረሙትን የቃል ኪዳን ሰነድ በማስታወስ የፌደራል መንግሥትን እያስተዳደረው ያለው ፓርቲ እና ትግራይ ክልልን እያስተዳደረ ያለው ፓርቲ ይህንን የቃል ኪዳን ሰነድ እንዲያከብሩ ግፊት ማድረግ ከፓርቲዎች እንደሚጠበቅ ይናገራሉ። በቃል ኪዳን ሰነዱ በአሁኑ ሰዓት በሥራ ላይ ያለውን ሕገመንግሥት ማክበር፣ የሚደረጉ አንቅስቃሴዎች በሙሉ የሰላማዊ የሌሎችን ዜጎች መብት ያከበሩ እንዲሆን መስማማታቸውን ይጠቅሳሉ። ኢዜማ ከዚህ አንጻር ይህ እንዲከበር ምክር ቤቱን እንደሚጎተጉት በመጥቀስ፣ በዚህ ጉዳይ ፓርቲዎች በጋራም ሆነ በግል ሁለቱ ወገኖች በውይይት ጉዳያቸውን እንዲፈቱ መጎትጎት እንደሚያስፈልጋቸው ይጠቅሳሉ። የሁለቱ ወገኖች አለመግባባትም ወደ መሬት ወርዶ ተግባራዊ እንዳይሆን ፓርቲዎች ሚናቸውን መጫወት እንዳለባቸው ያሰምሩበታል። አቶ አዳነ የሕወሓትና የብልጽግና ችግር የሁለቱ ፓርቲዎች ብቻ ሆኖ እንደማይቀር በመግለጽ፣ የተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ መንግሥት እርምጃ እንዲወስድ ከመቀስቀስ ይልቅ ወደ ውይይት እንዲመጡ ተሰባስበው ጥረት ማድረግ እንዳለባቸው ይመክራሉ። በፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ውስጥ የሚሳተፉ ከአንድ መቶ በላይ ፓርቲዎች እንዳሉ የሚናገሩት አቶ አዳነ፣ እነዚህ ፓርቲዎች አንድ ልዑክ በማዋቀር የሁለቱ ፓርቲዎች ችግር እንዲፈታ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመር እንዳለባቸው ያስታውሳሉ።
news-53657254
https://www.bbc.com/amharic/news-53657254
“የኑሮ ውድነቱ ማህበራዊና ፖለቲካዊ መፍትሄ ያስፈልገዋል”
ነዋሪነቱ በአዲስ አበባ ከተማ የሆነውና መካከለኛ ገቢ ካለቸው ሰዎች ሊመደብ የሚችለው ግለሰብ በተለይ የኮቪድ-19 ወረረሽኝ ስጋትን ከመጣበት ከወርሃ ሚያዚያ አንስቶ የመሰረታዊ ሸቀጦች ዋጋ መጨመር ህይወቱ ላይ የሚጨበጥ ተፅዕኖ ማምጣቱን ለቢቢሲ ይገልፃል።
የብር የመግዛት አቅም እየቀነሰ ነው "ሃገር ውስጥ የሚመረቱ እንደ ሽንኩርት፣ ጤፍ፣ ቲማቲም የመሳሰሉት ላይ ከፍተኛ የሆነ የዋጋ ጭማሪ ታይቷል፤ ከዚያ ባሻገር ከውጭ የሚገቡ እንደ መዋቢያ ምርቶች፣ አልባሳት የመሳሰሉትም ከፍተኛ ጭማሪ ታይቷል" የሚለው ይሄው ግለሰብ ምናልባትም ከዓለም አቀፍ ወረርሽኙ ጋር በተያያዘ የንግድ እንቅስቃሴዎች መቀዛቀዛቸው፣ እንደ ወትሮውም በቀላሉ መጓጓዝ ባለመቻሉ የአቅርቦት እጥረት ማጋጠሙ ለዋጋ ጭማሪ ምክንያት ሳይሆን እንደማይቀር ግምቱን ሰንዝሯል። "ሽንኩርት በአስራዎቹ ብር ደረጃ ነበር የምንገዛው፥ አሁን ወደ አርባ ብር ደርሷል፤ ቲማቲምም እንደዚሁ ከፍ ብሏል፤ እንደዚሁ ሃያ ስምንት ብር ሃያ ዘጠኝ ብር [ገደማ] እየተሸጠ ነው ያለው በኪሎ" የሚለው ይህ ሰው ከዚህም የተነሳ እርሱና በማኅበራዊ ከባቢው የሚያውቃቸው ሌሎች ሰዎች አጠቃቀማቸውን ለማስተካከል መገደዳቸውን ይናገራል። የፍቼ ከተማ ነዋሪ የሆነችው ዘውዲቱ አሰፋም ከአዲስ አበባው ነዋሪ ጋር ተመሳሳይ ሃሳብ ነው ያላት። የኑሮ ውድነቱ ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ መሆኑን ለቢቢሲ ስትገልጽ፤ "ለምሳሌ ሽንኩርት ከ45 እስከ 50 ብር እየተሸጠ ይገኛል። ሁሉም ነገር ጨምሯል። ጤፍ ከ4300 በላይ እየሆነ ነው። ዘይት ድሮ መንግሥት ያቀርብ ነበር፤ አሁን ግን አያቀርቡም፤ ስለዚህ ከነጋዴ እየገዛን ነው። ዋጋው ጨምሯል። የመንግሥት ሰራተኛ የሆነ፣ ደሞዙ አነስተኛ የሆነ፣ ቤተሰብ ያለው በጣም እየተቸገረ ነው።" ብላለች። የኑሮ ውድነቱ መናር በአኗኗሩ ላይ ያመጣውን ለውጥ የሚገልፀው የአዲስ አበባ ነዋሪ ". . .በምንጠቀማቸው ምግቦች ውስጥ ቲማቲም የምናዘወትር ከሆነ እርሱን እንተዋለን ማለት ነው፤ ሽንኩርትም የምንገዛውን እየቀነስን ሄደናል"፤ ስለዚህ "የምታገኘው ገቢና ለፍጆታዎችህ የምታወጣው ካልተመጣጠነልህ ፍጆታውን ወደ መቀነስ ብሎም ወደ ማቆም ነው የምንሄደው" ብሏል። ይኼው ሰው የኮቪድ-19 ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ ወደ ኢትዮጵያ መግባቱ እርግጥ የሆነበት ሰሞን በርካታ ሰዎች፣ የተለያዩ ምርቶችን በጅምላ ይሸምቱና ያከማቹ እንደነበር አስታውሶ፣ በወቅቱ አጋጣሚውን ለመጠቀም በፈለጉ አንዳንድ ነጋዴዎች የዋጋ ጭማሪ መደረጉን ይጠቅሳል። "እኛ አገር የተለመደው ነገር ደግሞ ዋጋ አንድ ጊዜ ከፍ ካለ በኋላ ተመልሶ የመውረድ ዕድሉ በጣም አናሳ ስለሆነ" በዚያው ከፍ ብሎ ቀርቷል ይላል። የአርባምንጭ ነዋሪ የሆኑ ሌላ ግለሰብ ለቢቢሲ ሲናገሩ ገበያው "እሳት ነው" ይላሉ። ዋጋውን ለማነጻጸር ሩቅ መሄድ አልፈለጉም፤ "በቅርቡ እንኳ ቲማቲም እንገዛ የነበረው 20 ብር ነው አሁን ግን 30 ገብቷል" ካሉ በኋላ ሽንኩርት ደግሞ 30 ብር መግባቱን፣ ድንች በኪሎ 15 ብር፣ ነጭ ሽንኩርት 150 መሆኑን ለቢቢሲ ገልፀዋል። ነጋዴዎችም እንደ ከዚህ ቀደሙ ደፍረው የሚገዙ ደንበኞቻቸው እየቀነሱ መምጣታውን ለቢቢሰ ተናግረዋል። በላሊበላ የሚኖሩት ሌላው ቢቢሲ ያነጋገራቸው ግለሰብ ኑሯቸው የተመሰረተው ከተማዋን ለመገብኘት በሚመጡ ቱሪስቶች ላይ እንደነበር ተናግረው አሁን ግን በኮቪድ-19 ምክንያት ጎብኚ በመጥፋቱ ኑሯቸው ፈተና ውስጥ መውደቁን ለቢቢሲ አልሸሸጉም። ከዚህ ቀደም 30 እና 40 ብር ይገዙት የነበረውን ሽንኩርት አሁን 120 ብር እንደሚሸጥም አስረጅ በመጥቀስ ተናግረዋል። ከቅርብ ወራት ወዲህ በምግብ ምርቶች ላይ ከፍተኛ የዋጋ መጨመር ታይቷል "ጤፍ ከ4000 ብር በላይ ገብቷል" በማለትም ኑሮ ከእለት ወደ እልት እየከበደ መምጣቱን ለቢቢሲ በሃዘን ስሜት ውስጥ ሆነው አስረድተዋል። ኮሮናቫይረስና የዋጋ ንረት የምጣኔ ሃብት ባለሙያው ዶ/ር ጉቱ ቲሶ በአሁኑ ወቅት በመላው ዓለም በኮሮናቫይረስ ምክንያት የሸቀጣሸቀጥ ዋጋ መጨመሩን ይገልፃሉ። ለዚህ ደግሞ ምክንያቱ በኮቪድ-19 እና በተጓዳኝ ችግሮች ምክንያት ምርትና አቅርቦት ላይ መስተጓጎል በመፈጠሩ መሆኑን ያስረዳሉ። ምሁሩ አክለውም ከየካቲት ወር ጀምሮ ይህ መከሰቱን እና እስካሁን መቀጠሉን ይናገራሉ። ዶ/ር ጉቱ በተለይ ደግሞ የአለማቸችን የሸቀጣሸቀጥ እቃዎች ዋነኛ አቅራቢ ቻይና በኮሮናቫይረስ ክፉኛ መጎዳቷ ምርቶችን ማስተጓጎሉንና በዚህም የተነሳ የዋጋ ንረት መከሰቱን ገልፀዋል። "አቅርቦት ሲቀንስ ዋጋ ይጨምራል" የሚሉት ባለሙያው፤ በተፈጠረው የአቅርቦት እጥረት ገበያ ውስጥ ያለውን መቀራመት በመፈጠሩ የምርት ዋጋ መናሩን አብራርተዋል። ሌላኛው ምርቶችን ከውጪ አገራት ገዝቶ ለማምጣት የውጭ ምንዛሬ በማስፈለጉ እና በበቂ ሁናቴ የውጪ ምንዛሬ ማግኘት አለመቻል ለዋጋ ግሽበቱ መናር አንዱ አስተዋጽኦ እንደሆነ ያስረዳሉ። በኮሮናቫይረስ ምክንያት አምራቾች የግብአት እጥረት ስለሚገጥማቸው የዋጋ ንረት ይከሰታል የሚሉት ዶ/ር ጉቱ፣ አምራቾች የማምረት ወጪያቸው ሲጨምር አብሮ የምርት ዋጋ ይጨምራል ይላሉ። አምራቹ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ከትራንስፖርትና ከማምረት ጋር የተገናኘ የግብአት አቅርቦት እየተገታና እጥት እየተፈጠረ በመምጣቱ ለምርት እጥረቱ አስተዋጽኦ ማድረጉን ገልፀዋል። "ግብአት አቅርቦት ቀነሰ ማለት፣ የግብአት ዋጋ ጨመረ ማለት ነው" በማለትም ናገራሉ። የማምረቻ ዋጋ ሲጨምር፣ በተዘዋዋሪ አምራቹ ዋጋውን ወደ ሸማቹ እንደሚያዞር የሚያስረዱት ዶ/ር ጉቱ፤ ዋጋው ወደ ተጠቃሚ ሲዞር ምርቱ ላይ ጭማሪ ያሳያል ሲሉ ይተነትናሉ። ከእነዚህ በተጨማሪ የስርጭት መሰተጓጎል መኖሩን ባለሙያው ጨምረው አስድተዋል። "በአንድ ቦታ የተመረተ ምርት በሚፈለግበት ወቅት ወደ ተለያየ የአገሪቱ ክፍል ማሰራጨት ሲያቅት፣ እጥረት ስለሚፈጠር ለተጨማሪ ወጪ ይዳረጋል፤ የዋጋ ጭማሪ ይከሰታል።" በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የሰላምና መረጋጋት ጥያቄ ትልቅ ፈተና ውስጥ መውደቁን በማስታወስ፣ ይህ ሁሉ በምርት ሰንሰለት፣ በግብዓት አቅርቦት፣ በምርት ስርጭቶች ላይ ትልቅ መስተጓጎል መፍጠሩን ይናገራሉ። በሰላም እና መረጋጋት እጦቱ ፋብሪካዎች ምርታቸውን መቀነሳቸውን፣ ምርት ስርጭት ላይ የተሰማሩም መስተጓጎል ገጥሟቸዋል ሲሉ ይገልጻሉ። መኪናዎች ጭነት ጭነው መንገድ ላይ ከአንድ ቀን በላይ ተስተጓጉለው መቅረት፣ ለተጨማሪ ወጪ እና ኪሳራ ሲዳርጋቸው በተዘዋዋሪ ሸማቹ ላይ የምርቱ ዋጋ ከተገቢው በላይ ዋጋ እንዲጫን እንደሚያደርጉ ጨምረው ያስረዳሉ። እነዚህ ነገሮች በጥቅሉ ሲታዩ የሸቀጣ ሸቀጥ ዋጋ ላይ ብቻ ሳይሆን ሌሎችም አገልግሎቶችና አቅርቦቶች ላይ የዋጋ ንረት እንደሚያሳዩ ዶ/ር ጉቱ ገልፀዋል። የምግብ እህሎች ንረት ለዋና ዋና ከተሞች የምግብ ፍጆታ ምርቶች የሚመጡት በከተሞቹ አቅራብያ ከሚገኙ የክልል ከተሞች መሆኑን በማስታወስ እነዚህ የግብርና ምርቶች ከየትኛውም ጊዜ ይልቅ የዋጋ ንረት ማሳየታቸውን ገልፀዋል። እነዚህ የፍጆታ እቃዎች አሳሳቢ በመባል ደረጃ ዋጋቸው እየጨመረ ነው የሚሉት ምሁሩ፣ ለዋጋ መናር ምክንያቱ ምን እንደሆነ ሲያስረዱም እነዚህ የእለት ፍጆታ ምርቶች ( እንደ ጥራጥሬ ያሉት) ለገበያ የሚቀርቡት ባለፈው አመት የተመረቱ መሆናውን በመጥቀስ ነው። ባለው አመት በተለያየ የአገሪቱ ክፍል አካባቢዎቹ የነበሩበት ሁናቴ የነበረውን ሁኔታም በማስታወስ፣ ለማምረት፣ ለመሰብሰብ፣ ለማሰራጨት አስቸጋሪ በሆነ ሁናቴ ውስጥ ማሳለፋቸውን ይጠቅሳሉ። በዚህ የተነሳ የምርት ማሽቆልቆል ተከስቶ ዘንድሮ ለገበያ ሲደርስ የዋጋ መናር መፈጠሩን ያስረዳሉ። ባለፉት ወራት የተከሰተውንም በተመለከተ ሲያስረዱም፣ ከድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዳሴ ግድያ በኋላም ወደ አዲስ አበባ የሚመጡ ምርቶች ትልቅ መስተጓጎል እንደገጠማቸው ያብራራሉ። በተጨማሪም ነጋዴዎች ባለፈው አመት የገዙት ምርት እንኳ ቢሆን በእንዲህ አይነት ወቅት ዋጋ ከመጠን በላይ ጨምረው እንደሚሸጡ ሸማቾችም በገፍ ገዝው እንደሚያከማቹ ይህም ለዋጋ ንረቱ አስተዋጽኦ እንዳለው ይገልጻሉ። ወደ 80 በመቶ የሚጠጋው አትዮጵያዊ መደበኛ ባልሆነ ስራ ውስጥ ተሰማርቶ፣ ከእጅ ወደአፍ ገቢ እንደሚያገኝ የሚናገሩት ምሁሩ፤ በዚህም ለበርካታው ኢትዮጵያዊ ኑሮን ማክበዱን ይገልፃሉ። ገንዘብ ያለውም ቢሆን የፍጆታ እቃዎች ዋጋ በናረበት ቁጥር ያለውን ገቢው በአጠቃላይ ወደ ሚመገበው ነገር ለማዞር ይገደዳል ይላሉ። ይህም ቁጠባን፣ የወደፊት የማደግ ተስፋውንና ጥረቱን እንደሚያመክን ገልፀው፣ ይህ እንደ ግለሰብ ቢሆንም እንደ አገር ማህበረሳባዊ እድገትንም ፈተና ውስጥ እንደሚጥል ይገልፃሉ። ምን መደረግ አለበት እንደ ዶ/ር ጉቱ ከሆነ ለዋጋ ግሽበቱ መፍትሄ ለመስጠት ችግሩ ከምን መነጨ የሚለውን መለየት አስፈላጊ ነው። አንዳንድ ጊዜ ለምጣኔ ሃብት ችግር የምጣኔ ሃብት መልስ መስጠት ያስቸግራል የሚሉት ምሁሩ፣ የችግሩ መንስኤ ምጣኔ ሃብታዊ ሳይሆን ማህበራዊ አልያም ፖለቲካዊ ሊሆን ይችላል ይላሉ። ከኮሮናቫይረስ ጋር ተያይዞ የተከሰተን የዋጋ ንረት በፍጥነት በሽታውን በቁጥጥር ስር በማዋል፣ ህብረተሰቡ ወጥቶ ሰርቶ መግባት እንዲችል ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ይናገራሉ። ለዚህ ደግሞ የመንግሥት ብቻ ሳይሆን የሁሉም አካላት ተሳትፎ እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል። ይህን በፍጥነት መቆጣጠር ካልተቻለ የምጣኔ ሃብቱን ቀውስ እያባባሰው እንደሚሄድ ይናገራሉ። ሌላው በየዓመቱ ያለው የሰላም መደፍረስ ምክንያቱ ተጠንቶ እውነተኛ፣ አሳታፊ እና ግልጽ የሆነ ውይይት ተደርጎ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ምላሽ ሊሰጠው እንደሚገባ ይመክራሉ። በሶስተኛ ደረጃ እንደ ህዝብ ያሉትን ፖሊካዊ ብሶቶችና ጥያቄዎችን የምንገልፅበት መንገድን ቆም ብሎ መመልከት ተገቢ መሆኑን ይመክራሉ። ሁል ጊዜ የምጣኔ ሃብት ተቋማትን በማውደም፣ ምርትና ምርታማነትን በማስተጓጎል ብቻ ሳይሆን ሌሎች በተዘዋዋሪ ጫና መፍጠር የተፈለገው አካል ላይ ጫና መፍጠር የሚያስችሉ አማራጮችን መመልከትና መፈተሽ ተገቢ መሆኑን ያስታውሳሉ። ካልሆነ ግን አሁን የዋጋ ንረቱ እየሄድንበት ያለው ፍጥነትና መንገድ ከምጣኔ ሃብት አንፃር ሲታሰብ አገሪቷን መጥፎ ደረጃ ላይ እያደረሰ መሆኑን ለቢቢሲ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
41483893
https://www.bbc.com/amharic/41483893
ከሰሞኑ የኢትዮ-ቴሌኮም የተንቀሳቃሽ ስልኮች ምዝገባ ጀርባ
ሰሞኑን ኢትዮ-ቴሌኮም በሃገሪቱ ዉስጥ ያሉ ሁሉም የሞባይል ቀፎዎች እና ሌሎች በሲም ካርድ የሚሰሩ የቴሌኮም መገልገያ መሳሪያዎች እንዲመዘገቡ ባስቀመጠው ቀነ-ገደብ መሰረት ብዙዎች ተመዝግበዋል።ይህንንም ተከትሎ ምዝባው ምንድን ነው? ለምን አስፈለገ? እንዲሁም መንግስት በዜጎች ላይ የሚያደርገውን "የስለላ ስራ ለማጧጧፍ ነው" የሚሉ መረጃዎች ከተለያየ የሕብረተሰቡ ክፍል እየመጣ ነው።
ሰሞኑን ኢትዮ-ቴሌኮም ተንቀሳቃሽ ስልኮችን ለመመዝገብ የወጣው ጥሪ ተንቀሳቃሽ ስልኮች ከተመረቱ በኋላ አምራቾቹ 15 አሃዝ የያዙ ቁጥሮች ለእያንዳንዱ ስልኮች ይሰጣል፤ ይህም አይኤምኢአይ (IMEI) ቁጥር ይባላል። ይህ ቁጥር አንድን ስልክ ከሌላ የሚለይ እንደሆነ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ደኅንነት ባለሙያው አቶ ተክሊት ኃይላይ የሚናገር ሲሆን ቁጥሩም ለአንድ ስልክ ብቻ የሚሰጥ ነው። ምዝገባው አዲስ እንዳልሆነ የሚናገረው አቶ ተክሊት፤ አሁን የተደረገው ምዝገባ በተጨማሪም ተንቀሳቃሽ ስልኮችን መክፈትና መዝጋት ለማስቻል ኮርፖሬሽኑ አዲስ ሶፍትዌርንም አስገብቷል። ለምን መመዝገብ አስፈለገ? የኢትዮ-ቴሌኮም የኮሙዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ አብዱራሂም አህመድ እንደሚሉት የዚህ ምዝገባ ዋና አላማ ተገልጋዩን ደንበኛ ከስርቆት እንዲሁም ደረጃቸውን ያልጠበቁ ስልኮች ከሚያስከትሉት የጤናና የአገልግሎት ጥራት መጓደል ለመከላከል ነው። በሲም ካርድ የሚሰሩ የቴሌኮም መገልገያ መሣሪያዎች በስርቆትም ሆነ በሌላ ምክንያት ከደንበኞች እጅ ሲጠፉ ደንበኞች በሚያቀርቡት ጥያቄ መሠረት ቀፎው የቴሌኮም አገልግሎት እንዳይሰጥ ለማድረግም ይረዳልም ይላሉ። እነዚህንም ተንቀሳቃሽ ስልኮች በጥቁር መዝገብ ላይ የሚያሰፍሩ ሲሆን ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በየትኛውም ሃገር መጠቀም አይቻልም። አቶ አብዱራሂም እንደሚሉት በህጋዊ መንገድ ወደ ሃገር ውስጥ የገቡ እና ኦሪጅናል የቴሌኮም መገልገያ መሣሪያዎች የመኖራቸውን ያህል ቁጥራቸው ጥቂት የማይባል ጥራታቸውንና ደረጃቸውን ያልጠበቁ ተመሳስለው ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ መሣሪያዎች አገልግሎት ላይ እየዋሉ ይገኛሉ፡፡ ይህም ሁኔታ አገር ውስጥ ተንቀሳቃሽ ስልኮችን ገጣጥመው የሚሸጡ ነጋዴዎች ቀረጥ ከፍለው በሚያስገቡት ላይ ኢ-ፍትሐዊ የገበያ ውድድር እየፈጠረ መሆኑን የሚናገሩት አቶ አብዱራሂም፤ ይህ ምዝገባ ይህንን ለማስቀረት ይረዳልም ይላሉ። ከዚህ በተጨማሪ ሃገሪቷ የምታገኘውን ቀረጥ ለማሳደግ፣ በኢትዮ ቴሌኮም የሞባይል ኔትወርክ ውስጥ ያሉ ሁሉንም የሞባይል ተጠቃሚዎችን ባሉበት ለመለየትና በባለቤቱ ወይም በደንበኛው ስም ለመመዝገብ ያስችላል። በአጠቃላይ በሃገሪቷ 58 ሚሊየን ያህል ደንበኞችን ሲስተሙ በቀጥታ እንደመዘገባቸው የሚናገሩት አቶ አብዱራሂም ተጨማሪ ቀፎ እንዲሁም አይ ፓድና ሌሎች ሲም ካርድ የሚወስዱ የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች ሲም ካርድ በማስገባት መመዝገብ ይችላሉ። ይህ የምዝገባ ሂደት ለኢትዮጵያ የተለየ እንዳልሆነ የሚናገሩት አቶ አብዱራሂም በዓለም አቀፍ ደረጃ ዘመናዊ የቴሌኮም አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት ባደጉ ሃገራትና በሌሎች የአፍሪካ ሃገራት ጭምር እየተተገበረ ያለ ዘመናዊ አሰራር ነውም ይላሉ። ከምዝገባው ጀርባ? አቶ ተክሊት በበኩሉ የግለሰቦችን ፕራይቬሲ (ግላዊ ምስጢር) በተመለከተ ምንም አይነት ለውጥ እንደማያመጣ ቢናገሩም ቁጥጥርን በተመለከተ ሥራን እንደሚያቀል ጨምረው ይገልፃሉ። "ሌላ ጊዜ አስመስለው በተሰሩ ስልኮች ያመልጡ የነበሩት አሁን በዚህ አሰራር ማምለጥ አይችሉም" ይላሉ። የ አይኤምኢአይ ቁጥር ግለሰቦች አድራሻቸውን ቢቀይሩ እንኳን በቁጥሩ አማካይነት ትክክለኛ አድራሻቸውን ለማወቅ ያስችላል። "የምትከታተለውን ሰው እንዳያመልጥህ ይረዳሃል።" በማለትም ያስረዳል። አቶ ተክሊት እንደሚለው አንድ ሰው ሲምካርዱን ትቶ ሌሎች አይኤምኢአይ ቁጥራቸው የማይታወቁ ስልኮችን በመያዝ በሌላ ሲም ካርድ መጠቀም ይችል ነበር "ሲምካርድ በመቀየር ያመልጥ የነበረ ሰው አሁን አያመልጥም"ይላል። ጦማሪው በፍቃዱ ኃይሉ መንግሥት ምንም እንኳን ስርቆትን ለመከላከልና አስመስለው የተሰሩ ከጥራት በታች ያሉ ስልኮችን አገር ውስጥ እንዳይገቡ ለመከላከል ነው ቢልም ከዚህ ቀደም ስልካቸው ተጠልፎ እንደ መረጃ የቀረበባቸው እንደ በፍቃዱ ኃይሉ ያሉ ጦማሪዎች "አስጨናቂ ጉዳይ ነው" በማለት ይገልፁታል። የሽብር ድርጊት ፈፅማችኋል በሚል ምክንያት ታስረው ከነበሩት የዞን ዘጠኝ ቡድን አባል የሆነው በፍቃዱ "መንግስት በስልክ በኩል ዜጎቹን ይሰልላል የሚባለው ውሸት አይደለም። " ይላል። ከመታሰራቸው በፊት ለአንድ ዓመት ያህል ያለምንም ፍርድ ቤት ፍቃድ ስልካቸው እንደተጠለፈ የሚናገረው በፍቃዱ እንደ መረጃም የተያያዘው ሰነድ የስልክ ንግግሮቻችን ናቸው ይላል። "እኛ በቁጥጥር ስር የዋልነው ሚያዝያ 2006 ዓ.