id
stringlengths
8
14
url
stringlengths
36
42
title
stringlengths
8
90
summary
stringlengths
6
505
text
stringlengths
133
19.2k
news-53638908
https://www.bbc.com/amharic/news-53638908
ኮሮናቫይረስ፡ የውጭ አገር ተጓዦች የኮቪድ-19 ምርመራ ለማድረግ ፈተና ሆኖባቸዋል
አገራት ድንበሮቻቸውን በጥንቃቄ እየከፈቱ ባሉበት በአሁኑ ወቅት የአየር በረራ መጀመርን ተከትሎ በወጡ አዳዲስ ደንቦች ምክንያት ተጓዦች ከኮቪድ-19 ተህዋሲ ነጻ መሆናቸውን በምርመራ እንዲያረጋግጡ ይገደዳሉ።
በኢትዮጵያ ይህንን ምርመራ በማድረግ ውጤት ከሚሰጡ ተቋማት መካከል የሆነውና አብዛኞቹ የውጭ አገር ተጓዦችን የሚያስተናግደው ተቋም የምርመራ ፈላጊዎች ቁጥርና አገልግሎቱ ተመጣጣኝ እንዳልሆነ ተገልጋዮች እየተናገሩ ነው። የአየር በረራ አገልግሎት ለረጅም ጊዜ ተቋርጦ በመቆየቱ ለወራት ሲጠባበቁ የነበሩ ተጓዦች ይህንን ምርመራ ለማድረግ ከባድ ፈተና ሆኖብናል ይላሉ። ምክንያቱ ደግሞ ምርመራውን የሚያከናውነው ተቋም የወሰደውን ናሙና ውጤት ለማሳወቅ ቢያንስ 48 ሰዓታትን ይፈልጋል። አገራት ደግሞ ተጓዦች ከመሳፈራቸው በፊት ምርመራ እንዲያደርጉ የሚፈልጉበት የሰዓት ገደብ ከ48 ሰዓት እስከ 96 ሰዓት እንደየአገሩ ይለያያል። ምርመራውን ከብዙ ጥበቃ በኋላ ባለፈው አርብ ዕለት ማድረግ የቻሉ ተጓዦች ውጤት አልደረሰም በመባላቸው በረራቸውን ለመሰረዝ እንደተገደዱ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ክሊኒኩ ለተመርማሪዎች ውጤት የሚሰጠው የጉዞው ዕለት ወይም ከአንድ ቀን ቀደም ብሎ በ10 ሰዓት ብቻ ነው። በዚህም ምክንያት የጉዞ ቀን፣ የሚጓዙበት አገር የምርመራ ደንብና የክሊኒኩ ውጤት መስጫ ዕለት ለማጣጣም ፈታኝ እንደሆነ ተጓዦቹ ጠቅሰዋል። ቢቢሲ ሰኞ ማለዳ ከንጋቱ 11፡00 ሰዓት ጀምሮ ምርመራ በሚሰጠው ተቋም ደጃፍ ላይ ተሰልፈው ያገኛቸው ተጓዦች ተቋሙ ስለምርመራው በቂ መረጃ እንዳልሰጣቸው፣ በረራቸውን በተደጋጋሚ ለመሰረዝ እንደተገደዱና ላልተጠበቀ ወጪና መጉላላት እንደተዳረጉ ገልጸዋል። አገልግሎቱን ፈልገው ወደተቋሙ የሄዱ ሰዎች ለቢቢሲ እንደገለጹት ምርመራውን የሚያደርገው ላቦራቶሪ ሥራውን የሚያስኬድበት ግልጽ አሰራር እንዳልዘረጋም ተናግረዋል። አገልግሎት ፈላጊዎች የሚስተናገዱት በቅድሚያ በኢሜይልና በስልክ ከተመዘገቡና የጉዞ ትኬታትና የፓስፖርታቸውን ቅጂ ከሰጡ በኋላ ነው የሚል ማስታወቂያ በክሊኒኩ ደጃፍ ላይ የተለጠፈ ቢሆንም፤ በክሊኒኩ የማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ የተጠቀሱት የስልክ መስመሮች ከአገልግሎት ወጪ ናቸው አልያም ተዘግተዋል። የኢሜይል ምላሽም ከክሊኒኩ ማግኘት አልተቻለም። የቢቢሲ ዘጋቢዎችም ይህንኑ ማረጋገጥ ችለዋል። የክሊኒኩ ሠራተኞች በበኩላቸው ሰዎች ከተመዘገቡ በኋላ በራሳቸው ምክንያት ሊቀሩ ስለሚችሉ ይህንን የቅድመ ምዝገባ አሰራር ትተን ሰዎች እንደ አመጣጣቸው ማስተናገድ ጀምረናል ይላሉ። ሰኞ ማለዳ በስፍራው ተሰልፈው ከነበሩ ተጓዦች ቢቢሲ እንደተረዳው አንዳንዶቹ ተገልጋዮች እሑድ ከቀትር ጀምሮ ለረዥም ሰዓት አገልግሎቱን ለማግኘት በዝናብ ተሰልፈው የጠበቁ ቢሆንም "አሁን ደክሞናል ከዚህ በላይ አናስተናግድም" በሚል እንዲበተኑ ተደርገዋል። ሌሎች ደግሞ ነገ በአዲስ መልክ አንሰለፍም በሚል ቅሬታ በማንሳታቸውና የክሊኒኩን በር አናዘጋም በማለታቸው ስም ዝርዝራቸው ተጽፎ በቀጣይ ቀን ቅድሚያ ተሰጥቷቸው እንደሚስተናገዱ ቃል እንደተገባላቸው ተናግረዋል። ክሊኒኩ በዚህ መንገድ ተገልጋዮቹን ካሰናበተ በኋላ የተወሰኑ ሰዎችን "አሾልኮ እንዳስገባና አገልግሎት እንደሰጣቸው" በቦታው ነበርኩ ያሉ እማኝ ተናግረዋል። በአካባቢው የሚገኙ የመኪና አስተናባሪዎችና የጎዳና ተዳዳሪዎች የችግሩን ስፋት በመረዳት በጠዋት ወረፋ በመያዝ ሰልፋቸውን እስከ 200 ብር እየሸጡ እንደሚገኙ ተገልጋዮች ይናገራሉ። የምርመራ አገልግሎት ሰጪው ተቋም በርካታ ለምርመራ የሚመጡ ሰዎች በሚስተናገዱበት በአንደኛው ቅርንጫፉ በሁለት ነርሶችና በሁለት ናሙና ሰብሳቢዎች ብቻ አገልግሎቱን እየሰጠ እንደሆነና የሚሰጠው ምርመራው አገልግሎቱን ከሚፈልገው ሰው ጋር ተመጣጣኝ እንዳልሆነ ቢቢሲ ለመታዘብ ችሏል። የቢቢሲ ዘጋቢ ሰኞ ማለዳ በስፍራው እንደተመለከተ የአገልግሎት ደረሰኝ ወረቀት ማተሚያ ማሽን ብልሽት ገጥሟል በሚልም ክሊኒኩ ለግማሽ ሰዓት ያህል ሥራውን አቁሞ ነበር። ክሊኒኩ ምንሊክ ሆስፒታል አካባቢና ቡልጋሪያ ባሉት ቅርንጫፎቹ የምርመራ አገልግሎት ይሰጣል ቢባልም የሌሎች ቅርንጫፎቹ ተገልጋዮች ከሌሎች ቅርንጫፎች ይልቅ ወደ አንደኛው ክሊኒክ በብዛት ሄደው ምርመራ ለማግኘት እየጣሩ ነው። "ወደ ሌላ ቅርንጫፍ ሄደን እድላችንን እንሞክር ስንላቸውም መልስ አይሰጡንም፣ መረጃ እንኳን ማግኘት ብርቅ ነው" ይላሉ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ ተገልጋይ። ሰኞ በዚህ ቅርንጫፍ ረዣዥም ሰልፎች የነበሩ ሲሆን በምንሊክ ሆስፒታል አካባቢ በሚገኘው የክሊኒኩ ቅርንጫፍ ግን የተገልጋዩ ቁጥር አነስተኛ ሆኖ ታይቷል። ክሊኒኩ ተመርማሪዎችን አንድ ሺህ ሦስት መቶ ሃያ ብር ለአገልግሎቱ ካስከፈለ በኋላ ውጤቱን የሚሰጠው ከ48 ሰዓታት በኋላ እንቁላል ፋብሪካ አካባቢ በሚገኘው ቅርንጫፉ ብቻ ነው። ጠዋት በረራ ያላቸው ሰዎች ውጤት ስለማይደርስላቸው በብዛት ለድጋሚ የትኬት ማስቀየሪያ ወጪ፣ እንዲሁም ለሌላ አዲስ ምርመራ ወጪ እየተዳረጉ መሆናቸውን ቢቢሲ ካናገራቸው ሰዎች ለመረዳት ችሏል። ቢቢሲ ምርመራውን ከሚሰጠው የኢንተርናሽናል ክሊኒካል ላቦራቶሪስ ምላሽ ለማግኘት በማስታወቂያ ሰሌዳቸው ላይ ባሰፈሩት የስልክ አድራሻ በተደጋጋሚ ቢደውልም ቁጥሩ ስለማይሰራ መልስ ማግኘት አልቻለም።
news-55347651
https://www.bbc.com/amharic/news-55347651
የአንድ ቢትኮይን ዋጋ ከ20ሺህ ዶላር በላይ ሆነ
ቢትኮይን በዚህ ዓመት ዋጋው በ170 በመቶ ከፍ በማለት የአንድ ቢትኮይን ዋጋ ከ20 ሺህ ዶላር በላይ ሆነ።
ይህ ቨርቿል ከረንሲ ዋጋው የጨመረው የድርሻ ገበያዎች እየተንኮታኮቱ በሚገኙበት ወቅት ነው። ትናንት ዋጋው በ4.5 በመቶ በመጨመር አንድ የቢትኮይን ዋጋ 20 ሺህ 440 ሆኖ ነበር። ዋጋው በከፍተኛ ሁኔታ የሚዋዥቀው ይህ ዲጂታል ከረንሲ እአአ 2017 ላይም በተመሳሳይ ዋጋው በከፍተኛ ፍጥነት ጨምሮ የአንድ ቢትኮይን ዋጋ ከ20 ሺህ ዶላር ለመሻገር ተቃርቦ ነበር። ይህ በእንዲህ እንዳለ ዲጂታል ከረንሲው ከዚህ ቀደም ዋጋው በአስደንጋጭ መጠን ወርዶ እስከ 3ሺህ 300 ዶላር ድረስ ተገምቶ ነበር። እንደ ማይክሮሶፍት፣ ስታርባክስ እና ፔይፓል ያሉ ግዙፍ ኩባንያዎች ዲጅታል ከረንሲውን ለግብይት መጠቀም መጀመራቸው የቢትኮይን ዋጋ ሊጠናከረው እንደሚችል ይጠበቃል። በሌላ በኩል ቢትኮይን ግብይት ለመፈጸም መዋል የለበትም የሚሉ አሉ። የባንክ ኦፍ ኢንግላንድ ገዢ አንድሪው ቢሊ የቢትኮይን ዋጋ በከፍተኛ ደረጃ ከፍ እና ዝቅ ስለሚል ሰዎች ዲጂታል ከረንሲውን ለግብይት መጠቀማቸው እንደሚያሳስባቸው ተናግረዋል። ቢትኮይን እአአ 2009 ላይ ከተፈጠረ ወዲህ በአማካይ እድገትን ሲያሳይ ቆይቷል። በዚህ ዓመት ደግሞ ዋጋው ታይቶ የማይታወቅ ጣሪያን ነክቷል። 'ኮምፒቲቲቭ ኮምፕሊያንስ' የተሰኘ አማካሪ ድርጅት መስራች የሆኑት ያና አፍናሲዬቫ የቢትኮይን ዋጋ በቀጣይ ወራትም ሊጨምር እና ሊቀንስ ይችላል ብለዋል። በአሁኑ ሰዓት በርካታ አይነት ክሪፕቶካረንሲዎች (ዲጂታል ገንዘቦች) አሉ። በስፋት ከሚታወቁት መካከል አንዱ ቢትኮይን ነው። ቢትኮይን ማለት በቀላል ቋንቋ፤ ዲጂታል+ገንዘብ+መገበያያ በማለት ማጠቃለል ይቻላል። ይህ መገበያያ በኪሳችን ተሸክመን እንደምንዞረው የብር ኖት ወይም ሳንቲም ሳይሆን 'ኦንላይን' የሚቀመጥ ዲጂታል ገንዘብ ነው። ሌላው የቢትኮይንና የተቀሩት የክሪይፕቶከረንሲዎች ልዩ ባህሪ በመንግሥታት እና በባንኮች አለመታተማቸው እንዲሁም ቁጥጥር አለመደረጉ ነው። ቢትኮይን የሚፈጠረው 'ማይኒንግ' በሚባል ሂደት ነው። በመላው ዓለም በኔትወርክ በተሳሰሩ ኮምፒውተሮች ቁጥጥር ይደረግበታል። ባለፉት ዓመታት ዋጋ በፍጥነት ሲጨምር ለዋጋው መጨመር ምክንያቱ በትክክል ይህ ነው ማለት አልተቻለም። አንዳንድ የምጣኔ ሃብት ባለሙያዎች ግን ኢንቨስተሮች ''እድሉ እንዳያልፋቸው'' ከሚገባው በላይ ፈሰስ እያደረጉበት ነው የሚል ምክንያት ያቀርባሉ። ሌሎች ደግሞ የቢትኮይን ተቀባይነት እየጨመረ በመምጣቱ ዋጋው እንደጨመረ ያስቀምጣሉ። ቢትኮይን እንደ ስጋት? አሸረትስ በተባለ የፋይናንስ ተቆጣጣሪ ኩባንያ ውስጥ ባለሙያ የሆኑት ብራደሊይ ራይስ በቢትኮይን ላይ ምንም አይነት ቁጥጥር እንደማይደረግበት ያስታውሳሉ። ቢትኮይንን በመጠቀም የገዢው ማንነት ይፋ ሳይደረግ በየትኛውም ሰዓት እና በየትኛውም ስፍራ የቢትኮይን ዝውውር ማድረግ ይቻላል። የግዢው ማንነት ይፋ ሳይደረግ ግብይት መፈጸም ይቻላል። በዚህም ሕገ-ወጥ ቡድኖች የጦር መሳሪያዎች እና እጾችን ሊገዙ እና ሊሽጡ ይቻላሉ፣ ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር እና አሸባሪዎችን ለመደገፍ ያስችላል በማለት ቢትኮይንን ጨምሮ ሌሎች ክሪይፕቶከረንሲዎች ላይ ያላቸውን ስጋት የሚያነሱ በርካቶች ናቸው።
