id
stringlengths
8
14
url
stringlengths
36
42
title
stringlengths
8
90
summary
stringlengths
6
505
text
stringlengths
133
19.2k
news-54430430
https://www.bbc.com/amharic/news-54430430
ሰው ሰራሽ ልህቀት፡ ሰዎች ከርቀት የሚቆጣጠሯት የሱቅ ሰራተኛ ሮቦት
ዓለም በቴክኖሎጂ እየተራቀቀ ነው። በተለይ የሰው ሰራሽ ልህቀት [አርተፊሻል ኢንተለጀንስ] ዘርፍ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል።
The remote-controlled shop assistant አሁን ላይ ሰዎችን ተክተው የሚሰሩ ሮቦቶችን ማየቱ አዲስ አይደለም። በጃፓኗ መዲና ቶክዮ በሚገኝ አንድ አነስተኛ የገበያ ማዕከልም አንዲት ሮቦት ሥራዋን በትጋት እየተወጣች ነው። ሰዎች የሚፈልጓቸውን የመጠጥ አይነቶች ታነሳለች፤ ትሰጣለች፤ በማቀዝቀዣው መደርደሪያ ላይ ታስቀምጣለች። ብቻ ብቻዋን ተፍ ተፍ ትላለች። ሰዎችም ይመጣሉ፤ ይሄዳሉ። የሮቦቷ ሥሪት በጣም የተቀናጀና ራስ ገዝ የመካኒካል ሥራ ይመስላል፤ ግን አይደለም። ሮቦቷ የራሷ አዕምሮ የላትም። እንደ ሰው አታስብም። ሥራዋን የምትወጣው ከብዙ ኪሎ ርቀት ላይ ሆኖ በሚቆጣጠራት ሰው አማካይነት ነው። የሮቦቷን እይታ በሚሰጠው 'በቨርቹዋል ሪያሊቲ' [ምናባዊ እውነታ] መመልከቻ መሳሪያ ማለት ነው። ሮቦቷ የጃፓኑ ቴልኤግዚስታንስ ድርጅት ሥራ ውጤት ናት። 'ሞዴል ቲ' የተሰኘው የሮቦት ዲዛይኑ ሰዎች ከቤታቸው ወይም ከሌላ ሩቅ ቦታ ሆነው የሰዎችን ጉልበት የሚጠይቁ ሥራዎችን እንዲሰሩ የሚያስችል ነው። የድርጅቱ የቦርድ ዳሬክተር ዩቺሮ ሂኮሳካ የሮቦት ሞዴሉ "አምሳለ ሰው" ነው ብለዋል። "ባላችሁበት ሆናችሁ የፈለጋችሁበት ቦታ መሄድ ትችላላችሁ" ብለዋል ዳሬክተሩ፤ የቴክኖሎጂ ሥራው ቴሌሮቦቲክስ ወይም በስልክ የሚሰራ ሮቦት ይባላል። ይህም በሳይንሳዊ ልቦለድ ፊልሞች በሆኑት ሰሮጌትስ እና ሰሊፕ ዲለር ፊልሞች ላይ ተስለው ታይተዋል። በርቀት በመቆጣጠር ቦምብ የሚጥሉ ሮቦቶች ለዘመናት ያሉ ሲሆን ፤ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወቅት ምግብ ለሰዎች ቤት የሚያደርሱ ሮቦቶችን ጨምሮ በቴሌ የሚሰሩ መሳሪያዎች ቀድሞ ከነበረው በይበልጥ እየተሰሩ ነው። ዳሬክተሩ "በእድሜ የገፉ በርካታ ሕዝብ የሚኖርባት ጃፓን፤ አሁን ላይ የሰው ኃይል እጥረት አለባት። በተለይ ደግሞ ዝቅተኛ ገቢ በሚያስገኙ ሥራዎች ላይ ችግሩ ይብሳል" በማለት የፈጠራ ስራው ይህን ሊያቃልል እንደሚችል ተናግረዋል። አካላዊ መገኘትን በሚጠይቁ ሥራዎች ላይ በሺዎች የሚቆጠሩ ሮቦቶችን በማሰማራት በተወሰነ መልኩ ችግሩን መቅረፍ እንደሚቻልም አክለዋል። ይህ ድርጅቶች በርቀት የሚቆጣጠሩ ሰራተኞችን ለመቅጠር ያስችላቸዋል በማለትም ጠቀሜታውን አስረድተዋል። "መጀመሪያ ቶክዮ ሰርቶ ከአስር ደቂቃ በኋላ ደግሞ ሆካይዶ መስራት ይቻላል" ብለዋል። በመኪና አሊያም በባቡር መጓዝ ሳጠበቅብዎት ማለት ነው። ሮቦቶቹን የሚቆጣጠሩት ሰራተኞች በኦንላይን መገበያያ ቦታው በመግባት፣ መስራት የሚፈልጉትን በመምረጥ እና 'ቨርቹዋል ሪያሊቲ' ማዳመጫውን በማድረግ ሮቦቶችን እንዲሰሩ ማንቀሳቀስ ይችላሉ። አንድ ሰው በተለያዩ ቦታዎች ያሉ በርካታ ሮቦቶችን መቆጣጠር ይችላል "ሃሳቡ በተለይ አሁን ባለንበት ወቅት ተስፋ ሰጭ ነው። ምክንያቱም ሰዎች ከሰዎች ጋር ያላቸውን ግንኙነት ስለሚቀንስ ለወረርሽኙ የመጋለጥ እድላቸውን ይቀንሳል" ብለዋል ዳሬክተሩ። ይሁን እንጅ ድርጅቱ ያልፈታቸው ችግሮች መኖራቸውንም ሳይገልፁ አላለፉም። 'ሞዴል ቲ' ሮቦቶች የሰው ያህል በፍጥነት መንቀሳቀስ አይችሉም፤ እንዲሁም የሚቆጣጠረው ሰው የሚያደርው 'ቨርቹዋል ሪያሊቲ' [ ምናባዊ እውነታ] መከታተያውን በተለይ ደግሞ ለረዥም ጊዜ ካደረገውየመፍዘዝና የማጥወልወል ስሜት ሊፈጥር ይችላል። በመሆኑም እርሳቸውና ባልደረቦቻቸው ለዚህ ችግር መፍትሔ ለማፈላለግ እየሰሩ መሆናቸውን ዳሬክተሩ ተናግረዋል።
news-52703605
https://www.bbc.com/amharic/news-52703605
"ፖሊስ በጓደኛዬ ላይ እንዲተኩስ የሚያደርግ አንድም ምክንያት አልነበረም" የሟች ሽሻይ ጓደኛ
በትግራይ ክልል፤ በመቀለ ከተማ 05 ቀበሌ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ተሰብስበው የነበሩ ወጣቶችን ለመበተን በተደረገው ጥረት ግጭት ተከስቶ አንድ ወጣት በፖሊስ አባል መደገሉን የከተማው ፖሊስ ጽህፈት ቤት ለቢቢሲ ገለጸ።
ፖሊስ እንዳለው ከሆነ የቫይረሱን ሥርጭት ለመግታት መጠጥ ቤቶች ዝግ መሆናቸውን ተከትሎ ወጣቶች 05 ቀበሌ በተባለው አካባቢ በአንድ ላይ ተሰባሰበው እየጠጡ ነው የሚል መረጃ እንደደረሰው አስታውቋል። በጥቆማው መሠረት ፖሊስ ወደተባለበት ሥፍራ ተሰማርቶ ወጣቶቹ እንዲበተኑ ለማድረግ ሲጥር፤ በተፈጠረ ግጭት የአንድ ሰው ህይወት አልፏል ብሏል። ከዚህ በተጨማሪም በሁለት ወጣቶች ላይ ጉዳት መድረሱ ተነግሯል። በጠፋው ህይወት የተጠረጠረው ፖሊስም በቁጥጥር ሥር መዋሉን የከተማው ፖሊስ ለቢቢሲ አስታውቋል። ፖሊስ በሟች ሽሻይ ኪሮስ ላይ እንዲተኩስ የሚያደርግ አንድም ምክንያት እንዳልነበረ ጓደኛው ለቢቢሲ ተናግሯል። «በሰፈራችን ቁጭ ብለን ስንጫወት ነበር። ከዚያ ሁለት ፖሊሶች መጡ ሁለተኛው ፖሊስ ብረት ይዞ ነበር። ምን እያደረጋቹ ነው? አለን እሁድ ስለሆነ እየተጫወትን ነው አልነው። ከዛ ወደ ኮምዩኒቲ ፖሊስ እንሂድ አለን። እኛም እዚሁ አናግረን አልነው። ከዛ ሁለተኛው ፖሊስ ምንድነው ብሎ ጥይቱን ተቀበለው እና ማቹ ጓደኛችን ምን ሆነህ ነው ሲለው አንተማ አቃጥለሃለው በማለት ተኮሰበት።» የ23 አመቱ ሽሻይ ከልጅነቱ ጀምሮ ብረታ ብረት እየሠራ ቤተሰቦቹን ያስተዳድር እንደነበር ጓደኛው ይናገራል። የወጣቱ የቀብር ስነ ስርአት ዛሬ ጠዋት በመቐለ ከተማ በገብረመንፈስቅዱስ ቤተክርስትያን ተፈፅሟል። የአካባቢው ወጣቶች ከቀብር በኋላ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ተዘጋጅተው እንደነበር ነገር ግን በኮሮናቫይረስ ምክንያት ሀሳባቸውን ቀይረው ለአካባቢው አስተዳደር ሁኔታውን እንዳሳወቁ ይናገራሉ። ሟች ወጣት ሺሻይ ኪሮስ በግራ በኩል በሚታየው ሥፍራ ከጓደኛው ጋር ቁጭ ብሎ ነበር ይህንን ግድያ የፈፀመው ፖሊስ ከቀበሌ 05 ዓይደር ወደሚባል አካባቢ በማምለጥ በአካባቢው በአንድ ህንፃ ቢደበቅም በዚህ ድርጊት የተቆጣ ህዝብ ህንፃውን ከቦት ነበር። ሆኖም የፖሊስ ኃላፊዎች እና ልዩ ሃይል ሰራዊት አካባቢውን ተቆጣጥረውታል። የመቀለ ከተማ የወንጀል መከላከያ እና ማጣርያ ፅህፈት ቤት ኮማንደር አንድነት ለገሰ፤ ግድያውን የፈፀመው ፖሊስ በቁጥጥር ስር እንደዋለ ተናግረዋል። ከዚያ በኋላ በድርጊቱ የተበሳጩ ወጣቶች ወደ ኮሚዩኒቲ ፖሊስ ፅህፈት ቤት ቀጠና ራህዋ በመሄድ ከፀጥታ ሃይሎች ጋር ተጋጭተዋል። ይህንን ተከትሎም ሁለት ወጣቶች ከፀጥታ አካላት በተተኮሶባቸው ጥይት ጉዳት ደርሶባቸዋል። የተጎዱት ወጣቶች፡ በአሁኑ ሰአት በመቀለ ከተማ በሚገኘው ዓይደር ከፍተኛ ሆስፒታል ሕክምና እያገኙ ነው። አንደኛው ወጣት እጁ ላይ የተመታ ሲሆን ሁለተኛው ወጣት ግን ጎኑን ስለተመታ ቀዶ ህክምና ተደርጎለት በጽኑ ህሙማን ማቆያ እንደሚገኝ ከሆስፒታሉ ህዝብ ግንኙነት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን ተከትሎ የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለማስፈጸም የሚንቀሳቀሱ ፖሊሶች በክልሉ ግድያ ሲፈጽሙ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ አይደለም። ቀደም ሲልም በመጋቢት ወር፤ በትግራይ ናዕዴር ዓዴት በሚባለው ወረዳ አንድ ወጣት በጸጥታ ኃይል አባል መገደሉ ይታወሳል። ሓጎስ ንጉሥ የተባለ ይህ ወጣት የተገደለው በተመሳሳይ ፖሊስ መጠጥ ቤት ውስጥ ተሰባስበው የነበሩ ሰዎችን ለመበተን ሲሞክር በተነሳ አለመግባባት ነበር። በመላዋ አገሪቱ የኮሮናቫይረስን መስፋፋት ለመከላከል ከታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቀደም ብሎ የትግራይ ክልል ውስጥ የሰዎችን በአንድ ላይ መሰባሰብን የማስቀረት ክልከላ ጨምሮ የተለያዩ እገዳዎች ተጥለው ነበር።
news-57265517
https://www.bbc.com/amharic/news-57265517
ጀርመን ናሚቢያን ቅኝ በገዛችበት ወቅት የዘር ጭፍጨፋ ማካሄዷን አመነች
ጀርመን ናሚቢያን ቅኝ በገዛችበት ወቅት የዘር ጭፍጨፋ ማካሄዷን አምናለች።
ካሳ በሚመስል ሁኔታም የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ እንደምትፈልግ ከሰሞኑ አስታውቃለች። ጀርመን ናሚቢያን በቅኝ ግዛት የያዘችው በአውሮፓውያኑ ከ1884-1915 ወቅት ሲሆን በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ናሚቢያውያንን ጨፍጭፋለች። የዘር ጭፍጨፋ የተካሄደባቸው የሄረሮና የናማ ህዝቦች ናቸው። በዚህ ጭፍጨፋም 80 በመቶ የሚሆኑት የነዚህ ማህበረሰብ አባላት ተጨፍጭፈዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሄይኮ ማስ በዛሬው ዕለት እንዳመኑት የጅምላ ግድያውንም ሆነ የዘር ጭፍጨፋ መፈፀሙን አምነዋል። "የጀርመንን ታሪክን ፈትሸን በአሁኑ ወቅት የሞራል ኃላፊነት እንዳለብን እንረዳለን። ናሚቢያውያንም እንዲሁ በቀጥታ የዘር ጭፍጨፋው ተጠቂ የሆኑ የልጅ ልጆችን ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ" ብለዋል። ሚኒስትሩ አክለውም ጀርመን "የዘር ጭፍጨፋው ጥቃት ሰለባዎች ምን ያህል ለማይሽር ቁስልና ህመም እንዳደረገቻቸውም እንረዳለን።" በማለትም ከዚህም ጋር በተያያዘ ለአገሪቱ የልማት ፕሮግራም የሚውል 1.34 ቢሊዮን ዶላር አገራቸው መለገስ እንደምትፈልግ ገልፀዋል። ገንዘቡም በጭፍጨፋው ተጠቂ ለሆኑት ማህበረሰቦች ለልማት፣ የጤና ተቋማትን ግንባታና ስልጠናዎችን ለመስጠት የሚውል ሲሆን በ30 አመታትም ውስጥ የሚለገስ ነው ተብሏል። "አሁን ላይ ቆመን ታሪክን ወደ ኋሊት ስንመለከት በናሚቢያ ላይ የተፈፀመው የዘር ጭፍጨፋ ነበር። በቅጭ ግዛት የተፈፀሙ ድርጊቶችን ልንሸፋፍናቸው አይገባም። ልንወያይባወቸው" ይገባል በማለትም በዛሬው መግለጫቸው ዳስሰዋል። የናሚቢያ መንግሥት ቃለ አቀባይ ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ የዜና ወኪል እንደተናገሩት ጀርመን የዘር ጭፍጨፋ ተካሂዷል ብላ እውቅና መስጠቷ "በትክለኛው መንገድ የተወሰደ የመጀመሪያ እርምጃ ነው" ብለውታል። ነገር ግን አንዳንድ የአገሪቱ ባህላዊ መሪዎች መንግሥትን በገንዘብ ራሱን የሸጠ ብለው ከመወንጀል በተጨማሪ የጀርመን መንግሥትን የእርዳታ ገንዘብ መቀበል የለብንም በማለት በፅኑ አውግዘውታል።
news-54101682
https://www.bbc.com/amharic/news-54101682
እግር ኳስና ኮሮናቫይረስ፡ የኢትዮጵያን ስም በአውሮፓ ያስጠራችው ሎዛ
ሎዛ አበራ በማልታ በሴቶች ዘርፍ የ2019/2020 የውድድር ዘመን ምርጥ ተጫዋች በመሆን በማልታ የእግርኳስ ተጫዋቾች ማህበር ተሸልማለች።
ሎዛ ለቢቢሲ አዲስ አይደለችም። የማልታውን ቡድን ቢርኪርካራ እንደተቀላቀለች እንዴት ነው ሕይወት በአውሮፓ ስንል አናግረናት ነበር። ከዚያ ቃለ ምልልስ በኋላ ሎዛ ብዙ ታሪክ ፅፋለች። ሪከርድ ሰብራለች። ሎዛ ለሌሎች አንጋፋ የስፖርት መገናኛ ብዙሃንም አዲስ አይደለችም። ከጎል ዶት ኮም ጀምሮ እስከ ካፍ ኦንላይን ስለሎዛ አውርተው አይጠግቡም። ቡድኗ ቢርኪርካራ ተቃናቃኙ ሂበርኒያንስን በማልታ ታሪክ ከፍተኛ በሆነ ጎል 17 ለምንም ሲረታ ሎዛ 7 ጎል መረብ ላይ አሳርፋለች። የተወሰኑ ኳሶችንም ለጎል አመቻችታ አቀብላለች። ሎዛ ከዚህ ታሪካዊ ጨዋታ በፊትና በኋላ በርካታ ጎሎችን በማስቆጠር ቡድኗ የማልቲዝ ሊግ ዋንጫ አሸናፊ እንዲሆን አድርጋለች። ሎዛአሁንየትነች? ሎዛ አሁን ያለችው ትውድል ቀዬዋ ነው። ከምባታ ዞን የምትገኘው ዱራሜ ከተማ። አጥቂዋ ለእረፍት ወደ ኢትዮጵያ በመጣችበት ነው የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ የተከሰተው። በዚህ ምክንያት ወደ ማልታ ተመልሳ ማቅናት አልቻለችም። ለነገሩ የማልቲዝ ሊግ በወረርሽኙ ምክንያት ተቋርጦ ነበር። ሎዛ ኢትዮጵያ እያለች ቡድኗ ቢርኪርካራ የማልታ የሴቶች ፕሪሚዬር ሊግ ዋንጫ አሸናፊ መሆኑ ይፋ ሆነ። ኢትዮጵያዊት ተስፈኛ አጥቂ በማልታ ሊግ የመጀመሪያ ዓመት ቆይታዋ በ12 ጨዋታዎች 30 ጎሎች በማስቆጠር ኮከብ ጎል አግቢ ሆናለች። 'ከቢርኪርካራ ጋር ባለድል በመሆኔ እጅግ በጣም ደስ ብሎኛል። እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ሁሉም ነገር በመልካም ሁኔታ ተጠናቋል' ትላለች ሎዛ። የወደፊት ዕቅድ የማልታ የሴቶች ፕሪሚዬር ሊግ የቀጣዩ ዓመት ውድድር በመጪው ጥቅምት ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል። ከአዳማ ከነማ ቢርኪርካራን መስከረም 2012 ላይ የተቀላቀለችው ሎዛ ከቡድኑ ጋር ያላት ውል ተጠናቋል። ለመሆኑ ውሏን ለማራዘም አስባ ይሆን? 'ከቢርኪርካራ ጋር የነበረኝ ውል የአንድ ዓመት ነው። እሱ ተጠናቋል። እርግጥ ነው ቢርኪርካራ ውሌን ለማራዘም ጥያቄ አቅርበዋል። እኔም ያቀረብኩላቸው ቅድመ ሁኔታ አለ። በእሱ የምንስማማ ከሆነ ልቀጥል እችላለሁ።' ሎዛ ከቢርኪርካራ ጋር የነበረኝ ቆይታ በጣም መልካም ነበር ትላለች። 'እርግጥ ነው አንድ ነገር ሲጀመር ሊከብድ ይችላል። ነገር ግን የማይለመድ የለም። ቡድኑ የነበረው ጥንካሬ ነበር። እዚያ ላይ የሁላችንም ጥረት ሲታከልበት ውጤታማ መሆን ችለናል።' እውን የማልታ የሴቶች ሊግ ለተጫዋቾች ጥሩ ክፍያ ይከፍላል ወይ የሚል ጥያቄ ከቢቢሲ የቀረበላት ሎዛ፤ ክፍያው እንኳ ቢቀር የማልታ ልምዱ ለወፊት የተሻለ ውድድር ውስጥ ራሷን እንድታገኝ እንደሚረዳት ትናገራለች። 'አንድን ነገር ለማሳካትስ ስታስብ ብዙ ነገሮችን ከግምት ታስገባለህ። እኔ ክፍያን እዚህ ውስጥ አልከተውም። የክፍያ ማነስ አለ እያልኩ ሳይሆን አላማዬ በዚህ ጉዞ ራሴን ለማሳየት፤ ወጥቼ መጫወት እንደምችል ለማሳየትና ፕሮፋይሌን ከፍ ለማድረግ ስለሆነ ተሳክቶልኛል ብዬ ነው የማስበው።' 'እርግጥ ነው የሃገሬ ምግብ ናፍቆኝ ነበር' ትላለች ከግማሽ ዓመት በላይ በአውሮጳዊቷ ትንሽዬ የጠረፍ ሃገር የቆየችው ሎዛ። ኮሮናቫይረስና እግር ኳስ ባለፈው ታኅሣሥ ድምፁ የተሰማው የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ የሰው ልጅ ከጠበቀው በላይ ጥፋት አድርሷል፤ የተለመዱ የሕይወት መስተጋብሮችን እንዳይሆኑ አድርጓል። ወረርሽኙ ካመሰቃቀላቸው መስኮች አንዱ እግር ኳስ ነው። ይህ ወረርሽኝ በሎዛ ፕሮፌሽናል የእግር ኳስ ሕይወት ላይ ያመጣው ተፅዕኖ ምን ይመስላል? 'በጣም ከባድ ነው። እግር ኳስን ብቻ ሳይሆን ሌሎች መስኮችንም የጎዳና ለዓለም የመጣ ስለሆነ ምንም ማድረግ አይቻልም።' ከወረርሽኙ ጋር ተያይዞ ከውድድር ርቀው የነበሩ እግር ኳስ ተጫዋቾች አንዱ ፈተናቸው በያሉበት ሆነው የአካል ብቃታቸውን ጠብቀው መቆየት ነው። ሎዛስ? 'በአቅራብያዬ በሚገኙ ቦታዎች እየሄድኩ እሠራ ነበር። ሠፈር ውስጥም ቤትም ነው ስፖርታዊ እንቅስቃሴ የማደርገው። ራቅ ብሎ ሄዶ እንቅስቃሴ ለማድረግ ጊዜው ስለማይፈቅድ በምችለው መልኩ በአቅራቢያዬ ነበር እንቅስቃሴ ሳደርግ የነበረው።' ሎዛ እሷ ብቻ ሳትሆን የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድንና የቀድሞ ቡድኗ አዳማ ከነማ ተጫዎቾችን አልፎ አልፎ በስልክ እንደምታገኛቸው በታቻላቸው መጠን በአካባቢዎች እንቅስቃሴ እያደረጉ እንዳሉ ትናገራለች። አልፎም ሎዛ 'እንቅስቃሴ ማድረግ ከወረርሽኙ ሊታደገን ስለሚችል ሁሉም ሰው በያለበት የተቻለውን ያክል እንቅስቃሴ ቢያደርግ' ስትል ምክሯን ትለግሳለች። የሎዛ የአዲስ ዓመት ምኞት 'ሁላችንም ከምንወደው ሙያ ርቀን በቤታችን ነው ያለነው። ፈጣሪ ይህን ዓመት በሰላም አሻግሮ ይህንን ወረርሽኝ ያርቅልን፤ እንዲሁም ሁላችንንም ወደ ሥራ ይመልሰን ብዬ እመኛለሁ።' 'ስፖርተኛውም በስፖርቱ፤ ሌላውም በተሰማራበት መስክ በአዲሱ ዓመት የተሻለ ነገር እንሠራለን ብዬ ነው የማስበው።' ቢቢሲ፡ እናመሰግናለን ሎዛ፤ ለአንቺና ለቤተቦችሽ መልካም አዲስ ዓመት ማለት እንወዳለን። ሎዛ፡ እኔም አመሰግናለሁ። ለእናንተም መልካም አዲስ ዓመት!
news-45831062
https://www.bbc.com/amharic/news-45831062
የሲንጋፖር አየር መንገድ 15 ሺህ ኪሎሜትር በመብረር ረጅሙን የበረራ ሰዓት ሊያስመዘግብ ነው
በአለማችን ላይ ረጅሙን የአውሮፕላን ጉዞ ክብረ ወሰን ለመያዝ የሚደረገውን ፉክክር ለማሸነፍ የሲንጋፖሩ አየር መንገድ ወደ ኒውዮርክ የሚያደርገው በረራ በጉጉት እተጠበቀ ነው።
የሲንጋፖር አየር መንገድ በረራውን ወደ ኒውዮርክ የጀመረው ከአምስት ዓመታት በኋላ በድጋሚ ሲሆን፤ የመጀመሪያው በረራ ውድ ሆነብኝ ብሎ ነበር ያቋረጠው። በረራው 15 ሺህ ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን፤ አውሮፕላኑ ያለምንም እረፍት ለ19 ሰዓታት ይበራል። የአውስትራሊያው ኳንታስ አየር መንገድ በያዝነው ዓመት መጀመሪያ አካባቢ 17 ሰዓታት የሚፈጅ በረራ ወደ ለንደን የጀመረ ሲሆን፤ የኳታር አየር መንገድ ደግሞ 17.5 ሰዓታት የሚፈጅ በረራ አድርጎ ነበር። • ሴራሊዮን በቻይና ብድር አየር መንገድ አልገነባም አለች • አፍሪካዊያን ሌሎች የአፍሪካ ሃገራትን መጎብኘት ለምን ይከብዳቸዋል? ከቻንጊ አየር መንገድ ተነስቶ ኒውዮርክ አየር ማረፊያ መዳረሻውን ያደረገው አውሮፕላን ገና በመጀመሪያዎቹ ሰዓታት ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ መቀመጫዎቹ ተይዘዋል። የሲንጋፖር አየር መንገድ እንዳስታወቀው በዓለም ረጅሙ በረራ የተጀመረው ያልተቆራረጠ በረራ ማድረግ የሚፈልጉ ተጠቃሚዎች ቁጥር በመጨመሩ ነው። አየር መንገዱ ለቢቢሲ እንደገለጸው አብዛኛዎቹ የአውሮፕላኑ መቀመጫዎች ቀድመው የተያዙ ሲሆን፤ የተንደላቀቁ የተባሉት ክፍሎች ብቻ ጥቂት ቀርቷቸዋል። ተጓዦች በአውሮፕላኑ በሚኖራቸው ቆይታ ሁለት የምግብ ሰዓቶች ይኖሯቸዋል፤ ከዚህ በተጨማሪም ጀርባቸውን አረፍ ማድረግ ሲያምራቸው ደግሞ የሚጠቀሙት ቅንጡ አልጋ ተዘጋጅቶላቸዋል። 19 ሰዓታት በአየር ላይ? ለበረራው ጥቅም ላይ የሚውለው አዲሱ ኤርባስ አውሮፕላን መለስተኛ ቅንጡ በተባሉ ወንበሮቹ 161 ተሳፋሪዎችን ማስተናገድ ይችላል። የመነሻውም የመዳረሻውም ከተሞች እጅግ ከፍተኛ ንግድ የሚካሄድባቸው ቦታዎች ስለሆኑ ነጋዴዎችና በተለያዩ ስራዎች ላይ የተሰማሩ ሰዎች በደስታ ረጅሙን በረራ ይጠቀማሉ ይላል የአቪዬሽን ባለሙያ የሆኑት ጆፍሪ ቶማስ። 'ከዚህ በተጨማሪም ሁል ጊዜም ቢሆን አዲስ በረራ ሲጀመር ተጠቃሚዎች ቁጥራቸው ይጨምራል።' ከዚህ ጎን ለጎን ኳንታስ አየር መንገድ 20 ሰዓታት የሚፈጅ ከለንደን ሲድኒ በረራ ለማስጀመር ከአውሮፕላን አምራቾቹ 'ኤርባስ' እና 'ቦይንግ' ጋር ድርድር መጀመሩን አስታውቋል። • የትናንቱ የ4 ኪሎ ውሎ እና አንድምታው • እንግሊዝ "ራስን የማጥፋት" ተከላካይ ሚኒስትር ሾመች በተጨማሪም አየር መንገዱ አውስትራሊያን ከሰሜን አሜሪካ የሚያገናኝ ያልተቆራረጠ በረራ ለመጀመር አቅዷል። ፍላይት ግሎባል በተባለው ጋዜጣ ዋና አርታኢ የሆኑት ማክስ ኪንግስሊ ግን ይህ አካሄድ አዋጪ ላይሆን ይችላል ይላሉ። በመጀመሪያዎቹ ወራትና ምናልባትም ዓመታት የተጠቃሚዎች ቁጥር ከፍተኛ ሊሆን ይችላል። 'ነገር ግን ከዓለም ኢኮኖሚ ጋር በተያያዘ አንዳንድ ለውጦች ሲመጡ ተጠቃሚዎች ወደ ድሮዎቹ በዋጋ ቅናሽና የተቆራረጡ በረራዎች ፊታቸውን መመለስ ይጀምራሉ።'
news-52773544
https://www.bbc.com/amharic/news-52773544
የልጅ ልጆቻቸውን ፎቶ ፌስቡክ ላይ የለጠፉት አያት በአውሮፓ ሕብረት ሕግ ተከሰሱ
የልጅ ልጆቸቻቸውን ፎቶ ያለ ፈቃድ ፌስቡክ ላይ ለጥፈዋል የተባሉት አያት በአውሮፓ ሕብረት ሕግ ተከሰው ፎቶዎቹን እንዲያወርዱ ታዘዋል።
አያት፤ የልጅ ልጆቻቸውን ፎቶ ፌስቡና ፒንተረስት የተሰኙት የማኅበራዊ ድር-አምባዎች ላይ ያለፈቃድ ለጥፈዋል የሚል ክስ የተመሠረተባቸው ከልጃቸው ነው። ብይኑን የሰጠው አንድ የኔዘርላንድስ ፍርድ ቤት ዳኛ አያት የአውሮፓ ሕብረትን ሕግ ጥሰዋል ሲሉ ኮንነዋቸዋል። አያት የልጅ ልጆቼን ፎቶ ከፌስቡክ ላይ አላጠፋም ማለታቸውን ተከትሎ ነው በልጃቸው ክስ የቀረበባቸው። የግራ ቀኙን የተመለከተው ፍርድ ቤት አያት የጠቅላላ መረጃዎች ጥበቃ የሚለውን የአውሮፓ ሕብረት ሕግ አልተከተሉም ሲል ፈርዷል። የልጆቹ እናት የሆነችው ከሳሽ "ብዙ ጊዜ የልጆቼን ፎቶ አውርጂ ስል ጠይቅያለሁ" ስትል ለፍርድ ቤቱ አቤቱታዋን አሰምታለች። ምንም እንኳ የአውሮፓ ሕብረት ሕግ ለግለሰቦች የሚያገለግል ባይሆንም፤ "አያት የልጆቹን ፎቶና መረጃ ለብዙሃን አጋልጠዋል" ብለዋል ዳኛው። "ፌስቡክ ላይ የሚለጠፉ ፎቶዎች ለሦስተኛ ወገን ተላልፈው ሊሰጡ ይችላሉ። ፎቶዎቹ ለብዙሃኑ ስለሚጋለጡ ያለአግባብ ሊሰራጩ ይችላሉ" ብሏል የፍርድ ቤቱ ብይን። አያት ፎቶዎቹን አላወርድም የሚሉ ከሆነ በየቀኑ 50 ዩሮ [1800 ገደማ ብር] እንዲከፍሉ ይገደዳሉ። የቅጣቱ ከፍታ 1 ሺህ ዩሮ ነውም ተብሏል። አያት ፍርድ አያግደኝም ብለው ሌሎች ፎቶዎች የሚለጥፉ ከሆነ ተጨማሪ 50 ዩሮ በየቀኑ ይቀጣሉ። "ፍርዱ ብዙዎችን ሊያስገርም ይችላል፤ በርካቶች ፎቶ ወይም ፅሑፍ ሳያስተውሉ ሊለጥፉ ይችላሉና" ይላሉ የቴክኖሎጂ ጠበቃው ኒል ብራውን።
news-55570564
https://www.bbc.com/amharic/news-55570564
የጆርጂያን ድል ተከትሎ ዲሞክራቶች የሕግ መወሰኛ ምክር ቤቱን ተቆጣጠሩ
"ሁለተኛው የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ" የሚል ስም የተሰጠው የጆርጂያ ግዛት እንደራሴዎች ምርጫ በዲሞክራቶች የበላይነት ተጠናቋል።
ሚስተር ዋርኖክ እና ሚስተር ኦሶፍ ድል ቀንቷቸዋል። ሁለቱ እጩዎች በቀጥታ የሴኔት አባል በመሆናቸው ሪፐብሊካኖች በላዕላይ ምክር ቤት ውስጥ የነበራቸውን የበላይነት አጥተዋል። ዲሞክራቶቹ ራፋኤል ዋርኖክ እና ጆን ኦሶፍ ተቀናቃኞቻቸውን ኬሊ ሊዮፍለርን እና ዴቪድ ፐርዲዩን ያሸነፉት በጠባብ ልዩነት ነው። ይህ በመሆኑም ከእንግዲህ በሕግ መወሰኛው ምክር ቤት ውስጥ የዲሞክራቶችና የሪፐብሊካኖች ቁጥር እኩል 50=50 ሆኗል። ከእንግዲህ በድምጽ አሰጣጥ ሂደት ወሳኙ እጅ ከምክትል ፕሬዝዳንት ተመራጭ ካሜላ ሐሪስ የሚመጣ ነው የሚሆነው። ምክንያቱም የላእላይ ምክር ቤቱን ሸንጎ የሚመሩት እርሳቸው ስለሚሆኑ ነው። ዲሞክራቶች ናንሲ ፒሎሲ በአፈ ጉባኤነት የሚመሩትን የታችኛው ምክር ቤትን ብቻ ነበር በበላይነት የሚመሩት። አሁን ግን የጆርጂያን ድል ተከትሎ ሴኔቱም የዲሞክራቶች ሆኗል። ዲሞክራቶች የሕግ መምሪያን፣ የሕግ መወሰኛንና ዋይት ሐውስን በአንድ ጊዜ መቆጣጠር ሲችሉ ከ2009 ወዲህ ለመጀመርያ ጊዜ ነው። በጆርጂያ ሴኔትን የሚወክል የሕዝብ እንደራሴ ምርጫ 4 ሚሊዮን ነዋሪዎች ድምጽ ሰጥተዋል። ምርጫው የተካሄደው በድጋሚ ነው። ይህ ምርጫ ባለፈው ኅዳር ተደርጎ አንዳቸውም እጩዎች ከ50 በላይ የሕዝብ ድምጽ ማግኘት ስለተሳናቸው ነው ባለፉት ቀናት በድጋሚ እንዲካሄድ የተደረገው። በመጀመርያ ድል የተሰማው ከራፋኤል ዋርኖክ ነበር። ዋርኖክ በታሪክ ውስጥ በባሪያ አሳዳሪነቷ በምትታወቀው ጆርጂያ ውስጥ ለመጀመርያ ጊዜ የሕዝብ ይሁንታን አግኝቶ ሴኔት የገባ ጥቁር የሕዝብ እንደራሴ ለመሆን በቅቷል። በአሜሪካ ታሪክም ዋርኖክ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ሴኔት ለመግባት 11ኛው ጥቁር ሰው ነው። ዋርኖክ ማሸነፉን ተከትሎ የድሉን መታሰቢያ ለ82 ዓመት እናቱ አውሎታል። እናቱ ጥቁር በመሆናቸው በጥጥ እርሻ ውስጥ የጉልበት ሥራ ሲሰሩ የነበሩ ናቸው። ዋርኖክ በአትላንታ አቤኔዘር ቤተክርስቲያን ሰባኪ ሲሆን፣ ይህ ቤተክርስቲያን በታሪክ እንደሚታወቀው ዝነኛው የጥቁሮች መብት ታጋይ ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየር ሲሰብክበት የነበረ ቤተእምነት ነው። ሁለተኛው የዲሞክራት ተመራጭ ጆን ኦሶፍ እድሜው ገና 33 ሲሆን የተወለደው በአትላንታ ነው። በሙያው የዘጋቢ ፊልም አሰናጅ የሆነው ኦሶፍ፣ የ2ኛ ደረጃ ተማሪ ሳለ ከዝነኛው የጥቁሮች መብት ታጋይ ከጆን ልዊስ ጋር አብሮ በመሥራቱ ዝናን አግኝቷል። ጆን ኦሶፍ በ2012 በሎንዶን መቀመጫውን ያደረገ የምርመራ ጋዜጠኛ ቡድን ጋር መሥራት ከጀመረ ወዲህ ነው ይበልጥ እየታወቀ የመጣው። 50ዎቹ የአሜሪካ ግዛቶች እኩል 2 እንደራሴዎችን በመላክ የሚወከሉበት ሴኔት በዲሞክራቶች ቁጥጥር መዋሉ ቀጣዩ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የሚሾሟቸው ባለሥልጣናትና ዳኞች እንዲሁም ፖሊሲዎችና ሕጎች በቀላሉ በሁለቱም ምክር ቤቶች በድምጽ ብልጫ እንዲጸድቁላቸው ያግዛቸዋል። በተለይም ሪፐብሊካኖች አምርረው በሚቃወሟቸው የጤና መድኅን እና የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች ዙርያ ባይደን ፍላጎታቸው ለማስፈጸም ትልቅ እድል ያገኛሉ ተብሏል። ሪፐብሊካኖች በጆርጂያ ለገጠማቸው ሽንፈት ፕሬዝዳንት ትራምፕን ተጠያቂ ማድረግ ጀምረዋል።
news-49822045
https://www.bbc.com/amharic/news-49822045
ኢንዶኔዢያውያን ከትዳር በፊት ወሲብ የሚከለክለውን ህግ ተቃወሙ
ትናንት ማምሻውን የኢንዶኔዢያ ፓርላማ አካባቢ ዜጎች ከትዳር በፊት ወሲብ የሚከለክለውን ህግ በመቃወም ሰልፍ አድርገው ከፖሊስ ጋር ተጋጩ።
ፖሊስ ሰልፈኞቹን ለመቆጣጠር አስለቃሽ ጭስ እና የውሃ ፓምፖችን ተጠቅሟል። በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎችም ረቂቅ ህጉን በመቃወም ዜጎች ቁጣቸውን ሲገልጹ ነበር። ከዚህ በተጨማሪ ረቂቅ ህጉ የጽንስ ማቋረጥና ፕሬዝዳንቱን መሳደብን ህግወጥ እንደሆነ አስቀምጧል። • ደም የለበሰው የኢንዶኔዥያ ሰማይ • ወሲባዊ ትንኮሳ ያደረሰባት አለቃዋን በማጋለጧ የታሠረችው ሴት ምንም እንኳን ረቂቅ ህጉ እስካሁን ሙሉ በሙሉ ባይጸድቅም ዜጎች ፓርላማው በሙሉ ድምጽ እንዳይቀበለው ስጋታቸውን እየገለጹ ነው። ለፓርላማው የቀረበው ረቂቅ ህግ የሚከተሉትን ዋና ዋና ሃሳቦች ይዟል፡ ረቂቅ ህጉ ዛሬ ለፓርላማው ቀርቦ ውሳኔ እንደሚያገኝ ሲጠበቅ የነበረ ቢሆንም ፕሬዝዳንት ጆኮ ዊዶዶ ሂደቱ ማካተት ያለበት አንዳንድ ነገሮች አሉ በማለት ወደ አርብ እንዲዘዋወር ማድረጋቸው ታውቋል። ተቃዋሚዎች ከዚህ ባለፈ ረቂቅ ህጉ በሃገሪቱ ተንሰራፍቶ የነበረውን ሙስና ከምንጩ ለማድረቅ ሲሰራ የነበረውን የሙስና አስወጋጅ ኮሚሽን ያዳክመዋል ሲሉ ስጋታቸውን ሲያሰሙ ነበር። • በውሃ እየተዋጠች ያለችው ከተማ አብዛኛዎቹ ተማሪዎች የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢንዶኔዢያውያን በመላው ኢንዶኔዢያ ዋና ዋና መንገዶች ላይ በመውጣት ተቃውሟቸውን አሰምተዋል። ተቃዋሚዎች ከፖሊስ ጋር የተጋጩት ግን በዋና ከተማዋ ጃካርታ ሲሆን የፓርላማው አፈ ጉባኤ የሆኑት ባምባንግ ሶሳትዮ መጥተው እንዲያነግሩን እንፈልጋለን የሚል መልእክትም አሰምተዋል። በመቀጠል ሰልፈኞቹ ፖሊስ ላይ ድንጋይ መወርወር መጀመራቸውን ተከትሎ አድማ በታኝ ቡድኖች አስለቃሽ ጭስና ውሃ ፓምፖችን በመጠቀም ተቃዋሚዎቹን ለመበተን ጥረት አድርገዋል።
news-45186961
https://www.bbc.com/amharic/news-45186961
ለተማሪ ሲፈተኑ የተያዙት ርዕሰ-መምህር 5 ዓመት ተፈረደባቸው
በአንድ ተማሪ ስም የዩንቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ሲወስዱ የተያዙት በቡሩንዲ የሚገኝ የአንድ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ-መምህር በአምስት ዓመት እስራት ተቀጡ።
ቤንጃሚን ማኒራምቦና ከእስሩ በተጨማሪ ለአስር ዓመታት በመምህርነት እንዳያገለግሉ እና በየትኛውም የመንግሥት ሥራ እንዳይሳተፉ ተበይኖባችዋል። • ርዕሰ-መምህሩ ለተማሪ ሲፈተኑ በፖሊስ ተያዙ • በኬንያ በርካታ ትምህርት ቤቶች በተማሪዎች ተቃጠሉ በጉዳዩ ላይ ተሳታፊ ነበሩ የተባሉት የሒሳብ ባለሙያው ኤሪክ ንኩሩንዚዛ እና መምህሩ ላዛርድ ኒሄዛጊሬ በሁለት ዓመት እስራት እንዲቀጡ ተወስኖባቸዋል። ሁለቱ ርዕሰ-መምህሩን ተባብረዋል በሚል ነው ቅጣቱ የተላለፈባቸው። ርዕሰ-መምህሩ ወደ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት ተማሪዎች መውሰድ ያለባቸውን ፈተና ላይ በአንድ ተማሪ ስም ወደ ፈተና ክፍል ገብተው ሲፈተኑ የተያዙት። በዋና ከተማዋ ቡጁምቡራ ሰሜናዊ ክፍል የሚገኘው ቡቴሬሬ የቴክኒክ ኮሌጅ ርዕሰ-መምህር የሆኑት ቤንጃሚን ማኒራምቦና የመጨረሻውን የፈተና ወረቀት እየሰሩ ሳለ ነበር ፖሊስና የሃገሪቱን የትምህርት ሚኒስትርን ጨምሮ ባለስልጣናት ወደፈተናው አዳራሽ በመግባት ያፋጠጧቸው። እጅ ከፍንጅ ተይዘው ማምለጫ ያላገኙት ርዕሰ-መምህሩ ቤንጃሚን የፈፀሙትን ወንጀል እዚያው ፈተና አዳራሽ ውስጥ አምነው ተናዘዋል።
news-51557294
https://www.bbc.com/amharic/news-51557294
"ትግራይ ላይ ያለው ጥላቻ ካልተስተካከለ፤ ትግራይ ራስዋን የቻለች አገር ናት ብላችሁ አውጁ" ዶ/ር ደብረፅዮን
''በኢትዮጵያ እየተከሰተ ያለው ጣልቃ ገብነት እንዲሁም በትግራይ ላይ ያለው ጥላቻ የማይስተካከል ከሆነ ትግራይ ራስዋን የቻለች አገር ናት ብላችሁ ልታውጁ ይገባል" ሲሉ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል መልዕክት አስተላለፉ።
ይህንን መልዕክት ያስተላለፉት ህወሓት የተመሰረተበትን 45ኛውን ዓመት አስመልክቶ በዛሬው ዕለት በመቀሌ ስታዲየም ለታደሙ ሰዎች ባደረጉት ንግግር ነው። የትግራይ ምክትል ፕሬዝደንት ደብረፅዮን (ዶ/ር) ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ባስተላለፉት መልዕክት፤ "የስልጣን ጊዜያችሁ [የአባልነት ጊዜ] እያለቀ ስለሚገኝ ከመበታተናችሁ በፊት ታሪክ ስሩ። በኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው ጣልቃ ገብነት፣ በተለይም ትግራይን በተመለከተ በመሪዎች ደረጃ የተሰጡት የጥላቻና የፀረ ህዝብ ንግግሮችን በይፋ ኮንኑ" ብለዋል። አክለውም "ይህ የማይሆን ከሆነ ትግራይ ራሷን የቻለች አገር መሆኗን ወስኑ፤ አውጁ" ብለዋል። "አገር በመበተን ሂደት ነበሩ ተብላችሁ በታሪክ እንዳትወቀሱ፤ ግዳጃችሁን ተወጡም" በማለት መልዕክታቸውን በተሰበሰው ህዝብ ፊት አስተላልፈዋል። ደብረፅዮን (ዶ/ር) ከዚህም በተጨማሪ በትግራይና በኤርትራ መካከል ያለውን ታሪካዊ ዳራም እንዲሁም አሁንም ስላለው ግንኙነት ምክር አዘል መልዕክት አስተላልፈዋል። ህወሓት በትጥቅ ትግል በነበረበት ወቅት "የደርግን ስርዓት ለመጣል የትግራይ እና የኤርትራ ልጆች አንድ ጉድጓድ ላይ ተቀብረዋል" ያሉት ዶ/ር ደብረጽዮን፤ ከኤርትራ ነጻነት በኋላም ቢሆን የትግራይ ህዝብ እና ህወሓት በኤርትራ ህዝብ የነጻነት ጥያቄ የማያወላዳ አቋም በመያዛቸው ብዙ ፖለቲካዊ ተቃውሞ ቢገጥመውም ከአቋሙ ውልፍት እንዳላለ ተናግረዋል። በሁለቱ ሃገራት ከተካሄደው ጦርነት በኋላ ሰላም ከመምጣቱ በፊትም የኤርትራ ተፈናቃዮችን "አቅፎ ጥላ በመሆን'' ለኤርትራ ህዝብ ወዳጅ መሆኑን አስመሰክረዋል ብለዋል። በየካቲት 11 በዓል ደግሞ የነበሩ ቅራኔዎችን ለመፍታት ዝግጁ መሆናቸውን የገለፁት ደብረፅዮን (ዶ/ር) የህዝብን ቀጣይነት አስምረውታል። "መንግሥታት ፈራሾች ናቸው እና ሰላማችንን ለማስቀጠል በህዝቦች መካከል ውይይት እንዲጀመር እንፈልጋለን።" በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። በትግራይና ኤርትራ ህዝቦች መካከል ያለውን የቋንቋ እና ባህል ተመሳሳይነት፣ የጋራ ታሪክ እንዲሁም በደም የተሳሰሩ ከመሆናቸው አንፃር ለጦርነት የሚፈላለጉ ህዝቦች አለመሆናቸውን አፅንኦት በመስጠት ተናግረዋል። ለዚህም የተለያዩ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትን በወነጀሉበት ንግግራቸው ህዝቡን የፖለቲካ አጀንዳ መደበቂያ አድርገውታልም ብለዋል። "የትግራይ እና ኤርትራ ህዝቦችን ወደ ጦርነት ሊማግዱት የሚያስቡ ኃይሎች አሉ፤ የተጀመረውን የሰላም ሂደት ተቋማዊ በሆነ መንገድ ከመፍታት ይልቅ ለፖለቲካ አጀንዳ መደበቅያ እያደረጉት ይገኛሉ" ብለዋል። የትግራይ ህዝብ እህትማማች ከሆነው የኤርትራ ህዝብ ጋር ግጭት የመግባት ምንም አይነት አላማ የለውም የሚሉት ደብረፅዮን (ዶ/ር) ሁለቱን ሃገራት ወደ ጦርነት ለመክተት የሚደረጉ ሴራዎች እንዳሉም አልደበቁም። ሁለቱን ሃገራት የሚያገናኙ መንገዶች መዘጋት እንዲሁም በኢትዮጵያ የሚገኙ የኤርትራውያን የስደተኞች መጠለያ እንዲዘጉ እና አዳዲስ ስደተኞች እንዳይቀበሉ የማድረግ ሥራ "በኢትዮጵያና በኤርትራ መንግሥት የተደረገ ሴራ ነው" ብለዋል። አክለውም "የኤርትራ ህዝብ ችግር ችግራችን ስለሆነ ለእናንተ የሚዘጋ በር የለንም። ትግራይ አገራችሁ ነው፤ የኤርትራ ሠራዊት ትግራይ አገርህ ነው። እየታለመ ያለው የፖለቲካ ሴራ አብረን እናክሽፈው" በማለት ንግግራቸውን አድርገዋል። በአገሪቷ የተለያዩ አካባቢዎች እየተካሄደ ስላለው የሠራዊት ስምሪት እና እሱን ተከትሎ ስለተከሰተው ጉዳት ተጠያቂ ሊኖር ይገባል ያሉት ደብረፅዮን (ዶ/ር)፤ ስለየትኛው የሠራዊት ስምሪት እና ጉዳት እንደሆነ ያሉት ነገር የለም።
news-48130433
https://www.bbc.com/amharic/news-48130433
ፆታዋ ያከራከረው ደቡብ አፍሪካዊት ሯጭ በፍርድ ቤት ተረታች
የ800 ሜትር ኦሎምፒክ ሻሚፒዮን የሆነችው የ28 ዓመቷ ደቡብ አፍሪካዊት ሯጭ ካስተር ሰሜንያ ዓለም አቀፉን የአትሌቲክስ ፌደሬሽን የከሰሰችው 'ቴስቶስትሮን' የተሰኘው የወንድ ሆርሞን ከፍ ባለ መጠን ያላቸው ሴት ሯጮችን በተመለከተ ባወጣው ህግ ምክንያት ነበር።
ሰሜንያ የኦሎምፒክ 800 ሜትር ሁለት ጊዜ አሸናፊ ነች • ተስፋዬ ገብረአብ ስለ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ምን ይላል? ዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፌደሬሽን 'ቴስቶስትሮን' ለሴት ሯጮች ከፍተኛ ጉልበት ስለሚሆን እንደ ሰሜንያ ያሉ ይህ ሆርሞን በከፍተኛ መጠን ያላቸው ሴት ሯጮች በውድድር ፍትሃዊ ያልሆነ ብልጫ ያሳያሉ በሚል ነው በሴት ሯጮች የቴስቶስትሮን መጠን በመድሃኒት መገደብ አለበት የሚል ህግ ያወጣው። ሰሜንያም ይህ ህግ እንደ ተፈጥሮዬ እንዳልሆን የሚያደርግ ነው በማለት ነበር ጉዳዩን ወደ ዓለም አቀፉ የስፖርት የግልግል ዳኝነት ተቋም የወሰደችው። ቀደም ሲልም መሮጥ የምትፈልገው ምንም ምንም ሳይባል ተፈጥሮ እንደሰጣት፤ እንደማንነቷ እንደተፈጥሮዋ እንደሆነ ተናግራ ነበር- ሰሜንያ አሁን ግን ፍርድ ቤቱ ክሱን ውድቅ ስላደረገው እንደ ሰሜንያ ያሉና ከ400 ሜትር ጀምሮ እስከ ማይል የሚሮጡ ሴቶች በህጉ መሠረት በመድሃኒት የወንድ ሆርሞን ማለትም 'ቴስቶስትሮን' መጠናቸውን ለመቀነስ ወይም የሚሮጡበትን መጠን ለመቀየር ይገደዳሉ። • የኤርትራ መንግሥት ለ13 ዓመታት የቁም እስር የፈረደባቸው ፓትርያርክ ማን ናቸው? "ለአስር ዓመታት ያህል ዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌደሬሽን ፍጥነቴን ሊገታ ሞክሯል። ይህ ግን እንዲያውም ጠንካራ አደረገኝ" በማለት የአሁኑ የፍርድ ውሳኔም ወደ ኋላ እንደማይዛት ሰሜንያ ተናግራለች። ዳግም ከዚህ ፍርድ በላይ ከፍ ብላ የደቡብ አፍሪካን እንዲሁም ለዓለም ወጣት ሴቶችና ሯጮች ምሳሌ እንምትሆንም አስታውቃለች። የስፖርት ግልግል ዳኝነት ፍርድ ቤቱ የዓለም አቀፉ ሩጫ ፌደሬሽን ውሳኔ አድሏዊነት ያለው ሊባል ቢችልም ውሳኔውን ግን "አስፈላጊ፣ ምክንያታዊና ሚዛናዊ" ብሎታል። ለሌሎች ሴት ሯጮች ውድድሮች ፍትሃዊ እንዲሆኑ ከማድረግ አንፃርም ውሳኔው አስፈላጊ እንደሆነም አስረግጧል። • በቻይና የተደረሱት ስምምነቶች የትኞቹ ናቸው?