ም ቢሆንም የቀረበብን መረጃ ከግንቦት 2005 ጀምሮ የተቀዳ ነው።" በማለትም ያስረዳል። ምንም እንኳን በፀረ-ሽብርተኝነት ህጉ የሽብርተኝነት ድርጊትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በሽብርተኝነት የተጠረጠረን ሰው የስልክ፣ የፋክስ፣ የሬድዮና የኢንተርኔት፣ የኤሌክትሮኒክስና የፖስታ ግንኙነቶችን የመሳሰሉትን ለመጥለፍ ወይም ለመከታታል የፍርድ ቤት ፍቃድ እንደሚያስፈልግ በግልፅ ቢያትትም እንደ በፍቃዱ ላሉ በሽብር ለተፈረጁ ግለሰቦችም ህጉ ተፈፃሚ እንዳልሆነም ጨምሮ ይናገራል። ብዙ የሽብር ክሶችን የተከታተለው በፍቃዱ አብዛኞቹ ተቃዋሚ ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች የሚቀርብባቸው መረጃ በስልክ ያደረጉዋቸው ንግግሮች መሆናቸውንም ይጠቅሳል። ከተፈታ በኋላ በነበረው የስልክ ቁጥር መጠቀም ከብዶት የተለያዩ ሲምካርዶችን እየለዋወጠ እንደነበር የሚናገረው በፍቃዱ፤ በድጋሚ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጋር በተያያዘ ከታሰረ በኋላ "ወደ ዱሮው እንደተጠለፈ ወደማውቀው ስልክ ተመልሻለሁ፤ ሲም ካርድ እየቀያየርኩ መሸወድ እችል ነበር። ነገር ግን መንግሥት የማወራውን ሰምቶ ንፁህነቴን ቢረዳልኝ ይሻላል የሚል ነው"በማለትም ይናገራል። ምንም እንኳን በፍቃዱ ወደ ቀድሞ ሲም ካርዱ ቢመለስም ብዙ ታስረው የተፈቱ ተቃዋሚዎችና ጋዜጠኞች ሲም ካርዳቸውን እንደሚቀይሩ በፍቃዱ ይናገራል። "ያለፍርድ ቤት ፍቃድ የስልክ ንግግሮችን የሚሰማ የመንግሥት ፀጥታ ኃይል መኖሩ በራሱ የሚፈጥረው የሚያሸብር ስሜት አለው" ይላል በፍቃዱ። የ አይኤምኢአይ ቁጥር ምዝገባ መምጣት የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች የስለላ መረብን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያጠናክረውም ጨምሮ ይናገራል። "ፕራይቬሲን ከማጣት በተጨማሪ አሁን ደግም አካላዊ ነፃነታችንም ሊገደብ ነው" በማለት ይናገራል። የሶፍትዌር ባለሙያው ሐፍቶም በርኸ ሌላኛው የሶፍትዌር ባለሙያና የየሓ ቴክኖሎጂስ ሥራ አስኪያጅ የሆነው ሓፍቶም በርኸ የቴሌፎን ጠለፋ በተለያዩ ሃገራት በፍርድ ቤት ትእዛዝ ይደረጋል፤ ይህም ህጋዊ ጠለፋ ይባላል ይላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች የጠለፋ ተግባር ይፈፀማል። ይህንንም ተግባር ከግለሰብ ጀምሮ እስከ ተደራጁ ቡድኖች እንዲሁም በመንግሥታት ጭምር እንደሚካሄድም ይናገራል። ከዚህ ቀደም የነበሩ ጠለፋዎች ሂውማን ራይትስ ዎች ከሁለት ዓመት በፊት ባጠናቀረው ሪፖርት ያነጋገራቸው ኢትዮጵያውያን እንደተናገሩ በኬንያ እንዲሁም በአውሮፓ የመኖርያ ፍቃድ አግኝተው ወይም ጥገኝነት ጠይቀው የሚጠባበቁ በርካታ ግለሰቦች ስልካቸውና ኢሜይላቸው በፀጥታ ኃይሎች ተጠልፎ የተናገሩትና የተፃፃፉትን መልሰው ለራሳቸው እንዳሳዩዋቸው ይናገራሉ። ከዚህ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ መንግስትም በተለያዩ ጊዜያት በሽብር የተጠረጠሩ ሰዎች ያደርጓቸዋል የተባሉ የተጠለፉ የስልክ ንግግሮች በመንግስት መገናኛ ብዙሃን ሳይቀር መሰማቱ የሚታወስ ነው። ከቻይናና ከጣልያን የተገኙ የጠለፋ ሶፍትዌር ቴክኖሎጂዎች በተለይ በኢትዮጵያ ያለአግባብ የሰዎችን ግለሰባዊ ሚስጢራዊነትን ለመበርበር ተግባር እንደሚውል ሲንትያ ዎንግ የተባሉ በሂውማን ራይትስ ዋች የኢንተርኔት ከፍተኛ ተመራማሪ ይናገራሉ። ይህ ድርጊት መሰረታዊ የሆኑ ሰብአዊ መብትን የሚጥስ ድርጊት እንደሆነ፤ ሃገራቱም እነዚህ ቴክኖሎጂዎች ለኢትዮጵያ መንግሥት ከመሸጣቸው በፊት ለምን ጥቅም እንደሚዉሉ ማረጋገጥ አለባቸውም ይላሉ ተመራማሪዋ። ምዝገባውን በተመለከተ ብዙዎች መንግሥት ዜጎቹ ላይ ጠለፋ ለማካሄድ እንዲቀለው ነው ሲሉ፤ ሃፍቶምም የሰዉን ጥርጣሬ አያጣጥለውም። የአይኤምኢአይ ቁጥር ምዝገባ ዋናው የመንግሥት ትኩረት ስርቆትን እንዲሁም ኮርፖሬሽኑ የሚያስቀምጣቸውን ጥቅሞች ለመስጠት ቢሆንም ስለላን በተመለከተ ለመንግሥት ቀላል ሥራ እንደሚያደርግለትም ጨምሮ ይጠቅሳል። ይህ አስተያየት ከፍራቻ የመነጨ ነው የሚሉት አብዱራሂም አንድን ሰው ለመከታተል ከአይኤምኢአይ ቁጥር ጋር እንደማይገናኝና ክትትልን በተመለከተ ኤችኤልአር ከሚባል ሶፍትዌር ጋር የተያያዘ አሰራር እንዳለም ይናገራሉ።
news-53080078
https://www.bbc.com/amharic/news-53080078
በጋና ሌቦች ፖሊስ ጣቢያን ዘረፉ
በዛሬዋ ዕለት በጋና መዲና አክራ ዘራፊዎች አንድ የፖሊስ ጣቢያን መስኮት ሰብረው በመግባት ላፕቶፕ፣ ቴሌቪዥንና የፖሊስ መለዮ አልባሳቱን እንደሰረቁ ተገልጿል።
ኒማ በተባለው ፖሊስ ጣቢያ መስኮት ሰብረው በመግባት መዝረፋቸው ተገልጿል። ባለስልጣናቱ ምርመራ ቢጀምሩም እስካሁን በተጠርጣሪነት የያዙት እንደሌለም አሳውቀዋል። ክስተቱ ብዙዎችንም አስደንግጧል፤ መገረምም ፈጥሯል። አንደኛ ሌቦቹ እንዴት ቢደፍሩ ነው ፖሊስ ጣቢያውን ለመዝረፍ የቻሉት የሚለው ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ ፖሊስ ጣቢያ የተመደቡ ጠባቂዎች አለመኖራቸው መነጋገሪያ ሆኗል። ነገር ግን ባለስልጣናቱ ለቢቢሲ እንዳስታወቁት ዘራፊዎች መስኮት ሰብረው በገቡበት ወቅት ፖሊሶች የጦር መሳሪያዎችን እንዲሁም ሌሎች ተጠርጣሪዎች የተያዙበትን ህንፃ እየጠበቁ ነበር ብለዋል። በአሁኑ ወቅትም በዘራፊዎቹ የተሰበረው የፖሊስ መስኮትም እየተጠገነ ነው ተብሏል።
news-57222401
https://www.bbc.com/amharic/news-57222401
'ለኤርትራ ነጻነት 30 ዓመት ተዋደቅን፤ ለ30 ዓመት ዲሞክራሲን ጠበቅን፤ አልመጣም' የቀድሞው የቢቢሲ ትግርኛ አርታኢ
ኤርትራ ነጻነቷን ካገኘች 30 ዓመት ደፈነች። የቀድሞው የቢቢሲ ትግርኛ አርታኢ የነበረው ሳሙኤል ገብረሕይወት ለነጻነቱ ነፍጥ አንግበው ከተዋደቁ ኤትራዊያን አንዱ ነበረ። ስለ ትግሉ እና እንደ ጉም ስለተነነው ኤርትራዊያን የነጻነትና ዲሞክራሲ ተስፋ እንዲሁም አገሪቱ እንዴት በአምባገነን እጅ ስር እንደወደቀች እንዲህ ይተርካሉ።
በርካታ ወጣቶች በኤርትራ የነጻነት ትግል ውስጥ ተሳትፈዋል ለሰላሳ ዓመታት ነፍጥ አንስተን ለነጻነት ተዋጋን፣ እያንዳንዱ ቀንና ሰዓት በጦርነት የሚያልፍ ነበር። ስቃይንና መስዋዕት መሆንን ለመድነው። አብዛኞቻችን ሁለት ወይም ለሦስት ጊዜ ቆስለናል። ይህ ብርቅ አይደለም። እንደነገሩ ታክመን ወደ ሌላ ጦርነት እንዘምት ነበር። በሰሜን ኤርትራ ቃሮራ ግንባርን እንዴት እንደታደግን ይገርመኛል። በደቡብ ኤርትራ ዱሜራን እንዴት እንደተከላከልን ይደንቀኛል። ምሽግ ለምሽግ እየተሳብን፣ እዚያው እያደርን፣ ተራራ እየቧጠጥን፣ ከሸለቆ ሸለቆ እየዘለልን…። ብቻ እኔ ከዕድለኞቹ እመደባለሁ። 65 ሺህ ጓዶቻችን በጦርነቱ ሞተዋል። የነጻነት ግንባሩን የተቀላቀልኩት በፈረንጆች 1982 ላይ ገና በ16 ዓመቴ ነበር። ስለነጻነት ተዋጊ ኤርትራዊያን ብዙ እሰማ ነበር። ቁምጣቸው፣ ረዥም ጸጉራቸው፣ የሚይዙት ኤኬ 47 ጠመንጃ …፣ ይህ ሁሉ ታሪካቸው ያጓጓኝ ነበር። በአራግ ሸለቆ ለጥቂት ወራት ስልጠና ተሰጠኝ። እንዴት ጥቃት መሰንዘር እንደምንችልና እንዴት ማፈግፈግ እንደሚቻል ተማርን። እንዴት ራሳችንን ከአካባቢው ጋር ማመሳሰል እንደምንችል፣ እንዴት መደበቅ እንደምንችል፣ እንዴት ቦምብ ፈቶ መግጠም፣ ነቅሎ መጣል እንደሚቻል፣ አርፒጂ መሣሪያ አጠቃቀምን ሁሉ ሰለጠንን። ስልጠናችን መጥፎ የሚባል አልነበረም። ጎን ለጎን ደግሞ የፖለቲካ ትምህርት እንደወስድ ነበር። ከዚህ መሀል እንዴት ዲሞክራሲያዊ መንግሥት ማቋቋም እንደምንችል ጭምር ተምረናል። ከዚህ ስልጠና በኋላ በበርካታ ጦርነቶች ውስጥ ተሳትፊያለሁ። መደምደሚያው የነበረው በ1990 (እአአ) በምጽዋ ወደብ ላይ የተደረገው 'የፈንቅል ዘመቻ' ነበር። ሳሙኤል ገብረሕይወት ያ ድል እጅግ ወሳኝ ነበር። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትን ከኤርትራ እንዲወጣም ያስገደደ ቁልፍ ወታደራዊ ድል ነበር። ያን ጊዜ ያለማቋረጥ ለ72 ሰዓታት ተዋግተናል። እጅግ ወሳኝ የነበረችውን ምጽዋን ለመያዝ ያልሆነው የለም ማለት ይቻላል። ከዚያ በኋላ ደግሞ ለመከላከል 100 ኪሎ ሜትር ምሽግ ቆፍረን ከአንድ ዓመት በላይ ቆይተናል። በዚህ ውጊያ ጭንቅላቴ ላይ እንዲሁም እጄ ላይ ቆስያለሁ። ከዚያ ሆስፒታል ታክሜ ዳንኩ። ታዲያ ወዲያውኑ ወደ ውጊያ ነበር የተመለስኩት። በ1980ዎቹ መጨረሻ ወደ ኪነትና ባሕል ክፍል ተዛወርኩ። የዚህ ክፍል ዋና ዓላማ ወታደሩን በሙዚቃና ድራማ ሞራሉን ከፍ ማድረግ፣ ማነሳሳት ነበር። በ1991 (እአአ) ከምጽዋ ቅርብ ርቀት በዳሕላክ ደሴት ላይ ነበርን። ዳሕላክ ሳለን ነበር በሕይወታችን እጅግ ጣፋጩን ዜና የሰማነው። ኤርትራ ነጻነቷን እንደተቀዳጀች ተነገረን። የፈንጠዚያ ቀናት በደስታ ሰክረን በጀልባ ወደ ምጽዋ ተጓዝን። እዚያ ስንደርስ ከባድ ተሸከርካሪ ላይ ተጭነን ወደ ዋና ከተማ አሥመራ ጉዞ ጀመርን። ጉዞው ሦስት ሰዓታትን የፈጀ ነበር። የኢትዮጵያ ሠራዊት ደቡባዊ ቀጠናን አለፍነው። ሰው የሚባል አልነበረም። የኢትዮጵያ ወታደሮች ጥለውት ሄደዋል። በአሥመራ ውስጥ ሕልም የሚመስል አውድ ነበር። ነዋሪዎች እኛን የነጻነት ታጋዮችን ለመቀበል ጨርቄን ማቄን ሳይሉ አደባባይ ወጥተው ነበር። በጓይላ ጭፈራ ራሳቸውን ስተው ነበር። ጎዳናው በሙሉ ሕዝብ ፈሶበት አስታውሳለሁ። ይህ በአሥመራ ብቻ ሳይሆን በሌሎች ከተሞችና መንደሮችም የታየ ኩነት ነበር። ይህ ቀን ከመምጣቱ በፊት አሥመራ ሙሉ በሙሉ ጭንቅ ውስጥ ነበረች። አየር ማረፊያው በተከታታይ በተኩስ ሲናጥ ነበር የሰነበተው። ጥብቅ ሰዓት እላፊም ታውጆ ነበር። ልክ በግንቦት 24 (እአአ) ሁሉ ነገር ተለወጠ። እናቶች የጣዱትን ጀበና ትተው፣ የለኮሱትን ሞጎጎ እንጀራ መጋገሪያቸውን ጥለው፣ የቡና ሥነ ሥርዓታቸውን ጣጥለው ግልብጥ ብለው አደባባይ ወጥተው ነበር። ይህም እኛን ታጋዮችን ለመቀበል ነበር። ብዙ ኤርትራውያን የዘንባባ ዝንጣፊ ይዘው ይታዩ ነበር። ወጣቶች እየዘለሉ ታንክ ላይ ይወጡ እንደነበረና የዘንባባ ዝንጣፊ እያውለበለቡ ሲቀበሉንም አስታውሳለሁ። ይህ ፈንጠዝያ ለቀናት ቀጠለ። ምሽቶቹም ደማቅ ነበሩ። በእርግጥ በዚህ ደማቅ ስሜት መሀል ጭንቅም ነበረ። ወላጆች የልጆቻቸውን ፎቶ ይዘው በመውጣት በሕይወት ይኖሩ እንደሁ ይጠይቁ ነበር። ሕዝበ ውሳኔ ከተካሄደ በኋላ እናቶች ደስታቸውን ሲገልጹ "ልጄ ተርፎልኝ ይሆን? ልጄ ሞታ ይሆን?" የሚል የማያባራ ጥያቄ። በኛ ምድብ ገድለና አባየይ የሚባሉ ጓዶች ነበሩ። ሁለቱ ጓዶች ፊት ለፊት በመኪና ላይ ተጭነው ቤተሰባቸውን ባዩ ጊዜ የሆኑት ትዝ ይለኛል፤ ሲጮኹ፣ ሲስቁ፣ የደስታ እንባ ሲያነቡ። የገድለ አባት "ልጄን አገኘሁት! ልጄን አገኘሁት!" እያለ ወደኛ መኪና ሲሮጥ ትዝ ይለኛል። አባየይ ደግሞ ሴት ታጋይ ነበረች። ጋቢና ነበር የተቀመጠችው። የባለቤቷን እናት ስታይ ጊዜ ድንገት እየሄደ ከነበረ መኪና ዘላ ልትወርድና ራሷን ለከፍተኛ አደጋ ልታጋልጥ ስትል ነበር በተአምር የዳነችው። በኋላ ላይ በአዛዦቻችን ፈቃድ ተሰጠን፤ ፈቃዱ ወጥተን ቤተሰባችንን እንድናገኝ ነበር። በጥቂት ሰዓታት ውስጥ ቤተሰብን ማግኘት ቀልድ አልነበረም። ለእነዚያ ሁሉ ዓመታት የተለዩትን ማግኘት እንዲህ የዋዛ አልነበረም። ሆኖም ብዙዎቻችን ዘመድ አላጣንም። በዚያ ቅጽበት ሁላችንም እናስብ የነበረው ከዚህ ሁሉ በኋላ ኤርትራ በልጽጋ፣ ችግር ከኤርትራ ምድር ጠፍቶ እያንዳንዱ ኤርትራዊ በደስታና በፍሰሐ መኖር ይጀምራል የሚል ነበር። ነገር ግን ይህ ተስፋችን እንደ ጉም ሊተን ብዙ ጊዜ አልወሰደበትም። የነበረንን ሁሉ ሰጠን፣ ለነጻነት ስንል። ወጣትነታችንን፣ ሕይወታችንን…። ብዙዎቻችን ከነጻነት በኋላ ከውትድርና ተሰናብተን ቤተሰባችንን ተቀላቅለን፣ ትምህርታችንን ቀጥለን፣ ወደ ግል ሥራና ኑሮ ለመመለስ ነበር ዕቅዳችን። ሆኖም ሠራዊቱን እንኳ ለመልቀቅ እንደማንችል ስናውቅ ተደነቅን። ወታደራዊ አዛዦቻችን የፖለቲካ መሪዎች ሆኑ። አዲሲቷ አገር በእጇ ምንም ቤሳቤስቲ እንደሌላት ነገሩን። ኤርትራ ያላት ብቸኛ ሀብት የያዝናቸው የጦር መሣሪያዎች እንደሆኑ ተነገረን። ከዚያ ሁሉ የጦርነት ፍዳና መከራ በኋላ የቀድሞ ተዋጊዎች ቀበቷችንን ይበልጥ እንድናጠብቅ በድጋሚ አረዱን። ማንኛውንም ሥራ ያለ ክፍያ እንድንምንሰራ ነገሩን። ምግብ ብቻ ይሰጡናል። በነጻ እናገለግላለን። ይህ ሁኔታ ለሁለት ዓመት ቀጠለ። ከዚያ በኋላ ነው ትንሽ ገንዘብ ማግኘት የጀመርነው። በትግሉ ጊዜ ልክ እንደ አንድ ቤተሰብ ይተሳሰቡ የነበሩ ታጋዮች የመሪዎቹን እውነተኛ ባሕሪ ሲረዱ ተከፉ። ብዙዎቹ ወታደራዊ መሪዎች አገሪቱ ልክ ነጻ ከመውጣቷ አስረሽ ምቺው ውስጥ ገብተው ነበር። በርካታ ታላላቅ አመራሮች በየመሸታ ቤቱ ይታዩ ነበር። ራሳቸውን እስኪስቱ ይጠጡም ነበር። በዚህ ወቅት ታጋዩ ኑሮው አለት ሆኖበት ነበር። የዕዝ ሰንሰለቱ እየላላ፣ መደበኛ ስብሰባዎች እየተረሱ መጡ። መደበኛ ታጋዮች ነገሮች ከዛሬ ነገ ይስተካከላሉ ሲሉ ተስፋ አደረጉ፤ ገፋ ብለው ጠበቁ፣ ጠየቁ። አዲስ ነገር አልነበረም። በርካታ ሴቶች በኤርትራ የነጻነት ትግል ውስጥ ተሳትፈዋል ከጎረቤት ጋር አዲስ ጦርነት እንደ አውሮፓውያኑ በ1993፣ የኤርትራ ነጻነት 2ኛ ዓመት ሊከበር ዋዜማ፣ የቀድሞ ተዋጊዎች አመጹ። መሪዎቻቸው ብሶታቸውን እንዲያዳምጡም ተማጸኑ። መሪዎቻቸው ታላቅ ስብሰባ በአሥመራ ስታዲየም እንዲጠሩ አስገደዷቸው። የተሰጠው ምላሽ ግን፣ "ችግራችሁ ይገባናል፣ የተለደመ ችግር ነው፤ ሁሉንም በቅርብ እንፈታዋለን" የሚል ነበር። ልክ ይህ ስብሰባ እንዳበቃ ታዲያ መሪዎቹ የአመጹን አስተባባሪዎች አፍነው ወሰዱ። አንድ በአንድ። በጥቂት ጊዜ ውስጥ ከአንድ ዓመት እስከ 15 ዓመት እንደተፈረደባቸው ሰማን። የታጋዩን ችግር በይፋ በመናገራቸው ትልቅ ዋጋ ከፈሉ። ብዙ "ሰዎች በቃ መሪዎቻችን ወደ አምባገነንነት ሊለወጡ ነው" ማለት ጀመሩ። ሌሎች ግን ትንሽ መታገስና ማየት እንደሚገባ መከሩ። ኤርትራ እያረቀቀችው ያለው ሕገ መንግሥት ሲጠናቀቅ አገራችን ወደ ዲሞክራሲ እንደምታመራ ተነገረን። ይህ ሁሉ ግን መና ቀረ። ኤርትራ በአንድ ፓርቲ የምትመራ፣ ምርጫ አካሄዳ የማታውቅ አገር ሆና ቀረች። በዚህ ሁኔታ ላይ እያለን ኤርትራ ከሁሉም ጎረቤቶቿ ጋር ጦርነት ውስጥ ገባች። ከየመን በ1995፣ ከሱዳን በ1996፣ ከኢትዮጵያ በ1998 እና ከጂቡቲ ጋር በ2008። አዲሷ አገራችን ኤርትራ ሌሎች ተጨማሪ 10ሺህ ወጣቶቿን ሕይወት አስቀጠፈች። አሁን የኤርትራ ወታደሮች ከነጻነት በኋላ በ5ኛው ዙር ጦርነት ውስጥ ይገኛሉ። አሁን የኤርትራ ወታደሮች በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ውስጥ ነው። ከህወሓት ጋር ጦርነት ላይ ናቸው። ህወሓት ኤርትራ ነጻነቷን ባወጀች ጊዜ ሥልጣን ላይ የነበረ ነው። ከ1998 እስከ 2000 ከኢትዮጵያ ጋር በተደረገው ጦርነት ወቅትም የነበረ ነው። ከነጻነት በኋላ በነበረው ጊዜ ከገዢው ፓርቲ የባሕል ክፍል ውስጥ ገባሁ። ለታጋዮች የሚገባቸውን ሞገስ ለማሰጠት ብሎም አገሪቱን ለመገንባት ብዙ ሥራ እሠራለሁ በሚል ነበር። በርካታ ተውኔቶችን፣ ሙዚቃዎችን ደረስኩኝ። ተሳትፌባቸዋለሁም። ተወዳጇ ሔለን መለስ 'ምጽዋ' የሚለውን የኔን ሙዚቃ ተጫወተችው። ሙዚቃው 'ምጽዋ ወድ ልጆችሽ የት ገቡ?' የሚል ነበር። ለውጥ አይቀሬ ነው ትንሽም ቢሆን ጭል ጭል ትል የነበረችው የፖለቲካ ምህዳር ተስፋ የኢትዮጵያ-ኤርትራ ጦርነት ማግስት ከሰመች። መንግሥት ልወረር ነው የሚል ሥነልቦና በሕዝቡ ዘንድ ገዢ ሐሳብ እንዲሆን አደረገ። ይህ ጦርነት በጠረጴዛ ዙርያ ንግግር ብቻ እንዲቀር ማድረግ ይቻል እንደነበር ብዙዎች ያምናሉ። በመስከረም 2001 (እአአ) ደግሞ መንግሥት ያልተጠበቀ እርምጃ እንዲወሰድ አዘዘ። አሥራ አንድ ከፍተኛ ባለሥልጣናት እና መካከለኛ ካድሬዎች ድንገት ዘብጥያ ወረዱ። ለዚህ የተዳረጉት ታዲያ አንዳንድ ማሻሻያዎች እንዲደረጉ ስለጠየቁ ብቻ ነው። ከዚያች ዕለት ጀምሮ ሰዎቹ የት እንዳሉ ምንም አልተሰማም። እነዚህን መሻሻል እንዲደረግ የጠየቁ ባለሥልጣናትን ያናገሩ፣ ስለነሱ የጻፉ 11 ጋዜጠኞችም ታስረዋል። ከነዚህ መሐል ወዳጄና ጓደኛዬ ስዩም ይገኝበታል። ስዩም ያኔ በድል ስንገባ ፎቶ ሲያነሳ የነበረ ልጅ ነው። እነዚህ ሁሉ እስረኞች አንዳቸውም ፍርድ ቤት አልቀረቡም። አንዳቸውም ያሉበት አይታወቅም። ኤርትራ አሁንም የአንድ ፓርቲ አገር ናት። ከነጻነት ወዲህ ለ30 ዓመት ምርጫ የሚባል ነገር አድርጋ አታውቅም። ነጻ ፕሬስ የለም። ነጻ አደረጃጀት የለም። ሁሉም ዓለም አቀፍ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችም ሆኑ የአገር ውስጥ ሲቪክ ድርጅቶች ታግደዋል። ይፋ የሚደረጉ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከነጻነት ወዲህ በአገሪቱ ውስጥ የጤናና የትምህርት አገልግሎት እንደተሻሻሉ ያሳያሉ። ይህን ማመን ግን ከባድ ነው። ካለው ጥቂት የሥራ ዕድል እና አስገዳጅ እንዲሁም ክፍያ አልባ የብሔራዊ ውትድርና አገልግሎት ጋር ተያይዞ በርካታ ወጣቶች አገሪቱን እየለቀቁ ነው። በርካታ ወጣቶች በሌሎች የአፍሪካ አገሮችና በአውሮፓ ተጠልለው ይኖራሉ። ይህ ሁሉ ሆኖ ግን አሁንም ብዙዎቻችን ተስፋ አልቆረጥንም። ለውጥ አይቀሬ እንደሆነ በጽኑ እናምናለን። ኤርትራ አንድ ቀን በሰማዕታት ቃል የተገባላትን የዲሞክራሲ ሕልም ትኖረዋለች።