54094328
https://www.bbc.com/amharic/54094328
የኤርትራ መንግሥት በሃይማኖታቸው ምክንያት ያሰራቸውን 20 ያህል ግለሰቦች ለቀቀ
የኤርትራ መንግሥት በእምነታቸው ምክንያት ለዓመታት አስሯቸው የነበሩ ከ20 በላይ ግለሰቦችን መለቀቁን የተለያዩ ምንጮች ለቢቢሲ ገለፁ።
ታሳሪዎቹ አብዛኞቹ ከወንጌላውያን እና ጴንጤቆስጣል ቤተ እምነቶች እንደነበሩ ጨምረው አረጋግጠዋል። ከእነዚህ ግለሰቦች መካከል የተወሰኑትም ከአስመራ ውጪ ታስረው መቆየታቸው ቢቢሲ ያገኘው መረጃ ያሳያል። ኑሮው በአሜሪካ የሆነው እና በኤርትራ ስላለ የእምነት ነጻነት የሚከራከረው ሃኒባል ዳንኤል እንደሚለው ከሆነ ከእስር ከተለቀቁት ግለሰቦች መካከል ለ16 ዓመታት ታስረው የቆዩ ይገኙበታል። የኤርትራ መንግሥት በይፋ ስለ እስረኞቹ መለቀቅ ያለው ነገር የለም። ቢቢሲ ኤርትራ ውስጥ ካሉ ምንጮች እንዳጣራው ግለሰቦቹ የዋስትና መብታቸው ተጠብቆላቸው ነው የተለቀቁት። ለዋስትና ማስያዣነት የተጠየቀው የቤት ባለቤትነት ወይንም የንግድ ፈቃድ መሆኑንም ምንጮቻችን ጨምረው ገልፀዋል። የእምነት ነጻነት እንዲኖር የሚሰሩ አካላት በበኩላቸው በኤርትራ ሶስት የይሖዋ እምነት ምስክር አባላት ከ25 ዓመት በላይ በእስር ላይ እንዳሉ ይናገራሉ። እንደ ሃኒባል ከሆነ ለእስረኞቹ መፈታት ምክንያት ሊሆን የሚችለው የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ስርጭት ይሆናል ሲል ግምቱን ሰጥቷል። በኤርትራ መንግሥት እውቅና ያላቸው የኦርቶዶክስ ክርስትና፣ ካቶሊክ፣ ሉትራን እና እስልምና ሃይማኖቶች ብቻ ናቸው። እኤአ ከ2002 ጀምሮ ከእነዚህ ሃይማኖቶች ውጪ ያሉ በአጠቃላይ እምነታቸውን በይፋ ለማካሄድ ህጋዊ እውቅና ተነፍገዋል። የኤርትራ መንግሥት በ1994 ላይ የጴንጤቆስጤ አብያተ ክርስትያናትን ሙሉ በሙሉ መዝጋቱ ይታወሳል። በዚህም የተነሳ ለአምልኮ ስርዓት ወይንም የተለያዩ ማህበራዊ ህይወቶቻቸውን ተሰባስቦ ማከናወን መከልከላቸውን የዓለም አቀፍ ሃይማኖቶች ነጻነት ላይ የሚሰራው የአሜሪካው ተቋም፣ USCIRF ገልጿል። የኤርትራ መንግሥት በአገሪቱ አለ ስለሚባለው የሃይማኖት ነጻነት ጥሰት ውንጀላ ያስተባብላል። የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት በኤርትራ 1,200 እስከ 3,000 የሚሆኑ ሰዎች በእምነታቸው የተነሳ መታሰራቸውን ይገምታል። የሰብዓዊ መብት ቡድኖች የኤርትራ መንግሥት በሺህ የሚቆጠሩ ግለሰቦችን በሐይማኖት እና ፖለቲካ ምክንያት አስሯል ሲሉ ይወቅሳሉ። በጉዳዩ ዙሪያ ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት የኤርትራ መንግሥትን ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።
42874257
https://www.bbc.com/amharic/42874257
በሞባይል ኢንተርኔት መቋረጥ የተገደቡ እንቅስቃሴዎች
ከአዲስ አበባ ውጭ ባሉ ትላልቅ ከተሞች የሞባይል ኢንተርኔት ከተቋረጠ ከአንድ ወር በላይ እንደሆነና በዚህ መቸገራቸውንም ብዙዎች ይገልፃሉ። ቢቢሲ ያነጋገራቸው የተለያዩ ከተሞች ኗሪዎችም ይህንኑ አረጋግጠዋል።
እነዚህ ሰዎች እንደሚሉት የሞባይል ዳታ ኢንተርኔት መጠቀም አለመቻላቸው በብዙ መልኩ ተፅእኖ አሳድሮባቸዋል። ተማሪዎች ተጨማሪ ንባብ ማድረግ፤ መረጃዎችን ማግኘትም አልቻሉም። በስልካቸው ኢንተርኔት የግል ሥራቸውን የሚያሳልጡም መቸገራቸውን እንዲሁም በቀላሉ መገናኘት ባለመቻላቸውም ማህበራዊ ግንኙነታቸው እንደተጎዳ የገለፁም አሉ። በሃዋሳ ከተማ ውስጥ በሚገኝ የግል ባንክ ውስጥ ሰራተኛ የሆነችው ሊዲያ ሳሙኤል ሥራ ለመፈለግም ሆነ መረጃ ለማግኘት ከዚህ በፊት የተለያዩ ድረ-ገፆችን ትከታተል እንደነበር አሁን ግን የኢንተርኔት ሞባይል ዳታ ስለተቋረጠ ይህን ማድረግ አለመቻሏን ትናገራለች። በተጨማሪም የኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጥ ትምህርቷ ላይም ተፅኖ አለው።"የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርቴን ለማጠናቀቅ ጥናት እያደረግኩ ነው። ለዚህ መረጃ ያስፈልገኛል። ይሁን እንጂ ከሥራ ወጥቼ ዋይፋይ ሳስስ ነው ጊዜዬን የማጠፋው" ትላለች ሊዲያ። ቤተሰቦቻቸውና የቅርብ ጓደኞቻቸው ውጭ አገር ያሉት ሰዎችም በሞባይል ዳታ ኢንተርኔት መቋረጥ ምክንያት እንደቀድሞ መገናኘት አለመቻላቸውን ይናገራሉ። ስሟ እንዲገለፅ ያልፈለገች የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ገላኔ ፉፋ የተባለች የሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንደሚሉት ቤተሰቦቻቸው ካልደወሉላቸው በስተቀር መገናኘት አለመቻላቸውንም ያስረዳሉ። "ዶርማችን ቁጭ ብለን በሞባይል ኢንተርኔት በምናገኘው መረጃ የቤት ሥራዎችን እንሰራ ነበር። ተጨማሪ እውቀት ለማግኘትም መረጃ እናገኝ ነበር" የምትለው ገላኔ አሁን ግን ኢንተርኔት ለማግኘት ወጥተው በምሽት ዋይ ፋይ ያለበት ለመሄድ እንደሚገደዱ ትናገራለች። በመቀለ ኗሪ የሆነው አቶ ፍፁም ብርሃነ ደግሞ ከአንድ ወር በፊት በአዲግራት ዩኒቨርሲቲ የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ በመቀሌና በሌሎች የትግራይ አካባቢዎች የሞባይል ኢንተርኔትና ሲዲኤምኤ መጠቀም እንዳልተቻለ ይናገራል። "ኢሜል የምላላከው በሞባይል ኢንተርኔት ነበር። አሁን ግን ብሮድባንድ ኢንተርኔት ወዳለበት መሄድ ግድ ብሎኛል። ይህ ደግሞ ያላግባብ ጊዜዬን እንዳባክን አድርጓል" ይላል ፍፁም። አገራዊና ዓለምአቀፋዊ አዳዲስ መረጃዎችን ከፌስቡክና ከሌሎች ማህበራዊ ሚዲያዎች ማግኘት ስላልተቻለ እንደዚህ ያሉ ነገሮችን ከአዲስ አበባ ሰዎች እየነገሩት እንደሆነም አመልክቷል። "ይህ አገልግሎት ለምን እንደተቋረጠ አናውቅም። እንደ ምገምተው ግን አገሪቱን የገጠማት ያለመረጋጋት እንዳይስፋፋ ሊሆን ይችላል። ቢሆንም ግን ኢንተርኔት መዝጋት መፍትሄ አይሆንም"ይላል አቶ ፍፁም። በደሴ ከተማ የሞባይል ዳታ ኢንተርኔት ከተቋረጠ ሦስት ወር እንደሆነና በንግድ ሥራቸው ላይ ጉዳት እንዳስከተለ እንደዚሁም ከመንግሥት ሚዲያ ውጭ የተለያዩ የማህበራዊ ድረ ገፅ መረጃዎችን ማግኘት አስቸጋሪ እንደሆነ የከተማዋ ነዋሪዎች ለቢቢሲ ገለፀዋል። ስሙ እንዲጠቀስ የማይፈልገው የጊንጪ ከተማ ነዋሪም መላ ቤተሰቡ አሜሪካ እንደሚገኝና ከእነሱ ጋር ያለው ግንኙነት ላለፉት ሁለት ወራት መቋረጡን ይናገራል። "እናቴ፣ አባቴ፣ እህትና ወንድሞቼ አሜሪካ ነው የሚኖሩት። እኔ በምኖርበት ጊንጪ ደግሞ የሞባይል ዳታ ኢንተርኔት የተቋረጠው ከሁለት ወር በፊት ስለሆነ እንደ ድሮ ቤተሰቦቼን ማግኘት አልቻልኩም" ይላል። እሱ እንደሚለው በቀጥታ መስመር ተደዋውሎ መገናኘት ከወጪው አንፃር የማይታሰብ ነው። የአዳማው ነዋሪው ቤኛ ደግሞ በአገሪቱ ውስጥ ላለው የፖለቲካ አለመረጋጋት ምክንያት ኢንተርኔትን መዝጋት መፍትሄ እንደማይሆን ይናገራል። "አዲስ አበባ ብቻ ነው ሞባይል ዳታ ኢንተርኔት የሚሰራው። እሱንም ከተፅኖ ለማምለጥ ይሆናል ያልዘጉት። ቀድሞውንም አገሪቱ የኢንተርኔት ተደራሽነት ዝቅተኛ ነው። ይህ እርምጃ ደግሞ ነገሩን በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ አድርጎታል። ይህ ውሳኔ ህዝቡንም አገሪቱንም ይጎዳታል" ይላል ቤኛ። በተለያዩ ከተሞች የሞባይል ኢንተርኔት ከተቋረጠ አንድ ወር ሆኖታል መባሉን በተመለከተ የጠየቅናቸው የኢትዮ ቴሌኮም ኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ሃላፊ አቶ አብዱራሂም አህመድ ከአንድ ሰዓት በኋላ ደውሉልኝ ቢሉም ባሉት ሰዓት ስልካቸው ተዘግቷል። ከዚያ በኋላም ደጋግመን ብንሞክርም ስልካቸው ስለማይነሳ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም። በማህበራዊ ድረ ገፆች ለብዙዎች የዕለት ተለት እንቅስቃሴ ጠቃሚ የሆኑ መረጃዎችን የሚሰጡ፤ ለበጎ አላማ ሰዎችን የሚያስተባብሩ እንዲሁም የትምህርትና የሥራ እድልን የሚመለከቱ መረጃዎችን የሚያጋሩ ሰዎች እንቅስቃሴም በሞባይል ኢንተርኔት መዘጋት ተገድቧል። አብዛኛውን ጊዜ መገናኛ ብዙሃን ምን ዘገቡ ብለው ቅኝታቸውን በስልክ የሚያደርጉ ሰዎች የሞባይል ዳታ ኢንተርኔት መዘጋት ተፅእኖ ያሳድሮባቸዋል። ከንግድ፣ ከጤና፣ ከፖለቲካና ከማህበራዊ ሁነቶች አንፃር ብዙዎች ከስልካቸውና ከኢንተርኔት ጋር ያለቸው ቁርኝት ከፍተኛ በሆነበት በዚህ ጊዜ የሞባይል ዳታ ኢንተርኔት ከአንድ ወርና ከዚያም በላይ ለሆነ ጊዜ መቋረጡ ተፅእኖው ከባድ እንደሆነ ቢቢሲ ያናገራቸው የተለያዩ ከተሞች ነዋሪዎች ገልፀዋል። •ኢትዮጵያ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎችን በመበደል ከዓለም ቀዳሚ ሃገራት አንዷ ነች ተባለ