news-41029287
https://www.bbc.com/amharic/news-41029287
ታሪክ ብዙም እውቅና ያልሰጠው የዓለማችን ቱጃር
በግሪጎሪሳውያን የዘመን አቆጣጠር ከ1459-1525 ዓመተ ምህረት የኖረው ጄኮብ ፉገር ዛሬ በሕይወት ቢኖር ኖሮ ቢል ጌትስ፥ ዋረን ቡፌት እንዲሁም ማርክ ዙከርብረግ አንድ ላይ ተደምሮ ከሚኖራቸው በላይ ሀብት ይኖረው ነበር።
"ጄኮብ ፉገር በታሪክ ከታዩ ሁሉ በጣም ጠንካራው የባንክ ባለቤት ነው" የፉገር የሕይወት ታሪክ ጸኃፊ የሆነው ግሬግ ስቴይንሜትዝ እንደሚናገረው በቅጽል ስሙ 'ሀብታሙ ሰው' በመባል የሚታወቀው ጀርመናዊው የባንክ ባለቤት እና ነጋዴ ፉገር በሕይወት በነበረበት ወቅት በዚህ ዘመን የአራት መቶ ቢሊዮን ዶላር ሊጠጋ የሚችል ሀብት አካብቶ ነበር። የቀድሞው የዋል ስትሪት ጋዜጣ አርታኢ እና ታሪክ ጸሃፊው ስቴይንሜትዝ እንደሚገልጸው ጄኮብ ፉገር በዓለም ታሪክ ከታዩ ባለጸጋዎች ቁጥር አንድ መሆኑን ነው። ስቴይንሜትዝ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2015 የፉገርን የሕይወት ታሪክ "የዓለማችን ቱጃሩ ሰው "በሚል ርዕስ በመጽሃፍ ጠርዞ ለአንባቢያን አብቅቷል። ከቢቢሲ ጋር ቆይታ ያደረገው ታሪክ ጸሃፊው ስቴይንሜትዝ ሀብትን እና ጊዜ እያነጻጸሩ ትችት ለሚሰነዝሩበት ሰዎች ምላሽ ሲሰጥ ሌላው ቢቀር በአንድ ነገር በጣም እርግጠኛ እንደሆነ ይናገራል። "ጄኮብ ፉገር በታሪክ ከታዩ ሁሉ በጣም ጠንካራው የባንክ ባለሙያ ነው" በማለት ይናገራል ሀሳቡን ሲያስረግጥም በኣውሮፓውያን የሕዳሴ ዘመን ጠንካራ ለነበሩት የሮም ገ እንዲሁም የካቶሊክ ቤተክርስትያን ሊቀ ጳጳስን ገንዘብ ይሰጥ እንደነበረ ይመሰክራል። እንደ ታሪክ ጸኃፊውም አባባል ማንም የባንክ ሰው በዓለም ፖሊቲካዊ ሚዛን ላይ የፉገርን ያህል ተጽዕኖ ፈጣሪ ሆኖ አያውቅም። ፉገር በሕይወት በነበረበት ወቅት ወደ አራት መቶ ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ሀብት አካብቶ ነበር የፉገር አለመታወቅ ጉዳይ በሱ ዘመን የነበሩትን እነ ሜዲሲ፥ ቄሳር፥ እንዲሁም የሉክሬዚያ ወንድማማቾችን እና ማኪያቬሊን ታሪክ ሲዘክራቸው እንዴት ይህን ሰው ታሪክ ሳያውቀው ቀረ? ትንታኔ የሚያሻው ጉዳይ ነው። ለዚህ ጥያቄ ምላሽ የሚሰጠው ስቴይንሜትዝ የፉገር ጀርመናዊ መሆን እና በእንግሊዝኛ ተናጋሪው ማህብረሰብ አለመታወቅ ትልቁን ሚና ይጫወታል ይላል። ይህም እውነት ስቴይንሜትዝን ስለ ጄኮብ ፉገር ብዙ እንዲጠይቅ እንዳደረገው ይናገራል። "የዎል ስትሪት ጆርናል ጋዜጣ የጀርመን ቢሮ ኃላፊ በነበርኩበት ወቅት ነው ስለ ፉገር ጥቂት መስማት የጀመርኩት፤ ነገር ግን ስለሱ በእንግሊዛኛ የተጻፈ ነገር ማግኘት አልቻልኩም።" ይላል ስቴይንሜትዝ። ሌላኛው ፉገር በዓለም ያለመታወቅ ምክንያት ሰውየው ያን ያህል የጎላ ገፀባህርይ ወይም ህይወት ስላልነረው ሊሆን ይችላል ሲል ያክላል ። "ሊቀ ጳጳስ ለመሆን ወይም የፖለቲካ ስልጣን ለመያዝ አልሞከረም፤ ከየትኛውም የህዳሴ ዘመን አርቲስት ጋር ግንኙነት አልነበረውም፥ ቤተ-መንግስት ወይም ካቴድራል አልገነባም " ይላል ታሪክ ጸኃፊው ። ፉገር የተሰኘው በጀርመን ኦግዝበርግ የሚገኘው የጋራ መኖሪያ ቤት ከፉገር ስራዎች ውስጥ ትልቅ እውቅና ያስገኘለት በስሙ የሚጠራውና በጀርመን ኦግዝበርግ የሚገኘው የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታ ሲሆን በነዚህ ቤቶች የሚኖሩ ሰዎች በዓመት የሚከፍሉት አንድ ዶላር ብቻ መሆኑ ሌላው ቦታውን ታዋቂ ያደረገው እውነታ ነው። ፉገር ከካፒታሊዝም ስርዓት ፈጣሪዎች አንዱ እንደሆነም ይነገርለታል፤ ዘመናዊው የቁጠባ ስርዓት እንዲስፋፋም ከፍተኛ ሚናም ተወጥቷል።
news-45742581
https://www.bbc.com/amharic/news-45742581
በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የጤና ባለሙያዎች ጥቃት ደረሰባቸው
ኢቦላ ዳግም ባገረሸበት ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የሚሰሩ የጤና ባለሙያዎች ቫይረስ የምትሉት ሀሰት ነው ሲል በተቆጣ የአካባቢው ነዋሪ ጥቃት ደረሰባቸው።
በምስራቃዊው ኮንጎ ክፍል ከሁለት ወር በፊት ዳግም ባገረሸው ኢቦላ ከ100 የሚበልጡ ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል። የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከተማ ቡቶሞ ከቤኒ ቀጥላ የኢቦላ ቫይረስ ስርጭት የታየባት ከተማ ናት። በኡጋንዳ ድንበር ቅርብ በሆነችውና የአሳ ምርት በሚቸበቸብባት ሌላኛዋ ትቾይማ ከተማም ኢቦላ መታየቱ ተሰምቷል።ይሁን እንጂ ቫይረሱን ለመግታት በጤና ባለሙያዎች የሚደረገውን ጥረት የሚያደናቅፉ ጥቃቶች በአካባቢው ማህበረሰብ በመፈፀሙ ችግሩን አስጊ አድርጎታል። • ኢቦላ በኮንጎ እየተዛመተ ነው • በእርጥብ ሳርና ቅጠል ጥቃትን ያስቆሙ አባቶች የኢቦላ ቫይረስ ከሞቱት ሰዎች ጋር በሚደረግ ንክክኪ ይተላለፋል፤ በመሆኑም የሞቱትን ሰዎች በጥንቃቄና ለንክኪ በማያጋልጥ ቦታ መቅበር የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት ከሚደረግ ጥንቃቄ አንዱ ነው። ይሁን እንጂ የሟች ቤተሰቦችና የአካባቢው ማህበረሰብ ይህንን እውነታ ለመቀበል ይቸገራሉ። በተለይ ደግሞ የሟች ግብዓተ መሬት ከመፈፀሙ አስቀድሞ ለስንብት የሟችን አስክሬን የሚነኩበት ልማድ ባለበት አካባቢ ጉዳዩን ፈታኝ አድርጎታል። በዚህም ሳቢያ አራት የቀይ መስቀል የጤና ባለሙያዎች ሕይዎታቸው ያለፉ ሰዎችን ለቀብር ስነ ስርዓት በማጓጓዝ ላይ ሳሉ ቡቴሞ በተባለ አካባቢ ጥቃት ተፈፅሞባቸዋል። የአካባቢው ነዋሪዎች መኪናቸው ላይ ድንጋይ በመወርወር በፈፀሙባቸው ጥቃት ሁለት የጤና ባለሙያዎች ለከፋ ጉዳት ተዳርገዋል። • «የምታገለው ለማንም ብሔር የበላይነት አይደለም» አቶ በቀለ ገርባ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ኢቦላ ላይ ትኩረት ባደረገውና በአሜሪካ ኒዮርክ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት የፀጥታ ምክርቤት ስብሰባ ላይ ባደረጉት ንግግር በአገሪቱ ኢቦላ ያገረሸባቸውን አካባቢዎች ማንጊና እንዲሁም በቅርቡ ቫይረሱ የተከሰተባትን ቤኒን እንደጎበኙ ተናግረዋል። "ከቀድሞው በባሰ በጣም አሳስቦኛል፤ አሁንም ጉዳዩ እንዳስጨነቀኝ ነው" ሲሉ የሁኔታውን ፈታኝነት በንግግራቸው ገልፀዋል። በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙ የተናገሩት ዳይሬክተሩ በአጠቃላይ 161 የተረጋገጠና የተጠረጠሩ ታማሚዎች፣ 106 የሚሆን ሞት ሲመዘገብ በሕይወት የተረፉ 45 ሰዎች እንደሚገኙ ጠቅሰዋል። ማንኛውም እንቅስቃሴ በአገሪቱ መንግስት የሚመራና መንግስትም ጉዳዩን እየተከታተለ በማሳወቅ የተቻለውን እያደረገ እንደሆነ አስረድተው የዓለም ጤና ድርጅትም 200 የሚሆኑ የህክምና ባለሙያዎችን በሁለት ማዕከላት አሰማርቷል ብለዋል። 13, 700 የሚሆኑ ሰዎችም ክትባቱን ወስደዋል። • አቶ ጌታቸው አሰፋ የሀዋሳውን ጉባኤ ይታደማሉ? ነገር ግን ቦታዎቹ ገጠራማና ከከተማ የወጡ በመሆናቸው በተለይ የደህንነት ጉዳይ አሳሳቢ ነው ፤ የጤና ባለሙያዎቹ በታጠቁ ሰዎችና በተለያዩ ቡድኖች ጥቃት እየደረሰባቸው እንደሆነ ገልፀዋል። ከዚህ ቀደም በብኒ ከተማ 21 ሰዎች በሞቱበት የቦምብ ጥቃት ሳቢያ አገልግሎት የሚሰጡበትን ማዕከል ለቀናቶች ለመዝጋት ተገደዋል። የአካባቢው ሰዎች በእነርሱ ላይ እምነት አለመጣላቸውም ሌላኛው ተግዳሮት እንደሆነ ገልፀው የገንዘብ ድጋፉም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስምረዋል።
news-48488783
https://www.bbc.com/amharic/news-48488783
በአዲስ አበባ የኮሌራ በሽታ ምልክት ታየ
በአዲስ አበባ ከተማ የኮሌራ በሸታ ምልክት መታየቱን የጤና ጥበቃ ሚንስትሩ ዶ/ር አሚር አማን አስታወቁ።
የጤና ጥበቃ ሚንስትሩ እንዳሉት በአዲስ አበባ ከተማ በአጣዳፊ ተቅማጥ እና ትውከት ህመም ህክምና እያገኙ ካሉ አምስት ሰዎች መካከል የአንዱ በላብራቶሪ የኮሌራ በሽታ መሆኑ መረጋገጡን በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል። ዶ/ር አሚር የአጣዳፊ ተቅማጥ እና ትውከት ህመም በአዲስ አበባ፣ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በትግራይ እና በሶማሌ ክልሎች በአጠቃላይ በ365 ሰዎች ላይ የታየ እንደሆነ እና ከእነዚህም መካከል 9 የሚሆኑት ሰዎች የተያዙት በኮሌራ በሽታ ስለመሆኑ በላቦራቶሪ ተረጋግጧል ብለዋል። ሚንስትሩ በአጣዳፊ ተቅማጥ እና ትውከት እንዲሁም በኮሌራ በሽታ የተያዙ ሰዎች አፋጣኝ ህክምና እያገኙ እንደሆነ እና በሽታውን የመከላከል ሥራ ለማከናወን ከፍተኛ ዝግጅት እየተካሄደ እንደሆነ ጠቅሰዋል። • አተት እና ኮሌራ ምን እና ምን ናቸው? • በኢትዮጵያ የተፈናቃዮች ቁጥር ማሻቀብ የደቀነው ፈተና አክለውም ለበሽታው በከፍተኛ ሁኔታ ተጋላጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችም በቅርቡ የክትባት አገልግሎት የሚሰጥ ይሆናል ብለዋል። ማንኛውም ምልክቱ የታየባቸውን ሰዎች ወደ ጤና ተቋማት በፍጥነት መውሰድ እንዳለባቸው ሚንስትሩ አሳስበዋል። የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትም ትናንት ምሽት የኮሌራ ወረርሽኝ በአዲስ አበባ፣ በኦሮሚያ፣ በአማራ እና በትግራይ ክልሎች የመከሰቱን ይፋ አድርጓል። ኢንስቲትዩቱ ወረርሽኙ በቀላሉ ሊዛመት እና ከፍተኛ ጉዳት ሊያስከትል ስለሚችል ሕዝቡ ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊያደርግ እንደሚገባ ገልጿል። በዚህም የመጸደጃ ቤት በአግባቡ መጠቀም፣ የመመገቢያ፣ የመጠጫ እና የውሃ ማስቀመጫ እቃዎችን በንጹህ ውሃ በማጠብ እና ከድኖ በማስቀመጥ ከዝንቦች እና ከበካይ ነገሮች መጠበቅ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አሳስቧል። ለማንኛውም አገልግሎት የሚውልን ከቧንቧ፣ ከጉድጓድ፣ ከምንጭ፣ ከወንዝ እና ከመሳሰሉት የተቀዳ ውሃን በውሃ ማከሚያ መድሐኒቶች በማከም ወይም በማፍላት መጠቀም እንደሚገባ፤ ምግብን ከማዘጋጀት፣ ከማቅረብ እና ከመመገብ በፊት ከመጸዳጃ ቤት መልስ እና ሕጻናትን ካጸዳዱ በኋላ እጅን በሳሙና መታጠብ እንደሚገባም ኢንስቲቲዩቱ አስታውሷል። • በአተት ሳቢያ የአምስት ሰዎች ሕይወት አለፈ ቢቢሲ ከሁለት ቀናት በፊት የአማራ ክልል የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጠቅሶ በአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት ሳቢያ የአምስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን መዘገቡ ይታወሳል። የኢንስቲትዩቱ የቅድመ ማስጠንቀቂያ እና የኅብርተሰብ ጤና ስጋት ቅብብል ባለሙያ አቶ አሞኘ በላይ እስከ ባለፈው ሃሙስ ድረስ 190 ገደማ ሰዎች በአተት መያዛቸውን ገልጸው፤ "በአተት ምክንያት በተቋም ደረጃ መሞታቸው የተረጋገጠው 5 ሰዎች ናቸው" ብለው ነበር። የተከሰተው አተት ነው ወይስ ኮሌራ? በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ፤ "አተት በተለያዩ ነገሮች ሊከሰት ይችላል፤ በባክቴሪያ፣ በቫይረስ፣ በፕሮቶዞዋ ወይም በምግብና ውሃ መመረዝ ሊከሰት ይችላል። አተትን ከሚያመጡት ውስጥ አንዱ ባክቴሪያ ሲሆን፤ ከባክቴሪያዎቹ ውስጥ ደግሞ አንዱ ኮሌራ ነው። "አተት ግን በብዙ ምክንያቶች ሊከሰት የሚችል ማንኛውም አጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት ማለት ሲሆን፤ ኮሌራ ማለት አተትን ከሚያስከትሉ ባክቴሪያዎች አንዱና በወረርሽኝ መልክ ሲከሰት ነው" ሲሉ አብራርተዋል። ኮሌራ አጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት በማስከትል በሰውነት ውስጥ የሚገኝን ፈሳሽ አሟጥጦ በማስወጣት አቅምን በማዳክም በአጭር ጊዜ ውስጥ ለሞት የሚዳርግ በሽታ ነው። የዓለም ጤና ድርጅት መረጃ እንደሚያሳየው ቪብሮ በተሰኘ ባክቴሪያ የተበከለ ውሃ እና ምግብ የኮሌራ በሽታን ያስከትላል። በየዓመቱ ከ1.3-4 ሚሊዮን ሰዎች በኮሌራ በሽታ እንደሚያዙ እና ከእነዚህም መካከል ከ21ሺ-143ሺ የሚያህሉት ህይወታቸውን እንደሚያጡ የዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ይጠቁማል።
news-56717684
https://www.bbc.com/amharic/news-56717684
የመጀመሪያው የጠፈር ጉዞና ያልተነገሩ ክስተቶቹ
"ይኸው ከዓለም ርቄ ትንሽዬ ኩባያ መሳይ ዕቃ ውስጥ እገኛለሁ። መሬት ሰማያዊ ናት። ምንም ማድረግ አልችልም።"
ዩሪ ጋጋሪን ይህ መስመር የተወሰደው ከድምፃዊ ዴቪድ ቦዊ ዘፈን ነው። ድምፃዊው ዩሪ ጋጋሪን ወደ ጨረቃ በተጓዘ ወቅት የተሰማው ይህ ሳይሆን አይቀርም ሲል ነው የገጠመው። ጋጋሪን ወደ ሕዋ የተጓዘው ሁለት ሜትር ስፋት ባላት መንኮራኩር ነው። የተጓዘው እንደ ጠፈር ተመራማሪ ሳይሆን እንደ መንገደኛ ነበር። በወቅቱ መንኮራኩሯ ውስጥ ያሉ ቁልፎችን መነካካት ክልክል ነበር። ያኔ ጋጋሪን ምድር ላይ ካሉ ተቆጣጣሪዎች ጋር ያደረገው ንግግር ተተይቦ ተቀምጧል። ጽሑፉ ጋጋሪን ባየው ነገር ቀልቡ እንደተሰረቀ ያትታል። ጋጋሪን በፈረንጆቹ ሚያዚያ 12፣1961 ያደረገው ጉዞ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ለሶቪዬት ሕብረት ትልቅ ድል ነበር። ነገር ግን ታሪክ ለመፃፍ ቆርጦ የተነሳው ጋጋሪን ትልቅ ብርታት የሚጠይቅ ሥራ ሠራ። ጋጋሪን ጥልቅ ወደሆነው ሚስጢራዊው ሕዋ ያለማንም እርዳታ ተጓዘ። ጠፈርተኛው ወደ ሕዋ ያደረገው ጉዞ ብዙ ጥያቄዎችን ለመመለስ ያቀደ ነበር። አንደኛው ጥያቄ ሰው ሕዋ ላይ መቆየት ይችላል ወይ የሚለው ነበር። ሌላኛው ዓላማ መንኩራኩሯ ሕዋ ላይ ምን ያህል መቆየት ትችላለች የሚለውን መፍታት ነው። የዛኔ መንኮራኩሮች ምን ያህል ደህንነታቸው የተጠበቀ ነው? ከምድር ጋር ግንኙነት ማድረግ ይቻላል? የምር ሰዎች ሕዋ ላይ መቆየት ይችላሉን? የሚሉት ጥያቄዎች ምላሽ አልነበራቸውም። "ያኔ ጋጋሪን የተወነጨፋባትን መንኮራኩር ለዘንድሮ ሳይንቲስቶች ብናቀርብ ማንም ሰው በዚህች ተስፋ በሌላት መንኮራኩር ለመብረር አይደፍርም" ይላሉ ኢንጅነር ቦሪስ ቼርቶክ። "በወቅቱ ሁሉም ነገር ሰላም ነው ብዬ ብዙ ሰነዶች ላይ ፈርሚያለሁ። ጉዞው ሊሳካ ይችላል ብዬም ማስረገጫ ሰጥቻለሁ። አሁን ዞር ብዬ ሳየው ብዙ አደጋ እንደተጋፈጥን ይሰማኛል።" የቮስቶክ ውድቀቶች ቮስቶክ የተሰኘው መንኮራኩር አስተኳሽ መሣሪያ አር-7 በተባለው ሮኬት ላይ ተመሥርቶ የተሠራ ነው። ሮኬቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የተተኮሰው በፈረንጆቹ 1957 ነበር። በዛው ዓመት የመጀመሪያው ሰው ሰራሽ ሳተላይት ስፑትኒክ 1 አር-7 ላይ ተመስርቶ ተተኩሶ ነበር። አር-7 አሁንም ሩስያ ወደ ጠፈር ሳይንቲስቶችን ለመላክ የምትጠቀምበት ሮኬት ነው። የመጀመሪያው የቮስቶክ ፕሮግራም የተወነጨፈው ግንቦት 1960 ነበር። ይህ ደግሞ ከጋጋሪን ጉዞ አንድ ዓመት ቀደም ብሎ የተካሄደ ነው። ለመጀመጀሪያ ጊዜ በቮስቶክ አማካይነት የተተኮሰችው ሳተላይት ከምድር ውጭ መውጣት ብትችልም ባጋጠማት ችግር ምክንያት አልተመለሰችም። ነሐሴ 19 ቤልካ እና ስትሬልካ የተሰኙት ውሾች ወደ ሕዋ ተላኩ። ጉዟቸውን በስኬት አጠናቀውም ተመለሱ። ይህ በ1960ዎቹ ከተካሄዱ ሙራዎች ብቸኛው ስኬታማ ጉዞ ነበር። ታኅሣሥ 1 ደግሞ ሌላ ሙከራ ተደረገ። አሁንም ተጓዦቹ ውሾች ነበሩ። ሙሽካ እና ፕቼልካ። ነገር ግን ይህ ጉዞ ስኬታማ አልነበረም። ውሾቹን የጫነችው ሳተላይት ስትመለስ ከታቀደላት ቦታ ውጭ በመሄዷ ምክንያት አየር ላይ እያለች ከነውሾቹ እንድትደመሰስ ተደረገ። ሶቪዬት ሕብረት ይቺን ሳተላይት ከጥቅም ውጭ ያደረገችው ቴክኖሎጂዋ ለሌላ አገር ተላልፎ እንዳይሰጥ በመስጋት ነበር። ሞስኮ ውስጥ የቆመው የዩሪ ጋጋሪን ሐውልት ጋጋሪን ሚያዝያ 12፣1961 ወደ ሕዋ ሲመጥቅ ጉዞው ከሞላ ጎደል ስኬታማ ነበር። በወቅቱ አጋጥመው ከነበሩ ችግሮች መካከል አንዱ መንኮራኩሯ ከታሰበላት ከፍታ [አልቲትዩድ] በላይ መውጣቷ ነው። መንኮራኩሯ 'ፍሬን' ባይኖራት ኖሮ ጋጋሪን ማድረግ የሚችለው ሳተላይቷ በራሷ ጊዜ ወደ ምድር እንድትወርድ መጠበቅ ብቻ ነው። ምንም እንኳ ጋጋሪን ከሳምንት በላይ ለሚሆን ጊዜ ምግብና መጠጥ ይዞ ቢሄድም መንኮራኩሯ ከፍታዋን ጥላ ብትሄድ ኖሮ ወደ ታች የምትወርደው በራሷ ጊዜ ስለሆነ ምግብና መጠጡ ላይበቃው ይችል ነበር። ዕድሜ ለፍሬኑ ጋጋሪን በረሃብ ከመሞት ተርፏል። ሌላኛው ሳተላይቷ የገጠማት ችግር ውስጥ የነበረው ሙቀት መጠን እጅግ መጨመር ነው። ጋጋሪን ወደ ምድር ሲመለስ በጣም ይወዛወዝ ስለነበር ራሱን ሊስት ይችል ነበር። ጋጋሪን ወደ ምድር ሲመለስ መንኮራኩሯ ከምድር ጋር ተላትማ ከመፈራረሷ በፊት በፓራሹት ወርዶ ነው የተረፈው። አንድ የሕዋ ጉዞ ስኬታማ ነው የሚባለው ጠፈርተኛው መንኮራኩሯ ውስጥ ሆኖ ምድር ላይ ማረፍ ሲችል ነው። ይህንን ተከትሎ ባለሥልጣናት ጋጋሪን የመጨረሻዎቹን ኪሎ ሜትሮች ከመንኩራኩሯ ጋር አልተጓዘም በሚል ጉዞው ስኬታማ አልነበረም ብለው ነበር። ኋላ ላይ ግን በትክክል ተወንጭፎ ምድርን ዞሮ ከነጠፈርተኛው በመመለሱ የጋጋሪን ጉዞ ስኬታማ ተብሎ እንዲመዘገብ ተደረገ። ቢቢሲ ሩስኪ፤ ለበርካታ ሩስያዊያን ሳይንቲስቶች ጋጋሪን በተጓዘባት መንኮራኩር ዘንድሮ ትጓዛላችሁ ወይ? ብሎ ላቀረበው ጥያቄ፤ ብዙዎቹ ጋጋሪን ያኔ የተጓዘው ስለተጋረጠበት አደጋ ብዙም ስላላወቁ ነው ሲሉ መልሰዋል። የገበሬ ልጅ የሆነው ጋጋሪን ወደ ጠፈር ሲመነጠቅ ማንም አያውቀውም ነበር። ሲመለስ ግን የምድራችን ታዋቂው ሰው ሆነ። ጋጋሪን ወደ ምድር ከተመለሰ በኋላ የሶቪዬት ሕብረትን የሕዋ ፕሮግራም ለማስተዋወቅ ወደ ቼኮስሎቫኪያ፣ ቡልጌሪያ፣ ፊንላንድ፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ አይስላንድ፣ ኩባ፣ ብራዚል፣ ካናዳ፣ ሃንጋሪና ሕንድ ተጉዟል። ጋጋሪን በድጋሚ ወደ ሕዋ ሊሄድ ዕቅድ ተይዞለት የነበረ ቢሆንም የአገር ጀግና በመሆኑ ምክንያት እንዳይበር ታግዷል። ነገር ግን በርካታ ጠፈርተኞችን አሰልጥኗል። ጋጋሪን 1968 ላይ በአውሮፕላን አደጋ ምክንያት በ34 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
50401660
https://www.bbc.com/amharic/50401660
በስጋት የሚናጡት ዩኒቨርስቲዎች
ባለፈው ቅዳሜ ምሽት ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ከደረሰውና የሁለት ተማሪዎችን ሕይወት ከቀጠፈው ግጭት በኋላ በአማራና በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ አንዳንድ ዩኒቨርስቲዎች ስጋት መኖሩን ያነጋገርናቸው ተማሪዎችና መምህራን ገልጸዋል።
ካለው ስጋትና ፍርሃት የተነሳም ትምህርት የተቋረጠባቸው ዩኒቨርስቲዎች መኖራቸውን፣ በዩኒቨርስቲዎቹ የመከላከያ ኃይል መግባቱንም ለማወቅ ችለናል። ትናንት በደምቢ ዶሎ ዩኒቨርስቲ አንድ ተማሪ መሞቱ የተሰማ ሲሆን፤ በሌሎች ዩኒቨርስቲዎችም አለመረረጋጋት ነበር። • ከወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ግጭት ጋር በተያያዘ 13 ተማሪዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ • በአክሱም ዩኒቨርስቲ ግጭት የተጠረጠሩ ተያዙ በደምቢ ዶሎ ዩኒቨርስቲ በስለት ተወግቶ የተገደለው ተማሪ ጥቃቱን ማን እንዳደረሰበት አለመታወቁን የሚናገሩት የዩኒቨርስቲው ምክትል ፕሬዝዳንት ቡሊ ዮሐንስ (ዶ/ር) ከዚህ ጥቃት በፊትም ሆነ በኋላ በዩኒቨርስቲው ምንም ዓይነት ግጭት አለመከሰቱን አረጋግጠዋል። ሰኞ ጠዋት በመደወላቡ ዩኒቨርስቲ ከአማራ ክልልና ከኦሮሚያ ክልል በሄዱ ተማሪዎች መካከል በተከሰተው ግጭት ዘጠኝ የሚሆኑ ተማሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት አቡበከር ከድር (ዶ/ር ) ለቢቢሲ ተናግረዋል። በወለጋና በአምቦ ዩኒቨርስቲም ተማሪዎች ወደ ክፍል ገብተው ለመማር ፈቃደኛ ሳይሆኑ መቅረታቸውንና በግቢዎቹ በጸጥታ አካላት ጥብቅ ጥበቃ እየተደረገ መሆኑን ያነጋገርናቸው ተማሪዎች አስረድተዋል። ያነጋገርነው የወለጋ ዩኒቨርስቲ የሁለተኛ ዓመት ተማሪ፤ እሁድ ዕለት የጸጥታ ኃይሎች በዩኒቨርስቲው 610 ሕንጻ ላይ ከገቡ በኋላ ተማሪዎች የመረበሽ ስሜት ውስጥ እንዳሉ ያስረዳል። የዩኒቨርስቲው የጸጥታ አስከባሪ አካላትና የተማሪው ቁጥር በአቻነት እንደሚገኝ የሚናገረው ይህ ተማሪ፤ ብዙ ተማሪዎች በፍርሃት ወደ ቤተሰቦቻቸው እየተመለሱ መሆኑን ተናግሯል። • የደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ስጋት ላይ ነን ይላሉ • በመቱ ዩኒቨርስቲ ብሔር ተኮር ውጥረት ነግሷል በዩኒቨርስቲዎች የተከሰተውን ችግር ለማረጋጋት የኦሮሚያ ልዩ ኃይል፣ ፌደራል ፖሊስና የመከላከያ ሠራዊት መግባቱን የየተቋማቱ ተማሪዎችና ኃላፊዎች ለቢቢሲ አረጋግጠዋል። ተማሪዎቹ የጸጥታ ኃይሎች በግቢው ውስጥ ቢኖሩም እንኳ ካለባቸው ፍርሃት የተነሳ ሳይነጣጠሉ በጋራ በመሆን በማሳለፍ ላይ መሆናቸውን ገልጸው፤ የተወሰኑት ደግሞ በዩኒቨርስቲዎቹ አቅራቢያ ወደሚገኝ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ መጠለላቸውን ይናገራሉ። በወለጋ ዩኒቨርስቲ የ3ኛ ዓመት ተማሪ የሆነው ሌላ ተማሪ ሰሞኑን በወልዲያ ዩኒቨርስቲ በተፈጠረው ነገር ተማሪዎች እጅግ መቆጣታቸውን ገልጾ፤ ሰላማዊ ሠልፍ በማድረግ ድምጻቸውን እንዳያሰሙ ነቀምት ከተማ በሚገኘው ኮማንድ ፖስት ምክንያት አለመቻላቸውን ይናገራል። ይሁን እንጂ ቁጣና ተቃውሟቸውን የረሃብ አድማ በማድረግ መግለፃቸውን ተናግሯል። "ወንድሞቻችን እየሞቱ፣ ወንድሞቻችን እየተቸገሩ እኛ እንዴት ምግብ እንመገባለን ብለን [ሰኞ] ዕለት ምሳችን ባለመመገብ ሀዘናችንን ገልፀናል" በማለት ዩኒቨርስቲ ውስጥ በብሔር ምክንያት የተፈጠረ ችግር እንደሌለ ያስረዳል። ቢቢሲ ያነጋገረው የወለጋ ዩኒቨርስቲ መምህር በበኩሉ፤ ተማሪዎች ላነሱት ቅሬታ ዩኒቨርስቲው የሰጠው መልስ እንደሌለ ገልጾ ትምህርት መቋረጡን አረጋግጧል። "እኛ ለማስተማር ዝግጁ ነን። በየእለቱ ሥራችን ላይ ብንኖርም አንድ ተማሪ ተረጋግቶ መማር የሚችለው በሥነ ልቦና የተረጋጋ አካባቢና ሁኔታ ውስጥ ሲኖር ነው" ብሏል። ወልዲያ ዩኒቨርስቲ ሐሰን አሚን ሐሰን በወልዲያ ዩኒቨርስቲ ተማሪ የነበረ ሲሆን ሕይወታቸውን ካጡት ሁለት ተማሪዎች አንዱ ነው። አባቱ አቶ አሚን ሐሰን ልጃቸው የተወለደው አባታቸው በሞተ በወሩ መሆኑን ያስታውሳሉ። አባታቸውን ለማስታወስ በማለትም ለልጃቸው የአያቱን ስም አውጥተውለታል። ልጃቸው የሞተ ማታ ደውለው እንዳወሩት የሚናገሩት አቶ አሚን፣ ከሐሰን ጋር የአባትና የልጅ ጨዋታ መጨዋወታቸውን በመናገር በእለቱ ስለተፈጠረው ነገር ምንም ነገር እንዳላወሩ ያስረዳሉ። ስለልጃቸው ሲናገሩም "ጠባዩ ውሃ ነው" በማለት በጎረቤት፣ በወዳጅ ዘመድ በትምህርት ቤትም ሆነ በመስጂድ ምስጉን ልጅ እንደነበር ገልፀዋል። አስተምሬ ወደ ዩኒቨርስቲ ስልከው ለመንግሥት ነው የሰጠሁት ያሉት አቶ አሚን "ልጆቻችንን ደብተርና ብዕር ገዝተን ልከን እንዴት ሕይወታቸውን አጥተው ይላኩልናል?" ሲሉ ለልጃቸው ሕይወት መጥፋት የፌደራል መንግሥቱን ተጠያቂ እንደሚያደርጉ ያስረዳሉ። ስለ ስለልጃቸው አሟሟት የሰሙት አስክሬኑን ይዘውላቸው ከሄዱ ሰዎች መሆኑን ገልፀዋል። ሰኞ ዕለት በወልዲያ ከተማ ውስጥ ከኦሮሚያ ክልል በሄዱ ተማሪዎች ላይ የደረሰውን ድብደባና ግድያ በማውገዝ ሰልፍ የተደረገ መሆኑን ያነጋገርነው የዩኒቨርስቲው ተማሪ ገልጿል። አሁንም ቢሆን በፌደራል የጸጥታ ኃይሎች ጥበቃ እንደሚንቀሳቀሱም ጨምሮ ተናግሯል። "አሁንም ፈርተን አንድ ቦታ ላይ ተሰብስበን ነው ያለነው፤ እኛ ፍላጎታችን ወደ ቤተሰቦቻችን መመለስ ነው" የሚለው ይህ ተማሪ ዩኒቨርስቲው እንዲሄዱ እንዳልፈቀደላቸው ይናገራል። "መንቀሳቀስ ፈርተናል፤ ራሳችን ወጥተን ለመሄድ ደግሞ [ጥቃት ይደርስብናል] ስንል ፈርተናል፤ መላው ጠፍቶን ተቀምጠናል" በማለት ያለባቸውን ስጋት ለቢቢሲ አስረድቷል። ሰኞ ዕለት ተማሪዎችን የሚያወያዩ አካላት ለግቢው ጸጥታ እንደሚቆሙ ተናግረው ቢወጡም፤ ማስፈራሪያና ዛቻ እንደሚደርስባቸው የሚናገረው ይህ ተማሪ በዩኒቨርስቲው ግቢ ውስጥ የመከላከያ፣ የፌደራል ፖሊስ እና የአማራ ልዩ ኃይል በብዛት እየተንቀሳቀሰ መሆኑንም ተናግሯል። በተጨማሪም በወልዲያ ዩኒቨርስቲ የመማር ማስተማሩ ሂደት ሙሉ በሙሉ መቋረጡንና ከኦሮሚያ ክልል የመጡ ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው ለመሄድ በጋራ እየጠየቁ መሆኑንም አስረድቷል። • በደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ በተቀሰቀሰ ረብሻ የአንድ ተማሪ ህይወት አለፈ • "ትልቅ ዋጋ ተከፍሎበት ዋጋ ያላገኘሁበት ቢኖር ትምህርት ነው" በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች በተደጋጋሚ የሚነሳው ብሔርን መሰረት ያደረገ ግጭት ምን ያሳያል? ስንል ያነጋገርናቸው የፖለቲካ ምሁሩ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና "የአገሪቱ ልሂቃን ወደ ቀኝና ወደ ግራ የወጠሩትን ፖለቲካ ወጣቱ በገባው መንገድ መልስ ለመስጠት ይሞክራል" ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተውናል። አክለውም በአገሪቱ ውስጥ ያለው የፖለቲካ ውጥረት ለእንደዚህ አይነት ግጭቶች መንስዔ መሆኑን ያስረዳሉ። "በአገሪቱ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ልሂቃን የሚያደርጉትን ነገር በግብታዊነት ከማድረግ ባሻገር በኃላፊነት፣ የሚያስከትለውን በማሰብ ስለማይሠሩ እንዲህ ዓይነት የፖለቲካ ውጥረት ሊፈጥ ችሏል" ሲሉም አስተያየታቸውን ያጠቃልላሉ።
news-50093601
https://www.bbc.com/amharic/news-50093601
ፕሬዝዳንት ሙሴቪኒ ቦቢ ዋይንን የኡጋንዳ ጠላት ሲሉ ተናገሩ
የኡጋንዳው ፕሬዝዳንት ዮዌሪ ሙሴቪኒ አስተዳደራቸውን በመተቸት የሚታወቀውን የቀድሞ ድምጻዊ የአሁን ፖለቲከኛ፣ ቦቢ ዋይንን "የሀገሪቱ ብልፅግና ጠላት" ሲሉ ከቢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገለፁ።
የ36 ዓመቱ ድምጻዊና በደጋፊዎቹ ዘንድ "የምንዱባኖች ፕሬዝዳንት" ተብሎ የሚጠራው ቦቢ ዋይን፤ ከሁለት ዓመት በፊት የአገሪቱ ምክር ቤት አባል ሆኖ ከተመረጠ በኋላ ከፕሬዝዳንቱ ጋር አይንና ናጫ ሆኗል። ቦቢ ዋይን እውነተኛ ስሙ ሮበርት ኪያጉላኒ ሲሆን፣ በ2021 ፕሬዝዳንት ሙሴቪኒን ተፎካካሪ ሆኖ ለፕሬዝዳንትነት እንደሚወዳደር ተናግሯል። • ሙዚቀኛው የፓርላማ አባል በኡጋንዳው ፕሬዝዳንት ላይ በመሳለቁ ተከሰሰ • እንግዳ ሰዎችን በመርዳት ላይቤሪያ ከአፍሪካ ቀዳሚ ሆነች ቦቢ ዋይን የህዝቦች ኃይል የተሰኘ እንቅስቃሴ መሪ ሲሆን ፕሬዝዳንት ሙሴቪኒ የ33 ዓመት የሥልጣን ዘመን ጨቋኝ መንግሥት ሲመሩ ቆይተዋል ሲል ይከሳቸዋል። ሙሴቪኒ ከቢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ ይህንን ክስ ያጣጣሉ ሲሆን ቦቢ ዋይንን ግን በጠላትነት እንደሚመለከቱት ተናግረዋል። "ቦቢ ዋይን አሜሪካ ሄዶ ባለሃብቶች ኡጋንዳ መጥተው ሀብታቸውን እንዳያፈሱ ተናገረ። ይህ ማለት የኡጋንዳ እድገት ጠላት ነው ማለት ነው። ወደ ባህር ማዶ ሄደህ ባለሀብቶች እንዳይመጡ ከቀሰቀስክ ብልፅግና ላይ ጦርነት ከፍተሃል ማለት ነው። ስለዚህ ስለምን መጥቶ የዚህ ብልፅግና ተቋዳሽ መሆን ይፈልጋል?" ሲሉ ተናግረዋል። ቦቢ ዋይን የሙዚቃ ሥራውን እንዳያቀርብ ስለመከልከሉም ሲናገሩ "ከፖሊስ ጋር በዝርዝር በጉዳዩ ላይ ባላወራም ለዚያ [አሜሪካ ሄዶ ባለሃብቶች ወደ ኡጋንዳ እንዳይመጡ በመቀስቀሱ] ይመስለኛል" ብለዋል። ፕሬዝዳንት ሙሴቪኒ በኡጋንዳ በፕሬዝዳንትነት ማከናወን የሚፈልጓቸው በርካታ ነገሮች እንዳሉ ተናግረው ከስልጣን ሊወርዱ የሚችሉት በፓርቲያቸው ከተጠየቁ ብቻ መሆኑን ገልፀዋል። "ቤቴ እየጠበቀኝ ነው፤ ነገር ግን እንደ ኡጋንዳዊ ገና የማከናውነው በርካታ ነገር አለኝ። . . . ፓርቲው የአንጋፋዎችን ድጋፍ አንፈልግም ብሎ ከወሰነ ለቅቀን ሌሎች ጉዳዮችን ለመከወን ደስተኞች ነን" ብለዋል። • የቅማንት የማንነትና የራስ አስተዳደር ጥያቄ ከየት ወደ የት? • ተማሪዎች በተመደቡበት ዩኒቨርስቲ ብቻ ነው መማር የሚችሉት- የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሙሴቪኒ አክለውም በኡጋንዳ ሥራ አጥ ወጣቶችን "እንደ ስጋት ሳይሆን እንደ እድል" እንደሚመለከቷቸውም ተናግረዋል። ሙሴቪኒ በግብርናውና በኢንፎርሜሽነ ቴክኖሎጂ መስክ ገና ያልተነካ እድል እንዳለ ገልፀው ወጣቶች በዘርፉ ለመሰማራት መጣር እንዳለባቸውም መክረዋል። "ሱፍ ለብሰው ቢሮ ለመዋል ብቻ ሳይሆን በግብርና፣ በኢንደስትሪ፣ በፋብሪካዎች፣ በአገልግሎት ሰጪው ዘርፍና በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ላይ ለመሰማራት አእምሯቸውን ማዘጋጀት ይኖርባቸዋል፤ በእነዚህ መስኮች ሥራ ለመፍጠር ጠንክረን እየሰራን ነው" ብለዋል።
news-49950130
https://www.bbc.com/amharic/news-49950130
ሳዑዲ አረቢያ፡ የውጭ አገር ዜጋ ጥንዶች ሆቴል እንዲከራዩ ተፈቀደ
የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት ወደ አገሪቷ የሚመጡና ያልተጋቡ የውጭ አገር ዜጋ ጥንዶች ሆቴል ተከራይተው አንድ ላይ ማሳለፍ እንደሚችሉ ገለፀ።
ሳዑዲ አረቢያ ለጎብኝዎች ሳቢ ለመሆን ሕጎቿን እያለዘበች ነው። ይህ የሆነው በአገሪቷ የወጣውን አዲሱን የቪዛ ሕግ ተከትሎ ሲሆን ሕጉ የሳዑዲ አረቢያ ሴቶች በሆቴል ውስጥ ብቻቸውን ማሳለፍ እንደሚችሉም ይፈቅዳል። ከዚህ ቀደም ጥንዶች በሆቴል ለማሳለፍ በጋብቻ የተሳሰሩ መሆናቸውን ማረጋገጥ ይጠበቅባቸው ነበር። • ሳዑዲ አረቢያ ሴቶች ያለ ጠባቂ እንዲጓዙ ፈቀደች • የሳዑዲ ሴቶች መሪ ጨበጡ የሕጉ መሻሻል የአገሪቷ መንግሥት ጎብኝዎችን ለመሳብ የወሰደው እርምጃ ነው ተብሏል። ከዚህ ቀደም ጥንዶች በጋብቻ መተሳሰራቸውን የሚያሳይ ማረጋገጫ ካላቀረቡ ሆቴል መከራየት እንደማይችሉ የሚከለክለው ሕግ አሁን ላይ ለውጭ አገር ዜጎች ተፈቅዷል። የአገሪቷ የቱሪዝምና ብሔራዊ ቅርስ ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ "ማንኛውም የሳዑዲ ዜጋ ሆቴል ለመከራየት የቤተሰብ መታወቂያ አሊያም የግንኙነታቸውን ሁኔታ ማረጋጋጫ እንዲያሳዩ ይጠየቃሉ" ይላል። ይሁን እንጂ ይህ ሕግ ከውጭ አገር ለሚመጡ ጎብኝዎች፣ የሳዑዲ አረቢያ ዜጎችን ጨምሮ ሁሉም ሴቶች መታወቂያ በማሳየት ብቻ ሆቴል መከራየትና በክፍሎቹ በነፃነት ማሳለፍ እንዲችሉ ይፈቅዳል። አዲሱ የቪዛ ሕግ እንደሚያትተው የውጭ አገር ሴት ጎብኝዎች በአለባበሳቸው ሙሉ በሙሉ እንዲሸፈኑ ባይገደዱም የሰውነት ክፍላቸውን የማያጋልጥ እንዲለብሱም ያዛል። የአልኮል መጠጦች መጠጣት ግን የተከለከለ ነው። በ'ኢንድፔንደንት' ጋዜጣ ኤዲተር የሆኑት ሳይመን ካልደር የቪዛ የሕጉ መሻሻል ወደ አገሪቷ የሚገቡ ጎብኝዎችን ቁጥር ሊያሳድገው ይችላል ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። • ሳዑዲ ሴቶች ወደ ስታዲየም እንዲገቡ ልትፈቅድ ነው በዓለማችን ሃብታም ከሆኑት አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ሳዑዲ አገሪቷን ለጎብኝዎችና ለባለሃብቶች ምቹ ለማድረግ ሕጎቿን እያለዘበች ትገኛለች። ልዑል አልጋ ወራሽ መሐመድ ቢን ሰልማን በቅርቡ ሴቶች መኪና እንዲያሽከረክሩና ያለምንም ጠባቂ ሴቶች ከአገር ውጭ ጉዞ እንዲያደርጉ የሚያዘውን ሕግ ጨምሮ በጣም የከረሩ ሕጎች ላይ የተወሰነ ማሻሻያ ማድረጋቸው ይታወቃል። ይሁን እንጂ ሳዑዲ አረቢያ ከጋዜጠኛ ጀማል ኻሾግጅ ግድያ ጋር በተገናኘ አሁንም ገፅታቸው እንደጠለሸ ነው። • ስለ ጀማል ኻሾግጂ አሟሟት እስካሁን የምናውቃቸው እውነታዎች
news-52830838
https://www.bbc.com/amharic/news-52830838
119 ቤተ እስራኤላውያን ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል አቀኑ
119 ቤተ እስራኤላውያን ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል ማቅናታቸው ተገለጸ። እንደ የእስራኤል መገናኛ ብዙሃን ከሆነ ቤተ እስራኤላውያኑ ከቀናት በፊት ነው የተጓዙት።
ቤተ እስራኤላውያን ከኢትዮጵያ ተነስተው እስራኤል ሲደርሱ ይህንኑ በኢትዮጵያ የሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ አረጋግጧል። ጥር ላይ የእስራኤል ካቢኔ 400 የሚጠጉ ቤተ እስራኤላውያንን እና የሃገሪቱን ህግ የሚያሟሉ ሰዎችን ለመወስድ የቀረበውን ዕቅድ ማጽደቁን ኤምባሲው ገልጿል። በዚህ ውሳኔ መሠረትም ነው 119ኙ ቤተ እስራኤላውያን ወደ ሃገሪቱ ያቀኑት። በኢትዮጵያ ያለው የአይሁዳዊያን ድርጅት ቅርንጫፍም የካቢኔውን ውሳኔ ለማስፈጸም እየሰራ መሆኑን ሲያስታውቅ በተመሳሳይም በኢትዮጵያ የሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲም ውሳኔውን በማስፈጸም ላይ መሆኑን አስታውቋል። ሰዎቹ እስራኤል ሲደርሱም የአይሁዳዊያን ድርጅት ሊቀመንበር አይዛክ ሄርዞግ እና አዲሷ የስደተኞች እና ውህደት ሚንስትር ፕኒና ታማኖ-ሻታ አቀባበል አድርገውላቸዋል። ፕኒና “አዲሱን ሥራዬን በምጀምርበት ወቅት 119ኙን ሰዎች በመቀበሌ ትልቅ ኩራት ተሰምቶኛል” ሲሉ ገልጸዋል። ቤተ እስራኤላውያኑ “ህልማቸው የሆነው ጉዞ እንዲሳካ ለዓመታት ጠብቀዋል። አሁን ሃገራቸው ደርሰዋል በዚህም ደስታ ተስምቶኛል” ብለዋል። አዲሱን ህይወታቸውን እንዲጀምሩ ለመርዳት በሁሉም ረገድ ድጋፍ ይደረግላቸዋልም ሲሉ ተናግረዋል። ቤተ እስራኤላውያኑ የገበቡበት ቀን ወደ እስራኤል ሲያቀኑ ህይወታቸው ያለፉ ቤተ እስራኤላውያን በሚታሰቡበት ዕለት ላይ መሆኑ ተዘግቧል። ቤተ እስራኤላውያን ከኢትዮጵያ ተነስተው እስራኤል ሲደርሱ የኮሮናቫይረስን ለመከላከል የሃገሪቱ ጤና ሚንስትር እና የትራንስፖርት ባለስልጣን ካወጧቸው ደንብ ጋር በተጣጣመ መልኩ ቤተ እስራኤላውያኑ በልዩ በረራ ነው እስራኤል የደረሱት ተብሏል። ቤተ እስራኤላውያኑ ወደተዘጋጀላቸው የለይቶ ማቆያ እንደገቡም ነው የሃገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ያስታወቁት። ከሁለት ወራት በፊት እስራኤል በተመሳሳይ 72 ቤተ እስራኤላውያንን ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል ወስዳለች። ባለፉት ጥቂት ቀናት እስራኤል 111 ስደተኞችን ከዩክሬን እንዲሁም 41 ደግሞ ከሩሲያ ተቀብላለች። ፕኒና ታማኖ-ሻታ ኢትዮጵያ ውስጥ የተወለዱ ቤተ እስራኤላዊ ሲሆኑ በቅርቡ ነበር በሚኒስተርነት የተሾሙት።
53245478
https://www.bbc.com/amharic/53245478
የሰኔ 15ቱ አይነት ግድያን ለመድገም ታቅዶ እንደነበር የፌደራል ፖሊስ ገለፀ
የፌደራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ዘላለም መንግሥቴ ዛሬ [ረቡዕ] ማምሻውን ከፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ጋር በመሆን ለመንግሥት የመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ የማክሰኞው የጃዋር መሐመድ እንቅስቃሴ የሰኔ 15 ግድያ ለመድገም ያለመ ነበር ሲሉ ተናገሩ።
ኮሚሽነሩ አክለውም አዲስ አበባ ተጀምሮ አዲስ አበባ የሚያልቅ የአመጽ እንቅስቃሴ የመምራት እቅድ ወጥቶ፣ በጀት ተበጅቶለት አመራሮችን ለመግደል ሲመራ የነበረ ነው ሲሉ የተፈጠረውን ሁኔታ ገልፀውታል። በፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የፌደራል ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ፈቃዱ ጸጋ በበኩላቸው ስለ እስክንድር ነጋ በአዲስ አበባ ሁከትና ግጭት እንዲፈጠር በመቀስቀስ ተጠርጥሮ በቁጥጥር ስር መዋሉን ተናግረዋል። ምክትል ኮሚሽነሩ በመግለጫቸው የድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ አስከሬን ወደ ቤተሰቦቹ እየተወሰደ ሳለ "መንገድ በማስቀየር፣ በመቀማት አመፁን አዲስ አበባ ተጀምሮ አዲስ አበባ እንዲያልቅ ሲቀሰቀስ" ነበር ካሉ በኋላ የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በኦሮሞ ባህል ማዕከል ስብሰባ ላይ እንዳሉ እያወቁ በቀጥታ ወደዚህ ተቋም ጥበቃውን ሰብረው መግባታቸውን ተናግረዋል። በወቅቱ የተፈጠረውን ሲገልፁም ትጥቅ አቀባብለው በመግባት አመራሮቹ ላይ ጭምር ተጨማሪ የሰኔ 15 ዓይነት ተግባር ለመፈፀም እንቅስቃሴ ተደርጓል ብለዋል። እንደ ኮሚሽነሩ ገለፃ ከሆነ በኦሮሞ ባህል ማዕከል የነበረው የፖሊስ ኃይል አመራሮቹ በሌላ አዳራሽ እንዳሉ በመናገር ወደዚያ እንዲሄዱ ማድረጋቸውን ገልፀው በመካከል ግን የአንድ የፖሊስ ህይወት ይዘውት ከመጡት ታጣቂ ቡድን በተተኮሰ ጥይት መሞቱን ገልፀዋል። በስፍራው የነበረውን የፀጥታ ኃይልም "በዚህ መካከል የመልስ ምት አለማደረጉ እንጂ የበርካታ ሰዎች ህይወት፣ የበርካታ አመራሮች ግድያ በዚያ ባህል ማዕከል ለመፈፀም እቅድ ነበረ" ሲሉ ተናግረዋል። የፖሊስ ምርመራ በዚህ መንገድ የእየተካሄደ መሆኑን የገለፁት ምክትል ኮሚሽነሩ "የታቀደ፣ የተጠና ረዥም ጊዜ የደም ማዕበል ለመፍጠር ሴራ የነበረ መሆኑ ለመግለጽ እንወዳለን። ምርመራችንም የሚያሳየው ይህንኑ ነው" ብለዋል። ምክትል ኮሚሽነር ዘላለም መንግሥቴ ለአገር ውስጥ መገናኛ ብዙኀን ማምሻውን በሰጡት በዚህ መግለጫ ከዚህ በፊትም ወደኋላ ሄደን የበርካታ ሰዎች ሕይወት ያለፈበትን የጥቅምቱን ግርግር መነሻ ያደረገ ምርመራም ከዚሁ ምርመራ ጋር አብሮ የተያያዘ እንደሚሆን ገልፀዋል። ኮሚሽነሩ የ97 ሰዎች ህይወት ያለፈበት ምርመራ በዚህ መንገድ አብሮ ይታያል ሲሉ አረጋግጠዋል። "በተለያየ ጊዜ በሚዲያ ላይ እየወጡ የሚጠሯቸው የተለያዩ የጦርነትና ብሄርን ከብሄር ለማጋጨት፣ ስርዓት ለማፍረስ የሚደረጉ የተለያዩ ቅስቀሳዎች ጭምር በዚህ ውስጥ ተካትተው የሚታዩ ይሆናል።" በፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ የፌደራል ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ፈቃዱ ጸጋ በበኩላቸው ስለ እስክንድር ነጋ ሲገልፁ "የመልስ ምት ያስፈልጋል፤ ኦሮሚያ ላይ እኔ የምወክለው እኔ የምታገልለት ህዝብ ነው እየተጎዳ ያለው፤ ስለዚህ አዲስ አበባ ያለህና ሌላ ቦታ ላይ ያለህ የዚህ ቡድን የሆንክ ተነስ" መልስ ስጥ የሚል ቡድን በአዲስ አበባ ውስጥ ተደራጅቶ እንቅስቃሴ ሲያደርግ ነበር ብለዋል። በዛሬው እለት እስከአሁን ድረስ በመረጃ 10 ወጣቶችን በተለያዩ 10 ቦታዎች በመመደብ ተሽከርካሪ በመመደብ የተለያዩ ሎጀስቲኮችን በማመቻቸት ቅስቀሳዎች ሲደረጉ እንደነበር ገልፀዋል። በአዲስ አበባ ውስጥ "የብሔር ግጭት ለመቀስቀስ" ተንቀሳቅሰዋል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በበኩሉ በሰጠው መግለጫ የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ አብን እና ባልደራስ በአዲስ አበባ የብሔር ግጭት ለመቀስቀስ ሞክረዋል ብለዋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው ከትናንት ጀምሮ በመዲናዋ የጸጥታ መደፍረስ እንዳጋጠመ አስታውቀዋል። የግል እና የመንግሥት ተሽከርካሪዎችን መሰባበር እና ማቃጠል፣ የዜጎችን ያፈሩትን ሃብት እና ንብረት የመዝረፍ እንቅስቃሴ ነበር" ያሉት ኮሚሽነሩ ይህን አጋጣሚ በመጠቀም በከተማዋ ሁከት እና ብጥብጥ በመፍጠር ህብረተሰቡ እርስ በእርሱ እንዲጋጭ እንቅስቃሴዎች ሲካሄዱ እንደነበር ገልፀዋል። የጸጥታ ችግር ለማረጋጋት ተልዕኮ ተሰጥቷቸው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የፖሊስ አባላት ላይ ከቀላል እስከ ሞት ድረስ ጉዳት ደርሶባቸዋል ያሉት ኮሚሽነሩ "ዛሬ እና ትናንት 57 የሚሆኑ የፌደራል እና የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት ላይ ጉዳት ደርሷል" በማለት ሁለት አባላት ህይወታቸው ማለፉን ተናግረዋል። በዜጎች ላይ ደረሰ ባሉት ጉዳት "ትናንት እና ዛሬ 8 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል" ካሉ በኋላም፣ ነዋሪዎች ህይወታቸው ያለፈው "በቦምብ፣ ጥይት፣ በድንጋይ እና በመሳሰሉት ነው" ብለዋል። • ፌደራል ፖሊስ ሃጫሉ ሁንዴሳ በጥይት የተመታው መኪናው ውስጥ መሆኑን ገለፀ • "በሦስቱ ሰኔዎች ጉዟችንን የማደናቀፍና ደም የማፍሰስ ሙከራዎች ተደርገዋል” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ንብረትነታቸው የግሰብ እና የመንግሥት የሆኑ 250 ተሽከርካሪዎች ተሰባብረዋል፣ 20 ተሽከርካሪዎች ተቃጥለዋል ሲሉም አክለዋል። "የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እና አባላት ጭምር የተሳተፉበት በተለይ የባልደራስ እና አብን አመራሮች እና አባላት በግልጽ ቲሸርት በመልበስ እና የፓርቲያቸውን ባንዲራ በመያዝ የከተማዋ የተለያየ አከባቢ ላይ በመንቀሳቀስ የብሔር ግጭት ለመፈጥር ሰፊ እንቅስቃሴ ለመፍጥር ሲደረግ ነበር" ብለዋል። "በተለያዩ የከተማው አቅጣጫ በመንቀሳቀስ አንዱ ብሔር ሌላውን ሊጠቃ እንደመጣ፤ እየተወረረ እንደሆነ" በማሳወቅ "እንዲከላከል" ቅስቀሳ ሲያደርጉ ነበር ብለዋል።
news-54970898
https://www.bbc.com/amharic/news-54970898
ፓኪስታን ፡ በካርቱን ስዕል ምክንያት የፈረንሣይ ምርቶችን መጠቀም ልታቆም ነው
አንድ የፓኪስታን እስላማዊ ቡድን የጠራውን የፀረ-ፈረንሳይ ተቃውሞን የፓኪስታን መንግሥት የፈረንሳይ ምርቶችን ላለመጠቀም በመወሰኑ ማቋረጡን አሳወቀ።
ሰልፎቹ የተጠሩት ፈረንሳይ የነቢዩ ሙሐመድን ካርቱን የማሳየት መብትን በመደገፏ ነበር። አንድ መምህር በክፍል ውስጥ በነበረ ውይይት ወቅት የነቢዩ መሐመድን ካርቱን ካሳዩ በኋላ መገደላቸውን ተከትሎ የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ማክሮን አገራቸው በሐይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አትገባም ሲሉ በጥብቅ ተከላክለዋል። ይህም በሙስሊሙ ዓለም ቁጣን ቀስቅሷል። የአክራሪው ተህሪክ ኢ-ላባይክ ፓኪስታን (ቲ.ኤል.ፒ) የተሰኘው ቡድን አባላት የፈረንሳይን ምርት ላለመግዛት የቀረበውን ውሳኔ የደገፉ ቢያንስ የሁለት ሚኒስትሮችን ፊርማ ያካተተ የስምምነት ቅጅዎችን አሳይተዋል። የፓኪስታን መንግስት በጉዳዩላይ በይፋ መግለጫ ካለመስጠቱም በላይ የፈረንሳይ ምርቶችን ያለመጠቀም አድማው እንዴት እንደሚተገበር አላሳወቀም። በፈረንሣይ እስልምናን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት ማክሮንን ከተቹ የፖለቲካ መሪዎች መካከል የፓኪስታኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢምራን ካን አንዱ ናቸው። ተቀዋሚዎቹ አሁንም ተጨማሪ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቀዋል። ደጋፊዎች ከእሁድ ጀምሮ ወደ መዲናዋ ኢስላማባድ የሚወስደውን ቁልፍ መንገድ በመዝጋታቸው ከፍተኛ የእንቅስቃሴ መስተጓጎል አስከትሏል። የቲ.ኤል.ፒ አመራሮች መንግሥት ለጥያቄዎቻቸው ምላሽ መስጠቱን ከተናገሩ በኋላ ተቃውሞው እንዲቋረጥ ተጠይቋል። የቡድኑ ቃል አቀባይ የሆኑት ኢጃዝ አሽራፊ ለሮይተርስ እንደተናገሩት "የፈረንሳይ ምርቶችን እንደማይጠቀም መንግሥት በይፋ እንደሚደግፍ ስምምነት ከፈረመ በኋላ የተቃውሞ ሰልፎቻችንን እያቆምንው ነው" ብለዋል። ለመገናኛ ብዙሃን ይፋ የተደረገው የስምምነት ሰነድ የሐይማኖታዊ ጉዳዮች ሚኒስትሩን እና የአገር ውስጥ ሚኒስትሩን ፊርማ ይዟል። የፈረንሣይ አምባሳደር ከአገር እንዲወጡ በማድረግ ዙሪያ ላይ ፓርላማው እንዲወስን መንግሥት ሐሳብ እንደሚያቀርብም ገልጿል። የፓኪስታን መንግሥት በስምምነቱ ላይ የሰጠው አስተያየት የለም። ቲ.ኤል.ፒ ቀደም ሲል ሐይማኖታዊ ስድብን ምክንያት በማድረግ ተቃውሞ ለማሰማት እጅግ ብዙ ሰዎችን በመሰብሰብ ይታወቃል። በፓኪስታን ሕግ መሠረት ነቢዩ ሙሐመድን በመሳደብ ጥፋተኛ የተባሉ ሰዎች የሞት ቅጣት ሊጣልባቸው ይችላል። በፈረንሳይ የመንግሥት በሐይማኖት ጉዳይ ላይ ጣልቃ ያለመግባት የአገሪቱ ዋነኛ መገለጫ ነው። በትምህርት ቤቶች እና በሌሎች ሕዝባዊ ቦታዎች ሀሳብን በነፃነት መግለጽም የዚህ አካል ሲሆን የአንድን የተወሰነ ሐይማኖት ስሜት ለመጠበቅ የሃሳብ ነጻነቱን መግታት ብሔራዊ መገለጫውን እንደሚያደፈርስ ተደርጎ ይወሰዳል። 'ቻርሊ ሄብዶ' የተሰኘው መጽሔት የነቢዩ ሙሐመድ ካርቱን ይዞ መውጣቱን ተከትሎ እ.አ.አ በ2015 በፓሪስ ውስጥ የጥቃት ዒላማ ቢሆንም የካቶሊክን እና የአይሁድን እምነት ጨምሮ ሌሎች ሐይማኖቶችም የሚያመለክቱ ስዕሎችን ይዞ ወጥቷል። የፈረንሣይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቀደም ሲል በበርካታ ሙስሊሞች በብዛት በሚገኙባቸው አገሮች ውስጥ የፈረንሳይ ሸቀጦችን ላለመጠቀም የሚደረጉ ጥሪዎችን "መሠረተ ቢስ" ብለው "በአፋጣኝ መቆም" እንዳለባቸውም ገልጸው ነበር። ባለፈው ወር ለተገደሉት መምህር ክብር የሰጡት ፕሬዝዳንት ማክሮን ፈረንሳይ "ካርቱኑን አታቆምም" ብለዋል።
news-57140209
https://www.bbc.com/amharic/news-57140209
ባለፈው እሑድ በፍልስጤም-እስራኤል ግጭት ከፍተኛ የሟቾች ቁጥር ተመዘገበ
እስራኤልና ፍልስጤም ግጭት ከተጀመረ ወዲህ እንደ እሑድ ዕለት በርካታ ሞት የተመዘገበበት ዕለት የለም፡፡
የጋዛ ባለሥልጣናት እንደሚሉት በትንሹ 40 ሰዎች እስራኤል ባደረሰችው የአየር ጥቃት ተገድለዋል፡፡ የእስራኤል ባለሥልጣናት በበኩላቸው የፍልስጤም ተዋጊዎች በድምሩ ሦስት ሺህ ሮኬቶችን አስወንጭፈዋል ይላሉ፡፡ የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ግጭቱ ወደማያባራ ጦርነት እንዳይሄድ ፍርሃት አለኝ ብለዋል፡፡ የተባበሩት መንግሥታት በበኩሉ በጋዛ የነዳጅ እጥረት እየተከተለ መሆኑ አሳስቦኛል ብሏል፡፡ ምክንያቱም ሆስፒታሎች ኃይል የሚያገኙት ከዚሁ ስለሆነ ነው፡፡ በርካታ ቁስለኛ ባለበት ሁኔታ ሆስፒታሎች ኃይል ከተቋረጠባቸው ለብዙዎች ሞት ምክንያት እንዳይሆን ስጋት አለ፡፡ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የመካከለኛው ምሥራቅ ሰላም ማስተባበርያ ዴስክ ምክትል ኃላፊ ሊየን ሀስቲንግስ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ለጋዛ ነዳጅ ለማቅረብ የእስራኤል ባለሥልጣናት እንዲፈቅዱ ጠይቀው ተከልክለዋል፡፡ ነዳጅ ለማቅረብ አካባቢው አስተማማኝ እንዳልሆነም ተነግሮናል ብለዋል፡፡ የጋዛ ባለሥልጣናት እንደሚሉት ትናንትና እሑድ ብቻ 16 ሴቶችና 10 ሕጻናትን ጨምሮ በድምሩ 42 ፍልስጤማዊያን እስራኤል ባደረሰችው የአየር ጥቃት ተገድለዋል፡፡ ሁለት ሕጻናትን ጨምሮ በድምሩ 10 ሰዎች ከእስራኤል ወገን ተገድለዋል፡፡ ይህ አሐዝ ግን ግጭቱ ካገረሸ ጀምሮ የተመዘገበ ነው፡፡ በጋዛ እስከ ትናንት ድረስ ብቻ ድምር የሟቾች ቁጥር 188 አልፏል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 55ቱ ሕጻናት ናቸው፡፡ 33 የሚሆኑት ሴቶች ናቸው፡፡ በድምሩ ከአንድ ሺህ በላይ ሰዎችም ቆስለዋል፡፡ እስራኤል እንደምትለው ከሟቾቹ አብዛኛዎቹ ተዋጊዎች ናቸው፡፡ ትናንት እሑድ እኩለ ሌሊት ላይ እስራኤል በወሰደችው የአየር ጥቃት 3 ሕንጸዎች ሙሉ በሙሉ ፈርሰዋል፡፡ ሕንጻዎቹ የሚገኙት ደግሞ ሰው በሚበዛባቸው ጎዳናዎች ላይ ነበር፡፡ ሐማስ የአጸፋ ምላሽ የሰጠ ሲሆን ሮኬቶችን ወደ ደቡባዊ እስራኤል አስወንጭፏል፡፡ የማስጠንቀቂያ ደውሉን ተከትሎ ሚሊዮን የሚሆኑ እስራኤላዊያን ወደተዘጋጁላቸው ምሽጎቻቸው ተደብቀዋል፡፡ ፍልስጤማዊያንም በጥቃቱ ላለመሞት የሚቻላቸውን ቢሞክሩም በተጨናነቀው ጋዛ ወደየትም መሸሸግ አልቻሉም፡፡ ሐማስ የሚያስወነጭፋቸው ሮኬቶች አሽከሎን፣ አሽዶድ እና ኔቲቮት በሚባሉ ደቡባዊና መካከለኛ የእስራኤል ከተሞች ነው የሚወድቁት፡፡ እስከአሁን ይህ ነው የሚባል ጉዳት ስለማድረሳቸው የተዘገበ ነገር የለም፡፡ አብዛኛዎቹ የሐማስ የሮኬት ጥቃቶች በእስራኤል አይረን ዶም ዲፌንስ ሲስተም በሰማይ ሳሉ የሚመክኑ ናቸው፡፡
54748694
https://www.bbc.com/amharic/54748694
ናይጄሪያውያን የሚቃወሙትን ልዩ የፖሊስ ኃይል እንግሊዝ አሰልጥናለች ተባለ
ዘረፋን ለማስቆም የተቋቋመውና ሳርስ ተብሎ የሚጠራውን የናይጄሪያ ልዩ የፌደራል ፖሊስ ኃይል አባላት የእንግሊዝ መንግሥት እንዳሰለጠናቸው የእንግሊዝ የፓርላማ አባል አስታውቀዋል።
ስልጠና ከመስጠትም በተጨማሪ በጦር መሳሪያዎችም እገዛ እንዳስታጠቃቸው በተጨማሪ ይፋ አድርገዋል። ይህ እገዛም ለአራት አመታት ያህል ቀጥሏል ተብሏል። የሌበር ፓርቲ ፖለቲከኛዋና የፓርላማ አባሏ ኬት አዛሞር ኦሳሞር በትዊተር ገፃቸው እንዳስታወቁት አገራቸው ከጎሮጎሳውያኑ 2016 ጀምሮ ድጋፍ ያደርግ እንደነበር ነው። ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ሰዎችን በማሰር፣ ማሰቃየትና ግድያም ይፈፅማል በሚል ከፍተኛ ውግዘት እየቀረበበት ያለውን ልዩ ፖሊስ ተቃውሞ በናይጄሪያ ብቻ ሳይሆን በዩኬና በዲያስፖራ ናይጄሪያውያን አማካኝነት ለሳምንታት ያህል ተካሂዷል። ፖሊሶች አንድን ሰው ሲገድል የሚያሳይ ቪዲዮ መውጣቱን ተከትሎም ነው ተቃውሞቹ የተቀጣጠሉት። የፖሊስ የጭካኔ በትርን ተቃውመው ከወጡ ሰልፈኞች መካከል 69 ሰዎች መገደላቸውን የናይጄሪያው ፕሬዚዳንት ሙሃማዱ ቡሃሪ ባለፈው ሳምንት ገልፀው ነበር። ከፍተኛ ተቃውሞ የቀረበበት ሳርስ እንዲበተን ቢደረግም የሳርስ አባላት በሌሎች የፖሊስ ክፍሎች እየተሰማሩና እየተመደቡ ነው የሚሉ ጉዳዮች መሰማታቸውን ተከትሎም እንደገና ተቃውሞቹ የቀጠሉት። ሰልፈኞቹ እነዚህ የሳርስ አባላት ለፈፀሙት ወንጀል ህግ ፊት መቅረብ አለባቸውም እያሉ ነው፤ እንዲሁም በአስተዳደሩ ላይ ማሻሻያም ያስፈልጋል እያሉ ነው። በተለይም ጥቅምት 10/ 2013 ዓ.ም በንግድ ማዕከሏ ሌጎስ በፀጥታ ኃይሎች የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 12 መድረሱን የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት አምነስቲ ማሳወቁን ተከትሎም ነው ተቃውሞው የተዛመተው። የናይጄሪያ ጦር በበኩሉ ሪፖርቱ ሃሰተኛ ዜና ነው በማለት አጣጥሎታል። ከሰሞኑ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት "ስር ነቀል" የፖሊስ ማሻሻያ እንደሚደረግና የሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈፅመዋል የተባሉትም የሳርስ አባላት ወደ ፍርድ ይቀርባሉ ብለው ነበር።
44052330
https://www.bbc.com/amharic/44052330
ፖምፔዮ የትራምፕና ኪምን ውይይት ለማመቻቸት ፒዮንግያንግ ገብተዋል
የአሜሪካው የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፔዮ ታሪካዊውን የሰሜን ኮርያው መሪ ኪም ጆንግ-ኡን እና የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕን የንግግር መድረክ ለማመቻቸት የሰሜን ኮርያዋ መዲና ፒዮንግያንግ ገብተዋል።