52854628
https://www.bbc.com/amharic/52854628
"ሚዲያው ዛሬ በአግባቡ ካልተገራ ነገ ከባድ ዋጋ ሊያስከፍለን ይችላል" ዘነበ በየነ (ዶ/ር)
ባለንበት ዘመን ማኅበራዊው የመገናኛ መድረክን ጨምሮ የተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ስፍር ቁጥር የሌለውን መረጃ በየደቂቃው ለታዳሚዎቻቸው ያቀርባሉ።
በዚህ ሂደት ውስጥ ጠቃሚና ሐቀኛ መረጃዎች የመቅረባቸውን ያህል አሳሳችና አደገኛ ወሬዎች ተሰራጭተው አለመግባባትና ጉዳትን ያስከትላሉ። በተለይ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ቁጥራቸው የበዛ የተለያየ አላማ ያላቸው የመገናኛ ብዙሃን ወደ ሕዝቡ እየደረሱ ባሉበት ጊዜ ስጋት የሚፈጥሩባቸው አጋጣሚዎች ጥቂት የሚባል አይደለም። ከዚህ አንጻር የታዘቡትንና መደረግ አለበት የሚሉትን እንዲያካፍሉን ዘነበ በየነን (ዶ/ር) ጋብዘናል። ዘነበ በየነ (ዶ/ር) አሜሪካ በሚገኘው የሚሲሲፒ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት ትምህርት መምህር ናቸው። በአብዛኛው ጥናቶቻቸው መገናኛ ብዙኀን ለሰላምና ለአገር ግንባታ ያላቸውን አስተዋጽኦን ይመለከታል። በቅርቡ ደግሞ፤ 'ሁሉ የሚያወራበት፤ አድማጭ የሌለበት' የሚለው ጥናታቸው በተለይ አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ አለ የሚሉትን ነባራዊ ሁኔታን እንደሚገልጽላቸው ይናገራሉ። መገናኛ ብዙኀን የሚጠበቅባቸውን ከወገንተኝነት በራቀ ሁኔታ ሙያዊ በሆነ መልኩ የሚሰሩ ከሆነ በሕዝብ መካከል መግባባትን ለመፍጠር የመቻላቸውን ያህል በተቃራኒው ከሆኑ ደግሞ አለመግባባትና የሠላም መናጋትን ሊያስከትሉ ይችላሉ። ከዚህ አንጻር ቢቢሲ ለ ዘነበ (ዶክተር) የሕዝብን ሰላም ሊያናጉ የሚችሉ ዘገባዎች የሚሉዋቸው የትኞቹ እንደሆኑና ሕዝቡ ሐሰተኛውን ከሐቀኛ ዘገባ እንዴት ነው መለየት ይችላል? ለሚለው ጥያቄ መልስ በመስጠት ይጀምራሉ፡ ዘነበ (ዶ/ር)፡ ብዙ ነው። ሌላ አካባቢ የተደረጉ ነገሮችን ኢትዮጵያ ውስጥ እንደ ተደረገ አድርጎ ማቅረብ ኃላፊነት የጎደለው ነው። ከሁሉ በላይ ለአንድ ሚድያ ትልቁ ዋጋው እምነት ነው። አንድን ነገር ሲፈጸም አንዳንድ ሚድያዎች "የሆነው ነገር ምንድን ነው፤ መረጃ ከየት ነው የምናገኘው? ያገኘነው እንዴት ነው የምንጠቀምበት?" ብለው ሊያስቡበት ይገባል። የሕብረተሰቡን ንቃተ ህሊና መጨመር ያስፈልጋል። ሕዝቡ፣ ውሸት የሚነዙ ሚድያዎችን እርግፍ አድርጎ የሚተዋቸው፤ ንቃተ ህሊናው ከፍ ያለ እንደሆነ ብቻ ነው። የዛሬ ሦስት ዓመት የተደረጉትን ዛሬ እንደተደረጉ አድርጎ ማቅረብ ከማንም በላይ የሚጎዳው ራሱ ሚድያውን ነው። ለጊዜው ሕዝብን ሊያደናግር ይችላል፤ ከሁሉም በላይ ግን ራሱ ሚድያው ነው ተዓማኒነቱን የሚሸረሸረው። መንግሥት፤ እንደዚህ ዓይነት ኃላፊነት የጎደላቸው የሚድያ አውታሮችን ተጠያቂ ሊያደርግ ይገባል። ያ ሚድያ መንግሥታዊ ሊሆን ይችላል የግል ሊሆን ይችላል። ምንም ለውጥ የለውም። ኃላፊነት የጎደለው ሥራ እስከሰራ ድረስ፣ መጠየቅ የመንግሥት ግዴታ ነው። መንግሥት የሕዝብን ደኅንነት የመጠበቅ ግዴታ አለበት። ቢቢሲ፡ ከዚህ በፊት በነበረው የኢህአዴግ ሥርዓት፡ ሚድያው የመንግሥት አፈቀላጤ ሆነ ተብሎ ሲተች ነበርና፣ አሁን በዚህ ሁለትና ሦስት ዓመታት ውስጥ በሚድያው ላይ ምን ለውጥ ተመለከቱ? ዘነበ (ዶ/ር)፡ ይህ ተደጋግሞ ሲነሳ እሰማለሁ። "መንግሥት ተለውጧል፤ ሚድያውስ ለውጧል ወይ?" የሚል። አንድ ደረጃ ወደ ኋላ መሄድ ያለብን ይመስለኛል። ኢትዮጵያ ውስጥ መንግሥት ተቀይሯል ወይ? ሁላችንም ጥያቄ አለን። ምክንያቱም እርግጥ ነው አስተዳደሩ ተቀይሯል። ከአቶ መለስ ወደ አቶ ኃይለማርያም፤ ከአቶ ኃይለማርያም ወደ ዶክተር ዐብይ የስልጣን ሽግግር ተደርጓል። መዘንጋት የሌለብን ግን ሁሉም ኢህአዴጎች መሆናቸውን ነው። በዶ/ር ዐብይ ጊዜ ብዙ ልናስባቸው የማንችላቸው አንዳንድ ለውጦችን እየተመለከትን ነው። እሱ ላይ ጥርጣሬ የለኝም። 'ከዚያው አንጻር ሚድያው ተቀይሯል ወይ?' የሚለው ጥያቄ ግን ልንመረምረው የሚገባ ጉዳይ ይመስለኛል። ምክንያቱም፣ ጋዜጠኞቹ እነዚያው ናቸው፣ መሰረተ ልማቱ ያው ነው። አስተሳሰቡ [ማይንድ ሴቱ] ያው ነው። ከሁሉም በላይ የፖለቲካ ባህል የምንለው ያው ነው። ጋዜጠኛው የኅብረተሰቡ ውጤት ነው። ኅብረተሰቡ ውስጥ ያለው የፖለቲካ ባህል ተቀይሯል ወይ? ብለን በምናስብበት ሰዓት እንደውም ጥግ የመያዝ ሁኔታ አሁን የባሰ እየጎላ የመጣ ይመስለናል። ምክንያቱም አንዳንድ ሚድያዎች በተለይ ደግሞ ሶሻል ሚድያው ላይ፤ ጥግ ይዞ ድንጋይ መወራወር ላይ ነው ያለው። ያ ድንጋይ የሚወረወረው ግን ሕዝብ ላይ ነው፤ ወገን ላይ ነው። አገር ላይ ነው። አንዳንዴ ሁላችንም ኢትዮጵያውያን መሆናችን የረሳን ይመስለኛል። ምንድነው እያደረገን ያለነው? እየሄድን ያለነው ወዴት ነው? የሚለውን ነገር በአግባቡ ልንመለከተው ይገባል። ቀደም ሲል እንዳልኩት፤ የመንግሥት አስዳደር ለውጥ የፖለቲካ ባህሉና ባህሪው እስካልቀየረው ድረስ ያ በድሮ 'ማይንድ ሴት' ውስጥ ያለው ሚድያ አዲስ ነገር ያመነጫል ብሎ መጠበቅ በጣም ከባድ ነው። ከሁሉ በላይ አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ አስቸጋሪ የሚያደርገው ሁኔታ ሁሉም በየአካባቢው ሶሻል ሚድያ አለው፤ ወይም ደግሞ ጠንካራ የሆነ የራሱ ሚድያ አለው። ስም መጥቀስ አያስፈልግም። ሁላችንም የምናውቃቸው ናቸው። በነገራችን ላይ ሚድያው ዛሬ በአግባቡ ካልተገራ ነገ ዋጋ ያስከፍለናል። ቢቢሲ፡ የመገናኛ ብዙሃን ሁኔታ በዚህ ከቀጠለ ምን ሊያስከትል ይችላል ይላሉ? ዘነበ (ዶ/ር)፡ ምሳሌ ለመጥቀስ ኬንያ በ2007/8 (እኤአ) ከምርጫው በኋላ የተከሰተው ግጭት በአብዛኛው እሳት ያቀጣጥሉ የነበሩት፤ ለግጭቱ ከፍተኛ አስተዋጸኦ ሲያደርጉ የነበሩት የሬድዮ ጣብያዎች ናቸው። ለምሳሌ ሪፍት ቫሊ አካባቢ የነበረው የሬድዮ ጣብያ ትልቁን ሚና ተጫውቷል። አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ነባራዊ ሁኔታም መንግሥት አስፈላጊውን ትኩረት ሰጥቶ ሚድያዎቹን ማስተካከል ካልቻለ ነገ ከፍተኛ ዋጋ ያስከፍሉናል። ስለዚህ "የመንግሥት ለውጥ ተደርጓል፤ ሃሌ ሉያ ስለዚህ የሚድያ ለውጥ ይኖራል፤ ወደ ተስፋይቱ ምድር እየገሰገስን ነው፤ ነገሮች ሁሉ አልጋ በአልጋ ሆነዋል" ብለን የምናስብ ከሆነ ራሳችንን እያታለልን ነው። ከሁሉ በላይ ሶሻል ሚድያው እየፈጠረው ያለው አደጋ ቀላል አይደለም። ሚድያው አንዳንድ ጊዜ የሚሰነዝራቸው ነገሮች ለሶሻል ሚድያ መልስ የመስጠት እስከሚመስል ድረስ ነው። ማይንማር [በርማ] የተፈጠረው ከፍተኛ ዘር ተኮር ጥቃት [ዘር ማጥፋት] በማኅበራዊ ሚድያው ዋና መሪነት የተካሄደ መሆኑን ልናውቅ ይገባል። እኛ አካባቢስ ሚድያዎቻችን ምን እየሰሩ ነው ያሉት ብሎ መመርመር ያስፈልጋል። በሌሎች ሚድያዎች የማየው ነገር ችግሩ እንዳለ ነው። አፈቀላጤ የመሆን፣ ኃላፊዎችን የመፍራት፣ በአንድ አቅጣጫ የመሄድ ነገር ይታያል። ከዚያ በዘለለ የሕዝቡ የልቡ ትርታ ማደመጥና ብዙ ሥራ መስራት የሚጠበቅብን ይመስለኛል። ይህንን ስል በፌዴራል ላይ ያሉትንም በክልል ላይ ያሉትንም ይመለከታል። ቢቢሲ፡ አሁን በተጨባጭ ኢትዮጵያ ውስጥ ካለው ነባራዊ ሁኔታ ካነሱዋቸው ችግሮች ኣንጻር ምን ይደርግ ይላሉ? ዘነበ (ዶ/ር)፡ ሚድያው ውስጥ ያሉት ሰዎች መሆናቸው አንዘንጋ። በተለያዩ ምክንያቶች ስህተት ይሰራሉ። 'ኢትዮጵያ ውስጥ እንዴት ብቁ ጋዜጠኛ መፍጠር እንችላለን?' ብለን ማሰብ አለብን። ሕንድ ለምሳሌ ትልቁ የዲሞክራሲ አገር እየተባለች የምትንቆለጳጰሰው ጥሩ የሚባል ሚድያ ስላላት ነው። ጋና፣ ኬንያና ደቡብ አፍሪካ እነዚህ ሚድያዎች ከሌላ ጋር ሲነጻጸር ውጤታማ የሆነ ዲሞክራሲ እንዲፈጠር የራሳቸው ሚና ተጫውተዋል። ኢትዮጵያም ውስጥ የምንፈልገው ዲሞክራሲና የሰብዓዊ መብት አያየዝ እንዲመጣ ከፈለግን የሚድያው ሁኔታው መለወጥ አለብን። ማብቃት አለብን። መጀመሪያ ነገር ሁልጊዜ በተደጋጋሚ ስልጠናዎች መስጠት ይገባል። ለምሳሌ በእርድ ሥራ ላይ የተሰማራ ሰው ቢላውን አስር ግዜ መሞረድ አለበት፤ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ መስራት ስለሚያቆም። ብዙ ነገሮች ስለሚለዋወጡ ሚድያውም እንደዚያ ነው። ጋዜጠኞች አቅማቸውን የምንገነባ ከሆነ አስፈላጊውን ግብዓት የምናቀርብላቸው ከሆነ የማይቀየሩበት ምክንያት የለም። ይሄ ሁሉ ተደርጎ የማይቀየሩ ካሉ፤ ኬንያ ውስጥ አንድ የሚታወቁበት ነገር አላቸው። 'ኔሚንግ ኤንድ ሼሚንግ' [መጥፎ ድርጊትን ማጋለጥ] ይሉታል። ጋዜጠኞች ሆኑ ፖለቲከኞች ኃላፊነት የጎደለው ሥራ በሚሰሩበት ጊዜ፣ ሕዝብን ከሕዝብ ለማጋጨት በሚሞክሩበት ጊዜ እንዲሸፈኑና እንዲደበቁ አይፈቅዱላቸውም። አሜሪካ በምትመጣበት ጊዜ ሲቪክ ማኅበረሰቦች አሉ፤ ዘረኝነትን የሚሰብክ የሚድያ አውታሮችን 'ኔሚንግ ኤንድ ሼሚንግ' የሚለው ዘዴ እየተከተሉ ይሰራሉ። ኢትዮጵያ ውስጥ እንደዚህ ካልተደረገ በስተቀር፤ የእኔን ፍላጎት ስለአንጸባረቀልኝ ብቻ ይሄኛው ሚድያ ትክክል ነው የምል ከሆነ፤ ልክ አይደለም። ዛሬ ምናልባት ሴቶችን ብቻ ለይቶ የሚያጠቃ ሚድያ ካለ፣ 'እኔ ወንድ ነኝ፤ አይመለከተኝም' ብለን የምናልፈው ከሆነ፤ ነገ እኔጋ ሲመጣ ሊያስቆመው የሚችል ኃይል አይኖርም። ስለዚህ በአንድ ወገናችን ላይ የሚሰራው የሚድያ ጥቃትና ግፍ ሁላችንም ላይ እንደተሰራ አድርገን ልንቆጥረው ይገባል። ስለ እውነትና ስለልጆቻችን ስንል ሚዲያው ዛሬ በአግባቡ ካልተገራ ነገ ከባድ ዋጋ ሊያስከፍለን ይችላል።
news-50484487
https://www.bbc.com/amharic/news-50484487
ከብራና ወደ ኮምፒውተር . . .
ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና ባህል ተቋም (ዩኔስኮ) ያስመዘገበቻቸው የሥነ ጽሑፍ ቅርሶችን ጨምሮ (በ14ኛው ክፍለ ዘመን የተጻፈው አርባዕቱ ወንጌል እና ዳግማዊ አፄ ምኒሊክ ለሞስኮው ንጉሥ ኒኮላር ቄሳር ሁለተኛ የጻፉት ደብዳቤ ይገኙበታል) የበርካታ ጥንታዊ መዛግብት ባለቤት ናት።
በላሊበላ ናኩቶ ለአብ ቤተ ክርስቲያን የሚገኝ ጥንታዊ የጽሑፍ ቅርስ እነዚህ ጽሑፎች የቀደመውን ዘመን ታሪክ ከማንጸባረቅ ባሻገር የማኅበራዊ መስተጋብር፣ የፖለቲካዊ ሥርዓት፣ የህክምና፣ የሥነ ከዋክብት ጥናት እና ሌሎችም መረጃዎችን ይዘዋል። ዲጂታይዜሽን (ጽሑፎችን በካሜራ ቀርጾ በዲጂታል ቅጂ ማስቀመጥ) እነዚህ ጥንታዊ ጽሑፎች ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሻገሩበት ዘመነኛ መንገድ ነው። ያለንበት የቴክኖሎጂ ዘመን ሰዎች እንደቀድሞው ጽሑፍ የሚያገላብጡበት ሳይሆን በኮምፒውተር መረጃ የሚያገኙበት ነው። ይህንን ከግምት በማስገባትም በርካታ አገሮች ጥንታዊ ጽሑፎችን ዲጂታይዝ ማድረግ ከጀመሩ ዓመታት ተቆጥረዋል። በብራና ላይ በግዕዝና በአረብኛ የሠፈሩ ጥንታዊ ጽሑፎችን በዲጂታል ቅጂ የማስቀመጥ ሂደት ውስጥ ከሚሳተፉት አገራዊ ተቋሞች መካከል ብሔራዊ ቤተ መጻሕፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ (ወመዘክር) ይጠቀሳል። ውጪ አገር የሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋሞች እና ተመራማሪዎችም ጥንታዊ መዛግብትን ዲጂታይዝ ማድረግ ጀምረዋል። የሥነ ጽሑፍ ቅርሶች ሰው ሰራሽ ወይም ተፈጥሯዊ አደጋ ቢደርስባቸው፤ ቅጂያቸውን ለማትረፍ በካሜራ ይቀረጻሉ። ቅርሶቹ ባሉበት ቦታና ይዞታ ተጠብቀው፤ ቅጂያቸው ለተመራማሪዎች እንዲሁም መረጃውን ለሚፈልጉ ግለሰቦች በአጠቃላይ ተደራሽ እንዲሆንም ዲጂታይዜሽን ሁነኛ አማራጭ ነው። • ወመዘክር፡ ከንጉሡ ዘመን እስከዛሬ • የሎሬት ጸጋዬ ገ/መድህን የባህል ጥናት እና ምርምር ማዕከል ተመረቀ በርካታ ጥንታዊ የሥነ ጽሑፍ ቅርሶች ያሏት ኢትዮጵያ ምን ያህሉን መዛግብት ዲጂታይዝ ማድረግ ችላለች? በባለሙያዎች ከሚነሱ ጥያቄዎች አንዱ ነው። ዘመኑ ከደረሰበት ቴክኖሎጂ አንጻር የጽሑፎቹን ዲጂታል ቅጂ ለተጠቃሚዎች ማድረስ ተችሏል ወይ? ሌላው ጥያቄ ነው። የዘርፉ ባለሙያዎች በዋነኛነት ከሚያነሷቸው ተግዳሮቶች መካከል በቴክኖሎጂ ብቁ አለመሆንና የባለሙያ እጥረት ይገኙበታል። በቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን የቅርስና የታሪክ ከፍተኛ ባለሙያ እንዲሁም የፊሎሎጂ ሦስተኛ ዲግሪ ተማሪ እስራኤል አራጌ በበኩላቸው የቅርሶቹ ባለቤቶች ዲጂታይዜሽንን እንደማይደግፉ ያስረዳሉ። የቅርሶቹ ባለቤት ከሆኑት አንዷ የሆነችው ቤተ ክርስቲያን፤ የሥነ ጽሑፍ ሀብቶቹ ይሰረቃሉ በሚል ስጋት ዲጂታይዜሽንን እንደማታበረታታ ይናገራሉ። "በተለይም የውጪ አገር ምሁራን ዲጂታይዝ ለማድርግ ሲመጡ፤ ቅርሶቹ ተዘረፉ ስለሚባል በቤተ ክርስቲያን ዘንድ የዲጂታይዜሽን ጥቅም አይታይም። ቤተ ክርስቲያኗ እንኳን ለውጪ ተመራማሪዎች ለቅርስ ጥናትና ጥበቃ ሠራተኞችም በሯን መዝጋት ጀምራለች።" ጥንታዊ ጽሑፎችን ለመቁጠር፣ ያሉበትን ሁኔታ ለማጥናትና ለቱሪስቶች ክፍት የሚሆኑበትን መንገድ ለማመቻቸት ሲሞከርም፤ ቤተ ክህነት እንዲሁም የቤተ ክርስቲያኖች አስተዳዳሪዎችም ፈቃደኛ እንደማይሆኑ ያስረዳሉ። በእርግጥ ቅርሶች ይሰረቃሉ የሚለው ስጋት መሠረት አልባ አይደለም። ባለፉት ዓመታት በርካታ የሥነ ጽሑፍ ቅርሶች ተዘርፈው ከኢትዮጵያ ወጥተዋል። በተለይም ከ17ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ብዙ የብራና መጻሕፍት በተለያየ መንገድ በውጪ አገር ሰዎች መወሰዳቸው ይታወቃል። የቅርስና ታሪክ ባለሙያው እስራኤል፤ ከ18ኛው ክፍለ ዘመን ወዲህ የተወሰዱ ብርቅዬና በሌላ አገር የማይገኙ ቅርሶችን እንደምሳሌ ይጠቅሳሉ። "እንደምሳሌ መጽሐፈ ሔኖክ፣ መጽሐፈ ኩፋሌ፣ ገድለ አዳም ወ ሔዋን ይጠቀሳሉ። በሐረርና በደቡብ ወሎ የነበሩ የእስልምና መዛግብትም ተዘርፈዋል። አሁንም በቱሪስቶች፣ በዲፕሎማሲ ሠራተኞችና በሌሎችም ሰዎች የብራና መጻሕፍት እየተሰረቁ እየወጡ ነው።" • በታሪካዊው ቤተ መንግሥት ውስጥ ምን አለ? • ለኢትዮጵያዊያን የንባብ ወዳጆች ምርጡ መጽሐፍ የትኛው ነው? ሆኖም ግን መፍትሔው ስርቆትን መከላከል እንጂ ዲጂታይዜሽንን መግታት አለመሆኑን ባለሙያዎች ይስማሙበታል። የቅርስና ታሪክ ባለሙያው እንደሚሉት፤ በዋነኛነት በሰሜን ኢትዮጵያ ብዙ መጻሕፍት ዲጂታይዝ ቢደረጉም አጥጋቢ ነው ማለት አይቻልም። በተለይም ባለፉት ጥቂት ዓመታት በአገሪቱ የተስተዋለው አለመጋጋት የፈጠረው ስጋት ሥራው ላይ እንቅፋት መፍጠሩን ያክላሉ። "ከዘመኑ ሥልጣኔ አንጻር ዲጂታይዜሽን አማራጭ የሌለው ዘዴ ነው። የብራና ጽሑፎችን ገልብጦ ማስቀመጥ ጊዜ ይወስዳል፤ በብራና የሚጽፉ ኢትዮጵያዊያን ቁጥርም እየተመናመነ ነው" ሲሉ ያስረዳሉ። በአክሱም አባ ጴንጤሌዎን ገዳም የሚገኝ ጥንታዊ የጽሑፍ ቅርስ በኢትዮጵያ፤ ዲጂታይዜሽን በ1963 ዓ. ም ገደማ መጀመሩን ሰነዶች ያሳያሉ። በወቅቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የነበሩት ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ቲዎፍሎስ፤ ሜኖሶታ ከሚገኝ የቅዱስ ዩሐንስ ዩኒቨርስቲ፣ የሂል ገዳም የብራና ቤተ መጻሕፍት ጋር በመተባበር የኢትዮጵያ ጥንታዊ የብራና መጻሕፍት በፎቶ ተቀርጸው እንዲቀመጡ ማድረጋቸውን ባለሙያው እስራኤል ይናገራሉ። ይህ እንቅስቃሴ በ1980ዎቹ በአገሪቱ በነበረው አለመረጋጋት ሳቢያ በጊዜያዊነት ተቋርጦ ነበር። ባለሙያው ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በዲጂታይዜሽን ከሚጠቅሷቸው የውጪ ተቋሞች መካከል፤ የኢትዮጵያ ብራና ማይክሮፊልም ቤተ መጻሕፍት (ኢትዮጵያን ማኑስክሪፕት ማይክሮፊልም ላይብረሪ ወይም ኢኤምኤምኤል) ይገኝበታል። በተቋሙ ወደ 9238 የብራና መጻሕፍት በማይክሮፊልም መቀረጻቸውን ይናገራሉ። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፣ በኢትዮጵያ ጥናትና ተቋም (ኢንስቲትዮት ኦፍ ኢትዮጵያን ስተዲስ ወይም አይኢኤስ) ከተሠራው የፕ/ር ታደሰ ታምራት እና ሥርግው ሀብለሥላሴን እንቅስቃሴ፤ ውጪ አገር መቀመጫቸውን ካደረጉ መካከል ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌን ይጠቀሳሉ። የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና ባህል ተቋም (ዩኔስኮ) በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የብራና መጻሕፍትን ዲጂታይዝ ያደርጋል። የሙዝየም ባለሙያ እና በአሁን ወቅት በአረብኛና ግዕዝ ጽሑፎች ላይ ጥናት እያደረጉ ያሉት ፕሮፌሰር አህመድ ዘካሪያ እንደሚሉት፤ በአገር ውስጥም ይሁን በውጪ አገር ዲጂታይዝ የሚደረጉ የሥነ ጽሑፍ ቅርሶች ተደራጅተው ለተጠቃሚዎች የሚቀርቡበት ወጥ አሠራር ያስፈልጋል። "ለሥራው ያለው ተነሳሽነት ጥሩ ቢሆንም ማቀናጀቱ ላይ ክፍተት አለ። አጠቃቀሙ ሕግና ሥርዓት ይፈልጋል" ይላሉ። ኢትዮጵያ ከድንጋይ ጽሑፎችና ከዋሻ ሥዕሎች አንስቶ በብራና ላይ የሰፈሩ የሥነ ጽሑፍ ሀብቶች ባለቤት እንደመሆኗ፤ በተለያየ ዘመን የነበሩ የሥነ ጽሑፍ ሀብቶችን ዲጂታይዝ አድርጎ ጥቅም ላይ ማዋል ያስፈልጋል። ፕሮፌሰር አህመድ፤ በግዕዝም በአረብኛም በየቦታው የሚገኙ ጽሑፎችን በመሰብሰብ ረገድ የፊሎሎጂ ትምህርት ክፍል ተማሪዎች እያደረጉ የሚገኙትን ጥረት ያደንቃሉ። • የኢትዮጵያ ፊልም ወዲያና ወዲህ • በኦሮምኛና በትግርኛ አፋቸውን የፈቱ የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ባለውለታዎች ሀምቡርግ ዩኒቨርስቲ፤ በአፍሪካ ቀንድ የእስልምና ጽሑፍን የማሰባሰብ ንቅናቄውንም ይጠቅሳሉ። ጥንታዊ ጽሑፎች በተጠቀሱት የአገር ውስጥና የውጪ አካሎች ዲጂታይዝ መደረጋቸው ቢበረታታም፤ ወደ አንድ ማዕከል መምጣት እንዳለባቸው ያስረግጣሉ። ጥቅም ላይ የሚውሉበትን መንገድ የሚመራ ሥርዓት ከተዘጋጀ፤ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ተደራሽ እንደሚሆኑም ያክላሉ። "ተመራማሪዎች እንዴት እንደሚጠቀሙበት ደንብ መውጣት አለበት፤ አቀራረቡም ሕጋዊ አካሄድ ያስፈልገዋል።" ጥንታዊ ታሪክን፣ ማኅበራዊ ኑሮን፣ ምጣኔ ሀብትን፣ ፖለቲካን፣ ሀይማኖትን ወዘተ. . . የሚያሳዩትን መዛግብት በመተንተን የዛሬው ትውልድ ጥቅም ላይ እንዲያውለው የሚያደርግ የተማረ የሰው ኃይል እንደሚያስፈልግም ፕ/ር አህመድ አያይዘው ያነሳሉ። "ከሌሎች የአፍሪካ አገራት አንጻር ብዙ የሥነ ጽሑፍ ሀብት አለን። ሚስጥሮቻችን ብዙ ናቸው። የቀደመውን ዘመን እውቀት ማብላላት፣ ወደ ዛሬው ተጨባጭ ሁኔታ መለወጥም ያስፈልጋል። እኒህ የትላንት እውቀቶች ለአገርም፣ ለዓለምም ይበጃሉ" ይላሉ። ጥንታዊ ጽሑፎችን ዲጂታይዝ የማድረግ እንቅስቃሴ በአንድ አካል መመራት እንዳለበት የሚያስረዱት ደግሞ በብሔራዊ ቤተ መጻሕፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ (ወመዘክር) የመረጃ ሀብቶች አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሙሉእመቤት ጌታቸው ናቸው። "በአገር ውስጥም በውጪም እንቅስቃሴ አለ። ሁሉም በየራሱ ዘርፍ መሮጡ ግን ውጤታማ አያደርግም። ሁሉም በየራሱ መንገድ ሲሄድ ክፍተት ይፈጠራል። ሀብቶቹ ሊጠፉም ይችላሉ። ስለዚህም የሚመለከታቸው አካላት በቅንጅት መሥራት አለባቸው።" ወመዘክር በአዋጅ የተሰጠውን ሥልጣን ተጠቅሞ ጥንታዊ የሥነ ጽሑፍ ቅርሶችን ዲጂታይዝ ያደርጋል፤ የመዛግብቱን ቅጂ አከማችቶም በቤተ መጻሕፍቱ ለተጠቃሚዎች ያቀርባል። መዛግብቱ በድረ ገጽ ተለቀው ማንኛውም ሰው ባለበት ሆኖ መጠቀም እንዲችል ፖሊሲ ቢረቀቅም ገና አልጸደቀም። ዳይሬክተሯ እንደሚሉት፤ ሰዎች ያለውን ክምችት እንዲያውቁ እንዲሁም በሚፈልጓቸው ወቅትም እንዲጠቀሙ የሕግ ማዕቀፍ ያስፈልጋል። "ሙሉ መረጃው በድረ ገጽ የሚለቀቅ፣ የማይለቀቅም ሊኖር ይችላል። ሰው የትኛውን መረጃ፣ እንዴት ይጠቀምበት? በነጻ ይሁን ወይስ በክፍያ? የሚለውም በፖሊሲ የሚወሰን ይሆናል" ሲሉ ያስረዳሉ። ወመዘክር የትኛው የሥነ ጽሑፍ ቅርስ የት ይገኛል፤ የሚለውን በዳሰሳ ጥናት ይለያል። በጥቆማ የሚያገኛቸው መዛግብትም አሉ። ቅርሶቹ እንዴት ተጠብቀው መያዝ እንዳለባቸው ለባለቤቶቹ ሥልጠና ከመስጠት ባሻገር ዲጂታል ቅጂም ይወስዳል። የዲጂታይዜሽን ጅምሩ ቢኖርም ሂደቱ አመርቂ አለመሆኑን ሙሉእመቤት ያስረዳሉ። የባለሙያ እጥረትና የቴክኖሎጂ ውስንነትም በሚፈልጉት መጠን እንዳይሄዱ እንቅፋት ሆነዋል። መዛግብቱ የት እንዳሉ ለማወቅና ለመሰነድ የሚደረገው ጥረት የተጓተተ መሆኑንም ዳይሬክተሯ ያክላሉ። "ወመዘክር እየሞከረ ነው እንጂ እየሠራ ነው ለማለት ያስቸግራል። እየሠራን ነው ለማለት የሚፈለገውን ያህል እየሠራን አይደለም፤ የምንሰበስባቸው መዛግብት ቢኖሩም በቂ አይደሉም።" • የታሪክ መማሪያ መጻሕፍት ለምን ይከለሳሉ? • ፍቅርና ጋብቻ በቀይ ሽብር ዘመን የሥነ ጽሑፍ ቅርሶችን እንዲሰበስቡ በአዋጅ ቢፈቀድላቸውም የመዛግብቱ ባለቤቶች ቅርሱ ዲጂታይዝ እንዲደረግ ፈቃደኛ የማይሆኑበት አጋጣሚ አለ። "ለምሳሌ በቤተ ክህነት ማንም ሰው ዲጂታይዝ እንዳያደርግ መመሪያ ወጥቷል። ከመዛግብቱ ባለቤቶች ጋር ስምምነት ላይ ለመድረስ እየሞከርን ነው። የእስልምና የሥነ ጽሑፍ ቅርሶችና ሌሎችም መዛግብትን ከባሌቤቶቹ ጋር በመነጋገር መሰብሰቡን ግን ቀጥለናል።" ጥንታዊ የኢትዮጵያ መዛግብት ዲጂታይዝ የሚደረጉት አገር ውስጥ ብቻ አይደለም። ከኢትዮጵያ ውጪ ከሚገኙ ተቋሞች የእንግሊዙ ብሪትሽ ላይብረሪ ተጠቃሽ ነው። በቤተ መጻሕፍቱ የእስያና አፍሪካ ስብስብ ክፍል ውስጥ በ 'ኢትዮፒክ ኮሌክሽንስ ኢንጌጅመንት ሰፖርት' የሚሠራው እዮብ ድሪሎ እንደሚናገረው፤ በመላው ዓለም አደጋ ያንዣበበባቸው መዛግብት የሚሰነዱበት 'ኢንዴንጀርድ አርካይቭስ ፕሮግራም' የተሰኘ ክፍል አለ። ይህም ቸል የተባሉ፣ የመጥፋት አደጋ የተጋረጠባቸው ጥንታዊ የጽሑፍ ቅርሶች የሚሰነዱበት ክፍል ሲሆን፤ በየዓመቱ ጥንታዊ መዛግብትን ለይተው ዲጂታይዝ ለሚያደርጉ ተመራማሪዎች የገንዘብ ድጋፍ ያደርጋል። በዓለም በ90 አገሮች፣ ከ100 በላይ በሚሆኑ ቋንቋዎች፣ ከ400 በላይ ፕሮጀክቶች የነበሯቸው ሲሆን፤ ከ 1000 በላይ የኢትዮጵያ ጥንታዊ መዛግብት ዲጂታይዝ ተደርገዋል። ከነዚህ መካከል ከገዳማት የተገኙ መዛግብት ይጠቀሳሉ። በቤተ መጻሕፍቱ የሚገኙ ጥንታዊ መዛግብት ለሕዝብ እይታ ከመቅረባቸው ባሻገር፤ የ25 መዛግብት ዲጂታል ቅጂም በድረ ገጽ ይገኛል። ባለፈው ዓመት የዘመናት ውጤት የሆኑ ጽሑፎች ዓውደ ርዕይ ተካሂዶም ነበር። "ዘመናትን ያስቆጠሩ የእውቀትና የጥበብ ሥራዎችን አሳይተናል። 'አፍሪካን ስክራይብስ፡ ማኑስክሪፕት ካልቸር ኦፍ ኢትዮጵያ' በሚል የተዘጋጀው ዓውደ ርዕይ ዋነኛ አላማው ላልታወቁ ኢትዮጵያዊያን ጸሐፍትና ጥበበኞች ቦታ መስጠት ነበር" ሲል እዮብ ይገልጻል። በቤተ መጻሕፍቱ ከሚገኙ ስብስቦች መካከል የመቅደላ መዛግብን የመሰሉትን በመጥቀስም "የኢትዮጵያዊያን ጸሐፍት የእውቀትና ጥበባዊ ተሰጥኦ መገለጫ ናቸው" ሲል ያስረዳል። ቤተ መጻሕፍቱ በዚህ ዓመት፤ ወደ 100 የሚደርሱ ጥንታዊ መዛግብትን ለወመዘክር መስጠቱን በመጥቀስ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ተቋሞች ጋር ለመተባበር ዝግጁ መሆናቸውንም ያክላል።
news-47786938
https://www.bbc.com/amharic/news-47786938
የፈረሰው የደጃዝማች ዐምዴ አበራ ቤት ጠባቂ ምን ይላል?
መጋቢት 17/2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ የካ ክፍለ ከተማ በቅርስነት ተመዝግቦ የነበረው የደጃዝማች ዐምዴ አበራ መኖሪያ ቤት ከቤቶች ኮርፖሬሽን ታዘን ነው በሚሉ ሰዎች መፍረሱን የአገር ውስጥ መገናኛ ብዙሐን ዘግበዋል። ድርጊቱ በቤቶች ኮርፖሬሽን፣ በቅርስ ጥበቃ፣ በክፍለ ከተማ እንዲሁም በባህል፣ ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ መካከል ውዝግብ የፈጠረ ነው።
• በአዲስ አበባ ከተማ ሊታዩ የሚገባቸው 5 ታሪካዊ ቤቶች • ባሕልና ተፈጥሮን ያጣመረው ዞማ ቤተ መዘክር መረጃዎች እንደሚያሳዩት የደጃዝማች ዐምዴ አበራ መኖሪያ ቤት በ1967 ዓ.ም በደርግ ከተወረሰ በኋላ በኪራይ ቤቶች አስተዳደር ስር ሆኖ ግለሰቦች በኪራይ ኖረውበታል። ከ1977 ዓ.ም ጀምሮ ሕይወታቸው እስካለፈበት 2002 ዓ.ም ድረስ ከቤተሰቦቻቸው ጋር የኖሩበት ጁሴፔ የተባሉ ጣሊያናዊ ናቸው። ኃይለእየሱስ በክሩ በአጋጣሚ ትውውቅ ከጣሊያናዊው ጋር አንደ አንድ የቤተሰብ አካል ሆኖ ይኖር ነበር። ትውውቁ የጀመረው ጣሊያናዊው ከባለቤቱ ጋር በፍች ተለያይተው ስለነበር በዚሁ ቤት ውስጥ በወር 300 ብር ለኪራይ ቤቶች እየከፈሉ ሁለት ልጆቻቸውን በሞግዚት ያሳድጉ ነበር። የእርሳቸው ልጅ ኤርኔስቶ ኮዜንቲኖ ከኃይለእየሱስ ጋር የአንድ ሠፈር ልጅ በመሆኑ አብረው ኳስ ይጫወታሉ። እርሳቸውም ቢሆን በአካባቢው የእግር ጉዞ ማድረግን ያዘወትሩ ነበር። • የአፄ ቴዎድሮስ ቁንዳላ ሊመለስ ነው በዚህ መካከል ጣሊያናዊው ቤቱን በሚጠብቁላቸው ግለሰቦች እንደተማረሩ የልባቸውን ያጫውቱታል። ለጨዋታ ብቻም ሳይሆን ጭንቀታቸውን እንዲጋራ አስበው ነበርና ከእርሳቸው ጋር እየኖረ ቤቱን እንዲጠብቅ ይጠይቁታል። ኃይለእየሱስ ጥያቄያቸው አይኑን ሳያሽ ተቀበለ። በአባትና ልጅ ግንኙነት ሥራውን ጀመረ -ኃይለየሱስ። በዚህ መካከል "እንደ ልጃቸው አሳድገውኛል" የሚላቸው ጣሊያናዊ በልብ ሕመም ምክንያት በድንገት በሞት ተለዩ። "የጁሴፔ ባለቤት ወደ አገር ውስጥ መጥታ ንብረቶቹን ወሰደች፤ ቤቱን እንድጠብቅና እንድንከባከብ የኪራይ ቤቶች አስተዳደር ቁልፍ ሰጠኝ" የሚለው ኃይለእየሱስ በዚህ መልኩ ቤቱን እየጠበቀ ለ6 ዓመታት እዚያው ግቢ ውስጥ አትክልቶቹን እየተንከባከበና ቤቱን እየጠበቀ ኖረ። ይሁን እንጅ ከአራት ወራት በፊት ቤቱን ለቆ እንዲወጣ መጠየቁን ያስታውሳል። በብዙ ሙግት ከቆየ በኋላ ቤቱን በለቀቀ ማግስት መጋቢት 17/2011ዓ. ም ቤቱን ፈርሶ እንዳገኘው ይናገራል። "ከውስጤ አንድ ነገር እንዳጣሁ ነው የተሰማኝ፤ በማልቀስ ነው የገለፅኩት... ለማየት እንኳን የሚሳሳለት ቤት በዚህ መልኩ መፍረሱ ከልቤ አሳዝኖኛል" ሲል ይገልፃል። ቤቱ ታድሶ ተጠብቆ ይኖራል የሚል እንጂ ይፈርሳል የሚል ቅንጣት ያህል ስጋት እንዳልነበረውም ይናገራል። የደጃዝማች ዐምዴ አበራ መኖሪያ ቤት የቀደመውን ዘመናዊ የቤት አሰራርን የሚገልጥ ጥበብ ያለው ነው የሚለው ኃይለየሱስ ወለሉ በጣውላ፤ የጭስ ማውጫው በእብነ በረድ የተሰራ ሲሆን በቤቱ ውስጥ የተለያዩ ቅርፃ ቅርፆችም ነበሩ። "የጣሪያው ዲዛይን በጣም የተለየ ነው፤ በዘመናዊ ጣውላ የተሰራ ነው፤ አሰራሩ በቃ ለየት ያለ ነው" ይላል። • ያልታበሰው የላሊበላ እንባ በግቢው ውስጥ የዋናውን ቤት ያህል አሰራራቸው የተለየ ባይሆኑም 6 ክፍል ቤቶች የነበሩ ሲሆን፤ ከዚህ ቀደም እንዲፈርሱ እንደተደረገ ያስታውሳል። ከዚህ በተጨማሪም ዓይነተ ብዙ የሆኑ እንደ የሀበሻ ፅድ፣ ወይራና ሌሎች እድሜ ጠገብ ዛፎች ይገኙበታል። "በመኪና ተገጭቶ ፈርሶ ነው እንጂ 'ፋውንቴንም' ነበረው" ይላል። እርሱ እንደሚለው መኝታ ቤት፣ የእንግዳ ማረፊያ፣ ሳሎንና በረንዳው እንዳሉ ፈርሰዋል፤ የሚታየው ፊት ለፊት ገፅታም ጉዳት ደርሶበታል። ደጃዝማች ዐምዴ በደርግ የተገደሉ ሲሆን አባታቸው አበራ ካሣ ደግሞ በጣሊያን በግፍ እንደተገደሉ ታሪክ ያስረዳል፤ ራሳቸውን ለሀገራቸው አሳልፈው ሰጥተዋል። ታዲያ በተወረሰው የእርሳቸው ቤት ጣሊያናዊ መኖራቸው ግጥምጥሞሹ ያስገርማል። እንደው ምን ይሰማቸው ነበር ያልነው ኃይለየሱስ ቤቱ በጣሊያን እጅ እንደተሰራ ከመንገር በዘለለ የነገሩት እንደሌለ ገልፆልናል። ከአገር ውጭ የሚገኙት የጣሊያናዊው ልጆች ለቤቱ ልዩ ፍቅር እንደነበራቸውና አንድ ቀን ተመልሰው ሊኖሩበት እንደሚፈልጉ ያጫውቱት እንደነበርም ነግሮናል። ይሄው ታሪካዊ ቤት ለሙዚቃ ክሊፖችና ፊልሞች የቀረፃ ቦታ ያገለግል ነበር። የአዲስ አበባ ባህል ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ረዳት ፕሮፌሰር ነብዩ ባዬ በበኩላቸው ቤቱ ላይ የተፈጸመውን ነገር አውግዘዋል። "አዲስ አበባን ትዝታና ታሪክ ያሳጣታል፣ የአዲስ አበባ አከታተም እንዴት እንደተጀመረ፣ የከተሜነቱን ሁኔታ የሚያሳይ ሲሆን ሥነ ህንፃን ማጥናት ለሚፈልጉ ትልቅ ጠቀሜታ የነበረው ነው፤ ደጃዝማች ዐምዴ ለሀገራቸው ሲሉ ህይወታቸው ያለፈ ታላቅ ኢትዮጵያዊ ማስታወሻም ነበር" ሲሉ በሆነው ሁሉ ማዘናቸውን ገልፀዋል። መኖሪያ ቤቱ በ1930 ዓ.ም እንደተሰራና ከቀደምቶቹ የአዲስ አበባ መኖሪያ ቤቶች አንዱ እንደሆነ ይናገራሉ - ኃላፊው። ከዚህ ቀደም እንደ ሰፈር የሚቆጠሩ በርካታ ቦታዎች ታሪካቸውን ማጣታቸውንም አውስተዋል። የደጃች ውቤ ሰፈርን፣ አራት ኪሎንና መርካቶን በምሳሌነት ይጠቅሳሉ። ኃላፊው አክለውም የደጅ አዝማች ዐምዴ አበራን ቤት በተመለከተ በህግ መጠየቃቸውን እንደሚቀጥሉ ገልፀው፤ ጥገና እስከሚደረግለት ፍርስራሹ ባለበት ሁኔታ እየተጠበቀ እንደሆነ ነግረውናል። የጉዛራን ቤተ መንግሥት ጥገና እያስታወሱ ቤቱ በቀላሉ መልሶ መጠገን እንደሚቻል ከባለሙያዎች አስተያየት ማግኘታቸውን ጠቅሰው ሥራውን ለማከናወን ጥናት እየተደረገ እንደሆነ ለቢቢሲ ገልፀዋል። በአዲስ አበባ ከተማ 440 ቅርሶች በተለያየ ይዞታ በቅርስነት ተመዝግበው ይገኛሉ።
news-44720966
https://www.bbc.com/amharic/news-44720966
"ከሞቱት አንለይም" የሶማሌ ክልል እስረኞች
በእስር ቤቱ የሚወልዱ እናቶች በሙሉ የህክምና አገልግሎት አያገኙም የምትለው የ31 ዓመቷ የሶማሌ ክልል የቀድሞ ታራሚ አያን "ሴት እስረኞች እርስ በርስ መረዳዳት ያለን ብቸኛ አማራጭ መሆኑን ባውቅም የመውለጃዬ ጊዜ ሲደርስ የህክምና አገልግሎት እንዲሰጡኝ ጠየቅኩኝ። የክልሉ ልዩ ፖሊሶች ግን የሰጡኝ ምላሽ ግን ልጁ አድጎም ስለማይረባ ሽንት ቤት ጣይው የሚል" እንደሆነ ትናገራለች።
የኦጋዴን ነፃ አውጭ ግንባር ደጋፊ ስለሚሆን መሞት እንዳለበት የነገሯት ታራሚም ተስፋ ባለመቁረጥ ሆስፒታል ውሰዱኝ ስትላቸው ምላሻቸው ሳቅ እንደነበር ትናገራለች። "ተጨማሪ ውሀም ሊሰጡኝም አልቻሉም" ትላለች። እዚያው አስር ቤት በአስቸጋሪ ሁኔታ የተገላገለችው አያን የልጁንም እትብት ለመቁረጥ ስለት ያለው ብረት ከአካባቢያቸው መፈለግ ነበረባቸው። ይህ የአያን ታሪክ የተወሰደው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች የሆነው ሂውማን ራይት ዋች "ዊ አር ላይክ ዘ ዴድ" (ከሞቱት አንለይም) በሚል ርዕስ ዛሬ ካወጣው ሪፖርት ሲሆን በሶማሌ ክልል ኦጋዴን እስር ቤት የሚደርሰውን የዘፈቀደ እስራት፣ መደብደብ፣ መደፈርና የሰው ልጅ ማሰብ ከሚችለው በላይ እንግልትን ያጋለጠ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አስቸኳይ ምርመራ እንዲጀምሩ የሚጠይቀው ሪፖርቱ የክልሉን የፀጥታ ኃይሎች እንዲቆጣጠሩና ባለሥልጣናቱም ተጠያቂነት ሊኖራቸው የሚያስችል ሥርዓት እንዲዘረጋና እርምጃ እንዲወስዱም አፅንኦት ይሰጣል። በዚህ 88 ገፅ ባለው ሪፖርት እስረኞች የሚደርስባቸውን ስቃይ፣ እንግልት፣ መደፈር በተጨማሪ የህክምና እጦት፣ ረሃብ እንዲሁም ቤተሰብም ሆነ ጠበቃዎቻቸው እንዳያዩዋቸው እንደተደረጉም እስረኞቹ ለድርጅቱ እንደገለፁ ሪፖርቱ ያስረዳል። በሪፖርቱ መሰረት ይህንን ሲፈፅሙ የነበሩት የእስር ቤቱ የሥራ ኃላፊዎችና የፀጥታ ኃይሎች፤ የሶማሌ ክልል ልዩ ፖሊስ ናቸው። እነዚህ ቡድኖች በሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አብዲ መሀመድ ኦማር ስር የሚገኙ ሲሆን ብዙዎቹም ከኦጋዴን ነፃ አውጭ ግንባር ጋር ግንኙነት አላችሁ በሚል ስቃይ እንደደረሰባቸው ተናግረዋል። ግንባሩ በኢትዮጵያ መንግሥት አሸባሪ ተብለው ከተፈረጁ ቡድኖች መካከል አንዱ መሆኑ የሚታወስ ነው። መንግሥት አድርጎ በማያውቀው ሁኔታ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ኢትዮጵያ ውስጥ በእስረኞች ላይ ስለሚደርሰው እንግልትና ስቃይ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው ማስረዳታቸው የሚታወስ ነው። በሶማሌ ክልል እየደረሰ ስላለው እንግልትም ሆነ ተጠያቂነት ስለሚረጋገጥበትም ሆነ ስለተጠቂዎቹ ፍትህ ዝርዝር ጉዳይ ግን አልተናገሩም። ይህ ሪፖርት ሂውማን ራይትስ ዋች በሶማሌ ክልል የሚገኙ 100 የፀጥታ ኃይሎችን ጨምሮ የመንግሥት ባለሥልጣናትንና በባለፉት ሰባት ዓመታት ውስጥ ስቃይና እንግልት የደረሰባቸውን 70 ግለሰቦችን መጠይቅ አድርጎ ያጠናቀረው ነው። "ለሦስት ዓመታት በጨለማ ቤት ተዘግቶብኝ ነው የኖርኩት" የሚለው የቀድሞ እስረኛ "በየቀኑ ማታ ማታ እደበደባለሁ። የማረሚያ ቤቱ ኃላፊዎች ያላደረሱብኝ ነገር የለም የዘር ፍሬዬን በኤሌክትሪክ ማቃጠልና በኤሌክትሪክ ሽቦ መጠፈር፣ በጭንቅላቴም ላይ በርበሬ ጨምረው በፌስታል ያፍኑኛል። እንዳልጮህም በጨርቅ አፌን ይጠቀጥቁት ነበር" ብሏል። ራቁታቸውን በእስረኞች መካከል እንዲረማመዱ ማድረግ፣ እስረኞን ማደባደብና የሚያሸማቅቁ ተግባራትን እንዲያከናውኑ እንደሚያደርጓቸውም ታራሚዎቹ ተናግረዋል። "በአንድ ወቅት በሁሉም እስረኞች መካከል ራቁቴን በጭቃ ላይ እንድንከባለል አዘዙኝና በዱላ ይደበድቡኝ ጀመር" የምትለው የ40 ዓመቷ ሆዳን ስትሆን ያለምንም ክስ አምስት ዓመታትን በእስር አሳልፋለች። "በሌላ ጊዜም እንዲሁ አንድ በእድሜ ሸምገል ያሉ ሰውዬን ከሴት ልጃቸው ጋር ራቁታቸውን እንዲቆሙ አድርገዋቸዋል። በጣም የሚያሳፍር ነገር ነው" ትላለች። እስረኞቹ እንደሚሉት የእስር ቤቶቹ ኃላፊዎች፣ የልዩ ፖሊስ ከፍተኛ ኃላፊዎች እንግልቱን፣ መደፈሩን፣ ምግብ ክልከላውን ከማዘዝ በተጨማሪ ተሳታፊም ነበሩ ይላሉ። በተጨናነቁት በእነዚህ እስር ቤቶች ውስጥ በሚፈጠር ረሃብ፣ በሽታና ስቃይ ምክንያት ብዙዎችም ለሞት እንደተዳረጉ ሪፖርቱ ጨምሮ ያትታል።
news-55526507
https://www.bbc.com/amharic/news-55526507
አሜሪካ፡ ለትራምፕ የጎን ውጋት ሆነው የቆዩት ናንሲ ፔሎሲ ማን ናቸው?
ካፒቶል ሂል የአሜሪካ 4 ኪሎ ማለት ነው። ቦታው የወንዶች የፖለቲካ አውድማ ሆኖ ነው የቆየው።