news-56599702
https://www.bbc.com/amharic/news-56599702
ትግራይ፡ ኢትዮጵያ ሠራዊት ግድያ መፈጸሙን ማስረጃዎች አመለከቱ
የቢቢሲ 'አፍሪካ አይ' ፕሮግራም ባደረገው ምርመራ በሰሜን ኢትዮጵያ የተፈጸመ አንድ ጭፍጨፋ በኢትዮጵያ ሠራዊት አባላት መፈጸሙን የሚያመለክቱ ማስረጃዎች አግኝቷል። በዚህም ቢያንስ 15 ወንዶች የተገደሉበትን ትክክለኛውን ቦታ ለመለየት ችሏል።
በወታደሮቹ የተያዙት የሲቪል ልብስ የለበሱ ሰዎች ከግድያው በፊት የታጠቁና የወታደር የደንብ ልብስ የለበሱ ሰዎች ያልታጠቁ ወንዶችን ከአንድ የገደል አፋፍ ላይ በመውሰድ አንዳንዶቹን ላይ በቅርብ ርቀት በመተኮስ አስከሬኖችን ወደ ገደል ገፍተው ሲጨምሩ የሚያሳይ ቪዲዮ በየካቲት ወር መጨረሻ ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ታይቶ ነበር። ቢቢሲ ይህ ድርጊት የተፈጸመው የኢትዮጵያ ሠራዊት የህወሓት ኃይሎችን እየተዋጋ ባለበት ትግራይ ክልል ውስጥ ማኅበረ ዴጎ ከተባለች ከተማ አቅራቢያ መሆኑን አረጋግጧል። ቢቢሲ ያገኛቸውን ማስረጃዎች ለኢትዮጵያ መንግሥት በማቅረብ ምላሽ የጠየቀ ሲሆን መንግሥት "በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የወጡ ነገሮችና ክሶች እንደ ማስረጃ ሊወሰዱ አይችሉም" በማለት "ገለልተኛ ምርመራዎችን ለማካሄድ የትግራይ ክልል ክፍት ነው" ሲል መልሷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው እንደተናገሩት፣ ትግራይ ውስጥ በኢትዮጵያ ሠራዊት ተፈጸሙ ስለተባሉት ጥፋቶች አስፈላጊው ምርመራ ተደርጎ አጥፊዎች በሕግ እንደሚጠየቁ መናገራቸው ይታወሳል። ትግራይ ውስጥ ግጭቱ የተቀሰቀሰው የህወሓት ኃይሎች በመንግሥት ጦር ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ወታደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ ካዘዙ በኋላ ነበር። ህወሓትም የጠቅላይ ሚኒስትሩን እርምጃ በመቃወም "ትግሉን እንደሚቀጥል" ገልጾ ነበር። የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር እንዳለው ግጭቱ አስካሁን ድረስ ከሁለት ሚሊዮን ሰዎች በላይ እንዲፈናቀሉ ያደረገ ሲሆን፤ ከአራት ሚሊዮን በላይ የሚሆኑትን ደግሞ የሰብአዊ እርዳታ እንዲጠብቁ አድርጓቸዋል። የአካባቢው መልክአ ምድር በከፊል ቪዲዮው ላይ የተያው አካባቢ ከሳተላይት ከተገኘ ምስል ጋር ሲመሳከር ቪዲዮው የተቀረጸበትን ሥፍራ መለየት የቢቢሲ 'አፍሪካ አይ' የምርመራ ጋዜጠኞች ቡድን፤ ቤሊንግካት እና ኒውሲ ከተባሉ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት ተንታኞች ጋር በመሆን ጭፍጨፋው የተፈጸመበትን ሥፍራ ለመለየት የተለያዩ ተግባራት አከናውኗል። ቪዲዮውን በመጀመሪያ ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ያወጡት ሰዎች ምስሉ የተቀረጸው ማኅበረ ዴጎ ከተባለ ቦታ አቅራቢያ መሆኑን ገልጸው ነበር። አፍሪካ አይም ጥርጊያ መንገድን፣ ኮረብታዎችን፣ ገደላማ ቦታዎችን ለየት ከሚያደርጋቸው ሁኔታና የከተማዋ አቅራቢያ የሚያሳዩ የሳተላይት ምስሎችን ጨምሮ በቪዲዮው ላይ የሚታዩትን መልክአ ምድራዊ ገጽታዎችን መርምሯል። የታጠቁት ወታደሮች የጥላ አቅጣጫና ርዝመት ድርጊቱ የተፈጸመበትን ሰዓት ለመለየት የረዳ ሲሆን፤ የገደላማ አካባቢው ከሰሜን ወደ ደቡብ የተዘረጋ በመሆኑ የአፍሪካ አይ ቡድን ትክክለኛውን ቦታ ለማወቅ አስችሎታል። በቪዲዮው ላይ የተራሮችን ቅርጽ ተከትሎ መስመር በማስመር የአካባቢውን መልክአ ምድር በሚያሳይ የማመሳከሪያ ካርታ ላይ ተመሳሳይ መስመር ሲሰመር አንድ ዓይነት መሆናቸው ተረጋግጧል። በአካባቢው ያለ የደረቀ የወንዝ መውረጃ መስመር፣ እጽዋቶችና የዛፎች አቀማመጥ በተጨማሪ ስፍራውን ለመለየት ጠቅመዋል። ቢቢሲ አንድ የማኅበረ ዴጎ ነዋሪን በስልክ ያነጋገረ ሲሆን፤ እሱም የኢትዮጵያ ሠራዊት በጥር ወር ላይ ሦስት ዘመዶቹን ጨምሮ 73 ሰዎችን ከከተማው ይዘው መውሰዳቸውን ገልጾ ሰዎቹ እሰካሁን የት እንዳሉ እንደማይታወቅ ተናግሯል። በተጨማሪም በከተማዋ አቅራቢያ በምትገኝ መንደር ውስጥ ነዋሪ የሆነ ሌላ ግለሰብ ወንድሙ በጭፍጨፋው ከተገደሉት መካከል እንደሆነ ለቢቢሲ ገልጿል። ግድያው የተፈጸመው ጥር ወር ላይ ማኅበረ ዴጎ ውስጥ እንደሆነም አስረድቷል። "ከገደሉ አፋፍ ላይ ነበር የገደሏቸው" ብሏል። ከቪዲዮ ላይ ከተገኘ ምስል ጋር ሲመሳከር በአካባቢው ያለው በእጸዋት የተሸፈነ ቦታ ከሳተላይ ምስል ጋር ሲመሳከር ወታደሮቹንና የሞቱትን ሰዎች መለየት አፍሪካ አይ በቪዲዮው ላይ የሚታዩትን የታጠቁ ወታደሮች ማንነት ለማረጋገጥ ባይችልም፤ ከለበሱት የደንብ ልብስና የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ቀለም ያለው በክንዳቸው ላይ ያረፈ አርማን በማየት የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ከሚለብሰው የደንብ ልብስ ጋር ተመሳሳይ ሆኖ አግኝቶታል። በደንብ ልብሱ ላይ ያለው የስፌት አይነትና ኪሶቹም ከኢትዮጵያ ሠራዊት ልብስ ጋር ይመሳሰላሉ። ከመካከላቸው አንደኛው ያደረገው አረንጓዴ ኮፍያና ላዩ ላይ ያለው አርማ ሠራዊቱ ከሚጠቀመው ጋር የቀረበ መመሳሰል አለው። ወታደሮቹ የሚነጋገሩት በአማርኛ ሲሆን በቪዲዮዎቹ ላይ መሬት ላይ እንዲቀመጡ ከተደረጉት ካልታጠቁት ሰዎች ዙሪያ ቆመው እርስ በርስ ሲያወሩ ይሰማሉ። "እነዚህን ሰዎች መልቀቅ የለብንም። አንዳቸውም መትረፍ የለባቸውም" ይላል አንድ ለካሜራው የቀረበ ድምጽ። "እንዴት እንደሞቱ የሚያሳይ ቪዲዮ መቅረጽ አለብን" ይላል ሌላኛው ድምጽ። ሌሎች ቪዲዮዎች ደግሞ ያልታጠቁት ሰዎች መሳሪያ ተደግኖባቸው ወደ ገደሉ ጫፍ ሲወሰዱና የታጠቁት ሰዎች በርካታ እስረኞችን ሲገድሉና አስከሬናቸውን ወደ ገደሉ ሲጥሉ ያሳያሉ። በቪዲዮው አንዳንድ ክፍሎች ላይ ታጣቂዎቹ ተጠግተው አስከሬኖቹ ላይ ሲተኩሱ የሚታይ ሲሆን በሌላ ላይ ደግሞ ሟቾቹን ሲሳደቡና ሲሳልቁባቸው ይሰማል። "ጋዝ አርከፍክፈን ማቃጠል ብንችል ደስ ይለኛል" ይላል ለካሜራው የቀረበው ድምጽ። "እነዚህን ሰዎች ለማቃጠል ጋዝ ቢኖር ኖሮ ጥሩ ነበር" በማለት ሌላኛው ድምጽ ይመልሳል። "እንደ ሕንዶች አስከሬናቸውን ማቃጠል ነበር።" የሲቪል ልብስ ለብሰው የሚታዩትና የተገደሉት ሰዎች ማንነት አይታወቅም። በታጣቂዎቹ የተያዙት ሰዎች በትግርኛ ሲነጋገሩ የሚሰሙ ሲሆን በቪዲዮው ላይ ወታደሮቹ የያዟቸው ሰዎች የህወሓት አባላት እንደሆኑ እንደሚያምኑ አመላካች ነገሮች አሉ። "ይህ የወያኔ መጨረሻ ነው" ሲል ከታጣቂዎቹ መካከል አንዱ ይሰማል። "ምህረት የለንም።" የሂዩማን ራይትስ ዋች የአፍሪካ ቀንድ ኃላፊ የሆነችው ላቲሻ ባደር ለቢቢሲ እንደተናገረችው በቅርብ ወራት ውስጥ በክልሉ "በጣም ከፍተኛ የመብት ጥሰቶች መፈጸማቸውን" ታዛቢዎች መመልከታቸውን ገልጻ፤ ነገር ግን ይህ ቪዲዮ "በተለይ አስደንጋጭ" ነው ብላለች። "በቁጥጥር ስር የዋሉ ያልታጠቁ ሰዎች ሲገደሉ አይተናል" ያለችው ላቲሻ "በቪዲዮዎቹ ላይ የተመለከትናቸው ነገሮች የጦር ወንጀል ሊሆኑ ስለሚችሉ ክስተቱ ተጨማሪ ምርመራን የሚፈልግ ነው" ስትል ገልጻለች። በኢትዮጵያ ሠራዊት አባላት የሚለብሱት የደንብ ልብስና አርማ በቪዲዮው ላይ ካለው ጋር ይመሳሰላል
news-55914757
https://www.bbc.com/amharic/news-55914757
ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በስደተኞች ጉዳይ አዳዲስ መመሪያዎች አስተላለፉ
ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የትራምፕ አስተዳደራዊ ውሳኔ ያረፈባቸውን ፊርማዎች መቅደዳቸውን ቀጥለዋል፡፡