ማይክ ፖምፔዮ ከወር በፊት ከኪም ጋር ከተገናኙ በኋላ ወደ ፒዮንግያንግ ሲያቀኑ ሁለተኛቸው ነው። የመጀመርያውን ጉብኝታቸውን ተከትሎ በሰሜን ኮሪያና በአሜሪካ መሀከል "መልካም ወዳጅነት ተፈጥሯል።" ብለዋል። ። በጉብኝታቸው የኮሪያን ቀጠና ከኒውክሌር ለማፅዳት የሚደረገውን ውይይት ከድምዳሜ የማድረስ እቅድ እንዳላቸው አሳውቀዋል። በተጨማሪም ጉብኝታቸው ሰሜን ኮሪያ ውስጥ የታሰሩትን ሦስት አሜሪካውያን የማስፈታት ድርድር ጋር እንደሚያያዝ ጭምጭምታዎች አሉ። ወደ ፒዮንግያንግ ከማምራታቸው በፊት "ሦስቱ እስረኞች እንዲለቀቁ ለ 17 ወራት ጠይቀናል። ሰሜን ኮሪያ እስረኞቹን ትለቃለች ብለንም ተስፋ እናደርጋለን" ማለታቸው ይታወሳል። አንድ የደቡብ ኮሪያ ባለስልጣን ዮንሀፕ ለተባለ የዜና ማሰራጫ እንደተናገሩት የአሜሪካና የሰሜን ኮሪያ መሪዎች ከመገናኘታቸው በፊት ሶስቱ እስረኞች ነፃ ይወጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። ከፖምፔዮ ጋር ወደ ሰሜን ኮሪያ ያመራው የልኡካን ቡድን ሰሜን ኮሪያ በኒውክሌር ረገድ የአቋም ለውጥ ማድረግ ወይም አለማድረጓን በቅርበት እንደሚከታተሉ አሳውቀዋል። ፕሬዚዳንት ትራምፕ ፖምፔዮ ወደ ሰሜን ኮሪያ እንደሚሄዱ የተናገሩት የቀድሞው ፕሬዘዳንት ባራክ ኦባማ ከኢራን ጋር ያደረጉት የኒውክሌር ድርድር እንዳከተመ ካሳወቁ በኋላ ነበር። ፕሬዚዳንቱ "ከሰሜን ኮሪያ ጋር ያለን ግንኙነት እየተጠናከረ መሆኑን እናምናለን" ሲሉ ሁኔታውን ገልፀዋል። የሰሜን ኮሪያውን መሪ ኪም ጆንግ-ኡን የሚያገኙበት ቀን፣ ሰዓትና ቦታ መመረጡንም አክለዋል። ፕሬዚዳንቱ "ነገሮች እንዴት እንደሚሄዱ እናያለን። ምናልባትም እንዳሰብነው ላይሄድ ይችላል። ቢሆንም ውይይቱ ለሰሜን ኮርያ፣ ለደቡብ ኮርያና ለመላው ዓለምም ታላቅ ነገር ነው።" ብለዋል። ትራምፕ የሰሜን ኮሪያን ጥሪ ተከትለው ለውውይት ወደ ፒዮንግያንግ ለመሄድ መስማማታቸው ብዙዎችን ያስገረመ ውሳኔ ነበር። ለውይይት ይመቻሉ ተብለው ከተመረጡት ቦታዎች አንዳቸውም በአሜሪካ ስለማይገኙ፤ ውይይቱ በቅርቡ በሰሜን ኮርያ ይከናወናል ተብሎ ይጠበቃል። ኪም ጆንግ-ኡን ከቻይናው ፕሬዚዳንት ዢ ጂፒንግ ጋር ለመወያየት ወደ ቤጂንግ በሄዱበት ወቅት፤ "የኮሪያን ቀጠና ከኒውክሌር የፀዳ ለማድረግ ጊዜውን የጠበቀና የተቀናጀ እርምጃ ይወሰዳል።" ሲሉ ለቻይና መገናኛ ብዙሀን መናገራቸው ይታወሳል።
news-54554015
https://www.bbc.com/amharic/news-54554015
ህንድ፡በሬሳ ማቀዝቀዣ ውስጥ በህይወት የተገኙት ህንዳዊ ከቀናት በኋላ ሞቱ
በስህተት ሞተዋል ተብለው 'ሬሳቸው' ማቀዝቀዣ ውስጥ እንዲገባ የተደረጉት ህንዳዊ ከቀናት በኋላ ህይወታቸው አልፏል።
ባላስቡራማንያም የተባሉት የ74 አመቱ ህንዳዊ ታሚል ግዛት ውስጥ በሚገኝ የግል ክሊኒክ ውስጥ ሞተዋል ተብለውም የሬሳ ማቀዝቀዣ ውስጥ አስገብተዋቸዋል። በነገታውም የቀብር ስነ ስርአታቸውን ለመፈፀም ማቀዝቀዣውን ከፍተው በሚያዩበት ወቅት ሰውነታቸው እየተንቀጠቀጠና በህይወት መኖራቸውም ታወቀ። ሆስፒታል እንደገና ቢወሰዱም ከአምስት ቀናት በኋላ ህይወታቸው እለፏል። ተመልሰው የተወሰዱበት የመንግሥት ሆስፒታል ኃላፊ ዶክተር ባላጂናታን እንደተናገሩት ህመምተኛው በከፍተኛ ሁኔታ ደክመው እንደነበርና ከሳንባ ጋር በተገናኘ እክልም ህይወታቸው ማለፉን ለቢቢሲ ታሚል ተናግረዋል። በሬሳ ማቀዝቀዣው ውስጥም ምን ያህል ሰዓታትን እንዳሳለፉ የተገለፀ ነገር የለም። ሰኞ እለት ሞተዋል ብሎ ዶክተሩ ከተናገረ በኋላ ቤተሰቡ አስከሬኑን ይዘው ወደቤታቸው ከወሰዱ በኋላም በአካባቢው የሚገኝ የጤና ባለሙያም ማቀዝቀዣ እንዲልክላቸው ጠየቁ። ለወዳጅ፣ ዘመድ አዝማዱም በነገታው የቀብር ስነ ስርአታቸውም እንደሚፈፀም ተነግሮም ነበር። የቀብር ስነ ስርአት አስፈፃሚ ድርጅቱም የባላስቡራማንያም ወንድም በጤና ባለሙያ የተፈረመ የሞት ሰርቲፊኬት እንዳላቸውም መነገራቸውን አስረድተዋል። ሆኖም የፖሊስ ኃላፊው ሴንቲል ኩማር እንዳሉት ከሆነ ቤተሰቡ የሞት ሰርቲፊኬቱን ማምጣት አልቻሉም። ፖሊስም ቤተሰቡ በመጣደፍና ችላ በማለት የሰውን ህይወት አደጋ ላይ ጥለዋል በማለትም ወንጅሏቸዋል። ግለሰቡ በነርቭ ህመም ችግርም ይሰቃዩ እንደነበር ቤተሰቡ ለፖሊስ ማሳወቃቸውን ኃላፊው አክለው ተናግረዋል። ባላስቡራማንያም ከባለቤታቸው፣ ሁለት ልጆቻቸውና ወንድማቸው ጋር ይኖሩ ነበር። በአስከሬን ማቀዝቀዣው ውስጥ ለሰዓታት ያህል በዚያ ቅዝቃዜ ውስጥ በህይወት እንዴት ቆዩ የሚለው ሚስጥራዊ ሆኗል። ከዚህም በተጨማሪ መጀመሪያ ግለሰቡን ሞቷል ያለው የግል ሆስፒታል እንዲሁም ዶክተር ምርመራ ተከፍቶባቸዋል።
news-49996513
https://www.bbc.com/amharic/news-49996513
ሻኪል አፍሪዲ፡ ኦሳማ ቢን ላደንን ለማግኘት ሲ አይ ኤን የረዱት ዶክተር
የአልቃይዳን መሪ ኦሳማ ቢን ላደንን ለማግኘት የአሜሪካ የስለላ ድርጅትን ሲ አይ ኤን ረድተዋል የተባሉትና በእስር ላይ የሚገኙት ፓኪስታናዊ ዶክተር ይግባኝ ጠየቁ።
ዶክተር ሻኪል የቀረቡባቸውን ክሶች የተቃወሙ ሲሆን ፍትህ እንዳላገኙ ተናግረዋል የዶክተር ሻኪል አፍሪዲ የፍርድ ጉዳይ በክፍት ፍርድ ቤት ሲታይ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ነገር ግን አቃቤ ሕግ ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው በመጠየቁ ጉዳያቸውን ለማየት የ12 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቷል። • አልቃይዳ ከወዴት አለ? • የኦሳማ ቢን ላደን ልጅ 'በአየር ጥቃት መገደሉ' ተነገረ የዶክተሩ ሚና በፓኪስታኖች ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን የፈጠረ ቢሆንም ዶክተሩ ግን ድርጊቱን አልፈፀምኩም ሲሉ የቀረበባቸውን ክስ ተቃውመውታል። በዓለማችን እጅግ ተፈላጊ የነበረውን ቢን ላደንን ለማደንና ለመግደል ዶክተሩ ተጫውተውታል በተባለው ሚና እስከ አውሮፓዊያኑ አቆጣጠር 2011 ድረስ ይፋዊ የሆነ ክስ አልተመሰረተባቸውም ነበር። ከዚያ በኋላ በዶክተሩ መታሰር የተቆጣችው አሜሪካም ለፓኪስታን የምትሰጠውን ዓመታዊ የገንዘብ ድጋፍ ከ33 ሚሊየን ወደ 1 ሚሊየን ዶላር ቀንሳለች። ምንም እንኳን ዶክተሩ በአሜሪካውያን እንደ ጀግና የሚወደሱ ቢሆንም በፓኪስታኖች ዘንድ ደግሞ ከዳተኛና አገሪቷን ያዋረዱ ተደርገው ይቆጠራሉ። የአሜሪካው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ በ2016ቱ የምርጫ ቅስቀሳ ወቅት ከተመረጡ ዶክተር ሻኪልን "በሁለት ደቂቃ ውስጥ" እንደሚያስፈቱ ቃል ገብተው ነበር፤ ነገር ግን የገቡት ቃል እውን አልሆነም። የአሜሪካ የባህር ኃይል ወደ ሥፍራው በመግባት በመስከረም 11ዱ የሽብር ጥቃት ላይ ዋና ተዋናይ የሆኑትን ቢን ላደንን ያለምንም ተግዳሮት ለመግደል ችለዋል። ይህ መሆኑም በርካታ ጥያቄዎችን ሳይፈጥር አልቀረም። የአገሪቷን ደህንነት የሚያስጠብቀው የፓኪስታን የጦር ኃይል የት ነበር? ቢን ላደን በአገሪቷ ውስጥ ይኖር እንደነበር ያውቁስ ነበር ወይ? የሚል። ዶክተር ሻኪል አፍሪዲ ማን ናቸው? ዶክተር ሻኪል በፓኪስታን ሃይበር ግዛት ታዋቂ የሆኑ የሕክምና ባለሙያ ናቸው። በዚያው ግዛትም የጤና አገልግሎቶች ኃላፊ በመሆን በርካታ በአሜሪካ የሚደገፉ የክትባት ፕሮግራሞችን መርተዋል፤ ተቆጣጥረዋል። እንደ መንግሥት ተቀጣሪም በአገሪቷ ጦር አፍንጫ ስር ቢን ላደን ይኖርበት ነበር በተባለው በአቦታባድ፣ ጋሪሰን ከተማን ጨምሮ የሄፒታይተስ ቢ የክትባት ፕሮግራም ያካሂዱ ነበር። በመሆኑም የአሜሪካ የስለላ ድርጅት እቅድ የነበረው በአቦታባድ አካባቢ ከሚኖሩ ህፃናት ከአንዳቸው የደም ናሙና በመውሰድ ከቢን ላደን ጋር ዝምድና እንዳላቸው ማረጋገጥ ነበር። በዚህም መሠረት የዶክተር ሻኪል የሥራ ባልደረባ ወደ ግቢው በማቅናት የደም ናሙና እንደሰበሰቡ ይነገራል። ይሁን እንጂ ይህ ናሙና አሜሪካ ኢላማዋን ለመምታት ረድቷት ይሁን አይሁን የታወቀ ነገር የለም። • ኻሾግጂ የዓመቱ ምርጥ ሰው ዝርዝር ውስጥ ተካተተ • የቢንላደን የቀድሞ ጠባቂ በጀርመን ዶክተር ሻኪል በአውሮፓዊያኑ አቆጣጠር ግንቦት 23፣ 2011 ኦሳማ ቢንላድን ከተገደሉ ከ20 ቀናት በኋላ በቁጥጥር ሥር ዋሉ። በወቅቱ በአርባዎቹ መጨረሻ የእድሜ ክልል የሚገኙ ጎልማሳ ነበሩ። በጣም ሥነ ሥርዓት ያለው የአስተዳደግ ዳራ እንዳላቸው የሚነገርላቸው ዶክተሩ፤ በአውሮፓዊያኑ 1990 ከሃይበር ሜዲካል ኮሌጅ ከመመረቃቸው፣ ቤተሰባቸው እርሳቸው ከታሰሩ በኋላ የታጣቂዎች ጥቃት ይደርስብናል ብለው በመፍራት ተደብቀው እንደሚኖሩ ካለው መረጃ በስተቀር ስለ ግል ሕይወታቸውም በዝርዝር አይታወቅም። ባለቤታቸው የትምህርት ባለሙያ ሲሆኑ ራሳቸውን ደብቀው ከመኖራቸው በፊት በአንድ የመንግሥት ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር በመሆንም ሠርተዋል። ጥንዶቹ ሁለት ወንድ እና አንድ ሴት ልጆችም አፍርተዋል። በአውሮፓዊያኑ ጥር 2012 የአሜሪካ ባለሥልጣናት ዶ/ር ሻኪል ለአሜሪካ የስለላ ድርጅት ሲ አይ ኤ ይሠሩ እንደነበር አምነዋል። ይሁን እንጂ ዶክተሩ በድርጅቱ ያላቸውን ሚና ምን ያህል ያውቁት እንደነበር ግልፅ አይደለም። ከግድያው ጋር በተያያዘ የኦቦታባድ ኮሚሽን ባደረገው ምርመራ አደረጉ የተባሉትን አስተዋፅኦ በተመለከተ ምንም ያሉት ነገር የለም። የአገሪቷ የምርመራ ውጤት እንደሚያስረዳውም ዶክተር ሻኪል የድርጊቱ ኢላማ ማን እንደነበር እና እርሳቸው በሲ አይ ኤ እንዴት እንደተመለመሉ አያውቁም። ታዲያ ጥፋተኛ ያስባላቸው ምንድን ነው? በእርግጥ ዶክተሩ በመጀመሪያ በአውሮፓዊያኑ ግንቦት 2012 በክህደት የተከሰሱ ሲሆን አሁን ላይ የሌለውን 'ላሽካር ኢ እስላም' የተባለ በአገሪቷ እንዳይንቀሳቀስ የታገደ ታጣቂ ቡድንን በገንዘብ በመርዳት ጥፋተኛ ተብለው ታስረው ነበር። ከዚህ ቡድን ጋር አላቸው በተባለው ግንኙነት የ33 ዓመታት እስር የተበየነባቸው ሲሆን በኋላ ላይ በጠየቁት ይግባኝ እስሩ ወደ 23 ዓመታት ተቀንሶላቸዋል። ክሱ የተመሠረተባቸው ከታጣቂ ቡድኑ ጋር ግንኙነት ስላላቸው ብቻም ሳይሆን ለቡድኑ የህክምና ርዳታ በመስጠት እና እርሳቸው በሚያስተዳድሩት የመንግሥት ሆስፒታል ውስጥ ቡድኑ ስብሰባ እንዲያካሂድ በመፍቀዳቸውም ጭምር ነበር። ቤተሰቦቻቸው ግን በእሳቸው ላይ የተላለፈውን ውሳኔ አጥብቀው ተቃውመውታል። ጠበቃቸውም ዶክተሩ ለቡድኑ የከፈሉት ገንዘብ ቢኖር በ2008 በእነዚህ ታጣቂዎች ታግተው በነበሩበት ወቅት እንዲለቋቸው 6375 ዶላር [1 ሚሊየን የፓኪስታን ሩፒ] ብቻ እንደሆነ አስረድተዋል። በ2012 ከታሰሩ በኋላ በፓኪስታን የደህንነት ድርጅት ስቃይና እገታ እንደተፈፀመባቸው ዶክተሩ ለፎክስ ኒውስ ተናግረዋል። ከዚያም ከአንድ ዓመት በኋላ ለሕግ ባለሙያዎቻቸው 'ፍትህ ተነፍጌያለሁ' ሲሉ በእጃቸው የተፃፈ መልእክት ማስተላለፍ ችለው ነበር። ታዲያ አሜሪካንን በመርዳት ለምን አልተከሰሱም? ለምን እንደሆነ ግልፅ የሆነ ነገር ባይኖርም የቢን ላደን ጉዳይ ግን ለፓኪስታን ትልቅ ኪሳራ ነበር። ምንም እንኳን የአገሪቷ ባለሥልጣናት ጉዳዩን የሉዓላዊነት ጥሰት አድርገው ቢያዩትም፤ የደህንነት ተቋሙ የአልቃይዳ መሥራችና መሪ ኦሳማ ቢን ላደን ትልቅ ግንብ ጀርባ፣ በባለ ሦስት ፎቅ ህንፃ ውስጥ ለበርካታ ዓመታት በምስጢር ይኖሩ እንደነበር እንደማያውቁ በአደባባይ ገልፀዋል። ቢንላደን ይኖርበታል የተባለው ግቢ በ2012 ሙሉ በሙሉ ከመፍረሱ በፊት በዋይት ሃውስ የሽብርተኝነት ተቆጣጣሪ ኃላፊ ጆን ብሬናን "በዚህ ጊዜ ቢን ላድን በፓኪስታን ውስጥ ድጋፍ አልነበራቸውም ማለት አሳማኝ አይደለም" ሲሉ ቢከሱም፤ ኢስላማባድ ግን ክሱን አልተቀበለችውም። ፓኪስታን ዶ/ር ሻኪልን አሜሪካ ባካሄደችው ዘመቻ ተጫውተውታል በተባለው ሚና መክሰስ የባሰ የአገሪቷን ገፅታ ሊያጠለሽ ይችላል በሚል በይፋ የመሠረተችው ክስ አልነበረም። ዶክተር ሻኪል በቀጣይ በሚኖራቸው የፍርድ ቤት ቀጠሮ ክሳቸው ሊቋረጥላቸው አሊያም የእስራቱ ጊዜ ሊጨመርባቸው እንደሚችል አቃቤ ሕግ አሳውቋል። በሌላ በኩል ባሳለፍነው ዓመት ከፔሻዋር እስር ቤት ወደ ፑንጃብ የተዛወሩት ዶክተሩ፤ ከአልቃይዳ ጋር በተያያዘ በአሜሪካ በእስር ላይ ከሚገኙት ፓኪስታናዊ የነርቭ ሐኪምና የ3 ልጆች እናት ከሆኑት አፊያ ሲዲቂ ጋር የእስረኛ ልውውጥ በማድረግ ሊፈቱ እንደሚችሉ ጭምጭምታ አለ።
news-55068434
https://www.bbc.com/amharic/news-55068434
የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ 'ፕራንክ' ተደረጉ
የካናዳው ጠቅላይ ሚንስትር የአየር ጸባይ ለውጥ ተሟጋቿ ግሬታ ተንበርግን ድምጽ በማስመሰል በደወሉላቸው ሰዎች 'ፕራንክ' ተደርገዋል።
የካናዳው ጠቅላይ ሚንስትር ጀስቲን ትሩዶ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተመሳሳይ መልኩ ከተሸወዱ ታዋዚ ሰዎች ዝርዝር ውስጥ ተካተዋል። የሰዎችን ድምጽ በማስመሰል እውቅናን ማትረፍ የቻሉት ቭላድሚር ኩዝኔትሶቭ እና አሌክሲ ስቶሪያሮቭ ባሳለፍነው ዓመት ጥር ወር ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩን የሸወዱበትን የስልክ ንግግር የድምጽ ቅጂ ይፋ አድርገዋል። ለጠቅላይ ሚኒስትሩም ግሬት ተንበርግን በመመሰል ስለ የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃልኪዳን (ኔቶ) እና ስለ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በርካታ ጥያቄዎችን አቅርበውላቸዋል። ''የዓለም መሪ ላይ እንዲህ አይነት ነገር ሲፈጸም ይህ የመጀመሪያው አይደለም'' ብሏል የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ባወጣው መግለጫ። አክሎም ''ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ የስልክ ጥሪው ሐሰተኛ መሆኑን ሲረዱ ጥሪውን አቋርጠውታል'' በማለት አስታውቋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ '' ሄሎ ግሬታ፤ እንደምን አለሽ?'' ሲሉ ንግግራቸውን ጀምረዋል። ''እጅግ በጣም ብዙ ኃላፊነቶች እንዳሉብዎት እረዳለሁ፤ ከእንደኔ አይነት ትንሽ ልጅ ጋርም ለማውራት ጊዜ ላይኖርዎት እንደማችልም ይገባኛል። በመላው ዓለም እሆነ ያለው በጣም አሳስቦኛል'' ይላል ግሬታን የሚያስመስለው ግለሰብ። የስልክ ጥሪው ተደረገው የዩክሬኑ 'ፒኤስ752' አውሮፕላን ከኢራን ዋና ከተማ ቴሄራን ከተነሳ በኋላ ተመትቶ ወድቆ በነበረበት ወቅት ጊዜ ነው። በአውሮፕላኑ ተሳፍረው ከነበሩት 57 ካናዳ ዜጎች ሲሆኑ፤ ወቅቱ በኢራን እና አሜሪካ መካከልም የነበረው ውጥረት እጅግ የተከራረበት ጊዜ ነበር። በስልክ ንግግሩ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉዳዩ ላይ በርካታ የስልክ ጥሪዎችን እየደረሳቸው እንደሆነ ገልጸዋል። በመቀጠልም ግሬታን በመምሰል የደወለው ግለሰብ ''የዓለም መሪዎች አዋቂ ሰዎች ቢሆኑም ተግባራቸው ግን እንደ ህጻናት ነው'' ይላል። ''ኔቶን ተዉት፤ መሳሪያዎቻችሁን ጣሏቸው፤ አበባዎችን በእጃችሁ ያዙ፤ በተፈጥሮ ተደስታችሁ ፈገግ በሉ'' ይላል ይሄው ግለሰብ። በአስተያየቱ ግራ የተጋቡ የሚመስሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለነገሮች ያላትን አስተያየት በማድነቅ በስሜት የተናገረችውን ነገር አድንቀዋል። ቭላድሚር ኩዝኔትሶቭ እና አሌክሲ ስቶሪያሮቭ ከዚህ ቀደም በቅርቡ ታዋቂው አቀንቃኝ ኤልተን ጆን፣ የእንግሊዙ ልኡል ፕሪንስ እና አዲሷ ተመራጭ የአሜሪካ ምክትል ፕሬዝደንት ካማላ ሃሪስ ላይ ተመሳሳይ ነገር አድርገዋል። ከሁለት ዓመታት በፊት ደግሞ የአርሜኒያን ጠቅላይ ሚኒስትር በመመሰል ቦሪስ ጆንሰን ጋር ስልክ ደውለው ነበር። አንዳንዶች ጥንዶቹ ከሩሲያ የደህንነት ሰዎች ጋር ግንኙነት እንዳላቸው በተገዳዳሚ የሚገልጹ ሲሆን እነሱ ግን ሙሉ በሙሉ ሐሰት ነው በማለት ተከራክረዋል።
news-53761620
https://www.bbc.com/amharic/news-53761620
ካናዳውያን፡ አሜሪካውያን ወደ ሃገራችን እንዳትመጡ
የዩናይትድ ስቴትስና የካናዳ ድንበር ከመቼውም ጊዜ በላይ ውጥረት ሰፍኖታል። ምክንያቱ ቢሉ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ።
ካናዳውያን በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ግብሩ የጠፋባቸው አሜሪካውያን ቫይረሱን ይዘው ወደ ሃገራቸው እንዲመጡባቸው አይፈልጉም። ፒች አርክ እየተባለ የሚጠራው በአሜሪካዋ ዋሺንግተን ግዛትና በካናዳዋ ብሪቲሽ ኮለምቢያ መሃል የሚገኘው ባለ 20 ሜትሩ ሽንጣም ኬላ የሁለቱ ሃገራት ውጥረት ከምን እንደደረሰ ማሳያ ነው። "እኚህ በሮች መቼም ቢሆን አይዘጉ" የሚል ፅሑፍ የሰፈረበት ይህ ኬላ ኮሮናቫይረስ ይመጣብኛል ብሎ ያሰበ አይመስልም። አሜሪካና ካናዳ 8 ሺህ 891 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ከወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ነፃ የሆነ ድንበር ይጋራሉ። ለ100 ዓመታት ያክል ሕጋዊ [አንዳንዴም ሕግ ያልበገራቸው] ሰዎች ሲያሻቸው ወደ ካናዳ ይወጣሉ አሊያም ወደ አሜሪካ ይወርዳሉ። አሁን ግን ይህ ኬላ ተዘግቷል። ድንበሩ የተዘጋው ባለፈው መጋቢት ነው። በሁለቱ ሃገራት ስምምነት መሰረት። ስምምነቱ ብዙ ጊዜ ሲራዘም ቆይቶ የሁለቱ ሃገራት መሪዎች እስኪ እስያዝነው ወር መጨረሻ ድረስ እንየው ቢሉም ብዙዎች ድንበሩ ይከፈታል የሚል ተስፋ የላቸውም። ምንም እንኳ የድንበሩ መዘጋት በአቅራቢው ለሚኖሩ ሚሊዮኖች የገቢ ባልቦላቸው እንዲዘጋ ቢያደርግም ካናዳውያን ግን ኬላው እንደተዘጋ ቢቆይ ደስታቸው ነው። ሐምሌ ላይ ጥናት የሠራ አንድ ድርጅት ከ10 ካናዳውያን ስምንቱ ድንበሩ ይዘጋ፤ አሜሪካውያንም እንደው እስከ ዓመቱ መጨረሻ ባይመጡብን ይላሉ ይላል። ወረርሽኙ አሜሪካን ማጥለቅለቁን ሲቀጥል በጣም አስፈላጊ ካልሆነ በቀር ድንበር ማቋረጥ የማይታሰብ ነው። ሸቀጥ ይዘው ድንበሩን ደጋግመው የሚጎበኙ የጭነት መኪናዎች አስፈላጊ ከሚባሉ ውስጥ በመመደባቸው እንደልባቸው ይንቀሳቀሳሉ። የአሜሪካ ታርጋ የለጠፉ የጭነት መኪናዎች በካናዳውያን የሚደርስብን መገለል አልበቃ ብሎ መኪናችን ላይ ጉዳት እየደረሰ ነው ሲሉ ያማርራሉ። ይህ ሁኔታ ስጋት የጣለባቸው የካናዳዋ ብሪቲሽ ኮለምቢያ ግዛት አስተዳዳሪ ጆን ሆርጋን የአሜሪካ ታርጋ ለጥፈው የሚንቀሳቀሱ ካናዳውያን የግል መኪናቸውን ቤት አስቀምጠው በባስ አሊያም በብስክሌት እንዲንቀሳቀሱ መክረዋል። ድንበሩ ዙሪያ ያለው ጥበቃ ጠበቅ ማለቱ ለወትሮው በቀላሉ ያልፉ የነበሩ አጭበርባሪዎችን አስጨንቋል። ከጥቂት ቀናት በፊት እንኳ የተሰረቀ መኪና ይዞ ድንበር ሊያቋርጥ የነበረን ግለሰብ ፖሊስ ለሁለት ሰዓታት ካሳደደው በኋላ ይዞታል። ምንም እንኳ የገንዘብ ቅጣቱ ተግባራዊ መደረግ አይጀምር እንጂ ኬላው ሕግ የጣሰ ሰው ቢያንስ 750 ሺህ የካናዳ ዶላር [566 ሺህ የአሜሪካ ዶላር] ይቀጣ ተብሏል። አሊያም የስድስት ወር እሥር ይጠብቀዋል። ይህ ቅጣት ታድያ አስበውና አቅደው ጥፋት ለፈፀሙ ብቻ አይደለም። የአሜሪካና ካናዳ ድንበርን ተሳስተው እንኳ ኳቋረጡ ቅጣቱ አይቀርሎትም። በቅድመ ኮሮና ወቅት ቢያንስ 3 መቶ ሺህ ሰዎች በየቀኑ የአሜሪና ካናዳ ድንበርን ያቋርጡ ነበር። ነገር ግን ከመጋቢት በኋላ ነገሮች እንዳይሆኑ ሆነዋል። የድንበሩ መዘጋት ለአካባቢው ከተማዎች የምጣኔ ሃብት ኪሳራ ቢሆንም ካናዳ ድንበሯን ለአሜሪካ ክፍር ብታደርግ ኖሮ የበለጠ ዋጋ ልትከፍል ትችል እንደነበር ብዙዎች ይናገራሉ። አሜሪካ ወረርሽኙ እንደ አዲስ ጎምርቶባታል። በቀን እስከ 40 ሺህ ድረስ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው እየተረጋገጠ ነው። ካናዳ ደግሞ ካላት የሕዝብ ብዛት አንፃር በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር እዚህ ግባ የሚባል አይደለም።
news-56110666
https://www.bbc.com/amharic/news-56110666
ኮሮናቫይረስ፡ ወረርሽኙን ተከትሎ ራሳቸውን የሚያጠፉ ሰዎች የተበራከቱባት ጃፓን
ጃፓን ከየትኛውም ዓለም በፈጠነና ትክክለኛ በሆነ መልኩ ራሳቸውን የሚያጠፉ ሰዎችን መረጃ በአግባቡ ትመዘግባለች።
ከሌሎች አገራት በተለየ መልኩ ራሳቸውን የሚያጠፉ ሰዎች መረጃ በየወሩ እየተጠናቀረ ይቀመጣል። በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት ደግሞ ይህ መረጃ በጣም አስፈሪ ታሪኮችን ይፋ አድርጓል። 2020 ላይ ከ11 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ራሳቸውን የሚያጠፉ ሰዎች ቁጥር በጣም ከፍ ብሏል። በሚያስገርም ሁኔታ ደግሞ የወንድ ሟቾች ቁጥር በትንሹም ቢሆን የቀነሰ ሲሆን ራሳቸውን የሚያጠፉ ሴቶች ቁጥር ደግሞ 15 በመቶ ጨምሯል። ባለፈው ጥቅምት ወር ላይ በአንድ ወር ውስጥ ብቻ ከዛ በፊት በነበረው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ራሰቸውን የሚያጠፉ ሴቶች ቁጥር 70 ከመቶ በላይ ጭማሪ አሳይቶ ነበር። በጃፓን ምን እየሆነ ነው? የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ከወንዶች በተለየ ሴቶችን ለምን ራሳቸውን እንዲያጠፉ አደረጋቸው? ማስጠንቀቂያ፡ አንዳንድ አንባቢያን ይህ ጽሁፍ ሊያስደነግጣቸው ይችላል? በተደጋጋሚ እራሷን ለማጥፋት የሞከረችን ሴት በአካል አግኝቶ ማውራት ከባድ ነገር ነው ይላል የቢቢሲው የቶክዮ ዘጋቢ ሩፐርት ዊንግፊልድ። ያየውን እንዲህ ይገልጻል. . . ሰዎች ራሰችውን እንዳያጠፉ መከላከል ላይ የሚሰሩ ሰዎችን በጣም እንዳደንቃቸው አድርጎኛል። በዮኮሀማ ሬድ ላይ ዞን ውስጥ በሚገኝ በዚሁ ጉዳይ ላይ የሚሰራ ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት ውስጥ ነው የምገኘው። ከፊልት ለፊቴ አንድ የ19 ዓመት ወጣት ተቀምጣለች። ምንም አይነት ስሜት አይታይባትም። ቀስ ብላ የግል ታሪኳን ታጫውተኝ ጀመር። ነገሩ የጀመረው የ15 ዓመት ታዳጊ ሳለች ነበር። በወቅቱ ታላቅ ወንድሟ ቀላል የማይባል አካላዊ ጥቃት ይፈጽምባት ነበር። በመጨረሻ ከቤት ጠፍታ ለማምለጥ ወሰነች። ነገር ግን ብቸኝነቱንና ህመሙን መቋቋም አልቻለችም። የታያት የመጨረሻ አማራጭም ራሷን ማጥፋት ነበር። ''ከባለፈው ዓመት ወዲህ በተለያዩ ጊዜያት ሆስፒታል ስገባና ስወጣ ነበር የቆየሁት'' ትላለች። ''ብዙ ጊዜ ራሴን ለማጥፋት ሞክሬያለው ነገር ግን ሊሳካልኝ አልቻለም። ምናልባት አሁን ተስፋ በመቁረጥ ራሴን ለማጥፋት መሞከር ትቻለሁ።'' ራሷን ለማጥፋት ከመሞከር እንድትቆጠብ ያደረጋት ደግሞ በጎ አድራጎት ድርጅት ውስጥ ያለው 'ቦንድ' የተሰኘው ፕሮግራም ነው። ደህንነቱ የተጠበቀ መኖሪያ ቦታ አግኝተውላታል፤ በተጨማሪም ተገቢውን የአእምሮ ጤና ክትትል እንድታገኝ ረድተዋታል። ጁን ታቺባና የቦንድ ፕሮጀክት መስራች ነች። በ40ዎቹ የእድሜ ክልል ውስጥ የምትገኝ ጠንካራ ሴት ናት። ''ሴቶች በተለይ ታዳጊ ሴቶች ችግር ውስጥ ሲገቡና ስነ ልቦናዊ ህመም ሲሰማቸው በትክክል ምን ማድረግ እንዳለባቸው አያውቁም። እኛ እዚህ ያለነው የእነሱን ችግር ለመስማት ነው። መፍትሄ ለመስጠትና ችግራቸውን ለመጋራት'' ትላለች። ጁን እንደምትለው የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መጀመሪያውኑ ችግር ያለባቸውንና ተጋላጭ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎችን በጣም ጎድቷል። በፕሪጀክቱ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች በወረርሽኙ ወቅት እጅግ አስፈሪና አሳዛኝ የስልክ ጥሪዎችን እንዳስተናገዱም ታስታውሳለች። ''ብዙ ጊዜ መሞት እፈልጋለሁ አልያም ምንም አይነት የምሄድበት ቦታ የለኝም የሚሉ ጥሪዎች ይደርሱናል። በጣም የሚያም ነገር እንደሆነ ይነግሩናል። አንዳንዶቹም ብቸኝነት እንደሚሰማቸውና መጥፋት እንደሚፈልጉ ነው የሚገልጹት።'' ከዚህ በፊት አካላዊና ጾታዊ ጥቃት ይደርስባቸው የነበሩ ሰዎች ደግሞ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ነገሮችን ይበልጥ አስከፊ አድርጎባቸዋል። ''በአንድ ወቅት አንዲት ታዳጊ ደውላ በአባቷ ጾታዊ ጥቃት እየደረሰባት እንገሆነ ገልጻ ነበር። በኮሮናቫይረስ ምክንያት አባትየው ለስራ ብሎ ከቤት ስለማይወጣ በየቀኑ ይህንን አሳዛኝ ጥቃት መጋፈጥ ነበረባት።'' በጃፓን ከዚህ በፊት የነበሩትን ቀውሶች ስንመለከት ለምሳሌ በአውሮፓውያኑ 2008 አጋጥሞ በነበረው የባንክ ዘርፋ ቀውስ ወይም በ1990ዎቹ አካባቢ በነበረው የአክስዮን ገበያ መውደቅ ምክንያት በርካታ ጃፓናውያን በተለይ አዋቂ ወንዶች በእጅጉ ተጎድተው ነበር። በነዚህ ጊዜያት ራሳቸውን የሚያጠፉ ወንዶች ቁጥር በጣም ከፍ ብሎ ነበር። ኮቪድ-19 ግን የተለየ ነገር ነው። የወረርሽኙ መዘዝ በዋነኛነት ወጣቶችን በተለይ ደግሞ ወጣት ሴቶችን እያጠቃ ይገኛል። ምክንያቶቹ ደግሞ የተወሳሰቡ ናቸው። ጃፓን ከዚህ በፊትም ቢሆን ካደጉት አገራት ጋር ስትወዳደር ከፍተኛውን ራሳቸውን የሚያጠፉ ሰዎች ታስተናግድ ነበር። ባለፉት አስር ዓመታት ደግሞ አገሪቱ ራሳቸውን የሚያጠፉ ሰዎችን ቁጥር በአንድ ሶስተኛ መቀነስ ችላለች። ፕሮፌሰር ሚቺኮ ኡዌዳ በጃፓን በዙዳዩ ላይ ቀዳሚ የሚባሉ ተመራማሪ ናቸው። እሳቸው እንደሚሉት በጃፓን ባለፉት ቅርብ ወራት ውስጥ ብቻ የታየው ራሰቸውን የሚያጠፉ ሰዎች ቁጥር መጨመር በእጅጉ የሚያስደነግጥ ነው። ''በተለይ ደግሞ ሴቶች ራሳቸውን እያጠፉ ያሉበት አካሄድ ያልተለመደና አሳሳቢ ነው። በዚሁ ጉዳይ ላይ ጥናት ማካሄድ ከጀመርኩበት ጊዜ አንስቶ እንዲህ አይነት ቁጥር ተመልክቼ አላውቅም። ምናልባት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በእጅጉ ካዳከማቸው ዘርፎች መካከል እንደ ቱሪዝም፣ ችርቻሮ ንግድና ምግብን የመሳሰሉት ሴቶች በብዛት የሚሰማሩባቸው መሆናቸው እንደ ምክንያት ሊወሰድ ይችላል'' ይላሉ ፕሮፌሰሯ። በጃፓን ሌላው ቀርቶ ብቻቸውን የሚኖሩ ሴቶች ቁጥር እየጨመረ ሲሆን፤ ዋነኛ ምክንያታቸው ደግሞ ትዳርን ሽሽት ነው። ብቻቸውን ሲኖሩ ደግሞ ከማህበረሰቡ የሚደርስባቸውን ጫና መቋቋም በጣም ከባድ ነገር ነው። ''በርካታ ወጣት ጃፓናውያን ሴቶች አላገቡም። ቤተሰቦቻቸውንም የሚረዱት እነሱ ናቸው። በርካታዎቹ ደግሞ ቋሚ ስራ የሌላቸው ሲሆን በወረርሽኙ ምክንያት የሚደርስባቸውን ጫና መገመት ቀላል ነው። ባለፈው ዓመት ጥቅምት ወር ላይ ብቻ በጃፓን 879 ሴቶች ራሳቸውን አጥፍተዋል። ከዛ በፊት ከነበረው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ደግሞ ቁጥሩ 70 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። ጃፓን በአሁኑ ሰአት ሶስተኛው ዙር የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ላይ ትገኛለች። መንግስትም ለሁለተኛ ጊዜ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተግባራዊ እንዲሆን አዟል። እስከሚቀጥለው ወር ድረስ ሊቀጥል እንደሚችልም ይገመታል። በርካታ ሆቴሎችና ሬስቶራንቶች በራቸውን እየዘጉ ሲሆን በዚሁ ምክንያትም በርካቶች ስራቸውን እንዳጡ ነው። ራስን ማጥፋት ውስብስብ ከመሆኑ የተነሳ እንዲሁ በቀላሉ መፍትሄ መዘርዘር የሚቻል አይደለም። ትልቁና ተመራጩ መፍትሄ ግን ተግባቦትን ማጠናከር ነው። ሰዎች ስለ ሕይወታቸው እንዲያወሩ ማድረግ፣ የሚደገፉበትን ትከሻ አለመንፈግ፣ ሙሉ ጆሮ እና ጥሞናን መስጠት። ሌላው ሊዘነጋ የማይገባው ነገር፤ ሰዎች ራስን የማጥፋት መዘዝ ለሌላውም እንደሚተርፍ ማወቅ አለባቸው። ራስን አለማጥፋት ምርጫ እንደሆነ ማሳየት ባለሙያዎች የሚመክሩት አንዱ የመፍትሄ ሃሳብ ነው። ሰዎች ራሳቸውን ሲያጠፉ ወዳጅ ዘመዶቻቸው ላይ ትቶ የሚያልፈውን ጠባሳ ማስተዋል፤ ሃሳቡ ያላቸው ሰዎች ቆም ብለው እንዲያጤኑ ያደርጋል። በበርካታ ሃገራት እራስን ማጥፋት የመኪና አደጋ ከሚያደርሰው በላይ ጥፋት ያደርሳል። ነገር ግን ለመኪና አደጋ የሚሠራውን ያህል ግንዛቤ ስለ ለራስ ማጥፋት አይሠራም። አንዳንድ ቦታዎች ራስ ማጥፋትን በተመለከተ ምክር የሚሰጡና የሚሠሩ ተቋማት መመሥረታቸው እንደ በጎ ጅምር እየታየ ነው። ለምሳሌ እንግሊዝ የራስ ማጥፋት መከላከል ሚኒስቴር አላት። የችግሩ መጠንም በትንሹ መቀነስ አሳይቷል።
50974430
https://www.bbc.com/amharic/50974430
በወሎ ዩኒቨርሲቲ የተፈጠረው ምንድነው?
በወሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ የነበረ አንድ ወጣት ዛሬ ጠዋት በግቢው ውስጥ ድብደባ ደርሶበት ሕይወቱ ማለፉ ታውቋል።
ተማሪው ወደ መመገቢያ አዳራሽ በሚሄድበት ወቅት ድብደባው እንደረሰበት ቢቢሲ ያነጋገረው ተማሪ ሰኢድ መሃመድ ገልጿል። ''ከጠዋቱ ሁለት ሰአት አካባቢ ወደ መመገቢያ አዳራሽ እየሄደ እያለ ሶስት የሚሆኑ ልጆች ተሰብስበው እንደደበደቡት ሰምቻለሁ'' ብሏል። ''ጉዳት ከደረሰበት በኋላ ወደ ሆስፒታል ወስደነው ከረፋዱ አምስት ሰአት አካባቢ ነው ሕይወቱ ያለፈው። የልጁ ሞት ከተሰማ በኋላ በዩኒቨርሰቲው ብጥብጥ ተነስቶ ተማሪዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል" ሲልም ሰኢድ አክሏል። • የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ወደቤታቸው ለመላክ ለምን ወሰነ? • በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንቅስቃሴ ላይ ጊዜያዊ ገደብ ተጣለ በደሴ ሪፈራል ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ሰይድ የሱፍ፤ ሁለት ተማሪዎች ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ሆስፒታላቸው መምጣታቸውን ነግረውናል። ''ሁለት ተማሪዎች ለህክምና ወደ ተቋማችን መጥተዋል። አንደኛው ህክምና እየተከታተለ ባለበት ወቅት ሕይወቱ ያለፈች ሲሆን ሌላኛው ተማሪ ግን ቀላል ጉዳት ስለደረሰበት በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል'' ብለዋል። ሕይወቱ ያለፈው ተማሪ ምን አይነት ጉዳት እንደደረሰበት ገና አልተጣራም ያሉት ሥራ አስኪያጁ ''እኛ የሠራነው የህክምና ባለሙያዎችን አስተባብረን ፈጣን ህክምና እንዲያገኝ ማድረጉ ላይ ነው። በወቅቱ ጽኑ ህሙማን ተኝተው የሚታከሙበት ክፍል ውስጥ ነው ሲታከም የነበረው'' ብለዋል። የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አባተ ጌታሁን በበኩላቸው፤ አንድ ተማሪ ሕይወቱ ማለፉን ያረጋገጡ ሲሆን ሌሎች ሁለት ሰዎች ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸው ሆስፒታል መወሰዳቸውን ነግረውናል። ''በሚያሳዝን ሁኔታ አንድ ተማሪያችን ጉዳት ደርሶበት ሕይወቱ አልፏል። በግቢው ውስጥ በግንባታ ሥራ ላይ የነበረ አንድ ግለሰብም በግርግሩ ጉዳት ደርሶበታል። ሶስተኛው ጉዳት የደረሰበት ግጭቱን ለማብረድ መሀል የገባ የጥበቃ አባል ነው።'' ፕሬዝዳንቱ አክለውም ከቀናት በፊት ተማሪዎችን በማሰባሰብ ትልቅ የእርቅና የይቅርታ መድረክ አዘጋጅተው በጥሩ ሁኔታ መጠናቀቁንና የአሁኑ ክስተት ነገሮችን ወደኋላ የጎተተባቸው እንደሆነ ገልጸዋል። ''እርቅ ሁለት ጊዜ አድረገናል። እናቶችና አባቶች ከቀኑ ስድስት ሰአት እስከ ዘጠኝ ሰአት ድረስ ተንበርክከው ተማሪዎችን አስታርቀዋል። የሀይማኖት አባቶች ጭምር መጥተው መልእክት አስተላልፈዋል።'' እሳቸው አንደሚሉት፤ ተማሪው ተላቅሶ እየተቃቀፈ እርቅ ከፈጠረ በኋላ አንዱ መጥቶ የሆነ ነገር ያደርግና ያ ሁሉ እርቅና ሰላም ተረስቶ ድፍርስርሱ ይወጣል። "ግቢያችንን ለመበጥበጥ አንድ ቀላል ነገር በቂ ነው። ጥፋተኛ ተማሪዎችን ማግኘት ከባድ ነው። የሆነ ነገር ያደርግና ከተማሪዎች ጋር ይቀላቀላል'' ሲሉም አስረድተዋል። ከዛሬው ክስተት በኋላም ከምሥራቅ አማራ የፌደራል ፖሊስ ጋር በመተባበር የማጣራትና የክትትል ሥራ እንደሚከናወን ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል። ''የምሥራቅ አማራ የፌደራል ፖሊስ ዋና አዛዥ በተገኙበት ለተማሪዎች ትዕዛዝ ተላልፏል። ጥቃት ፈጻሚዎቹ ገብተውበታል የተባለው ህንጻ ላይ ተገቢውን ማጣራት አድርገን እርምጃ እንወስዳለን። ተማሪዎቹ እራሳቸው ካጋለጡ እሰየው፤ ካላጋለጡ ግን የራሳችንን አማራጭ እርምጃ እንወስዳለን።'' • ዩኒቨርስቲዎች በፌደራል ፖሊስ እንዲጠበቁ መወሰኑ ተገለፀ ተማሪ ሰኢድ እንደነገረን ከሆነ፤ ከተለያየ ብሔር የመጡ ተማሪዎች ካለፉት ሁለት ሳምንታት ጀምሮ በተለያየ ማደሪያ ውስጥ እየኖሩ ነው። የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አባተም ጉዳዩ እውነት ነው ብለዋል። ''በአሁኑ ሰአት ምርጫ የለንም። ከ2008 ዓ.ም. ጀምሮ ነው ይሄን መሰል ችግር ሲፈጠር የነበረው። አንድ ዶርም ውስጥ የሚያድሩ ጓደኛማቾች እኮ እስከመገዳደል ደርሰዋል። ስለዚህ ተለያይተው እንዲኖሩ ማድረጋችን አማራጭ ስላጣን ነው። ለምሳሌ ዛሬ አንደኛውን ለብቻ ሌላኛውን ለብቻ በተለያየ ሰአት ነው ምግብ ያበላነው፤ በፌደራል ፖሊስም እንዲጠበቁ እያደረግን ነው'' ብለዋል። ተማሪ ሰኢድ ''ሁሌም አለመረጋጋት ይፈጠራል፤ በነጋታው ትምህርት ጀምሩ እንባላለን። መንግሥትም ሆነ ዩኒቨርሲቲው መፍትሄ ሊሰጡን ይገባል። ወይም ደግሞ እንደ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ወደቤታችን ይላኩን'' ይላል። ዶ/ር አባተ ግን ተማሪዎችን ወደቤታቸው መላክ አማራጭ አያደለም ብለዋል። ''ተማሪዎችን ወደቤታቸው አንልክም፤ ተማሪውን አሳትፈን ለችግሮቹ መፍትሄ እንፈልጋለን እንጂ ወደቤት ልከን ለቤተሰቦቹ ሌላ ሸክም እንዲሆን አንሻም'' ሲሉም ያስረዳሉ።
news-49969269
https://www.bbc.com/amharic/news-49969269
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ የኖቤል የሰላም ሽልማትን ያሸንፉ ይሆን?
በመጪው አርብ በኖርዌይ መዲና ኦስሎ በሚዘጋጀው የ2019 የኖቤል የሰላም ሽልማት ያሸንፋሉ ተብለው ከሚጠበቁ ሰዎች አንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ሊሆኑ እንደሚችሉ ታይም መፅሄት አስነብቧል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ከሁለት አስርት አመታት ፍጥጫ እልባት በመስጠት፤ ሰላም በማምጣት፣ የፖለቲካ እስረኞችን በመፍታትና ሌሎች ባመጧቸውም መሻሻሎች ሽልማቱን ሊያሸንፉ እንደሚችሉ በእንግሊዝ የተለያዩ ፖለቲካዊ ትንበያዎችን በመስጠት የሚወራረደው ላድብሮክ አሳውቋል። ድርጅቱ 80% (4/1) ሊያሸንፉ እንደሚችሉ ግምቱን አስቀምጧል። • 'ሰልፊ' ለመነሳት ሲሞክሩ የሰመጡት ሙሽሮች • ጃፓን ያለ መሬትና ያለ አርሶ አደሮች የፈጠረችው የግብርና አብዮት • ሕገ ወጥ ስብሰባ አካሂደዋል የተባሉት አሜሪካዊ ፓስተር በሩዋንዳ ታሰሩ ዓመታዊው ሽልማት በአለም ውስጥ ለሰላም አስተዋፅኦ ያደረጉ ግለሰቦችን ወይም ድርጅቶችን እውቅና ይሰጣል። በባለፈው ዓመት የኮንጎ ዜግነት ያለው ዶክተር ዴኒስ ሙክዌጋና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቿ ናዲያ ሙራድ ወሲባዊ ጥቃትን ለጦርነት መሳሪያነት መጠቀሚያነት ለማቆም በሰሩት ስራ አሸናፊ ሆነዋል። በዚህ ዓመቱ ሽልማት 301 ዕጩዎች ያሉ ሲሆን፤ 223 ግለሰቦች እንዲሁም 78 ድርጅቶች መሆናቸውንም የኖቤል ተቋም አስታውቋል። ምንም እንኳን እነማን ዕጩዎች እንደሆኑ ባይታወቁም የተለያዩ ግለሰቦችና ድርጅቶች ግምቶቻቸውን እያስቀመጡ ነው። ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ በተጨማሪ የአየር ንብረት ለውጥ ተሟጋቿ ግሬታ ተንበርግና የኒውዚላንዷ ጠቅላይ ሚኒስትር ጃሲንዳ አርደርን ግምት ተሰጥቷቸዋል።
news-43382436
https://www.bbc.com/amharic/news-43382436
ጠ/ሚ ሜይ ሞስኮ በሰላዩ መመረዝ ጉዳይ አስተያየት መስጠት አለባት ብለዋል
የቀድሞው የሩሲያ ሰላይ እና ልጁን ለመመረዝ ጥቅም ላይ የዋለው ኬሚካል ነርቭን የሚያሽመደምድና በሩስያ ወታደራዊ ኃይል የተሠራ ነው በማለት ቴሬዛ ሜይ ለእንግሊዝ ሕዝብ ተወካዮች ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ቴሬዛ ሜይ የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ጋር ካደረጉት ስብሰባ በኃላ ሕዝብ ተወካዮችን አነጋግረዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ቴሬዛ ሜይ በሳልዝበሪ የተደረገው ጥቃት የሩስያ እጅ የሚኖርበት ዕድሉ ከፍተኛ ነው ብለዋል። የእንግሊዝ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የሩስያውን አምባሰደር በመጥራት ሁኔታውን እንዲያስረዱ ጠይቋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ቴሬዛ እስከ ማክሰኞ ባለው ጊዜ ውስጥ አጥጋቢ መልስ ካልተሰጠ ሞስኮ ሕጋዊ ያልሆነ ኃይል ተጠቅማለች ብላ ዩናይትድ ኪንግደም እንድትደመድም ትገደዳለችም ብለዋል። ጥቃቱን ለማድረስ የተጠቀሙበት ኬሚካል 'ኖቪቾክ' በመባል የሚታወቀው መርዝ መሆኑ እንደተደረሰበትም ጠቅላይ ሚንስትሯ ተናግረዋል። ቴሬዛ ''ይህ ሩስያ በቀጥታ በሃገራችን ላይ የወሰደችው እርምጃ እንደሆነ ወይም ደግሞ የሩስያ መንግሥት አደገኛና ነርቭ ጎጂ የሆነው መርዝ ቁጥጥሩን አጥቶ በሌላ ሰው እጅ እንደገባ ያሳያል'' ብለዋል። የእንግሊዙ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ለሩስያ አምባሳደር እንደተናገሩት ሞስኮ ኖቪቾክ የተሰኘውን ነርቭ ጎጂ ኬሚካል ፕሮግራም ሙሉ በሙሉ ለዓለም አቀፉ የኬሚካል መሣሪያዎች እገዳ ድርጅት ማስረከብ አለባት። የ66 ዓመቱ የቀድሞ የሩሲያ ሰላይ እና ልጁ ቴሬዛ አክለውም ዩናይትድ ኪንግደም ወደፊት ከባድ እርምጃ ለመውሰድ መዘጋጀት እንደሚያስፈልጋትና ከሩስያ ምንም ምላሽ ካልመጣ በረቡዕ ዕለት እርምጃዎቹን እንደሚያሳውቁ ተናግረዋል። ባላፈው ሳምንት እሁድ ጡረተኛው የሩስያ ወታደር የ66 ዓመቱ ሰርጌ ስክሪፓል እና የ33 ዓመት ልጁ ዩሊ ስክሪፓል በሳልዝበሪ የገበያ ማዕከል በአግዳሚ ወንበር ላይ ነበር እራሳቸውን ስተው የተገኙት። እስካሁን ጤናቸው አስጊ ደረጃ ላይ ቢደርስም ግን በሕይወት እንዳሉ ተነግሯል። ሰርጌ በአውሮፓውያኑ 2004 ለኤምአይሲክስ ምስጢር አቀብለሃል ተብሎ በሩስያ መንግሥት ከተከሰሰ በኋላ በ2010 የሰላዮች ልውውጥ ሲደረግ በዩናይትድ ኪንግደም ጥገኝነት ተስጥቶት ነበር። ኖቮቾክ ምንድን ነው? ጠቅላይ ሚኒስትር ቴሬዛ ሜይ የሕዝብ ተወካዮችን ሲያነጋግሩ ''እንደዚህ ዓይነት ነርቭ ጎጂን መርዝ ተጠቅሞ ለመግደል የተደረገው ሙከራ በስክሪፓል ቤተሰብ ላይ ብቻ የተደረግ ጥቃት አይደለም'' ብለዋል። አክለውም "ይህ ዩናይትድ ኪንግደም ላይ የተሰነዘረ ጥንቃቄ የጎደለው ድርጊት የብዙ ንጹሃን ግለሰቦችን ሕይወት አደጋ ላይ የጣለ ነው'' ብለዋል። ጣታቸውን ወደ ሩስያ ለመቀሰር ውሳኔ የወሰዱት ''ሩስያ ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ የመንግሥት እጅ ያለበት ግድያዎች በማካሄዷ እና ሃገር ሸሽተው የወጡ ሰዎች ለእንደዚህ ዓይነት ግድያዎች ዒላማ የተጋለጡ በመሆናቸው ነው'' ብለው ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስረድተዋል። የሌበር ፓርቲ መሪ የሆነው ጄሬሚ ኮርብን ነገሮች የተወሳሰቡ ሳይመጡ ከሩስያ ጋር ጠጣር ንግግር እንደሚያስፈልግ አሳውቀዋል። መርማሪዎች በሳልዝበሪ አካባቢ የነበረን መኪና አስነሱ ሰርከስ መሰል ሁኔታ የዩናይትድ ስቴትስ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሬክስ ቲለርሰን ዩናይትድ ስቴትስ በዚህ ጉዳይ ከዩናይትድ ኪንግደም ጋር እንደምትስማማ ተናግረዋል። ቴሬዛ ሜይ ሰኞ ዕለት ከፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኤማኑኤል ማክሮን ጋር በጉዳዩ ዙሪያ ተነጋግረው ነበር። የኔቶ ዋና ጸሐፊ የሆኑት ጄንስ ስቶለተንበርግ የነርቭ ጎጂው ኬሚካል አጠቃቀም ''አስቀያሚ እና ተቀባይነት ሊኖረው የማይችል ነው'' ሲሉ ተደምጠዋል። የሩስያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ የሆኑት ማሪያ ዛካሮቫ ቴሬዛ ሜይ ''በእንግሊዝ ፓርላማ ያደረጉት መግለጫ የሰርከስ ትርዒት ነበር'' ብለዋል። የቢቢሲ ፖለቲካ አርታዒ ሎራ ኩዎንዝበርግ በቦሪስ ጆንሰንና በሩስያው አምባሳደር አሌክሳንደር ያኮቬንኮ መካከል የተደረገው ንግግር የተረጋጋና ቀጥተኛ ነበር ብላለች። ሁለቱ እጅ እንዳልተጨባበጡና ቦሪስ ጆንሰን የእንግሊዝን ሕዝብ 'ቁጣ' እንዳንፀባረቁ አርታኢዋ ፅፋለች።
news-53660953
https://www.bbc.com/amharic/news-53660953
በቤይሩቱ ፍንዳታ የሟቾች ቁጥር ከ100 በላይ ሆኗል
በሌባኖሷ መዲና ቤይሩት በተከሰተው ከባድ ፍንዳታ ቢያንስ 100 ሰዎች መሞታቸውን እና ከ4 ሺህ በላይ ሰዎች ደግሞ የተለያየ መጠን ያለው ጉዳት እንደደረሰባቸው ተነግሯል።
ትናንት ከሰዓት ላይ ፍንዳታው ሲያጋጥም መላ መዲናዋ በፍንዳታው ተናውጣ ነበር። ፕሬዝደንት ማይክል አኑን ፍንዳታው ባገጠመበት ቦታ ላይ 2750 ቶን የሚመዝን አልሙኒየም ናይትሬት ደኅንነቱ ባልተጠበቀ ሁኔታ ለስድስት ዓመታት ተከማችቶ ነበር ብለዋል። ፕሬዝደንቱ ለዛሬ አስቸኳይ የካቢኔ ሰብሰባ የጠሩ ሲሆን፤ ለሁለት ሳምንታት የሚዘልቅም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጀዋል። ሌባኖስ ለሦስት ቀናትም የብሔራዊ የሃዘን ቀን አውጃለች። ከዚህ በተጨማሪ ፕሬዝደንቱ 66 ሚሊዮን ዶላር የአስቸኳይ ጊዜ የገንዘብ ድጋፍ እንዲመደብ አዘዋል። “ከባድ አደጋ ነው የገጠመን። ህይወታቸውን ያጡ እና ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በየቦታው ነው የሚገኙት” ያሉት የሌባኖስ ቀይ መስቀል ሥራ አስኪያጅ ጆርጅ ጄታኒ ናቸው። የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች አሁንም ድረስ ተጎጂዎችን ከፍርስራሽ ስር እያወጡ ይገኛሉ። በዚህም የሞቱ እና ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ቁጥር ሊጨምር ይችላል ተብሏል። ትናንት ባለስልጣናት ለፍንዳታው ቀጥተኛ ምክንያት ምን እንደሆነ ምርመራ እንዲካሄድ ወስነው ነበር። የሌባኖስ የጦር ኃላፊ ለፍንዳታው ተጠያቂ ሆነው የሚገኙት ላይ የሚቻለውን “ከፍተኛ ቅጣት ይተላለፍባቸዋል” ብለዋል። አልሙኒየም ናይትሬት ምንድነው? አልሙኒየም ናይትሬት በርካታ ጠቀሜታዎች ቢኖሩትም፤ አብዛኛውን ጊዜ ጥቅም ላይ የሚውለው ለእርሻ ሥራ ማዳበሪያነት እና ተቀጣጠይ ነገር ሆኖ ነው። አልሙኒየም ናይትሬት ከእሳት ጋር ከተገናኘ እጅግ ተቀጣጣይ ሲሆን እንደመጠኑ ፍንዳታ ያስከትላል። በእሳት ሲያያዝ ናይትሮጅን ኦክሳይድ እና አሞኒያ ጋዝ የሚባሉ ለጤና ጎጂ የሆኑ አደገኛ የጋዝ ልቀትን ያስከትላል። ይህ ኬሚካል አደገኛ ተቀጣጣይ እንደመሆኑ መጠን የሚጓጓዝበት እና የሚከማችበት ሁኔታን በተመለከት ጥብቅ መመሪያዎች ተፈጻሚ ይሆናሉ። አልሙኒየም ናይትሬቱ ለምን አስፈለገ? የሌባኖስ ዜጎች እንዴት ከ2700 ቶን በለይ የሚመዝን ተቀጣጣይ ነገር በመሃል ከተማ በመኖሪያ ስፍራ ላይ ይከማቻል ሲሉ እየጠየቁ ይገኛሉ። የአገሪቱ ፕረዝደንት አልሙኒየም ናይትሬቱ ለስድስት ዓመታት በስፍራው ተከማችቶ መቆየቱን ተናግረዋል። ዜጎች ይህ "የመንግሥት እንዝላልነትን የሚያሳይ ነው" እያሉ አጥብቅ የመንግሥትን ቸልተኝነት እየኮነኑ ይገኛሉ። የመከከለኛው ምሥራቅ እና ሰሜን አፍሪካ የቻተም ሃውስ ፕሮግራም መሪ የሆነችው ሊና ካሃቲብ፤ "2750 ቶን አልሙኒየም ናይትሬት ማን ምን ሊያደርግለት ይፈልጋል?" ስትል ጠይቃለች። ሊና ይህ ኬሚካል ተቀጣጣይ ነገሮችን ለመሠራት ጥቅም ላይ ሊውል እንደሚችል በማስታወስ፤ የሌባኖሱ ታጣቂ ኃይል ሔዝቦላህ የቤይሩት ወደብ በመጠቀም አልሙኒየም ናይትሬት በድብቅ ወደ አገር ውስጥ እንደሚያስገባ ተናግራለች። ይሁን እንጂ አልሙኒየም ናይትሬቱ ይህን አይነት ጉዳት እንዲያስከትል ያደረገው ምን እንደሆነ አልተረጋገጠም። ከፍንዳታ በብዙ ርቀት ላይ የሚገኙ ህንጻዎች ጭምር ጉዳት ደርሶባቸዋል። ፍንዳታው ያጋጠመው የከተማዋ ወደብ የሚገኝበት አቅራቢያ ሲሆን በስፍራው ተከማችቶ የነበረው አልሙኒያም ናይትሬት ከ6 ዓመታት በፊት ከአንድ መርከብ ላይ ወርዶ በስፍራው እንዲከማች ተደርጓል። ይህ ፍንዳታ የተከሰተው የሌባኖስ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ከፍተኛ ደረጃ ላይ በደረሰበት ወቅት ነው። የዓለም ምጣኔ ሃብት ፎረም በዓለማችን ላይ በከፍተኛ ውዝፍ እዳ ውስጥ ከሚገኙ አገራት መካከል ሌባኖስን በሦስተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል። ከሳምንታት በፊት ሥራ አጥ የሆኑ የሌባኖስ ወጣቶች አደባባይ ወጥተዋል። የቫይረሱን ስርጭትም የአገሪቱን ኢኮኖሚ ግን 'ከድጥ ወደ ማጡ' እንዲገባ ሊያደርገው እንደሚችል ተገምቷል። ከዚህም በተጨማሪ በአውሮፓውያኑ 2005 ላይ የቀድሞ የሌባኖስ ጠቅላይ ሚንስትር ራፊክ ሃሪሪን ገድለዋል የተባሉ አራት ተጠርጣሪዎች ላይ የፊታችን ዓርብ በሌሉበት ብይን ይሰጣል ተብሎ በሚጠበቅበት ወቅት ነው ፍንዳታው ያጋጠመው። በጠቅላይ ሚንስትሩ ግድያ የፍርድ ውሳኔ የተላለፈባቸው አራቱም ግለሰቦች በኢራን መንግሥት የሚደገፈው የሔዝቦላህ ቡድን አባላት ናቸው። ሔዝቦላህ በጠቅላይ ሚንስትሩ ግድያ ውስጥ እጄ የለበትም ሲል በተደጋጋሚ ተከላክሏል። የቤሩት ፍንዳታ በብዙ ርቀት ላይ የሚገኙ ህንጻዎችን አውድሟል የተፈጠረው ምን ነበር? ፍንዳታው ያጋጠመው ከሰዓት በኋላ 9 ሰዓት ገደማ ላይ ነበር። ወደብ አቅራቢያ የደረሰው ፍንዳታ ወደቡን ከሥራ ውጪ አድርጎታል። ፍንዳታው የፈጠረው ንቅናቄ ከ240 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ ተሰምቶ ነበር። በቆጵሮስ ደሴት ላይ የሚኖሩ ሰዎች የመሬት መንቀጥቀጥ መስሎን ነበር ብለዋል። የአገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ፍርስራሽ ሥር የተቀበሩ ሰዎች ምስልም ማስመልክት ጀመሩ። በብዙ ርቀት ላይ የሚገኙ ህጻዎች እና ተሽከርካሪዎች በፍንዳታው ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸው ታይተዋል። “በፍንዳታው ዙሪያ የነበሩ ህንጻዎች በሙሉ ፈራርሰዋል። የመስታውት ስብርባሪ ላይ እየተራመድኩ እገኛለሁ” ሲል አንድ የዓይን እማኛ ለኤኤፍፒ የዜና ወኪል ተናግሯል። ሆስፒታሎች የሕክምና እርዳታ በሚፈልጉ ሰዎች መጨናነቅ የጀመሩት ወዲያው ነበር። አስክሬን ማቆያ ስፍራ እየተዘጋጀ ነው እስካሁን በፍንዳታው ከ100 በላይ ሰዎች መሞታቸው ይረጋጋጥ እንጂ ከፍንዳታው መጠን እና ካደረሰው ጉዳት አንጻር የሟቾች ቁጥር ከዚህ በላይ እንደሚሆን ይጠበቃል። የሌባኖስ ቀይ መስቀል ማህበር ከሌባኖስ የጤና ባለስልጣናት ጋር በመሆን የሰዎች አስክሬን እሰከሚለይ እንዲሁም ለቀብር እስኪዘጋጅ ድረስ የማቆያ ስፍራ ለማቋቋም እየሰሩ መሆኑ ተነግሯል። ፍንዳታው ያጋጠመበት ስፍራ ይሰሩ የነበሩ የወደብ ሠራተኞች ከፍተኛ ጉዳት እንዳጋጠማቸው ታውቋል። ከ300 ሺህ በላይ ቤት አልባ ሆነዋል የቤይሩት አስተዳዳሪ የሆኑት ማርዋን አባውድ ለኤኤፍፒ የዜና ወኪል እንደተናገሩት ፍንዳታው ከ300 ሺህ በላይ ሰዎችን ቤት አልባ አድርጓል። አስተዳዳሪው ጨምረው እንደተናገሩት በፍንዳታው ምክንያት የደረሰው ጉዳት በገንዘብ ሲለካ ከ3-5 ቢሊዮን ዶላር እንደሚገመት ተናግረዋል። የመካከለኛው ምሥራቅ 'ዘ ኢኮኖሚስት' አርታዒ ከታች ያሉትን የመኖሪያ ቤቱን ምስል በትዊተር ገጹ ላይ አጋርቷል።
45267707
https://www.bbc.com/amharic/45267707
ሻደይ፦ለሴቶች፣ በሴቶች ፌስቲቫል
በየአመቱ ከነሐሴ 14 ጀምሮ ለሶስት ቀናት በሰቆጣ፣ በላሊበላና በትግራይ ክልል የሚገኙ ሴቶች በመንገዶችና አደባባዮች ላይ በመውጣት ነፃነታቸውን የሚያውጁበት እንደሆነ ይነገራል።
በአማራ ክልል በሰቆጣና በላሊበላ ሻደይ፣ አሸንድየ፤ በትግራይ ክልል አሸንዳ ክብረ በዓል ሴቶችን ማዕከል ያደረገ፤ ለሴቶችና በሴቶች የምትዘጋጅ ክብረ በዓል ናት። ሴቶች ያለምንም ተፅእኖ የሚጫወቱበት ባህል እንደሆነ የሰቆጣ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ቸኮሉ በለጠ ይናገራሉ። ቤተሰቦች አልባሳትንና ጌጥን ከመግዛት ጀምሮ፣ በባህሉ ለሴቶች ብቻ ተብሎ የተተወውንም የቤት ስራም ለሶስት ቀናት ያህል ለመስራት አይገደዱም ይላሉ። •"ማንም መብታችንን ሊሰጠን ስለማይችል፤ ሴቶች ማንንም ሳይጠብቁ በራሳቸው መታገል አለባቸው" •የተነጠቀ ልጅነት •የባለዳንቴሏ የክር ጫማዎች "በሶስቱ ቀናት ሴቶች ነፃ ሆነው መጫወት ብቻ ነው ያለባቸው" ይላሉ። የበዓሉ አከባበር ሻደይ የሚለው ቃል አገውኛ ሲሆን የቅጠል ስያሜ ነው የሚሉት ወይዘሮ ቸኮሉ አሸንዳ/ አሸንዳየ/ ከሚሉት ሌሎች ስያሜዎች ጋርም የበዓሉ አከባበሩም ሆነ መነሻው ተመሳሳይነት አለው ይላሉ። ዝግጅቱ የሚጀምረው ከሳምንት በፊት ሲሆን የአንድ ሰፈር ሰዎች በመሰባሰብ፣ የሚለብሷቸውን አልባሳት መምረጥ፣ ጌጣጌጦችን በመግዛትና በመጨረሻም ቡድኑን የሚያስተባብር አንድ ሰብሳቢም በመምረጥ ይጀመራል። አከባበሩ በሶስት የእድሜ እርከን ተከፍሎ የነበረ ሲሆን እስከ 10 አመት ዕድሜ ያላቸው ህፃናት፤ ከ10-15 አመት ድረስና ከ15 አመት በላይ የነበረ ቢሆንም፤ አሁን ለህፃናት የተተወ መሆኑን ይናገራሉ። ከ15 አመት በላይ የሆኑት ድኮት (የእጅ አምባር)፣ ሁለት አይነት መስቀል፣ በአንገታቸው ድሪ፣ የብር አልቦ እግራቸው ላይ ያጠልቃሉ፤ በጥልፍ ቀሚስ ተሽቆጥቁጠው ይሄዳሉ። ከ15 አመት በታች የሆኑት ከብር የተሰራ ድሪ፤ ትልልቅ ክብ ቀለበት ጆሮ ጌጥ፤ ከ10 አመት በታች የሆኑት ቁንጮና ጋሜ (መሀል ፀገራቸው ተላጭቶ ዳርዳሩን ያደገ) የፀጉር ቁርጥ ይቆረጣሉ። ጉዟቸውንም የሚጀምሩት ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ነው ሲሆን በቀድሞው ጊዜ ወደ አካባቢው አስተዳደር ወይም አገረ ገዥው ይሄዱ እንደነበር ወይዘሮ ቸኮሉ ያስታውሳሉ። በአሁኑ ወቅት በአካባቢያቸው ያሉ ትልልቅ ሰዎች ቤት በመሄድ ዘፈናቸውን ይጀምራሉ። "አስገባኝ በረኛ፣ አስገባኝ ከልካይ፤ እመቤቴን ላይ" በማለት ማንጎራጎር ሲጀምሩ በሩ ይከፈትላቸዋል " ይሄ የማን አዳራሽ የጌታየ የድርብ ለባሽ፤ ይሄ የማን ደጅ የእመቤቴ የቀጭን ለባሽ" በማለት ዘፈናቸውን ይቀጥላሉ። በእለቱ ከሚዘፈኑ ዘፈኖች መካከል በሰቆጣ ከተማ ታዋቂው ዘፈን "አሽከር አበባየ አሽከር ይሙት፣ ይሙት ይላሉ የኔታ አሽከር አይደለም ወይ የሚሆነው ጌታ"እንደሆነ ወይዘሮ ቸኮሉ ይገልፃሉ። በር ተከፍቶላቸው ከገቡ በኋላ የቤቱን ባለቤቶች ማወደስ ይጀመራል። ከውደሳዎቹም መካከል "ከፈረስ አፍንጫ ይወጣል ትንኝ፤ እሰይ የኔ ጌታ ጤና ይስጥልኝ፤ ምድር ጭሬ፣ ጭሬ አወጣሁ ማሰሮ እሰይ የኔ እመቤት ድልድል ወይዘሮ" ይገኙበታል። ይቀጥሉናም "ስለለየ፣ ስለለየ ....እሰይ የኔ እመቤት የፈተለችው ሸማኔ ታጥቶ ማርያም ሰራችው" በማለት ያንጎራጉራሉ። ዘፍነው ሽልማት ካልተሰጣቸው ወይ ከዘገየ "አንቱን አይደለም የማወሳሳው፤ ቀና ብለው እዩኝ የሰው ጡር አለው" ብለው በነገር ሸንቆጥ ያደርጓቸዋል። በዚያን ቀን ያው ሽልማት መስጠት ግድ ነው፤ እሱን ተቀብለው "አበባየ ነሽ አበባየ ጉዳይ ሰመረች በአንች ላይ" እያሉ ወደ ሌላ መንደር ይሄዳሉ። በአራተኛው ቀን በተለያዩ ሰፈሮች ያሉ ሴቶች ተሰብስበው በግጥምና በዜማ ውድድር እንደሚጀምሩ ወይዘሮ ቸኮሉ ይናገራሉ። ህዝብ በተሰበሰበት ቦታም በዘፈን ከሚገጠሙት መካከል " የቀሃ ገብርኤል ልጅ የሰራችው ዶራ ኩኩ ብሎ ወጣ መጉላሊቱን ሰብሮ" በማለት ሲዘፍኑ በምላሹ " የመከንዝባ ልጅ መጣች ተመልሳ፤ ከወገቧ በላይ አመድ ተለውሳ፤ከወገቧ በታች አቡጀዲ ታጥቃ" ይሉና ተመራርቀው፣ ተቃቅፈው ይለያያሉ። የበዓሉ መሰረት ክብረ በዓሉ ባህላዊና ኃይማኖታዊ መሰረት እንዳለው ወይዘሮ ቸኮሉ ይነገራሉ። መነሻውም አንድ የእስራኤል ንጉስ ጠላቴን አሸንፌ ከመጣሁ መጀመሪያ ያገኘሁትን መስዋዕት አደርጋለሁ ብሎ ቃል ገባ። አሸንፎ ሲመጣ የተቀበለችው አንዷ ልጁ ሆና ተገኘች። አባትው ቢያዝንም ልጁ እንዳፅናናችው የምትናገረው ወይዘሮ ቸኮሉ "ልጃገረድ ስለነበረች ከጓደኖቼ ጋር ተራራ ላይ ተጫውቼ ልምጣ ብላ ተጫውታ መስዋዕት ሆነች" ይላሉ። ክብረ በዓሉም ልጅቷ ለሶስት ቀናት ያህል የተጫወተችበትን ማስታወሻ እንደሆነ ይናገራሉ። ከዚህም በተጨማሪ ክብረ በዓሉ መፅሐፍ ቅዱስንና ትውፊቶችን በማጣመር ማርያም በምታርግበት ወቅት ለሐዋርያት የተገነዘችበትን ሰበን (ቅጠል) የሰጠቻቸው ማስታወሻ እንደሆነ ይናገራሉ። ከትውልድ ትውልድም የተለያዩ ትውፊቶች እየተጨመሩበት ለማስታወሻነትም ቅጠሉን ሴቶች በጀርባቸው በኩል አስረው እንደሚጫወቱ ወይዘሮ ቸኮሉ ይናገራሉ። በአመታት ውስጥ አከባበሩ ቀዝቅዞ የነበረ ሲሆን በባለፉት ጥቂት አመታት ብቻ እንደ አዲስ መከበር እንደጀመረ ይናገራሉ። "የባለፉትን ሃያ አመታት የነበረው ትውልድ ትውፊቱን ዘንግቶታል፤ እየደበዘዘ ነበር" ይላሉ።
news-52902906
https://www.bbc.com/amharic/news-52902906
ደቡብ ሱዳን በግዛቷ ግብጽ የጦር ሰፈር እንድታቋቁም ፈቅዳለች?