አሜሪካ "ሴቶች ወደ ማጀት" ማለት ካቆመች መቶ ዓመት ቢሆናት ነው። በዚህ ዘመን የወንዶች ብቻ ተደርጎ የሚታሰበውን የፖለቲካ መድረክ እንደ ፔሎሲ ገብቶ ለማተራስ የበቃ ሴት ፖለቲከኛ የለም። አሁን ፔሎሲ 80 ዓመታቸው ነው። በአፈ ጉባኤነት ለ4ኛ ዘመናቸው ተመርጠው ዜና ሆነዋል። ለማንም የማይመለሱ ብርቱ ሴት ናቸው። የካፒቶል ሂል ፖለቲከኞች ፔሎሲን ሲመለከቱ የሚናወጡት የሴትዮዋን ጥንካሬ አሳምረው ስለሚያውቁ ነው። ሕግን ጠፍጥፎ የሚጋግረውና አብስሎ የሚያወጣው የታችኛው ምክር ቤት የ435 እንደራሴዎች የሙግት ቤት ነው። ይህን የሙግት ምክር ቤት የሚመሩት ደግሞ እኚህ ብርቱ ሴት ናቸው። የሕግ መምሪያው ምክር ቤት የአፈ ጉባኤ የሥልጣን ዘመን 2 ዓመት ነው። ፔሎሲ እንደ አውሮፓዊኑ በ2007 ተመርጠው 2 የሥልጣን ዘመን አገልግለዋል። ከዚያ ወዲያ በ2019 ተመልሰው መጥተው አሁን ለ4ኛ ዙር ተመርጠዋል፤ በትናንትናው ዕለት። ፔሎሲ የዋዛሴት አይደሉም። 50 ዓመታት በአሜሪካ ፖለቲካ የጽኑ ብርቱ ሴት ናቸው። 50 ዓመት ከዲሞክራቲክ ፓርቲ ጋር ተጣምረው ኖረዋል። ካምላ ሐሪስ መጥተው በአሜሪካ ፖለቲካ ታሪክ አዲስ ምዕራፍ ከመክፈታቸው፣ የፖለቲካ ሥልጣን ከመቆናጠጣቸው በፊት በአሜሪካ ቁጥር አንድ ኃያሏ ሴት ፖለቲከኛና ተጽዕኖ ፈጣሪ ማን ነበሩ ቢባል መልሱ ናንሲ ፔሎሲ እንጂ ሌላ አይሆንም። አሁን የዲሞክራቶች ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት መግባትን ተከትሎ ናንሲ ፔሎሲ ወሳኝ ኃላፊነት ይጠብቃቸዋል። ለዲሞክራቶቹ የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ጆ እና ምክትላቸው ሐሪስ የሚስማሙ አጀንዳዎችን ወደ ፊት ማምጣት። ማቀበል፣ ማስወሰን፣ ወዘተ ይኖርባቸዋል። የአሜሪካ የታችኛው ምክር ቤት አሁንም ድረስ የዲሞክራት እንደራሴዎች ብልጫ ያለበት ቢሆንም ቁጥሩ ከቀድሞው ተመናምኖ ድንጋጤ ፈጥሯል። ዲሞክራቶች ታችኛውም ሆነ ላይኛው ምክር ቤት አብላጫነት ከእጃቸው ተንሸራቶ ሊወጣ ጫፍ ላይ ነው ያለው። ናንሲ ፔሎሲም ቢሆን ለ4ኛ ጊዜ በአፈ ጉባኤነት ሲመረጡ የተወሰኑ የእኔ የሚሏቸው ዲሞክራቶች ድምጽ ነስተዋቸው ለጥቂት ነው ያሸነፉት፤ እንጂማ ጉድ ሆነው ነበር። በጠባብ ልዩነት ማሸነፋቸው የናንሲ ፔሎሲ መጪዎቹ 2 ዓመታት ፈተና እንዴት ያለ እንደሚሆኑ አመላካች ነው ተብሏል። ከቤት እመቤትነት እስከ ብርቱ ፖለቲከኛነት ፔሎሲ የተገኙት ፖለቲካ የዕለት ተዕለት ቀለቡ ከሆነ ቤተሰብ ነው። ገና የ12 ዓመት አዳጊ እያሉ ፔሎሲ የዲሞክቲክ ፓርቲ ስብሰባ ላይ ተገኝተዋል። ልጅ እያሉ በሪፐብሊካን ባንዲራ ያጌጠ አሻንጉሊት አልቀበልም እንዳሉ በአፈ ታሪክ ይነገርላቸዋል። ጥብቅ ካቶሊክ እንደሆኑ የሚነግርላቸው ፔሎሲ በ20 ዓመታቸው ከጆን ኤፍ ኬኔዲ ጋር ተዋውቀዋል። ብዙ ሰዎች እሳቸውን ከድሀውና ከጭቁኑ አሜሪካዊ የራቁ፣ ግራ ዘመምነት በጭራሽ የማይታይባቸው "የሳንፍራንሲስኮ ለዘብተኛ" እያሉ ይጠሯቸዋል። እውነታው ግን ያ አይደለም። ፔሎሲ 6 ወንዶች ከሚገኙበት ትልቅ ቤተሰብ ውስጥ የመጨረሻ ሴት ልጅ ሆነው ነው ያደጉት። በምሥራቃዊ አሜሪካ ሜሪላንድ፣ ባልቲሞር ነው የተወለዱት። አባቷ ደንበኛ ዲሞክራት ነበሩ። አባቷ ቶማስ ዴ አሌሳንድሮ የባልቲሞር ከተማን ለ12 ዓመታት በከንቲባነት መርተዋል። አባቷ ብቻ ሳይሆን ወንድሟ ቶማስ ዴ አሌሳንድሮም ባልቲሞርን በከንቲባነት መርተዋል። ፖለቲካ ወደ ፒሎሲ የተሸጋገረው በእውቀት ብቻ ሳይሆን በቤተሰብም ነው የሚባለው ለዚህ ነው። ፔሎሲ ከዚያ በኋላ ዋሺንግተን ጆርጅ ታውን ኮሌጅ ገብተው ተማሩ። የአሁን ባላቸውን ፖል ፔሎሲን ያገኙትም እዚያው ኮሌጅ ነበር። መጀመርያ ወደ ማንሐተን ከዚያም ወደ ሳንፍራንሲስኮ ሄደው መኖር ጀመሩ። ያን ጊዜ የቤት እመቤት ነበሩ። አምስት ልጆችን በተከታታይ አፍርተዋል። አራቱ ሴቶች ናቸው። በአንድ አንድ ዓመት ልዩነት ነው ልጆቹን የወለዷቸው። ፔሎሲ በ1976 ነበር ለመጀመርያ ጊዜ ፖለቲካ ውስጥ የገቡት። የካሊፎርኒያው ገዥ ጄሪ ብራውን የምረጡኝ ቅስቀሳ ላይ ነበሩ። እርሳቸውን በማገዝ ፖለቲካን 'ሀ' ብለው ጀመሩ። ከዚያ በኋላ በሜሪላንድ የዲሞክራቲክ ፓርቲ ውስጥ ሊቀመንበር ከዚያም ደግሞ ኮንግረስ ተመራጭ ሆኑ። ይህም በ1988 ነበር የሆነው። በ2011 በታችኛው ምክር ቤት የመንግሥት ተጠሪ ለመሆን ተወዳደሩ። ይህ ሥልጣን በሕግ መምሪያው ምክር ቤት ውስጥ ሁለተኛው ትልቁ ሥልጣን ነበር። በቀጣይ ዓመት ደግሞ በሕግ መምሪያ ምክር ቤት ውስጥ የተቃዋሚ ፓርቲ ተጠሪ ሆነው ተመረጡ። ይህም ማለት በሕግ መምሪያ ምክር ቤት ውስጥ አነስተኛ መቀመጫ ያለውን ፓርቲ የመምራት ሥልጣን ማለት ነው። ፔሎሲ በ2003 ትንሹ ቡሽ ኢራቅን ለመውረር ሲነሱ አምርረው ወረራውን በመቃወማቸው በይበልጥ ይታወሳሉ። የእርሳቸው የያኔው አቋም በኋላ ላይ ወረራው ባስከተለው ጉዳት ተረጋግጧል። ይህም የማይናወጥ አቋማቸው በ2006 ዲሞክራቶች ወደ ሥልጣን እንዲመጡና የሕግ መምሪያ ምክር ቤቱን ከ12 ዓመታት በኋላ በበላይነት እንዲይዙት ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል። ከዚያ በኋላ በፓርቲያቸው የሕግ መምሪያው ምክር ቤት ተመራጭ ሆነው ረዥሙን የአፈ ጉባኤነት ሥልጣን ያዙ። በአሜሪካ ታሪክም የመጀመርየዋ ሴት አፈ ጉባኤ በመሆን አዲስ ታሪክ ሠሩ። እሳቸው ሥልጣን በያዙ ከ4 ዓመት በኋላ ዲሞክራቶች የሕግ መምሪያውን ምክር ቤት ቁጥጥር ከእጃቸው ወጣ። ፔሎሲ እጅ አልሰጥ ብለው ብዙ ትግል አደረጉ። ከዚህ ወዲያ ጥረታቸው ፍሬ አፍርቶ በ2018 ዲሞክራቶች በምክር ቤቱ ተመልሰው መጡ። የሕግ መምሪያው ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ሥራ ምንድን ነው? የሕግ መምሪያ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ መሆን ማለት በአሜሪካ የሥልጣን እርከን ከምክትል ፕሬዝዳንቱ ቀጥሎ ያለ ትልቅ ኃላፊነት ነው። በካፒቶል ግቢ በተንጣለለው የምክር ቤቱ ሕንጻ የፔሎሲ ቢሮ ስፋት የሥልጣናቸውን ግዝፈት የሚያመላክት ነው ማለት ይቻላል። የራሱ የሆነ ግዙፍ ባልኮኒ ያለውና በረንዳውም ወደ ዋሺንግተን ሐውልት የሚያሳይ ነው። በሕግ ማውጣት ሂደት ውስጥ ዋናው ይህ የታችኛው ምክር ቤት ነው። አፈ ጉባኤዋ እና ምክትላቸው እንዲሁም ቋሚ ኮሚቴ አባላት ጋር ተማክረው የትኛው ረቂቅ ሕግ ድምጽ ይሰጥበት በሚለው ላይ ይወስናሉ። የመወያያ አጀንዳ የሚቀርጹት እርሳቸው ናቸው። ክርክሮች የሚመሩበትን ሕግ የሚወስኑትም አፈ ጉባኤዋ ናቸው። ምክር ቤቱ ዱላ ቀረሽ ክርክር ሲያደርግ እንደራሴዎችን አደብ የሚያሲዙ እርሳቸው ናቸው። አፈ ጉባኤዋ በሕግ መምሪያው ምክር ቤት ውስጥ የፓርቲያቸውን የበላይነት እስካስጠበቁ ድረስ የመረጧቸው ረቂቆች ሕግ የማድረግ ጋሬጣ ላይጋረጥባቸው ይችላል። አነዚህ ምክር ቤት የሚወስናቸው ውሳኔዎች በአሜሪካ ሕዝብ ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ የመፍጠር አቅም አላቸው። ለምሳሌ ፔሎሲ አፈ ጉባኤ ሳሉ ከ2009 እስከ 2011 ድረስ ብቻ ምክር ቤቱ 840 ቢሊዮን ዶላር የምጣኔ ማነቀቂያ ገንዘብ እንዲረጭ ውሳኔ አሳልፏል። ፔሎሲ ተመጣጣኝ የጤና መድኅን (Affordable Care Act) ተግባራዊ እንዲሆን ታላቅ ተጋድሎ ያደረጉ የኦባማ ቀኝ እጅ የነበሩ ብርቱ ሴት ናቸው። ለትራምፕ ደግሞ የጎን ውጋት። የፔሎሲ የስላቅ ጭብጨባ ፔሎሲ በ2018 ወደ ምክር ቤቱ የአፈ ጉባኤነት መዶሻቸውን ይዘው ሲመለሱ ነገሮች ተቀያይረው ነበር የጠበቋቸው። ፕሬዝዳንት ትራምፕና የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ተጠሪ ሚች ማኮኔል ለፔሎሲ ደንቃራ ሆኑባቸው። በሕግ መምሪያ ምክር ቤት በእርሳቸው አርቃቂነት አብላጫ ድምጽ ተሰጥቶባቸው ወደ ሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ሲላኩ ውድቅ እየተደረጉ ተቸገሩ። ከሕግ መወሰኛ ሲያልፍ ደግሞ ትራምፕ ጠልፈው ይጥሉት ጀመር። ከዚህ ወዲያ ትራምፕና ፔሎሲ ተቃቃሩ። ይህ መቃቃራቸውም አንዳንድ ጊዜ ግላጭ ከመውጣቱ የተነሳ ለአሜሪካ ሚዲያ መዝናኛ ሆነ። ለምሳሌ #PelosiClap (የፔሎሲ የሹፈት ጭብጨባ) የሚለው የኢንተርኔት የስላቅ ኢሞጂ የተፈጠረው በዚህን ጊዜ ነበር። ፔሎሲ የስላቅ ጭብጨባውን ያደረጉት ዶናልድ ትራምፕ በሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ወቅት ተንኳሽ ንግግር ባደረጉበት ቅጽበት ነበር። ፔሎሲ በዚህን ጊዜ ገና ሥልጣኑን ከያዙ አንድ ወራቸው ነበር። ዛሬም ድረስ ይህ የናንሲ ፔሎሲ የስላቅ ጭብጨባ የኢንተርኔት ተወዳጅ የደቂቀ ምሥል ገላጭ (ኢሞጂ) መግባቢያ ሆኖ ቀጥሏል። ያን ቀን ምሽት ደግሞ ሌላ አስደናቂ ድርጊት ፈጸሙ። ፔሎሲ ለትራምፕ እጃቸውን ሲዘረጉ ትራምፕ ሳይጨብጧቸው ቀሩ። ፔሎሲ ደነገጡ። አፈሩም። ትራምፕ የሚያደርጉት ንግግር ግልባጭ ለሁሉም እንደራሴዎች ታድሎ ነበር። በጽሑፍ ለምክር ቤት አባላት የታደለውን የትራምፕን ንግግር ናንሲ ፔሎሲ ካሜራ ፊት እንደ ቆሻሻ ወረቀት ቡጭቅጭቅ አድርገው ቀዳደው ሲጥሉት በቀጥታ በቴሌቪዥን ታየ። ይህ ትልቅ መነጋገርያ ሆኖ ቆየ። ትራምፕና ናንሲ ፔሎሲ ዓይንና ናጫ ሆነው ይኸው ትራምፕ ከነጩ ቤተ መንግሥት ሲወጡ፣ ፔሎሲ ወደ ካፒቶል ሂል ሰተት ብለው በድጋሚ እየገቡ ነው። ፔሎሲ ከትራምፕ ጋር በግንብ አጥር የበጀት ጉዳይ ከፍ ዝቅ ተደራርገው ተሰዳድበዋል። ይህም በብዙ ሰዎች የተጋራ የፖለቲካ ቪዲዮ ሆኖ ነበር። ፔሎሲ በአሜሪካ ታሪክ ሦስተኛው ተከሳሽ ፕሬዝዳንት በነበሩት ትራምፕ ላይ ክሱን ለመምራት አቅማምተው ነበር። በኋላ ላይ ግን ትራምፕ ከዩክሬን ጋር የገቡበትን ቅሌት ሲሰሙ ክሱን ለመምራት ፍቃደኛ ሆኑ። ትራምፕ በሥልጣናቸው ባልገዋል። ይህ ደግሞ ቸል ሊባል አይገባም ብለው መቀነታቸውን አጥብቀው ተነሱ። ትራምፕ በዚህን ጊዜ የዩክሬን ባለሥልጣናት በጆ ባይደንና በልጁ ላይ አንዳች ጥፋት እንዲያፈላልጉና እንዲከሱ፣ አለበለዚያ ግን ለጦር መሣሪያ የሚሰጥ እርዳታ እንደማይለቀቅላቸው እያስፈራሩ ነበር። ትራምፕ ላይ የተነሳው ክስ ገፍቶ ሄዶ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ደርሶ የነበረ ቢሆንም በትራምፕ ወዳጆች የተሞላው የላይኛው ምክር ቤት ክሱን ውደቅ አድርጎታል። ፔሎሲ ለትራምፕ የጎን ውጋት ሆነውባቸው ነው ዘመናቸውን ሁሉ ያሳለፉት። የሜክሲኮን ድንበር በግንብ አጥር እጋርዳለሁ ገንዘብ ስጡኝ ያሉት ትራምፕ፣ ገንዘብ ይፈቀድ አይፈቀድ በሚለው ዙርያ ፔሎሲ ለትራምፕ አስጨናቂ ሆነውባቸው እንደነበር አይዘነጋም። ይህን ተከትሎ ነበር ትራምፕና ፒሎሲ በሚዲያ ፊት መተነኮኳኮስ የጀመሩት። መጪዎቹ የፒሎሲ ዘመናት ያስፈራሉ የባይደንን ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት መጠጋትን ተከትሎና ከዚያ ቀደም በነበሩ የሕዝብ ስሜቶች ተመርኩዘው ፔሎሲ የሚመሩት የሕግ መምሪያ ምክር ቤት የበላይነቱን አጠናክሮ ይቀጥላል የሚል መተማመን ነበር። የሆነው ግን በተቃራኒው ነው። ዲሞክራቶች ከአንድ ደርዘን በላይ እንደራሴ ወንበሮችን ለሪፐብሊካን ለመስጠት ተገደዋል። ከዚህ በኋላ የፔሎሲ የምክር ቤት ወንበር ቀላል አይሆንም። ለግራ ዘመሙ ፓርቲያቸው የሚስማማ አጀንዳዎችን መቅረጽ፣ ከዚያም ረቂቅ አድርጎ ማወያየት፣ አወያይቶም ማጸደቅ እንደ ከዚህ በፊቱ ቀላል ተግባር አይሆንም። የቢቢሲው የአሜሪካ ፖለቲካ ተንታኝ አንተኒ ዘርቸር እንደሚለው የፔሎሲ የ50 ዓመታት ፖለቲካዊ ተጋድሎ ከባዱ ፈተና ከዚህ በኋላ ያለው ነው የሚሆነው። ፈተናውን እንዴት ይወጡት ይሆን? "አንዱ መንገድ ለዘብተኛ የሪፐብሊካን እንደራሴዎችን ወደ እርሳቸው ሐሳብ እያግባቡ ማምጣት ነው። ሁለተኛው ተስፋቸው በሕግ መወሰኛ ምክር (ሴኔት) ቤት ዲሞክራቶች አብላጫ ወንበር ማግኘት ከቻሉ ነው" ይላል አንተኒ። ነገ ለጆርጂያ ግዛት 2 የምክር ቤት አባላት ይወዳደራሉ። ከተሸነፉ የላይኛው ምክር ቤት በሪፐብሊካን የበላይነት ይያዛል። ይህ ደግሞ ለጆ ባይደንና ለሐሪስ አዲስ ራስ ምታት ነው። ነገ የጆርጂያ ውክልና በዲሞክራቶች አሸናፊነት ከሆነ ግን ምክር ቤቱ እኩል የሪፐብሊካንና የዲሞክራቶች ተወካዮች ይኖሩታል። ይህ ከሆነ ደግሞ የሕግ መወሰኛውን ምክር ቤት ሊቀመንበርነት ከማይክ ፔንስ የሚረከቡት ተመራጭዋ ምክትል ፕሬዝዳንት ካምላ ሐሪስ የልዩነት ድምጽ የሚሰጡ ወሳኝ ሰው ይሆናሉ ማለት ነው። ይህ የመሆን ዕድሉ ግን ጠባብ ነው። አምስት ልጆችና ዘጠኝ የልጅ ልጆችን ያፈሩት ፔሎሲ ምናልባትም በፖለቲካ የመጨረሻው ዘመናቸው ፍሬያማ ላይሆን ይችላል።
43151436
https://www.bbc.com/amharic/43151436
እስራኤል ካገር አልወጣም ያሉ ኤርትራውያን ስደተኞችን አሰረች
ወደ ሩዋንዳ አንሄድም ያሉ 16 ኤርትራውያን ስደተኞች ለእስር ተዳረጉ።
የእስራኤል መንግሥት ስደተኞችን ካገር የማስወጣትንም እቅድ ተከትሎም ለእስር የበቁ የመጀመሪያዎቹ ስደተኞች ናቸው። የእስራኤል መንግሥት በሀገሪቷ ተቀማጭነታቸውን ያደረጉ የኤርትራና የሱዳን ስደተኞችን ወደ ሩዋንዳና ኡጋንዳ በመላክ ሙሉ በሙሉ ካገር የማስወጣት እቅድ አላት። እስካሁን ባለው 600 የሚሆኑ ስደተኞች ከሀገር እንዲወጡ ትዕዛዝ የተሰጣቸው ሲሆን ወደ 35 ሺ የሚሆኑ ስደተኞችም ከሀገር የመባረር አደጋ ላይ እንደሆኑ አንድ የእስራኤል የስደተኞች መብት ድርጅት አስታውቋል። ስደተኞቹ ሆሎት ከሚባለው የማቆያ ማዕከል የተወሰዱ ሲሆን በማእከሉም የረሀብ አድማ መነሳቱ ታውቋል። የእስራኤል መንግሥት በጥር ወር አካባቢ ስደተኞቹ ካገር እንዲወጡ ቀነገደብ ያስቀመጠ ሲሆን ካለበለዚያ ግን እስር እንደሚጠብቃቸው ማስጠንቀቂያ ሰጥቶ ነበር። ስደተኞቹ እሰራኤልን በሚቀጥሉት ሦስት ወራት ውስጥ ለቀው ለመውጣት ከተስማሙ 3500 ዶላር ይሰጣቸዋል ተብሏል። በዚህ ወር መጀመሪያም የእስራኤል መንግሥት የቀድሞ የሰራዊት አባላት ኤርትራውያን ስደተኖችን ጥገኝነት እንደሚሰጥ ቃል ገብቶ ነበር።
news-44964862
https://www.bbc.com/amharic/news-44964862
"የእሱ አባት ኩራዝ የላቸውም፤ እሱ ግን ኢትዮጵያን ሊያበራ ነው የሞተው"
ትናንት ባልታወቀ ሁኔታ መኪናቸው ውስጥ ህይወታቸው አልፎ የተገኘው የኢንጂነር ስመኘው ቤተሰቦች መሪር ሃዘን ውስጥ ናቸው። የቢቢሲ ዘጋቢ ትናንት የአስክሬን ምርመራ በሚካሄድበት የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ተገኝታ በጥልቅ ሐዘን ላይ የሚገኙ የቅርብ ቤተሰቦቻቸውን አነጋግራለች።
የኢንጂነር ስመኘው በቀለ ቤተሰብ አባላት ሐዘናቸውና ቅሬታቸውን በለቅሶ መሐል ሆነውም አጋርተዋታል። የቅርብ ዘመድ ቢኾኑም ስለ ግድያው በሚዲያ መስማታቸውን የገለጹት እኒህ የቤተሰብ አባላት አስክሬኑ መጉላላቱና የሚገባውን ክብር አለማግኘቱ ቅሬታ እንደፈጠረባቸው ተናግረዋል። ሌሎች የቤተሰቡ አባላት ደግሞ አንድም የመንግሥት አካል በአካባቢው አለመኖሩ የፈጠረባቸውን ቅሬታንም አልሸሸጉም። • ኢንጂነር ስመኘው በቀለ ሕይወታቸው ያለፈው በጥይት ተመተው ነው፡ ፌደራል ፖሊስ • ስለኢንጂነር ስመኘው አሟሟት እስካሁን ምን እናውቃለን? "ቢሮ ተቀምጦ አይደለም መግለጫ መስጠት" ሲሉ የመንግሥት አካላት ላይ ያነጣጠረ የሚመስል ቅሬታን አሰምተዋል። "እሱ ቤቱን ትቶ በረሀ ላይ ነው የኖረው። ለስመኝ ይሄ አይገባውም። ምን አረጋቸው፣ የበደላቸውን ለምን አይነግሩንም? ምን አደረጋቸው? ይሄ ለሱ አይገባውም" ስትል በመሪር ሐዘን ሆና ስሟን ያልገለፀች አንድ የቤተሰብ አባል ተናግራለች። "ማነው ጀግና፣ ማነው ጎበዝ? ማነው ለአገር አሳቢ። የሚመስል ወይስ የሆነ?" ሲል በምሬት ሐዘኑን የገለጸው ሌላ ወጣት "የእሱ አባት ኩራዝ የላቸውም፤ እሱ ግን ኢትዯጵያን ሊያበራ ነው የሞተው" ሲል ሳግ እየተናነቀው ምሬቱን ገልጿል። ከሐዘንተኞቹ መሐል በቅርብ ቀናት ሟችን በስልክም ይሁን በአካል አግኝተዋቸው ያውቁ እንደሆነ ተጠይቀው ኢንጂነሩ ሥራ ላይ ስለሚያተኩሩ እምብዛም ከቤተሰብ ጋር እንደማይገናኙ የሚያመላክት አስተያየቶችን ሰንዝረዋል። "እሱ አገሬን ሥራዬን እያለ ሁሉም ሰው ረስቶታል። እሱ ሁሉ ነገሩ ሥራው ላይ ነው። ዘመድ አይልም..." ስትል ስሟን መግለጽ ያልፈለገች የቤተሰብ አባል። "ከሰው ጋር አልኖረም፤ በረሃ ነው የኖረው" ስትል ሟች ማኅበራዊ ሕይወት የሚባል ነገር እንኳ እንዳልነበራቸው ተናግራለች። ኢንጂነር ስመኘው በቀለ
news-48455870
https://www.bbc.com/amharic/news-48455870
ስለአልኮል ማስታወቂያ ክልከላ የሚዲያ ባለሙያዎች ምን ይላሉ?
የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አዲስ የምግብና የመድሃኒት አስተዳዳር አዋጅ የአልኮል መጠጦችን በራዲዮ፣ በቴሌቪዥንና በቢል ቦርድ ማስተዋወቅ የሚከለክለው ደንብ ከትናንት ግንቦት 21፣ 2011 ዓ. ም ጀምሮ ተግባራዊ ሆኗል።