ዛሬ ደግሞ በስደተኞች ጉዳይ ላይ ከዚህ ቀደም የትራምፕ አስተዳደር ያሳለፋቸውን ጥብቅ ውሳኔዎች ሽረው አዲስ የአስተዳደር መመርያዎችን አሳልፈዋል፡፡ ከነዚህ መሀል በዋንኛነት የተቀመጠው ልጆችን ከወላጆቻው የነጠለው የስደተኞች ጉዳይ ነው፡፡ ወላጆችና ልጆች የሆኑ ስደተኞች ተለያይተው የቀሩት በትራምፕ ጊዜ በወጣ የስደተኞች ፖሊሲ ምክንያት ነበር፡፡ አሁን ባይደን ለዚህ ውስብስብ ችግር መፍትሄ የሚሰጥ አንድ አዲስ ግብረ ኃይል እንዲቋቋም አዘዋል፡፡ ትራምፕ በተለይም በሜክሲኮ ድንበር በኩል በሕገ ወጥ መንገድ ወደ አሜሪካ ግዛት ገብተዋል የሚሏቸውን ሰነድ አልባ ስደተኞች ልጆችን ከአዋቂዎች ለይቶ በማስቀረት የወሰዱት እርምጃ ብዙ ውግዘት ያስከተለ ነበር፡፡ አሁን ባይደን ያቋቋሙት አዲስ ግብረ ኃይል እነዚህን ወደ 700 የሚጠጉ ልጆችን ከወላጆቻቸው ጋር ለማገናኘት መንገዶችን ይፈትሻል ተብሏል፡፡ ከ2017 እስከ 2018 ብቻ የትራምፕ አስተዳደር 5ሺህ 500 ልጆችን ድንበር ላይ ከወላጆቻቸው ለይቷቸው ነበር፡፡ ለዚህ ጉዳይ መፍትሄ እንዲያበጅ የተቋቋመው ግብረ ኃይል የሚመራው የአገር ውስጥ ደህንነት ሚኒስትር ሆነው በተሾሙት አለያንድሮ ማዮርካስ አማካኝነት ይሆናል፡፡ በዚህም ልጆች ከተለይዋቸው ወላጆቻቸው በቅርብ ጊዜ እንዲገናኙ መላ ይፈለጋል ተብሏል፡፡ ሌላው ባይደን አስተላለፉ የተባለው አስተዳደራዊ ውሳኔ ትራምፕ ያመጡትን የስደተኞች እና ጥገኝነት አመልካቾችን ጉዳይ የሚመለከት ነው፡፡ ትራምፕ በአሜሪካ ህጋዊ የጥገኝነት ጥያቄዎች የሚስተናገዱበትን መንገድ በመዘጋጋት፣ ሒደቱንም ቀርፋፋ እንዲሆን በማድረግ ይታወቃሉ፡፡ ከዚህም ሌላ ትራምፕ ለውጭ አገራት የሚሰጥ የገንዘብ ድጋፍን በአመዛኙ መቀነሳቸው ይታወሳል፡፡ ባይደን ይህን የሚቀለብስ ውሳኔንም ፈርመዋል፡፡ ባይደን ፊርማቸውን ካኖሩ በኋላ እንዲህ ብለዋል፣ "አገራችንን ውርደት ማጥ ውስጥ የከተቷትን ያለፈውን (የትራምፕ) መንግሥት የሞራልና የብሔራዊ ሀፍረት ፖሊሲዎች አንድ በአንድ እናጸዳለን፡፡ እናትን ከልጇ መነጠል…ያለ አንዳች እቅድ…ቤተሰብን መነጣጠል…እነዚህ ሁሉ መልክ እንዲይዙ ይደረጋል" ጆ ባይደን አንድ የሕግ ማእቀፍ ሐሳብ ያቀረቡ ሲሆን ይህም ዜግነት ለማግኘት ሂደት ላይ ያሉ ሰነድ አልባ የሆኑ 11 ሚሊዮን ሰዎችን ሕጋዊ ማድረግ የሚቻልበትን ሁኔታ የሚመቻች ነው፡
news-55082530
https://www.bbc.com/amharic/news-55082530
የሴቶችን የወሲብ ቪዲዮ በቴሌግራም ሲሸጥ የነበረው 40 ዓመት ተፈረደበት
የሴቶችን የወሲብ ቪዲዮ በቴሌግራም ቻናል ሲሸጥ የነበረው 40 ዓመት ተፈረደበት
ደቡብ ኮሪያዊው ቾ ጁ ቢን ደቡብ ኮሪያዊው ቾ ጁ ቢን ሴቶችን እያታለለ የወሲብ ቪዲዮ እንዲልኩ በማድረግና በቴሌግራም ቻናል በማሰራጨት ወንጀል ተከሶ 40 ዓመት ተፈርዶበታል። ይህን የቴሌግራም ቡድን ቾ ጁን ቢን ያስተባብረው እንጂ በርካታ አባላት ያሉትና በድበቅ የሚንቀሳቀስ ነበር ተብሏል። ቡድኑ ወሲባዊ ይዘት ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን በቴሌግራም ላይ ከሚገኙ ለአቅመ ሄዋን ያልደረሱ ሴቶችን ጭምር በማታለልና በማስፈራራት ቪዲዮ እንዲልኩ ያደርግ ነበር። ቡድኑ ተንቀሳቃሽ ምሥሎቹን በእጁ ካስገባ በኋላ ለአባላት ብቻ ክፍት በሆኑና 10ሺ አባላት ባሏቸው የቻትሩሞች በመውሰድ ወሲባዊ ቪዲዮዎቹን ለገበያ ያቀርባል። በዚህ ቻትሩም የሚገኙ አባላት ደግሞ የግለሰቦችን ወሲባዊ ቪዲዮዎቹን ከፍለው ለማየት የተሰባሰቡ ናቸው። እነዚህ አባላቱ የግለሰቦችን የወሲብ ቪዲዯዎች ለማየት እስከ 1ሺ 200 ዶላር ክፍያ ይፈጽማሉ። በዚህ ሁኔታ 14 ለአቅመ ሄዋን ያልደረሱ ሴቶችን ጨምሮ 74 ሰዎች የግል ገመናቸው በቪዲዮ ተሰራጭቶባቸዋል። ቾ ህጻናትን ለወሲባዊ ትርፍ በማዋል ተከሶ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ የደቡብ ኮሪያ ፍርድ ቤት 40 ዓመት እስር አከናንቦታል። ፖሊስ የቾን ማንነት ይፋ ያደረገው ባለፈው መጋቢት ሲሆን ይህ የወሲብ ቪዲዮዎች ነጋዴ ማንነቱ ለሕዝብ ይፋ እንዲደረግ 5 ሚሊዮን ደቡብ ኮሪያዊያን ፊርማቸውን አሰባስበዋል። በመጨረሻም ቾ የዩኒቨርስቲ ምሩቅ የሆነ የ25 ዓመት ወጣት እንደሆነ ተደርሶበታል። በሴቶች መብት ላይ የሚሰሩ ተቋማት የቾ የፍርድ ሂደትን በቅርብ ሲከታተሉ ነበር። ምክንያቱም በደቡብ ኮሪያ በሴቶች ላይ የሚደርሱ የበይነ መረብ ወንጀሎችን እንደ ጥፋት ያለመቁጠር አዝማሚያ በመኖሩ ነው። የቾ የፍርድ ሂደት ለሕዝብ ክፍት እንዲደረግና ጥፋተኛ ሆኖ ከተረጋገጠም ከፍተኛ ቅጣት እንዲጣልበት ጉዳዩን ለሚመለከቱት ፍርድ ቤት 80ሺ የድጋፍ ፊርማዎችና ደብዳቤዎች ደርሰውታል። አንዳንድ ደብዳቤዎች ቾን ጭራቅ እያሉ ነበር የሚጠሩት። አቃቢ ሕግ ቾ በእድሜ ልክ እስራት ይቀጣልኝ ቢልም ዳኛው የ40 ዓመት እስር ፍርድ ብቻ አስተላለፍዋል። የቾ ረዳት የነበሩ ቴሌግራም ቡድን አባላት 15 ዓመትና ከዚያ በታች ተፈርዶባቸዋል።
46299509
https://www.bbc.com/amharic/46299509
እውን እንጀራ ሱስ የሚያስይዝ ንጥረ ነገር አዝሏል?