የደቡብ ሱዳን በግዛቷ ውስጥ ግብጽ ጦር ሰፈር እንድታቋቁም ፈቃድ ሰጥታለች እየተባለ የሚነገር ሐሰት መሆኑን ዛሬ ጠዋት የአገሪቱ ጦር ሠራዊት አስታወቀ።
ከትናንት ጀምሮ የተለያዩ ምንጮች ግብጽ በደቡብ ሱዳን ውስጥ ጦር ሰፈር እንዲኖራት ጥያቄ አቅርባ ተቀባይነት እንዳገኘች ሲናፈስ ነበር። መረጃው የደቡብ ሱዳን መንግሥት በጥያቄው ተስማምቶ በአገሪቱ ምሥራቃዊ ክፍል ከኢትዮጵያ ጋር በሚያዋስነው ፓጋክ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ጦር ሰፈሯን እንድታቋቁም ፈቅዷል የሚል ነበር። "የተባለው ነገር ሐሰተኛ ዜና ነው። በሁለቱ አገራት ውስጥ ስምምነት ተደርጎ ቢሆን ኖሮ የደቡብ ሱዳን ጦር ሠራዊት ቀድሞ ያውቅ ነበር። ምንም አይነት ስምምነት አልተደረገም" ሲሉ አንድ ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ ከፍተኛ የጦር ባለስልጣን መናገራቸው ተዘግቧል። የጦር ባለስልጣኑ ጨምረው እንደተናገሩት "ከኢትዮጵያ ጋር የመከላከያ ስምምነት ስላለን ያንን በመጣስ ምንም አናደርግም። ኢትዮጵያ የዛሬዋ ደቡብ ሱዳን እንድትመሰረት አስተዋጽኦ አድርጋለች" ሲሉ ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን ጥብቅ ቁርኝት ገልጸዋል። ቢቢሲ አዲስ አበባ ከሚገኘው የደቡብ ሱዳን ኤምባሲ ስለጉዳዩ መረጃ ለማግኘት ጥረት እያደረገ ቢሆንም እስካሁን አልተሳካለትም። ይህ ደቡብ ሱዳን፣ ግብጽ ፓጋክ በተባለው ግዛቷ ውስጥ የጦር ሰፈር እንድታቋቁም ፈቅዳለች የሚለው ዜና ጁባ ቲቪ እና ሳውዝ ሱዳን ኒውስ ናው በተባሉ መገናና ብዙኀን ላይ ከተሰራጨ በኋላ ነው ከፍተኛ ትኩረትን ያገኘው። የጦር ሰፈሩ ይቋቋምበታል ተብሎ የተጠቀሰው ስፍራ ፓጋክ ደቡብ ሱዳንን ከኢትዮጵያ ጋር በሚያዋስነው ድንበር አቅራቢ ያለ ቦታ ሲሆን፤ ቦታው የአገሪቱ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ሬክ ማቻር የሚመሩት ተቃዋሚው የሱዳን ሕዝብ ነጻነት ንቅናቄ ጠንካራ ይዞታ ነው። ወሬውን ትኩረት እንዲስብ ያደረገው ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ እየገነባችው ያለው ግዙፍ ግድብን በተመለከተ ከሱዳንና ከግብጽ ጋር እያደረገችው የነበረው ድርድር መቋጫ ሳያገኝ በእንጥልጥል ባለበት ጊዜ መሆኑና ኢትዮጵያ ግድቡን በቀጣይ ወር በውሃ መሙላት ለመጀመር በምትዘጋጅበት ጊዜ መሆኑ ነው።
news-54115494
https://www.bbc.com/amharic/news-54115494
እግር ኳስ፡ ዛሬ የሚጀምረውን የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ማን ያሸንፍ ይሆን?
በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የ2020/21 እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ፉልሃም ከአርሰናል በሚያደርጉት ጨዋታ 8፡30 ሲል ይጀምራል።
ዛሬ ከሚደረጉ 4 ጨዋታዎች መካከል፣ ያለፈው ዓመት የውድድር ዘመን አሸናፊዎቹ ሊቨርፑሎች፣ ፕሪምየር ሊጉ ከተቀላቀሉት ሊድስ ዩናይትድ ጋር በአንፊልድ የሚያደርጉት ጨዋታ አንዱ ነው። ማንችስተር ሲቲ፣ ማንችስተር ዩናይትድ፣ ቼልሲና ዎልቭስ ፕሪምየር ሊጉ ከተጠናቀቀ በኋላ በአውሮፓ የውድድር መድረኮች ሲሳተፉ ስለነበር ጨዋታቸውን የሚጀምሩት በሚቀጥለው ሳምንት ነው። በዘንድሮ ፕሪሚየር ሊግድ ውድድር ፉልሃም፣ ሊድስ ዩናይትድ እና ዌስት ብሮም አልቢን አዲስ ተሳታፊ ቡድኖች ናቸው። ሊድስ ዩናይትድ ከ16 ዓመታት ጥበቃ በኋላ ወደ እንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ መመለሱን ሲያረጋግጥ፣ ዌስት ብሮም ደግሞ በቻምፒየንሺፕ ውድድር እስከመጨረሻው ጨዋታ ድረስ ጠብቆ ወደ ፕሪምየር ሊግ ማለፋቸውን አረጋግጠዋል። ፉልሀም ደግሞ በመጨረሻው የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ብርንትፎርድን በዌምብሌይ ስታዲየም በማሸነፍ በዘንድሮው ፕሪምየር ሊግ መሳተፍ የሚያስችላቸው ዕድል አግኝተዋል። ኖርዊች፣ ዋትፎርድና ቦርንማውዝ ወደ ቻምፒየንሺፑ በመውረድ ከላይ ለተጠቀሱት ሶስት ክለቦች ቦታቸውን የለቀቁ ቡድኖች መሆናቸው ይታወሳል። ደጋፊዎች ወደ ስታዲም መቼ ይመለሱ ይሆን? የዘንድሮው የውድድር ዓመት በዝግ ስታዲየሞች የሚጀመር ሲሆን የኮሮናቫይረስ ስርጭትና ሁኔታዎች እየታየ ተመልካቾች ቀስ በቀስ ወደ ስታዲየሞች መግባት እንደሚጀምሩም ተስፋ ተደርጓል። ምናልባትም የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች በዝግ ስታዲየም የሚካሄዱት እስከ ጥቅምት ወር ድረስ ብቻ ሊሆን ይችላል። አርሰናል ከሼፊልድ በኢሚሬትስ በሚያደርጉት ጨዋታ ታዳሚዎች በአነስተኛ ቁጥር ወደ ስታዲየም ሊመለሱ ይችላሉ የሚል ቅድመ ዝግጅት አለ። እንደውም አንዳንድ ቡድኖች በሙከራ ደረጃ የቅድመ ውድድር ጨዋታዎችና የሊጉ የመክፈቻ ጨዋታዎች በተመልካቾች ፊት እንዲካሄድና ሁኔታዎች እየታዩ ማስተካከያዎች እንዲደረጉ ሀሳብ አቅርበው ነበር። አዲስ ፈራሚዎች በዘንድሮው የዝውውር መስኮት ከፕሪሚየር ሊግ ቡድኖች እንደ ቼልሲ ድንቅ ተጫዋቾችን የሰበሰበ የለም። ፍራንክ ላምፓርድ እስካሁንም ስድስት ተጫዋቾችን ያስፈረመ ሲሆን ተጨማሪ ተጫዋቾችን ወደ ስታንፎርድ ብሪጅ ለማምጣት ቸልሲዎች ደፋ ቀና እያሉ ነው። የተከላካይ መስመር ተጫዋቹን ቲያጎ ሲልቫ ከፈረንሳዩ ፒኤስጂ፣ የግራ መስመር ተመላላሹ ቢን ቺልዌልን ከሌስተር ሲቲ፣ የአያክሱን የክንፍ መስመር አጥቂ ሃኪም ዚዬክ፣ የአርፒ ሌፕሲዥ የጎል አነፍናፊው ቲሞ ቨርነር፣ የባየር ሊቨርኩሰን የጨዋታ አቀጣጣዩ ኪያ ሃርቭዝ እንዲሁም ወጣቱን ተከላካዩ ማላንግ ሳር ከኒስ አስፈርመዋል። በዘንድሮው የዝውውር መስኮት በንቃት እየተሳተፉ የሚገኙት ደግሞ ኤቨርተኖች ናቸው። በካርሎ አንቸሎቲ የሚመሩት ኤቨርተኖች አብዱላዬ ዱኩሬን ከዋትፎርድ፣ ሃመስ ሮድሪጌዝን ከሪያል ማድሪድ እንዲሁም አላንን ከናፖሊ አስፈርመዋል። አርሰናል እስካሁን የሊሉን ተከላካይ ጋብሪኤል ማጋሊያስ እንዲሁም የቼልሲውን ዊሊያን ያስፈረመ ሲሆን ማንቸስተር ዩናይትዶች ደግሞ የአያክሱን የመሃል ሜዳ ተጫዋች ቫን ደ ቢክን አስፈርመዋል። ማን በበላይነት ያጠናቅቃል? የዘንድሮውን የውድድር ዓመት የትኛው ቡድን በአሸናፊነት ያጠናቅቃል የሚለው ጥያቄ ደግሞ የዘርፉ ባለሙያዎችን ለሁለት ከፍሏል። አንደኛው ጎራ ሊቨርፑሎች በድጋሚ ሻምፒዮን ይሆናሉ ሲል በሌላኛው ጎራ ደግሞ ዘንድሮ ማንቸስትር ሲቲዎች የሚያቆማቸው የለም ይላሉ። በርካታ አቋማሪ ድርጅቶች ግን ዘንድሮ ማንቸስተር ሲቲ እንደሚያሸንፍ ግምታቸውን እያስቀመጡ ነው። ነገር ግን የሲቲዎች ደካማ የተከላካይ መስመር ብዙ ጎሎችን የሚያስተናግድ ከሆነ አሁንም ለሊቨርፑል ዋንጫውን አሳለፈው ሊሰጡ እንደሚችሉ ተገምቷል። ሊቨርፑሎችም ቢሆኑ በዘንድሮው የዝውውር መስኮት ቡድኑን ሊቀይር የሚችል ተጫዋች እስካሁን አለማስፈረማቸው ጨዋታዎቻቸውን ከባድ ሊያደርግባቸው እንደሚችል ባለሙያዎቹ አስጠንቅቀዋል። በተጨማሪም ቡድኖች ከዚህ በኋላ ለሊቨርፑል የሚሆን አይነት አጨዋወት ይዘው እንደሚመጡ መገመት አይከብድም። ማንቸስተር ዩናይትድ እና ቼልሲ ደግሞ ቡድናቸውን በማጠናከር ስራ ላይ እንደመሆናቸው መጠን ከአንድ እስከ አራት ውስጥ ይጨርሳሉ አይጨርሱም የሚለው እንጂ የሊጉ ሻምፒዮን እንደማይሆኑ ግልጽ ነው ብለዋል አቋማሪዎቹ ድርጅቶች። አርሰናል፣ ቶተንሃም፣ ሌስተር ሲቲና ኤቨርተን ደግሞ ከአምስተኛ በታች ያለውን ቦታ ይዘው እንደሚጨርሱ ግምታቸውን አስቀምጠዋል።
50328013
https://www.bbc.com/amharic/50328013
ናይጄሪያ፡ ከንቲባው "ክቡርነትዎ" አትበሉኝ አሉ
የናይጄሪዋ ሌጎስ ከንቲባ "ክቡርነትዎ" ብላችሁ አትጥሩኝ ማለታቸው ተሰምቷል።
ከንቲባ ባባጂዴ ሳኖዎ - ኦሉ እንዳሉት፤ "ክቡርነትዎ" የሚለው አጠራር አምባገነን መሪን ያመለክታል። "አጠራሩ መታበይን፣ ራስን እንደ ጣኦት መመልከትን ያሳያል" ብለው፤ ሰዎች "ከንቲባ" ብለው እንዲጠሯቸው አሳስበዋል። • ከንቲባ ለመሆን ፈተናዎችን የሰበረች • ታግተው የነበሩት የትሪፖሊ ከንቲባ ተለቀቁ • የጆሃንስበርግ ከንቲባ በዘር ምክንያት ከሥልጣናቸው ለቀቁ ከንቲባው እንደሚሉት፤ "ክቡርነትዎ" የሚለው አጠራር የሕዝብ ተመራጮች ጨቋኞች እንዲሆኑ ያነሳሳል፤ ባለሥልጣኖች የሕዝብ ኃላፊነት እንዳለባቸው እንዲዘነጉም ያደርጋል። ስለዚህም፤ "የጨዋ አጠራር ለመጠቀም እንዲሁም በሰዎች ሕይወት ለውጥ ለማምጣትም" መወሰናቸውን አስረድተዋል። የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች በበኩላቸው፤ ጥያቄያቸው የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ጉዳይ እንጂ፤ ከንቲባው እንዴት ይጠሩ? የሚለው ግድ እንደማይሰጣቸው ተናግረዋል። ሌጎስ ውስጥ በጎርፍ ጉዳት የደረሰባቸውና ለጥገና በቂ በጀት ያልተመደበላቸው ጎዳናዎች የትለሌ ናቸው።
news-45936976
https://www.bbc.com/amharic/news-45936976
ፈረንሳያዊው አርፋጅ ተማሪ መምህሩ ላይ የመጫወቻ ሽጉጥ በመደቀኑ ተከሰሰ
ፈረንሳዊው ተማሪ መምህሩ ላይ ሽጉጥ ሲደቅን የሚያሳየው ተንቀሳቃሽ ምስል ከታየ በኋላ በከፋ ጠብ አጫሪነት ተከሷል።
የፈረንሳይ የትምህርት ሚኒስትር በጉዳዩ ላይ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሲሰጡ ተማሪው በወንበሯ ላይ የተቀመጠችው መምህርት ላይ የፕላስቲክ መጫወቻ ሽጉጥ ደቅኖ ቀሪ እንዳታደርገው እየጮሀ ሲናገር በተንቀሳቃሽ ምስሉ ላይ ይታያል። ድርጊቱ አብረውት በሚማሩ የክፍል ጓደኞቹ ተቀርጾ በማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን ላይ የተለቀቀው ሐሙስ ዕለት ነበር። • ዛሚ ሬዲዮ ሊዘጋ ይሆን? • ኢትዮጵያዊያን በህጋዊ መንገድ ለሥራ መሄድ የሚችሉባቸው ሃገራት የትኞቹ ናቸው? • በሥራ ቃለ መጠይቅ ወቅት ልንላቸው የማይገቡ 7 ነጥቦች መምህርቷ ግን ምንም እንዳልተፈጠረ ሁሉ ለተማሪዎቹ እያስረዳች ላፕ ቶፑዋ ላይ ስትሰራ ትታያለች። ተማሪው አርፍዶ በመምጣቱ ምክንያት ቀሪ በመደረጉ መበሳጨቱን በአካባቢው የሚታተም አንድ ጋዜጣ ዘግቧል። የ15 ዓመቱ ተማሪ ድርጊቱን "ለቀልድ ነው" ብሎ ያስተባበለ ሲሆን እየተቀረፀ መሆኑንም እንዳላወቀ ለመገናኛ ብዙሃን ተናግሯል። መምህርቷ አርብ ዕለት ወደ ፖሊስ ዘንድ ሄዳ አቤቱታዋን አቅርባለች። ተማሪውም ወላጅ አባቱን በመያዝ የዚኑ ዕለት ፖሊስ ጣቢያ ድረስ ሄዶ እጁን ሰጥቷል። ድርጊቱ በፕሬዝዳንት ማርኮንና በሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትሩ የተኮነነ ሲሆን በሚቀጥለው ሳምንት በትምህርት ቤቶች ውስጥ የሚከሰትን አመፅ ለመከላከል የሚያስችል ውይይት ይካሄዳል ተብሏል። በትምህርት ቤቱ ላለፉት 25 ዓመታት እንደሰሩ የተናገሩ አንድ መምህር ሌሞንድ ለተሰኘ ጋዜጣ እንደተናገሩት "እንዲህ አይነት ድርጊት አልተለመደም" ካሉ በኋላ ተማሪዎቹ "የተግባቦት ክህሎትና ግብረገብ" እንደሚማሩ ተናግረዋል።
news-53879112
https://www.bbc.com/amharic/news-53879112
ኮሮናቫይረስ ፡ በጀርመን የወረርሽኙን አደጋ ለማጥናት የሙዚቃ ድግሶች ተዘጋጀ
ወረርሽኙን ለመቆጣጠር አካላዊ ርቀትን ጠብቁ፤ ሰው የሚሰባሰብበት ቦታ አትሂዱ፤ ከሄዳችሁም ጥንቃቄ አይለያችሁ በሚባልበት ጊዜ የጀርመን ተመራማሪዎች ግን በአንድ ቀን ሦስት የፖፕ ሙዚቃ ድግስ አሰናድተዋል።
ታዲያ በግድ የለሽነትና በማን አለብኝነት አይደለም። ተመራማሪዎቹ ይህን ያደረጉት በዚህ ወረርሽኝ ወቅት ቤት ውስጥ በሚከናወኑና በርካታ ሰዎች በሚሳተፉባቸው ዝግጅቶች የሚከሰተውን አደጋ ለማጥናት ነው። በዚህ የሙዚቃ ድግስ ላይ ዕድሜያቸው በ18 እና 50 መካከል የሚገኙ ጤነኛ በጎ ፈቃደኞች ተሳትፈዋል። የተሳታፊዎቹ ቁጥር ግን ከሚጠበቀው ሲሶ ነው። በሃሌ ዩኒቨርሲቲ በሌፕዚንግ ከተማ የሚሰራው የዚህ ጥናት መሪ ዝግጅቱ በመሳካቱ ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ድምፃዊው እና የሙዚቃ ግጥም ፀሐፊው ቲም ቤንድዝኮ በሦስቱም የሙዚቃ ዝግጅቶች ላይ ሥራዎቹን ለማቅረብ ተስማምቷል። 'ሪስታርት-19' የሚል ስያሜ የተሰጠው የሙዚቃ ድግስ የተሰናዳው በወረርሽኙ ወቅት እንደዚህ ዓይነት ዝግጅቶች ሊከናወኑ የሚችሉበትን ሁኔታዎች ለመመርመር መሆኑን አጥኝዎቹ ተናግረዋል። ቅዳሜ ዕለት ከተሰናዳው ሦስት የሙዚቃ ድግሶች የመጀመሪያው ወረርሽኙ ከመከሰቱ በፊት የነበሩ ዝግጅቶችን ለማስመሰል ያለመ ሲሆን በሥፍራው ምንም ዓይነት የጥንቃቄ መመሪያዎች አልተተገበሩበትም። ሁለተኛው ደግሞ ንፅህና የተጠበቀበትና የተወሰነ አካላዊ ርቀት የተጠበቀበት እንዲሆን ተደርጓል። ሦስተኛው ደግሞ አዳራሹ ከሚይዘው የሰው ቁጥር በግማሽ የተቀነሰ ሲሆን እያንዳንዱ ሰውም በ1.5 ሜትር ልዩነት ተራርቆ ነበር የታደመው። ከዚህም ባሻገር ሁሉም ተሳታፊዎች በዝግጅቱ ላይ ከመሳተፋቸው በፊት የኮቪድ-19 ምርመራ የተደረገላቸው ሲሆን የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ እና አካላዊ ርቀት መጠበቃቸውን የሚከታተል መሳሪያም ተሰጥቷቸዋል። ተመራማሪዎቹም ታዳሚዎቹ በብዛት የሚነካኳቸው የትኞቹን ቦታዎች እንደሆነ ለመከታተልም 'የሚታይ ፀረ ተህዋስ' መጠቀማቸው ተነግሯል። "መረጃ የማሰባሰብ ሂደቱ በጥሩ መልኩ ሄዷል። ጥራት ያለው መረጃ አግኝተናል፤ ድባቡ ደስ የሚል ነበር፤ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማድረግንና ፀረ ተህዋስ በመጠቀም ልምዱም ረክተናል" ብለዋል የጥናቱ መሪ ስቴፋን ሞርቲዝ። ድምፃዊው ቲም ቤንዲዝኮም ዝግጅቱ ከምጠብቀው በላይ ነበር ብሏል። የጥናቱ ውጤት በድጋሜ በታዳሚዎች ፊት እውነተኛ ዝግጅቶችን ለማካሄድ እንደሚረዳ ድምፃዊው ተናግሯል። የጥናቱ የመጀመሪያ ደረጃ ውጤትም መስከረም ወር ላይ ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። የጥናት ፕሮጀክቱ የአደጋውን ደረጃ በመለየት በቤት ውስጥ የሚከናወኑ ዝግጅቶችን እንደገና ለመመለስ ይረዳል በሚልም ከዛክሰኒይ -አንሃልት እና ዛክሶኒይ ግዛቶች የ1.17 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አግኝቷል። ዝግጅቱ ከመካሄዱ በፊት የዛክሰኒይ -አንሃልት የኢኮኖሚና ሳይንስ ሚኒስተር ፕሮፌሰር አርሚን ዊሊንግ ማን፤ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መሰል ዝግጅቶችን ማሰናከሉን ገልፀው፤ "የቫይረሱ ሥርጭት ስጋት ስላለ የሙዚቃ ድግሶች ፣ የንግድ ባዛሮችና ስፖርታዊ ዝግጅቶች መካሄድ አይችሉም፤ በመሆኑም ምን ዓይነት ጥንቃቄዎች እና ቅንጅት ቢደረግ ይህንን አደጋ ሊቀንሱት እንደሚችሉ ለማወቅ ጥናቱ ጠቃሚ ነው" ሲሉ ተናግረዋል። የጥናቱ መነሻ በጀርመን ከሚያዚያ ወር መጨረሻ ጀምሮ በኮቪድ-19 የሚያዙ ሰዎች ከፍተኛ ቁጥር መመዝገቡ ነው። እንደ ሮበርት ኮች ተቋም መረጃ መሰረት ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በአገሪቷ ከ2ሺህ በላይ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሲሆን ይህም አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ቁጥር 232 ሺህ 82 አድርሶታል።
news-47958845
https://www.bbc.com/amharic/news-47958845
"ሕግ ማጥናት ከተለየ መብት ወይም ገንዘብ ጋር አይገናኝም" ኪም ካርዲሽያን
አሜሪካዊቷ ሞዴል፣ የሚዲያ ባለሙያ እና ቱጃር ነጋዴ ኪም ካርዳሺያን ሕግ መማር መጀመሯን ተከትሎ በርካታ አስተያየቶች እየዘነቡባት ነው። ከአስተያየቶቹ መካከል አንዳንዶቹም ሕግ የምታጠናው ሃብታምና ዝነኛ ስለሆነች እንጂ ብቁ ስለሆነች አይደለም የሚለው ይገኝበታል።
ኪም የሕግ ባለሙያ ለመሆን ትምህርት የጀመረችው ባለፈው ሳምንት ነበር። የማጠናቀቂያ ፈተናዋን ከሁለት ዓመታት በኋላ እንደምትወስድም ተነግሯታል። እርሷ እንደምትለው ሕግ የማጥናቷ ጉዳይ ከዝነኝነት አሊያም ከቱጃርነት ጋር ፈፅሞ ሊገናኝ እንደማይችል ተናግራለች። "ደስ ከሚያሰኘን ህልማችን ምንም ነገር ሊወስነን አሊያም ሊገታን አይገባም" ስትል ሕግ ማጥናት መፈለጓ ህልሟ እንጂ ዝነኝነት አለመሆኑን ተናግራለች። • ሙንጭርጭር ስዕሎች • 138 ሰዎች ዜግነታቸውን ተነጠቁ • አልሲሲ እስከ 2030 ግብጽን ሊመሩ ይችላሉ ኪም ከሁለት የሕግ አስተማሪዎቿ፣ ጀሲካ ጃክሰን እና ኤሪክ ሀኒ ጋር የተነሳቻቸውን ፎቶዎች በግል ኢንስታግራሟ ገጿ ላይ ለጥፋ ነበር። በዚህም ምክንያት በርካታ አስተያየቶችን ተመልክቻለሁ የምትለው ኪም "ወደ ሕግ ያመራኝ የተለየ መብት አሊያም ሃብታም ስለሆንኩ አድርገው የተሰጡ አስተያየት ተመልክቻለሁ፤ እውነታው ግን ይህ አይደለም" ብላለች። ከእነዚህ መካከል አንድ ሰው በያዘችው ሙያ ብቻ እንድትቆይ አስተያየቱን ሰጥቷታል። እኔ ግን ትላለች ኪም፤ ማንም ሰው ህልሙንና ራዕዩን ከማሳካት የሚያግደው አንዳች ነገር እንደሌለ መረዳት አለበት ብላለች። እሷ እንዳደረገችው ሁሉ እያንዳንዱ ሰው የራሱን ህልም ሊፈጥር ይችላል። "ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በሳምንት 18 ሰዓታት ትማራለች፤ በየወሩ የፅሁፍና የምርጫ ጥያቄዎችን መስራት ይጠበቅብኛል" ስትል የትምህርቱን ሂደት ገልፃለች። ልምምዱ በዚህ መልክ ካጠናቀቀች የታዋቂው ተዋናይ ፣ የማስታወቂያና የሚዲያ ባለሙያ ኦጀ ሲምፕሰን ጓደኛና የእርሳቸውን የግድያ ሙከራ በተመለከተ ጠበቃ የነበሩትን የአባቷን ሮበርት ካርዳሺያን ፈለግ ትከተላለች። ዝነኛዋ ካርዳሺያን ለብዙዎች ብዥታን የፈጠረውንና የኮሌጅ ትምህርቷን ሳታጠናቅቅ ህግ የምታጠናበትን ምክንያት አስረድታለች። ብዥታው ትክክል መሆኑን ያረጋገጠች ሲሆን የኮሌጅ ትምህርቷን አለማጠናቀቋንም አረጋግጣለች። ነገር ግን" ህግ ለማጥናት 60 የትምህርት ክፍለ ጊዜ የሚያስፈልግ ሲሆን ፤ እኔ ግን 75 ነበረኝ " ስትልም ትሟገታለች። ኪም እንደምትለው ሕግ ለማጥናት የእረፍት ቀናቶቿን፣ ከልጆቿ ሰዓት በመሸራረፍ እየተጠቀመች እንደሆነ ተናግራለች። በእርግጥ ብዙ ጊዜ እንደማልችል ተሰምቶኝ ነበር፤ ነገር ግን በዙሪያዬ ያሉ ሰዎች ድጋፍ አድርገውልኛል ስትልም አክላለች።
news-54378310
https://www.bbc.com/amharic/news-54378310
የስዊዲኑ ልብስ አምራች ኤች ኤንድ ኤም (H&M) የችርቻሮ መደብሮቹን እየዘጋ ነው።
በዓለም ግዙፍ ከሚባሉት የልብስ አምራቾች አንዱ የሆነው የስዊዲኑ ኤች ኤንድ ኤም በቅርቡ ብቻ 250 ማከፋፈያዎችን ሊዘጋ ነው፡፡
እነዚህን ሱቆች የሚዘጋው በሚቀጥለው ዓመት ነው፡፡ ይህን ሁሉ ማከፋፈያና የችርቻሮ መሸጫ ሱቅ ለመዝጋት እንዲወስን ያደረገው ደግሞ በርካታ ደንበኞች ግዢ የሚፈጽሙት ሱቅ እየመጡ ሳይሆን ባሉበት ሆነው በድረ ገጽ መንገድ በመሆኑ ነው፡፡ የገበያው ሁኔታ ከኮቪድ ወረርሽኝ በኋላ አሁን ወደነበረበት እየተመለሰ ነው ያለው ድርጅቱ፣ ነገር ግን በያዝነው መስከረም ሽያጭ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወር ጋር ሲነጻጸር በ5 እጅ ዝቅ ብሎብኛል ይላል፡፡ ኤች ኤንድ ኤም በመላው ዓለም 5ሺ የችርቻሮ መደብሮች አሉት፡፡ አሁን እዘጋቸዋለው ያላቸው መደብሮች የት አገር የሚገኙትን እንደሆነ ለጊዜው አልገለጸም፡፡ በዚህ ረገድ ገና የተብራራ ውሳኔ ላይ አልደረስንም፡፡ እንደ አገሩ ሁኔታና እንደ ገበያው እያየን የምንዘጋ ይሆናል ብሏል ቃል አቀባዩ፡፡ ኤች ኤንድ ኤም አብዛኛዎቹ ከመደብሮች ጋር የሚፈራረመው የኮንትራት ስምምነት በየዓመቱ ኪራይ ሱቆችን የመዝጋት፣ ዋጋ የመደራደር ዕድሎችን ይሰጡታል፡፡ ኤች ኤንድ ኤም ከታክስ በፊት 2.3 ቢሊዮን የስዊድሽ ክሮነር አትርፌያለው ብሎ ነበር፡፡ ድርጅቱ ትርፌ በዚህ ዓመት ወድቋል ቢልም ይህ ብዙ የምጣኔ ሀብት ተንታኞች ከጠበቁት በጣም የተሻለ የሚባል ነው፡፡ ድርጅቱ በኮሮና ምክንያት በመላው ዓለም 166 መደብሮቼ እንደተዘጉ ናቸው ብሏል፡፡ አንዳንዶቹ ደግሞ የሚከፈቱት ለተወሰኑ ሰዓታት ብቻ ነው፡፡ የዓለም ትልልቅ ድርጅቶች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የችርቻሮ መደብሮች አስፈላጊነት ላይ ጥያቄ እያነሱ መሆናቸው የሚታወስ ነው፡፡ የኢንተርኔት መስፋፋትና የክፍያ መዘመን ከጊዜና ገንዘብ ቁጠባ ጋር ተያይዞ ግብይት በበይነ መረብ እየተቀላጠፈ መምጣቱ ምናልባት ወደፊት የችርቻሮ ሱቆች እምብዛምም ላያስፈልጉ ይችላሉ የሚሉ ትንበያዎች እንዲነሱ እያደረገ ነው፡፡
news-45255562
https://www.bbc.com/amharic/news-45255562
የዙማ የሙስና ክስ፡ በደቡብ አፍሪካ የሙስና መረብ የሚያጋልጥ ምርመራ ተጀመረ
የደቡብ አፍሪካ የቀድሞ ፕሬዚደንትን የሙስና ቅሌት የሚያጋልጥ ምርመራ ተጀመረ።
የቀድሞው ፕሬዚደንት ጃኮብ ዙማ ቱጃር ቤተሰቦች በፖለቲካ ላይ ጫና እንዲያሳርፉ በመፍቀዳቸው ተከሰሱ ምርመራው 'ስቴት ካፕቸር' የተሰኘውንና በጉብታ ቤተሰብ ህንዳውያን ቱጃሮችና ከፍተኛ የአገሪቱ ሚንስትሮች በአገሪቱ የፖለቲካ ውሳኔ ላይ ያሳደሩትን ጫና ይመለከታል። • ጃኮብ ዙማ ስልጣን ለቀቁ • መቋጫ ያልተገኘለት የኦሮሚያ ሶማሌ ጉዳይ • ራማፎሳ አዲሱን ካቢኔያቸውን ይፋ አደረጉ ይሄው ጉቦ የመቀበል ክሱ የጀመረው በየካቲት ወር ዙማ ከስልጣን እንዲወርዱ ከመደረጋቸው አስቀድሞ ቢሆንም ፕሬዚዳንቱም ሆኑ የጉብታ ቤተሰቦች አይኔን ግንባር ያድርገው ሲሉ ቆይተዋል። የምርመራው ስራ መጀመሩን ተከትሎ የፍትህ ቢሮ ምክትል ሃላፊ ሬይ ዞንዶ ደቡብ አፍሪካውያን የሚያውቁትን ሁሉ ማስረጃ እንዲሰጧቸው ጠይቀዋል። "ሁላችንም አገራችንን የምንወድ ደቡብ አፍሪካውያን ሁሉ፤ ይህን ችግር ለመፍታት ኮሚሽኑን በትጋት ማገዝ አለብን" በማለት ጥሪ አስተላልፈዋል። 'ስቴት ካፕቸር' ምንድን ነው 'ስቴት ካፕቸር' ማለት የሙስና መረብ ሲሆን ቱጃሮች በመንግሥት አስተዳደር ስር የሚገኙ ትላልቅ ኩባንያዎች ኮንትራት ለማሸነፍ ሲሉ ለባለስልጣናት የሚሰጡት ጉቦ ነው። ባለፈው ታህሳስ ወር በዚሁ የሙስና መረብ የተጠመዱ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት የሙስና ቅሌት ማስረጃ ተገኝቶባቸው ነበር። ማስረጃው በአገሪቱ የሚገኙ የጉብታ ቤተሰብ አባላት ዙማ የሚንስትር ሹመት ሲያካሄዱ ተፅዕኖ ማሳደሩን ተመልክቷል። አንደኛው ክስ ምክትል የገንዘብ ሚንስትር 1.2 ሚሊየን ብር ከጉብታ ቤተሰብ አባላት በአንዱ ተሰጥቷቸው እንደነበር የሚያሳይ ነው የጉብታ ቤተሰቦች በበኩላቸው በጉዳዩ ላይ ምንም ማለት እንደማይችሉና በሚዲያ እየጠፋ ያለ ስማቸውን ለማደስ በሂደት ላይ እንደሆኑ ባለፈው ዓመት አስታውቀዋል።
51513392
https://www.bbc.com/amharic/51513392
ኦነግና ኦፌኮ አባሎቻችን እየታሰሩብን ነው ሲሉ ተናገሩ
በኦሮሚያ ክልል ከሚንቀሳቀሱ ተጽእኖ ፈጣሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ እና ኦሮሞ ነጻነት ግንባር-ኦነግ አባላቶቻችን እና ደጋፊዎቻችን በጅምላ እየታሰሩ ነው ሲሉ አቤቱታቸውን አቀረቡ።
የኦነግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ቦረን ትናንት አርብ፣ ረፋድ ላይ ፓርቲያቸው በሰጠው መግለጫ ላይ "ከ350 በላይ የሚሆኑ አባላቶቻችን እና ደጋፊዎቻችን ለእስር ተዳርገውብናል" ብለዋል። "ከሰሞኑ ደግሞ በበርካታ የኦሮሚያ ዞኖች ውስጥ እኛ በማናውቅም ምክንያት አባላቶቻችን እና ደጋፊዎቻችን በጅምላ እየታሰሩ ይገኛሉ።" ይህ የጅምላ እስር እየተጠናከረ እየሄደ ያለው ደግሞ የአዲስ አበባ ዙሪያ ባሉ አከባቢዎች ነው ሲሉ ያክላሉ አቶ ሚካኤል። ባሳለፍነው አንድ ሳምንት ብቻ በ7 የኦሮሚያ ዞኖች የሚገኙ 350 አባሎቻችን እና ደጋፊዎቻችን በጅምላ የታሰሩ ሲሆን፤ ይህን የጅምላ እስር እያደረገ ያለው ደግሞ የኦሮሚያ ፖሊስ መሆኑን አውቀናል ሲሉ ይከስሳሉ። በተመሳሳይ መልኩ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ- ኦፌኮ ፓርቲም ደጋፊዎቼ እና አባላቶቼ ለእስር እየተዳረጉብን ነው ብሏል። የፖርቲው የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እና የጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ጥሩነህ ገምታ በቅርቡ 27 አባላት እና ደጋፊዎቻቸው ለእስር መዳረጋቸውን ተናግረዋል። "በጥቅሉ 27 ሰዎች ታስረዋል። 23 አባላት እና 4 ደጋፊዎች ናቸው። እነዚህ ሰዎች የት ናቸው ቢባል፤ ጉጂ፣ ምዕራብ ኦሮሚያ ጊምቢ ከተማ፣ የኦፌኮ ወጣት ሊግ ፊቼ ከተማ ላይ ዱጎምሳ የሚባል አባላችን ታስሯል። ሰበታ ላይ ብቻ 11 ሰዎች ታስረውብናል። ይህ እስር የፖለቲካ ምህዳሩ እየጠበበ መምጣቱን ያሳያል" ይላሉ። ኦሮሚያ ፖሊስ ለቀረበበት ወቀሳ ምላሽ እንዲሰጥ ሙከራ ብናደርግም ልናገኛቸው አልቻልንም። የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ባልቻ ግን በፖለቲካ ተሳትፏቸው ብቻ ለእስር የተዳረጉ ሰዎች ስለመኖራቸው የማውቀው ነገረ የለም ብለዋል። "በክልላችን የፖለቲካ ፓርቲ አባል ስለሆነ ብቻ ማንም ሰው አይታሰረም መታሰርም የለበትም። በሌላ የወንጀል ድርጊት ተጠርጥረው የታሰሩ ካሉ እሱን በቁጥጥር ሥር ካዋላቸው አካል ማጣራት ያስፈልጋል ሲሉ ለቢቢሲ ምላሻቸውን ሰጥተዋል። ለእስር የታደረጉት ሰዎች የፖለቲካ ፓርቲ አባል ሊሆኑ ይችላሉ የሚሉት አቶ ጌታቸው፤ የፖለቲካ ተሳትፎ ላይኖራቸውም ይችላል ሲሉ ሃሳባቸውን ያጠናክራሉ። "የታሰሩበት ምክንያት በፖለቲካ ተሳትፏቸው ይሁን በሌላ ማወቅ በማይቻልበት ላይ እኔም ይህ ነው ማለት አልችልም።" በማለት ለቢቢሲ ቃላቸውን ሰጥተዋል። ከሁለት ቀናት በፊት የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ፤ ለሀገሪቱ ደህንነት ሲባል ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት የሚሳተፉ አካላት አልታገስም ማለቱ ይታወሳል። ጠቅላይ አቃቢ ሕግ ወንጀል ተፈጽሞባቸው በነበሩ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ተጠርጣሪዎችን ቁጥጥር ሥር እያዋለ እና ክስ እየመሰረተ መሆኑንም አስታውቋል። በመግለጫው ላይ በግጭቶቹ ላይ ተሳትፈዋል በሚል ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር እየዋሉ ከሚገኙባቸው ስፍራዎች መካከልም ምዕራብ ጉጂ፣ አዳማ፣ ምሥራቅ ሸዋ፣ አርሲ፣ ምሥራቅ ሐረርጌ፣ ባሌ፣ ምዕራብ አርሲ፣ ምዕራብ ሸዋ እና አዲስ አበባ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን፣ የተጠቀሱ ሲሆን ከደቡብ ክልል ደግሞ ጌዲኦ ዞን፣ ሐዋሳ፣ የቴፒና ሸካ ዞን ተጠቅሰዋልወ። በመግለጫው ላይ ተጠርጣሪዎችን በሕግ ቁጥጥር ስር የማዋል ሥራ የተጀመረባቸው ሌሎች አካባቢዎችም የተጠቀሱ ሲሆን ከእነዚህም መካከልም በሶማሌ ብሔራዊ ክልል በጅግጅጋና ሌሎች ዞኖች፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ብሔራዊ ክልል ካማሽ ዞን፣ መተከል ዞን የተጠቅሰዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎቹ አባላት እና ደጋፊዎች እስር ግን ከዚህ ከጠቅላይ አቃቢ ሕግ እርምጃ ጋር የተገናኘ ስለመሆኑ ግልጽ አይደለም።
news-55255839
https://www.bbc.com/amharic/news-55255839
የጋና ፕሬዝደንት አኩፎ-አዶ ዳግም ተመረጡ
የጋናው ፕሬዝደንት ናና አኩፎ-አዶ ሰኞ ዕለት የተካሄደውን ምርጫ በጠባብ ውጤት በማሸነፍ በድጋሚ ፕሬዝደንት በመሆን ተመረጡ።
ናና አኩፎ-አዶ ጋናን ከእአአ 2017 ጀምሮ ሲያስተዳድሩ ቆይተዋል። አኩፎ-አዶ ከተሰጠው አጠቃላይ ድምጽ 51.6 በመቶ ድምጽ ሲያገኙ ተቀናቃኛቸው የቀድሞ ፕሬዝደንት ጆን ማሃማ 47.4% በመቶ ድምጽ ማግኘታቸውን ይፋዊ ውጤቶች አመልክተዋል። የፕሬዝደንቱ ተቀናቃኝ እስካሁን ሽንፈታቸውን አልተቀበሉም። በአፍሪካ የተረጋጋ የዲሞክራሲያዊ ስርዓት አላት ተብላ በምትወደሰው ጋና ሁለቱ ፖለቲከኞች በፕሬዝደንታዊ ምርጫ ሲፎካከሩ ይህ ለሦስተኛ ጊዜ ነው። የምርጫው የሕዝብ ተወካዮች ምርጫ ውጤት እስካሁን ይፋ ባይሆንም ተቀራራቢ ውጤት ሊመዘገብ እንደሚችል ተገምቷል። ፕሬዝደንት አኩፎ-አዶ ምርጫውን ለሁለተኛ ጊዜ ማሸነፋቸው ይፋ ሲደረግ በመላው ጋና የፕሬዝደንቱ ደጋፊዎች ደስታቸውን ሊገልጹ አደባባይ ወጥተው ነበር። በኮሮናቫይረስ የተጎዳውን የጋናን ምጣኔ ሃብት ማነቃቃት እና የስራ አጥ ሰዎችን ቁጥር መቀነስ የተመራጩ ፕሬዝደንት የቤት ሥራ ይሆናል። ቀደም ሲል ፖሊስ ከምርጫ ጋር የተያያዙ 21 ግጭቶች ተከስተው አምስት ሰዎች መገደላቸውን አስታውቆ ነበር። ተቀናቃኙ ጆን ማሃማ ከእአአ 2013 - 2017 ጋናን በፕሬዝደንትነት መርተዋል። ከዚያም መንበረ ስልጣኑን ለአኩፎ-አዶ አሳልፈው ሰጥተዋል። በዘንድሮ ምርጫ ሁለቱ ተቀናቃኞች በኮሮናቫይረስ ስርጭት ምክንያት የምርጫ ቅስቀሳቸውን በሬዲዮ፣ ቴሌቪዥን እና በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲያደርጉ ቆይተዋል።
news-54384871
https://www.bbc.com/amharic/news-54384871
ኮሮናቫይረስ፡ በቫይረሱ ምክንያት 2.5 ሚሊዮን ታዳጊዎች የመዳር አደጋ ተጋርጦባቸዋል
የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በመላው ዓለም ያለ እድሜያቸው የሚዳሩ ሴት ልጆች ቁጥርን ከፍ ያደርጋል ተባለ።
ባለፉት 25 ዓመታት ያለ እድሜ ጋብቻን ለማስቆም የተደረገውን ጥረት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ወደኋላ እንደመለሰው የህጻናት አድን ድርጅቱ ሴቭ ዘ ችልድረስን አስታውቋል። ድርጅቱ እስከ ጎሮጎሳውያኑ 2025 ድረስ ኮሮናቫይረስ 2.5 ሚሊዮን ህጻናት ገና በለጋ እድሜያቸው እንዲዳሩ ምክንያት ሊሆን ይችላል ብሏል። ወረርሽኙ ድህነት እየጨመረ፤ ህጻናትን ከትምህርት ውጪ እያደረገ ለጉልበት ብዝበዛ እና ለትዳር እያጋለጣቸው ነው ብሏል ሴቭ ዘ ችልድረን። በደቡብ እስያ፣ አፍሪካ እና ላቲን አሜሪካ የሚገኙ ሴት ህጻናት ደግሞ የበለጠ ተጋላጭ ናቸው ተብሏል። መቀመጫውን ዩናይትድ ኪንግደም ያደረገው ድርጅት መንግሥታት ሴት ህጻናት ያለ እድሜያቸው እንዳይዳሩ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቋል። "መሰል ጋብቻዎችን የሴቶችን መብት የሚጥሱ፣ ለድብርት እና ጥቃት የሚያጋልጡ ከፍ ሲልም ለሞት የሚዳርጉ ናቸው" ሲሉ የድርጅቱ የህጻናት ጥበቃ አማካሪ ካረን ፍላንጋን ተናግረዋል። በመላው ዓለም በየዓመቱ 12 ሚሊዮን ህጻናት ያለ እድሜያቸው እንደሚዳሩ የሴቭ ዘ ችልድረን አሃዝ ያመላክታል። የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ያስከተለውን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ቀውስን ተከትሎ ያለ እድሜያቸው የሚዳሩ ልጆች ቁጥር እንደሚጨምር ተገምቷል። በጎሮጎሳውያኑ 2020 ላይ ብቻ 500ሺህ ሴት ልጆች ተገደው የተዳሩ ሲሆን ወደ 1 ሚሊዮን የሚጠጉ ሴት ልጆች ደግሞ ያረግዛሉ ተብሎ ይጠበቃል። መንግሥታት እና ድርጅቶች አስፈላጊውን እርምጃ ካልወሰዱ በ2025 ላይ ያለ እድሜያቸው የሚዳሩ ልጆች ቁጥር ከ61 ሚሊዮን በላይ ይሆናል ሲል ድርጅቱ አስጠንቅቋል። ከዚህ ቀደም የተባበሩት መንግሥታት የኮሮና ወረርሽኝን ተከትሎ በቀጣዩ 10 ዓመታት ያለ እድሜ የሚዳሩ ልጆች ቁጥር ከ13 ሚሊዮን ይሻገራል ብሎ ነበር።
news-53634185
https://www.bbc.com/amharic/news-53634185
ቢሊየነሩ ፒራሚዶችን የገነቡት 'ኤሊየኖች ናቸው' ማለቱ ግብፅን አስቆጣ
ግብፅ፤ ቢሊየነሩ ኢላን ማስክ ታዋቂ ፒራሚዶቿ በግዑዛን [ኤሊየኖች] ሳይሆን በሰው መገንባታቸውን እንዲያረጋግጥ ጋብዛለች።
ስፔስኤክስ የተሰኘው ኩባንያ ባለቤት የሆነው ማስክ የሴራ ትንታኔ መሰረት ያለው አንድ መስመር በትዊተር ገፁ ላይ ማስፈሩን ተከትሎ ነው ግብፅ ይህን ያለችው። ሰውዬው የፃፈው ፅሑፍ 'ፒራሚዶችን የገነቡት ኤሊየኖች መሆናቸው የማይካድ ነው' ይላል። የግብፅ የዓለም አቀፍ ትብብሮች ሚኒስትር ግን ይህ በፍፁም ሃሰት ነው ብለው። ሚኒስትሯ፤ ፒራሚዶቹን የሰሩት ሰዎች ቅሪተ-አካልን መጎብኘት በቂ ማስረጃ ነው ብለዋል። ተመራማሪዎች፤ በ1990ዎቹ ፒራሚድ ውስጥ የተገኙት መካነ-መቃብራት ጥንታዊው ሕንፃ በግብፃውያን ለመገንባቱ ምስክር ነው ይላሉ። ጉምቱው የቴክኖሎጂ ሰው ኢላን ማስክ 'ፒራሚድን የገነቡት ግኡዛን ናቸው' ሲል የለጠፈው ሐሳብ ቢያንስ 84 ሺህ ሰዎች ተጋርተውታል። የዓለም አቀፍ ትብብሮች ሚኒስትሯ ራኒያ አል-ማሻት በትዊተር ገፃቸው የማስክ ተከታይና አድናቂ መሆናቸውን ጠቅሰው ነገር ግን ሰውዬው ፒራሚዶች የተገነቡት በግብፃውያን ፈርዖኖች መሆኑን የሚያሳይ መረጃ መርምሮ እንዲያነብ አሳስበዋል። ግብፃዊው አርኪዮሎጂስት [የቅድመ-ታሪክ ተመራማሪ] ዛሂ ሃዋስ ለማስክ ምላሽ እንዲሆን አንድ ምስል በአረብኛ ቋንቋ ለጥፏል። ምስሉ፤ የማስክ ሐሳብ 'ፍፁም የማይታመን' ሲል ያጣጥላል። አርኪዮሎጂስቱ "እኔ የገንቢዎቹን ቅሪት አይቻለሁ። ሰዎቹ ግብፃውያን ናቸው፤ ደግሞም ባሪያዎች አይደሉም" ብሏል ሲል ኢጂፕትቱዴይ ዘግቧል። ማስክ ግብፃውያንን ካስቆጣው መልዕክቱ በኋላ የቢቢሲ ታሪክ ዘገባን ዋቢ አድርጎ 'ይህ የቢቢሲ ዘገባ እንዴት እንደተሰራ ስሜት የሚሰጥ ትንታኔ ይዟል' ሲል ፅፏል። ግብፅ ከመቶ በላይ ፒራሚዶች ይኑሯት እንጂ በጣም ታዋቂዎው ታላቁ የጊዛ ፒራሚድ ሲሆን ቁመቱም 137 ሜትር ነው። ፒራሚዶች ለያኔው የግብፅ ንጉሳውያን ቤተሰቦች መካነ-መቃብር እንዲሆኑ ተደርገው መገንባታቸውን ታሪክ ይዘክራል። ቢሊየነሩ ኢላን ማስክ ብዙ ጊዜ መሰል አወዛጋቢ አስተቶችን በመስጠት ይታወቃል።
news-57278892
https://www.bbc.com/amharic/news-57278892
በአስር ሺዎች የተሳተፉበት የአሜሪካንን እርምጃ የተቃወመ ሰልፍ ተካሄደ
የአሜሪካ መንግሥት በትግራይ ክልል ያለውን ግጭት በተመለከተ የሚከተለውን ፖሊሲ በመቃወም ከ10 ሺህ በላይ ሰዎች የተሳተፉበት ሰልፍ አዲስ አበባ ውስጥ ተካሄደ።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ባለፈው ሳምንት በሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ውስጥ የሚካሄደው ግጭት እንዲቆም የተኩስ አቁም እንዲደረግ ጥሪ አቅርበው ነበር። እሁድ እለት በተካሄደው ሰልፍ ላይ የተሳተፉ ሰዎች አሜሪካንን የሚተቹ መፈክሮችን ይዘው የነበረ ሲሆን፤ ሌሎች ደግሞ የሩሲያውን ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንንና የቻይናውን መሪ ዢ ጂንፒንግ ሲያደንቁ ነበር። በትግራይ ክልል ሰባት ወራትን ባስቆጠረው ጦርነት ሳቢያ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ጫናዎች ሲደረጉበት ቆይቷል። በግጭቱ በሺህዎች የሚቆጠሩ አብዛኞቹ ሰላማዊ የሆኑ ሰዎች እንደተገደሉ ሲነገር ቢያንስ ሁለት ሚሊዮን የሚሆኑት ደግሞ ተፈናቅለዋል። ባለፈው ጥቅምት ወር ማብቂያ ላይ የክልሉ ገዢ ፓርቲ የነበረው የህወሓት ኃይሎች በፌደራሉ ሠራዊት ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ወታደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ ካዘዙ በኋላ ነበር ግጭቱ የተቀሰቀሰው። ከሦስት ሳምንታት በኋላ የክልሉ ዋና ከተማ መቀለ በፌደራሉ ሠራዊት ቁጥጥር ስር ስትገባ ጦርነቱ ማብቃቱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ማወጃቸው ይታወሳል። ነገር ግን ከስድስት ወራት በኋላ አሁንም የኢትዮጵያ ሠራዊትና የጎረቤት አገር ኤርትራ ወታደሮች አሁንም የህወሓት ኃይሎችን ትግራይ ውስጥ እየተዋጉ ነው። በግጭቱ ውስጥ ተሳታፊ የሆኑት ኃይሎች በሙሉ የጅምላ ግድያንና አስገድዶ መድፈርን ጨምሮ በሰላማዊ ሰዎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች በመፈጸም በሰብአዊ መብት ቡድኖች ይከሰሳሉ። በሰልፈኞቹ የተያዘው የሩሲያውን ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንንና የቻይናውን መሪ ዢ ጂንፒንግ ምስል ባለፈው ሳምንት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት በግጭቱ ውስጥ እየተፈጸመ ነው ያሉት "ጾታዊ ጥቃትን" ጨምሮ "ሠፊ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች" እንዲቆሙ ጠይቀው፤ ረሃብ ሊከሰት እንደሚችል አስጠንቅቀዋል። ፕሬዝደንቱ ጨምረውም "በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች እየከፋ የመጣው ክልላዊና ብሔርን መሰረት ያደረገ ከፍፍል" በእጅጉ እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል። በሌላ በኩል ደግሞ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ላይ የቪዛ እገዳ ከመጣሉ በተጨማሪ ለአገሪቱ በሚሰጠው የደኅንነትና የምጣኔ ሀብት ድጋፍ ላይ እቀባዎችን መጣሉ ይታወሳል። በዚህ እርምጃም የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተቃወሞውን የገለጸ ሲሆን፤ ውሳኔውን "አሳዛኝ" በማለት ይህም የሁለቱን አገራት ግንኙነት "በከፍተኛ ሁኔታ ሊጎዳው ይችላል" ብሏል። የጆ ባይደን አስተዳደር በተጨማሪ በግጭቱ ውስጥ ተሳታፊ የሆነውና ከኢትዮጵያ ግዛት እንደሚወጣ የተነገረለት የኤርትራ ሠራዊት በአስቸኳይ ከትግራይ ክልል እንዲወጣ ግፊት ሲያደርግ ቆይቷል። በሰልፉ ላይ ምን ተባለ? በአዲስ አበባ ስታዲየም ውስጥ የተካሄደውን ይህንን የተቃውሞ ሰልፍ በወጣቶች ሚኒስቴር የተዘጋጀ ሲሆን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ደጋፊዎች ተሳትፈውበታል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ የሆኑት ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ንግግር ካደረጉ ታዳሚዎች መካከል አንዷ ነበሩ ። ወ/ሮ አዳነች አቤቤ "ፈጽሞ አንንበረከክም። በአሜሪካና በአጋሮቿ የቀረቡት ቅድመ ሁኔታዎችና የጉዞ እቀባዎች ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት የላቸውም። ሊስተካከሉ ይገባል" ማለታቸውን ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል። የሰልፉ ተሳታፊዎች በአማርኛ፣ በእንሊዝኛ እና በአረብኛ የተጻፉ መፈክሮችን ይዘው ነበር። ከእነዚህም መካከል "ኢትዮጵያ ሞግዚት አያስፈልጋትም"፣ "አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የያዘችውን አቋም እንድታጤነው እንጠይቃለን" እና "ለውጭ ጫና ፈጽሞ አንንበረከክም" የሚሉ ይገኙባቸዋል። አገሪቱ ከጥቂት ሳምንታት በኋላ የምታካሂደውን ምርጫ በመደገፍም "መሪዎቻችን የምንመርጠው እኛ ነን" የሚል መፈክርም የያዙ ነበሩ። አዲስ አበባ የሚገኘው የቢቢሲ ዘጋቢ እንዳለው የሩሲያው ፕሬዝዳንት ፑቲንናና የቻይናው መሪ ዢ በሰልፉ ላይ የተሞገሱት ኢትዮጵያ ሌሎች ኃያላን ወዳጆች እንዳሏት ለአሜሪካ መልዕክት ለማስተላለፍ ነው። የአሜሪካንን እርምጃ በመቃወም ከአዲስ አበባው በተጨማሪ ድሬዳዋን፣ ሐረርንና ጋምቤላን ጨምሮ በሌሎች ከተሞች መካሄዳቸው ተዘግቧል።
43031271
https://www.bbc.com/amharic/43031271
አሸባሪ ተብሎ የተፈረጀው ኦብነግ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር እየተደራደረ ነው
የኢትዮጵያ መንግሥት ከኦጋዴን ብሔራዊ ነጻ ኣውጪ ግንባር (ኦብነግ) አንጃ ጋር እየተደራደረ መሆኑን አንድ የመንግስት የውስጥ አዋቂ ለቢቢሲ አረጋግጧል።
የኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ከአምስት ዓመት በፊት በሽብርተኝነት ከፈረጃቸው አምስት ድርጅቶች መካከል የሆነው ኦብነግ የኦጋዴን ግዛትን ነፃ ለማውጣት በነፍጥ የሚታገል ድርጅት ነው። በአመራሩ ውስጡ የተፈጠረው መከፋፈል ተከትሎ አንዱ አንጃ በናይሮቢ ከመንግስት ጋር ለመደራረደር የሚያስችለውን ቅድመ ሁኔታ ላይ መስማማቱን ለማወቅ ተችሏል። ድርድሩ በይፋ እንዳልተጀመረ የሚናገሩት እኚሁ የውስጥ አዋቂ በናይሮቢ ውስጥ ትናንት እሑድ የተጀመረው ንግግር የድርጅቱ አንጃ አመራር ወታደሮቹን ይዞ ለመግባትና በመንግስት ምህረት ተደርጎላቸው መልሰው የሚቋቋሙበት ሁኔታ ላይ ይደራደራሉ። በድርድሩ የኢትዮጵያን መንግስት ወክሎ ከሚነጋገረው ቡድን ውስጥ የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አብዲ ኢሌ እና ኮሎኔል ገብረእግዚአብሄር አለምሰገድ እንደሚገኙበት ምንጫችን ገልፀውልናል። ከዚህ ቀደም ከድርጅቱ ተነጥሎ የወጣው አመራር ጋር ድረድር ተካሂዶ የተወሰነ አመራር ከእነ ወታደራዊ ኃይሉ ትጥቅ ፈትቶ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋርም እርቅ አውርዷል። ከጥቂት ወራት በፊት የሶማልያ መንግስት አንድ ከፍተኛ የኦብነግ መሪ ለኢትዯጵያ መንግስት ተላልፎ እንዲሰጥ ማድረጉ ይታወሳል።
45108842
https://www.bbc.com/amharic/45108842
አዲሱ የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አህመድ አብዲ ማን ናቸው?
የቀድሞውን የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አብዲ ሞሐመድ ኦማርን የተኩት አህመድ አብዲ ሼክ ሞሃመድ (ኤልካስ) በፊቅ ዞን ገርቦ በተባለ ስፍራ ተወለዱ ።
የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በአዲስ አበባ ከተማ በጊዜው በልማት ወደኋላ ለቀሩ ታዳጊ ክልሎች አገልጋሎት እንዲሰጥ በተቋቋመው ዕድገት አዳሪ ትምህርት ቤት ተምረዋል። በ2001 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ከጨረሱ በኋላ፤ ወደ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በመግባት በ2004 ዓ.ም በቢዝነስ እና ኢኮኖሚክስ ትምህርት በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቀዋል። ከምረቃ በኋላ በሶማሌ ክልል ጎዴ እና ጂግጂጋ ከተሞች የገቢዎች መስሪያ ቤት ባልደረባ ሆነው በመስራት የሥራ ዓለምን ተቀላቅለዋል ። •"አብዲ ሞሃመድ ኡመር ስልጣን ለመልቀቅ በተደጋጋሚ ጠይቀው ነበር" አዲሱ የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት •አብዲ ሞሃመድ ኡመር በቁጥጥር ስር ዋሉ •በጅግጅጋ ግጭት ሸሽተው የተሸሸጉ ሰዎች በከፋ ችግር ላይ ናቸው ተባለ በ2006 ዓ.ም የቀብሪ ደሃር ከተማ ከንቲባ ሆነው የተሾሙ ሲሆን በቀጣይ ዓመት ደግሞ የክልሉ ምክትል የፋይናንስ ሃላፊ ሆነው ለመስራት ችለዋል። ከ2008 ዓም ጀምሮ የክልሉ የፋይናንስ ቢሮ ዋና ሃላፊነትን ተረክበው የሰሩ ሲሆን ከሦስት ወራት ወዲህ የክልሉ የውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት ሃላፊ ሆነው እየሰሩ ነበር። በ2009 ዓ.ም ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ በ'ዲዛስተር ማኔጂመንት' ተመርቀዋል። በ30ዎቹ ዕድሜ መጀመሪያ የሚገኙት አቶ አህመድ ሼክ ሞሐመድ ባለትዳር እና የሰባት ልጆች አባት ናቸው።
news-56071857
https://www.bbc.com/amharic/news-56071857
ግብፅ ውስጥ ጥንታዊ የቢራ ፋብሪካ ተገኘ
የሥነ-ቅርስ ምርምር ተመራማሪዎች [አርኪዮሎጂስትስ] በዓለም ጥንታዊ ነው ያሉትን የቢራ ፋብሪካ ቆፍረው አግኝተዋል።
5 ሺህ ዓመት ዕድሜ ያስቆጠረ የቢራ ፋብሪካ የቢራ ፋብሪካው 5 ሺህ ዓመት ዕድሜ ያስቆጠረ ነው ተብሏል። አሜሪካዊያንና ግብፃዊያን ተመራማሪዎች በትብብር ያገኙት ይህ ፋብሪካ አቢዶስ በተሰኘችው የግብፅ በራሃማ ሥፍራ የተተከለ ነው። የሥነ-ቅርስ ሙያተኞቹ ያገኙት ጥንታዊ ፋብሪካ 40 ጉድጓዶች ያሉት ሲሆን ብቅል እና ውሃ ተደባልቆ ቢራ የሚጠመቅበት ነው። የቢራ መጥመቂያ ፋብሪካው በንጉሥ ናርመር ዘመን የተተከለ እንደሆነ ከጠቅላይ ጥንታዊ ዕቃዎች ካውንስል የተገኘው መረጃ ያሳያል። መረጃው ይህ ፋብሪካ በዓለማችን ጥንታዊና ግዙፍ የቢራ ፋብሪካ ነው ይላል። ንጉሥ ናርመር ከ5 ሺህ ዓመታት በፊት የነበረ ንጉሥ ነው። ንጉሡ የመጀመሪያውን አገዛዝ የመሠረተና ግብፅን አንድ ያደረገ እንደሆነ የታሪክ መዛግብት ይናገራሉ። የቢራ መጥመቂያው እያንዳንዳቸው 20 ሜትር ርዝመት ያላቸውና 40 ጉድጓዶች ያዘሉ ስምንት ግዙፍ ክፍሎች አሉት ይላሉ የካውንስሉ መሪ ሙስጠፋ ዋዚሪ። ፋብሪካው በሥራ እያለ በርካታ ሺህ ጋሎን ቢራ እንደተጠመቀበት ይታመናል። ለቢራ የሚሆን ብቅል እና ውሃ ተደባልቆ በተዘጋጀለት ጋን ውስጥ ይቀመጥና እንዲግል ይደረጋል ሲሉ መሪው አጠማመቁን ያስረዳሉ። ከፋብሪካው ተጠምቀው የሚወጡ መጠጦች በጊዜው ለነበሩ ንጉሣዊ አከባበሮች ጥቅም ላይ ይውሉ እንደነበር ይታመናሉ ሲል የግብፅ ቱሪዝም ሚኒስትር ያወጣው መግለጫ ይናገራል። መግለጫው፤ እኒህ አከባበሮች በግብፅ ነገሥታት የቀብር ሥፍራ ውስጥ ይከናወኑ እንደነበር የቆፋሪዎቹ ቡድን አጋር መሪ የሆኑትና በኒው ዮርክ ዩኒቨርሲቲ የሚያስተምሩት ማቲው አዳምስን ዋቢ አድርጎ ያትታል። በወቅቱ ፋብሪካው ቢራ በገፍ ያመርት እንደነበርና እስከ 5 ሺህ ጋሎን ቢራ ሳይጠመቅ እንዳልቀረ ተመራማሪዎቹ ይናገራሉ። በወቅቱ የነበሩ ግብፃዊያን በተለያዩ ዝግጅቶች ወቅት ቢራ ይጠቀሙ እንደነበር በቁፋሮው ሊታወቅ እንደቻለም ነው የቱሪዝም ሚኒስቴሩ የሚያስረዳው። አቢዶስ ግብፅ ውስጥ ያለች እጅግ ጥንታዊ ከተማ ስትሆን ሺህ ዓመታት ያስቆጠሩ ቤቶችና ቤተ-መንግሥቶች መገኛ ናት። አቢዶስ በላይኛው ግብፅ በሶሃግ ግዛት ስትሆን የምትገኘው ሥፍራው ሉክዞር የተሰኘውና በቱሪስቶች ዘንድ ታዋቂ የሆነው ቦታ መገኛም ነው። በያዝነው ወር መጀመሪያ አካባቢ አሌክዛንድሪያ ውስጥ 2 ሺህ ዓመት ዕድሜ ያላቸውና ምላሳቸው ወርቅ የሆነ የደረቁ ሬሳዎች [ማሚ] መገኘታቸው ይታወሳል።
news-53775702
https://www.bbc.com/amharic/news-53775702
ካናዳ ፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ቱሩዶ በተደጋጋሚ የግድያ ዛቻ የሚደርሳቸው ለምንድነው?
የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ቱሩዶ በየቀኑ የሚደርሳቸው የሞት ዛቻ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ሲነጻጸር በእጥፍ መጨመሩ ተነገረ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ቱሩዶ እንደ ካናዳ ፖሊስ መረጃ ከሆነ ከጥር እስከ ሐምሌ ድረስ ብቻ 130 የግድያ ዛቻዎች ደርሷቸዋል። ባለፈው ዓመት በእነዚሁ የወራት ልዩነት ጊዜ ይህ የዛቻ ቁጥር ከመቶ አላለፈም ነበር። ባሳለፍነው ሐምሌ ወር አንድ መሣሪያ የታጠቀ ጎልማሳ ጠቅላይ ሚኒስትር ቱሩዶ የሚኖሩበትን ቤት ዋና መግቢያ ጥሶ መኪናውን አቁሞ ሲንጎማለል በቁጥጥር ሥር ውሏል። ጠቅላይ ሚኒስሩ ቱሩዶና ባለቤታቸው ይፋዊ መኖርያ ቤታቸው እየታደሰ ስለሆነ አሁንም እየኖሩ ያሉት በጊዜያዊነት በዝነኛው ሪዶ ሆል (Rideau Hall) ሪልስቴት ቅጥር ግቢ ውስጥ ነው። ይህ ሥፍራ የካናዳ ጠቅላይ ገዥ የጁሊ ፓየት ይፋዊ መኖርያ ነው። ጁሊ የእንግሊዟ ንግሥት ዳግማዊት ኤልሳቤት የካናዳ ወኪል ሆና ታገለግላለች። ኢንስቲትዩት ፎር ስትራቴጂክ ዳያሎግ የተሰኘ ተቋም ባወጣው ሌላ መረጃ ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትር ቱሩዶ ላይ ቀኝ አክራሪዎች በማኅበራዊ ሚዲያ ውይይቶቻቸው መካከል ከሙስሊም ጠልነትና ከአይሁድ ጠልነት አጀንዳዎች ቀጥሎ የሚወያዩት ጀስቲን ቱሩዶን ነፍስ ማጥፋት ላይ ነው። ጀስቲን ትሩዱ በቀኝ አክራሪዎች የማኅበራዊ ድር አምባ ላይ 11.4 ከመቶ ርዕሰ ጉዳይ ሆነው የሚነሱ ሰው ሲሆኑ በየትዩብ ላይ ደግሞ ይህ አሐዝ 28 በመቶ ከፍ ይላል። ይህም አሐዝ የሚያሳየው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀኝ አክራሪዎች ጥቃት ኢላማ መሆናቸውን ነው። ለምን ባልተለመደ ሁኔታ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቀኝ አክራሪዎች ዒላማ ተደረጉ፣ ለምንስ ተደጋግሞ የግድያ ዛቻ ይደርሳቸዋል ለሚለው የጥናት ቡደኑ የሚከተለውን ብሏል። የቀኝ አክራሪዎች የሚያስተሳስሯቸው ሁለቱ ትልልቅ አጀንዳዎች ፀረ እስልምናና ፀረ መጤነት በተለይም ጸረጥቁር መሆናቸው ነው። ሙስሊሞችና ጥቁሮች በካናዳ በሰላም መኖራቸው ቀኝ አክራሪዎችን የሚያንገበግቧቸው ጉዳዮች ናቸው። እነዚህ እንዲሆኑ ያስቻሉት ደግሞ ቱሩዶ ናቸው ብለው ያምናሉ። ግራ ዘመም ፖለቲከኞች በተለይ የቱሩዶ ሊበራል ፓርቲ ለኢስላምና ለጥቁር መጤዎች የሚያሳየው ቀናኢ ስሜት ቀኝ አክራሪዎችን እንቅልፍ ነስቷቸዋል ይላል ሪፖርቱ። ከዚህ በተጨማሪ ቀይ አክራሪዎች ከሙስሊምና አይሁድ ጠልነትም ባሻገር "ቢሊየነሩ ጆርጅ ሶሮስ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በመተባበር በድብቅ ብዙ ጥቁሮችን ወደ ካናዳ በስደተኛ መልክ አስርጎ በማስገባት ካናዳን የጥቁሮች አገር ለማድረግና ነጩን ከምድረ ገጽ ለማጥፋት እየሰሩ ነው" ብለው ጭብጥ የሌለው የሴራ አዳብረዋል።
news-53675030
https://www.bbc.com/amharic/news-53675030
የቤይሩት ነዋሪዎች ለደረሰው ፍንዳታ መንግሥት ተጠያቂ ነው እያሉ ነው
የቤይሩት ነዋሪዎች ማክሰኞ እለት የደረሰው ከባድ ፍንዳታ በቸልተኝነት ምከንያት የተፈጠረ ነው በማለት ቁጣቸውን መንግሥት ላይ እየገለፁ ነው።
ፍንዳታው በዙሪያው የነበሩትን ነገሮች በሙሉ አውድሟል ፕሬዝደንት ማይክል አውን ፍንዳታው ባገጠመበት ቦታ ላይ 2750 ቶን የሚመዝን አልሙኒየም ናይትሬት ደኅንነቱ ባልተጠበቀ ሁኔታ ለስድስት ዓመታት ተከማችቶ ነበር ማለታቸው ይታወሳል። በርካቶች ባለስልጣናትን በሙስና፣ በቸልተኛነትና ሃብት በማባከን ይከሷቸዋል። በሊባኖሷ መዲና ቤይሩት በተከሰተው ከባድ ፍንዳታ ቢያንስ 135 ሰዎች መሞታቸውን እና ከ4 ሺህ በላይ ሰዎች ደግሞ የተለያየ መጠን ያለው ጉዳት እንደደረሰባቸው ተነግሯል። ለሁለት ሳምንት ያህል የሚቆይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅም ተደንግጓል። የፀጥታ ኃይሎች ፍንዳታው የደረሰበትን ስፍራ አጥረው የነፍስ አድን ሰራተኞች በፍርስራሽ ውስጥ ተቀብረው ያሉ አስከሬኖችን እየፈለጉ ነው። አሁንም በርካቶች መጥፋታቸው እየተነገረ ነው። የህብረተሰብ ጤና ሚኒስትሩ ሃማድ ሃሰን በፍንዳታው የተጎዱ እና የህክምና ድጋፍ የሚፈልጉ ዜጎችን ለማከም የሊባኖስ ሆስፒታሎች የአልጋ እና ህክምና ቁሳቁስ እጥረት ገልፀዋል። "ቤይሩት እያለቀሰች፣ ቤይሩት እየጮኸች ነው፤ ሰዎች ተጨንቀዋል፤ ዝለዋል" በማለት ዜጎች ፍትህን በመጋፈጥ ኃላፊነት እንዲወስዱ ለቢቢሲ የተናገረው የፊልም ባለሙያው ጁድ ቼሃብ ነው። በሆስፒታል የሚገኘው የቤይሩት ነዋሪ የሆነው ቻዳይ ኤልሜኦውቺ ናውን ደግሞ "ብቃት በሌላቸው ሰዎች፣ ብቃት በሌለው መንግሥት እየተመራን እንደሆነ ሁሌም አውቅ ነበር።. . . ነገር ግን አንድ ነገር ልንገራችሁ - አሁን የሰሩት ነገር ሙሉ በሙሉ ወንጀል ነው" ብሏል። ረቡዕ ዕለት መንግሥት የቤይሩት ወደብ ባለስልጣናት ከፍንዳታው ጋር በተያያዘ ምርመራ በመጀመሩ በቁም እስር ውስጥ መሆናቸውን ተናግሯል። የሌባኖስ የጦር ኃላፊ ለፍንዳታው ተጠያቂ ሆነው የሚገኙት ላይ የሚቻለውን “ከፍተኛ ቅጣት ይተላለፍባቸዋል” ብለዋል። ፍንዳታው ያጋጠመው የከተማዋ ወደብ የሚገኝበት አቅራቢያ ሲሆን በስፍራው ተከማችቶ የነበረው አልሙኒያም ናይትሬት ከ6 ዓመታት በፊት ከአንድ መርከብ ላይ ወርዶ በስፍራው እንዲከማች ተደርጓል። ይህ ፍንዳታ የተከሰተው የሊባኖስ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ከፍተኛ ደረጃ ላይ በደረሰበት ወቅት ነው። የዓለም ምጣኔ ሃብት ፎረም በዓለማችን ላይ በከፍተኛ ውዝፍ እዳ ውስጥ ከሚገኙ አገራት መካከል ሊባኖስን በሦስተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል። ከሳምንታት በፊት ሥራ አጥ የሆኑ የሊባኖስ ወጣቶች አደባባይ ወጥተው ነበር። የቫይረሱን ስርጭትም የአገሪቱን ኢኮኖሚ 'ከድጥ ወደ ማጡ' እንዲገባ ሊያደርገው እንደሚችል ተገምቷል። ከዚህም በተጨማሪ በአውሮፓውያኑ 2005 ላይ የቀድሞ የሌባኖስ ጠቅላይ ሚንስትር ራፊክ ሃሪሪን ገድለዋል የተባሉ አራት ተጠርጣሪዎች ላይ የፊታችን ዓርብ በሌሉበት ብይን ይሰጣል ተብሎ በሚጠበቅበት ወቅት ነው ፍንዳታው ያጋጠመው። በጠቅላይ ሚንስትሩ ግድያ የፍርድ ውሳኔ የተላለፈባቸው አራቱም ግለሰቦች በኢራን መንግሥት የሚደገፈው የሔዝቦላህ ቡድን አባላት ናቸው። አልሙኒየም ናይትሬት ምንድነው? አልሙኒየም ናይትሬት በርካታ ጠቀሜታዎች ቢኖሩትም፤ አብዛኛውን ጊዜ ጥቅም ላይ የሚውለው ለእርሻ ሥራ ማዳበሪያነት እና ተቀጣጠይ ነገር ሆኖ ነው። አልሙኒየም ናይትሬት ከእሳት ጋር ከተገናኘ እጅግ ተቀጣጣይ ሲሆን እንደመጠኑ ፍንዳታ ያስከትላል። በእሳት ሲያያዝ ናይትሮጅን ኦክሳይድ እና አሞኒያ ጋዝ የሚባሉ ለጤና ጎጂ የሆኑ አደገኛ የጋዝ ልቀትን ያስከትላል። ይህ ኬሚካል አደገኛ ተቀጣጣይ እንደመሆኑ መጠን የሚጓጓዝበት እና የሚከማችበት ሁኔታን በተመለከት ጥብቅ መመሪያዎች ተፈጻሚ ይሆናሉ። አልሙኒየም ናይትሬቱ ለምን አስፈለገ? የሌባኖስ ዜጎች እንዴት ከ2700 ቶን በለይ የሚመዝን ተቀጣጣይ ነገር በመሃል ከተማ በመኖሪያ ስፍራ ላይ ይከማቻል ሲሉ እየጠየቁ ይገኛሉ። የአገሪቱ ፕረዝደንት አልሙኒየም ናይትሬቱ ለስድስት ዓመታት በስፍራው ተከማችቶ መቆየቱን ተናግረዋል። ዜጎች ይህ "የመንግሥት እንዝላልነትን የሚያሳይ ነው" እያሉ አጥብቅ የመንግሥትን ቸልተኝነት እየኮነኑ ይገኛሉ። የመከከለኛው ምሥራቅ እና ሰሜን አፍሪካ የቻተም ሃውስ ፕሮግራም መሪ የሆነችው ሊና ካሃቲብ፤ "2750 ቶን አልሙኒየም ናይትሬት ማን ምን ሊያደርግለት ይፈልጋል?" ስትል ጠይቃለች። ሊና ይህ ኬሚካል ተቀጣጣይ ነገሮችን ለመሠራት ጥቅም ላይ ሊውል እንደሚችል በማስታወስ፤ የሌባኖሱ ታጣቂ ኃይል ሔዝቦላህ የቤይሩት ወደብ በመጠቀም አልሙኒየም ናይትሬት በድብቅ ወደ አገር ውስጥ እንደሚያስገባ ተናግራለች። ይሁን እንጂ አልሙኒየም ናይትሬቱ ይህን አይነት ጉዳት እንዲያስከትል ያደረገው ምን እንደሆነ አልተረጋገጠም። Interactive See extent of damage at Beirut blast site 5 August 2020 25 January 2020 የቤይሩት አስተዳዳሪ የሆኑት ማርዋን አባውድ ለኤኤፍፒ የዜና ወኪል እንደተናገሩት ፍንዳታው ከ300 ሺህ በላይ ሰዎችን ቤት አልባ አድርጓል። አስተዳዳሪው ጨምረው እንደተናገሩት በፍንዳታው ምክንያት የደረሰው ጉዳት በገንዘብ ሲለካ ከ3-5 ቢሊዮን ዶላር እንደሚገመት ተናግረዋል። አስተዳዳሪው" ቤሩት የምግብ የአልባሳትና ቤቶችን መልሶ ለመገንባት የሚኣገለግሉ ቁሳቁሶች ድጋፍ ትፈልጋለች" ቤሩት ለስደተኞች መቆያ ትፈልጋለች" ብለዋል። በርካታ አገራት ሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገብተዋል። ሶስት የፈረንሳይ አውሮፕላኖች 55 የነፍስ አድን ሰራተኞችን፣ 500 ሰዎችን ማከም የሚያስችል የህክምና ቁሳቁሶችን፣ እና ተንቀሳቃሽ ክሊኒክ ጭነው እንደሚመጡ ፕሬዝዳንት ማክሮን ተናግረዋል። የአውሮፓ ህብረት፣ ሩሲያ፣ ቱንዚያ፣ቱርክ፣ኢራን እና ከወታር እርዳታ የላኩ ሲሆን ዩናእትድ ኪንግደምምም የሕክምና ባለሙያዎችን እና የሰብዓዊ ርዳታ ለመላክ ዝግጁ መሆኗን አስታውቃለች።
news-54039813
https://www.bbc.com/amharic/news-54039813
ኮሮናቫይረስ፡ የሩሲያ የኮቪድ-19 ክትባት በሽታ የመከላከል አቅምን ከፍ ያደርጋል ተባለ
የሩሲያ ሳይንቲስቶች ለኮሮረናቫይረስ በተሰራው ክትባት ዙሪያ የመጀመሪያ ሪፖርታቸውን አቅርበዋል።
በክትባቱ ላይ የተደረጉ ምርምሮችን መሠረት በማደረግ ክትባቱ የሰዎችን የበሽታ የመከላከል አቅምን ከፍ እንደሚያደርግ ደርሰንበታል ብለዋል ተመራማሪዎቹ። ሪፖርቱ ዘ ላንሴት በተሰኘው ሜዲካል ጆርናል ላይ ነው የወጣው። በሪፖርቱ ላይም ሁሉም የጥናቱ ተሳታፊዎች ክትባቱ ከተሰጣቸው በኋላ ቫይረሱን ለመዋጋት የሚያስችላቸው አንቲቦዲ ማዳበራቸውን እና የከፋ የጎንዮሽ ጉዳት እንዳልታየባቸው ተገልጿል። ሩሲያ በአገሯ ለተመረተው ክትባት ለሰዎች ጥቅም እንዲውል ባሳለፍነው ወር ፈቃድ የሰጠች ሲሆን እስካሁን ድረስ ከሩሲያ በስተቀር ለኮሮናቫይረስ የሚሆን ክትባት ጥቅም ላይ እንዲውል የፈቀደ ሌላ አገር የለም። አሁን የዓለም ሳይንቲስቶችን እያነጋገረ ያለው ነጥብ የትኛውም መድኃኒት ወይም ክትባት ሲፈጠር ሦስት ጥብቅ ምዕራፎችን ማለፍ እያለበት ፑቲን በሁለት ምዕራፍ ክትባቱ ጥቅም ላይ እንዲውል ማዘዛቸው ነው። ሪፖርቱ ምን ይላል? 'ስፑትኒክ ቪ' የሚል ስያሜ በተሰጠው ክትባት ላይ ባሳለፍነው ሰኔ እና ሃምሌ ወራት ላይ ሁለት ሙከራዎች ተከናውነውበታል። ዘ ላንሴት ላይ የወጣው ሪፖርት እንዳመላከተው በሁለቱም ሙከራዎች 38 ጤናማ በጎ ፈቃደኛ ተሳታፊዎች ክትባቱ ተሰጥቷቸዋል። እድሜያቸው ከ18 እስከ 60 የሆኑት ተሳታፊዎች ለ42 ተከታታይ ቀናት በተመራማሪዎች ጥብቅ ክትትል ሲደረግባቸው ነበር ተብሏል። በሶስተኛው ሳምንት ደግሞ ሁሉም የጥናቱ ተሳታፊዎች ቫይረሱን ለመዋጋት የሚያስችል አንቲቦድ ሰውነታቸው ማዳበሩ ተጠቅሷል። በተሳታፊዎቹ ላይ ምንም አይነት ከባድ የጎንዮሽ ህመም ያልተስተዋለ ሲሆን አብዛኛዎቹ ግን ራስ ምታት እና የመገጣጠሚያ ህመም እንደተሰማቸው ተመዝግቧል። በሚቀጥሉት ሳምንታት ደግሞ 40 ሺ ጤናማ በጎ ፈቃደኞችን የሚያካትት ሶስተኛ ዙር ሙከራ የሚደረግ ሲሆን ይበልጥ ተጋላጭ በሆኑ የእድሜ ክልሎች የሚገኙ ሰዎች በብዛት እንዲካተቱ ይደረጋልም ተብሏል። ክትባቱን በበላይነት የሚቆጣጠረው የሩሲያ ኢንቨስትመንት ፈንድ ዋና ኃላፊ የሆኑት ኪሪል ድሜትሪቭ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ሪፖርቱ ''የሩሲያን ክትባት በጥብቅ ሲተቹ ለነበሩ ሰዎች ምላሽ ይሆናል'' ብለዋል። አክለውም ለቀጣይ ዙር ሙከራ እስካሁን ድረስ 3 ሺ ሰዎች መመረጣቸውን ገልጸዋል። የአገሪቱ የጤና ሚኒስትር የሆኑት ሚካይል ሙራሽኮ በበኩላቸው ሩሲያ ከሕዳር እስከ ታህሳስ ባለው ጊዜ ውስጥ ለቫይረሱ ተጋላጭ ለሆኑ ሰዎች ክትባቱን መስጠት እንደምትጀምር አስታውቀዋል።
news-49889111
https://www.bbc.com/amharic/news-49889111
የሞ ፋራህ የቀድሞ አሠልጣኝ ለአራት ዓመት ከአትሌቲክስ ታገዱ
የሞ ፋራህ ቀድሞ አሠልጣኝ፣ አልቤርቶ ሳላዛር፣ ከአበረታች መድሀኒት ጋር በተያያዘ ከስፖርት ለአራት ዓመት ታገዱ።
በ2012 በተካሄደው የለንደን ኦሎምፒክ ላይ ሳላዛር (መካከል) ሞ ፋራህ (በስተቀኝ ) ጋሌን ሩፕ (በስተግራ) የ61 ዓመቱ ሳላዛር የአራት ጊዜ የኦሎምፒክ ሻምፒዮን የሆነው ፋራህን ማፍራት የቻለው የናይክ ኦሪጎን ፕሮጀክት ከ2011 እስከ 2017 ድረስ ሲመሩ ቆይተዋል። ውሳኔው የተላለፈው በአሜሪካው የፀረ አበረታች መድሃኒት ኤጀንሲ ለአራት ዓመት ያህል ምርመራ ሲደረግ ከቆየና ለሁለት ዓመት ያህል በፍርድ ቤት ክርክር ከተካሄደ በኋላ ነው። ምርመራው የተጀመረው ቢቢሲ በ2015 ፓናሮማ የተሰኘ ፕሮግራሙ ላይ ጉዳዩን ካቀረበ በኋላ ነው። • የዛሬዋን ኤርትራ የሚገልጹ አስደናቂ እውነታዎች • የጤፍ ቢራ አሜሪካ ውስጥ ገበያ ላይ ዋለ • ከአንደኛ ክፍል ዲግሪ እስኪጭኑ ከልጃቸው ጋር የተማሩት አባት ይህ የቢቢሲ ፕሮግራም ከአሜሪካው ፕሮፑብሊካ ድረገፅ ጋር በጋራ በመሆን በአሜሪካ ኦሪጎን ውስጥ በሚገኘው የአትሌቲክስ ማሰልጠኛ ስፍራ የሚሰጡ አበረታች መድሃኒቶችንና የሚካሄዱ ተገቢ ያልሆነ ተግባራትን አጋልጧል። የዩኬ ስፖርቶችን የሚቆጣጠረው ዩኬ አትሌቲክስ፣ የራሱን ምርመራ ያካሄደ ሲሆን ለስድስት ጊዜ የዓለም ሻምፒዮናው፣ እንግሊዛዊው ፋራህ፣ ከ አሜሪካዊው ሳላዛር ጋር እንዲሰራ ይሁንታውን ሰጥቶት ነበር። በናይክ እየተከፈላቸው በርካታ የሳላዛር አትሌቶችን የሚያክሙት ዶክተር ጄፍሪ ብራውን ደግሞ ለአራት ዓመት ታግደዋል። ፋራህ ከሳላዛር ጋር የተለያየው በ2017 መሆኑን ጠቅሶ ከአበረታች መድሃኒት ጋር በተያያዘ አለመሆኑን ግን ገልጿል።
news-56268973
https://www.bbc.com/amharic/news-56268973
በህዳሴ ግድብ ላይ ሌሎች አደራዳሪዎች ይግቡበት ማለት የአፍሪካ ህብረትን አስተዋፅኦ የሚያኮስስ ነው-ኢትዮጵያ
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር በአፍሪካ ህብረት አሸማጋይነት እየተከናወነ ባለበት ወቅት ሌሎች አደራዳሪዎች ይግቡ ማለት የድርጅቱን አስተዋፅኦ የሚያኮስስ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በዛሬው ዕለት የካቲት 24፣ 2013 ዓ. ም ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫም ነው ይህንን የተናገሩት። ከሰሞኑ ሱዳን ከአፍሪካ ህብረት በተጨማሪ የተባበሩት መንግሥታት፣ የአውሮፓ ህብረትና አሜሪካ በአሸማጋይነት እንዲገቡበትና ኢትዮጵያ በብቸኝነት የምታደርገው የውሃ ሙሌት ግድቡን ይጎዳል ማለቷ ተዘግቧል። ቃለ አቀባዩ በዛሬው መግለጫቸው በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር የሚደረገው የሶስትዮሽ ድርድር ለሁሉም አካላት እንደሚጠቅም አስታውሰው ድርድሩም አልተቋጨም ብለዋል። ድርድሩ ባልተቋጨበት ወቅት ሌሎች አደራዳሪዎችን መጋበዙ የድርጅቱን አስተዋፅኦ እንደሚያኮስሰውም ተናግረዋል። ከዚህም በተጨማሪ ኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለውን የሶስትዮሽ ድርድር አራዝማዋለች መባሉ ተጨባጭነት የሌለው ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ የሶስትዮሹን ድርድር የምታካሂደው ውሃዋን የመጠቀም መብቷን መሰረት ባደረገና ሁለቱን የታችኛው ተፋሰስ አገራትን በማይጎዳ መልኩ በመርሆች ስምምነት መመሪያዎችን በተከተለ መሆኑንን ዲና ሙፍቲ አስታውሰዋል። እስካሁንም ባለው የድርድር ሂደት የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበርነትን ቦታ በቅርቡ የተሰናበተችውን ደቡብ አፍሪካን አመስግነው ቦታውን ለተረከበችው ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ይኸው ሂደት እንዲቀጥል መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ለዓመታት ሲካሄድ የነበረው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድርድር ፍሬ ሳያፈራ ሶስቱንም አገራት አጣብቂኝ ውስጥ ከቷቸዋል። ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ ግብጽ የቅኝ ግዛት ውሎችን ሙጥኝ እንዳለችና ኢ-ፍትሃዊና አግላይ የሆነውን ስምምነት ተቀባይነት እንዲያገኝ ጫና እያደረገች ነው በማለትም ትወቀሳለች። ባልነበረችበት የተፈረመ ስምምነት ለናይል ወንዝ 77 ቢሊየን ሜትር ኪዩብ ውሃ ለምታመነጨው ኢትዮጵያ ምንም ድርሻ የማይሰጥና ተፈጥሯዊም ሆነ ሕጋዊ መብቴን የሚነጥቅ ነው በማለትም ኢትዮጵያ ትከራከራለች። ግብጽ ከምታነሳቸው ቅሬታዎች መካከል ኢትዮጵያ ግድቡን ሙሉ አቅም እየተጠቀመች ድርቅ ቢያጋጥም ችግሩ የሦስቱም አገራት ጉዳይ ነው የሚል አቋም ላይ መድረሷን ነው። ረዘም ላለ ጊዜ ድርቅ የሚከሰት ከሆነ ኢትዮጵያ የታችኛው ተፋሰስ አገራት ጥቅምን ለመጠበቅ ዋስትና ልትሰጠን ይገባል በማለትም ግብጽ ትከራከራለች። ኢትዮጵያ ያለ ታችኛው ተፋሰስ አገራት ስምምነትም ግድቡን ለመሙላት መወሰኗም ሁለቱን አገራት የማስገደድ ውሳኔ ነው ይላሉ ግብፅና ሱዳን። "በትግራይ እየተደረገ ስላለው እርዳታ" አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በዛሬው ዕለትም በግጭት በተጎዳችው የትግራይ ክልል መንግሥታቸው እያደረገ ስላለው ሁኔታም አብራርተዋል። ኢትዮጵያ በትግራይ ክልል ሰብዓዊ እርዳታ ማድረስ ለሚፈልጉ ከመቶ በላይ አለም አቀፍ ድርጅቶች ፍቃድ መስጠቷን አስታውቀዋል። በአጠቃላይ በክልሉ እንዲንቀሳቀሱ ፍቃድ የተሰጣቸው አለም አቀፍ ድርጅቶች ቁጥር 135 መሆኑን ገልፀው ከነዚህ ውስጥ ቢቢሲና አልጀዚራን ጨምሮ 11ዱ ሚዲያዎች ናቸው ብለዋል። በአለም አቀፍ ደረጃ መንግሥታቸው በክልሉ ባለው ሁኔታ የሚቀርብበት ትችት ትክክለኛ እንዳልሆነ ገልፀው "በትግራይ ክልል ያልተቋረጠ ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ ነው" እንዲሁም 70 በመቶ የሚሆነው እርዳታ እየተሸፈነ ያለውም በኢትዮጵያ መሆኑን አመላክተዋል። የተለያዩ አለም አቀፍ አካላት እርዳታ አናሳ ነው ያሉት ቃለ አቀባዩ "ትችት ያለ ድጋፍ የተጎዳውን ህዝብም ሆነ የኢትዮጵያ መንግሥትን አይጠቅምም" ብለዋል። የአለም አቀፉ የምግብ ድርጅት ኃላፊ ዴቪድ ቢስሊይን ዋቢ አድርገው በክልሉ ለሚደረገው ድጋፍ 107 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ እንደሚያስፈልግና መንግሥታቸውም አለም አቀፉን ድጋፍ እንደሚሻ ጠቁመዋል። በክልሉ እስካሁን ድረስ 3.5 ሚሊዮን ነዋሪዎችም እርዳታ ማድረስ ተችሏል ብለዋል። ከትግራይ ክልል ግጭት ጋር በተያየዘ የተነሱ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችንና ግድያዎችን በተመለከተም ቃለ አቀባዩ መንግሥት ከፌደራል ፖሊስ፣ ጠቅላይ አቃቤ ህግ፣ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳር ጋር በመጣመር ተፈፀሙ የሚባሉ ወንጀሎችን ይመረምራል ብለዋል። የነዚህን አካላት ምርመራ መሰረት በማድረግም መንግሥት ጥፋት ያጠፉትን አካላት ወደ ፍትህ እንደሚያቀርብ አፅንኦት ሰጥተዋል። በምርመራው ላይ ተጨማሪ እርዳታ ካስፈለገ መንግሥት የውጭ አካል ሊጋብዝ እንደሚችል ጠቆም አድርገዋል። በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በአክሱም ተገድለዋል የሚለውን የአምነስቲን ሪፖርት አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ባወጣው ሪፖርትም በአክሱም ዝርፊያዎች፣ መደፈሮች እንዲሁም የንፁኃን ዜጎች መሰረተ ልማት መውደሙን አረጋግጧል ብለዋል። የኢትዮጵያ ባለስልጣናትና የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የሚያደርጉት ምርመራ ሲጠናቀቅ ለኢትዮጵያም ሆነ ለአለም ህዝብ በወቅቱ እንደሚያሳውቁ ጨምረው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ የትግራይ ክልል የኤርትራ ወታደሮች በኅዳር ወር በሁለት ቀናት ውስጥ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን መግደላቸውን በተመለከተ በአምነስቲ ኢንተርናሽናል የወጣው ሪፖርት "ባልተሟላ መረጃና ውስን በሆነ የጥናት ዘዴ ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው" ሲል የኢትዮጵያ መንግሥት መተቸቱ ይታወሳል። አምነስቲ በበኩሉ በነዚህ ቀናት የተፈፀመው የቡድን ግድያ በሰብኣዊነት ላይ የተፈፀመ ወንጀል ሊሆን ይችላል በማለት በሪፖርቱ አስቀምጧል። ጥቅምት 4፣ 2013 ዓ.ም በትግራይ ክልል በሚገኘው የሰሜን ዕዝ ላይ በህወሓት ኃይሎች ጥቃት በመፈፀሙ መንግሥት "ህግ የማስከበር" ወታደራዊ ዘመቻን ማካሄዱን ገልጿል። የፌደራል መንግሥቱ ሠራዊት በኅዳር ወር አጋማሽ ላይ መቀለን ከተቆጣጠረ በኋላ በትግራይ ያካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ መጠናቀቁን ቢገልጽም በአንዳንድ የትግራይ ክልል አካባቢዎች ወታደራዊ ግጭቶች እንዳሉ በተለያዩ ጊዜያት የሚወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
news-55472414
https://www.bbc.com/amharic/news-55472414
ኮሮናቫይረስ፡ ስርጭቱ እንደ አዲስ ያገረሸባት ደቡብ አፍሪካ ገደቦችን አስቀመጠች
በደቡብ አፍሪካ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ከአንድ ሚሊየን መሻገራቸውን ተከትሎ የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ አዲስ ጠበቅ ያሉ ገደቦችን ማስተላለፋቸው ተሰምቷል።
ቤት ውስጥና ከቤት ውጪ ሰዎች ሰብሰብ ማለት አይችሉም ተብሏል፣ ከመሸ በኋላ እንቅቃሴ ማድረግም የተከለከለ ሲሆን ማንኛውም አይነት የአልኮል መጠጥም ቢሆን አይሸጥም። ፕሬዝዳንት ራማፎሳ በቴሌቪዥን መስኮት ባስተላለፉት መልዕክት ላይ ደቡብ አፍሪካ በወረርሽኙ ምክንያት አስፈሪና አሳሳቢ ሁኔታ ላይ መድረሷን ጠቅሰው አፋጣኝ እርምጃ መውሰድ ግድ አንዳለ አስረድተዋል። በቅርብ ቀናት የአገሪቱ ባለስልጣናት በፍጥነት እየተዛመተ የሚገኝ አዲስ አይነት ቫይረስ መኖሩን ማረጋገጣቸው ይታወሳል። አንዳንድ ሆስፒታሎችና የሕክምና ማዕከላት በርካታ ሰዎችን ተቀብለው እያስተናዱ እንደሆነና የግብአት እጥረት እያጋጠማቸው ስለመሆኑም እየገለጹ ነው። ይህንን ተከትሎ ፕሬዝዳንቱ ባስተላለፉት መልዕክት ''501.V2 የሚባል አዲስ የኮሮናቫይረስ ዝርያ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ተገኝቷል። በአሁኑ ሰአት ደግሞ በርካታ ሰዎች በቫይረሱ እየተያዙ መሆኑ በጣም አሳሳቢ ያደርገዋል። የጥንቃቄ እርምጃዎቻችንን ችላ ማለታችን ነው ለዚህ ያበቃን'' ብለዋል። ፕሬዝዳንቱ አክለውም አዲሶቹ ጥብቅ ገደቦች ከሰኞ ምሽት ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆንና ቢያንስ ለሚቀጥሉት ሶስት ሳምንታት ተግባራዊ ሊሆን እንደሚችል አስረድተዋል። ''ከቀብር ስነ ስርአት ውጪ ማንኛውም አይነት ሰዎችን የሚያሰባስብ ማህበራዊ ክንውን ተከልክለሏል፣ ሰዎች ከመሸ በኋላ መንቀሳቀስ አይችሉም፣ ሁሉም ሱቆች፣ መጠጥ ቤቶችና ምግብ ቤቶች ልክ ከምሽቱ ሁለት አሰት ላይ መዘጋት አለባቸው'' ብለዋል ፕሬዝዳንቱ። የአልኮል መጠጦችን መሸጥም ቢሆን የተከለከለ ሲሆን ህዝብ በሚበዛባቸው አካባቢዎች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማስክ ማድረግ ግዴታ ነው ተብሏል። አለበለዚያ ደግሞ እስር እንደሚጠብቃቸው ተገልጿል። ባሳለፍነው እሁድ ደቡብ አፍሪካ በቫይረሱ የተያዙ ከአንድ ሚሊየን ሰዎችን በማስመዝገብ ከአፍሪካ ቀዳሚ የሆነች ሲሆን እስካሁን ድረስ 26 ሺ 735 ሰዎች በዚሁ ቫይረስ ምክንያት ሞተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በአማካይ 11 ሺ 700 ሰዎች በየቀኑ በኮቪድ-19 እየተያዙ እንደነበር የተገለጸ ሲሆን ከባለፈው ሳምንት ጋር ሲነጻጸር ደግሞ የ39 በመቶ ጭማሪ አለው ተብሏል። ለዚህ ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር በዋነኛነት የተቀመጠው ምክንያት ደግሞ አዲሱ የኮሮረናቫይረስ አይነት እንደሆነ ተጠቁሟል። አዲሱ ቫይረስ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው በሰሜናዊ ኬፕ ሲሆን በአሁኑ ሰአት በፍጥነት እየተዛመተ ነው። ዩናይትድ ኪንግደም በዚህ አዲስ አይነት ቫይረስ ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ የሚመጡ ተጓዦችን ማገዷን አስታውቃ ነበር። ሌላ አይነት ቫይረስ ደግሞ በዩናይትድ ኪንግደም መገኘቱም የሚታወስ ነው።
news-54702171
https://www.bbc.com/amharic/news-54702171
ኮቪድ-19፡ በኮሮናቫይረስ መመሪያዎች ምክንያት በጣልያን ከፍተኛ ተቃውሞ ተነሳ
ጣልያን እንደ አዲስ ያገረሸውን ሁለተኛ ዙር የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን ለመግታት መመሪያዎችን ማሳለፏን ተከትሎ ከፍተኛ የሆነ ተቃውሞ ተነስቷል።
በበርካታ ከተሞቿም ግጭቶች ተቀስቅሰዋል ተብሏል። በቱሪን ከተማም በቤት የሚሰራ ተቀጣጣይ ጠርሙሶች በፖሊሶች ተወርውሮባቸዋል ተብሏል። በሚላን ተቃዋሚዎችን ለመበተን ፖሊስ አስለቃሽ ጋዝ የተጠቀመ ሲሆን በኔፕልስም እንዲሁ ግጭቶች መፈጠራቸው ሪፖርት ተደርጓል። ለነዚህ ተቃውሞዎች መነሻ የሆነውም ማዕከላዊው መንግሥት ሬስቶራንቶች፣ መጠጥ ቤቶችና የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎች (ጂሞች) ከምሽቱ አስራ ሁለት ሰዓት በኋላ እንዳይሰሩ እግድ በመተላለፉ ነው። ሌሎች ግዛቶችም እንዲሁ የምሽት ሰዓት እላፊ አዋጅ ማስተላለፋቸውም ተሰምቷል፤ ከነዚህም ውስጥ ሎምባርዲና ፔድሞንት ይገኙበታል። ከሰዓት እላፊ በተጨማሪ ትምህርት በበይነ መረብ ወይም በርቀት እንዲሆን እንዲሁም ከከተማ መውጣትም ተከልክሏል። ከነዚህም በተጨማሪ ሮምና ፓሌርሞም ከተሞችም ከፍተኛ የሆነ ተቃውሞ ተነስቷል። የመጀመሪያው የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በተነሳበት ወቅት አገሪቷ ወረርሽኙ ከመዛመት ለመቆጣጠር ያወጣቻቸው መመሪያዎችን በርካቶች ተቀብለውም ተግባራዊ አድርገውታል። ክፉኛ በወረርሽኙ የተጎዳችው ጣልያንም ሙሉ በሙሉ የእንቅስቃሴ እግድ ጥላ ነበር። በአሁኑ ወቅት የተላለፉት መመሪያዎችን ግን በርካቶች እየተቃወሙም ነው፤ በተለይም ትንንሽ የንግድ ቦታዎች ያሏቸው ጣልያናውን ከመጀመሪያው የእንቅስቃሴ እግድ ምክንያት ካጡት ገቢ በማገገም ላይ ነን ብለዋል። ሁለተኛ እግድ ከተደገመ ሙሉ በሙሉ እንከስራለንም እያሉ ነው። ተቃውሞ በሚላን ተቃውሞዎቹ በተወሰኑ ቦታዎችም ወደ ዝርፊያ መቀየራቸውም ተነግሯል። በማእከላዊ ቱሪን በሚገኝ የጉቺ የልብስ መደብር በተቃዋሚዎች ተዘርፏል ተብሏል። በርካታ ተቃዋሚዎች ርችት በማፈንዳትም ከተሞቹን እንደሸፈኗቸው የሮይተርስ የዜና ወኪል የዘገበ ሲሆን ፖሊስም በምላሹ አስለቃሽ ጋዝ ተጠቅሟል። በሚላን የወጡ ሰልፈኞች "ነፃነት፣ ነፃነት፣ ነፃነት" እያሉ በመጮህና በመዘመር ተቃውሟቸውን የገለፁ ሲሆን ከፖሊስም ጋር ተጋጭተዋል። ሚላን በኮሮና ቫይረስ ክፉኛ የተመታቸው የሎምባርዲ ግዛት መዲና ናት።
news-56514037
https://www.bbc.com/amharic/news-56514037
ቴክኖሎጂ፡ የዓለም ቋንቋዎችን በአጠቃላይ የሚተረጉም ቴክኖሎጂ እውን ይሆናል?
በዓለም ላይ ከ7 ሺህ በላይ ቋንቋዎች አሉ። 4 ሺህ ያህሉ የጽሑፍ ፊደላት አሏቸው። ከእነዚህ ቋንቋዎች መካከል ጉግል የሚተረጉማቸው ወደ 100 የሚጠጉትን ነው።
ውልፍ፣ ሉጋንዳ፣ ትዊ እና ሌሎችም በርካታ ቋንቋዎችን የሚተረጉም መተግበሪያ እስካሁን የለም። እነዚህ ቋንቋዎች በዋነኛነት ወደ ሌሎች ቋንቋዎች የሚተረጎሙት በቋንቋው ተናጋሪዎች አማካይነት ነው። ቴክኖሎጂን ያማከለ የትርጉም አገልግሎት ከሚሰጡ አንዱ ጉግል ነው። ጉግል 108 ቋንቋዎችን ይተረጉማል። ማይክሮሶፍት ደግሞ 70 ቋንቋዎችን። መረጃን በፍጥነት መለዋወጥ አስፈላጊ በሆነበት ዓለም ከ4,000 በላይ ቋንቋዎችን በመተግበሪያ መተርጎም አለመቻል የመረጃ ፍሰትን ማጓተቱ አይቀርም። በአሜሪካ የደህን ነት ምርምር ተቋም የሚሠራው ካርል ሩቢኖ እንደሚለው፤ በቋንቋ መግባባት አለመቻል በፓለቲካና በምጣኔ ሀብት ጉዳዮች ክፍተት ይፈጥራል። አንድን ሰው አዲስ ቋንቋ ማስተማር ጊዜ ይጠይቃል። ለምሳሌ በናይጄሪያ ከ500 በላይ ቋንቋ ይነገራል። ካርል የሚሠራበት ተቋም ይህንን ችግር ለመቅረፍ ጥናት ጀምሯል። ጥናቱ በተለያዩ ቋንቋዎች የሚደረግ ንግግርን ወይም ጽሑፍን መተርጎም የሚችል አሠራር መፍጠር ላይ ያተኩራል። በኮሎምቢያ ዩኒቨርስቲ የኮምፒውተር ሳይንስ ምሁሯ ካትሊን ማኮን፤ ይህንን ቴክኖሎጂ መተግበር ከተቻለ በርካቶች በቀላሉ ሊግባቡ የሚችሉበት ቀን ሩቅ አይሆንም ትላለች። አጥኚዎቹ ሰው ሠራሽ ክህሎት (አርቴፍሻል ኢንተለጀንስ) በመጠቀም ልክ እንደ ሰው የሚያስብ መሣሪያ ለመሥራት ነው ሐሳባቸው። መሣሪያው ቃላትን ከማወቅ ባሻገር ትርጉማቸውንም የሚገነዘብ ይሆናል። በእርግጥ አንዳንዴ ከአውድ ውጪ የሆነ ትርጉም ሊሰጥ ይችላል። ማሽን ቋንቋዎችን ተረድቶ እንዲተረጉም ለማስቻል በሚሊዮኖች በሚቆጠሩ ገጾች የተዘጋጀ ጽሑፍን ማስተማር የመጀመሪያው ደረጃ ነው። ሂደቱ ቀላል አይደለም። የኤምአይቲዋ ኮምፒውተር ሳይንቲስት ረጂና ባርዝሊ "ማሽን ቋንቋ ሲማር፤ ሰው ቋንቋ ሲማር ማወቅ ከሚጠበቅበት መረጃ በላይ ይሰጠዋል" ትላለች። ቴክኖሎጂው እውን ከሆነ ቀጣዩ ትውልድ ምናልባትም አስተርጓሚዎች ላያስፈልጉት ይችላሉ። ማሽኑ የቃላት ትርጉም መፈለጊያ ክፍል፣ ድምጽ ሰምቶ የሚተረጉም ክፍል እንዲሁም ሌሎችም ይዘቶች አሉት። አጥኚዎች ከጎርጎሮሳውያኑ 2017 ጀምሮ እያንዳንዱን ይዘት ተከፋፍለው ምርምር እያደረጉ ይገኛሉ። በጥናቱ ከተካተቱ ቋንቋዎች መካከል ስዋሂሊ፣ ታጋሎግ፣ ሶማሊ እና ካዛክ ይጠቀሳሉ። አንዱ የጥናቱ ትኩረት ዜና፣ ቪድዮ እና ሌሎችንም ማሽኑ እንዲተረጉም ማስቻል ነው። በሳውዘርን ካሊፎርንያ ዩኒቨርስቲ የኮምፒውተር ሳይንቲስቱ ስኮት ሚለር እንደሚለው፤ ብዙዎች በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ጽሑፎችና ቪድዮዎች ድረ ገጽ ላይ መለጠፋቸው ለምርምሩ ረድቷል። ማሽኑ አንድን ቋንቋ ወደሌላ ቋንቋ እንዲተረጉም ይደረጋል። ለምሳሌ ከስዋሂሊ ወደ እንግሊዘኛ መተርጎም። በቀጣይ ደግሞ የትኛውንም ቋንቋ ወደመተርጎም ይሸጋገራል። አንድ ሰው ትርጉም ሲፈልግ ማሽኑን በጽሑፍ ወይም በድምጽ መጠየቅ ይችላል። ተመራማሪዎቹ የአንድ ሰው ስም በአፍ መፍቻ ቋንቋው እንዴት እንደሚነበብ ወይም ሌላ ከቋንቋ ጋር የተያያዘ መረጃ ሲፈለግ በቀላሉ እንዲገኝ ማስቻል አስበዋል። የኢዲንበጓ ኮምፒውተር ሳይንቲስት ሚርላ ላፓታ አንድ ጽሑፍን ሙሉ በሙሉ ለመተርጎም ከመሞከር ይልቅ በቁልፍ ቃላት ከፍሎ መተርጎም ይቀላል ትላለች። ይህንን ለማሽኑ ለማስተማርም እየሞከች ነው። ማሽኑ እውን ከሆነ አሁን ላይ ሰዎች ከሚግባቡባቸው ቋንቋዎች ባሻገር ቀደምትና የጠፉ ቋንቋዎችን ለማጥናትም ታስቧል። ጥንታዊ ቋንቋዎች በግንባር ቀደምትነት የሚገኙት በጽሑፍ ስለሆነ ጥናቱ ቀደምት መዛግብት ላይ ያተኩራል። አሁን ላይ ማሽኑ የተለያዩ ቋንቋዎችን ትርጉም ለመፈለግ የሚውለው (ሰርች ኢንጅን) ተሠርቷል። የጥናቱ መሪ እንደሚለው፤ ከደህንነት ጥበቃ ጋር የተያያዙ እንደ ስለላ ያሉ ሥራዎችን ጨምሮ ማሽኑ በተለያዩ ዘርፎች አገልግሎት ላይ ይውላል። የሕክምና ተማሪው ዴቪድ ኢፍልዋ አድላኒ እንደሚለው፤ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ሲነሳ በተለያዩ ቋንቋዎች የተዘጋጁ መረጃዎችን መተርጎም አስፈላጊ ሆኗል። በተለይም በቀላሉ አስተርጓሚ ማግኘት ባልተቻለባቸው ሁኔታዎች ነገሮች ፈታኝ ነበሩ። "እንደ ወረርሽኙ ያሉ አስቸኳይና አንገብጋቢ ሁነቶች ሲፈጠሩ የትርጉም መተግበሪያ የግድ ያስፈልገናል" ይላል። ናይጄሪያዊው ዴቪድ የዩርባ ቋንቋ ተናጋሪ ነው። ዴቪድ ዮርባ ወደ እንግሊዘኛ የሚተረጉም መተግበሪያ የሚሠራ ቡድን አባል ነው። የፊልም ጽሑፍ፣ ዜና፣ ንግግር እና ሌሎችም ጽሑፎችን በመሰብሰብ ነው መተግበሪያውን ያበለጸጉት። ሃይማኖት የሚያስተምሩ ጽሑፎችንም የተጠቀሙ ሲሆን፤ ኢዊ፣ ፎንግቤ፣ ትዊ እና ሌሎችም የአፍሪካ ቋንቋዎችን የሚተረጉም ዳታቤዝ የመሥራትም እቅድ አላቸው። ማሽኑን እውን ለመሆን ያብቃው እንጂ፤ ማንኛውንም ቋንቋ በቀላሉ የምንተረጉምበት፣ በቀላሉ መረጃ የምንለዋወጥበት፣ የማናውቀውን ቋንቋ ከሚናገር ሰው ጋር የምንግባባት ቀን ሩቅ አይመስልም።
news-52217124
https://www.bbc.com/amharic/news-52217124
ኮሮናቫይረስ፡ እንዴት ቱርክሜንስታን እስካሁን ምንም በኮሮና የተያዘ ሰው ሪፖርት አላደረገችም?
የኮቪድ-19 ስርጭት በመላው ዓለም እያደገ ቢሄድም እስካሁን በርካታ አገራት በቫይረሱ የተያዘ ሰው አላስመዘገቡም። ከእነዚህ መካከል ጨቋኝ መንግሥት ያላት ቱርክሜንስታን አንዷ ናት።
የብስክሌት ውድድር ብዙ ባለሙያዎች ግን ወረርሽኙን ለማስቆም የሚደረገውን ሙከራ ሊያስተጓጉል በሚችል መልኩ መንግሥት እውነትን እየደበቀ ሊሆን ይችላል በሚል ስጋታቸውን ይገልጻሉ። ዓለም ከኮሮናቫይረስ ጋር እየታገለ አንዳንድ አገራትም ዜጎቻቸው ከቤት እንዳይወጡ በሚያደርጉበት በአሁኑ ወቅት ቱርክሜንስታን ግን የዓለም ጤና ቀንን ለማክበር የብስክሌት ውድድር ማክሰኞ ዕለት አካሂዳለች ። የመካከለኛው እስያዋ አገር በኮሮናቫይረስ የተያዘ ሰው እንደሌለባት አስታውቃለች። ሆኖም ሳንሱር በማድረግ ታዋቂ በሆነው መንግሥት የቀረበውን አሃዝ ማመን እንችላለን? "ከቱርክሜንስታን የተገኘው መረጃ በግልፅ የማይታመን ነው" ሲሉ የአገሪቱን የጤና አጠባበቅ ሥርዓትን ያጠኑት በለንደን የሃይጂንና ትሮፒካል ሜዲሲን ትምህርት ቤት ባልደረባ የሆኑት ፕሮፌሰር ማርቲን ማኪ ተናግረዋል። "በማይታመን መልኩ ላለፉት አስር ዓመታት ከኤችአይቪ /ኤድስ ጋር የሚኖሩ ሰዎች እንደሌሉ ገልጸዋል። በፈረንጆቹ በ 2000ዎቹ የተለያዩ ወረርሽኞችን መረጃ ሲደብቁ ኖረዋል" ይላሉ። ብዙዎች በቱርክሜንስታን የኮቪድ -19 ከወዲሁ ሊኖር ይችላል ብለው ይፈራሉ። "በመንግሥት ድርጅት ውስጥ የሚሠራው ባልደረባዬ ቫይረሱ እዚህ አለ ወይም ሰምቻለሁ አትበል። ካልሆነ ግን ችግር ውስጥ እገባለሁ ብሎኛል" ሲሉ ማንነታቸው እንዳይገለጽ የሚፈልጉ የዋና ከተማዋ አሽጋባት ነዋሪ አስታውቀዋል። ቱርክሜንስታን አብዛኛዎቹን የድንበር መግቢያዎቿን ከዘጋች ግን ከአንድ ወር በላይ ሆናት። ከየካቲት መጀመሪያ ጀምሮ ወደ ቻይናና ወደ ሌሎች አገሮች የሚደረጉ በረራዎችን የሰረዙ ሲሆን ሁሉንም ዓለም አቀፍ በረራዎች ከመዲናዋ ለይቶ ማቆያ ወደ ተቋቋመበት እና በሰሜን-ምሥራቅ ወደምትገኘው ቱርሜንባባት አዙራለች። ሆኖም እንደ ነዋሪዎች ገለፃ አንዳንዶች ከለይቶ ማቆያው እጅ መንሻ እሰጡ በመውጣት ለሁለት ሳምንት ያህል በድንኳን ውስጥ ላለመኖር ወስነዋል። ወደ አገሪቱ የሚገቡ እና ምልክቶችን የሚያሳዩ ሁሉ ምርመራ እየተደረገባቸው ነው። ሆኖም በቀን ምን ያህል ምርመራዎች እንደተካሄዱ እና አገሪቱ በአጠቃላይ ስንት መመርመሪያ መሳሪያዎች እንዳሏት ትክክለኛ ቁጥር ለመስጠት አልተቻለም። ይሁን እንጂ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በሽታን ለመቋቋም የጤና ሥርዓቱ ምን ያህል ዝግጁ ነው? "አናውቅም። እኛ የተወሰነ ዝግጁነት ደረጃ እንዳላቸው ተነግሮናል። እኛም አንጠራጠርም… ምክንያቱም ሆስፒታሎች የተሟሉ በመሆናቸው" ብለዋል ሲሉ በአገሪቱ ያሉ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተወካይ ተናግረዋል። ጨምረውም "ወረርሽኝ ከተከሰተ ግን እንደማንኛውም አገር በጤናው ሥርዓት ላይ ከፍተኛ ጫና ያሳድራል። ለዚህም ነው ምንም ያህል ቢዘጋጁ (አብዛኛውን ጊዜ በቂ አይደለም) ተጨማሪ መሣሪያዎችን እንዲገዙ እያግባባን ነው።" ሕዝቡ ስለተከሰተው ወረርሽኝ ግንዛቤ ግንዛቤ አለው። በከተሞች መካከል የሚደረግ እንቅስቃሴ የተከለከለ ሲሆን ወደ አሽጋባት የገቡ ሰዎች ለመንቀሳቀስ የሐኪም ፈቃድ ያስፈልጋቸዋል። ገበያዎች እና መስሪያ ቤቶች ዩዛርሊክ በተሰኘ የሳር ዓይነት እንዲታጠኑ እየተደረገ ነው። ምንም እንኳን ማስረጃ ባይኖርም የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ጉርባንጉሊ ቤርዲሙክሃሜዶቭ ዕጽዋቱን ማቃጠል ቫይረሱን እንደሚዋጋ አስታውቀዋል። ከአብዛኛው ዓለም በተቃራኒ ቱርክሜኒስታን ውስጥ የዕለት ተዕለት ኑሮ በመደበኛነት ቀጥሏል። ካፌዎች እና ምግብ ቤቶች ክፍት ናቸው። ብዙ ሰዎች ለሠርግ ይሰበሰባሉ። ጭምብል የሚያደርጉ ሰዎች ካለመኖራቸውም በላይ ሰዎች የሚሰበሰቡባቸው ዝግጅቶች ቀጥለዋል። ኮሮናቫይረስ ያመጣውን ስጋት ለመቀበል ሀገሪቱ እየተቸገረች እንደሆነ ያሳያል። ለምን ሊሆን ይችላል? የዓለም የጤና ቀንን ለማክበር የተደረገው የብስክሌት ውድድር ማብራሪያ ሊሰጥ ይችላል። ፕሬዝዳንት ጉርባንጉሊ ቤርዲሙክሃሜዶቭ ኮከብ እና የዓመታዊው ዝግጅት ዋናው ትኩረት ነበሩ። የጤናማ አኗኗር ምስል ተደርገውም ይወሰዳሉ። መንግሥት ቴሌቪዥን በመደበኛነት በጂም ውስጥ ክብደትን ሲያነሱ ወይም ብስክሌት ሲነዱ በተደጋጋሚ ያሳያል። መሳሳይ ዩኒፎርም የለበሱ የመንግሥት ሠራተኞች የጠዋት ስፖርታዊ ልምምዶቻቸውን የሚያካሂዱበት የ"ጤና እና ደስታ" ዘመቻ አንቀሳቃሽም ናቸው። የእነዚህ ሁሉ ዋና መልዕክት ምስጋና ለፕሬዚዳንቱ አገሪቱ ጤናማ እና ደስተኛ መሆኗን ለማሳየት ነው። ፕሬዝዳንት ጉርባንጉሊ ቤርዲሙክሃሜዶቭ የስልጣን ዘመናቸውን "የኃይል እና የደስታ ዘመን" ሲሉ አውጀዋል። የኮቪድ-19 ወረርሽኝ መልዕክቶቹ ምን ያህል እንዳልተሳኩ ሊያጋልጥ ይችላል። በዚህ ምክንያት ሊሆን ይችላል መንግሥት ምንም እንኳን ዜጎቹ በበሽታው ቢያዙም ወረርሽኙን ለመደበቅ የሚሞክረው። ይህ ነው ፕሮፌሰር ማኪን ያስጨነቀው "ኮቪድ-19 በፍጥነት ከቻይና ወደ ተቀረው ዓለም እንዴት እንደተዳረሰ አይተናል። አሁን በምንኖርበት ዓለም ሁሉም አገር እኩል በሚባል ደረጃ ተጋላጭ ነው" ብለዋል። "አንዳንድ ሃገራት ወረርሽኙን ለመቆጣጠር ቢችሉም፤ በሌሎች አገራት የመቀጠል አደጋ አለው። ቱርክሜኒስታንም ሌላ ምሳሌ ልትሆን ትችላለች።"
news-54412474
https://www.bbc.com/amharic/news-54412474
ጃዋር መሐመድ፡ የእነ አቶ ጃዋር ጠበቆች ማስፈራሪያና ጫና እየደረሰብን ነው አሉ
ከሦስት ወራት በፊት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ የሚገኘው የእነ አቶ ጃዋር መሐመድ ጠበቆች ጫናና ማስፈራሪያ ከተለያዩ አካላት እየደረሰብን ነው ሲሉ ለቢቢሲ ተናገሩ።
ይህንን የተናገሩት ከድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በኋላ ከተከሰተው ሁከት ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር የዋሉትን የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች፣ አባላት እንዲሁም ሌሎች ተጠርጣሪዎችን ጉዳይ በተለያዩ ፍርድ ቤቶች እየተከታተሉ የሚገኙት 13 አባላት ያሉት የሕግ ባለሙያዎች ቡድን ተወካይ የሆኑት አቶ ምስጋን ሙለታ ናቸው። እሳቸው እንደሚሉት ከጠበቆቹ መካከል በተወሰኑት ላይ በተለያዩ አጋጣሚዎች እየገጠማቸው ያለው ጫናና ማስፈራሪያና እየበረታ መምጣቱን ምሳሌዎች በመጥቀስ ለቢቢሲ ተናግረዋል። የጠበቆቹ ቡድን ተወካይ በእራሳቸውና በባልደረቦቻቸው ላይ እየደረሰ ነው ያሉትን ችግር በተመለከተ ምላሽ እንዲሰጡ ቢቢሲ ያነጋርናቸው የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ጽህፈት ቤት ምክትል ጠቃላይ ዐቃቤ ሕግ የሆኑት አቶ ፍቃዱ ፀጋ፤ ጠበቆቹ እየደረሰብን ነው ያሉትን ተጽዕኖ አስመልክቶ ጽህፈት ቤታቸው የደረሰው መረጃው እንደሌለ ገልፀዋል። "የተባለውን ነገር በተመለከተ መረጃ የለኝም። እነርሱ የሕግ ባለሙያዎች ናቸው፤ የሕግ ባለሙያ ስለሆኑ እንዲህ አይነት ችግር ሲገጥማቸው ለየትኛው አካላት ማሳወቅ እንዳለባቸው ያውቃሉ። እስከ አሁን በዚህ ረገድ አንድም የደረሰን ቅሬታ የለም" ብለዋል። አቶ ጃዋር መሐመድ እና በቀለ ገርባን ጨምሮ በሌሎቹ ተከሳሾች ጉዳይ ላይ በቡድን በመሆን ፍርድ ቤት በመቅረብ ጉዳያቸውን እየተከታተሉ የሚገኙት እነዚህ ጠበቆች፤ "በሙያችን ለደንበኞቻችን ቆመን በመከራከራችን ምክንያት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚደርስብን ማስፈራሪያ እና ችግር እየበረታ መጥቷል" ሲሉ ተወካያቸው አቶ ምስጋን ተናግረዋል። አቶ ምስጋን ሙለታ እንደአብነትም በእራሳቸው ላይ ደረሰ ያሉትን አጋጣሚ ሲያስረዱ "አንድ ቀን በቡራዩ ከተማ ፍርድ ቤት ለአንድ ተከሳሽ ተከራክሬ ስወጣ በፖሊስ ተጠራሁ። ከዚያም ወደ ቢሮ እንደገባሁ ያስጠራኝ ሰው ዘለፋና ተገቢ ያልሆኑ ቃላትን በመጠቀም ስልኬን ተቀብለው መፈተሽ ጀመሩ። ሸኔ ነህ ብለውም አስረው አጉላልተውኛል" ይላሉ። ከዚህ በተጨማሪም በአዲስ አበባ ከተማ የአራዳ ፖሊስ ጣቢያ የተገኙት ሌላ የጠበቆቹ ቡድን አባል የሆኑት አንድ የሕግ ባለሙያ ላይ በጦር መሳሪያ ማስፈራራት እንደተፈጸመባቸው ጠቅሰዋል። እንዲሁም ባልታወቁ ሰዎች ከጠበቆቹ መካከል መኪና ተሰብሮ የተለያዩ ሰነዶች እንደተወሰደባቸው በማንሳት ጫናው የተለያየ መሆኑን አቶ ምስጋናው ጨምረው ገልፀዋል። በዚህም ሳቢያ "ጠበቆች በሚደርስባቸው የመታሰር፣ ዘለፋ፣ ማንጓጠጥ እና ማስፈራራት የተነሳ የመኖሪያ አካባቢያቸውን ለቅቀው እስከመሄድ የደረሱም አሉ። ስለዚህ የሚታይ ተጽዕኖና የሥነ ልቦና ጫና እየደረሰብን ይገኛል" በማለት ለቢቢሲ ተናግረዋል። ምክትል ጠቃላይ ዐቃቤ ሕጉ አቶ ፍቃዱ ፀጋ በበኩላቸው "እስካሁን ጠበቆች ፍርድ ቤት ቀርበው በነጻነት ለደንበኞቻቸው ሲከራከሩ እያየን ነው" በማለት "ነገር ግን እንዲህ አይነት ቅሬታ ካላቸው ደግሞ እዚያው ፍርድ ቤት ላይ እየገጠመን ነው የሚሉትን ጉዳይ በማንሳት እንዲስተካከልላቸው መጠየቅ ይችላሉ" ሲሉ ለቢቢሲ ምላሻቸውን ሰጥተዋል። አቶ ፍቃዱ እንደሚሉት የተጠቀሱት አይነት ችግሮች አጋጥመው ከሆነ "በጠበቆች ላይ የሚፈፀም ተጽዕኖ በየትኛውም መስፈርት ተቀባይነት የለውም" ብለዋል። "ግለሰብ ይህንን ድርጊት ሊፈጽም ይችላል። በቢሮ ደረጃ እንዲህ አይነት ነገር ይፈፀማል ብዬ አላስብም። ተደርጎ ከሆነ ደግሞ ትልቅ ወንጀል ነው" ሲሉም አክለዋል። ጨምረውም ጠበቆቹ በሙያቸው በሕግ ፊት ለተከሳሾች መብት ተከራካሪ መሆናቸው አመልክተው፤ ይሁን እንጂ "በቀረበው ቅሬታ እውነትነት ላይ ጥርጣሬ አለኝ" ሲሉ ተናግረዋል። ነገር ግን የትኛውም ጠበቃ ደረሰብኝ ለሚለው የትኛውም አይነት ተጽዕኖ ተጨባጭ መረጃ ካለው ወደ ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመውሰድ ቅሬታውን ማቅረብ እንደሚችል አቶ ፍቃዱ ገልፀዋል። ከወራት በፊት በአዲስ አበባና በአንዳንድ የኦሮሚያ ከተሞች ተከስቶ ለበርካታ ሰዎች ህይወት መጥፋትና በቢሊዮን ብሮች ለሚገመት ንብረት ውድመት መከሰት ምክንያት ከሆነው ሁከት ጋር በተያያዘ በርካቶች ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ ነው። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ክስ ለተመሰረተባቸው የፖለቲካ ፓርቲ አባላትና የሌሎችንም ጉዳይ በተመለከተ በፍርድ ቤት ተጠርጣሪዎች በመወከል ጉዳያቸውን የሚከታተሉ ከአስር በላይ የሚሆኑ ጠበቆች ያሉበት አንድ የሕግ ባለሙያዎች ቡድን ጥብቅና መቆሙ ይታወቃል።
news-54815231
https://www.bbc.com/amharic/news-54815231
መቀሌ አሁን ያለችበት ሁኔታ ከዘጋቢያችን አንደበት