(ከግራ ወደ ቀኝ) ጋዜጠኛ ታምራት ኃይሉ፣ ኤልሳ አሰፋ እና ጥበቡ በለጠ በዚህ መሠረት ማንኛውንም መገናኛ ብዙሃን የአልኮል መጠጥ ማስታወቂያ ሕጉ ከሚፈቅደው ሰዓት ውጭ ማስተላለፍ እንደማይችል ተነግሯል። በኢትዮጵያ በርካታ የሬዲዮና የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች እንዲሁም የሕትመት ውጤቶች በቢራ ፋብሪካዎች ድጋፍ አድራጊነትና ከአልኮል መጠጦች ማስታወቂያ በሚገኝ ገንዘብ ይደገፋሉ። አንዳንዶቹ እንደውም ዋና የገቢ ምንጭ የሚያገኙበትም መንገድም ነው። ታዲያ አዲሱ ሕግ ምን ዓይነት ተፅእኖ ሊያሳድርባቸው ይችላል? • ለአንድ ወር ከአልኮል መታቀብ የሚኖረው አስደናቂ ውጤት • ብቻቸውን ወደ መዝናኛ ስፍራ የሚሄዱ ሴቶች ፈተና የቁም ነገር መፅሔት አዘጋጅና ባለቤት ታምራት ኃይሉ "ለመጭው ትውልድ በማሰብ ከሆነ በመልካም ጎኑ ሊወሰድ ይችላል፤ ነገር ግን እኛ አገር የማስታወቂያ ችግር በራዲዮና በቴሌቪዥን መተዋወቁ ሳይሆን አቀራረቡ ነው" ይላል። እሱ እንደሚለው፤ የአልኮል መጠጦች ማስታወቂያ በሌሎች አገራትም የተለመደ ሲሆን አቀራረቡ ግን የተጠና ነው። ባለው ልምድ፤ የቢራ ማስታወቂያዎቹ የሚተላለፉበት መንገድና ህፃናትን ሊስብ በሚችል መልኩ መቅረባቸው እንጂ ማስታወቂያው ሰዉን ጠጪ አድርጓል? ጠጪስ አለ? የሚለው ጥናት የሚፈልግ ጉዳይ እንደሆነ ይናገራል። ታምራት እንደሚለው፤ ከፍተኛ ማስታወቂያ አስነጋሪዎች ቢራ ፋብሪካዎች በመሆናቸው ሕጉ የመዝናኛ ዘርፉንና ሚዲያውን ይጎዳል። አዋጁ ተግባራዊ ሳይሆን በፊት የቢራ ፋብሪካዎች ማስታወቂያ መስጠት ማቆማቸው ተፅእኖ አሳድሯል የሚለው ታምራት፤ ከመከልከል ይልቅ በአቀራረቡ ላይ መነጋጋር ይሻላል ይላል። ከዚህም ባሻገር የቢራ ፋብሪካዎቹ ከፍተኛ ገንዘብና በርካታ ሠራተኞች የያዙ በመሆናቸው፤ ባለማስተዋወቃቸው ገበያቸውን የሚያጡ ከሆነ የአገሪቱን ኢኮኖሚ ይጎዳል የሚል ስጋትም አለው። "በርካታ ፕሮግራሞች የሚደገፉት የቢራ ፋብሪካዎች በሚያሰሩት ማስታወቂያ ነው" የምትለው በብስራት ኤፍኤም የፋሽንና ውበት ፕሮግራም አዘጋጅና ጋዜጠኛ ኤልሳ አሰፋ ጉዳዩን በሦስት መንገድ እንደምታየው ትገልፃለች። የመጀመሪያው በተለይ ከአልኮል መጠጥ ፋብሪካዎች በሚገኝ የድጋፍና የማስታወቂያ ገንዘብ የተቋቋሙና በዚያም ፕሮግራማቸውን የሚያስኬዱ ተቋማትን ገቢ ያሳጣል። በሌላ በኩል እንደአንድ ማኅበረሰብ ማስታዋቂያዎች ከሚሠሩበት መንገድና ከቢራ ፋብሪካዎቹ ስያሜ ታዳጊዎች ምን እየተማሩ ያድጋሉ? የሚለው ጥያቄ ያስነሳል ትላለች። • ወንዶች የማያወሯቸው አምስት አሳሳቢ ነገሮች • እውን ቡና መጠጣት እድሜ ይጨምራል? "ቢራ እንደመድሃኒትና እንደምግብ ነበር ሲተዋወቅ የነበረው" የምትለው ኤልሳ፤ ህፃናትን በማይጎዳ መልኩ ጥናት ተሠርቶ ማስታወቂያዎቹ እንዲተላለፉ ማድረግ ይቻል ነበር ስትል ትሞግታለች። የአሀዱ ኤፍኤም ራዲዮ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጥበቡ በለጠ የተለየ ሃሳብ አላቸው። "ባለፉት ዓመታት በማስታወቂያና በፕሮሞሽን ድጋፍ ጉልህ ቦታ የነበራቸው የቢራ ፋብሪካዎች ነበሩ፤ ራዲዮና ቴሌቪዥን ጣቢያዎችን ለመክፈት ከቢራ ፋብሪካዎች ጋር መነጋጋር የተጀመረበት ወቅትም መጥቷል" ይላሉ። በአብዛኛው ቢራዎች ሚዲያውን የመቆጣጠር ደረጃ ላይ ደርሰዋል የሚሉት አቶ ጥበቡ፤ ማስታወቂያዎቹንም ከኢትዮጵያዊነት፣ ከማንነት፣ ከታላቅነት ጋር በማያያዛቸው ሰዎች ጠጪ እንዲሆኑ የማድረግ ተፅዕኖ ሲያሳድሩ መቆየታቸውን ያምናሉ። ነገሩ ያሳስባቸው እንደነበርም አልሸሸጉም። በመሆኑም የቢራ ማስታወቂያዎቹ መከልከላቸው በአገሪቱ ላይ በጎ አሻራ ያሳርፋል ይላሉ። "ኃላፊነታቸውን አልተወጡም፤ ትውልድ ላይና አገር ላይ የሚሰሩ ጉዳዮችን የቢራ ፋብሪካዎች ሲደግፉ አይታዩም" በማለት ሚዲያው ሊወጣ የሚችለውን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ሚና እንደጎዱት ያብራራሉ። አቶ ጥበቡ እንደሚሉት፤ ከቢራ ፋብሪካዎች ውጭ ከሚዲያ ጋር መሥራት የሚፈልጉ ሌሎች ድርጅቶችም ቢኖሩም የቢራ ፋብሪካዎቹ ከፍተኛ ገንዘብ በመክፈል ሌሎቹ ገፍተው እንዳይመጡ የማድረግ ሚናም ነበራቸው። የሚዲያ ተቋማቱ ጥራት ያለውና ሊደመጥ የሚችል ፕሮግራም ማቅረብ ከቻሉ ድጋፍ የሚያደርግላቸው አያጡም የሚል እምነትም አላቸው። • የሰሞኑ የአዲስ አበባ እስርና ሕጋዊ ጥያቄዎች • ከእግር ኳስ ሜዳ ወደ ኮኛክ ጠመቃ ሕጉ ለሕትመት ሚዲያዎች ተስፋ ይሰጥ ይሆን? አዲሱ የምግብና የመድሃኒት አስተዳዳር ሕግ የአልኮል ማስታወቂያዎችን ማስተላለፍ የሚከለክለው በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን እና በቢል ቦርድ ነው። በመሆኑም በህትመት ዋጋ ውድነትና አንባቢ ባለመኖሩ ለሚንገዳገዱት የህትመት ሚዲያዎች ተስፋ ይሰጥ ይሆን? የቁምነገር መፅሔት አዘጋጅና ባለቤት ታምራት በዚህ ረገድ ተስፋ አለው። መፅሔትና ጋዜጣ የሚያነቡት ኃላፊነት የሚሰማቸውና ትልልቅ ሰዎች እንደሆኑ የሚናገረው ታምራት፤ በየጊዜው እየጨመረ የመጣውን የህትመት ዋጋ መቋቋም የሚቻለው በማስታወቂያ ገቢዎች ነው ይላል። በዚህም ጥራቱን ማሻሻል፣ ሥርጭቱን ማሳደግ፣ የንባብ ባህልን መጨመር ይቻላል ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል። • የኦነግ ጦር መሪ በትግላችን እንቀጥላለን አለ ይሁን እንጂ አሁንም በሕጉ ላይ ብዥታ በመኖሩ፤ የቢራ ፋብሪካዎችም ሆኑ የአልኮል ማስታወቂያ የሚሰጡ ድርጅቶች ክልከላው ለሁሉም መገናኛ ብዙሀን ነው በማለት እየተንቀሳቀሱ እንዳልሆነ ገልጿል። "በኢትዮጵያ የህትመት ሚዲያው ሥርጭት የተዳከመ ነው፤ ግፋ ቢል ከአምስት ወይም ስድስት ሺህ ቅጂ በላይ አይሸጥም" የሚሉት አቶ ጥበቡ፤ የአልኮል መጠጥ ማስታወቂያዎች በህትመት ሚዲያዎች ላይ ቢወጡ አቀራረባቸው የተገደበ ስለሚሆን፣ በተለይም ለህጻናት ፊት ለፊት ስለማይታዩ ተፅእኖ አይኖረውም ይላሉ። "ፋብሪካዎቹ ብራንዳቸው እንዳይረሳ ወደህትመት ሚዲያ ሊመጡ ይችላሉ" የምትለው ኤልሳ፤ አሁን በመነቃቃት ላይ ያለውን የህትመት ሚዲያው የበለጠ እንደሚያበረታው እምነት አላት። በሚዲያው ላይ ምን ተፅእኖ አሳረፈ? ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ሚዲያዎች ላይ ጥናት እንዳደረጉ የሚናገሩት አቶ ጥበቡ፤ ወሳኝ የሚባሉት ሰዓቶች ከድጋፍ አድራጊ አካላት ጋር ግንኙነት አላቸው ይላሉ። ከቢራ ፋብሪካዎች ጋር ተፈራርመው ገንዘብ ይዘው የሚመጡ ፕሮግራሞች ቅድሚያ እንደሚሰጣቸውም ያክላሉ። ዋና ዋና የሚባሉት ሰዓቶች 'መዝናኛ' ለሚባሉና በቢራ ፋብሪካዎች ለተደገፉ ፕሮግራሞች ይሰጣሉ። ይህም በአገሪቱ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ፋይዳ የሌላቸው ፕሮግራሞች በኢትዮጵያ ሚዲያ ላይ እንዲደረጁ እንዳደረገ ያስረዳሉ። • የተሟላ የወጪ ማስረጃ ሳይቀርብ ከ1.4 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ ተደርጓል የታምራት ሀሳብም ተመሳሳይ ነው። የስፖንሰርሺፕ (ድጋፍ) ሃሳብ ተግባራዊ የሚደረገው በተዛባ መልኩ ነው ይላል። "የውጭ አገር ሚዲያዎችና ዓለም አቀፍ የስፖርት ውድድሮች ላይ የአልኮል መጠጥ ማስታወቂያዎች ይተላለፋሉ፤ ነገር ግን እንደ እኛ መልክ ያጣ አይደለም" ሲል የማስታወቂያ አሠራር እውቀትና አቅም ችግር እንዳለ ይናገራል። "ወላጆች ከልጆቻቸው ጋር ቁጭ ብለው ቴሌቪዥን ማየት የተቸገሩበት ጊዜ ላይ ደርሰን ነበር" ሲልም ያክላል። ኤልሳ በበኩሏ የአልኮል መጠጥ ፋብሪካዎቹ ምርቶቻቸውን ለማስተዋወቅ የራሳቸው ምርጫ ቢኖራቸውም፤ በአብዛኛው አስተማሪና ጠንከር ያሉ ፕሮግራሞችን ተመራጭ ሲያደርጉ አይታይም ስትል ልምዷን አጋርታናለች። "በቤተሰብ ላይ ያተኮረ ተወዳጅ ፕሮግራም ነበረኝ፤ ነገር ግን ዓመቱን ሙሉ አንድም የቢራ ስፖንሰር አልነበረኝም፤ ምክንያቱም ፕሮግራሙ ስለሚያስተምር አያዝናናም የሚል ነው" ስትል በርካታ ቁም ነገር አዘል ፕሮግራሞች ያለድጋፍ ሲሠሩ እንደሚስተዋል አክላለች። የፋብሪካዎቹ የገበያ ዘርፍ ኃላፊዎች (ማርኬቲንግ) የየራሳቸው አድማጭ ሊኖራቸው ቢችልም፤ በተለያዩ መንገዶች ማኅበራዊ ግዴታዎችን መወጣት እንደሚገባቸው አስተያየቷን ሰጥታለች።
43695226
https://www.bbc.com/amharic/43695226
ባባኒ ሲሶኮ፦ 'ዓለም አቀፉ ምትሃተኛ'
ጊዜው በፈረንጆቹ ወርሃ ነሃሴ 1995 ዓ.ም.፤ ፎቱንጋ ባባኒ ሲሶኮ የተባለ ግለሰብ ወደ ዱባይ እስላማዊ ባንክ ጎራ ይልና "መኪና ልገዛ ነው ብድር ስጡኝ" ይላል።
የባንኩ ስራ አስኪያጅ ሞሃመድ አዩብም "ምን ገዶን ዕዳህን በጊዜው ክፈል እንጂ" ይለዋል። በዚህ የተደሰተው ሲሶኮ ስራ አስኪያጁን "ፈቃድህ ሆኖ እራት አብረን እንበላ ዘንድ እንዳው ቤቴ ብቅ ብትል" ሲል ግብዣ ያቀርባል። በዓለማችን ከታዩ አስደናቂ ማታለሎች አንዱ የሆነው ታሪክ የሚጀምረው እንዲህ ነው። የቢቢሲዋ ብሪዢት ሺፈር እንዲህ ታቀርበዋለች። እራት እየበሉ ሳለ ሲሶኮ ለስራ አስኪያጁ አንድ አስደናቂ ታሪክ ያካፍለዋል። "አንድ ኃይል አለኝ" ይለዋል. . .ይህን ኃይል ተጠቅሜም ገንዘብ እጥፍ ማድረግ እችላለሁ። እንደውም በሚቀጥለው ጊዜ የተወሰነ ገንዘብ ይዘህ መጥተህ ለምን አላሳይህም?" ሲል ሲሶኮ ጥያቄ ያቀርባል። ምትሃት በእስልምና የተወገዘ ሲሆን እንደ ትልቅ ኃጥያትም የሚቆጠር ነው። ቢሆንም በርካታ ሰዎች በምትሃት ያምናሉ። ሞሃመድ አዮብ ከአንድ ከከተማ ራቅ ብላ ከምትገኝ የማሊ ገጠራማ ሥፍራ ወደመጣው ሲሶኮ ገንዘቡን ይዞ ተከሰተ። ልክ በሩን ከመርገጡ አንድ ሰው ከውስጥ ወጥቶ "መንፈስ (ጅኒ) መታኝ" ይለዋል። "ወደ ውስጥ ስትገባ ጅኒውን እንዳታበሳጨው ጠንቀቅ በል፤ ያለዚያ ገንዘብህ እጥፍ አይሆንም" ሲል ይነግረዋል። አዩብም ወደውስጥ ከዘለቀ በኋላ ገንዘቡን አስቀምጦ እጥፍ እንዲሆንለት በጥሞና ይጠብቅ ጀመር። "ድንገት ከክፍሉ ውስጥ መብራት እና ጭስ እንዲሁም የመናስፍቱ ድምፅ መውጣት ጀመረ" ይላል አዩብ። ለጥቆም ገንዘቡ እጥፍ ሆነለት፤ አየብም ፊቱ ፈካ። በአውሮፓውያኑ 1995 እስከ 98 ባለው ጊዜ ብቻ አዩብ ለሲሰኮ ምትሃቱን ተጠቅሞ ገንዘቡን እጥፍ እንዲያደርግለት በማለት 83 ጊዜ በባንክ ደብተሩ አማካይነት ገንዘብ አስገብቶለታል፤ ገንዘቡ የባንኩ መሆኑ ሳይረሳ። 98 ላይ የዱባዩ ባንክ እየከሰረ መሆኑ መዘገብ ያዘ። ዜናውን ያነበቡ የባንኩ ደንበኞችም ገንዘባቸውን ለማውጣት በየቅርንጫፉ ተሰለፉ። ቢሆንም የዱባይ ባለሥልጣናት ዘገባው ሃሰት የተሞላ ነው እንጂ ባንኩ የገንዘብ እጥረት አልገጠመውም ሲሉ ተደመጡ። እውነታው ግን ይህ አልነበረም። ኋላ ላይ በጉዳዩ ጣልቃ የገባው የዱባይ መንግሥት ባንኩን በገንዘብ በመደጎም ራሱን ችሎ እንዲቆም አደረገው። ይህ ሁላ ሲሆን ታዲያ ሲሶኮ በጣም ሩቅ ሥፍራ ነበር፤ ምትሃቱን የበለጠ ድንቅ የሚያደርገው ደግሞ ገንዘቡን ለማግኘት ዱባይ መገኘት ግዴታ አለመሆኑ ነው። ጊዜው ጥቅምት 1995...ምትሃቱን በሞሃመድ አዩብ ላይ የተጠቀመው ሲሶኮ ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ወደ ኒው ዮርክ በማቅናት ተመሳሳይ ድርጊት ፈፀመ። ሲቲባንክ የተባለ ባንክ በመዝለቅ አንድ የደንበኞች አገልግሎት ሠራተኛ ተዋወቀ፤ ትንሽ ቆይቶም አገባት። ይህንን ተጠቅሞም ከሲቲባንክ ጋር ያለውን ግኑኝነት ማሳመር ቻለ። ሲሶኮ ከሲቲባንክ ወደ ዱባይ እስላማዊ ባንክ ደብተሩ ከ100 ሚሊዮን ዶላር በላይ እንዳስተላለፈም ይታመናል፤ ለዚህ የረዳችው ሚስቱን በረብጣ ዶላሮች እንደካሳትም ተነግሯል። ስለሲሶኮ ይህንን መረጃ የሚናገሩት የዱባዩ ባንክ በጉዳዩ ላይ ክስ በከፈተ ጊዜ ጠበቃ አድርገው የቀጠሩት አለን ፋይን ናቸው። ከጊዜ ወደ ጊዜ ምትሃቱን ተጠቅሞ ገንዘብ ማፍራቱን የቀጠለው ሲሶኮ ምኞቱ የነበረውን በምዕራብ አፍሪካ አየር መንገድ መክፈት ያመቸው ዘንድ ቦይንግ አውሮፕላን ገዛ። አየር መንገዱን በትውልድ መንደሩ ስም ዳቢያ ብሎ ሰየመው። ነገር ግን ወርሃ ሐምሌ 1996 ላይ ሲሶኮ አንድ ስህተት ሠራ። ሁለት ከቪየትናም ጦርነት የተረፉ ሄሊኮፕተሮች ምክንያቱ ባልታወቀ ምክንያት ለመግዛት ሞከረ። ሄሊኮፕተሮቹ ለጦርነት ጥቅም ላይ የዋሉ በመሆናቸው ምክንያት ለመብረር ልዩ ፍቃድ ያሻቸዋል። ይህን ያስተዋሉት የሲሶኮ ሰዎች ፖሊሶችን ለመደለል ሲሞክሩ ለእስር በቁ። ዓለም አቀፉ ኢንተርፖልም ሲሶኮ በቁጥጥር ሥር እንዲውል ትዕዛዝ አወጣ። ሌላ የባንክ ደብተር ለመክፈት ወደ ጄኔቫ አቅንቶ የነበረው ሲሶኮ በቁጥጥር ሥር ዋለ፤ ለጥቆም ወደ አሜሪካ ተላከ። ምንም አንኳ የአሜሪካ መንግሥት ሲሶኮ በቁጥጥር ሥር እንዲውል ቢፈልግም በ20 ሚሊዮን ዶላር ዋስ እንዲለቀቅ ሆነ። ሲሶኮ ለዚህ ላበቁት የህግ ሰዎች ውድ የሚባሉ መኪኖችን ሸለመ። አንድ መኪና ሻጭ ሲሶኮ ቢያንስ 53 መኪናዎችን ገዝቶኛል ሲል ይናገራል። ነዋሪነቱን ማያሚ ያደረገው ሲሶኮ በከተማዋ ታዋቂ ሆነ፤ በርካታ ሚስቶችንም አገባ፤ 23 አካባቢ አፓርትማዎችንም ተከራየ። ሲሶኮን የሚያውቁት ግርማ ሞገስ ያለው፣ አለባበሱ ያማረ እና መልከ-መልካም ሰው ነው ሲሉ ይገልፁታል። አልፎም ከገንዘቡ ወደ 413 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ለእርዳታ አዋሏል። ጠበቃዎቹ ከነበሩ በርካታ ግለሰቦች መካከል አንዱ የሆነው ስሚዝ የተባለ ሰው ሲናገር ሲሶኮ ዘወትር ሃሙስ በመኪናው እየዞረ ለቤት አልባ ሰዎች ገንዘብ ያድል ነበር። የጠበቃዎቹን ምክር አልሰማም ያለው ሲሶኮ ጥፋተኛ ነኝ ሲል አመነ። ለ43 ቀናት እሥር እንዲሁም ለ250 ሺህ ዶላር ቅጣትም ተዳረገ። ከተፈረደበት ፍርድ ግማሹን የፈፀመው ሲሶኮ 1 ሚሊዮን ዶላር ለቤት አልባ ሰዎች በመስጠት የተቀረውን ፍርድ በቤት ውስጥ እስር እንዲጨርስ ሆነ። በዚህ ጊዜ ነው ታድያ የዱባዩ እስላማዊ ባንክ ኦዲትሮች የሆነ ነገር ትክክል እንዳልሆነ መጠርጠር የጀመሩት። አዩብም ፀባዩ መለዋወጥ ታየበት፣ ሲሶኮም እንደ ድሮ በተፈለገ ጊዜ ስልክ አላነሳ ማለት ይጀምራል። በስተመጨረሻም አዩብ ለሥራ ባልደረባው ያጋጠመውን ይተነፍሳል። "ምን ያህል ብር ነው የጠፋው?" ሲል ለጠየቀው ጓደኛው በቃላት ምላሽ መስጠት የተሳነው አዩብ በብጣሽ ወረቀት ፅፎ ያቀብለዋል. . .242 ሚሊዮን ዶላር። በዚህ ጉዳይ ጥፋተና ሆኖ የተገኘው አዩብ የሶስት ዓመታት እሥር ይፈረድበታል፤ "በምትሃት አምነሃልና ሸይጣንህን እናስወጣልህ" ተብሎ በኃይማኖቱ መሠረት ሸይጣን ማስወጣት እንደተካሄደለትም ይነገራል። አዩብ በዚህ ሁሉ ውጣ ውረድ ሲያልፍ ሲሶኮ ግን ዱባይ ሊገኝ ባለመቻሉ ምክንያት በሌለበት የሶስት ዓመታት ፍርድ ይወሰንበታል። ዓለም አቀፉ ፖሊስ 'ኢንተርፖል' ግን "አፈልገዋለሁ" ሲል ማስታወቂያ ይለጥፋል። ሲሶኮ ለ12 ዓመታት ያክል ማለትም በአውሮፓውያኑ ከ2012 እስከ 2014 ባለው ጊዜ በማሊ የሕዝብ እንደራሴ ሆኖ በመሾሙ ምክንያት ያለመከሰስ መብቱ ተጠብቆለት ቆየ። ላለፉት አራት ዓመታት ደግሞ ሃገሩ ማሊ ወንጀለኞች አሳልፎ የመስጠት ስምምነት ከየትኛውም ሀገር ጋር ስምምነት ባለመፈረሟ ምክንያት ያለ ምንም ስጋት ሕይወቱን እያጣጠመ ኖረ። ከዚያ በኋላ ነው ሲሶኮን ፍለጋ ወደ ማሊ ርዕሰ መዲና ባማኮ ያቀናሁት ትላለች የቢቢሲዋ ብሪዢት። ከዚያም የሲሶኮ ሹፌር የሆነውን ሉካሊ ኢብራሂምን ታገኘዋለች። በትውልድ መንደሩ ዳቢያ ሊኖር እንደሚችልም መረጃው ለብሪዢት ይደርሳታል። ከሰዓታት ጉዞ በኋላ ብሪዢት ሲሶኮ መኖሪያ የተባለው ቤት ትደርሳለች፤ በወታደሮች የሚጠበቅ ሰፋ ያለ ግቢ። በስተመጨረሻም ሰውየውን በአካል ታገኘዋለች. . .የሰባ ዓመቱን 'ምትሃተኛ' ፎቱንጋ ባባኒ ሲሶኮን። ለቃለ-መጠይቅ ፈቃደኛ ሆኖ የተገኘው ሲሶኮ "ስሜ ፎቱንጋ ባባኒ ሲሶኮ ይባላል። የተወለድኩ ዕለት ማሪየቶ ወንድ ልጅ ወለደች በማለት ሰፈሩ ቀለጠ" በማለት ታሪኩን ለብሪዢት መተረክ ይጀምራል። "እንደው ከዱባዩ እስላማዊ ባንክ ጠፋ ስለተባለው 242 ሚሊዮን ዶላር የምታወቀው ነገር ይኖራል?" ለሲሶኮ የተሰነዘረ ጥያቄ ነው። "እመቤት...ይህ 242 ሚሊዮን ዶላር የማይመስል ታሪክ ነው። የባንኩ ሠራተኛ ቢያስረዳሽ ነው የሚሻለው እንጂ ያን ያክል ገንዘብ ሲጠፋ መቼም ዝም ብለው አይቀመጡም። በዚያ ላይ ይህን ያህል ገንዘብ ከባንክ ለመውሰድ በርካታ ቢሮዎች መሄድ አለብሽ።" "አዩብ ግን. . . ?" ብሪዢት የሰነዘረችው ጥያቄ። "አዩብ የባንኩ ሠራተኛ? አዎ እሱን ሰውዬ አንድ ጊዜ አግኝቸዋለሁ። መኪና ለመበደር የሄድኩ ጊዜ። ምርጥ የጃፓን መኪና ነበረች። ዕዳዬንም በጊዜው ከፍዬ ጨረስኩ" የሲሶኮ ምላሽ። ጋዜጠኛዋ በስተመጨረሻም ስለ 'ምትሃት' ጠየቀችው። "እመቤት አንድ ሰው እንዲህ ዓይነት ኃይል ካለው ለምን ይሠራል? ቁጭ ብሎ ባንክ እየዘረፈ መብላት እየቻለ። ቢፈልግ ከአፍሪካ፣ አሜሪካ፣ ፈረንሳይ ያሻውን ባንክ እየዘረፈ መኖር ይቻል አልነበር።" "እና አሁንስ ሃብታም ነህ?" "ኧረ በጭራሽ። እኔ ሃብታም አይደለሁም። እንደውም ደሃ ነኝ።" ምንም እንኳ ዓለም አቀፉ ፖሊስ 'ኢንተርፖል' አሁንም ሲሶኮን ፍለጋውን ቢቀጥልም፣ ምንም እንኳ በርካታ ገንዘብ አፍርቶ ቢያጠፋም ፎቱንጋ ባባኒ ሲሶኮ በሃገሩ ማሊ በጤና ኑሮውን እየገፋ ይገኛል።
news-49069302
https://www.bbc.com/amharic/news-49069302
ሳባ አንግላና፡ "ኢትዮጵያዊትም፣ ጣሊያናዊትም ሶማሊያዊትም ነኝ"
ሳባ አንግላና ከኢትዮጵያዊት እናቷና ከጣሊያናዊ አባቷ የተወለደችው ሞቃዲሾ ውስጥ ነው። የእናቷ ቤተሰቦች በኢትዮ-ሶማሊያ ጦርነት ወቅት ነበር በምርኮኛነት ወደ ሶማሊያ የተወሰዱት። ከዓመታት በኋላ እናቷ አንድ ጣሊያናዊ ሞቃዲሾ ውስጥ ተዋወቀች፤ ትውውቃቸው ወደ ፍቅር፣ ፍቅራቸው ወደ ትዳር አደገ፤ ከዚያም ሳባ ተወለደች።