መቀሌ የሚገኘው የቢቢሲ ዘጋቢ ከትላንት ጀምሮ በከተማዋ የነበረው ሁኔታ እንዲህ ዘግቦታል። የሚከተሉትን ፎሮ ግራፎችም ልኮልናል።
መቀለ ከተማ ዛሬ ትላንት [ማክሰኞ] እኩለ ለሊት ገደማ መቀሌ ከተማ ተኩስ ይሰማ ነበር። የከተማው ሰው እየሆነ ባለው ነገር ተደናግጦ ነበር። ይሄኔ ሁኔታውን ለማረጋገጥ ወደ ፀጥታ ኃይል ሰዎች ስደውል 'አሁን ልናናግርህ አንችልም፤ ቢዚ ነን' አሉኝ። ከደቂቃ በኋላ የስልክ መስመር ተቋረጠ። ስልኬ 'ኖ ሰርቪስ' የሚል ምልክት ያሳየኝ ጀመር። በመቀጠል የኢንተርኔት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ተቋረጠ። ጥዋት ስንነሳ ከተማዋ የኤሌክትሪክ አገልግሎቷ እንደተቋረጠ ተረዳሁ። መብራት የጠፋው መቀሌ ብቻ ሳይሆን ትግራይ ክልል ሙሉ እንደሆነ ማረጋገጥ ችያለሁ። በርካታ ሰዎች በከተማ ሲንቀሳቀሱ ተመልክቷል። ወደ ከተማ ወጣ ስል የሰዎች ፊት ላይ ግራ መጋባት ተመለከትኩ። አብዛኛው ሰው በእግሩ ነበር ሲንቀሳቀስ የነበረው። ከተማዋ ላይ ያሉ የባንክ ቅርንጫፎች ተዘግተው ነበር። ሁለት የባንክ አስተዳዳሪዎች እንደነገሩኝ አገልግሎት ያቋረጡ የበይነ መረብ [ኢንተርኔት] አገልግሎት ስለሌለ ነው። ረፋድ ላይ የኢትዮቴሌኮም ሠራተኞች መስሪያ ቤታቸው ደጃፍ ላይ ሰብሰብ ብለው ቆመው ነበር። ከረፋፈደ በኋላ ከፀጥታ ኃይል ሰዎች እንደተረዳሁት ተኩሱ የተሰማው የትግራይ ክልል ወታደሮች ከሰሜን ዕዝ ጋር በነበራቸው የተኩስ ልውውጥ መሆኑን ተረድቻለሁ። ወደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ ቢሮና ወደ ሌሎች የጉዞ ወኪሎች አምርቼ ለጊዜው በረራ ሙሉ በሙሉ መቋረጡን መረዳት ችያለሁ። በትግራይ የስልክ እና ኢንተርኔት አገልግሎት ተቋርጧል መቀሌ ከተማ ያሉ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችና ሆቴሎች አካባቢ ከበድ ያለ የፀጥታ ኃይል ይታያል። የክልሉ መንግሥት ክልሉ ውስጥ ምንም ዓይነት ወታደራዊ እንቅስቃሴ እንዳይኖር አግዷል። የትራንስፖርት አገልግሎትም ሙሉ በሙሉ ቆሟል። የክልሉ የአየር ክልልም ከበረራ ውጭ እንዲሆን ታዟል። መቀሌ ከተማ አሁን ላይ ሰላማዊ ሁኔታ ላይ ትገኛለች።
news-55905192
https://www.bbc.com/amharic/news-55905192
በሚየንማር ሳን ሱቺ ይለቀቁ የሚሉ ጥያቄዎች መበርታታቸው ተሰማ
በትናንትናው ዕለት በቀድሞዋ በርማ በአሁኗ ሚየንማር ጦሩ በመፈንቅለ መንግሥት ስልጣን መቆጣጠሩን ተከትሎ የአገሪቷ መሪ ኦንግ ሳን ሱ ቺ ይለቀቁ የሚሉ ጥያቄዎች በርትተዋል።
የኖቤል ተሸላሚዋና በምርጫ ስልጣን የተቆናጠጡት ኦንግ ሳን ሱ ቺ በወታደሮች በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ አልታዩም ተብሏል። ከሳቸው በተጨማሪ በመቶዎች የሚቆጠሩ የፓርላማ አባላትም በመዲናዋ በሚገኘው መኖሪያ ስፍራቸው በወታደሮች ተከበው ነው የሚገኙት። ምንም እንኳን ይኸንን ያህል ጠንከር ያለ ተቃውሞ በአደባባዮች ባይሰማም የህክምና ባለሙያዎች የስራ ማቆም አድማ መትተዋል ፤አንዳንድ እምቢተኝነትም እየተስተዋለ ነው። በቅርቡ በምርጫ ማሸነፋቸው የታወጀውን ኦንግ ሳን ሱ ቺን ፓርቲ ምርጫውን አጭበርብሯል በማለት ጦሩ የሚወነጅል ሲሆን በትናንትናው ዕለት ስልጣን በእጁ ካስገባም በኋላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጇል። ፓርቲያቸው ናሽናል ሊግ ፎር ዲሞክራሲ (ኤን ኤል ዲ) ኦንግ ሳን ሱቺ በአስቸኳይ እንዲለቀቁ ጥያቄውን በዛሬው እለት አቅርቧል። ከዚህም በተጨማሪ በዚህ አመት በህዳር ወር የተደረገውና 80 በመቶ አሸናፊነቱን ያገኘው ኤንልዲ ፓርቲ ውጤቱን በፀጋ እንዲቀበል ለጦሩ ጥያቄ አቅርቧል። ምንያማር የሲቪል አስተዳደር በአውሮፓውያኑ 2011 ስልጣን እስኪይዝ ድረስ በጥምር ወታደራዊ ኃይል ትመራ ነበር። ምንያማር በመፈንቅለ መንግሥቱ ማግስት አገሪቷ በመፈንቅለ መንግሥቱ ማግስት ፀጥ ረጭ ያለች ሲሆን፤ ጎዳናዎቿም ነዋሪዎች አይታዩባቸውም። ወታደሮች በመኪና ተጭነው በተለያዩ ከተሞች በመዞር እየቃኙ ሲሆን የምሽት የሰዓት እላፊ አዋጅም ተጥሏል። በትናንትናው ዕለት ተቋርጦ የነበረው የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎት ተመልሷል። በዋነኛዋ ከተማ ያንጎን ጎዳናዎች ላይ አንዳንዶች ለአመታት የተዋጉለት ዲሞክራሲ መና ቀረ ማለታቸው ተሰምቷል። የኦንግ ሱን ሱቺ መለቀቅ እየጠየቀ ያለው ፓርቲዋ ብቻ ሳይሆን በመንግሥት ሆስፒታሎች የሚሰሩ ዶክተሮች ካልተለቀቀች ከነገ ጀምሮ ስራ አንገባም ማለታቸው ተሰምቷል። አንዳንዶችም ተቃውሟቸውን ለማሳየት ለየት ያለ ልብስ ለብው መጥተዋል። አንድ ዶክተር ከስራው መልቀቁ ተነግሯል።
news-53595985
https://www.bbc.com/amharic/news-53595985
ዶናልድ ትራምፕ በቀጣዩ ዓመት የሚካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እንዲዘገይ ጠየቁ
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በህዳር ወር የሚካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በፖስታ የሚሰጥ ድምጽ ወደ ማጭበርበርና የተሳሳተ ውጤት ያመራል በሚል ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ ጠየቁ።
ምርጫው የሚዘገየው እስከመቼ ድረስ እንደሆነ ሲናገሩም ሰዎች "በአግባቡ፣ ደህንነታቸውና ምስጢራቸው ተጠብቆ" መምረጥ ሲችሉ ብለዋል። የፕሬዝዳንቱን ንግግር የሚደግፍ መረጃ ያለው አነስተኛ ሲሆን፤ ፕሬዝዳንቱ ለረዥም ጊዜ ግን በፖስታ የሚሰጥ ድምጽ ለማጭበርበር ሊጋለጥ እንደሚችል አጠራጣሪ ሁኔታዎች መኖራቸውን ሲጠቅሱ ነበር። የአሜሪካ ግዛቶች በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ የተነሳ በፖስታ የሚሰጥን ድምጽ ቀላል ለማድረግ ይፈልጋሉ። ፕሬዝዳንት ትራምፕ በትዊተር ሰሌዳቸው ላይ "በዓለም ደረጃ በፖስታ የሚሰጥ ድምጽ" በህዳር ወር የሚደረገውን ምርጫ "በጣም ልክ ያልሆነ እና በታሪክ የተጭበረበረ ያደርገዋል" በማለት "ለአሜሪካም ማፈሪያ" ነው ሲሉ ተናግረዋል። በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ስድስት የአሜሪካ ግዛቶች በህዳር ወር የሚካሄደውን ምርጫ በአጠቃላይ "በፖስታ በሚሰጥ ድምጽ" ለማድረግ አቅደው ነበር። እነዚህ ግዛቶች ዋሺንግተን፣ ኦሪገን፣ ኮሎራዶ፣ ሃዋይ፣ ዩታህ እና ካሊፎርኒያ ናቸው። እነዚህ ስድስት ግዛቶች ለተመዘገቡ መራጮች ወዲያውኑ በፖስታ ድምጽ መስጫ የሚልኩ ሲሆን፤ ፖስታዎቹም በምርጫ ቀን ተመልሰው የሚላኩ አልያም በምርጫ ጣቢያ የሚመለሱ ይሆናል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በአንዳንድ አስገዳጅ ሁኔታዎች ምክንያት በአካል ድምጻቸውን የሚሰጡ የተወሰኑ ሰዎች ይኖራሉ ተብሏል። ግማሽ ያህል የአሜሪካ ግዛቶች ለተመዘገቡ መራጮች በጥያቄ መሰረት በፖስታ ድምጽ መስጠትን ይፈቅዳሉ። በፖስታ ድምጽ መስጠትን የሚቃወሙ አካላት መራጮች በማይመርጡ ተመዝጋቢዎች ምትክ ከአንድ በላይ ደምጽ ሊሰጡ ይችላሉ ሲሉ ይከራከራሉ። ከዚህ በፊት ፕሬዝዳንት ትራምፕ "በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በአንድ ሰው ሳሎን ቁጭ ብለው የምርጫ ወረቀቶችን ሊሞሉ ይችላሉ" ሲሉ ስጋታቸውን ተናግረው ነበር። ይሁን እንጂ ለዓመታት በመላ አገሪቱ በተደረገ ጥናት እስካሁን ድረስ እንዲህ እንደሚሰጋው በሰፊው ያጋጠመ ማጭበርበር አልታየም።
42884109
https://www.bbc.com/amharic/42884109
ትራምፕ ወቅቱ "የአሜሪካ አዲስ ዘመን ነው" አሉ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለኮንግረስ ባደረጉት የመጀመሪያው የፕሬዝዳንትነት ቆይታቸውና የአገሪቱ ሁኔታ የሚገልፀው ንግግር ወቅቱ ''የአሜሪካ አዲስ ጊዜ'' ነው በማለት አውጀዋል።
ከዲሞክራቶች ጋር አብሮ ለመስራትም እጃቸውን መዘርጋታቸውን ተናግረዋል። የአሜሪካ ኢኮኖሚ እያደገ ቢሆንም የትራምፕ ተቀባይነት ግን እየቀነሰ ነው። ከአንድ ዓመት በፊት የመጀመሪያውን የፕሬዝዳንታዊ ንግግራቸውን ሲያደርጉ አስተዳደራችው "አስተማማኝ፣ ጠንካራና ኩሩ አሜሪካንን" እየገነባ እንደሆነ ተናግረው ነበር። በዚህኛው ንግግራቸው ደግሞ "የአሜሪካን ህልም ለመኖር ከዚህ የተሻለ ጊዜ የለም " ሲሉ ለኮንግረስ አባላቱ ተናግረዋል። የአገሪቱ ዜጎች እንደ አንድ ቡድን፣ እንደ አንድ ህዝብና የአሜሪካ ቤተሰብ አንድ ላይ መቆም እንዳለባቸው የገለፁበት የትራምፕ ንግግር 40 ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎች በቴሌቪዥን እንደተከታተሉት ይገመታል። የውጭ ግንኙነትን በሚመለከት ሲናገሩ ደግሞ የሰሜን ኮሪያውን መሪ ኮንነዋል። ገደብ የለሹ የፒዮንግያንግ የኒኩሌር መሳሪያ ፍላጎት በቅርቡ የአገራቸውን ደህንነት አደጋ ላይ እንዳይጥልም አስጠንቅቀዋል። ይህ እንዳይሆንም በከፍተኛ ደረጃ አገሪቱ ላይ ጫና እየፈጠሩ መሆናቸውንም አስታውቀዋል። ትራምፕ ከሰሜን ኮሪያ ለሸሸውና ለኮንግረሱ ያደረጉት ንግግር ታዳሚ ለነበረው ሰሜን ኮሪያዊው የመብት አቀንቃኝ ጂ ሲዎንግ ሆም ምስጋና አቅርበዋል። በሶሪያና ኢራቅ በአክራሪ እስላማዊ ኃይሎች ተይዞ የነበረ ግዛት ሁሉ ነፃ መሆኑን የተናገሩት ትራምፕ "አይኤስ እስኪሸነፍ ትግላችን ይቀጥላል" ብለዋል። ከእሳቸው በፊት የነበሩ ሁለት ፕሬዘዳንቶች ለኮንግረሱ መሰል ንግግር ሲያደርጉ ያተኮሩት አሜሪካ በአፍጋኒስታን በምታደርገው ጦርነት ላይ ነበር። በአገሪቱ የደህነትና ፀጥታ ሁኔታ ማሽቆልቆሉን በማመን የአሜሪካ ጦር ኃይል ግን እንዲሁ በዋዛ የሚበገር እንዳልሆነ ተናግረዋል። በንግግራቸው ሩሲያን ከቻይና ጋር አንድ ላይ ተቀናቃኝ ሲሉ የጠቀሷት አንድ ጊዜ ብቻ ነበር። የማሳቹሴትስ ኮንግረስ አባልና የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ የቅርብ ቤተሰብ የሆነው ዲሞክራቱ ጆሴፍ ኬኔዲ የትራምፕን አንድ ዓመት የስልጣን ዘመን "በሁከት" የተሞላ ብሎታል። በስልጣን ስልጣን ዘመናቸውም አሜሪካ እየተከፋፈለች እንደሆነች ገልጿል።
41758439
https://www.bbc.com/amharic/41758439
የታይላንዱ ንጉሥ ከሞቱ አንድ ዓመት በኋላ ግብዓተ መሬታቸው ተፈፀመ
ንጉሥ ቡሚቦል ኣዱልያዴጅ ባለፈው ዓመት ወርሃ ጥቅምት ላይ ነበር ይህችን ዓለም በሞት የተለዩት።
በቡድሂስት መነከኮሳት እና በታዳሚዎች ታጅቦ ወደቀብር ሥፍራ የመጣው የንጉሱ አስከሬን በቡድሂዝም እምነት መሠረት በሥርዓቱ ፍፃሜ ላይ ይቃጠላል። የንጉሱን አስከሬን የሚያቃጥሉት ልጃቸው ንጉስ ማሃ ቪጂራሎንግኮርን ናቸው። የአምስቱ ቀናቱ ሥነ-ሥርዓት ዕለተ-ረቡዕ በይፋ የተጀመረ ሲሆን ዋና ከተማዋ ባንኮክ በቢጫና ወርቃማ ቀለሞች አጊጣለች። 14 ሺህ ኪሎግራም የሚመዝነውና የንጉሡን አስከሬን የያዘው ጋሪ በ200 ወታደሮች ታጅቦ የመጨረሻው ሥነ-ሥርዓት ወደሚፈፀምበት ሥፍራ እየተጓዘ ይገኛል። ወደ 250 ሺህ ታይላንዳዊያን እንደሚሳተፉበት የተገመተው ይህ ሥነ-ሥርዓት ከሌሎች አርባ ያህል ሃገራት የሚመጡ እንግዶች እንደሚሳተፉበትም ታውቋል። ንጉሡ የአባታቸውን አስከሬን ካቃጠሉ በኋላ ዕለተ-አርብ አመዳቸው ተመልሶ ወደ ቤተ-መንግስት ይገባል። ከዚያም ለሁለት ተጨማሪ ቀናት ሥርዓቱ ይቀጥላል። ሟቹ ንጉሥ በታይላንዳውያን ዘንድ ተወዳጅ እንደነበሩና የሃገሪቱን ምጣኔ ሃብታዊና ፖለቲካዊ ቀውሶችን በማረጋጋት ወደሰከነ መንፈስ እንዳመጡ ይነገራል። ንጉሥ ቡሚቦል አዱልያዴጅ ባለፈው ዓመት ወርሃ ጥቅምት ላይ ከሞቱ ጀምሮ ታይላንድ ለአንድ ዓመት ያክል ሃዘን ላይ የነበረች ሲሆን ሰዎች ጥቁር ለብሰው ይታዩም ነበር። አናብስትና ዝሆኖችን የመሳሰሉ እንስሳትና እና በተለያዩ ዓይነቶች የተሠሩ ቅርፃ ቅርፆች በቀብር ሥፍራው እንደሚገኙም ታውቀል። ሥነ-ሥርዓቱን የሚታደሙ ጎብኚዎች ጥቁር እንዲለብሱ ባይገደዱም በወጉ ለብሰው እንዲመጡ ማሳሰቢያ ተሰጥቷቸዋል። በታይላንድ የንጉሡን ቤተሰቦች ያልተገባ ነገር መናገርና መሳደብ ለከፍተኛ ቅጣት የሚዳርግ ጥፋት ነው፤ ይህም ከሌሎች ንጉሣዊ ሃገራት ለየት ያደርጋታል።
49969039
https://www.bbc.com/amharic/49969039
በ'ሰልፊ' ምክንያት ሳይጀመር የተቋጨው ትዳር
በሕንድ አዲስ ሙሽሮች ከቤተሰቦቻቸው ጋር በመሆን ሰልፊ ሲነሱ ውሃ ውስጥ ገብተው መሞታቸው ተሰማ።
ታሚል ናዱ በርካታ ግድቦችና የውሃ ማከማቻዎች የሚገኙበት ሲሆን በጎብኝዎች የሚዘወተር ስፍራ ነው ከሞቱት መካከል ሙሽሪት እና ሶስት ቤተሰቦቿ እንደሚገኙበት የምዕራብ ኢንዲያና ግዛት ፖሊስ አስታወቋል። ስድስት ሰዎች እጅ ለእጅ ተያይዘው በግድቡ ዳርቻ ፎቶ እየተነሱ ሳለ አንዳቸው በመንሸራተታቸውና ቀሪዎቹን ይዘው ወደ ግድቡ መውደቃቸውን የፖሊስ ሪፖርት ያሳያል። የሙሽሪት ባል እህቱን ማዳን የቻለ ሲሆን ሌሎቹ ግን መትረፍ ሳይችሉ ቀርተዋል። • "ምን ተይዞ ምርጫ?" እና "ምንም ይሁን ምን ምርጫው ይካሄድ" ተቃዋሚዎች • የናይጄሪያ ዩኒቨርስቲ በቢቢሲ ዘገባ ላይ ወሲባዊ ትንኮሳ ሲፈፅም የታየውን መምህሩን አገደ • ሕገ ወጥ ስብሰባ አካሂደዋል የተባሉት አሜሪካዊ ፓስተር በሩዋንዳ ታሰሩ ሕንድ ሰልፊ ሲነሱ በሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ቀዳሚውን ተርታ ይዛለች። ከጎርጎሳውያኑ ከ2011 እስከ 2017 ሰልፊ ሲነሱ ከሞቱ ሰዎች መካከል 259ኙ በሕንድ ሲሆን፤ ሩሲያ፣ አሜሪካና ፓኪስታን በተከታይነት ይገኛሉ። አዲሶቹ ሙሽሮች እሁድ ዕለት ዘመዶቻቸውን ለመጠየቅ እህቶቻቸውን ወንድሞቻቸውን ይዘው ወደ ቤተሰቦቻቸው ዘንድ እየሄዱ ነበር። በዚህ መካከል ውሃው ወዳለበት ፎቶ ለመነሳት ይቆማሉ። አንድ የ14 ዓመት ልጅ ግን አዳልጦት ሊወድቅ ሲል የያዛቸውን ላለመልቀቅ ሲውተረተር ሁለት ዕድሜያቸው 18ና 19 የሆነ እህቶቹን፣ ሙሽሪትን እና የሙሽሪትን እህት ይዞ ውሃ ውስጥ ይወድቃል ። ልጁ ግን መትረፍ አልቻለም። አዳልጦት ውሃ ውስጥ ወደቀ። ወዲያው ሙሽራው እህቱን ለማውጣት ቢችልም አራቱ ግን የገቡበት ሰምጠው ቀርተዋል። ፖሊስ እንዳስታወቀው በኋላ ላይ አስክሬናቸው ወጥቷል። በግንቦት ወር በሐራያና ግዛት ሶስት ታዳጊዎች በባቡር መንገድ ላይ ሰልፊ ሲነሱ ከሚመጣ ባቡር ለማምለጥ ዘልለው በሌላ የባቡር መስመር ላይ በመግባታቸው ከሌላ አቅጣጫ በመጣ ባቡር ተገጭተው ሕይወታቸው አልፏል። እአአ በ2017 አራት ተማሪዎች ሰልፊ ሲነሱ ከሞቱ በኋላ በአንድ ግዛት አነሳሽነት " ሰልፊ ይገላል" የሚል ዘመቻ ተጀምሮ ነበር። በተመሳሳይ ዓመት ከዝሆን ጋር ሰልፊ ለመነሳት የሞከረ ግለሰብ ዙሆኑ በኩንቢው ጠቅልሎ በማፈን ገሎታል።
news-49246444
https://www.bbc.com/amharic/news-49246444
የዚምባብዌ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቤ ሆስፒታል ከገቡ ወራት እንዳለፋቸው ተነገረ
የዚምባብዌ የቀድሞ መሪ ሮበርት ሙጋቤ ላለፉት አራት ወራት በሲንጋፖር ሆስፒታል ውስጥ ሕክምና እየተደረገላቸው እንደሚገኙ የአገሪቷ ፕሬዝዳንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ ገለፁ።
የ95 ዓመቱ የእድሜ ባለፀጋ -ሙጋቤን " የአገራችን መሥራች አባትና ባለውለታ" ያሏቸው ፕሬዚዳንት ምናንጋግዋ የቀድሞው ፕሬዚደንት ምንነቱ ባልተገለፀ ሕመም በሲንጋፖር የሕክምና ክትትል እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል። ባለፈው ሰኞ ባወጡት መግለጫ እንዳሉት ሮበርት ሙጋቤ በየጊዜው ከሚያደርጉት የጤና ምርመራ በተጨማሪ በሆስፒታል ሆነው የቅርብ ሕክምና ክትትል እንዲያደርጉ ሐኪማቸው መወሰናቸውን ገልፀዋል። ፕሬዝዳንት ምናንጋግዋ፤ ሙጋቤ በጤናና በእርጅና ምክንያት መራመድ እንደተሳናቸው ባለፈው ሕዳር ወር አስታውቀው ነበር። • ቴክቫህ ኢትዮጵያ፡ የፀረ ጥላቻ ንግግር የወጣቶች እንቅስቃሴ • በመድፈር የተወነጀሉት ፓስተር መመለስ በናይጀሪያ ቁጣን ቀሰቀሰ • ታዳጊዎቹን አብራሪዎች ሲረዱ የነበሩት ፓይለቶች በአውሮፕላን አደጋ ሞቱ ባለፈው መጋቢት ወርም የቀድሞ ፕሬዝዳንቱ ለሕክምና ወደ ሲንጋፖር እንዳመሩና በግንቦት ወር አጋማሽ ወደ ሀገራቸውን እንደሚመለሱ ማስታወቃቸው ይታወሳል። ይሁን እንጂ ሮበርት ሙጋቤ አሁንም በሆስፒታል ውስጥ እንደሚገኙ ተገልጿል። ባለፈው ሳምንት ሙጋቤን ለመጠየቅ ወደ ሲንጋፖር ቡድን እንደላኩ የተናገሩት ፕሬዝዳንት ምናንጋግዋ የጤና መሻሻል እያሳዩ እንደሆነና በቅርቡ ተሽሏቸው ከሆስፒታል ሊወጡ እንደሚችሉ ተናግረዋል። በዚምባብዌ የሕብረተሰብ ጤና አገልግሎት በመዳከሙ የገንዘብ አቅም ያላቸው ሰዎች ወደ ደቡብ አፍሪካና ሌሎች አገራት በመሄድ ለመታከም ይገደዳሉ። ሮበርት ሙጋቤም በሥልጣን ላይ በነበሩ ጊዜ የሕክምና ክትትላቸውን የሚያደርጉት በሲንጋፖር ነበር። ፕሬዚዳንት ምናንጋግዋ ለ37 ዓመታት አገሪቷን ሲመሩ ከነበሩት ሮበርት ሙጋቤ እአአ ሕዳር ወር 2017 ላይ ሥልጣን መረከባቸው ይታወሳል።
news-52883365
https://www.bbc.com/amharic/news-52883365
የጆርጅ ፍሎይድ የአስከሬን ምርመራ ውጤት ይፋ ሆነ
ባለፈው ሳምንት በሜኔሶታ የ46 ዓመቱ ጥቁር አሜሪካዊ ጆርጅ ፍሎይድን ለሞት ያበቃው በትክክል ምንድነው የሚለውን ለመለየት የሕክምና ውጤት ይፋ እስኪሆን ሲጠበቅ ቆይቷል።
በሟች አስከሬን ላይ ምርመራ ሲያደርግ የቆየው የሕክምና ተቋም ውጤቱን በመጨረሻ ይፋ አድርጓል። በዚህም መሰረት ጆርጅ ፍሎይድ የተገደለው በሰው እንደሆነ ብያኔ ሰጥቷል። ከዚህ መረጃ መውጣት በፊት አንዳንድ መገናኛ ብዙሃን የጥቁሩ አሜሪካዊ ሞት ፖሊስ ኃይልን ከመጠቀሙ ጋር በፍጹም የሚያያዝ አይደለም ሲሉ መዘገብ ጀምረው ነበር። አንዳንዶች እንዲያውም የሞተው በራሱ የጤና ችግር ነው እስከማለት ደርሰው ነበር። ይህ የአስከሬን ምርመራ ውጤት ሲጠበቅ የነበረውም ለዚሁ ነው። ይፋ በሆነው የአስከሬን ምርመራ ሪፖርት እንደተገለጸው ፍሎይድ ከክስተቱ በፊት ለሞት የሚያበቃው አንዳችም ነገር አልነበረም። ሆኖም የፖሊስ መኮንኑ በጉልበቱ አንገቱን በመጫኑ የልብ መታፈን ገጥሞታል። ያም ነው ለሞት ያበቃው ብሏል። በሕክምና ስሙ "ካርዲዮፑልሙናሪ አሬስት" የሚባለው ችግር በድንገት የደም ዝውውር ሲቆምና ይህም ልብ ደም መርጨት እንዲያቆም ሲያስገደድ የሚፈጠር ውስብስብ ችግር ነው። ጆርጅ ፍሎይድ ማጅራቱ አካባቢ የተጫነው ጉልበት የደም ዝውውሩን ሳያቋርጠው አልቀረም ይላል ሪፖርቱ። የአስከሬን ምርመራውን ያደረገው የሄኒፒን ካውንቲ ጤና ጣቢያ ሲሆን ሟች የልብ ሕመም እንደነበረበት እና መድኃኒት ወስዶ እንደነበረ የሚያሳዩ መረጃዎችን ማግኘት ችሏል። ይህ ሁኔታም ፖሊስ የሟችን ማጅራት በከፍተኛ ሁኔታ ሲጫነው ለመተንፈስ እንዲቸገር አድርጎት በዚህም የሟች የልብ ምት እንዲቆም አድርጎታል ይላል። ይህ መረጃ ይፋ የሆነው የፍሎይድ ቤተሰብ የግል አስከሬን መርማሪ ቡድን መቅጠረን ተከትሎ ነው። የፍሎይድ ቤተሰብ የቀጠረው የሕክምና መርማሪ ቡድንም ተመሳሳይ ውጤት ላይ ነው የደረሰው። የአስከሬን ምርመራ ሪፖርቱ ድምዳሜ ሟች ለህልፈት የበቃው በአሲፊክሲያ ነው ይላል። አሲፊክሲያ የኦክሲጅን እጥረት ሲሆን ይህም ሊፈጠር የቻለው ደግሞ በማጅራቱና በጀርባው አካባቢ ፖሊስ ሟችን እጅግ ስለተጫነው ነው ይላል። ዶ/ር ማይክል ባደን የኒውዮርክ ከተማ የቀድሞ የአስከሬን ምርመራ ባለሞያ ናቸው። ባለፈው ሰኞ ለጋዜጠኞች ሲናገሩ "ጆርጅ ፍሎይድን ለሞት አብቅቶታል ብዬ በግሌ የምገምተው አሲፊክሲያ ነው፤ ይህም የሚፈጠረው ወደ ጭንቅላት የሚሄደው አየር ሲቋረጥ ነው" ብለው ነበር። የሟች ቤተሰብ ጠበቃ ቤንጃሚን ክራምፕ በበኩላቸው "ወንድማችን ፍሎይድን፤ የፖሊስ መኮንኑ ዴሪክ ቾቪን ማጅራቱን ባይጫነው ኖሮ፣ ሁለቱ ባልደረቦቹ ጀርባው ላይ ባይቆሙበት ኖሮ ዛሬ ከእኛ ጋር ይቆም ነበር" ብለዋል። ከዚህ ሁሉ በኋላ የመጣችው አምቡላንስ ግን ይላሉ ጠበቃው "የሬሳ ሳጥኑ ነበረች።"
news-52513106
https://www.bbc.com/amharic/news-52513106
ኮሮናቫይረስን ለማከም ስለተፈቀደው መድኃኒት ሬምዴሲቬር ምን ይታወቃል?
የአሜሪካ ምግብና መድኃኒት አስተዳደር ተቋም ለኢቦላ በሽታ የሚውለውን ሬምዴሲቬር የተባለውን መድኃኒት ለአስቸኳይ ጊዜ የኮሮናቫይረስ ህክምና እንዲውል ፈቀደ።
የኮሮናቫይረስ ህሙማንን ለማከም እንዲውል የተፈቀደው ሬምዴሲቬር በዚህም መሰረት ይህ ጸረ ቫይረስ የሆነው መድኃኒት በኮሮናቫይረስ በጽኑ ታመው ሆስፒታል የሚገኙ ሰዎችን ለማከም ይውላል። የአሜሪካ ምግብና መድኃኒት አስተዳደር ኮሚሽነር የሆኑት ስቴፈን ሃን "ይህ የኮሮናቫይረስን ለማከም ዕውቅና የተሰጠው የመጀመሪያው መድኃኒት ነው" ብለዋል። በቅርቡ ሬምዴሲቬርን በመጠቀም በተደረገ ሙከራ በኮሮናቫይረስ ክፉኛ ታመው ሆስፒታል የገቡ ሰዎች የሚያገግሙበትን ጊዜ ማፋጠን እንዳስቻለ ተረጋግጧል። ነገር ግን ይህ በተቋሙ መድኃኒቱን ለመጠቀም የተሰጠው የአስቸኳይ ጊዜ ፈቃድ ሙሉ ፈቃድ አለመሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ መደበኛ ዕውቅና ለማግኘት ከፍ ያለ ምዘናን ይጠይቃል። ባለሙያዎች እንደሚሉት ይህ ኢቦላን ለማከም የተሰራው መድኃኒት ኮሮናቫይረስን እንደሚፈውስ ተአምረኛ መፍትሄ መወሰድ የለበትም። ስለሬምዴሲቬር የምናውቀው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ይህ ሬምዴሲቬር የተባለው የኢቦላ መድኃኒት የኮሮናቫይረስን ለማከም ጥቅም ላይ እንዲውል ከፍተኛ ድጋፍ ሲሰጡ ቆይተዋል። ሬምዴሲቬር ሰዎች ከኮሮናቫይረስ በፍጥነት እንዲያገግሙ እንደሚረዳ በአሜሪካ የጤና ባለስልጣናት ዘንድ ጠንካራ እምነት ተጥሎበታል። በተጨማሪም መድኃኒቱ የህሙማኑን ህይወት በመታደግ በኩልም አቅም እንደሚኖረው የታመነ ሲሆን፤ መድኃኒቱን በስፋት ጥቅም ላይ ማዋል ከተቻለ በሆስፒታሎች ላይ ያለውን ጫና ለመቀነስ ያስችላል። በተጨማሪም ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫናን ያስከተለውን የእንቅስቃሴ ገደብ በተወሰነ ደረጃ ለማላላት ሊያግዝ ይችላል ተብሏል። ኢቦላን ለማከም የተሰራው ሬምዴሲቬር የጸረ ቫይረስ መድኃኒት ሲሆን፤ በዋናነት ኢላማ የሚያደርገው በህዋሳት ውስጥ ቫይረስ እንዲባዛ የሚያግዘውን ኤንዛይም በማጥቃት ማስቆም ነው። በኮሮናቫይረስ ዘመን እጅግ ተፈላጊው መሣሪያ፤ ቬንትሌተር የአሜሪካ ብሔራዊ የአለርጂና ተላላፊ በሽታዎች ምርምር ተቋም በሬምዴሲቬር ላይ ባደረገው የሙከራ ምርምር መድኃኒቱ በኮሮናቫይረስ ህሙምን ላይ የሚታየውን የበሽታውን ምልክቶች ቆይታ ከ15 ቀን ወደ አስራ አንድ ዝቅ ማድረጉን አመልክቷል። ሙከራው በዓለም ዙሪያ ያሉ ሆስፒታሎችን በማካተት በ1,063 ሰዎች ላይ የተካሄደ ሲሆን፤ ለተወሰኑት መድኃኒቱን የተሰጣቸው ሲሆን ለሌሎቹ ደግሞ ምንም ውጤት የማያመጣ ማስመሰያ መድኃኒት ተሰጥቷቸው ነበር። የተቋሙ ኃላፊና የፕሬዝዳንቱ የጤና አማካሪ የሆኑት ዶክትር አንቶኒ ፋውቺ በሙከራው ስለተገኘው ውጤት "ሬምዴሲቬር የኮሮናቫይረስ ህሙማን የሚያገግሙበትን ጊዜ በማሳጠር አዎንታዊ፣ ግልጽና ከፍ ያለ "ውጤትን እንዳሳየ አመልክተዋል። ነገር ግን ሬምዴሲቬር በኮሮናቫይረስ የታመሙ ሰዎች በቶሎ እንዲያገግሙ ምናልባትም ክፉኛ ታመው ወደ ጽኑ ህሙማን ክፍል እንዳይገቡ ሊያደርግ ቢችልም በሽታውን ሙሉ በሙሉ በመፈወስ በኩል የተረጋገጠ ነገር የለም። በተጨማሪም በመድኃኒቱ ላይ የተደረጉት ሙከራዎች ሬምዴሲቬር በኮሮናቫይረስ ምክንያት ሊከሰቱ የሚችሉ ሞቶችን በማስቀረት በኩል ያለውን ጠቀሜታ የሚያመለክት ግልጽ የሆነ ውጤት አልታየም። ይህ ሬምዴሲቬር የተባለው መድኃኒት የተፈጠረውና የዳበረው 'ጊሌድ ሳይንስስ' በተባለው ተቋም ኢቦላንና ማርበርግ የተባሉትን በቫይረስ የሚመጡ በሽታዎችን ለማከም በተደረገ ጥናት አማካይነት ነው። በኋላ ላይም ይህ መድኃኒት በተለያዩ የኮሮናቫይረስ ዝርያዎችና በሌሎችም በቫይረስ በሚመጡ በሽታዎች ላይ የጸረ ተህዋስነት ባህሪይ እንዳለው ጊሌድ ሳይንስስ ደርሶበታል። በጥቅምት ወር 2015 (እአአ) የአሜሪካ ጦር ሠራዊት የተላላፊ በሽታዎች ህክምና ምርምራ ተቋም በዝንጀሮዎች ላይ ባደረገው ሙከራ ሬምዴሲቬር የኢቦላ ቫይረስን ማገድ እንደሚችል አስታወቋል። ከዚያም ከ2013-2016 ድረስ ባሉት ዓመታት ውስጥ በምዕራብ አፍሪካ አገራት ውስጥ ባጋጠመው የኢቦላ ወረርሽኝ ሰብብ በፍጥነት በሰዎች ላይ እንዲሞከር ከተደረገ በኋላ በበሽታው የተያዙ ሰዎችን ለማከም ጥቅም ላይ ውላል።
51172208
https://www.bbc.com/amharic/51172208
የዓለማችን ቁጥር አንድ ሃቀኛዋ ሃገር ማን ትሆን?
እንኳን ቦርሳና ዋሌት፣ የእጅ ስልክና የመገበያያ ካርድ፤ ሃሳብ እንኳ አንዴ ከአፍ ከወጣ በማይመለስበት ዘበን የአንዲት ሃገር ዜጎች የጠፋ ንብረት በመመለስ የሚደርስባቸው አልተገኘም።
የዚህች ሃገር ዋና ከተማ 14 ሚሊዮን ሰዎች አቅፋና ደግፋ ይዛለች። ሆኖም በፈረንጆቹ 2018 ከጠፉ 545 ሺህ መታወቂያዎች መካከል ሳይምለስ የቀረ የለም። ሁሉም ባለቤቶቻቸው ጋር በድጋሜ ተገናኝተዋል። እና መታወቂያ ምን ዋጋ አለው? ሊሉ ይችላሉ። 130 ሺህ ስልኮች የጣሉ ሰዎች ከእጅ ስልካቸው ጋር በሰላም ተገናኝተዋል። አሁንስ? ምን ይሄ ብቻ 240 ሺህ ዋሌት ቦርሳዎች የጣሉ ግለሰቦች ቤሳ ቢስቲን ሳይነካባቸው ተመልሶላቸዋል። ምን ልባችንን አንጠለጠላችሁት ሃገሪቱን ንገሩን እንጂ እያሉ እንደሆነ እንገምታለን - ጃፓን ናት። ጃፓን ውስጥ የጠፋ ይገኛል፤ የተረሳ ይታወሳል። ሌላ ቦታ ዜና የሚሆነው የጠፋ ተመለሰ ነው። ፓጃን ግን ተቃራኒው ነው። የስነ-ልቡና ባለሙያው ካዙኮ በርኸንስ 'እኔ ሳን ፍራንሲስኮ ስኖር አንድ ግለሰብ ዋሌት መለሰ ተብሎ ቴሌቪዥን ላይ ሳይ ነበር' ይላሉ። ባለሙያው እውነት ብለዋል። የጠፋ የመለሰ የዜና ሲሳይ መሆኑ አይቀርም። ጃፓን ውስጥ ዜና መሆን ከፈለጉ የጠፋ አይመልሱ የሚል ምክር መስጠት አንሻም። ካዙኮ፤ እምብርታቸውን የቀበሩት፤ ጥርሳቸውን የነቀሉት ጃፓን ነው። ሃቀኝነት ምን ያክል ቦታ እንዳለው አይዘነጉም። ጃፓኖች የጠፋ የሚመልሱት ወረታ ፈልገው አይደለም። እንደውም የጠፋ ዕቃ ሲያገኙ ለፖሊስ አስረክበው እነሱ ወደ ሥራ ያመራሉ። ፖሊስ ያገኛቸውን ንብረቶች ባለቤቱን አፈላልጎ ያስረክባል። ባለቤቱ ካልተገኘ ይጠብቃል። ተጠብቆ ካልመጣ ዕቃ ከጥቅም ውጭ እንዲሆን ይደረጋል። ኮባን በመባል የሚታወቁት የቶኪዮ አነስተኛ ፖሊስ ጣብያዎች ቶኪዮ ውስጥ በየመቶ ስኩዌር ኪሎሜትር ርቀት 97 አነስተኛ ፖሊስ ጣብያዎች አሉ። ጣብያዎቹ ኮባን ይባላሉ። ይህ ማለት ጠፋብኝ ወይም አገኘሁ ብሎ ለማመልከት እጅግ ቀላል ነው። ሎንዶን ብትገቡ የምታገኙት 11 ብቻ ነው። የቶክዮ ፖሊስ መኮንኖች በትህትናቸው ይታወቃሉ። አዛውንትን መንገድ በማሻገርም የሚደርስባቸው የለም። ዜጎችም ወድቆ ያገኙትን ንብረት ለፖሊስ እንዲያስረክቡ ይበረታታሉ። ይህ ገና ከልጅነት የሚማሩት ሥነ-ምግባር ነው። አንዳንድ ንብረቶች ለፖሊስ ከተሰጡ በኋላ የንብረቱ ባለቤት ካልተገኘ ላመጣው ሰው በሽልማት መልክ ይበረከታል። የፖሊስ መኮንኑ ማሳሂሮ ታማሩ 'አንድ ታዳጊ አንዲት ሳንቲም ቢያገኝ ወደ ፖሊስ ይዞ ይመጣል፤ ፈላጊ ካለ [ምንም እንኳ አንዲት ሳንቲም ፈልጎ የሚመጣ ባይኖርም] ይመለሳል፤ ካልሆነ ግን ላመጣው ሰው በሽልማት መልክ ይሰጣል።' ይህን ፅንሰ-ሐሳብ ለማረጋገጥ የተሰማሩ አጥኚዎች እንደ ጠፉ አስመስለው ቶኪዮ መንገድ ላይ ከጣሏቸው ስልኮች መካከል 88 በመቶው ተመልሰዋል። መሃል ኒው ዮርክ ከተጣሉት መካከል ግን 6 በመቶ ብቻ ናቸው ሊገኙ የቻሉት። ቶኪዮ ውስጥ ከሚጠፉ ዋሌቶች 80 በመቶ ይገኛሉ፤ ኒው ዮርክ ውስጥ ደግሞ 10 በመቶ ብቻ። ቶኪዮ ውስጥ ቢጠፋም የማይፈለገው አንድ ንብረት ዣንጥላ ይመስላል። 338 ሺህ ዣንጥላዎች የጠፉባት ከተማ 1 በመቶ ብቻ ናቸው ጥላዬን ብለው የመጡት። ቶኪዮ ውስጥ የፕላስቲክ ዣንጥላዎች ርካሽ ከመሆናቸው የተነሳ በነፃ የሚቀመጡበት ሥፍራም አለ። ምንም እንኳ ጃፓን የጠፋ የሚመለስባት ይሁን እንጂ የግልፅነት ችግር እንዳለ የሥነ-ልቡና ባለሙያው ያወሳሉ። ይህ ደግሞ የባሕል ተፅዕኖ ነው። ሰዎች ባሕል አክባሪና ፈሪ ናቸው ይላሉ። ነገር ግን ነገሮች እየተቀየሩ እንደሆነ ባለሙያው ያሰምራሉ። ካዙኮ የጃፓናውያንን ሃቀኝነት ከቡድሃ እምነት ጋር ያይዙታል። ሃገሪቱ በሱናሚ በተናጠች ጊዜ እንኳን ያላቸው ለሌሎች ሲያካፍሉ ታይተዋል። ጃፓናውያን ለባሕላቸው ያላቸው አክብሮትም ለዚህ አስተዋፅዖ እንዳለው ይታመናል። ከግላዊ አስተሳሰብ ይልቅ አብሮነት ትልቅ ቦታ ይሰጠዋል።
news-51306277
https://www.bbc.com/amharic/news-51306277
በኮሮናቫይረስ ስጋት ናይጄሪያ የቻይናዊያን መደብርን ዘጋች
የናይጄሪያ ባለስልጣናት በዓለም ዙሪያ በአሳሳቢ ሁኔታ እየተዛመተ ካለው የኮሮናቫይረስ ጋር በተያያዘ በዋና ከተማዋ አቡጃ የሚገኝ የቻይናዊያን መደብርን ዘጉ።
እርምጃውን የወሰደው የናይጄሪያ ሸማቾች ጥበቃ ተቋም እንዳለው እንዲዘጋ የተደረገው የቻይናዊያን መደብር "በሕገ ወጥ መንገድ ወደ አገር ውስጥ የገቡ የዓሳና የሥጋ ምርቶችን ሲሸጥ" በመገኘቱ ነው። ተቋሙ እርምጃውን የወሰደው እነዚህ ምርቶች የኮሮና ቫይረስን ሊያዛምቱ ይችላሉ በሚል ስጋት እንደሆነም ተገልጿል። የናይጄሪያ መንግሥት የንግድ ውድድርና የሸማቾች ጥበቃ ኮሚሽን በሕገወጥ መንገድ የገቡትን የምግብ ምርቶች ሊይዝ የቻለው በመደብሩ ላይ ባደረገው "ድንገተኛ" ፍተሻ መሆኑን ገልጿል። • ኮሮናቫይረስ፡ ምን ያህል አሳሳቢ ነው? • የአፍ ጭምብል ማጥለቅ ከቫይረስ ይታደገን ይሆን? • አንድ የኮሮና ቫይረስ ተጠርጣሪ ኬንያ ውስጥ ተገኘ ተቋሙ ጨምሮ እንዳመለከተው ከሱፐርማርኬቱ ከተያዙት የምግብ ምርቶች መካከል አብዛኞቹ ደረጃቸውን ያልጠበቁና የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈባቸው ናቸው። ተቋሙ ስለወሰደው እርምጃ እንደተናገረው በመደብሩ ውስጥም "ለእስያዊያን ተጠቃሚዎች ተብሎ የተዘጋጀ የተለየና ድብቅ ቦታ" ማግኘቱን አመልክቷል። አክሎም በሕገ ወጥ መንገድ ከቻይና የገቡ የዓሳና የሌሎች እንስሳት ምርቶች ማግኘቱን አረጋግጦ፤ የኮሮናቫይረስን ስርጭትን ግምት ውስጥ በማስገባት መደብሮቹ እንዲዘጉ መደረጉን ገልጿል። እስካሁን ከ150 በላይ ሰዎችን የገደለውና ወደ ተለያዩ አገራት እየተዛመተ ያለው አዲሱ ኮሮናቫይረስ በቻይናዋ ዉሃን በተባለችው ከተማ ውስጥ በሚገኝ የዓሳ መሸጫ ገበያ ውስጥ እንደተቀሰቀሰ ይነገራል። የናይጄሪያ ባለስልጣናትም እርምጃ ከዚሁ ክስተት ጋር በተያያዘ በተፈጠረ ስጋት እንደሆነ ተነግሯል።
news-50914859
https://www.bbc.com/amharic/news-50914859
በሙስሊሞች የሚጠበቀው የአይሁዶች ቤተ መቅደስ
ቢያንስ ለ 140 ዓመታት፣ ከአውሮፓውያኑ 1772 እስከ 1911 ድረስ ማለት ነው፣ ካልካታ በእንግሊዝ ቁጥጥር ስር የነበረቸው ህንድ ዋና ከተማ ነበረች። ይህ ደግሞ ከተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች ለሚመጡ በርካታ ሰዎች የንግድ ማዕከል እንድትሆን አድርጓታል።
በዚህ ምክንያት ቻይናውያን፣ አርመኖችና ግሪኮች ንግዳቸውን በካልኮታ በኩል ያቀላጥፉ ነበር። በዚህ መንገድ ነበር ታድኣ ከመካከለኛው ምስራቅ የሚመጡ የአይሁድ እምነት ተከታዮች ብቅ ብቅ ማለት የጀመሩት። ባግዳዲዎች ወይም የባግዳዲ አይሁዶች በመባል የሚታወቁት እነዚህ ህዝቦች ከአሁኖቹ ኢራቅ፣ ሶሪያ እና ሌሎች አረብኛ ተናጋሪ ሀገራት የዘር ግንዳቸው ይመዘዛል። እ.አ.አ. በ 1798 አካባቢ ነበር እነዚህ አይሁዶች በካልካታ መስፈር የጀመሩት። • ''በፍርሀት የምንኖርና በሃገራችን እንደ ሁለተኛ ዜጋ የምንቆጠር ሰዎች ሆነናል'' • ቲፋኒ ሃዲሽ፡ ጥቁርነትና ይሁዳዊነት • የቢላል መስጂድንና ራጉዔል ቤተ ክርስትያንን የሚያሰሩት ካህን በ1990ዎቹ ደግሞ በሺዎች የሚቆጠሩ አይሁዶች ከሂንዱ እና እስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ጋር በካልካታ መኖር ጀመሩ። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ ደግሞ ከ 5000 በላይ አይሁዳውያን ይኖር የነበረ ሲሆን በአሁኑ ሰዐት አብዛኛዎቹ ወደ እስራኤል፣ አሜሪካ፣ እንግሊዝ፣ ካናዳ እና አውስትራሊያ ተሰድደዋል። በካልካታ የሚኖሩ የአይሁዶች ቁጥር ከ 24 እንደማይበልጥ ይነገራል። ምንም እንኳን የሀይማኖቱ ተከታዮች ቁጥር እጅጉን ቢቀንስም በአካባቢው ያለው የሌላ እምነት ተከታይ ከትውልድ ትውልድ ሲተላለፍ የኖረውን ባህል እያስቀጠለ ይገኛል። በካልካታ የቀሩት ሶስት የአይሁድ ቤተ መቅደሶች ደግሞ እንክብካቤ የሚደረግላቸውና ንጽህናቸው የሚጠበቀው በሙስሊም እምነት ተከታይ ወንዶች ነው። በ1856 የተሰራው ቤት ኤል የሚባለው ቤተ መቅደስ ውስጥ ለመጎብኘት የሚገቡ ሰዎች ብዙም ያልተለመደ ነገር ይመለከታሉ፤ ጭንቅላታቸው ላይ የሙስሊም ቆብ ያጠለቁ አራት ወንዶች በእንጨት የተሰራውን በረንዳና በእምነበረድ የተሰራውን ወለል ጎንበስ ብለው ሲያጸዱ። ሲራጅ ክሃን ላለፉት 120 ዓመታት ቤተሰቦቹ ተቀጥረው ሲሰሩት የነበረውን ስራ እያከናወነ ይገኛል። በካልኮታ የአይሁዶች ማህበረሰብ ዋና ጸሀፊ የሆኑት አም ኮኀን እንደሚሉት ሲራጅ ክሃን እና መሰል የእስልምና እምነት ተከታዮች ሆነው ቤተ መቅደሱን የሚንከባበከቡ የአካባቢው ነዋሪዎች እንደ አይሁድ ቤተሰብ አባላት ነው የሚቆጠሩት። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በፊትና በኋላ በርካታ አውሮፓ አይሁዶች ናዚ ጀርመኖችን ሸሽተው በካልካታ ተጠግተው ነበር። ልክ ከዚህ በፊት ቀድመው እንደመጡት የመካከለኛ ምስራቅ አይሁዶች የአውሮፓ አይሁዶችም በካልካታ ሰላምና አስገራሚ ባህልን አግኝተዋል። ''ፈጣሪ በሁሉም ቦታ ይገኛል፤ በመስጂድም፣ በቤተ ክርስቲያንም፣ በገዳምም፣ በአይሁድ ቤተ መቅደስም። በዚህ ቤተ መቅደስ የምሰጠው አገልግሎት ከፈጣሪ ምስጋናን የሚያስገኝልኝ እንደሆነ ስለማውቅ በሙሉ ፈቃደኝነት ነው የማደርገው'' ይላል ሲራጅ ክሃን። '' አያቴ፣ አባቴና ወንድሜ በዚሁ ተመሳሳይ ስራ ተሳትፈዋል። ቤተሰቤ በእስልምና ሀይማኖት ጠንካራ ነው፤ ነገር ግን የአይሁዶችን ቤተ መቅደስ ከመንከባከብ አላስቆምንም።'' የህንድ ምዕራባዊ ቤንጋል ከፍተኛ የሙስሊም እምነት ተከታዮች የሚገኙበት ሲሆን ካልካታ ደግሞ ዋና ከተማ ናት። 4.5 ሚሊየን የሚሆኑት የግዛቱ ነዋሪዎች ሙስሊሞች ሲሆኑ ክርስቲያኖች፣ አይሁዶች፣ ቡድሂስቶችና የሌሎች ሃይማኖት ተከታዮች በፍቅርና በስምምነት ይኖሩባታል። ለዚህም ነው 'የደስታ ከተማ' የሚል ስያሜ የተሰጣት። • እዩ ጩፋ፡ ማን ነው ነብይ ያለህ? • "ወደ እናት ሃገራችን እስራኤል ውሰዱን" በካልካታ የሂንዱ እምነት ተከታዮች መስጂድ ውስጥ ገብተው የኢድ አል አድሃ በአልን ሲያከብሩ መመልከት የተለመደ ነገር ነው። በአውሮፓውያኑ 1881 በአይሁዶች የተቋቋመው የሴቶች ትምህርት ቤት በአሁኑ ሰአት ሙሉ በሚባል ደረጃ ሙስሊም ተማሪዎች ብቻ ናቸው የሚገኙበት። የሃይማኖቱ ጉዳይ የተረሳ ይመስላል። ህንድ በ1974 ከእንግሊዝ ነጻነቷን ስታገኝ አይሁድ እምነት ተከታዮች ሀብት ንበረታቸው በአዲሱ የህንድ መንግስት እንደሚወረስባቸው በመፍራት ወደ አሜሪካና እንግሊዝ ተሰደዋል። ሌላኛው በካልካታ የአይሁዶች ቁጥር መቀነስ ምክንያት በ1948 እስራኤል እንደ አንድ ሀገር መቋቋም ነው። ምንም እንኳን በከፍተኛ ሁኔታ ቁጥራቸው እየቀነሰ የመጣው የካልካታ አይሁዶች የወደፊት እጣ ፈንታ ባይታወቅም ሁለቱ ቤተ መቅደሶች በህንዱ አርኪዮሎጂካል ሰርቬይ በሀገር ሀብትነት ተመዝግበው ይገኛሉ።
45293473
https://www.bbc.com/amharic/45293473
የተፈናቀሉ ኢትዮጵያውን አስከፊ ሁኔታ ላይ መሆናቸው ተገለፀ
በደቡብ ኢትዮጵያ የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ የተፈናቀሉ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ህዝቦች በአሳሳቢ ሁኔታ ጉስቁልና ላይ መሆናቸውን የእርዳታ ድርጅቶች ገልፀዋል።
በተለይም የዝናብ ወቅት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የመንገዶች ምቹ አለመሆን እርዳታ ለሚሹና ከሚሊዮን ለሚልቁ ሰዎች እርዳታ ማድረስን ከባድ እንዳደረገው ገልፀዋል። በጌዴዮና ምዕራብ ጉጂ ዞን ድንበር አካባቢ የተነሳው ግጭትን ተከትሎ ከስምንት መቶ ሺህ ሰዎች በላይ ተፈናቅለዋል። የቢቢሲ ጋዜጠኛ በአካባቢው ሄዶ እንደታዘበው ሰዎች በፈታኝ ሁኔታ ላይ መሆናቸውን ፤ ትምህርት ቤቶችና ኮሌጆችም ወደ ጊዜያዊ መጠለያነት ተቀይረዋል። •በኢትዮጵያ ብሔር ተኮር ግጭቶችና ጥቃቶች አሳሳቢ ሆነዋል •"ሥርዓቱ ይሆናል እንጂ አገር አትበታተንም" •በምሥራቅ ኢትዮጵያ ከሃምሳ ሺህ በላይ ሰዎች ተፈናቀሉ ምግብ ያላገኙ ህፃናት፣ ነፍሰጡር ሴቶችና በእድሜ የገፉ ሰዎች ዝናብ በሚያስገባ ጣራ ስርና በጠባብ ቤት ታጉረው እንደሚገኙም ተመልክቷል። በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በመጋቢት ወር በተነሳው ግጭት ህይወታቸውን አጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ግጭቶቹን አውግዘው ግጭቶቹን ያነሳሱና የተሳተፉ አካላትን ወደ ፍትህ እንደሚያቀርቡ ቃል ገብተው የነበረ ሲሆን በዚህ ሳምንት በደቡብ እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል በግጭቶች ከመሳተፍ ጋር በተያያዘ ስምንት መቶ ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ ተገልጿል። በዚህ ዓመት በብሔር ግጭትና ከተፈጥሮ አደጋ ጋር በተያያዘ ከሁለት ሚሊዮን ህዝብ በላይ መፈናቀሉ ተገልጿል።
news-52909601
https://www.bbc.com/amharic/news-52909601
ኮሮናቫይረስ፡ ደጁን ለረገጡ ሁሉ ቫይረስ ያደለው የሩሲያው ሆስፒታል
ወርሃ ሚያዚያ መግቢያ በሩሲያዋ ሴይንት ፒተርስበርግ በሚገኝ የአጥንት ሆስፒታል አንድ ታካሚ የሳንባ ምች ተገኘበት። የበሽተኛው የኮሮናቫይረስ ውጤት ሲመጣ ቫይረሱ እንዳለበት ተረጋገጠ። ይሄኔ ነው ሆስፒታል ውስጥ ያሉ ሁሉ ተለይተው እንዲቆዩ የተደረገው።
ከ700 በላይ የሕክምና ባለሙያዎች ለሚቀጥሉት 35 ቀናት ከማንም ጋር ሳይገናኙ መቆየት ነበረባቸው። ሁኔታው ዳይመንድ ፕሪንሰስ ከተሰኘችው መርከብ ጋር ተመሳሳይነት አለው። ኮቪድ-19 ገና በመስፋፋት ላይ ሳለ ይህች መርከብ ወደ ጃፓን ወደብ ትጠጋለች። ታድያ መርከቧ በኮቪድ-19 ተበክላ ኖሯል። መርከቧ ላይ የነበሩ ሰዎች ምርመራ ሲደርግላቸው አብዛኛዎቹ ቫይረሱ ተገኘባቸው። ከእነዚህ መካከል 9 ሰዎች መሞታቸው አይዘነጋም። የሩስያው ሆስፒታል ዕጣ ፈንታም ተመሳሳይ ሆኗል። ምርመራ የተደረገላቸው ሁሉ ውጤታቸው 'ፖዘቲቭ' ነው። እስካሁን ቢያንስ ሁለት የሕክምና ባለሙያዎችና ሁለት በሽተኞች ሞተዋል። የከተማይቱ አስተዳደር ሙሉ መረጃ ስላላወጣ ቁጥሮች ከውስጥ አዋቂ የተገኙ ናቸው። አብዛኛዎቹ ታሪካቸውን ያካፈሉት በማሕበራዊ ድር-አምባዎች ነው። ከእነዚህ መካከል ሁለቱ ለቢቢሲ ሩሲያ ክፍል ድምፃቸውን ሰጥተዋል። ሆስፒታሉ ጥንታዊ ነው። በግሪጎሪ አቆጣጠር 1906 ነው የተገነባው። ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች 'ሪፈር' የተፃፈላቸው በሽተኞች ናቸው የሚመጡት። ወረፋ ማግኘት ቀላል አይደለም። የወራት ቀጠሮ ማግኘት መታደል ነው። ሐኪሞች አጥንት ሰብረው፤ አጥንት ጠግነው፤ ቤት ሂዱና በአጥሚት ደግፉት የሚሉበት የታወቀ ሆስፒታል። ሆስፒታሉ አንድ ሰው በኮሮናቫይረስ ተይዞብኛል ብሎ መግለጫ ሲያወጣ ሩሲያውያን ከቫይረሱ ሽሽት ቤታቸው መሽገው ነበር። «መጀመሪያ አንድ ሰው ሳል እንዳለበት ተነገረን። ነገር ግን ኮቪድ-19 ይሁን አይሁን አልታወቀም ነበር። ለማንኛውም ጭምብል አጥልቁ ተባልን። መድኃኒት ቤት የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ በማጣታችን ፋሻ [ባንዴጅ] ሁላ ተጠቅመናል» ትላለች በሆስፒታሉ ሕክምና እያገኘች ያለችው አይሪና። ሌላኛዋ ታካሚ ኔድዛዳ ከሁለት ዓመት ጥበቃ በኋላ የረገጠችው ሆስፒታል መድኃኒት ሳይሆን ቫይረስ አድሏታል። ለመጣችበት በሽታ ሕክምና ከማግኘቷ በፊት ወደ ኮቪድ-19 ታካሚዎች ረድፍ ገብታለች። «ስመጣ ጤናማ ነበርኩ። ነገር ግን አሁን ቫይረሱ አለብኝ። የጠናባቸው ሰዎች ወደ ሌሎች ሆስፒታሎች እየተወሰዱ ነው» ስትል ፅፋለች። ሆስፒታሉ በሩን ሲዘጋ 474 ታካሚዎችና 239 የህክምና ባለሙያዎች ግቢው ውስጥ ነበሩ። በሚቀጥለው ቀን ዶክተሮችና ነርሶች ወደ ለይቶ ማቆያ ስለሚገቡ ቤታቸው ሄደው የሚያስፈልጋቸውን ጭነው እንዲመጡ ተነገራቸው። ታካሚዎች ግን ከግቢው ንቅንቅ እንዲሉ አልተፈቀደላቸውም። አንድ ዶክተር ሁኔታውን ሲገልፀው 'ሰዉ ለአገርህ እወቅ የመጣ ነበር የሚመስለው' ይላል። ሁሉም ሻንጣውን ሸክፎ ሆስፒታሉ ግቢ ተገኘ። አብዛኛዎቹ ታካሚዎች ከቀዶ-ጥገና ሕክምና በማገገም ላይ የነበሩ ናቸው። የተቀሩት ደግሞ በቀጠሯቸው መሠረት ሕክምና ሊደርግላቸው የታሰቡ ናቸው። ቫይረሱ በፍጥነት እንዳይሰራጭ በማሰብ የሆስፒታሉ ማጤዣ እንዲዘጋ ተደረገ። ለበሽተኞች ምግብ የሚቀርብላቸው ያረፉበት ክፍል ደጃፍ ነው። ነገር ግን ሆስፒታሉ ለኮሮናቫይረስ የተዘጋጀ አይመስልም። በተለይ ደግሞ የመከላከያ ቁሶች እጥረት ትልቁ ፈተና ነበር። ነገሮች መስተካከል ሲጀምሩ ቁሶችም ሲሟሉ ግን ቫይረሱ ሁሉንም አዳርሶ ነበር። ሆስፒታሉ የሕክምናም ሆነ የመከላከያ ቁሶች ያገኘው ከተዘጋ ከ10 ቀናት በኋላ ነበር። 20 በመቶ የሚሆኑ በሆስፒታሉ የነበሩ ታካሚዎች ሕመሙ ሲፀናባቸው ወደ ሌላ ሆስፒታል እንዲወሰዱ ተደርገዋል አጥንት ሰብሮ የሚጠግነው፤ አከርካሪ የሚያቃናው ሆስፒታል ኮሮናቫይረስ ፈተነው። ከዚህም ከዚያም ሰው ያስላል፣ የትኩሳቱ እንፋሎት ከሩቅ ይታያል። አብዛኛዎቹ የበሽታውን ምልክት ያሳዩት በመጀመሪያው የለይቶ መቆየት ሳምንት ነበር። የናዴዝዳ ጓደኛም ይህ ነው ያጋጠመው። ከዚያም በሽታው ሲፀናበት ወደ ሌላ ሆስፒታል ተወሰደ። ከቀናት በኋላ ጓደኛዋ መሞቱን ሰማች። ነገር ግን የሆስፒታሉ ሐኪሞች የሚችሉት አድርገዋል። ለዚህም ከብዙዎች ምስጋና ተችሯቸዋል። ባለሙያዎቹ ከኪሳቸው አውጥተው የማጠቢያ ማሽን በመግዛት የታካሚዎችን ልብስ ያጥቡ ነበር። የሆስፒታሉ ነርስ የሆነች ግለሰብ ዩቲዩብ ላይ ያሉበትን ሀኔታ የሚያሳይ ቪድዮ ለጠፈች። አምስት ጊዜ ተመርምራ ውጤቷ እንዳልመጣና የረሃብ አድማ እንደመታች አሳወቀች። ቪድዮው አሁን ከዩቲዩብ እንዲወርድ ቢደረግም ሁኔታው በጊዜው ሩስያውያንን አስደንግጦ ነበር። ከዚህ ቪድዮ መለቀቅ በኋላ ነው ሆስፒታሉ የኮሮናቫይረስ ማከሚያ ሥፍራና ከቫይረሰ ነፃ የሆነ ክፍል የተዘጋጀለት። ሆስፒታሉ እንዲዘጋ መታዘዙ ከመጀመሪያው ስህተት ነበር የሚሉ በርካቶች ናቸው። ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የሕክምና ባለሙያዎች ለቢቢሲ የሚናገሩትም ይህንኑ ነው። አልፎም የምርመራ ጊዜው መዘግየት ለችግሩ መባባስ ትልቅ አስተዋፅዖ ነበረው። ቢቢሲ በሆስፒታሉ ውስጥ ከነበሩ ሰዎች ምን ያክሉ እንደሞቱ ትክክለኛ ቁጥር እንዲሰጠው የሆስፒታሉን ኃላፊዎች ቢጠይቅም ምላሽ አላገኘም።
news-53753308
https://www.bbc.com/amharic/news-53753308
ወላይታ ፡ በወላይታው አለመረጋጋት የሞቱ ሰዎች ቁጥር 16 መድረሱ ተገለፀ
በወላይታ ዞን እሁድ ዕለት በዞኑ ውስጥ ያሉ ከተፍተኛ አስተዳዳሪዎችና ሌሎች ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ተከትሎ በተቀሰቀሰ አለመረጋጋት እስከ ትናንት ድረስ 16 ሰዎች መሞታቸው ተገለፀ።
ይህንንም በተመለከተ ከተለያዩ ሆስፒታሎች መረጃዎችን ማጠናቀራቸውን የሚናገሩት የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ሪፈራል ሆስፒታል (ኦቶና ሆስፒታል) መምህርና የአጥንት ክፍል ሐኪም የሆኑት ዶ/ር መብራቱ ጪሻ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ዶ/ር መብራቱ መረጃዎቹን ከሚያስተምሩበትና ከሚሰሩበት ኦቶና ሆስፒታል፣ ከወላይታ ሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል፣ ቦዲቲ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል እና ቦዲቲ ጤና ጣብያ እንዲሁም ከነዋሪዎች ማጠናቀራቸውን በመግለጽ፤ በዞኑ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 16 መድረሱን ለቢቢሲ አረጋግጠዋል። ዶ/ር መብራቱ ጪሻ እንደሚሉት በነበረው አለመረጋጋት ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ሕክምና ተቋማት የመጡት 49 ሰዎች ላይ ጉዳት የደረሰው በጥይት ተመትተው ነው ይላሉ። ከእሁድ ማታ ጀምሮ በጥይት ተመትተው ወደ ሆስፒታል ከመጡት መካከል ዘጠኝ ሰዎች ሞተዋል። በተጨማሪም 30 ሰዎች ሕክምና አግኝተው ወደ ቤታቸው መመለሳቸውን ሦስቱ ደግሞ በሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል በጽኑ ሕክምና ክፍል መሆናቸውን ለቢቢሲ አረጋግጠዋል። በሆስፒታል ከሞቱት በተጨማሪም ወደ ሆስፒታል ሳይመጡ በውጭ ህይወታቸው ያለፉ ሰዎች እንዳሉም ዶክተሩ ያስረዳሉ። ከእሁድ ማታ ጀምሮ በነበረው አለመረጋጋት ግጭቱ በበረታባት በቦዲቲ ከተማ የሞቱት ሰባት መሆናቸውን የገለፁት ዶ/ር መብራቱ፤ ወደ ሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል በአጠቃላይ 21 ሰዎች ተጎድተው የመጡ ሲሆን ሆስፒታሉ እንደደረሱ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ሁለት መሆኑን ተናግረዋል። በሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል በአሁኑ ሰዓት ሦስት ሰዎች በጽኑ ሕሙማን ክፍል እንደሚገኙ የሚናገሩት ዶ/ር መብራቱ ከእነዚህ መካከል ሁለቱ ክፉኛ የተጎዱ መሆናቸውን አመልክተዋል። ጉዳት ደርሶባቸው ከመጡት መካከል 16 ሰዎች የተለያየ ሕክምና አግኝተው ወደቤታቸው መሄዳቸውን ለቢቢሲ አረጋግጠዋል። ወደ ኦቶና ሆስፒታል በግጭቱ ተጎድተው የገቡት አራት መሆናቸውን ዶ/ር መብራቱ ቢገልፁም ሁለት ሰዎች ብቻ እግራቸው ላይ በጥይት ቆስለው መምጣታቸውን የሆስፒታሉ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ጌታሁን ሞላ ለቢቢሲ ተናግረዋል። በዞኑ በነበረው አለመረጋጋት ከሞቱት ሰዎች መካከል ሰባቱ ሆስፒታል አለመምጣታቸውን የጠቀሱት ዶ/ር መብራቱ ከእነሱም ውስጥ ሦስቱ በተለምዶ ማዘጋጃ ሰፈር የሚባለው አካባቢ፣ ሁለት ማዕዶት ሰፈር፣ ኦቶና ሆስፒታል መሄጃ ላይ 21 ማዞሪያ በመባል የሚታወቀው ሰፈር ደግሞ ሁለቱ መሞታቸውን አረጋግጠዋል። የተቀሩት ደግሞ ሁለቱ ወደ ሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል ለሕክምና እንደመጡ የሞቱ ሲሆን ሰባቱ ሰዎች ደግሞ በቦዲቲ ከተማ በደረሰባቸው ጉዳት ሳቢያ ወደ በሕክምና ተቋማት ከተወሰዱ በኋላ ህይወታቸው ያለፈ መሆኑን ገልጸዋል። እንደ ዶ/ር መብራቱ ገለፃ ከሆነ በግጭቱ የተጎዱ ሰዎች ወደ ኦቶና ሆስፒታል ያልሄዱበት ምክንያት የትራንስፖርት አገልግሎት ባለመኖሩ ነው ቢሉም ዶ/ር ጌታሁን በበኩላቸው ሆስፒታሉ ከኮሮናቫይረስ መከላከል ጋር በተያያዘ እየሰራ የነበረው ሥራ በመኖሩ ተጎጂዎችን መቀበል አለመቻላቸውን ተናግረዋል። ዶ/ር መብራቱ ኦቶና ሆስፒታል ተጎድተው ከመጡ አራት ሰዎች መካከል አንዱ የአስራ ሁለት ዓመት ልጅ መሆኑን በመጥቀስ እጁ ላይ በዱላ ተመትቶ ስብራት ደርሶበት መግባቱን ጨምረው አብራርተዋል። ቢቢሲ በዞኑ ስለተከሰተው አለመረጋጋትና ጉዳት ስለደረሰባቸው ሰዎች ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት ለደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ተደጋጋሚ የስልክ ጥሪ ቢያደርግም ምላሽ ለማግኘት አልቻልም። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር የሆኑት አቶ እርስቱ ይርዳው በወላይታ ዞን ስለተከሰተው አለመረጋጋት ለደቡብ መገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ ላይ የአምስት ሰዎች ህይወት ማለፉንና የአካል ጉዳት መድረሱን ተናግረው ለሞቱት የተሰማቸውን ሃዘን ገልጸዋል። በሶዶ አሁንም የሰዎች እንቅስቃሴ የተገደበ መሆኑን የሚናገሩት የከተማዋ ነዋሪዎች ንግድ ቤቶች፣ ባንክ ቤቶች፣ የመንግሥት ቢሮዎች ዝግ መሆናቸውንና የትራንስፖርት እንቅስቃሴም አለመኖሩን ለቢቢሲ ተናግረዋል። ወደ ተለያዩ አካባቢዎች የሚወስዱ የከተማዋ መንገዶችም ዝግ መሆናቸውን ለቢቢሲ ጨምረው አረጋግጠዋል። በቦዲቲ አሁንም ውጥረት መኖሩን የሚናገሩት የከተማዋ ነዋሪዎች ልክ እንደ ሶዶ ሁሉ ከተማዋ እንቅስቃሴ አልባ መሆኗን ለቢቢሲ ተናግረዋል። በትናንትናው ዕለት በወረዳና በዞን ደረጃ ያሉ አስተዳዳሪዎች ሕዝቡን እንዲያረጋጉ ከክልልና ከፌደራል የመጡ አመራሮች ጋር ጥያቄ የቀረበበት ስብሰባ መካሄዱን የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ የሥራ አስፈፃሚ አባል የሆኑት አቶ ማቴዎስ ባልቻ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ሆኖም በዋነኝነት የዞኑ አመራሮች፣ የሕግ ባለሙያዎችና ከሃያ በላይ ሰዎች በታሰሩበትና መንግሥት ያላግባብ ኃይል በመጠቀም የብዙዎች ህይወት በጠፋበት ሁኔታ ስብሰባውን ማካሄድ አንችልም በሚል ያለውጤት መበተኑን አንድ ተሳታፊን ዋቢ አድርገው አቶ ማቴዎስ ይናገራሉ። "አመራሮቹ ሕግን ባልተከተለ መንገድ ተከበው በወከባ ነው የታሰሩት፤ የሚያስጠይቅ ነገር ቢኖር እንኳን ሕግን በተከተለ ሁኔታ መሆን ነበረበት። ለምንስ የዚህን ያህል ሰው ህይወት ጠፋ? ትዕዛዝ የሰጠው አካልስ ማነው?" የሚሉ ጥያቄዎች መነሳታቸውን አቶ ማቴዎስ ያስረዳሉ። የታሰሩ አመራሮች ከተፈቱና እንዲሁም በፀጥታ ኃይል የተገደሉ ሰዎችን በተመለከተ ነፃና ገለልተኛ አካል ተቋቁሞ ትዕዛዝ ስለሰጠው አካልና ኃላፊነት የሚወስድ አካል መታወቅ ለመግባባቱና ለስብሰባውም እንደ ቅድመ ሁኔታዎች መቀመጣቸውን አቶ ማቴዎስ ያስረዳሉ። ከዚህም በተጨማሪ የታሰሩ አመራሮች ከህወሓትና ኦነግ ሸኔ ጋር ይዶልቱ ነበር ብለው የክልሉ ፖሊስ መናገራቸው አግባብነት የሌለው ነው በማለት ብዙዎች በስብሰባው ላይ ሃሳባቸውን አንፀባርቀዋል ብለዋል። በዚህም መሰረት ስብሰባው ለሌላ ጊዜ እንዲካሄድ በሚልም በቀጠሮ ተለያይተዋል። በትናንትናው ዕለት ከታሰሩት ውስጥ የአገር ሽማግሌዎችን የወከሉት አቶ ሰይፉ ለታና አቶ ዳንኤል ደሳለኝ የተፈቱ ሲሆን ሌሎች እስረኞችንም የሐይማኖት አባቶች መጎብኘታቸውንም አቶ ማቴዎስ ይናገራሉ። እስረኞቹ በደህና ሁኔታ ላይ የሚገኙ መሆናቸውን ለሐይማኖት አባቶቹ የገለፁላቸው ሲሆን ምግብና ውሃም ቀርቦላቸዋል፤ በሩቅም ሆነው ጎብኚዎችን ማየት እንደቻሉም እስረኞቹ መናገራቸውን አንድ አባት ለአቶ ማቴዎስ ነግረዋቸዋል። ከዚህም በተጨማሪ እስረኞቹ በአሁኑ ወቅት ፍርድ ቤት መቅረባቸውንም አቶ ማቴዎስ ለቢቢሲ ተናግረዋል። በሶዶም ሆነ በቦዲቲ አንፃራዊ ሰላም ቢኖርም የንግድም ሆነ የትራንስፖርት እንቅስቃሴዎች በአሁኑ ውስጥ ቀጥ እንዳሉ ናቸው። በትናንትናው ዕለት በተለያዩ ወረዳዎች እንዲሁም በዛሬው ዕለት ደግሞ ኪንዶ ኮይሻ በምትባል ወረዳ እስረኞች ይፈቱ፣ ለተገደሉ ሰዎች ኃላፊነት የሚወስድ አካል እንዲጠየቅና ሌሎችም ጥያቄዎችን የሚጠይቁ ሰላማዊ ሰልፎች መደረጋቸውንም አቶ ማቴዎስ ለቢቢሲ አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ወላይታ ዞን ውስጥ ስለተከሰተው አለመረጋጋትና የጸጥታ ኃይሎች ስለወሰዱት እርምጃ መግለጫ አውጥቶ ነበር። በዚህም በዞን አንዳንድ ከተሞች የፀጥታ ኃይሎች ተቃውሞ ባሰሙ ሰዎች ላይ የወሰዱት እርምጃ "ተመጣጣኝነት አጠያያቂ" መሆኑን ገልጾ "የፀጥታ ኃይሎች ሰላማዊ ሰልፈኞችን በሚቆጣጠሩበት ወቅት የሞት አደጋን የሚያስከትል የኃይል እርምጃ ከመውሰድ ሊቆጠቡ ይገባል" ብሏል።
news-46963272
https://www.bbc.com/amharic/news-46963272
ዋትስአፕ ከአምስት ጊዜ በላይ መልዕክት ማጋራት አገደ
ዋትስአፕ ተጠቃሚዎች አንድን መልዕክት ከአምስት ጊዜ በላይ እንዳያጋሩ አገደ። ከዚህ ቀደም ተጠቃሚዎች የጽሁፍ መልዕክት ወይም ምስል በአንድ ጊዜ ለ20 ሰዎች ማጋራት ይችሉ ነበር።
በዋትስአፕ አንድን መልዕክት ከአምስት ጊዜ በላይ መላክ አይቻልም ዋትስአፕ ከዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው የሀሰተኛ ዜና ስርጭትን ለመግታት እንደሆነ ተገልጿል። • 'ዋትስአፕ' በቻይና እክል ገጥሞታል • በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት አንዳንድ ስልኮች ዋትስአፕን አያስጠቅሙም • የውጭ ሀገራት ዜጎች በደቡብ አፍሪካዋ ሶዌቶ ጥቃትን እየሸሹ ነው የዋትስአፕ ተጠቃሚዎች ከአምስት ጊዜ በላይ መልዕክት እንዳያጋሩ የሚያግውን አሰራር ከስድስት ወር በፊት በሕንድ መተግበር ጀምሯል። ከዚህ ቀደም ሕንድ ውስጥ በዋትስአፕ በተሰራጨ ሀሰተኛ ዜና ምክንያት የመንጋ ጥቃት መከሰቱና ብዙዎች መጎዳታቸውም ይታወሳል። አንድ ሰው የሚደርሰውን መልዕክት አምስት ጊዜ ካጋራ በኋላ እያንዳንዶቹ ተቀባዮቹም አምስት ጊዜ መልዕክቱን ሊያጋራቱ ይችላሉ። ሆኖም ስርጭቱ ከቀደመው ጊዜ የተሻለ እንደሚገደብ የዋትስአፕ ቃል አቀባይ ተናግረዋል። አደገኛ ይዘት ያላቸው መልዕክቶች ስርጭትን ለመግታት ለወደፊት ሌሎች ተጨማሪ እርምጃዎች እንደሚወሰዱም ቃል አቀባዩ አክለዋል። በአንድ የዋትስአፕ ቡድን ውስጥ 265 ተጠቃሚዎች መግባት ይችላሉ። ስለዚህ አንድ ተጠቃሚ የሚልከው መልዕክት ቢበዛ ለ1,280 ሰዎች ይደርሳል። ቀድሞ ግን 5,120 ሰዎች ይደርስ ነበር። ዋትስአፕና ፌስቡክ ሀሰተኛ ዜናና ፕሮፖጋንዳ በመንዛት ስማቸው እየተብጠለጠለ ነው። ባለፈው ሳምንት ፌስቡክ 500 ሀሰተኛ ዜና የሚያሰራጩ ገጾችን ማገዱ ይታወሳል።
news-53956715
https://www.bbc.com/amharic/news-53956715
ቻድዊክ ቦስማን፡ የብላክ ፓንተር ፊልም ኮከብ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ
ብላክ ፓንተር በተሰኘው ፊልም ላይ በነበረው ተሳትፎ በስፋት የሚታወቀው አሜሪካዊው ተዋናይ ቻድዊክ ቦስማን በ43 ዓመቱ በካንሰር ህመም አረፈ።
ከሁለት ዓመት በፊት የወጣው ብላክ ፓንተር ፊልም ድንበር ሳይለይ በርካቶችን አስደምሟል። በተለይ ለአፍሪካዊያንና ጥቁሮች ክብርን ያላበሰ ነበር ማለት ይቻላል። ታዲያ ዛሬ በዚያ ፊልም ላይ በቴክኖሎጂ የዘመነ ከተማ ሆኖ በተሳለው ልብ-ወለዳዊ 'ዋካንዳ' መሪ በመሆን የተወነው እውቅ የፊልም ሰው ሕይወቱ ማለፉ ተሰምቷል። ቻድዊክ ሕይወቱ ያለፈው በሎስ አንጀለስ መኖሪያ ቤቱ ባለቤቱና ቤተሰቦቹ ከጎኑ ሳይለዩት መሆኑን በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የተሰራጨው መግለጫ ያመለክታል። ተዋናዩ ከአራት ዓመታት በፊት የአንጀት ካንሰር ሕክምና ሲያደርግ የነበረ ቢሆንም ይህን ግን በአደባባይ ተናግሮ አያውቅም። ደህና ነኝ ነበር የሚለው። አሁን ግን በዚሁ በሽታ ሕይወቱ ማለፉ ተገልጿል። የሞቱ ዜናም አድናቂዎቹንና የፊልም ቤተሰቦችን አስደንግጧል። ዳሬክተር ጆርዳን ፒሌም " የሞቱ ዜና በጣም አሳዛኝ ነው" ብሏል። "ቻድዊክ አልሸነፍ ባይ ነበር፤ ባለፈባቸው አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ሆኖም የምትወዷቸውን በርካታ ፊልሞች ለእናንተ አቅርቧል" ያሉት ደግሞ ቤተሰቦቹ ናቸው። "ቻድዊክ 21 ብሪጅስ፣ ዳ 5 ብለድስ፣ ኦገስት ዊለሶንስ ማ ሬኒይስ እና በርካታ ፊልሞችን ለተመልካቾች አድርሷል። እነዚህ ሁሉ የተቀረፁት በበርካታ ቀዶ ሕክምና እና ኬሞቴራፒ እየተከታተለ በነበረባቸው ፈታኝ ጊዜያት ነበር። በብላክ ፓንተር ፊልሙ ንጉሥ ቲ ቻላን እውን ስላደረገም ታላቅ ክብር ነው" ብለዋል ቤተሰቦቹ በሰጡት መግለጫ። ቻድዊክ እውነተኛ ሰዎችን ወክሎ በመጫዎትም ይታወቃል። የቤዝቦል ተጫዋቹን ጃኬ ሮቢንሰንን እንዲሁም የሶል ሙዚቃ አቀንቃኙን ጀምስ ብራውንን በመወከል ተውኗል። በርካቶች ግን ከሁለት ዓመታት በፊት በወጣው ብላክ ፓንተር ፊልሙ ይበልጥ ያስታውሱታል። አፍሪካዊያን በቴክኖሎጂ በዘመነ ምድር ላይ ሲኖሩ የሚያሳየው ብላክ ፓንተር ፊልም ላይ የዋካንዳ ገዢ ሆኖ ነበር የተወነው። በዚህ ፊልም ላይ በአተዋወን ብቃቱ ኮከብ ሆኖ የተመረጠ ሲሆን በዓለም አቀፍ ሲኒማ ከ1.3 ቢሊየን ዶላር በላይ ሽልማት አሸናፊም ሆኖ ነበር። ባለፈው ዓመት ቻድዊክ "ፊልሙ ወጣትነት፣ ባለተሰጥኦን እና ጥቁር የመሆንን ትርጉም የለወጠ ነው" ብሎ ነበር። ብላክ ፓንተር ፊልም በምርጥ ምስል ዘርፍ በኦስካር የታጨ የመጀመሪያው ፊልም ነው። ቻድዊክ በካፒቴን አሜሪካ፣ ሲቪል ዋር፣ አቬንጀርስ በሚሉ ፊልሞችም ላይ የትወና ብቃቱን አሳይቷል።
news-53040274
https://www.bbc.com/amharic/news-53040274
በለንደን ሃውልት እንጠብቃለን በሚሉና በፖሊስ መካከል በተከሰተ ግጭት ከ100 በላይ ሰዎች ታሰሩ
ቅዳሜ ዕለት በለንደን በተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ የተቀሰቀሰውን ግጭት ተከትሎ ከ100 በላይ ሰዎች መታሰራቸውን የከተማዋ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
በወቅቱ ተቃዋሚዎች በፖሊስ ላይ ጥቃት የፈጸሙ ሲሆን ከጥቃት አድራሾቹ አንዳንዶቹ የቀኝ አክራሪነት አቀንቃኞች ናቸው ተብሏል፡፡ ግጭቱ የተቀሰቀሰው በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የቸርችል ሃውልትን ለመጠበቅ ከተሰባሰቡ በኋላ ነው፡፡ በርካታ የቀኝ አክራሪ ቡድኖች የቀድሞውን የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዊንስተን ቸርችል ሃውልትን ከመገርሰስ ለማዳን ወደ ለንደን የመጡ ሲሆን አብዛኛዎቹም ነጭ ወንዶች እንደሆኑም ተነግሯል። ግለሰሰቦቹ የዊንስተን ቸርችል ሃውልትን ከበው በመጠበቅ ላይ ነበሩ። እነዚህ ተቃዋሚዎች ከፖሊስ ጋር በፈጠሩት ግጭት ስድስት የሚሆኑ ፖሊሶች ጉዳት ደርሶባቸዋል። ዊንስተን ቸርችል በነጭ እንግሊዛውያን ዘንድ አገሪቱን ለሁለተኛ ዓለም ጦርነት ድል ያበቃ መሪ እንዲሁም ድንቅ መሪ፣ ፀሐፊና ተናጋሪ ቢሉትም ከነጭ ዘር ውጪ በነበረው ንቀት አወዛጋቢም ሆኗል። በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር የዘር አከፋፈል መሰረት ከላይ የሚቀመጡት ነጭ ፕሮቴስታንቶች፣ በመቀጠል ነጭ ካቶሊኮች ከዚያም ከአፍሪካውያን በልጠው ህንዳውያን ናቸው። አፍሪካውያን የመጨረሻውን ቦታ ሲይዙም ከሰውም ያነሱ ናቸው ብሎ ያምን ነበር። ጠቅላይ ሚኒስተር ቦሪስ ጆንሰን ድርጊቱን "የዘረኝነት ልክ ያለፈ ቁጣ በመንገዳችን ላይ ቦታ የለውም" ብለዋል፡፡ ከሦስት ዓመታት በፊት በዌስትሚኒስተር ጥቃት በተገደለው በፒሲ ኬት ፓልመር መታሰቢያ ሃውልት ስር አንድ ግለሰብ ሽንቱን ሲሸና መታየቱን ተከትሎም ምርመራዎች እየተደረጉ ነው፡፡ የአገር ውስጥ ሚኒስትር ፕሪቲ ፓቴልም በመታሰቢያ ሃውልቱ ላይ የተፈጸመውን ድርጊት "በጣም አሳፋሪ" ሲሉ ኮንነውታል፡፡ የከተማዋ ፖሊስ ኮማንደር ባስ ጃቪድ በበኩላቸው፤ "አንድ ግለሰብ በመታሰቢያ ሃውልቱ ስር ሽንቱን ሲሸና የሚያሳይና በጣም አጸያፊ የሆነ ምስል በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲዘዋወር ተመልክተናል፤ ምርመራ የጀመርነውም ወዲያውኑ ነው፡፡ ማስረጃዎቹን ከሰበሰብን በኋላ ተገቢውን እርምጃ እንወስዳለን" ብለዋል፡፡ ከሦስት ዓመታት በፊት ፒሲ ፓልመር በዌስትሚኒስተር ደጅ ላይ በካሊድ ማሱድ በተፈጸመ የሽብር ጥቃት ተጎድተው ሳለ የመጀመሪያ ሕክምና እርዳታ የሰጧቸው የፓርላማ አባል ቶቢያስ ኢልውድም፤ በመታሰቢያ ሃውልታቸው ላይ የተፈጸመው ድርጊት አጸያፊ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ "ግለሰቡ ሲያደርግ የነበረውን ያውቀዋል፤ በመሆኑም ራሱን በማጋለጥ ይቅርታ ሊጠይቅ ይገባልም" ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል፡፡ ቅዳሜ እለት በለንደንና በሌሎች የአገሪቷ ክፍሎች ሰላማዊ የሆኑ ጸረ -ዘረኝነት ተቃውሞዎችም ተካሂደዋል፡፡ ከሰሞኑም በዩናይትድ ኪንግደም መዲና በሚገኘው የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ዊንስተን ቸርችል በተቃዋሚዎች ዘንድ ዘረኛ የሚል ጽሁፍ ተጽፎበት ታይቷል፡፡ የጥቁር አሜሪካዊውን ጆርጅ ፍሎይድ በነጭ ፖሊስ እጅ መሞቱን ተከትሎ የተቀጣጠለው ተቃውሞ በምዕራባዊን ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጣቸው አሳሾች እና ነገሥታት ሃውልቶች እንዲገረሰሱና ተመሳሳይ ድርጊቶች እንዲፈጸሙ አነሳስቷል፡፡ ምንም እንኳን እነዚህ ሰዎች ለምዕራባውያኑ ትልቅ ቢሆኑም በአፍሪካውያንም ሆነ በደቡቡ ዓለም ጭፍጨፋ፣ ዝርፊያና መደፈርን ሌሎች አሳፋሪ ታሪኮችን የፈፀሙ ናቸው።
news-57101748
https://www.bbc.com/amharic/news-57101748
ፕሬዝዳንት ባይደን ትራምፕ ያፀደቋቸውን ሕጎች ሰረዙ
ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጸድቀው የነበሩ የተወሰኑ አዋጆችን ሰረዙ።
ከሰረዟቸው አዋጆች መካከል ሐውልቶችን የሚያወድሙ ላይ ቅጣት የሚጥለው አዋጅ ይገኝበታል። ትራምፕ ይህንን አዋጅ ያጸደቁት ባለፈው ዓመት ማሕበራዊ ፍትህን የሚጠይቁ ተቃዋሚ ሰልፈኞች ሐውልቶችን ማበላሸት ወይንም ደግሞ መጣል ከጀመሩ በኋላ ነበር። ባይደን ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ጀግኖችን ለማሰብ በቅርጻ ቅርጽ የተሞላ መናፈሻ ለማቆም ያቀረቡትን እቅድ አብረው ውድቅ አድርገውታል። ከዚህም በተጨማሪ ውድቅ ካተደረጉ አዋጆች መካከል በ2019 የጤና መድን መክፈል የማይችሉ ስደተኞች ወደ አገር እንዳይገቡ የሚያግደው እና እኤአ በ2019 የጸደቀው ሕግ ይገኝበታል። ትራምፕ በ2020 ሰኔ ወር ላይ የፌደራል መንግሥቱ "ማንኛውም ግለሰብ ሐውልቶችን የሚያወድም፣ የሚዘርፍ፣ የሚያራክስ" ከሆነ "ሙሉ በሙሉ እንዲቀጣ " የሚል አዋጅ አጽድቀው ነበር። ይህ አዋጅ የጸደቀው የግራ ክንፍ አክራሪዎች፣ ሰልፈኞች እና መሳሪያ ያነገቱ ነውጠኞች ሪፐብሊካኑን ፕሬዝዳንትን በመደገፍ በምረጡኝ ቅስሳ ዘመቻ ወቅት ስማቸው በገነነበት ወቅት ነበር። ይህ አዋጅ ሲጸድቅ የጆርጅ ፍሎይድን መገደል በመቃወም በርካታ ተቃዋሚ ሰልፎች የተለያዩ ጉዳዮችን ለመዘከር የቆሙ ሐውልቶችን ማጥቃታቸውን ተከትሎ ነበር። ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አርብ ከሰአት ከሰረዟቸው ሕጎች መካከል በአሜሪካ ታሪክ ጉልህ ስፍራ ያላቸውን ሰዎችን ቅርጻ ቅርጽ በመስራት መናፈሻ ለመገንባት የሚያስችለው ሕግ ይገኝበታል። በዚህ መናፈሻ ውስጥ እንዲካተቱ በማለት ፕሬዝዳንት ትራምፕ ራሳቸው የመረጧቸውታዋቂ ሰዎች አሉ። ከእነዚህም መካከል ድምጻዊቷ ዊትኒ ሂዊስተን፣ የቅርጫት ኳስ ተጫዋቹ ኮቤ ብያንት፣ ወንጌላዊው ቢሊ ግርሃም እና ሌሎችም ይገኙበታል። ይህ መናፈሻ የት እንደሚገነባ ገና ያልተመረጠ ሲሆን ኮንግረስም ቢሆን ድጋፉን አልሰጠውም ነበር። ባይደን ከሰረዟቸው ሕጎች መካከል ትራምፕ በ2019 ጥቅምት ወር ላይ ካፀደቋቸው ሕጎች መካከል ስደተኞች ወደ አሜሪካ ከመግባታቸው በፊት የሕክምና ወጪያቸውን መሸፈን እንደሚችሉ ማረጋገጥ አለባቸው የሚለውና ወዲያውኑ በፌደራል ዳኛ የታገደው ሕግ ይገኝበታል። "አስተዳደሬ ጥራት ያለው እና ለሁሉም ተደራሽ የሚሆን የጤና ክብካቤ ስርዓት ለመዘርጋት ይሰራል" ያሉት ባይደን ይህ ደግሞ የአሜሪካ ዜጋ ላልሆኑት ጭምር መሆኑን በመግለጽ አዋጁን ሰርዘውታል። አርብ እለት ባይን ከሰረዟቸው ሕጎች መካከል ትራምፕ ማህበራዊ ሚዲያን ሳንሱር ለማድረግ ያለሙበትን ሕግ እና አሜሪካ ለተለያዩ አገራት የምትደርገው እርዳታ ላይ የአሜሪካ ሕዝብ ለጋስነትን ለማሳየት በሚል እንዲገባ የተጠየቀው አርማ ይገኝበታል።
49108187
https://www.bbc.com/amharic/49108187
በባንግላዲሽ በሐሰተኛ ወሬ ሳቢያ ስምንት ሰው ተገደለ
በባንግላዲሽ "ሕፃናት ሊሰርቁ ነው" በሚል በተነዛ ሐሰተኛ ወሬ ሳቢያ ስምንት ሰዎች በደቦ ጥቃት መሞታቸውን ፖሊስ አስታወቀ።
ሟቾቹ በባንግላዲሽ ዋና ከተማ ደቡባዊ አቅጣጫ በዳካ ድልድይ ለመገንባት ሕፃን በመስዋዕትነት ሊቀርብ ያስፈልጋል ተብሎ በሰፊው መወራቱን ተከትሎ ጥቃቱ እንደተፈፀመባቸው ለማወቅ ተችሏል። ይህ 3 ቢሊየን ዶላር የተመደበለት የድልድይ ግንባታ ፕሮጀክት የሕፃናት ደም ግብር ሊቀርብለት ይገባል የሚል አሉባልታ ሲወራ ነበር። • ከኢንጅነር ስመኘው ሞት በኋላ ህዳሴ ግድብ ምን ላይ ደረሰ? • "አዲስ አበባ የምንወዛገብባት ሳትሆን በጋራ የምንኖርባት ከተማ ናት" ም/ከንቲባ ታከለ ኡማ ከዚህ በኋላ ነው ሕጻናት ሰርቀው ለድልድዩ ግንባታ መስዋዕት ሊያቀርቡ ነው የተባሉ ስምንት ሰዎች ላይ በደቦ ጥቃት የተፈፀመባቸው። የፖሊስ አዛዥ የሆኑት ጃቬድ ፓትዋሪ፣ ዳካ ውስጥ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት በአሰቃቂ ሁኔታ ከተገደሉት መካከል አንዳቸውም በሕፃናት ስርቆት ውስጥ አልተሳተፉም። ከተገደሉት መካከል የሁለት ልጆች እናት የሆነችው ታስሊማ ቤገም የምትገኝበት ሲሆን የ11 ዓመትና የአራት ዓመት ልጆች እንዳሏት ለማወቅ ተችሏል። እንደ ፈረንሳዩ የዜና ወኪል ከሆነ ከዚህች እናት ግድያ ጋር በተያያዘ ስምንት ሰዎች በቀጥታ ተሳታፊነት ተጠርጥረው፣ አምስት ሰዎች ደግሞ ሐሰተኛ ወሬ በማናፈስ በቁጥጥር ስር ውለዋል። ሟቾቹ እነማን ናቸው? ቅዳሜ ዕለት የ42 ዓመቷና የሁለት ልጆች እናት የሆነችውን ቤገምን ከመኖሪያ አቅራቢያዋ በሚገኝ አንድ ትምህርት ቤት በራፍ ላይ 'የልጅ ሌባ' በሚል ቀጥቅጠው ገድለዋታል። ወደ ትምህርት ቤቱ የሄደችው ለልጆቿ ምዝገባ ለመጠየቅ ሲሆን፤ የጥቃቱ አድራሾቹ ግን 'ልጅ ልትሰርቅ ነው' በሚል እንዳጠቋት የአካባቢው ነዋሪዎች ለአንድ ድረ ገፅ ተናግረዋል። • በደቡብ ወሎ እውን የህፃናት ስርቆት አለ? • እንደወጡ የቀሩት ተመራማሪዎች ይህች እናት ስትገደል የተመለከተ መምህር ለድረ ገፁ ሲያስረዳ "ከሰዉ ብዛት አንፃር ምንም ማድረግ አንችልም ነበር " ብሏል። ሌሎች እድሜያቸው በ30ዎቹ ውስጥ የተገመተ ወንድና ሴትም ባለፈው ሐሙስና ቅዳሜ በተለያየ አካባቢ በተመሳሳይ ልጅ ሊሰርቁ ነው በሚል በደረሰባቸው ድብደባ ምክንያት እንደሞቱ ተነግሯል። ወሬው በምን ጀመረ? የአገር ውስጥ መገናኛ ብዙሀን እንደዘገቡት፤ ወሬው መናፈስ የጀመረው በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ሲሆን፤ ከሁለት ሳምንት በፊት ጀምሮ በፌስቡክ እና በዩቲዩብ ላይ በሚለጠፉ ቪዲዮዎች አማካኝነት መሰራጨቱን ያስረዳሉ። በዚህ የሐሰት ወሬ ላይ አንድ ሰው በባንግላዲሽ ሰሜናዊ ግዛት ኔትኦካና ውስጥ ህፃን ልጅ ቀልቶ አንገቱን ይዞ መታየቱን ይጠቅሳል። በፌስ ቡክ ላይ በተሰራጨው ወሬ ሕፃናትን እያገቱ አንገታቸውን የሚቀሉና ለሚገነባው ፓዳማ ድልድይ መስዋዕትነት የሚያቀርቡ ሰዎች በተለያዩ ቦታዎች ተሰማርተዋል ይላል። ቢቢሲ ይህንን ወሬ የሚያሰራጩ የተለያዩ የፌስቡክ ጽሁፎችና ቪዲዮዎችን ተመልክቷል። እሮብ ዕለት የመንግሥት አካላት በሰጡት መግለጫ ላይ እንደገለፁት ይህ ሐሰተኛ ወሬ እየተሰራጨ ያለው ሆን ተብሎ በአገሪቱ ውስጥ አለመረጋጋት ለመፍጠር ነው ብለው ነበር። • በኢትዮጵያ የመንጋ ፍትህ የሰው ህይወት እየቀጠፈ ነው • አምስት ሰዎች ደቡብ ወሎ ውስጥ በደቦ ጥቃት ተገደሉ ፖሊስ ምን እያደረገ ነው? እንደ መንግሥት ኃላፊዎች መግለጫ ከሆነ ይህንን ሐሰተኛ ወሬ የሚያሰራጩ 25 የዩቲዩብ፣ 60 የፌስቡክ፣ 10 ድረ ገፆች ተዘግተዋል። ከዚህ በተጨማሪም ይህንን ሐሰተኛ አሉባልታ ለመቀልበስ መንግሥት በመገናኛ ብዙኀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራሞች እያካሄደና ማህበረሰቡ ምንም አይነት ጥቃት እንዳይፈፅም እያስጠነቀቀ ይገኛል። በገጠሪቱ የአገሪቱ ክፍል ደግሞ መንግሥት የድምፅ ማጉያ ይዞ የወሬውን ሐሰተኝነት ለማስረዳት እየተንቀሳቀሰ ነው። የአገሪቱ መገናኛ ብዙኀን በ2010 በድልድይ ግንባታ ምክንያት ተመሳሳይ የደቦ ጥቃትመመፈፀሙን ዘግበዋል። በቅርቡም ኢትዮጵያ ውስጥ ደቡብ ወሎ አካባቢ ሕፃናት ይሰርቃሉ በሚል አምስት ሰዎች ላይ በተፈፀመ የደቦ ጥቃት መሞታቸውን መዘገባችን ይታወሳል።
news-55937235
https://www.bbc.com/amharic/news-55937235
በኬንያ የማደጎ ህፃናት ላይ ወሲባዊ ጥቃት የፈፀመው አሜሪካዊ በእስር ተቀጣ
በኬንያ የሚገኙ ማደጎ ህፃናት ላይ ወሲባዊ ጥቃት የፈፀመው አሜሪካዊ የ15 አመት እስር ተፈረደበት።
የክርስቲያን ሚሲዮናዊ (መልዕክተኛ) ነኝ የሚለው ግለሰብ ህፃናት ሴቶች ላይ ወሲባዊ ጥቃት በመፈፀም ጥፋተኛ ሆኖ ያገኘው የአሜሪካ ፍርድ ቤት ነው። የ61 አመቱ ግሪጎሪ ዶው ከባለቤቱ ጋር አቋቁሞ የነበረው የህፃናት ማሳደጊያ ከጎሮጎሳውያኑ 2008- 2017 ድረስ አገልግሎት ሲሰጥ ነበር ተብሏል። "ግሪጎሪ በመፅሃፉ ላይ የተጠቀሰው የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡት ተኩላዎች መካከል አንዱ ነው" በማለት የፌደራል ቢሮ ምርመራ (ኤፍቢአይ) ሚካኤል ድሪስኮል ተናግረዋል። ባለፈው አመት ግሪጎሪ የተከሰሰበትን አራት ወንጀሎች ጥፋተኝነቱን አምኗል። በምዕራብ ኬንያ በሚገኝ ቦታ የተቋቋመው የህፃናት ማሳደጊያው ፔንስይልቫኒያ በሚገኝ ቤተ ክርስቲያንም በከፊል የገንዘብ ድጎማ ይደረግለት ነበር ተብሏል። ግለሰቡ ላይ ምርመራ የተጀመረበት በአሜሪካዋ ኑሮዋን ያደረገች ኬንያዊት በህፃናቱ ማሳደጊያ አካባቢ ቤተሰቦቿን ልትጎበኝ በሄደችበት ወቅት የሰማችውን ሪፖርት ማድረጓን ተከትሎ እንደሆነ ዋሽንግተን ፖስት በዘገባው አስነብቧል። ማርጋሬት ሩቶ የተባለችው ይህችው ግለሰብ ከህፃናቱ ማሳደጊያ አምልጠው የመጡ የ12 አመትና የ14 አመት ታዳጊዎች የደረሰባቸውን ወሲባዊ ጥቃት ለአካባቢው ነዋሪዎች ማጋራታቸውን ተከትሎ የተነሳውን ቁጣ ለዋሽንግተን ፖስት አጋርታለች። ግለሰቧ በራሷ ተነሳሽነት ምርምሯን በመቀጠል ልጆቹን አዋርታ ቃላቸውንም ተቀብላቸዋለች። ያላትን መረጃ በሙሉ ለኤፍቢአይ ከሰጠች በኋላ፣ ኤፍቢአይ የደረሰውን ጥቆማ ተከትሎ ባደረገው ምርመራ ከ2013-2017 ድረስ ቢያንስ አራት ታዳጊዎች ላይ ጥቃት መፈፀሙን ደርሸበታለሁ ብሏል። "ሁለቱ ታዳጊዎች ጥቃቱ ሲጀመርባቸው እድሜያቸው 11 ነበር። የተከሳሹ ባለቤት ራሷ ታዳጊዎች የወሊድ መከላከያ በክንዳቸው እንዲቀበር በማድረግ የተባበረች ሲሆን፤ ግለሰቡ ለአመታት ታዳጊዎችን ያረግዙ ይሆን የሚለውን ፍራቻ በማስቀረት ለአመታት ወንጀሉን ሲፈፅምባቸው ነበር" በማለት የአሜሪካ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ግለሰቡ ኬንያ ከመሄዱ በፊትም በአውሮፓውያኑ 1996 በአሜሪካ በፈፀመው ወሲባዊ ጥቃት በማስጠንቀቂያ እንዲሁም ለአስር አመት ያህልም "ህፃናት ደፋሪ" በሚልም ስም እንዲመዘብ ተደርጎ ነበር።
news-56136268
https://www.bbc.com/amharic/news-56136268
ምርጫ 2013፡ ኦነግ ከምርጫው ወጥቷል የሚለው መረጃ የተሳሳተ ነው ሲል አስተባበለ
የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) በዚህ ዓመት ይካሔዳል በተባለው ምርጫ ላይ አይሳተፍም የሚለው መረጃ የተሳሳተ ነው ሲል አስተባበለ።
የኦሮሞ ነጻ አውጪ ግንባር (ኦነግ) ሊቀመንበር አቶ ዳዉድ ኢብሳ የግንባሩ ሊቀ መንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ኦነግ በምርጫው አይሳተፍም በሚል የተሰራጨው መረጃ የተሳሳተ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ ስድስተኛውን አገራዊ ምርጫ ግንቦት 28 እና ሰኔ 5/2013 ዓ.ም ለማካሄድ የጊዜ ሠሌዳ ይፋ ተደርጎ የተለያዩ እንቅስቃሴዎች እየተደረገ ነው። በዚህም መሠረት ፓርቲዎች በይፋ የምረጡኝ ዘመቻ የጀመሩ ሲሆን የዕጩዎች ምዝገባም ተጀምሯል። በምርጫው ይሳተፋሉ ተብለው ከሚጠቀሱት የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል አንዱ የሆነው ኦነግ ሊቀ መንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ ድርጅታቸው እተደረሰበት ነው ባሉት ጫና ምክንያት ከምርጫው ለመውጣት ተገዷል ማለታቸው ተዘግቦ ነበር። ነገር ግን ሊቀ መንበሩ ለቢቢሲ እንደተናገሩት በአሁኑ ወቅት ድርጅታቸው የተለያዩ ፈታኝ ሁኔታዎች እየገጠሙት መሆኑን አመልክተው፤ ቢሆንም ግን በመጪው ምርጫ ላለመሳተፍ አለመወሰኑን ገልጸዋል። "የዕጩዎች ምዝገባ ቀነ ገደብ እየተጠናቀቀ ነው። መንግሥት ደግሞ ጫና እያደረግብን ነው" ያሉት አቶ ዳውድ፤ "በምርጫው አንሳተፍም የሚል ውሳኔ ላይ ግን አልደረስንም" ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። "ከምርጫው እራሳችንን አግልለናል ብለን አላወጅንም። ከእንዲህ አይነት ውሳኔ ለመድረስ የራሱ አካሄድ አለው። መወያየት ያለብን ነገር አለ" ብለዋል አቶ ዳውድ ጨምረው። ኦነግ በአመራሩ መካከል በተፈጠረ አለመግባባት ጉዳዩ በምርጫ ቦርድ እየታየ የቆየ ሲሆን ችግሩን ለመፍታት ድርጅቱ ጠቅላላ ጉባኤ እንዲጠራና በአመራሩ በኩል የተፈጠረውን አለመግባባት መቋጫ እንዲያበጅለት ተወስኖ የጉባኤው መካሄድ እተጠበቀ ነው። በተጨማሪም ግንባሩ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ያሉት የፓርቲው ጽህፈት ቤቶች መዘጋታቸውንና በርካታ አመራርና አባላቱ በእስር ላይ መሆናቸውን በተደጋጋሚ ሲገልጽ ቆይቷል። ከኦሮሞ ነጻነት ግንባር በተጨማሪ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ እና የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲዎች በተደጋጋሚ በመጪው ምርጫ ለመሳተፍ የሚያስችል አቋም ላይ አንገኝም ሲሉ ተሰምተዋል። ፓርቲዎቹ መንግሥት አባላቶቻቸውን እና ከፍተኛ አመራሮቻቸውን ማሰሩን እንዲሁም ቢሮዎቻቸው እንደተዘጉባቸው ይገልጻሉ። መንግሥት በበኩሉ በእስር ላይ የሚገኙ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች አባላት ለእስር የተዳረጉት በፖለቲካ ተሳትፏቸው አይደለም ሲል ይደመጣል። ለአራት አስርት ዓመታት ያህል በፖለቲካዊና ወታራደራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ የቆው ኦነግ በኦሮሞ ሕዝብ ስም ከሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች መካከል በቀዳሚነት ይጠቀሳል። ኦነግ ከደርግ ውድቀት በኋላ የተመሠረተው የሽግግር መንግሥት አካል የነበረ ሲሆን ከገዢው ኢሕአዴግ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት አመራሩ ከአገር ወጥተው መቀመጫቸውን አሥመራ በማድረግ የትጠቅ ትግል ለማድረግ ወደ ጫካ ገብቶ ነበር። ለዓመታት በስደት የቆው ኦነግ ከሦስት ዓመታት በፊት የጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድን ወደ ሥልጣን መምጣት ተከትሎ ወደ አገር ቤት ተመልሷል። ከበርካታ ዓመታት የትጥቅ ትግል በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በምርጫ ለመወዳደር የተዘጋጀው ፓርቲው፤ በ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ከፍተኛ ግምት ከሚሰጣቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች አንዱ ነው። ፓርቲው በመንግሥት ይደርስብኛል በሚለው ጫናና በአመራሮቹ መካከል የተፈጠረው ቅራኔ በምርጫ ተሳትፎው ላይ ተጽዕኖ ካላደረገበት በቀር በኦሮሚያ ክልል ብርቱ ተፎካካሪ ሆኖ ሊቀርብ እንደሚችል ይጠበቃል። በዚህ ዓመት በሚደረገው አገራዊ ምርጫ እስከ 50 ሚሊዮን የሚደርሱ መራጮች ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማስታወቁ ይታወሳል።
news-48605326
https://www.bbc.com/amharic/news-48605326
የቴክኖሎጂ ፈጣሪዎች ልጆቻቸው 'ሞባይል' እንዳይጠቀሙ የሚያግዱት ለምን ይሆን?
አሁን ከመዳፋችን ተለይቶ የማውቀውን ተንቀሳቃሽ ስልክን የሚዘውሩ መተግበሪያዎችን [አፕሊኬሽን] የፈጠሩ ሰዎች ልጆቻቸው ከሞባይል ስልክ እንዲርቁ ያደርጋሉ።
የሲሊከን ቫሊ ሥራ ፈጣሪዎች ተብለው ከሚታወቁቱ አብዛኛዎቹ አሁን ትዳር መሥርተው ወላጆች ሆነዋል። አሁን በሕይወት የሌለው የአፕል ፈጣሪ ስቲቭ ጆብስ 2011 ላይ ልጆቹ ቤት ውስጥ ስልኮቻቸውንም ይሁን ሌሎች ቴክኖሎጂዎችን ለተወሰነ ሰዓት ብቻ እንደሚጠቀሙ ተናግሮ ነበር። •ኢትዮ ቴሌኮም... ወዴት? ወዴት? •የውጪ ሀገር ጥሪዎች ለምን በኢትዮጵያ ቁጥር ይወጣሉ? የማይክሮሶፍት ባለቤት እና ፈጣሪ የሆነው ቢል ጌትስም ቢሆን ልጆቹ ለዉሱን ሰዓት ብቻ ወደ 'ሞባይል ስክሪን' ብቅ እንደሚሉ ጠቁመው ነበር። የፌስቡክ ባለቤት ማርክ ዙከርበርግ፤ አቻምና ለተወለደች ልጁ በፃፈው ደብዳቤ ላይ «ወደ ውጪ ወጥተሽ ተጫወች» የሚል ቀጭን ትዕዛዝ አስፍሮ ነበር። ለመሆኑ ለምን ይሆን የቴክኖሎጂ ፈጣሪዎች ልጆቻቸው ከሞባይል ስክሪን እንዲርቁ የሚፈልጉት? •ኢኮኖሚያዊ ተቃውሞና ያስከተለው ውጤት ቴክ-ነፃ ልጅነት የሦስት ልጆች አባት ነው፤ ቴክ ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚሠራው ፒዬር ሎረንት። በርካታ የሥራ ባልደረቦቹም ሆነ እርሱ ልጆቻቸው ከቴክኖሎጂ እንዲርቁ አብዝተው ይመክራሉ። ልጆቻቸውን የሚሰዱበት አስኳላም ቢሆን 'ልጆቻችሁን ከቴክኖሎጂ አርቁ' ሲል ሁሌም ያስታውሳቸዋል። «በልጅነትህ ከምታየው ስክሪን ላይ አይደለም ትምህርት መቅሰም ያለብህ። የሰው ልጅ የስሜት ህዋሳቱን ተጠቅሞ ነው ነገሮችን መከወን ያለበት። አእምሮ ነገሮች እንዴት እንደሚሠሩ በሂደት ሊረዳ ይገባል።» በራስ መተማመን፣ ዲስፕሊን፣ ነፃ አስተሳሰብ፣ የቡድን ሥራ፣ ጥበባዊ አገላለፅ፤ እኒህ ከሞባይል ስክሪን ላይ የማይገኙ ጥበቦች ናቸው ሲል ይከራከራል ሎረንት። ሁለት አባቶች፤ የተለያየ ምክር ምንም እንኳ የሲሊከን ቫሊ ወላጆች ልጆቻችን ከቴክኖሎጂ መራቅ አለባቸው ብለው ቢከራከሩም፤ ቴክኖሎጂ ለ21ኛው ክፍለ ዘመን አስፈላጊ ነው ሲሉ የሚሞግቱ ወላጆች አልጠፉም። መርቬ ላፐስ በዘርፉ 'ጥርስ የነቀሉ' ባለሙያ ናቸው። «እርግጥ ነው፤ ቴክኖሎጂ በዝባዥ ነው። ግን እንዴት አድርገን ነው ልንጠቀመው የምንችለው? ምክንያቱም ሕፃናት ቴክኖሎጂን ተጠቅመው ሊበለልፅጉ ይችላሉና። ከቴክኖሎጂ ውጪ ያለውን ዓለም ደግሞ እንዲሁ ማጣጣም አለባቸው።» •ኤርትራውያን ኢሳያስን ለመጣል'#ይበቃል' የተሰኘ እንቅስቃሴ ጀመሩ የዓለም ጤና ድርጅትም በቅርቡ ሕፃናት ምን ያህል ጊዜ ስክሪን መጠቀም እንዳለባቸው የሚጠቁም መመሪያ አዘጋጅቷል። እስከ ሁለት ዓመት ድረስ ያሉ ሕፃናት ብቻቸውን ቴሌቪዥንም ሆነ ሌሎች ስክሪኖችን ማየት የለባቸውም ይላል መመሪያው። አክሎም በቀን ከአንድ ሰዓት በላይ ስክሪን ላይ አፍጥጠው እንዳይቆዩ ይመከራል። ላፐስ «እኔ ምግብ በማበስልበት ጊዜ ልጆቼ 'ሰሲሚ ስትሪት' የተሰኘውን የልጆች ሾው ይመለከታሉ። ይህ ለአንድ ወላጅ ግልግል ነው። ግን ምን ተማራችሁ ብዬ እጠይቃቸዋለሁ።» የሕፃናት እና ስክሪን ግንኙነት ጉዳይ አከራካሪነቱ ቢቀጥልም ባለሙያዎች ስክሪን እንጂ ሌሎች ቴክኖሎጂዎችን መከልከል አስፈላጊ ነው ብለን አናስብም ይላሉ።
news-55421048
https://www.bbc.com/amharic/news-55421048
ሊዮኔል ሜሲ ቫላዶሊድ ላይ ባስቆጠራት ግብ የፔሌን ክብረ-ወሰን ሰበረ
ከዓለማችን ኮከብ ተጫዋቾች መካከል አንዱ የሆነው ሊዮኔል ሜሲ 644ኛ ጎሉን ለክለቡ ባርሴሎና በማስቆጠር የፔሌን ክብረ ወሰን ሰብወል።
ሜሲ በጨዋታው 65ኛ ደቂቃ ላይ በሪያል ቫላዶሊድ ላይ ግብ ሲያስቆጥር ሜሲ የከፍተኛውን ግብ ክብረ ወሰን በእጁ ለማስገባት የቻለው ቡድኑ ባርሴሎና ከሪያል ቫላዶሊድ ጋር በነበረው ግጥሚያ ላይ ከመረብ ያገናኘው ጎል ነው። በዚህም ሜሲ ለአንድ ክለብ ብዙ ጎሎች በማስቆጠር የብራዚላዊውን እግር ኳሰኛ ፔሌ ክብረ ወሰን ሰብሯል። የ33 ዓመቱ አርጀንቲናዊ ባርሴሎና ሪያል ቫላዶሊድን ባሸነፈበት ጨዋታ ከክለብ አጋሩ ፔድሪ የተቀበላትን የቅንጦት ኳስ ወደ ጎል ቀይሮ ነው ክብረ ወሰኑን የጨበጠው። ሊዮኔል ሜሲ በትላንቱ ጨዋታ ድንቅ ብቃቱን አሳይቷል። ብራዚላዊው የእግር ኳስ ጥበበኛ ፔሌ ለሳንቶስ ክለብ ከ1956 እስከ 1974 ተጫውቷል። ለ19 የውድድር ዘመኖች ለአገሩ ክለብ የተጫወተው ፔሌ 643 ጎሎች ከመረብ ማገናኘት ችሏል። ሜሲ ለባርሳ የመጀመሪያ ጎሉን ያሰቆጠረው በፈረንጆቹ 2005 ነበር። አርጀንቲናዊው አጥቂ ከባርሳ ጋር 10 ጊዜ የላሊ ጋ ዋንጫ አንስቷል። 4 ጊዜ ደግሞ የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ባለድል ሆኗል። አጥቂው በአሁኑ ወቅት ከክለቡ ጋር ያለው ውል እየተገባደደ ነው። በሚቀጥለው ጥር ከሚፈልጉት ክለቦች ጋር መደራደር ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል። ሜሲ ባለፈው ነሃሴ ከባርሴሎና በነፃ መሰናበት እፈልጋለሁ ብሎ ጥያቄ ቢያቀርብም ክለቡ ውድቅ አድርጎበት ነበር። በወቅቱ ባርሴሎና ሜሲን የሚፈልግ ክለብ 700 ሚሊዮን ዩሮ ማቅረብ አለበት ሲል ጠይቋል። ሜሲ፤ ይህ ከክለቡ ጋር የነበረው አለመግባባት በእግር ኳስ ሕይወቱ ላይ ተፅዕኖ አሳድሮበት እንደነበር ተናግሯል። ማክሰኞ ምሽት ከቫላዶሊድ ጋር የነበረውን ጨዋታ የረታው ባርሴሎና ከስምንተኛ ደረጃ ወደ አምስተኛ ከፍ ብሏል። ባርሴሎና ላ ሊጋውን እየመራ ካለው አትሌቲኮ ማድሪድ ስምንት ነጥብ ዝቅ ብሎ ይገኛል።
news-52773545
https://www.bbc.com/amharic/news-52773545
ኮሮናቫይረስ: የዓለምን ታሪክ የቀየሩ አምስት አደገኛ ወረርሽኞች
የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ የዓለምን ታሪክ እየቀየረ ነው። ቢሊዮኖች አኗኗራቸው ከወራት በፊት ከሚያውቁት የተለየ ሆኖባቸዋል። ኮሮናቫይረስ ወደፊት በታሪክ ከሚጠቀሱ ክስተቶች አንዱ መሆኑ አያጠራጥርም።
ኮሮናቫይረስስ ዓለማችንን በምን መልኩ ይለውጣት ይሆን? ኮሮናቫይረስ የዓለምን ታሪክ የቀየረ የመጀመሪያው ወረርሽኝ አይደለም። እስቲ ዋና ዋና ከሚባሉት አምስቱን ከታሪክ መዛግብት እናገላብጥ። ጥቁሩ ሞትና የአውሮፓ ሥልጣኔ በርካቶች ፈጣሪ ጥቁሩን ሞት እንዲነቅልላቸው ይፀልዩ ነበር በግሪጎሪ አቆጣጠር በ1350 ላይ አውሮፓን የመታው ጥቁሩ ሞት ተብሎ የሚታወቀው [የቡቦኒክ ትኩሳት] ወረርሽኝ የአህጉሪቱን አንድ ሦስተኛ ሕዝብ እንደቀጠፈ ይነገራል። አብዛኞቹ ሟቾች ደግሞ ለመሬት ባላባቶች እየሠሩ የሚያድሩ ገባሮች ነበሩ። ከበሽታው በኋላ ግን የሠራተኞች ዋጋ እጅግ ተወደደ። ይህም በምዕራብ አውሮፓ የፊውዳል ሥርዓት እንዲወድቅ ምክንያት ሆኗል ይባላል። ይህ መላ ያሳጣቸው የመሬት ባላባቶች በሰው ፈንታ ቴክኖሎጂ ወደመጠቀም ገቡ። ይህ ሂደት ምዕራብ አውሮፓ ወደ ሥልጣኔ እንደትገባ አድረጓታል የሚሉ በርካቶች ናቸው። ምዕራብ አውሮፓውያን ዓለምን ለማሰስ ወደ ሌሎች አገራት ማቅናት የጀመሩትም በዚህ ወቅት በመሆኑ ወረርሽኙ ለቅኝ ግዛትም ሚና እንደተጫወተ ይገመታል። ፈንጣጣና የአየር ንብረት ለውጥ ስፔናውያን ቅኝ ገዢዎች ፈንጣጣን ይዘው ወደ ደቡብ አሜሪካ አገራት እንደሄዱ ይነገራል በ15ኛው ክፍለ ዘመን የደቡብ አሜሪካ አገራት በቅኝ ገዢዎች እጅ ስር መግባት ለዓለም የአየር ንብረት መለወጥ ምክንያት እንደሆነ ይነገራል። የለንደን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ አጥኚዎች የደቡብ አሜሪካ አገራት በአውሮፓውያን ቅኝ በመገዛታቸው ሳቢያ የሕዝብ ቁጥሩ ከ60 ሚሊዮን ወደ 6 ሚሊዮን ዝቅ ብሏል ይላሉ። በርካቶች የሞቱት ቅኝ ገዥዎች ይዘዋቸው በመጡ በሽታዎች ሳቢያ ነው። በጣም ብዙ ሰው የቀጠፈው ፈንጣጣ እንደሆነ ታሪክ ይናገራል። በተጨማሪም ኩፍኝ፣ ኮሌራ፣ ወባና ታይፈስ ቅኝ ገዢዎች ለደቡብ አሜሪካ ሰዎች ያዛመቷቸው በሽታዎች ናቸው። የቅኝ ገዢዎቹ ጣጣ ከደቡብ አሜሪካ አገራት አልፎ ለዓለም ሕዝብም ተርፏል። ነገሩ እንዲህ ነው፤ በሽታው ከቀጠፋቸው መካከል አብዛኞቹ አርሶ አደሮች ነበሩ። በዚህ ምክንያት በርካታ የእርሻ መሬቶች ወደ ጫካነት ተቀየሩ። በወቅቱ ከእርሻ መሬትነት ወደ ጫካነት የተቀየረው መሬት ስፋት ኬንያን ወይም ፈረንሳይን የሚያክል እንደሆነ ይገመታል። ይህ ክስተት የዓለምን ሙቀት መጠን ከተገቢው በላይ ቀነሰው። ምድርም ቅዝቃዜ እንደወረራት ይነገራል። በዚህ ምክንያት በሌሎች ዓለማት ያሉ ሰዎች ተጎዱ። ሰብሎች ውርጭ መታቸው። በጣም የሚገርመው በዚህ የዓለም ሙቀት መቀነስ እጅግ የተጎዳችው ምዕራብ አውሮፓ መሆኗ ነው። ቢጫ ወባና የሄይቲ አብዮት በቢጫ ወባ ምክንያት የሄይቲ አብዮት ፈረንሳዮችን ነቅሏል በ1801 በአህጉረ አሜሪካ በምትገኘው አገር ሄይቲ የተከሰተው የቢጫ ወባ ወረርሽኝ ትንሿ አገር የፈረንሳይን ቅኝ ገዢዎች ፈንቅላ እንድታስወጣ ምክንያት ሆኗል። የፈረንሳዩ መሪ ናፖሊዎን ቦናፓርቴ እራሱን የዕድሜ ልክ መሪ አድርጎ ሾመ፤ አልፎም ደሴቷ ሄይቲን እንዲቆጣጠሩለት በ10 ሺህ የሚቆጠሩ ወታደሮች ላከ። የቢጫ ወባ ወረርሽኝ ግን ለወታደሮችም አልተመለሰም። በሽታው 50 ሺህ ገደማ የፈረንሳይ ወታደሮችን ቀጠፈ። ሐኪሞችና አሳሾችም በበሽታው ከሞቱት መካከል ነበሩ። ወደ ፈረንሳይ በሕይወት የተመለሱት 3 ሺህ ብቻ እንደሆነ ታሪክ ያሳያል። አውሮፓውያን ምንጩ አፍሪካ እንደሆነ የሚነገርለት ቢጫ ወባን መቋቋም አልቻሉም። ይሄኔ ነው ናፖሌዎን ሄይቲን ብቻ ሳይሆን ሌሎች ቅኝ ሊገዛቸው ያሰባቸውን አገራት ጥሎ የወጣው። የፈረንሳዩ መሪ 2.1 ሚሊዮን ስኩዌር መሬት ከሄይቲ ቆርሶ ለዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት መሸጡ አይዘነጋም። ይህ በታሪክ የሉዊዚያና ሽያጭ ተብሎ ይታወቃል። የአፍሪካ ሪንደርፔስትና ቅኝ ግዛት ሪንደርፔስት በርካታ የቁም እንስሳትን እንደፈጀ መዛግብት ያሳያሉ የቁም እንስሳትን የፈጀው ሪንደርፔስት የተሰኘው በሽታ አውሮፓውያን የአፍሪካ አገራትን በቅኝ ግዛት እንዲቀራመቱ ምክንያት እንደሆነ ይታመናል። ከ1888 እስከ 1897 ባለው ጊዜ የተከሰተው ይህ እንስሳትን የሚያጠቃ ቫይረስ 90 በመቶ የአፍሪካ ከብቶችን እንደፈጀ ይነገራል። በተለይ ደግሞ በአፍሪካ ቀንድ፣ በምዕራብ እና ደቡብ ምዕራብ ያሉ አርብቶ አደሮች በዚህ ሳቢያ እጅግ ተጎድተዋል። ይህ እንስሳትን የሚያጠቃ ቫይረስ በርካቶች እንዲራቡና እንዲሰደዱ ምክንያት ሆኗል። አርብቶ አደሮች ብቻ ሳይሆኑ አርሶ አደሮችም ጭምር በዚህ ሳቢያ ተጎድተዋል። በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ አፍሪካን ለመውረር የመጡት የአውሮፓ ቅን ገዢዎች ወረርሽኙ አላማቸውን ምቹ አደረገላቸው። በ1870ዎቹ በአውሮፓ ቅኝ ግዛት ስር የነበረው የአፍሪካ አካል 10 በመቶው ብቻ ነበር። ነገር ግን በወረርሽኙ ሳቢያ የአፍሪካ አገራት አቅም በመዳከሙ በ1900 ዘጠና በመቶ የአፍሪካ መሬት በቅኝ ገዥዎች እጅ እንዲሆን አድርጓል። ወረርሽኝ የጣለው የቻይናው ሚንግ ስርወ መንግሥት ወረርሽኝ ጠንካራውን የቻይና ጥንታዊ ስርወ መንግሥት አንኮታኩቶታል የሚንግ ስርወ መንግሥት ቻይናን ለሦስት ክፍለ ዘመናት አስተዳድሯል። ይህ አገዛዝ በቻይና ብቻ ሳይሆን በበርካታ የምሥራቅ እስያ አገራት ዘንድ የተንሰራፋ ነበር። ነገር ግን የዚህ አገዛዝ ጨረሻ ያማረ አልነበረም። በ1641 በሰሜናዊ ቻይና ወረርሽኝ ተከሰተ። ይህ ወረርሽኝ የበርካቶችን ሕይወት ቀጥፏል። ችግሩን የከፋ ያደረገው ደግሞ በወቅቱ ተከስቶ የነበረው ድርቅና የአንበጣ ወረራ ነው። ሰዎች የሚበሉት በማታጣቸው የሞተ ሰው ስጋ ሁሉ እስከ መ፥ብላት ደርሰው እንደነበር ይነገራል። የቡቦኒክና የወባ በሽታ ቅልቅል ነው የሚባልለት ይህ ወረርሽን ያመጡት የሚንግ አገዛዝ መጣል የፈለጉት ቀጥሎ ወደ አገዛዝ የመጡት የኩዊንግ ስርወ መንግሥት ሰዎች እንደሆኑ ይነገራል። ያሰቡት ተሳክቶላቸውም ግዙፉን ሥርዓት ጥለውታል። እነዚህ በታሪክ የተመዘገቡና የዓለምን ታሪክ በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ የቀየሩ ወረርሽኞች ናቸው። የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝስ ታሪክ ይቀይር ይሆን?