ሳባ አንግላና ስልጣን ላይ በነበረው በሞሐመድ ዚያድ ባሬ መንግሥት አስተዳደር ወቅት የሳባ እናትና አባት ሞቃዲሾ ውስጥ ተደላድለው መኖርና ልጃቸውንም ማሳደግ የማይታሰብ ሲሆንባቸው ያላቸውን ሸክፈው ወደ አባቷ ሀገር ጣሊያን አመሩ። ሳባ የሦስት ሀገራት ነጸብራቅ በውስጧ በአንድ ላይ ይታይባታል። ስትጠየቅም ይህንኑ ታስረዳለች፤ በእናቷ ኢትዮጵያዊ፣ በአባቷ ጣሊያኒያዊ፣ እትብቷ የተቀበረው ደግሞ ሶማሊያ ውስጥ ቢሆንም ጥርሷን ነቅላ ያደገችው ግን ሮም ከተማ ውስጥ ነው። • "ኢትዮጵያዊነቴን ያገኘሁት ሙዚቃ ውስጥ ነው" አቨቫ ደሴ ሳባ ለጥበብ ጥሪ 'አቤት' ብላ ምላሽ የሰጠችም ናት፤ ትወና ነፍሷ ነው፤ ደራሲና ድምፃዊም ናት። "ሳባ ብለው የሰየሙኝ ንግሥቲቷን በማሰብ ነው ... ለእኔ ግን በስሜ ራሱ አንድ ከባድ ኃላፊነት እንደተጣለበኝ ነው የማስበው" ትላለች። ሳባ የኢትዮጵያ የሃገር ባህል ልብስ ተውባ መድረክ ላይ ስታንጎራጉር ሳባ "ብዙ ጊዜ ከአንድ ወይም ሁለት በላይ በባህል፣ በደምና በማንነት 'የተዳቀሉ' (ክልስ) ሰዎች ለየት ያለ እሳት በውስጣቸው እንደሚነድ አምናለሁ። ሆኖም ግን ነበልባሉ የሚተነፍስበትን ትክክለኛ መውጫ ማግኘት ያስፈልጋል" በማለት በውስጧ ስላለው ራሷን በሙዚቃ ለመግለፅ ስላላት ጽኑ ፍቅር ትናገራለች። ሙዚቃን የሕይወት ጥሪዬ ነው ብላ የተቀበለችውም በዚህ ምክንያት እንደሆነ ስታስረዳ "በውስጤ የነበረውን ነበልባል የማወጣበት የሆነ ነገር ያስፈልገኝ ነበር" በማለት ነው። ከልጅነቷ ጀምሮ እግሯ በረገጠበት ሁሉ ዜግነቷን ትጠየቅ ስለነበር፤ በሙሉ የራስ መተማመን መልስ ለመስጠት እንደትችል ማንነቷን ማወቅና መገንባት ነበረባት። • "ራሴን የምፈርጀው የሀቅ ታጋይ ነኝ ብዬ ነው" አሊ ቢራ "ሙዚቃ፤ ነፃነቴንና ተቃውሞዬን የምገልጽበት ቋንቋ ነው" የምትለው ሳባ ማንነቷን ራሷ እየገነባችው እንደመጣች ታስረዳለች። ሳባ ወደ ሙዚቃው ዓለም የተቀላቀለችው እድሜዋ ሠላሳን ከዘለቀ በኋላ ነው። ለምን? ስትባልም አባቷን ታነሳለች። "...በልጅነቴ ሁል ጊዜ አንጎራጉር ነበር። ነገር ግን ቤተሰቦቼ በተለይ አባቴ ሙዚቃው እንዳይስበኝ ይጥር ነበር" በማለት አባቷ ፊደል ቆጥራ፣ ተምራ፣ ተመራምራ የዕለት እንጀራዋን እንድታበስል ይመክሯት እንደነበር ትናገራለች። አባቷ ካረፉ በኋላ ግን ነገሮች ተቀየሩ፤ "አባቴ ቆንጆ ድምፅ እንዳለኝ ለሰው ሁሉ ይናገር እንደነበር ተነገረኝ። ውስጤ በጣም ደማ፤ ምክንያቱም ለእርሱ ባንጎራጉርለት ኖሮ ደስ ይለኝ ነበር። ምነው ለራሴ በነገረኝ ኖሮ እያልኩ ወደ ሙዚቃው ተሳብኩ" ትላለች። ኢትዮጵያዊት? ጣልያናዊት? ወይስ ሶማሊያዊት? ሶማሊያ ተወልዳ ያደገችው ሳባ ለዚህ ጥያቄ መልሷ "ሦስቱም" የሚል ነው። የልጅነትና የወጣትነት እድሜዋን በሮም ብታሳልፍም በእናቷ በኩል ያለውን የዘር ግንዷን ለማወቅ ወደ አዲስ አበባ መጥታ የአያቶቿን መቃበር ጎብኝታለች። "ሶማሊያዊያን ሶማሊያዊት ነሽ ይሉኛል፣ ኢትዮጵያውያንም ኢትዮጵያዊት ነሽ፤ ዓይኖችሽ ይናገራሉ ይሉኛል። ጣልያኖችም የራሳቸው ያደርጉኛል። እኔ ግን ሦስቱም ነኝ" ትላለች። • “እዚህ ደረጃ የደረስኩት በእርሷ ብርታት ነው” አርቲስት ደመረ ለገሰ "በውስጤ ከኢትዮጵያ ጋር የሚያገናኘኝን ነገር ለማግኘት በጣም እጓጓ ነበር። አማርኛ አለመቻሌ ትልቅ ቁስል ፈጥሮብኛል ... በተለይ ኢትዮጵያን ስጎበኝ 'ፈረንጅ' እያሉ የሚከተሉኝ ልጆች የኢትዮጵያዊነቴን ስሜት የተገፈፈኩ ያህል እንዲሰማኝ አድርጓል" የምትለው ሳባ የማንነቷን ፍለጋ ጉዞዋ በሙዚቃ በኩል እንደተያያዘችው ታስረዳለች። • ከድምፃዊት ቤቲ ጂ እና ቸሊና ጀርባ ሳባ አንግላና "አበበች" አበበች የሳባ ሙዚቃ አልበም መጠሪያ ነው። ነገር ግን ወ/ሮ አበበች ወደ ሳባ ሕይወት እንዲሁ የተከሰቱ አልፎ ሂያጅ መንገደኛ ሳይሆኑ አያቷ ናቸው። ከኢትዮጵያ ጋር በጥብቅ ገመድ ያስተሳሰሯት፤ የማነሽ? የከየት ነሽ? ጥያቄዎች መልሷ ናቸው። "አያቴ አበበች ነበር ስሟ" ትላለች ሳባ ስለእርሳቸው ማስረዳት ስትጀምር፤ "በእርሷም በኩል ነው የኢትዮጵያዊነቴ ግንድ የተገለጠልኝ" በማለትም የመጨረሻውን የሙዚቃ አልበሟን በእዚሁ ምክንያት በእርሳቸው ስም "አበበች" ብላ እንደሰየመችው ትናገራለች። ወ/ሮ አበበች ለአውሮፓያውያን ወግኖ በነበረ የሶማልያ ወታደር እንደ ምርኮኛ ወደ ሶማልያ ተወስደው እንደነበር ሳባ ትተቅሳለች። "ስለእርሷ በሙዚቃዬ ማውራቴ ደግሞ ስሬ ምን ያህል ኢትዮጵያዊ እንደሆነ የማመላክትበት ነው" ትላለች ሳባ። ሙዚቃዋን በኢትዮጵያ ፔንታቶኒክ ስኬል፣ በአምባሰልና በትዝታ ቅኝት የምትጫወትበትም ምክንያት ይኸው እንደሆነ ታስረዳለች። • አውታር - አዲስ የሙዚቃ መሸጫ አማራጭ በሙዚቃዋም በትዝታ ጎዳና በማንነትን ፍለጋ አቀበት እየተጓዘች፣ የሚያደምጧትንም ጭምር ጉዞዋን ተቀላቅለው አብረው እንዲነጉዱ ታደርጋለች። ሳባ አብዛኞቹ ሥራዎቿ እራስን ከመፈለግ ጋር የተያያዙ ናቸው። ማንነቷ በሙዚቃ ሥራዎቿ በግልጽ የሚንፀባረቀው ሳባ፣ በአራት የተለያዩ ቋንቋዎች ታንጎራጉራለች። ሶማልኛ፣ አማርኛ፣ ጣልያንኛና እንግሊዘኛ ሙዚቃዎቿን ያቀረበችባቸው ቋንቋዎች ናቸው። ይህን በማድረጓም ማንነቷን በደንብ እንደገለፀች ይሰማታል። አራቱንም ቋንቋዎች እንደ ተወላጆቹ እንደልብ አፏ ላይ ባታሾራቸውም መኮላተፏ ግን የመሳሳቷ ሳይሆን የውህድ ማንነቷ ውጤት መሆኑን ትናገራለች። "መኮላተፌም ሆነ መሳሳቴ ...የማንነቴ አካል ስለሆነ አላፍርበትም።" • 'ኢትዮጵያዊነት' ከጄሰን ድሩሎ ጀርባ ያለው ቡድን "የሁሉም ሰው ማንነት አንድ ነገር ብቻ ሊሆን አይችልም" የምትለው ሳባ በምዕራቡ ዓለም እየታዩ ያሉት ስደተኞችን ወደ ሀገራቱ እንዳይገቡ የመከላከል እርምጃን ታወግዛለች። ምክንያቱስ ስትባል "ውበታችን የሚጎላው እንደዚያ ስለሆነ ነው" በማለት "ምንም ልዩነቶች ቢኖሩ የሰው ልጅ አንድ ነው" በማለት ሃሳቧን ታጠናክራለች። መድረክ ላይ በምትሆንበት ጊዜ ፊት ለፊቷ ያለው ታዳሚዎች ኢትዮጵያዊም ሆኑ ጣልያናዊ አልያም ሶማሊያዊ መልዕክቷን ስለሚረዱ በጣም ዕድለኛ እንደሆነች ትገልፃለች። "ምንጊዜም ችግር የሚገጥመኝ አንዱን ባህል ብቻ እንዳንፀባርቅ ሲጠብቁ ነው... ለምን? አንድ ነገር ብቻ አይደለሁም" በማለት በሁሉም የሙዚቃ ሥራዋ ሦስቱንም ቋንቋና ባህልን እያደባለቀች የምትሰራበት ምክንያቷን ታስረዳለች። "ከእኔ በኋላ ለሚመጡት ሙዚቀኞች በር እንደከፈትኩ ያህል ይሰማኛል። ምክንያቱም መንፈሳዊነቴን፣ ባህሎቼንና ማንነቴን በአንድ ላይ በሙዚቃዬ ለመግለፅና ተቀባይነት ለማግኘት ብዙ ውጣ ውረዶችን አይቻለሁ። አሁን ግን የቅይጥነቱን መንፈስና ትርጉም ብዙዎች የተረዱት ይመስለኛል" የምትለው ሳባ የአቅሟን በመሥራት ለመጪው ትውልድ አሻራ ብቻ ሳይሆን መንገድ እንደምትጠርግም ተስፋ ታደርጋለች።
news-53977507
https://www.bbc.com/amharic/news-53977507
የቻይናና አውስትራሊያ ውጥረት፡ አውስትራሊያዊቷ ዜና አንባቢ ቻይና ውስጥ ታገተች
በቻይና እና አውስትራሊያ መካከል ያለው ውጥረት እያየለ መጥቷል።
የቻይና ባለሥልጣናት የአውስትራሊያ ዜግነት ያላትን አንዲት ዜና አንባቢ በቁጥጥር ሥር አውለዋል። የአውስትራሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳለው ለቻይና መንግሥት ቴሌቪዥን ጣቢያ ሲጂቲኤን የምትሠራው ቼንግ ሌይ በቁጥጥር ሥር የዋለችው ከሁለት ሳምንታት በፊት ነው። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማሪስ ፔይን እንዳሉት በቁጥጥር ሥር ከዋለችው አውስትራሊያዊት ጋዜጠኛ ጋር የቪድዮ ስልክ ልውውጥ ተደርጓል። የአውስትራሊያ መንግሥት ቻይና የሚገኙ ዜጎቹ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ያሳሰበው ባለፈው ሐምሌ ነው። አውስትራሊያና ቻይና በተለይ ከቅርብ ወራት ወዲህ ግንኙነታቸው እየሻከረ መጥቷል። አውስትራሊያ የኮሮናቫይረስ መነሾ በይፋ ይጣራ ማለቷን ተከትሎ ነው ቻይና የተቆጣችው። ቻይና ለሁለተኛ ጊዜ ከአውስትራሊያ የሚመጡ ወይኖች ላይ ምርመራ ይካሄድ ብላ አዛለች። ባለፈው ሳምንት የአውስትራሊያ መንግሥት ክልሎች ከውጭ ሃገራት ጋር ያላቸውን ግንኙት ፌዴራል መንግሥቱ ማቋረጥ እንዲችል የሚያዝ ሕግ ለማውጣት እያቀደ መሆኑን ይፋ አድርጓል። ቼንግ በቁጥጥር ሥር የዋለችው 'የሃገር ድህንነትን አደጋ ላይ በመጣል' በሚል ክስ እንደሆነ የአውስትራሊያው ኤቢሲ ዘግቧል። ቻይና ውስጥ በዚህ ክስ በቁጥጥር ሥር የዋለ ሰው እስከ ስድስት ወራት ድረስ ምርመር ሊደርግለትና ከእሥር ላይወጣ ይችላል። ነግር ግን ቻይና በጉዳዩ ላይ ገና ማብራሪያ አልሰጠችም። የአውስትራሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስለጋዜጠኛዋ በቁጥጥር ሥር መዋል መረጃ የተሰጠው ከሁለት ሳምንታት በፊት ነው። ነባሯ ዜና አንባቢ አውስትራሊያ የሚኖሩ ሁለት ልጀች አሏት። ኤቢሲ ኒውስ እንደዘገበው ቤተበሶቿና ወዳጅ ዘመዶቿ ከጥቂት ሳምንታት ወዲህ ስለ ቼንግ የሰሙት ምንም ነገር የለም። ቤተሰቦቿ ከአውስትራሊያ መንግሥት ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ጋር በቅርበት እየተነጋገሩ መሆኑን አሳውቀዋል። ቼንግ ለሲጂቲኤን ለስምንት ዓመታት ያገለገለች ሲሆን 'ግሎባል ቢዝነስ' በተሰኘው የቴሌቪዥን ሥርጭት ላይ አቅራቢ ሆና ትሰራለች። ጋዜጠኛዋ በቻይና መንግሥት ቁጥጥር ሥር ከዋለች ወዲህ ከቴሌቪዥን ጣቢያው ድረ-ገፅ ላይ ስለሷና ሥራዎቿ የሚያትተው ገፅ መጥፋቱ ተነግሯል። ቻይና ባለፈው ዓመት ጥር ላይ የቻይናና አውስትራሊያ ዜግነት ያለው ያንግ ሄንገጁን የተባለ ፀሐፊ ብሔራዊ ደህንነትን አደጋ ላይ ይጥላል በማለት በቁጥጥር ሥር ማዋሏ አይዘነጋም።
news-49007336
https://www.bbc.com/amharic/news-49007336
ደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል፡ 'ከሕግ ውጪ' የተዋሃዱት አምስቱ ክልሎች
ወታደራዊው መንግሥት ከስልጣን ከተወገደ በኋላ የኢትዮጵያ አስተዳደራዊ መዋቅር መሰረታዊ ለውጥ ተደርጎበት በዋናነት ቋንቋን መሰረት ባደረገ ሁኔታ የአስተዳደር ክልሎች ተመስርተዋል።
ከሰማኒያ በላይ የተለያየ ሐይማኖት፣ ቋንቋና ባሕል ያላቸው ሕዝቦችን መብትና ጥቅም ያስከብራል በሚል ዋና ዋና በሚባሉትና በርካታ የሕዝብ ቁጥር ባላቸው ብሔሮች ዙሪያ ውስጣዊ የአስተዳደር ሥርዓቱን ማዋቀር በወቅቱ የሃገሪቱን የመሪነት ሚና የተረከቡት ኃይሎች ዋነኛ ሥራ ነበር። በዚህም ለዘመናት ኤርትራን ጨምሮ በ14 ክፍላተ ሃገራት የተዋቀረው የአስተዳደር ሥርዓት ከ1983 ዓ.ም ወዲህ በአዲሱ ቋንቋን መሰረት ባደረገ የፌደራል አስተዳደራዊ አወቃቀር አንዲተካ ተደርጓል። • በሲዳማ ክልልነት ጉዳይ ህዝበ ውሳኔ እንዲካሄድ የምርጫ ቦርድ ወሰነ • የደቡብ ክልል፡ ውስብስቡ የዐብይ ፈተና ይህም የሆነው ሃገሪቱ የምትተዳደርበት ሕገ መንግሥት ከመጽደቁ በፊት በተቋቋመው ጊዜያዊ የሽግግር መንግሥት አማካይነት ነበር። የወቅቱ አከላለል 14 ክልሎች እንዲፈጠሩ ያደረገ ሲሆን አዲስ አበባም በክልል ደረጃ የተዋቀረች ከተማ ነበረች። በሽግግሩ ወቅት በአዋጅ ቁጥር 7/1984 መሰረት አዲስ የክልል አወቃቀር ሲታወጅ በሂደቱ ውስጥ ተሳታፊ እንደነበሩ የሚናገሩትና በወቅቱ የምክር ቤት አባል የነበሩት ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ከሁለት ዓመታት በኋላ አሁን በደቡብ ክልል ውስጥ የሚገኙ አምስት አካባቢዎች በሕገ ወጥ መንገድ ተዋህደው አንድ ክልል እንዲመሰርቱ መደረጉን ያስታውሳሉ። በሽግግሩ ጊዜ የተዋቀረው አዲሱ የአስተዳደር ሥርዓት በዋናነት በቁጥርና በአሰፋፈር ተለቅ ተለቅ የሚሉትን ማዕከል አድርጎ የተካለለ ቢሆንም የደቡብ ክልል ግን 56 የሚደርሱ ብሔር፣ ብሔረሰቦችን በመያዝ ከሌሎቹ ክልሎች በተለየ የተዋቀረ ነው። በወቅቱ አዲስ አበባም ራሷን የቻለች ክልል በመሆን የፌደራል መንግሥቱ አካል የነበረች ሲሆን በኋላ ላይ ይህ ተቀይሮ በቻርተር የምትተዳደር የከተማ አስተዳደር እንድትሆን ተደርጓል፤ ድሬዳዋም በተመሳሳይ የአስተዳደር ሁኔታ ውስጥ ትገኛለች። • ለሲዳማ ክልልነት 'ይሁንታ ተሰጠ' በሚል በርካቶች ደስታቸውን እየገለጹ ነው በወቅቱ ክልሎቹ ሲዋቀሩ ቋንቋንና ማንነትን መሰረት አድርገው ሲሆን አሁን ከያዙት ስያሜ በተለየ በቁጥር ነበር የሚታወቁት። ቁጥሩ ከትግራይ ክልል አንድ ብሎ ይጀምርና ደቡብ ተብሎ በአንድ እንዲጠቃለል የሆነው ክልል ከሰባት እስከ 11 የሚደርሱትን ክልሎች በውስጡ እንዲይዝ ተደርጎ አምስት ክልሎችን ነበሩት ይላሉ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ። እንደእርሳቸው አባባል በአከላሉ ሂደት ወቅት አሁን የደቡብ ኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ተብሎ ወደ አንድ የተጠቃለለው በአምስት ዋና ዋና ክልሎች ተዋቅሮ የተለያዩ ሕዝቦች የሚኖሩባቸው ክልሎች እንዲሆኑ ተደርገው ነበር የተደራጁት። በዚህም መሰረት በጊዜያዊው የሽግግሩ መንግሥቱ ዘመን እነዚህ አምስት ክልሎች እንደ ክልል ለሁለት ዓመት ራሳቸውን የቻሉ ክልሎች በመሆን ሲተዳደሩ ቆይተዋል። ብዙም ያልዘለቀው የእነዚህ ክልሎች እድሜ ማዕከላዊው የሽግግር መንግሥት ክልሎቹ የተዋቀሩበትን አዋጅ 7/1984ን በመጣስ አምስቱን ክልሎች በአንድ ላይ እንዲዋሃዱ የሚያደርግ ትዕዛዝ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽህፈት ቤት እንደወጣና በዚህ መሰረትም ክልሎቹ ከሁለት ዓመት በላይ ህልውና እንዳይኖራቸው ተደርጎ በአንድ ክልል እንዲጠቃለሉ መደረጉን ፕሮፌሰር በየነ ይገልጻሉ። "ለዚህ ምክንያቱ እነዚህ ክልሎችን በአንድ ክልል ስር የማካተቱ እርምጃ ለማዕከላዊው መንግሥት ጥቅምና ቁጥጥር አመቺነት ነው" ይላሉ ፕሮፌሰሩ፤ አክለውም ድርጊቱን ተቃውመው ውዝግብ ውስጥ መግባታቸውንና ከሽግግሩ ምክር ቤት እስከመባረር እንደደረሱ ይናገራሉ። ያስከተለው ጽዕኖ አምስቱን ክልሎች በአንድ ያማከለው የመንግሥት እርምጃ የተለያዩ ቦታዎች የየራሳቸው የሆነ የልማት ማዕከላት እንዳይኖራቸው እንደደረገ ይገላጻሉ ፕሮፌሰር በየነ። ይህም በተለያዩ ስፍራዎች ለሚኖር የሥራ ፈጠራና ለኢኮኖሚያዊ እድገት መፋጠን አስተዋጽኦ ይኖረው እንደነበር ያምናሉ። "ክልሎቹ በነበሩበት መተዳደር ቢችሉ ኖሮ አሁን ሐዋሳ ላይ የተከማቸው ሐብት በተለያዩ ቦታዎች ላይ ጥቅም ይሰጥ ነበር። በዚህም ደቡብ ውስጥ በእድገት ጎላ ብላ የምትታየው የሐዋሳ ከተማ ብቻ ሆናለች" የሚሉት ፕሮፌሰር በየነ፤ ነገር ግን አምስቱ ክልሎች በነበሩበት ቢቀጥሉ ኖሮ በርካታ ሊያድጉ የሚችሉ አካባቢዎችን መፍጠር ይቻል እንደነበር ያምናሉ። ነገር ግን ኢህአዴግ ክልሎቹን ወደ አንድ ለማምጣት በወሰደው የዘፈቀደ እርምጃ በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች የልማት ማዕከሎች እንዳይፈጠሩ እንቅፋት በመሆን ክልሉም ሕዝቡም ተጎድቷል። • ያልተነገረለት የኮንሶ ጥያቄ ከሃብት አንጻር ለተቀሩት የክልሉ አካባቢዎች በፍትሐዊነት ሊከፋፈልና ሊዳረስ የሚገባው ሐብት በሐዋሳ ላይ ብቻ እንዲፈስና እንዲከማች በማድረግ ሌሎቹ አካባቢዎች በተመጣጣኝ ሁኔታ እንዳያድጉ እንቅፋት መሆኑን ይናገራሉ። በደቡብ ክልል ውስጥ የቦታ ይገባኛል እንዲሁም ክልል እና ዞን ለመሆን በርካታ ጥያቄዎች በተለያዩ የክልሉ ማኅበረሰብ አባላት ሲቀርቡና በዚህም ሽኩቻና ውዝግብ የነበረ መሆኑን የሚናገሩት ፕሮፌሰር በየነ፤ የእነዚህ ምክንያቶች ደግሞ የመልካም አስተዳደርና የሕግ የበላይነት መጥፋት ያመጣው እንደሆነ ያምናሉ። ነገር ግን ይህ "ሁሉም ጋር ያለ መናቆር ነው" ደቡብ ውስጥ እነዚህ አምስት ክልሎች በአንድ በመዋቀራቸው ከሌሎች ክልሎች ከታዩት ችግሮች የተለየ ነገር ገጥሞታል ብለው የሚጠቅሱት እንደሌለ ይናገራሉ። ለፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ የቀረቡት ክልል የመሆን ጥያቄዎች ምላሽ ቢያገኙ በሃገሪቱ አንድነት ላይ የሚፈጥሩት ውጤት የለም። እንደ እርሳቸው አተያይ ዋነኛው ተግዳሮት የሚሆነው "በእነዚህ ቦታዎች ላይ ከሚያጋጥመው ኢኮኖሚያዊ ውስንነት ውጪ ክልልም ሆኑ ዞን፣ በኢትዮጵያ ማዕቀፍ ውስጥ እስካሉ ድረስ ከስም ለውጥ ባሻገር የሚኖር ጉልህ ለውጥ የለም።" ከአሉታዊው ውጤት ባሻገር ከተጠቀሱት ክልሉ ውስጥ የሚታዩ ውስጣዊ መሻኮቶችና መገፋፋቶች ባሻገር ከኢትዮጵያዊነትና ከኢትዮጵያ ህልውና አንጻር ሲታይ ሰፊ ቁጥር ያላቸው ሕዝቦች በአንድ ክልል ውስጥ መተዳደር እንደሚችሉ ትልቅ ማሳያ ሊሆን ይችላል ይላሉ ደቡብ ክልልን። "ለዚህም ነው ደቡብ ሲነሳ ዘወትር ትንሿ ኢትዮጵያ እስከመባል የተደረሰው" ሲሉ ሀሳባቸውን ያጠናክራሉ። የክልሎቹ መዋሃድና ውጤቱ ከሁለት አስርት ዓመታት በፊት የተወሰነው ክልሎቹን ያለሕዝቡ ፈቃድ የመቀላቀል ውሳኔ በየጊዜው በተለያዩ ደረጃዎች ራስን የማስተዳደር ጥያቄዎች ደጋግመው እንዲከሰቱ አድርጓል። አሁንም አስር የሚደርሱ የክልሉ አካባቢዎች ክልል እንሁን የሚል ጥያቄን ይዘው ምላሽ እየጠበቁ ነው። ፕሮፌሰር በየነም "ሕግን በመጣስ አምሰቱን ክልሎች ወደ አንድ ሲያጠቃልሏቸው ፖለቲካዊ ውሳኔ ነበር ። ይህም ለዛሬው ጥያቄና ችግር ዋነኛ ምክንያት ነው" በማለት ያምናሉ። ሌሎችም አካባቢዎች ክልል የመሆን ጥያቄ አንስተዋል፤ ይህ ተግባራዊ ቢሆን ትናንሽ ክልሎች ከመመስረት ባሻገር በኢትዮጵያ ሃገራዊ ህልውና ላይ ተጽእኖ ይኖራቸዋል ብለው አያስቡም። በርካቶች ክልል የመሆን ጥያቄን ያቀረቡት አካባቢዎች ሁሉም አወንታዊ ምላሽ ቢያገኙ በሚጠበቅባቸው ደረጃ ኃላፊነታቸውን መወጣት ይችላሉ ወይ የሚል ጥያቄ ይነሳል። ፕሮፌሰር በየነም "እነዚህ አዲስ ክልል የሚሆኑት አካባቢዎች ከውስጣቸው በቂ ሐብትና ገቢ ማመንጨት ይችላሉ ወይ? በራሳቸውስ በቂ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ማድረግና መተዳደር ይችላሉ ወይ? የሚሉና ሌሎች ጥያቄዎች በቅድሚያ መመለስ አለባቸው።" ባይ ናቸው። ከሌሎች የሃገሪቱ ክልሎች በተለየ በርካታ የክልል እንሁን ጥያቄዎች የቀረቡለት የደቡብ ክልል ምላሽ ለመስጠት የተቸገረ ይመስላል። የክልሉ ገዢ ፓርቲም ከመቀመጫው ሐዋሳ ርቆ አዲስ አበባ ውስጥ በጥያቄዎቹ ዙሪያ ለቀናት ተወያይቶ ያወጣው መግለጫ ተጨባጭ ነገርን አላቀረበም። • ያልጠገገው የሀዋሳ ቁስል ጥያቄዎቹ አዎንታዊ ምላሽን አግኝተው ቢያንስ አንድ ክልል መመስረቱ እንደማይቀር የበርካቶች እምነት ሲሆን ይህ ውጤትም በደቡብ ክልል ላይ በተለይ በዋና ከተማዋ ሐዋሳ ላይ የራሱ የሆነ ውጤት ሊኖረው እንደሚችል ይሰጋሉ። ከዚህ አንጻርም አዳዲስ የሚከሰቱ የቦታ ይገባኛልና የድንበር ጥያቄዎች በሚፈጠሩትና በነባር ክልሎች መካከል ሊከሰቱ እንደሚችሉ አንዳንዶች ቢሰጉም ፕሮፌሰር በየነ ግን "የሚባሉት ውዝግቦችና ግጭቶች አሁንም ያሉ ናቸው ነገር ግን በሰከነና በተረጋጋ ሁኔታ በሕግ አግባብ መፍታት ብቻ ነው የሚያስፈልገው" በማለት ከአዳዲስ ጥያቄዎች ባሻገርም የነበሩ ጥያቄዎች ወደ ፊት መምጣታቸው አይቀርም ይላሉ።