51043967
https://www.bbc.com/amharic/51043967
ሶማሊያውያን፤ አውስትራሊያን ግመሎቻችን ትመልስ የሚል ጥያቄ አቅርበዋል
በደቡብ አውስትራሊያ በተከሰተው ከፍተኛ ድርቅና ሙቀት የተነሳ በሺዎች የሚቆጠሩ ግመሎች በአልሞ ተኳሽ ጥይት እየተገደሉ መሆኑ ተሰምቷል።
ግመሎቹ ወደ አውስትራሊያ በ19ኛው ክፍለ ዘመን ተወስደው የዱር እንስሳ እንዲሆኑ ተደርገዋል እነዚህ በአውስትራሊያ የዱር እንስሳት የሆኑት ግመሎች በጥይት እየተገደሉ መሆኑን የሰሙ ሶማሌያውያን ግን ዜናው አስቆጥቷቸዋል። አውስትራሊያ አምስት ቀን ይፈጅብኛል ባለችው ግመሎችን የመግደል ዘመቻ ሂሊኮፕተርን የምትጠቀም ሲሆን ለመግደሏ ምክንያት የሆነው ደግሞ በድርቅና በከፍተኛ ሙቀት ምክንያት ግመሎቹ ውሃ ፍለጋ ወደ ሰው መኖሪያ መሄዳቸውና የአካባቢው ነዋሪዎች ለደህንነታቸው በመስጋት በማመልከታቸው ነው። በዚህ የተቆጡ ሶማሌያውያን ግመሎቻችንን ላኩልን እኛው እንከባከባቸዋለን ሲሉ ተደምጠዋል። በአውስትራሊያ ያሉት ግመሎች በቁጥር ምን ያህል እንደሆኑ ባይታወቅም በመቶ ሺህዎች እንደሚቆጠሩ ይገመታል። እነዚህ ግመሎች ከሚኖሩበት ዱር ወደ ሰው መኖሪያ አካባቢ በመምጣት አጥሮቻቸውን ማፈራረስ፣ ሰው መተናኮል እንዲሁም ውሃቸውን መጠጣት መጀመራቸው ተነግሯል። ከትናንት ጀምሮ የግመሎቹን እንቅስቃሴ ለመግታት በሂሊኮፕተር በመታገዝ ከሰው መኖሪያ ለማስወገድ በሚል በአልሞ ተኳሾች መግደል ተጀምሯል። ለግመል ከፍተኛ ፍቅር ያላቸው ሶማሊያውያን ታዲያ ይህ ለምን ይሆናል በሚል ግመሎቹን ወደ ትውልድ መንደራችን መልሱልን ሲሉ ጠይቀዋል። ሶማሊያውያን ግመሎቹ ከእኛ የተወሰዱት በ19ኛው ክፍለ-ዘመን ሶማሌላንድን ታስተዳድር በነበረችው ብሪታኒያ ነው ይላሉ። ሌሎች ግን ግመሎች በአውስትራሊያ የሚኖሩ ብሪታንያውያን ከሕንድ፣ አፍጋኒስታንና ከመካከለኛው ምስራቅ በመውሰድ የአውስትራሊያ በረሃ ላይ እንዲለምዱ አድርገዋቸዋል ሲሉ ይናገራሉ። የሶማሌላንድ ግመል አርቢዎች ማህበር ሊቀመንበር ሙስጠፌ አሊ ዲቅ እንስሳቶቹ ለሱማሌያውያን "እጅግ የተከበሩ ናቸው" ከሰው ቀጥሎ ሲሉ ተናግረዋል። አክለውም አውስትራሊያ የግመሎቹን ሕይወት መጀመሪያ ወደ ተወሰዱበት በመመለስ ልታተርፋቸው ይገባል ሲሉ ይጠይቃሉ። • እውን አውስትራሊያ እንዲህ እየተቃጠለች ነው? ሌሎች ደግሞ በትዊተር ገጻቸው ላይ ይምጡ መካከለኛው ምስራቅና አፍሪካ ለእነሱ አይጠብም ሲሉ ተናግረዋል። ሶማሊያውያን ምንም ያህል ገንዘብ ቢኖራቸው ሀብታቸውን የሚለኩት ባላቸው የግመል ብዛት ነው። አውስትራሊያ በአልሞ ተኳሾች የምትገለው የዱር ግመሎቿን ብቻ ሳይሆን ፈረሶችንም ጭምር መሆኑ ታውቋል። በአውስትራሊያ ከወራት በላይ በነበረው የእሳት ቃጠሎ 2ሺህ ቤቶች የተቃጠሉ ሲሆን 25 ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል።
news-53552808
https://www.bbc.com/amharic/news-53552808
የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ከስልጣን መነሳታቸውን ተከትሎ ኢንተርኔት ተቋረጠ
የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ከሥልጣን መነሳታችን ተከትሎ በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍሎች ኢንተርኔት መቋረጡን የኢንተርኔት ነጻነትን የሚከታተለው ኔትብሎክስ አስታወቀ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፕሬዝዳንቱ ጋር የተጋጩት ምርጫው በሚደረግበት ጊዜ ላይ ባለመስማማታቸው ነው ተብሏል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሊ ካሃይሬን ከፕሬዝዳንቱ ጋር የተጋጩት ምርጫው በሚደረግበት ጊዜ ላይ ባለመስማማታቸው ነው ተብሏል። የጠቅላይ ሚኒስትሩን መነሳት ተከትሎም በአገር ውስጥና ውጪ ተቃውሞ ተሰምቷል። የአውሮፓ ሕብረት የውጪ ጉዳይ ፖሊሲ ኃላፊ የሆኑት ጆሴፕ ቦረል አሊ ካሃይሬን ከስልጣን ለማንሳት የተወሰደው እርምጃ "ለሕገ መንግሥታዊ መሰረቱ ክብር ማጣት ነው" ብለውታል። የአገር ውስጥ ደኅንነት ሚኒስትሩ በበኩላቸው "ጨለማው ቀን" ሲሉ ክስተቱን ገልፀውታል። ኔትብሎክስ አክሎ እንዳስታወቀው ኢንተርኔት ሆን ብሎ መቋረጡንና ከማንኛውም ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ ጋርም መገናኘቱ አለመጠቀሱን ገልጿል። ካሃሬን ከሥልጣን ለማንሳት የሕዝብ ተወካዮች በሙሉ ደምጽ የወሰኑ ሲሆን፤ ከ178 ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት 170 ዎቹ ደግፈውታል። ፕሬዝዳንት ሞሀመድ አብዱላሂ "ፎርማጆ" እና ጠቅላይ ሚኒስትሩ መካከል ቀጣዩን ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በሚመለከት የሥልጣን ሽኩቻ እንደነበር ተሰምቷል። ከሥልጣናቸው የተነሱት ጠቅላይ ሚኒስትር ምርጫው መካሄድ ያለበት በሚቀጥለው የፈረንጆች ዓመት የካቲት ወር እንደሆነ ቢገልጹም፤ ፕሬዝዳንቱ ግን በዚያ መሰረት መሄድ የሚችለው ለአንድ ሰው አንድ ድምጽ በሚለው መርህ መሰረት ከሆነ ነው ሲሉ እንደሚከራከሩ ተገልጿል። በአሁኑ ሰዓት የሶማሊያ ጎሳዎች ተወካዮቻቸውን የሚመርጡ ሲሆን የሕዝብ ተወካዮቹ ደግሞ ፕሬዝዳንቱን ይመርጣሉ። ጉዳዮን በቅርበት የሚከታተሉ ፕሬዝዳንቱ የሚያቀርቡት ሃሳብ ምርጫውን በተቀመጠለት ጊዜ ለማድረግ ከፍተኛ ሃብት በማስፈለጉና በርካታ መራጮችን መመዝገብ ስለሚጠይቅ እንደማይቻል በማንሳት ይሞግታሉ። አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር እስኪሾም ድረስ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማሃዲ ሞሐመድ ጉሌድ ቦታውን ሸፍነው እንዲሰሩ በፕሬዝዳንቱ ተጠይቀዋል።
news-50364746
https://www.bbc.com/amharic/news-50364746
በወልዲያ ዩኒቨርሲቲ በተከሰተ ግጭት የሁለት ተማሪዎች ህይወት ማለፉ ተነገረ
ትናንት ቅዳሜ ምሽት በወልዲያ ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎች መካከል በተፈጠረ ግጭት ቢያንስ ሁለት ተማሪዎች መሞታቸው ተነገረ።
ያነጋገርናቸው የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች እና መምህር የብሄር መልክ በያዘው ግጭት የሁለት ተማሪዎች ህይወት ማለፉን እና በርካቶች መቁሰላቸውን አረጋግጠዋል። በዩኒቨርሲቲው መምህር የሆኑት ምንጫችን ትናንት ምሽት በተፈጠረው ግጭት ሁለት ተማሪዎች መሞታቸውን ወደ ዩኒቨርሲቲው ደውለው መስማታቸውን ነግረውናል። የሆስፒታል ምንጮች እንደጠቆሙት ደግሞ ወደ ወልዲያ ጄኔራል ሆስፒታል 14 ተማሪዎች ተጎድተው መጥተዋል። ስማቸወን መግለጽ ያልፈለጉ የወልዲያ ጀነራል ሆስፒታል ባልደረባ ለቢቢሲ "እኔ የገባሁት ዛሬ [እሁድ] ጠዋት 2፡30 ላይ ነው። ተማሪዎቹ ጉዳት ደርሶባቸው ሲመጡ አልተመለከትኩም። ግን አሁን ከ14-15 የሚሆኑ ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች በሆስፒታሉ የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ነው" ሲሉ ተናግረዋል። እኚሁ የሆስፒታል ባልደረባ በተማሪዎች ላይ የደረሰው ጉዳት ከቀላል እስከ ከባድ መሆኑን የጠቀሱ ሲሆን፤ ጉዳቱ ያጋጠመው በድብደባ መሆኑንም ጠቁመዋል። ከዚህ በተጫማሪ ትናንት ምሽት የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ በተፈጠረባቸው የደህንነት ስጋት ከዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ለመውጣት የሞከሩ ተማሪዎች ከግቢው እንዳይወጡ መከልከላቸውን ያነጋገርናቸው ተማሪዎች ተናግረዋል። ግጭቱን ተከትሎ የደህንነት ስጋት የገባቸው ተማሪዎች ከዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ለመውጣት ሲሞክሩ መከልከላቸውን ተናግረዋል። [ፎ፡ ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ እሁድ ጠዋት] ስሙ እንዳይጠቀስ የጠየቀ አንድ ተማሪ ለቢቢሲ "ትናንት የተፈጸመውን አይተን እንዴት ነው ዶርም ውስጥ የምንተኛው?" ሲል ተናግሯል። ጨምሮም "ትናንት የተፈጸመው ዳግም ላለመከሰቱ ምንም ማረጋገጫ የለንም" በማለት ከዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ እንዳይወጡ መደረጉ አግባብ አለመሆኑን ጠቁሟል። በጉዳዩ ላይ የሚመለከታቸው የዩኒቨርሲቲው ባለስልጣናትን ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም። የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ዲን ፕሬዝደንት መረጃ እያጠናቀርን ነው በማለት ዝርዝር መረጃ ሊሰጡን አልቻሉም። የዩኒቨርሲቲው ሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ ስልክ ደግሞ ሊሠራልን አልቻለም። የወልዲያ ዩኒቨርሲቲ የጥበቃ እና ደህንነት ሺፍት ኃላፊ የሆኑት ሻምበል መንግሥቱ ትናንት ምሽት በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ስለተፈጸመው መረጃ እንዲሰጡን ጠይቀናቸው "ምንም መረጃ የለኝም" በማለት መረጃ ከመስጠት ተቆጠበዋል። የአማራ መገናኛ ብዙሃን በበኩሉ የሰሜን ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ወልደትንኤ መኮንን በመጥቀስ ትናንት ምሽት ተማሪዎች በጋራ እግር ኳስ በቴሌቪዝን ተመልክተው ሲመለሱ በተፈጠረ ግጭት ሁለት ተማሪዎች መገደላቸውን እና ስምንት ተማሪዎች ላይ ደግሞ ጉዳት መድረሱን ዘግቧል። የአማራ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባዔ ላይ ተገኘተው ንግግር ያደረጉት የክልሉ የሰላምና ሕዝብ ደህንነት ቢሮ ኃላፊ አቶ አገኘሁ ተሻገር፤ በተማሪዎች መካከል የተነሳውን ግጭት የብሔር ለማስመሰል የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች አሉ ይላሉ። "በግጭቱ ተማሪዎች ተጎድተዋል። በአሁኑ ሰዓት ጉዳዩን አረጋግተነዋል። በዚህ ወንጀል ላይ የተሳተፉ ሰዎችን በቁጥጥር ሥር አውለናል። አልፎም አማራ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በሙሉ ሰላም ለማደፍረስ የሚሠሩ አካላትን ለይተን እርምጃ ለመውሰድ እየተንቀሳቀስን ነው።" የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ትናንት በወልዲያ ዩኒቨርሲቲ የተፈጸመውን ክስተት አውግዟል። የክልሉ ምክት ፕሬዝደንት አቶ ሽመልስ አብዲስ ዛሬ [እሁድ] ከሰዓት በጽሁፍ በሰጡት መግለጫ፤ "እስካሁን ባለን መረጃ በሰላማዊ ተማሪዎች ላይ በተፈጸመ ድብደባ የተገሉት ተማሪዎች ቁጥር ሁለት ናቸው" ያሉ ሲሆን በበርካቶች ላይ ደግሞ የተለያየ መጠን ያለው ጉዳት መድረሱን እና በተለያዩ ተቋማት የሚገኙ ተማሪዎች በሁኔታው መደናገጣቸውን ጠቁመዋል። ምክትል ፕሬዝደንቱ፤ "አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች በአቋራጭ ስልጣን ለመያዝ እና አስተሳሰቦቻቸውን በኃይል ህዝብ ላይ ለመጫን ጥረት እያደረጉ ነው" ያሉ ሲሆን፤ እንዲህ አይነት በፖለቲካ ንግድ የሰከሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚዘሯቸው አጀንዳዎች የኦሮሞ እና የሌሎች ብሄር ልጆች ያልተገባ መስዕዋትነት እየከፈሉባቸው ይገኛሉ" ብለዋል። ለትናንት ምሽቱ ጥቃት ተጠያቂ ናቸው የተባሉት ለፍርድ እንዲቀርቡ ከፌደራል እና ከአማራ ክልል መንግሥት ጋር አብረው እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ምክትል ፕሬዝደንቱ፤ "ወደ ክልላችን ዩኒቨርሲቲዎች የመጡ ተማሪዎችን ደህንነታቸወን በማስጠበቅ እንደ ልጆቻችን እንድንከባከባቸው እና የጥፋት ኃይሎች ፍላጎትን አንድናከሽፍ መልዕክት ማስተላለፍ እፈልጋለሁ" ብለዋል።
news-48010853
https://www.bbc.com/amharic/news-48010853
ከአምቦ ከተማ ነዋሪ ለዶ/ር አምባቸው የቀረቡ 4 ጥያቄዎች
የኦሮሞ እና የአማራ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት መድረክ ትናንት ሚያዝያ 13 ቀን 2011 ዓ. ም. በአምቦ ከተማ ተካሂዷል።
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ምክትል ፕሬዝደንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና የአማራ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳደር ዶ/ር አምባቸው መኮንን በአምቦ ከተማ በሕዝብ ለሕዝብ መድረኩ ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ዶ/ር አምባቸው መኮንን እና የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ የክልሎቹ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ተገኝተዋል። • የተጠበቀውን ያህል የቤንሻንጉል ተፈናቃዮች አልተመለሱም በውይይቱ ላይ የተለያዩ ጥናታዊ ጽሁፎች የቀረቡ ሰሆን ከመድረኩ ተሳታፊዎችም ጥያቄዎች ተሰንዝረዋል። ከተሳታፊዎቹ መካከል አቶ ተሳፋዬ ዳባ የተባሉ የአምቦ ከተማ ነዋሪ ለአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ዶ/ር አምባቸው መኮንን አራት ጥያቄዎች አቅርበው ነበር። የመጀመሪያ ጥያቄያቸው ሰሞኑን በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሄር አስተዳደር እና በሰሜን ሸዋ የተከሰተው ግጭት የሚመለከት ሲሆን አቶ ተስፋዬ እንዲህ ብለዋል። ጥያቄ 1 "እርስዎ በሚያስተዳድሩበት ክልል ውስጥ የሚገኙ ኦሮሞዎች በጠራራ ጸሃይ በታጣቂዎች እንደተገደሉ ከተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ሰምተናል። እርስዎ እና የክልሉ መንግሥት ሰዎችን የሚገድሉ ሰዎች ላይ የወሰዳችሁት እርምጃ ምን እንደሆነ እና አሁን ጉዳዩ የደረሰበትን ሊገልጹልን ይችላሉ?" ዶ/ር አምባቸው ንግግራቸው የጀመሩት በኦሮምኛ ''እንዴት ናችሁ? የኦሮሞ እና የአማራ ሕዝብ ወንድማማች ናቸው። ችግር የለም። እኛ አንድ ነን'' በማለት ነበር። • ኦሮሚያና አማራ የሚፈቱ እስረኞችን እየለዩ ነው ርዕሰ መስተዳድሩ በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሄር አስተዳደር እና በሰሜን ሸዋ በደረሰው ችግር የሰው ሕይወት በመጥፋቱ የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዝን በመግለጽ ለጥያቄው እንዲህ ምላሽ ሰጥተዋል። ''የሰው ሕይወት ጠፍቷል። ይህም በጣም አሳዝኖናል። የተጎዳው በጠቅላላ የእኛው አካል ነው። በዚህም ውስጣችን ተነክቷል። ይህንን እንዴት አድርገን እንፍታው በሚለው ላይ እየተሠራ ነው። አሁን በአከባቢው ሰላም እና መረጋጋት ተፈጥሯል። ይህ አይነቱ ተግባር በድጋሚ እንዳይፈጸም እንደምንሠራ ቃል ልገባላችሁ እወዳለው።'' የኦሮሞ እና የአማራ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ተሳታፊዎች ጥያቄ 2 ሁለተኛው የአቶ ተስፋዬ ጥያቄ ሕገ መንግሥቱ ላይ የኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ ላይ ልዩ ጥቅም አለው የሚለውን ጉዳይ ይመለከታል። "የኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ ስላለው የልዩ ጥቅም ፍላጎት የእርሶ እና የክልሉ አቋም ምንድነው?" ሲሉ ጠይቀዋል። ዶ/ር አምባቸው ለዚህ ጥያቄ ምላሸ መስጠት የጀመሩት ''የአዲስ አበባ አጀንዳ ባልተገባ መንገድ ወደ ሳማይ ተጓጓለ። በየጊዜው አጀንዳ የሚቀርጹልን ኃይሎች ወደፊትም ሊኖሩ እንደሚችሉ አትጠራጠሩ'' በማለት ነበር። • የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ከቃጠሎው በኋላ ''አዲስ አበባን በተመለከተ ሕገ መንግሥቱ ያስቀመጠዉን የሚሸራርፍ አቋም በውስጣችን ማንም የለውም . . . የኦሮሚያ ክልል ልዩ ሕገ መንግሥታዊ መብት አለው፤ ይህ መብቱ እንዲከበርለት እኛም እንታገላለን። ከዛ ውጪ ያሉት ጽንፈኛ ሃሳቦች ተቀባይነት የላቸውም'' ብለዋል። ጥያቄ 3 ሦስተኛው የአቶ ተስፋዬ ጥያቄ፦ "አፋን ኦሮሞ ከአማርኛ እኩል የፌደራል የሥራ ቋንቋ በመሆኑ ላይ ያለዎት አቋም ምንድነው?" የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ዶ/ር አምባቸው መኮንን ምላሽ፦ ''በክልላችን መገናኛ ብዙሃን ላይ ኦሮምኛ የስርጭት ሰዓት አለው። በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደርም የመማሪያ ቋንቋ ነው። ይህም ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንሠራለን። በአማራ ክልል ሌሎች ተጨማሪ ቋንቋዎች በትምህርት ቤቶች ለመስጠት እቅድ አለን።" ጥያቄ 4 ከአምቦ ከተማ ነዋሪው የቀረበው አራተኛው እና የመጨረሻው ጥያቄ፦ "የአምቦ ከተማ ነዋሪ ላለፉት በርካታ ዓመታት ትግል ላይ ነው የቆየው። በዚህም ምክንያት የከተማዋ መሰረተ ልማታዊ ፍላጎቶች አልተሟሉም። እርስዎ እና የአማራ ክልል ባለሃብቶች በዚህ ረገድ ከተማዋን እንዴት ልትረዱ ትችላላችሁ?" • ታዋቂው ኩባንያ ኢትዮጵያዊያን ሠራተኞችን ''ይበድላል'' ተባለ ዶ/ር አምባቸውም፤ የአማራ ክልል ባለሃብቶች ከተማዋን ለማሳደግ መጥተው እንዲሠሩ መልዕክት አስተላልፍላችኋለው ብለዋል።
news-50654888
https://www.bbc.com/amharic/news-50654888
ካማላ ሃሪስ ከአሜሪካ ፕሬዚዳንትነት ውድድር ራሳቸውን አገለሉ
የአሜሪካን ዲሞክራቲክ ፓርቲን ወክለው ለፕሬዚዳንትነት ሲወዳደሩ የነበሩት ካማላ ሃሪስ ከውድድሩ ራሳቸውን አግልለዋል።
በጥር ወር ላይ የምረጡኝ ቅስቀሳ ዘመቻ የጀመሩት የካሊፎርኒያዋ ሴናተር ካማላ ዘመቻቸው ይሳካል በሚል ከፍተኛ ተስፋ ተጥሎባቸው ነበር። ነገር ግን ከወራት በፊት ለቅስቀሳ ዘመቻ አቅደውት የነበረው የገንዘብ መጠን በማሽቆልቁሉ አጣብቂኝ ውስጥ ስለከተታቸው በውድድሩ መቀጠል እንደማይችሉ ተዘግቧል። •በቴክኖሎጂ ኢ-ፍትሐዊነትን የምትታገለው ኢትዮጵያዊት •የሴቶች መብት ታጋይዋ ወይዘሮ መዓዛ አሸናፊ ማን ናቸው? የአምሳ አምስት አመቷ ካማላ ሃሪስ ዶናልድ ትራምፕ ላይ የሰላ ትችት በመሰንዘር ይታወቃሉ፤ በፓርቲያቸውም ውስጥ ከፍተኛ ስፍራ ተሰጥቷቸው ነበር። ነገር ግን ከፓርቲያቸው ሌሎች ተቀናቃኞቻቸውን ጆ ባይደን፣ በርኒ ሳንደርስና ኤልዛቤት ዋረን መወዳደር አልቻሉም። ውድድሩን የጀመሩት በመሪነት ሲሆን፤ በባለፈው ሰኔ በነበረው የቀጥታ ቴሌቪዥን ስርጭት ላይ ጆ ባይደንን በክርክር ድባቅ በመምታታቸው (በክርክር በማሸነፋቸው) ቀጣዩን ውድድር ሊያሸንፉ ይችላሉ የሚል ከፍተኛ ግምት ተሰጥቷቸው ነበር ። •"ማንም መብታችንን ሊሰጠን ስለማይችል፤ ሴቶች ማንንም ሳይጠብቁ በራሳቸው መታገል አለባቸው" •"የመከላከያ ሚኒስቴርን በተሻለ መልኩ መምራት ይቻላል" ኢንጂነር አይሻ መሀመድ "በሁሉም አቅጣጫ ያለሁበትን ሁኔታ አይቸዋለሁ፤ እናም በህይወቴ ከባድ የሚባለውን ውሳኔ ላይ ደርሻለሁ" በማለት ለደጋፊዎቻቸው ማክሰኞ እለት በፃፉት ኢሜይል አሳውቀዋል። አክለውም " ለፕሬዚዳንትነት የማደርገው ውድድር በገንዘብ እጥረት ምክንያት መቀጠል አልቻለም" ብለዋል። አክለውም "እኔ ቢሊዮነር አይደለሁም፤ የምርጫ ዘመቻዬ ወጪየን በራሴ መሸፈን አልችልም። አሁን ባለንበት ሁኔታም ደግሞ ገንዘብ እናሰባስብ ብንል እንኳን አንችልም" ብለዋል። ኮንፈረንስ በመጥራት ለሰራተኞቻቸው ውሳኔያቸውን ያሳወቁ ሲሆን፤ ባለቤታቸውም በትዊተር ገፃቸው፤ "ከጎንሽ ነኝ፤ እደግፍሻለሁ" በማለት አስፍረዋል። ሌሎቹም ተቀናቃኝ ተወዳደሪዎች ውድድሩን በማቋረጣቸው ሃዘናቸውን ገልፀዋል። ከነዚህም ውስጥ የዴሞክራቲክ ፕሬዚዳንት ተወዳዳሪው ጆ ባይደን ይገኙበታል። የቀድሞዋ የሳንፍራንሲስኮ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ካማላ ሃሪስ በሚቀጥለው ወር ላይ ሊካሄድ እቅድ የተያዘለትን የዲሞክራቲክ ፓርቲ ክርክሮችን ለመሳተፍም መስፈርቱን አሟልተው ነበር። ለምረጡኝ ቅስቀሳቸው አስራ ሁለት ሚሊዮን ዶላር በሶስት ወር ውስጥ መሰብሰብ የቻሉት ፖለቲከኛዋ በመጡበት ፍጥነት መቀጠል አልቻሉም።
news-46069139
https://www.bbc.com/amharic/news-46069139
ለቀናት የተዘጋው የአላማጣ- ቆቦ መንገድ ተከፈተ
ለቀናት ተዘግቶ የቆየው የአላማጣ - ቆቦ መንገድ ትናንት ከሰዓት ጀምሮ መከፈቱን የቆቦ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ፅ/ቤት ተወካይ ኢንስፔክተር ዳዊት ዝናቤ ለቢቢሲ ገለፁ።
በዋጃና በአላማጣ የነበሩ ተቃውሞዎችን ተከትሎ በሰዎች ላይ የሚደርስ ድብደባና እስርን በመቃወም ጥያቄ ባነሱ ወጣቶች መንገዱ መዘጋቱን ያስታወሱት ኢንስፔክተሩ ፖሊስ መንገዱን በተደጋጋሚ ለመክፈት ሙከራ ቢያደርግም ወጣቶቹ ጥያቄያችን ካልተመለሰ አንከፍትም በማለት በተደጋጋሚ መንገዱን እንደዘጉት ያስረዳሉ። ወጣቶቹንም ለማግባባትና ችግሩን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ለቀናት ውይይት መደረጉን ይገልፃሉ። • በሰሜን ሸዋ ዞን በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ18 ሰዎች ህይወት አለፈ • ''የፍርድ ቤቶች ተዓማኒነት እና ገለልተኛነት ይመለሳል'' ወይዘሮ መዓዛ አሸናፊ ይህንኑ ተከትሎ መንገዱን መዝጋት ተገቢ እርምጃ እንዳልሆነና ለቀናት በተዘጋው መንገድ ሳቢያ በተሽከርካሪዎችና በመንገደኞች ላይ መጉላላት እንደደረሰ በማስረዳት መግባባት ላይ እንደተደረሰ ይናገራሉ። በመሆኑም ከትናንት ከሰዓት ጀምሮ ከወልዲያ -አላማጣ፣ ዋጃም ሆነ ከአላማጣ - ቆቦ ተሽከርካሪዎች መተላለፍ መጀመራቸውን ገልፀውልናል። ቀደም ብለን ያነጋገርናቸው ሰሜን ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ወልደትንሳዔ መኮንን በበኩላቸው ከወጣቶቹና ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ተደጋጋሚ ውይይት ማድረጋቸውን ያነሳሉ። በዚህም "መንገዱ በመዘጋቱ የሚገኘውን ጥቅምና ጉዳት በማስረዳት፣ ስሜታዊነት ብዙም አይጠቅምም በማለት፣ ጥያቄያቸውን በአግባቡ እንዲያቀርቡ ለረጂም ጊዜ የቆየ ጥልቅ ውይይት ማድረጋቸውን ነግረውናል። የሰሜን ወሎ የፖሊስ መምርያ ኃላፊ ኮማንደር ሃብታሙ ሲሳይ ባለፈው አርብ ጥቅምት 23፣ 2011 ዓ.ም "ከህዝቡ ጋር ውይይት በማካሄድ ላይ እንገኛለን፤ ዛሬ መንገዱን እናስከፍታለን ብለን ተስፋ እናደርጋለን" ሲሉ ለቢቢሲ ገልፀው ነበር። ለቀናት ስለተዘጋው መንገድ የቆቦ ከተማ ነዋሪ ወጣት ብርሃን መንገዱ የተዘጋው ቆቦን አለፍ ብሎ በሚገኝ ሲቀላ በተባለ ወንዝ አቅራቢያ እንደሆነ ነግሮናል። •የሴቶች መብት ታጋይዋ ወይዘሮ መዓዛ አሸናፊ ማን ናቸው? •"ሌሎች ሴቶች ላይ የአሲድ ጥቃት ሳይ ይረብሸኛል፤ ህመሜን ያስታውሰኛል" ካሚላት መህዲ መስመሩ ዋና መንገድ በመሆኑ ሁልጊዜም በርካታ ተሸከርካሪዎችን ያስተናግዳል የሚለው ብርሃን በርካታ ተሸከርካሪዎች በግምት 200 የሚደርሱ መንገድ ተዘግቶባቸው ቆመው እንደነበር ታዝቧል። "መጀመሪያ ላይ በወጣቶች አማካይነት ቢዘጋም፤ የአካባቢው ማህበረሰብም ሃሳቡን እየደገፈውና ወጣቶቹ ያነሱትን ጥያቄ እየተጋሩ ነው" ሲልም ይናገራል። ሌላኛዋ ስሟ እንዲጠቀስ ያልፈቀደች የከተማው ነዋሪ ደግሞ "መንገዱ በመዘጋቱ ሰዎች እየተጉላሉ፤ ለችግር እየተዳረጉ ነው" ስትል ለቢቢሲ ገልፃ ነበር። መንገዱ ከተዘጋበት አቅራቢያ ወደ ቆቦ ለመሻገር ባጃጅ እንደሚጠቀሙም እንዲሁም በወልዲያ ወደ ዋጃ አላማጣ የሚሄዱትም ማለፍ እንዳልቻሉና ቆቦ ከደረሱ በኋላ እንደሚመለሱ ገልጻልን ነበር። ጉዳዩን አስመልክተን ያነጋገርናቸው የሰሜን ወሎ ዞን ፖሊስ መምሪያ አዛዥ የሆኑት ኮማንደር ሃብታሙ ሲሳይ መንገዱ የተዘጋው ዋጃና አላማጣ አካባቢ በነበሩት ግጭቶች የሰው ህይወት መጥፋቱንና ንብረት መውደሙን ተከትሎ እንደሆነ አስረድተዋል። በዚህም ሳቢያ ቀደም ሲልም መንገዶች ተዘግተው የነበረ ሲሆን በውይይት እንደተፈታ አስታውሰው "የንግድ ሚኒባስ አሽከርካሪዎችና ለሥራ የሄዱ የመንግሥት ሰራተኞች ለምን ይደበደባሉ?" በሚል ጥያቄ ወጣቶቹ በድጋሚ መንገዱ ሊዘጉት እንደቻሉ ገልፀውልናል። ወጣቶቹ የሚያነሱት ጥያቄም የሚፈፀመውን ድብደባ በመቃወምና የክልል ልዩ ፖሊስ ወጥቶ መከላከያ ይግባ፤ የሚል እንደሆነ ኮማንደር ሃብታሙ ይናገራሉ። "ለሕይወታችን ሰግተናል፤ በዚህም ምክንያት መንገዱን ዘግተናል" ሲሉ መልስ እንደሰጧቸው ገልፀውልናል። እስካሁን በሰዎችም ሆነ በንብረት ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለ የሚገልጹት ኮማንደሩ መንገዱ የተዘጋው ለተሸከርካሪዎች ሲሆን ሰዎች እንዳይቸገሩ ሌላ የትራንስፖርት አገልግሎት ተመቻችቶ እየተሸጋገሩ እንደነበር ነግረውናል። ወጣቶቹ መንገዱን ለተሸከርካሪዎቹ ብቻ የዘጉት፤ የሁለቱም ክልል አመራሮች ተነጋግረው መፍትሔ ይስጡን በሚል ምክንያት እንደሆነ ያስረዳሉ።
news-50065673
https://www.bbc.com/amharic/news-50065673
ኬንያ በአንድ ቢሊዮን ዶላር ብድር የሰራችውን የባቡር መንገድ ልትመርቅ ነው
ኬንያ የባቡር መንገዷ ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆን የኬንያ ባቡር መንገድ በፌስቡክ ገፁ አስታውቋል።
አዲሱ የኬንያ የባቡር መስመር ከመዲናዋ ናይሮቢ ወደ ናይቫሻ ሲሆን በዛሬው ዕለትም ለአገልግሎት ክፍት ይሆናል። መስመሩ ለጊዜው አገልግሎት የሚሰጠው ለሰዎች ሲሆን የጭነት ማጓጓዝ አገልግሎት ደረቁ ወደብ እስኪገነባ ድረስ ይጠበቃል ተብሏል። •የሆሊውዱ ሃኪም ገብረወልድን ያውቁታል? •"ሰልፍ የዜጎች መሰረታዊ መብት ነው" መስፍን ነጋሽ ግንባታውም ረዘም ያለ ጊዜ እንደሚወስድም ተገምቷል። ለዚህም በአካባቢው የሚኖሩ የማሳይ ማህበረሰብ ግንባታውን በመቃወም ጉዳዩን ወደ ፍርድ በመውሰዳቸው እንደሆነ ተገልጿል። በቻይና ኮሚዩኒኬሽንና ግንባታ ኩባንያ የተገነባው ይህ መስመር 120 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ያለው ሲሆን 1.4 ቢሊዮን ዶላር ፈጅቷል። የተጓዦች አገልግሎት ከአስራ ሁለቱ ጣቢያዎች በአራቱ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀመር ዘ ቢስነስ ደይሊ ኒውስፔፐር የኬንያ የባቡር አገልግሎት ኃላፊ የሆኑት ፊሊፕ ማይንጋን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል። የመጀመሪያው የባቡር መንገድ ከመዲናዋ ናይሮቢ ወደ ሞምባሳ ከሁለት አመት በፊት በተመረቀበት ወቅት ከፍተኛ ደስታና ፈንጠዝያ የነበረ ሲሆን ይህ መስመር ግን እንደ መጀመሪያው አልሆነም ተብሏል። በወቅቱም ኬንያ ለምርጫ ስትዘጋጅ ነበር። •በኢትዮጵያ አየር መንገድ አደጋ የሞቱ ሰዎች አጽም ለቤተሰቦቻቸው እየተሰጠ ነው • በተሻሻለው የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ህግ ረቂቅ ጥፋተኛና አቃቤ ህግ ይደራደራሉ የአዲሱ የባቡር መንገድ ዋጋ ከአለም አቀፉ ስታንዳርድ አንፃር ጋር ሲታይ ሶስት እጥፍ እንዲሁም መጀመሪያ ያወጣል ተብሎ ከተገመተው አራት እጥፍ ነው ተብሏል። መንግሥት ዋጋው እንዲህ ለምን ናረ ለሚለው የሰጠው ምክንያት የመልክአ ምድሩ አስቸጋሪነት ድልድዮችንና ቱቦችን በመገንባት ላልታሰበ ወጪ እንደተዳረጉ ነው። ከዚህም በተጨማሪ ለመሬት ካሳ ተከፍሏል ተብሏል። ከዚህ ወጪ ውስጥ 80% የተገኘው ከቻይና በተገኘ ብድር ነው። የባቡር መስመሩ የመጀመሪያ እቅድ ከሞምባሳ- ኪሱሙን በመሻገር ኡጋንዳ ይደርሳል ተብሎ ነበር። አገሪቷ ይህንን የባቡር መስመር ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ 3.3 ቢሊዮን ዶላር ብድር ያስፈልጋታል ተብሏል።
news-52631332
https://www.bbc.com/amharic/news-52631332
በቤትዎ በቀላሉ ስለሚሠራ ጭምብል ማወቅ የሚገባዎት ነጥቦች
በኮሮናቫይረስ ምክንያት በሮቻቸውን ዘግተው የነበሩ አገራት ዳግመኛ ወደ እንቅስቃሴ እየተመለሱ ነው። ዜጎቻቸው ሕዝብ በተሰበሰበበት አካባቢ ሲሆኑ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል እንዲያደርጉም ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።
በመጓጓዣ እንዲሁም መገበያያ መደብር ውስጥ ጭምብል ማድረግን አስገዳጅ ሕግ ካደረጉ አገራት መካከል ፈረንሳይና ጀርመን ይገኙበታል። የጤና ባለሙያዎች ከሚያዘወትሩት ጭምብል ወይም ማስክ ባሻገር ግለሰቦችም በቤታቸው ማዘጋጀት ይችላሉ። እርስዎም ‘ማስክ’ የሚሠሩበትን መንገድ እና በምን መንገድ ሊጠቀሙበት እንደሚገባ ልንነግርዎ ወደድን። • እጅ ስፌት ላይ እንዴት ነዎት? ያረጀ ካናቴራ የመጠገን ልማድ አለዎት እንበል። ጭንብል ማዘጋጀትም እንደዚሁ ነው። ጨርቁ በርከት ሲል ማስኩ ጠንካራ ይሆናል። በፊትዎ ልክ መሆኑን እንዲሁም ለመተንፈስ አስቸጋሪ አለመሆኑን ማጣራት አይዘንጉ። • ጭንብሉ አፍና አፍንጫዎን በአግባቡ መሸፈን አለበት። ፊትዎ ላይ እንዲቀመጥ ጆሮዎ ላይ የሚታሰር ገመድ ሊዘጋጅለትም ይገባል። • ከጥጥ ወይም ከሐር የተሠሩ ጨርቆች ‘ማስክ’ ለመሥራት ተመራጭ እንደሆኑ ጥናቶች ያሳያሉ። እነዚህን ማግኘት ካልቻሉ ግን ቤት ውስጥ ባለ ጨርቅ ለማዘጋጀት ይሞክሩ። • ጭንብል ከማጥለቅዎም ሆነ ከማውለቅዎ በፊት እጅዎን በሳሙና ሙልጭ አድርገው መታጠብ አለብዎት። • ‘ማስክ’ በማይጠቀሙበት ወቅት ላስቲክ ውስጥ ያስቀምጡት፣ አዘውትረው ማጠብም ይጠበቅብዎታል። • ኮረናቫይረስ ይዞዎት ነገር ግን ምልክቶቹን እያሳዩ ካልሆነ ጭንብል በማጥለቅ በሽታውን ወደ ሌሎች ሰዎች ከማስተላለፍ ይታቀባሉ። • የኮቪድ-19 ምልክቶች ካሳዩ ደግሞ በቤትዎ ራስዎን አግልለው መቆት ይገባዎታል። ከምልክቶቹ መካከል ትኩሳት እና ደረቅ ሳል በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳሉ። • ‘ማስክ’ አጥልቀዋል ማለት ከበሽታው ራስን ለመከላከል መወሰድ የሚገባቸው ሌሎች ጥንቃቄዎችን መተው አለብዎ ማለት አይደለም። ጭምብል ቢያደርጉም እንኳን እጅዎን ቢያንስ ለ20 ሰከንድ መታጠብ የግድ ነው። • አሁን ላይ የፋሽን ዲዛይነሮችን ምሳሌ በማድረግ ጭምብል የሚሠራባቸውን መንገዶች የሚጠቁሙ ብዙ ገፆች አሉ። ማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ ያገኟቸዋል። • ከአንድ በላይ ‘ማስክ’ ማዘጋጀት አይዘንጉ! አንዱ እስኪታጠብ ሌላውን ማድረግ ይችላሉ። • ከሁለት ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናት ወይም በትክክል የአፍና አፍንጫ ጭምብል ማጥለቅ የማይችሉ ግለሰቦች ‘ማስክ’ እንዲጠቀሙ አይመከርም።
51922474
https://www.bbc.com/amharic/51922474
ሞሮኮ እንደ ፍልውሃ ያሉ የጋራ መታጠቢያ አገልግሎቶችን አገደች
ሞሮኮ ሃማምስ የተሰኙትን እንደ ፍል ውሃ ያሉ የህዝብ ገላ እጥበት አገልግሎቶችን የኮሮናቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ሲባል አገደች።
የህዝብ መታጠቢያ ቦታዎቹን እገዳ ይፋ ያደረገው የሞሮኮ የአገር ውስጥ ሚኒስቴር ነው። ሚኒስቴር መስሪያቤቱ ተጨማሪ እገዳዎችንም የጣለ ሲሆን ካፍቴሪያዎች፣ ሬስቶራንቶች፣ ሲኒማዎችና መስጂዶችም ጭምር ዝግ እንዲሆኑ ወስኗል። አስፈላጊ የሚባሉ ቁሳቁሶች የሚገኙባቸው ገበያዎች ወይም የሚሸጡ ሱቆች እንዲሁም ወደ ቤት የሚወሰድ ምግብ የሚያቀርቡ ሬስቶራንቶች ግን ከእገዳው ውጭ እንደሚሆኑ ተገልጿል። እስካሁን በሞሮኮ 29 በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች መኖራቸው ተረጋግጧል። ጥቂት የማይባሉ የአፍሪካ አገራት በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎችን እያገኙ መሆናቸውን ተከትሎ የጉዞን ጨምሮ የተለያየ እገዳ እየጣሉ ነው። • ኮሮና ቫይረስ ከየት መጣ? • ስለአዲሱ ኮሮና ቫይረስ ማወቅ የሚገባዎ ነጥቦች • አሜሪካ የኮሮናቫይረስ ክትባት ሙከራ ጀመረች ቀደም ሲል ኬንያ ከየትኛውም ኮሮናቫይረስ ከተገኘበት አገር ወደ ኬንያ የሚደረግን ጉዞ ማገዷ ሲሰማ የኬንያን ፈለግ በመከተል ደቡብ አፍሪካም ተመሳሳይ እገዳ ጥላለች። የደቡብ አፍሪካ እገዳ ቻይና፣ ኢራን፣ ጣልያን፣ ስፔን፣ እንግሊዝና አሜሪካን ይጨምራል። ጋናም የኮሮናቫይረስ ከፍተኛ ስርጭት ካለባቸው አገራት ተጓዦች እንዳይመጡብኝ ብላለች። የኮሮናቫይረስ ኬዝ ያልተመዘገበባቸው ጅቡቲና ታንዛኒያም ጭምር ዓለም አቀፍ በረራዎችን አግደዋል። በኮሮናቫይረስ የተያዙ 28 ሰዎች የተገኙባት እንዲሁም ሞት የተመዘገበባት ሞሮኮም ዓለም አቀፍ በረራዎችን አግዳለች። አልጄሪያ ከነገ ጀምሮ ወደ ፈረንሳይ የሚደረግን በረራ እንደምታቆም ስታስታውቅ ሞዛምቢክ ባለስልጣናቷ ወደ ውጭ አገር ጉዞ እንዳያደርጉ ከልክላለች። በአሁኑ ወቅት ቫይረሱ በ26 የአፍሪካ አገራት እንደተገኘ ተረጋግጧል።
news-45047215
https://www.bbc.com/amharic/news-45047215
ፌስቡክና ኢንስታግራም ላይ የምናጠፋው ጊዜ ገደብ ሊበጅለት ነው
የፌስቡክና ኢንስታግራም ተጠቃሚዎች በእነዚህ መተግበሪያዎች ላይ የሚያጠፉትን ጊዜ ለመገደብ የሚያስችል አሰራር ተግባራዊ ሊያደርጉ እንደሆነ ፈጣሪዎቹ ገልጸዋል።
ውሳኔው ላይ የተደረሰው አብዛኛዎቹ ተጠቃሚዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ከመጠን ያለፈ ጊዜ እያሳለፉ ስለሆነና ይህም በአእምሮ ጤና ላይ አሉታዊ ተጽህኖ እያስከተለ ስለሆነ ነው። • በሞባይልዎ የኢንተርኔት ወጪ ተማረዋል? • በፌስቡክ ማስታወቂያ የተሳካ ጋብቻ • ፌስቡክ የተጠቃሚዎችን ግላዊ መረጃ መበርበሩን አመነ በዚህ መሰረት ተጠቃሚዎች በፌስቡክና ኢንስታግራም ላይ ምን ያህል ጊዜ እንዳጠፉ ማወቅ የሚችሉ ሲሆን፤ የተመደበላቸው ጊዜ ሲያልቅም አስታዋሽ መልዕክት እንዲያገኙ እንደሚደረግም ተገልጿል። በተጨማሪም ለተወሰ ሰዓት ምንም አይነት መልእክቶች ከመተግበሪያዎቹ እንዳይደርሳቸው ማድረግ ይችላሉ። አንዳንድ ተጠቃሚዎች ግን አሰራሩ ተገቢ ያልሆነና ብዙ ርቀት የማያስሄድ ነው እያሉ ነው። ''በአዲስ መልኩ የሚተዋወቀው አሰራር ስር ነቀል ለውጥ ያመጣል ብዬ አላምንም፤ እንደውም በፌስቡክና ኢንስታግራም ተጠቃሚዎች ላይ ምንም አይነት የሰዓት ለውጥ አያመጣም'' ያሉት ከኦክስፎርድ ቤይነ መረብ ማእከል የመጡት ''ግራንት ብላንክ'' ናቸው። ፌስቡክ ተጠቃሚዎቹ በመተግበሪያው ላይ ብዙ ጊዜ እያጠፉ እንደሆነና ይህ ደግሞ አሉታዊ ተጽህኖዎችን እያስከተለባቸው እንደሆነ የሚያሳይ ጽሁፍ ባለፈው ታህሳስ አስነብቦ ነበር። በቅርቡ በተሰራ አንድ የሙከራ ጥናት ''በዩኒቨርሲቲ ኦፍ ሚቺጋን'' የሚማሩ ጥቂት ተማሪዎች ለ10 ደቂቃዎች ያህል ምንም ሳይሰሩ የፌስቡክ ገጻቸውን ብቻ እንዲመለከቱ የተደረገ ሲሆን፤ ሌላኞቹ ደግሞ ፌስቡክን በመጠቀም ከጓደኞቻቸው ጋር እንዲወያዩና መልእክቶች እንዲያስተላልፉ ተደርገው ነበር። በሙከራው መሰረት ፌስቡክን በአግባቡ ከተጠቀሙት ተማሪዎች ጋር ሲነጻጸር፤ ምንም ሳይሰሩ የፌስቡክ ገጻቸው ላይ 10 ደቂቃ ያሳለፉት ተማሪዎች ጥሩ ያልሆነ ስሜት ውስጥ እንደገቡ ተገልጿል።
news-49868824
https://www.bbc.com/amharic/news-49868824
የየመን አማጺያን በርካታ የሳኡዲ ወታደሮች መማረካቸውን ገለጹ
የሁቲ አማጺያን በየመንና በሳኡዲ ድንበር መካከል በሚገኝ ቦታ በፈጸሙት ጥቃት በርካታ ቁጥር ያላቸው የሳኡዲ አረቢያ ወታደሮች መማረካቸውን አስታወቁ።
የሁቲ አማጺያን ቃል አቀባይ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ናጅራን ተብላ በምትታወቀው የሳኡዲ አነስተኛ መንደር ውስጥ የሦስት ብርጌድ ወታደሮች እጃቸውን ሰጥተዋል። • ሳዑዲ ላይ በተፈጸመው ጥቃት የኢራን እጅ እንዳለበት የአሜሪካ መረጃ ጠቆመ • በሳዑዲ የደረሰው ጥቃት እጅጉን እንዳሳሰባቸው የኔቶ ኃላፊ ገለፁ ቃል አቀባዩ እንደሚሉት በሺዎች የሚቆጠሩ የሳኡዲ ወታደሮች የተያዙ ሲሆን በርካቶች ደግሞ ተደግለዋል። የሳኡዲ ባለስልጣናት ስለሁኔታው እስካሁን ምንም ያሉት ነገር የለም። ''ይህ ክስተት ግጭቱ ከተጀመረ አንስቶ እጅግ ከፍተኛ የሚባል ነው'' ብለዋል ቃል አቀባዩ። የሳኡዲ ሠራዊት ላይ በሰው ህይወትም ሆነ በጦር መሳሪያ ከፍተኛ የሚባል ውድምት መድረሱን ቃል አቀባዩ ኮሎኔል ያሂያ ሳሬአ አክለዋል። ሁሉም የተያዙት ወታደሮችም ዛሬ በሁቲ አማጺያን በሚመራው የአል ማሲራህ ቴሌቪዥን እንደሚቀርቡ ታውቋል። በኢራን የሚደገፉት የየመን ሁቲ አማፂያን ከሁለት ሳምንት በፊት በሳዑዲ ሁለት የነዳጅ ማቀነባበሪያ ተቋማት ላይ ለደረሰው ጥቃት ኃላፊነቱን እንወስዳለን ማለታቸው ይታወሳል። ነገር ግን አሜሪካም ሆነች ሳዑዲ አረቢያ ለጥቃቱ ተጠያቂ ያደረጉት ኢራንን ነው። በኢራን መንግሥት ድጋፍ የሚደረግላቸው የሁቲ አማጽያን የየመንን መንግሥትና የሳዑዲ መራሹን ኃይል ሲፋለሙ ቆይተዋል። የየመኑ ፕሬዝደንት አብደራቡህ ማንሱር ከመዲናዋ ሰነዓ በሁቲ አማጽያን ተባረው ከወጡበት ጊዜ ጀምሮ ሃገሪቱ ላለፉት 4 ዓመታት በጦርነት ስትታመስ ቆይታለች። • አሜሪካ ጦሯን ወደ ሳዑዲ ልትልክ ነው ሳዑዲ ከመዲናቸው የተባረሩትን ፕሬዝደንት በመደገፍ በሁቲ አማጽያን ላይ በየቀኑ ማለት በሚቻል መልኩ የአየር ጥቃቶችን ትፈጽማለች። የሁቲ አማጽያን በበኩላቸው ሚሳኤሎችን ወደ ሳዑዲ ያስወነጭፋሉ። የእርስ በርስ ግጭቱ ከ24 ሚሊዮን በላይ ከሚሆነው የየመን ሕዝብ 80 በመቶው ከፍተኛ ሰብአዊ ቀውስ ውስጥ እንዲገባ አድርጎታል። ከእነዚህ መካከል 10 ሚሊዮን የሚሆኑት ደግሞ በቀጥተኛ የምግብና ውሃ እርዳታ ነው ህይወታቸውን እየመሩ የሚገኙት። እ.አ.አ. ከ2016 ጀምሮ በግጭቱ ከ70 ሺ በላይ ሰዎች ህይወታቸውን እንዳጡ የተባበሩት መንግሥት ድርጅት ይገምታል።
news-54574582
https://www.bbc.com/amharic/news-54574582
ኮሮናቫይረስ፡''አፍሪካ ሁለተኛ ዙር ወረርሽኝ ይከብዳታል'' የዓለም ጤና ድርጅት
የዓለም ጤና ድርጅት ሁለተኛው ዙር የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ለአፍሪካ በእጅጉ አስጊና ከባድ ሊሆን እንደሚችል አስጠንቅቋል። ድርጅቱ አክሎም ወረርሽኙ በተለይ ለአፍሪካ ኢኮኖሚ አስጊ እንደሆነ አስታውቋል።
የዓለም ጤና ድርጅት ይህንን ያለው በርካታ አገራት የእንቅስቀሴ ገደቦችንና ሌሎች የጥንቃቄ እርምጃዎችን ማላላት መጀመራቸውን ተከትሎ የቫይረሱ ስርጭት እንደገና ማንሰራራት በመጀመሩ እንደሆነ ተጠቁሟል። የአፍሪካ አገራት ኢኮኖሚያቸውን ለማነቃቃት በማሰብ ወደቀደመው እንቅስቃሴያቸው መመለስ መጀመራቸው ቫይረሱ ከቁጥጥር ውጪ እንዲሆን እድል እንደሚፈጥር ድርጅቱ አስጠንቅቋል። በርካታ አገራትም በቂ ዝግጅት ሳያደርጉ እንቅስቃሴዎችን እንደገና እያስጀመሩ መሆኑ እንዳሳሰብው ጠቁሟል። ድርጅቱ አክሎም ነገሮች በዚሁ የሚቀጥሉ ከሆነ የኮሮረናቫይረስ ወረርሽኝ እንደአዲስ ተንሰራፍቶ አገራት ተመልሰው ሙሉ በሙሉ እንቅስቃሴ ማገድ ውስጥ ሊገቡ እንደሚችሉ አስታውቋል። አፍሪካ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ካጋጣት የኢኮኖሚ ውድቀት ለማገገም እንዲሁም የጤና ወጪ 1.2 ትሪሊየን ዶላር እንደሚያስፈልጋት ዓለም አቀፉ ገንዘብ ተቋም [አይኤምኤፍ] ማስታወቁ የሚታወስ ነው። ገንዘቡ ያስፈልጋታል የተባለው ደግሞ በሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት ነው። በአፍሪካ በኮሮናቫይረስ የተያዙ እንዲሁም የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከሌሎች አህጉራት ያነሰ ነው፤ ነገር ግን የዓለም ባንክ በወረርሽኙ ሳቢያ ተጨማሪ 43 ሚሊዮን የሚሆኑ አፍሪካዊያን ለከፋ ድህነት የመጋለጥ አደጋ ተጋርጦባቸዋል ብሏል። በወረርሽኙ ሳቢያ የሥራ እድሎች በመታጠፋቸው እና የቤተሰብ ገቢ በ12 በመቶ በመቀነሱ የደረሰው የኢኮኖሚ ተፅእኖ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአፍሪካ እየታየ የነበረውን ጠንካራ እድገት እየቀለበሰው መሆኑም ተጠቁሟል። አይኤም ኤፍ የአፍሪካ አገራት ከደረሰባቸው ተፅዕኖ እንዲያገግሙ 26 ቢሊዮን ዶላር የለገሰ ቢሆንም፤ የግል አበዳሪዎች እና በሌሎች አገራት ድጋፍ ቢኖርም፤ አሁንም ግን ከፍተኛ የሆነ የገንዘብ እጥረት አለ። የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ዳይሬክተር የሆኑት ማሺዲሶ ሞዌቲ እንዳሉት አህጉሪቱ የሚገባትን የክትባት ድርሻ እንድታገኝም ከአሁኑ እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው። በአፍሪካ እስካሁን 1.6 ሚሊየን ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሲሆን ወረርሽኙ አህጉሪቱ ውስጥ መግባቱ ከተሰማባት ዕለት አንስቶ ደግሞ ከ39 ሺ በላይ ሰዎች በዚሁ ቫይረስ ሳቢያ ሕይወታቸው አልፏል።
news-53734533
https://www.bbc.com/amharic/news-53734533
ፍትህ፡ የአቶ ልደቱ አያሌውና ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት የፍርድ ቤት ውሎ
የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) የብሔራዊ ምክር ቤት አባል የሆኑት ፖለቲካኛው አቶ ልደቱ አያሌው በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸው የተሰማው ከጥቂት ሳምንታት በፊት ነበር።
አቶ ልደቱን ፖሊስ የያዛቸው በቅርቡ በቢሾፍቱ ከተማ ተከስቶ የነበረውን አለመረጋጋት በማስተባበርና በመደገፍ ተጠርጥረው ነው። በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ከዋሉ በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረቡት የአዴፓ አባሉ አቶ ልደቱ አያሌው ተጨማሪ የ7 ቀናት ቀጠሮ እንደተሰጣቸው የፓርቲው ፕሬዝደንት አቶ አዳነ ታደሰ ለቢቢሲ ተናግረዋል። "ፍርድ ቤቱ ፖሊሶች የደረሰቡትን መረጃ ጠይቆ ፖሊሶች ከ14 ቀናት ጊዜ በኋላ ከቃል አቤቱታ ውጭ ማቅረብ አልቻንም ተጨማሪ 14 ቀናት ይሰጠን ብለው ጠይቀዋል። ይህን የተመለከተው ፍርድ ቤት ለመጨረሻ ጊዜ የ7 ቀናት የምርመራ ጊዜ ለፖሊስ ሰጥቷል።" የአቶ ልደቱ አያሌውን የጤና ሁኔታ በተመለከተ የፓርቲው ሊቀ-መንበር ይህን ብለዋል። "አቶ ልደቱ የልብ ህመምተኛ እንደሆኑና የሕክምና ሰርቲፌኬት እንዳላቸው ለፍርድ ቤቱ አመልክተው እስካሁን ግን ፍርድ ቤቱ ከዚህ በፊት ሕክምናቸውን እንዲከታተሉ የወሰነው ውሳኔ ተፈፃሚ አለመሆኑን ገልፀው ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ እንዲሰጥ በጠየቁት መሠረት ፍርደ ቤቱ በአቅራቢያው ከሚገኘው ሆስፒታል ለሚቀጥለው ቀጠሮ የሕክምና ማስረጃ ይዘው እንዲቀርቡ የሚል ትዕዛዝ ሰጥቷል።" አቶ ልደቱ አያሌው ነሐሴ 11/2012 ዓ.ም ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል። አቶ ልደቱ ነዋሪነታቸው ከአዲስ አበባ 40 ኪሎ ሜትር ርቃ በምትገኘው በቢሾፍቱ ከተማ ውስጥ ሲሆን፣ የፌደራል ፖሊስ ስልካቸው ላይ በመደወል እንደሚፈለጉ በመግለፁ፣ ወደ ፌደራል ፖሊስ ቢሮ በመሄድ እዚያ በቁጥጥር ስር መዋላቸውንና ፌደራል ፖሊስም ለሚፈልጋቸው የቢሾፍቱ ከተማ ፖሊስ እንዳስረከባቸው አይዘነጋም። አቶ ልደቱ የኢዴፓ መስራችና አባል አመራር ሆነው ለረጅም ዓመታት የቆዩ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ የድርጅቱ የብሔራዊ ምክር ቤት አባልና አብሮነት በሚባለው የፓርቲዎች ጥምረት ውስጥ የኢዴፓ አስተባባሪ ተወካይ ናቸው። ይልቃል ጌትነት [ኢንጂነር] በሌላ በኩል ይልቃል ጌትነት [ኢንጂነር] ትላንት [ሰኞ] ፍርድ ቤት ቀርበው ነበር። ፖሊስ ተጨማሪ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ቢጠይቅም ፍርድ ቤቱ የ9 ቀናት ጊዜ መፍቀዱን ጠበቃቸው አዲሱ ጌታነህ ለቢቢሲ ተናግረዋል። "ፖሊስ ድጋሚ ተጨማሪ 14 ቀናት ጠየቀ። አቶ ይልቃል ከታሰሩ ከሰኔ 25 ጀምሮ እስካሁን ድረስ ያለው ሲቆጠር 40 ቀናት ናቸው። እነዚህ 40 ቀናት ከተጠየቁትና እስካሁን ከተሰራው ሥራ አንፃር በጣም ረጅም ናቸው ብለን ከዚህ በላይ ተጨማሪ ጊዜ ሊፈቀድ እንደማይገባ ገልፀን ተከራክረናል።" ጠበቃው አክለው አሁን ፍርድ ቤቱ የፈቀደው የምርመራ ጊዜ የመጨረሻው ነው ብለዋል። "ፍርድ ቤቱም ክርክሩን ከሰማ በኋላ የተጠየቀው ጊዜ አስፈላጊ እንደሆነ አምኛለሁ፤ ሆንም ግን አሁን ለምርመራ የምንሰጠው ጊዜ የመጨረሻ ነው በማለት 14 ቀናት የተጠየቀውን ጊዜ ወደ 9 ዝቅ አድርጎ ለነሃሴ 14/2012 ቀጠሮ ሰጥቷል።" ይልቃል ጌትነት [ኢንጂነር] በቁጥጥር ሥር የዋሉት ከሰኔ 23 እስከ 25 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ ባሉት ቀናት በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ አካባቢዎች በሞቱ ሰዎችና በወደመ የመንግሥትና የግል ንብረት ጉዳይ እጃቸው አለበት በሚል ተጠርጥረው ነው።
48605254
https://www.bbc.com/amharic/48605254
የኢትዮጵያን አደራዳሪነት የሱዳን ህዝብ እንዴት ይመለከተዋል?
የሱዳን ተቃዋሚዎችና ወታደራዊ ኃይሉ በኢትዮጵያ አደራዳሪነት በድጋሚ በጠረጴዛ ዙሪያ ለመነጋገር ተስማምተዋል።
ሁለቱን የሱዳን ኃይሎች በድጋሚ ወደ ውይይት እንዲመለሱ በማድረጉ ላይ የኢትዮጵያ አስተዋጽኦ ምን ይመስል እንደነበር የጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ልዩ መልእክተኛ በመሆን ካርቱም የሚገኙት አምባሳደር ሙሐሙድ ድሪር ለቢቢሲ አብራርተዋል። አምባሳደር ሙሐሙድ ''ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ ሱዳን በነበራቸው አጭር ቆይታ ሁሉንም ሊባል በሚችል መልኩ የፖለቲካ ኃይሎች አነጋግረዋል'' ይላሉ። ሱዳን ሰላማዊ ሂደት ውስጥ እንድትገባ፣ ሽግግሩ ከመስመር ወጥቶ ወደ ግጭት እንዳያመራ እና ሁሉንም ኃይሎች ለማቀራረብ በማሰብ ኢትዮጵያ የማደራደር ኃላፊነት ውስጥ እንደገባች ይናገራሉ። • በዓመት አንዴ ብቅ የምትለው ከውሃ በታች ያለችው መንደር ኢትዮጵያ ሁለቱን ኃይሎች በማሸማገሉ ላይ ከሌሎች ሃገራት ድጋፍ አግኝታ እንደሆነ የተጠየቁት አምባሳደሩ፤ የኢትዮጵያ መንግሥት እንደ አንድ የአፍሪካ ሃገር የሱዳን ጉዳይ እንደሚያሳስበው ያስረዳሉ። ''ሱዳን የኢጋድ አባል ሃገር እና ጎረቤት ሃገር እንደመሆኗ ይሄንን ጉዳይ በዚህ አስተሳሰብ እና አመለካከት ነው የምንመለከተው።'' ብለዋል። የሱዳንን ወቅታዊ ፖለቲካዊ ለውጥ በቅርበት የሚከታተሉ ተንታኞች፤ ወታደራዊው የሸግግር መንግሥቱ በቅርብ ጊዜ ስልጣኑን ለሲቪል መንግሥት አሳልፎ ላይሰጥ ይችላል ይላሉ። ይህ በአንዲህ እንዳለ ለተቃውሞ አደባባይ የሚወጡ ሰልፈኞች ወታደራዊ የሽግግር መንግሥቱ ስልጣኑን በፍጥነት ለሲቪሎች አሳልፎ እንዲሰጥ እየጠየቁ ይገኛሉ። አምባሳደር ሙሃሙድ ድሪር በርካቶች በሱዳን ጉዳይ የመሰላቸውን ሃሳብ ሊሰጡ ይችላሉ፤ ''በዋናነት ግን የሱዳን ህዝብ፣ የሽግግር መንግሥቱ እና የተቃዋሚ ኃይሉ አሁን የተደረሰበትን ስምምነት እንደ እፎይታ ነው የሚመለከተው። የኢትዮጵያንም ሚና በማድነቅ እና በማመስገን እያየው ነው። በቀጣይም ሁሉም የየበኩሉን እንደሚወጣ ነው የምንገነዘበው።'' ብለዋል። ''ሱዳናውያን ጎረቤት ሃገር ኢትዮጵያ በቁርጥ ቀን ደርሳልናለች የሚል አስተሳሰብ አላቸው'' በማለት አምበሳደር ሙሐሙድ የኢትዮጵያ አሸማጋይነት በሱዳናውያን ዘንድ ተቀባይነት እንዳለው ይናገራሉ። '''ይህ ወገን ስልጣን ላይ ለመቆይት ይፈልጋል፤ ይህ ወገን ሌላኛውን እየተጋፋ ነው' ወደሚል አይነት አደራዳሪነት አንገባም።'' ብለዋል የጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ልዩ መልእክተኛ አምባሳደር ሙሐሙድ ድሪር። አምባሳደር ሙሐመድ ድሪር ትናንት ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት ወታደራዊ የሽግግር መንግሥቱ በቁጥጥር ስር ያዋላቸውን የፖለቲካ እስረኞች ለመልቀቅ ተስማምቷል። ተቃዋሚዎች አሁንም የሲቪል አስተዳደር እንዲመሰረት እየጠየቁ ነው። • የአክሱም ሙስሊሞች ጥያቄ መቼ ምላሽ ያገኝ ይሆን? በተቃዋሚዎችና በወታደሩ መካከል እየተደረገ የነበረው ውይይት የተቋረጠው በርካታ ተቃዋሚ ሰልፈኞች መገደላቸውን ተከትሎ ነበር። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ተቃዋሚዎች በጠሩት ሕዝባዊ አመፅ በርካታ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የስራ ማቆም አድማ ተመትቷል። ሐኪሞች የተገደሉት 118 ሰዎች ናቸው ሲሉ የመንግሥት ባለስልጣናት ግን 61 ሰዎች ከልዩ ኃይሉ በተተኮሰ ጥይት መሞታቸውን ይናገራሉ። ወታደሮች የካርቱምን አውራ ጎዳናዎች የሚጠብቁ ሲሆን በርካታ የንግድ ተቋማት ተዘግተዋል። ማክሰኞ ዕለት ኢትዮጵያ አሸማጋይ ሆና በተቀመጠችበት ጠረጴዛ ሁለቱም ወገኖች የሲቪል አስተዳደር ለመመስረት መስማማታቸው ተነግሯል። ተቃዋሚዎችም ከዛሬ ጀምሮ ዜጎች በሥራ ገበታቸው ላይ እንዲገኙም ጥሪ አቅርበዋል። የሕዝባዊ አመፁን በቅድሚያ የጠራው የሱዳን የሙያ ማህበራት ዜጎች ወደ ሥራ ገበታቸው ይመለሱ የሚለውን ስምምነት ተቀብሎታል። ወታደራዊ ኃይሉ በይፋ ውይይቱን ለመቀጠል መስማማት አለመስማማቱን አልተናገረም። ነገር ግን የሽግግር መንግሥቱ አባል የሆኑት ሳላህ አብደልካሀልክ ለቢቢሲ አረብኛ ፕሮግራም እንደተናገሩት ከተቃዋሚዎች ጋር ስልጣንን እኩል ለመጋራት ስምምነት ላይ ሳይደረስ አልቀረም ብለዋል። • በአማራ ክልል በተከሰቱ ግጭቶች 224 ሰዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ ቢሆንም ግን አሁንም የሽግግር መንግሥቱ ሊቀመንበር ከወታደሩ እንዲሆን እንደሚፈልጉ አልሸሸጉም። ወታደራዊ ኃይሉ ፕሬዝዳንት ኦማር አል በሺርን ከስልጣን በማውረድ ላይ ቁልፍ ሚና የተጫወተ ሲሆን በርካታ የወታደሩ ሹማምንቶች አሁንም በእስር ቤት ይገኛሉ ሲሉ ተናግረዋል። ነገር ግን የሽግግር መንግሥቱ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ለመደራደር ዝግጁ ነው ሲሉ አክለዋል። በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ የአሜሪካ ልዑካን ቡድን ወደ ሱዳን እንደሚያቀናና ሁለቱ ወገኖች ንግግር እንዲጀምሩ ለማድረግ እንደሚጥር አስታውቆ ነበር። አንዳንድ ከሱዳን የሚወጡ ሪፖርቶች እንደሚያሳዩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ 15 አባላት ያሉት የሽግግር ምክር ቤት እንዲቋቋምና ስምንት አባላቱ ከተቃዋሚዎች ሰባቱ ደግሞ ከወታደሩ እንዲሆን ሀሳብ ማቅረባቸው ይነገራል።
news-57065391
https://www.bbc.com/amharic/news-57065391
በሕወሓትና 'ሸኔ' ላይ አቃቤ ሕግ አደረግኩት ያለው ምርመራ ምን ያሳያል?
ጠቅላይ አቃቤ ሕግ በቅርቡ ሽብርተኛ ተብለው የተፈረጁትን ህወሓት እና ሸኔ በተመለከተ ትናንት መግለጫ ሰጥቷል።
በዚህ ሰፋ ባለ መግለጫው ባለፉት ሶስት ዓመታት ሰላማዊ ዜጎች ላይ ባነጣጠሩ ጥቃቶች የበርካታ ዜጎች ሕይወት መጥፋቱን፣ መፈናቀላቸውን እንዲሁም ንብረት መውደሙን ጠቅሶ እነኚህ ጥቃቶች ህብረተሰቡ በነጻነት እንዳይኖር እንዲሁም ዜጎች እርስ በእርስ እንዳይተማመኑ በማድረግ የመንግስትን ህልውና አደጋ ላይ ለመጣል ታቅደው ሲፈፀሙ የነበሩ መሆኑን ከተለያዩ ማስረጃዎች ለመረዳት ተችሏል ብሏል። ጥቃቶቹ በተለያዩ ቡድኖች የተፈፀሙ ቢሆንም ከጀርባቸው ግን በዕቅድ፣ በገንዘብ፣ በሀሳብ እንዲሁም የሚድያ ሽፋን በመስጠት የመሪነት ሚናውን ሲጫወቱ የነበሩ ቡድኖች አሉ ብሏል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ በመግለጫው። መሥሪያ ቤቱ አክሎ የውጭ ኃይሎች እነዚህን ቡድኖች ተጠቅመው ኢትዮጵያን የማመሰቃቀልና የማፍረስ ፍላጎታቸውን እያሰረፁ እንደሆነ ማሳያዎች አሉ ይላል። ጠቅላይ አቃቤ እነዚህ ድርጊቶች የሽብር ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በወጣው አዋጅ ቁጥር 1176/2012 አንቀጽ 3 ስር ስለሽብር የወንጀል ድርጊት የተሰጠውን ትርጓሜ ሙሉ ለሙሉ የሚያሟሉ ናቸው ይላል በመግለጫው። መሥሪያ ቤቱ አክሎ ድርጊቱን የፈፀሙትን በተናጠል ተጠያቂ ከማድረግ ይልቅ ድርጅቶቹን በሽብርተኝነት በመሰየም በህጉ በተቀመጠው አግባብ የሽብር ወንጀል ድርጊትን በተሻለ ሁኔታ ለመቆጣጠር እና ለመከላከል ይቻላል ይላል። ሕወሓት በለውጥ ምክንያት ከሥልጣን ከተነሳ በኋላ 'ጥቅማቸው የተነካባቸው ከፍተኛ አመራሮች ለውጡ ያመጣውን መንግሥት በማንኛውም መንገድ ከሥልጣን ለማስወገድ' መንቀሳቀሳቸውን መግለጫው አትቷል። በዚህም መሠረት ሕወሓት 2011 ዓ.ም የ “ትግራይ ማዕከላዊ ወታደራዊ ኮማንድ” በማለት ሕገወጥ የታጠቀ ሃይል እንዲደራጅ በስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ወስኗል ይላል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ። ጠቅላይ አቃቤ ሕግ በመግለጫው ሕወሓት በጡረታ በተገለሉ ጄኔራሎች እና ኮሎኔሎች እገዛ የትግራይ መከላከያ ሃይል የተባለ ወታደራዊ ሃይል እንደገነባ ያትታል። መግለጫው አክሎ 'ይህ ኃይል ከፍተኛ ወታደራዊ ሥልጠና በመስጠት ለጦርነት ሲዘጋጅና ሲደራጅ ነበር' ይላል። ጠቅላይ አቃቤ ሕጉ ሕወሓት ኅይሉን በተለያዩ መዋቅሮች አደራጅቶ እንደነበርና ደረጃ 1 ሚሊሻ የሚባለው ሰራዊት እድሜያቸው 40 ዓመት ያልበለጡ፣ ሙሉ ጤነኛ የሆኑ እና ጦርነት ላይ ለመሳተፍ የሚችሉ አባላትን የያዘ እንደሆነ ይገልፃል። የተደራጀዉ ወታደራዊ ሃይል በማንኛዉም ሁኔታ የክልል መንግስታት ሊታጠቁ የማይገባውን መካናይዝድ እና የቡድን መሳሪያ ስልጠና በመስጠት ለጦርነት ዝግጅት ሲያደርግ እንደነበርና ይህ ዝግጅት ለሕወሓት ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ እያቀረበ ይገመገም እንደነበር ከወንጀል ምርመራው ሂደት ማረጋገጥ ተችሏል ይላል መግለጫው። ሕወሓት የፌዴራል መንግስትን ለመጣል ከነበረው ጽኑ ምኞት በመነሳት ከወታደራዊ ሃይል ዝግጅቱ ጎን ለጎን ህዝቡ ለጦርነት እንዲዘጋጅ ያደርግ እንደነበርና በክልሉ ይገኝ የነበረው የሃገር መከላከያ ሰራዊት በሚፈለገው ልክ መንቀሳቀስ እንዳይችል በየቦታዉ ኬላዎችን በማቋቋም የሃገር መከላከያ ሰራዊት ፍተሻ እንዲካሄድበት አድርጓል ይላል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ። አሁን በሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀው ሕወሓት ለዓላማው ማስፈፀሚያ ይሆነው ዘንድ የአፋር አብዮታዊ ዲሞክራሲ አንድነት ግንባር (አርዱፍ) ለተባለ ፓርቲ የበጀትና የጦር መሳርያ ድጋፍ ሲያደርግ ነበር ይላል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ በዝርዝር ባወጣው መግለጫ። መሥሪያ ቤቱ፤ ሕወሓት የአማራ ክልልን ሰላም ለማደፍረስም ከተለያዩ አካላት ጋር ስምምነት አድርጎ እንቅስቃሴ ሲያደርግ ቆይቷል ሲልም ይወቅሳል። በዚህም መሠረት የቅማንት ህዝብን ደህንነት ለመጠበቅ በሚል ከፍተኛ ገንዘብ እና የጦር መሳርያ በመመደብ በአካባቢዉ ላይ የሚነሳ ግጭትን በመሳርያ እና ገንዘብ ሲደግፍ እንዲሁም በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን አካባቢ የሚኖር ህዝብ ከአፋር ህዝብ ጋር እንዲጋጭ ግጭት ለማባባስ አስቦ ከ100 በላይ ክላሽንኮቭ መሳርያ ለማስታጠቅ ሙከራ አድርጎ በፀጥታ ሃይሎች ክትትል ውጥኑ ሳይሳካለት ቀርቷል ይላል አቃቤ ሕግ። ከላይ ከተጠቀሱት በተጨማሪ በጋምቤላ እና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዉስጥ ህዝባዊ ግጭት እንዲነሳ በማሰብ በክልሎቹ ለሚንቀሳቀሱ ሁለት ድርጅቶ መሳርያ እና ገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ግጭት ለመቀስቀስ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል ሲል መግለጫው ያብራራል። የአቃቤ ሕግ መግለጫ አክሎ በኦሮሚያ ክልል ከሚንቀሳቀሰዉ በተለምዶ “ሸኔ” ተብሎ የሚጠራው ቡድን ጋር ዉይይት በማደርግ ቡድኑን በገንዘብ እና በመሳርያ በመርዳት የቡድኑን ታጣቂዎች በክልሉ ዉስጥ የሰዉ ህይወት እንዲያጠፉ፣ ንብረት ላይ ጉዳት እንዲያደርሱ እና ዜጎች እንዲፈናቀሉ አድርጓል ይላል። መግለጫው አክሎ ወደ ሰላማዊ ትግል እንዲገባ ጥሪ ተደርጎለት ፈቃደኛ ያልሆነው በተምዶ "ሸኔ" ተብሎ የሚጠራው ቡድን በኦሮሚያ የተለያዩ ዞኖች እና ወረዳዎች ዉስጥ እንዲሁም ከክልሉ ውጪ በመንቀሳቀስ ሰላማዊ ህብረተሰብን በመግደል እና ከቤት ንብረት በማፈናቀል የሽብር ወንጀል ፈፅሟል ይላል። የአቃቤ ሕግ መግለጫ እንደሚለው ቡድኑ በፈፀመው የሽብር ተግባር በ2013 ዓ.ም ብቻ በኦሮሚያ ክልል ውስጥ 463 ሰዎች ላይ አደጋ ደርሷል፡፡ 112 የፖሊስ አባላት፣ 57 ሚሊሻ አባላት እና 18 በተለያየ ደረጃ ላይ ያሉ አመራሮች ህይወት አልፏል፤ 160 መኖርያ ቤቶች 44 ተሽከርካሪዎች እና 84 የመንግስት መስርያ ቤቶች ተቃጥለዋል፡፡ መለግጫው በተጨማሪ ጥቅምት 22 ቀን 2013 ዓ.ም በምዕራብ ወለጋ ጉሊሶ ወረዳ ጋዋ ቃንካ ቀበሌ ንፁሃን ዜጎች ላይ በፈጸመው ጥቃት 36 ንፁሃን ዜጎችን በመግደል እና በርካታ ቤቶች በማቃጠል ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ ሰዉ ከአካባቢዉ እንዲፈናቀል አድርጓል ብሏል። በዚህም መሠረት ሁለቱ ድርጅቶች ማለትም ሕወሓትና በተለምዶ ሸኔ ተብሎ የሚጠራው ቡድን በሕዝብ እንራሴዎች ምክር ቤት አሸባሪ ተብለው እንዲጠሩ መወሰኑን ያወሳል።