Dataset Card for "XL-Sum"

Dataset Summary

We present XLSum, a comprehensive and diverse dataset comprising 1.35 million professionally annotated article-summary pairs from BBC, extracted using a set of carefully designed heuristics. The dataset covers 45 languages ranging from low to high-resource, for many of which no public dataset is currently available. XL-Sum is highly abstractive, concise, and of high quality, as indicated by human and intrinsic evaluation.

Supported Tasks and Leaderboards

More information needed

Languages

  • amharic
  • arabic
  • azerbaijani
  • bengali
  • burmese
  • chinese_simplified
  • chinese_traditional
  • english
  • french
  • gujarati
  • hausa
  • hindi
  • igbo
  • indonesian
  • japanese
  • kirundi
  • korean
  • kyrgyz
  • marathi
  • nepali
  • oromo
  • pashto
  • persian
  • pidgin
  • portuguese
  • punjabi
  • russian
  • scottish_gaelic
  • serbian_cyrillic
  • serbian_latin
  • sinhala
  • somali
  • spanish
  • swahili
  • tamil
  • telugu
  • thai
  • tigrinya
  • turkish
  • ukrainian
  • urdu
  • uzbek
  • vietnamese
  • welsh
  • yoruba

Dataset Structure

Data Instances

One example from the English dataset is given below in JSON format.

{
  "id": "technology-17657859",
  "url": "https://www.bbc.com/news/technology-17657859",
  "title": "Yahoo files e-book advert system patent applications",
  "summary": "Yahoo has signalled it is investigating e-book adverts as a way to stimulate its earnings.",
  "text": "Yahoo's patents suggest users could weigh the type of ads against the sizes of discount before purchase. It says in two US patent applications that ads for digital book readers have been \"less than optimal\" to date. The filings suggest that users could be offered titles at a variety of prices depending on the ads' prominence They add that the products shown could be determined by the type of book being read, or even the contents of a specific chapter, phrase or word. The paperwork was published by the US Patent and Trademark Office late last week and relates to work carried out at the firm's headquarters in Sunnyvale, California. \"Greater levels of advertising, which may be more valuable to an advertiser and potentially more distracting to an e-book reader, may warrant higher discounts,\" it states. Free books It suggests users could be offered ads as hyperlinks based within the book's text, in-laid text or even \"dynamic content\" such as video. Another idea suggests boxes at the bottom of a page could trail later chapters or quotes saying \"brought to you by Company A\". It adds that the more willing the customer is to see the ads, the greater the potential discount. \"Higher frequencies... may even be great enough to allow the e-book to be obtained for free,\" it states. The authors write that the type of ad could influence the value of the discount, with \"lower class advertising... such as teeth whitener advertisements\" offering a cheaper price than \"high\" or \"middle class\" adverts, for things like pizza. The inventors also suggest that ads could be linked to the mood or emotional state the reader is in as a they progress through a title. For example, they say if characters fall in love or show affection during a chapter, then ads for flowers or entertainment could be triggered. The patents also suggest this could applied to children's books - giving the Tom Hanks animated film Polar Express as an example. It says a scene showing a waiter giving the protagonists hot drinks \"may be an excellent opportunity to show an advertisement for hot cocoa, or a branded chocolate bar\". Another example states: \"If the setting includes young characters, a Coke advertisement could be provided, inviting the reader to enjoy a glass of Coke with his book, and providing a graphic of a cool glass.\" It adds that such targeting could be further enhanced by taking account of previous titles the owner has bought. 'Advertising-free zone' At present, several Amazon and Kobo e-book readers offer full-screen adverts when the device is switched off and show smaller ads on their menu screens, but the main text of the titles remains free of marketing. Yahoo does not currently provide ads to these devices, and a move into the area could boost its shrinking revenues. However, Philip Jones, deputy editor of the Bookseller magazine, said that the internet firm might struggle to get some of its ideas adopted. \"This has been mooted before and was fairly well decried,\" he said. \"Perhaps in a limited context it could work if the merchandise was strongly related to the title and was kept away from the text. \"But readers - particularly parents - like the fact that reading is an advertising-free zone. Authors would also want something to say about ads interrupting their narrative flow.\""
}

Data Fields

  • 'id': A string representing the article ID.
  • 'url': A string representing the article URL.
  • 'title': A string containing the article title.
  • 'summary': A string containing the article summary.
  • 'text' : A string containing the article text.

Data Splits

We used a 80%-10%-10% split for all languages with a few exceptions. English was split 93%-3.5%-3.5% for the evaluation set size to resemble that of CNN/DM and XSum; Scottish Gaelic, Kyrgyz and Sinhala had relatively fewer samples, their evaluation sets were increased to 500 samples for more reliable evaluation. Same articles were used for evaluation in the two variants of Chinese and Serbian to prevent data leakage in multilingual training. Individual dataset download links with train-dev-test example counts are given below:

Language ISO 639-1 Code BBC subdomain(s) Train Dev Test Total
Amharic am https://www.bbc.com/amharic 5761 719 719 7199
Arabic ar https://www.bbc.com/arabic 37519 4689 4689 46897
Azerbaijani az https://www.bbc.com/azeri 6478 809 809 8096
Bengali bn https://www.bbc.com/bengali 8102 1012 1012 10126
Burmese my https://www.bbc.com/burmese 4569 570 570 5709
Chinese (Simplified) zh-CN https://www.bbc.com/ukchina/simp, https://www.bbc.com/zhongwen/simp 37362 4670 4670 46702
Chinese (Traditional) zh-TW https://www.bbc.com/ukchina/trad, https://www.bbc.com/zhongwen/trad 37373 4670 4670 46713
English en https://www.bbc.com/english, https://www.bbc.com/sinhala * 306522 11535 11535 329592
French fr https://www.bbc.com/afrique 8697 1086 1086 10869
Gujarati gu https://www.bbc.com/gujarati 9119 1139 1139 11397
Hausa ha https://www.bbc.com/hausa 6418 802 802 8022
Hindi hi https://www.bbc.com/hindi 70778 8847 8847 88472
Igbo ig https://www.bbc.com/igbo 4183 522 522 5227
Indonesian id https://www.bbc.com/indonesia 38242 4780 4780 47802
Japanese ja https://www.bbc.com/japanese 7113 889 889 8891
Kirundi rn https://www.bbc.com/gahuza 5746 718 718 7182
Korean ko https://www.bbc.com/korean 4407 550 550 5507
Kyrgyz ky https://www.bbc.com/kyrgyz 2266 500 500 3266
Marathi mr https://www.bbc.com/marathi 10903 1362 1362 13627
Nepali np https://www.bbc.com/nepali 5808 725 725 7258
Oromo om https://www.bbc.com/afaanoromoo 6063 757 757 7577
Pashto ps https://www.bbc.com/pashto 14353 1794 1794 17941
Persian fa https://www.bbc.com/persian 47251 5906 5906 59063
Pidgin** n/a https://www.bbc.com/pidgin 9208 1151 1151 11510
Portuguese pt https://www.bbc.com/portuguese 57402 7175 7175 71752
Punjabi pa https://www.bbc.com/punjabi 8215 1026 1026 10267
Russian ru https://www.bbc.com/russian, https://www.bbc.com/ukrainian * 62243 7780 7780 77803
Scottish Gaelic gd https://www.bbc.com/naidheachdan 1313 500 500 2313
Serbian (Cyrillic) sr https://www.bbc.com/serbian/cyr 7275 909 909 9093
Serbian (Latin) sr https://www.bbc.com/serbian/lat 7276 909 909 9094
Sinhala si https://www.bbc.com/sinhala 3249 500 500 4249
Somali so https://www.bbc.com/somali 5962 745 745 7452
Spanish es https://www.bbc.com/mundo 38110 4763 4763 47636
Swahili sw https://www.bbc.com/swahili 7898 987 987 9872
Tamil ta https://www.bbc.com/tamil 16222 2027 2027 20276
Telugu te https://www.bbc.com/telugu 10421 1302 1302 13025
Thai th https://www.bbc.com/thai 6616 826 826 8268
Tigrinya ti https://www.bbc.com/tigrinya 5451 681 681 6813
Turkish tr https://www.bbc.com/turkce 27176 3397 3397 33970
Ukrainian uk https://www.bbc.com/ukrainian 43201 5399 5399 53999
Urdu ur https://www.bbc.com/urdu 67665 8458 8458 84581
Uzbek uz https://www.bbc.com/uzbek 4728 590 590 5908
Vietnamese vi https://www.bbc.com/vietnamese 32111 4013 4013 40137
Welsh cy https://www.bbc.com/cymrufyw 9732 1216 1216 12164
Yoruba yo https://www.bbc.com/yoruba 6350 793 793 7936

* A lot of articles in BBC Sinhala and BBC Ukrainian were written in English and Russian respectively. They were identified using Fasttext and moved accordingly.

** West African Pidgin English

Dataset Creation

Curation Rationale

More information needed

Source Data

BBC News

Initial Data Collection and Normalization

Detailed in the paper

Who are the source language producers?

Detailed in the paper

Annotations

Detailed in the paper

Annotation process

Detailed in the paper

Who are the annotators?

Detailed in the paper

Personal and Sensitive Information

More information needed

Considerations for Using the Data

Social Impact of Dataset

More information needed

Discussion of Biases

More information needed

Other Known Limitations

More information needed

Additional Information

Dataset Curators

More information needed

Licensing Information

Contents of this repository are restricted to only non-commercial research purposes under the Creative Commons Attribution-NonCommercial-ShareAlike 4.0 International License (CC BY-NC-SA 4.0). Copyright of the dataset contents belongs to the original copyright holders.

Citation Information

If you use any of the datasets, models or code modules, please cite the following paper:

@inproceedings{hasan-etal-2021-xl,
    title = "{XL}-Sum: Large-Scale Multilingual Abstractive Summarization for 44 Languages",
    author = "Hasan, Tahmid  and
      Bhattacharjee, Abhik  and
      Islam, Md. Saiful  and
      Mubasshir, Kazi  and
      Li, Yuan-Fang  and
      Kang, Yong-Bin  and
      Rahman, M. Sohel  and
      Shahriyar, Rifat",
    booktitle = "Findings of the Association for Computational Linguistics: ACL-IJCNLP 2021",
    month = aug,
    year = "2021",
    address = "Online",
    publisher = "Association for Computational Linguistics",
    url = "https://aclanthology.org/2021.findings-acl.413",
    pages = "4693--4703",
}

Contributions

Thanks to @abhik1505040 and @Tahmid for adding this dataset.

Downloads last month
37,992

Models trained or fine-tuned on csebuetnlp/xlsum

Spaces using csebuetnlp/xlsum 2