አቶ ወንድወሰን ግርማ በቤልጂየም የትራንስፖርት ሳይንስ የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪ ነው። ከዚያ ቀደም ብሎ ለሁለት ዓመትም ለሌላ ሁለተኛ ዲግሪ በኖርዌይ ቆይቷል።
"ያኔ ከአገር ስወጣ የመጀመርያዬ ስለነበር የእንጀራ አምሮቴ ከፍተኛ ነበር" ይላል። እንደ አጋጣሚ ሆኖ ወንድወሰን የሚኖርበት ሰፈር ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ቅርብ ነበር። ይህ ሁኔታ ሀበሾች በሰበብ አስባቡ ለመሰባሰብ ምክንያት ሆኗቸዋል "የእንጀራ አምሮታችንን በዚያው እንወጣው ነበር" ይላል። ኖርዌይ ውስጥ ቤተሰብ መሥርተው የሚኖሩ ብዙ ኢትዮጵያውያን መኖራቸው ሌላው መልካም አጋጣሚ ነው። "እነሱ እንጀራ ጋግረውና የተለያዩ ምግቦችን ሠርተው ይዘው ይመጣሉ" ይላል። እንደ ወንድወሰን ዓይነቱ ከአገሩ የራቀ የእንጀራ ጽኑ ወዳጅ ቢያንስ በዓላትን ጠብቆ እንጀራን የማጣጣም ዕድል አለው። ሐበሾች በሚበዙባቸው የአውሮፓ ከተሞች እዚህም እዚያም ብሎ አምሮቱን መወጣት አያቅትም። ከዚያ በብዙ ማይል የራቁትስ? ለዚህ ያልታደሉስ? • ጤፍን ሰዳ የምታሳድደው ኢትዮጵያ • ጤፍ ሃገሩ የት ነው? ደቡብ አፍሪካ? አውስትራሊያ? . . . ኧረ ለመሆኑ እንጀራ ሱስ ያስይዛል? ወንድወሰን ምንም እንኳ የእንጀራ አፍቃሪ ቢሆንም ሱስ ነው ብሎ ለመደምደም ይቸገራል። ሰዎች በአቅራቢያቸው ምንም ዓይነት እንጀራ ማግኘት እንደማይችሉ ሲያውቁ ያገኙትን ለመመገብ አይቸገሩም ብሎ ያምናል። ነገሩ ከአስተሳሰብ ጋር እንደሚያያዝም ይገምታል። ይህንኑ ጥያቄ ወደ ባለሙያ ይዘነው ብንሄድስ? አቶ አብነት ተክሌ የሥነ ምግብ ባለሙያ ናቸው። እንደሳቸው ሐሳብ ጉዳዩ ደንበኛ ጥናትን የሚፈልግ ነው። "እንጀራ ሱስ ያስይዛል ወይስ አያስይዝም የሚለውን ጥያቄ ጥርት ባለ መልኩ የሚመልስ ጥናት እኔ እስካሁን አላገኘሁም'' ይላሉ። በመጀመሪያ ግን ሱስ ምንድነው የሚለውን ጥያቄ ይመልሳሉ። እንደ ባለሙያው አስተያየት ሱስ በሁለት ደረጃዎች የሚከፈል ሲሆን፤ አንደኛው ሥነ አእምሯዊ ሆኖ የአንድን ጣዕም ከጥሩ ስሜት ጋር ከማያያዝ የሚመነጭ ነው። ሁለተኛው የሱስ ዓይነት ደግሞ 'ፊዚዮሎጂካል' የሚባለውና ሰውነታችን የሆነን ንጥረ ነገር ሲለምድ የሚጠይቀን ነው፤ በብዛት የተለመደው የሱስ ዓይነትም ይኸው ነው። "የእንጀራን ጉዳይ ሥነ-አእምሯዊ ከሚባለው የሱስ ዓይነት አንጻር ስንመለከተው..." ይላሉ አቶ አብነት ከሕይወታችን ጋር ያለው ቁርኝትን ሲያስረዱ፤ "...ከልጅነታችን ጀምሮ የለመድነው ጣዕም በመሆኑ ሥነ-አዕምሯዊ ሱስ ሊኖረው ይችላል" ይህም የሚሆነው በቀን ሁለት ወይም ሦስት ጊዜ ስለምንመገበው ነው። "እንጀራን ደጋግመን ከመመገባችን የተነሳ ውስጥ ውስጡን ያንን ጣዕም የመፈለግና ስናገኘው ደግሞ የመደሰት ስሜቶች ይከሰታሉ" ይላሉ። ሥነ አእምሯዊ ገጽታውን በዚህ መልኩ የተነተኑት አቶ አብነት 'ፊዚዮሎጂካዊ' ሱስነቱን እንደሚከተለው ይገልጹታል። "እንጀራ በውስጡ ኃይልና ጉልበት ሰጪ ንጥረነገሮች እንዲሁም አሲዶች አሉት። በእርሾ እንደመሠራቱ ግበአቶቹ ሲብላሉ አሲድ ይፈጠርና እንጀራውን ለጎምዛዛ የቀረበ ጣዕም ይሰጠዋል።" ከዚህ በተጨማሪ እንጀራ በውስጡ ለሰውነት አስፈላጊ የሆኑ ፕሮቲንና ካርቦሃይድሬት ያለው ሲሆን፤ ሰውነታችን እነዚህን ንጥረነገሮች ለኃይልና ጉልበትም ይሁን ለሰውነት ግንባታ ይጠቀምበታል፤ ልክ እንደማንኛውም ምግብ እንጀራን ስንበላ የመደሰትና የመርካት ስሜት ይፈጠራል" ባይ ናቸው። • ልጆችዎ ጤናማ ምግብ እንዲመገቡ ማድረጊያ መላዎች • አትክልት ብቻ ስለሚመገቡ ሰዎች ሊያውቋቸው የሚገቡ ነገሮች ነገር ግን በእንጀራ ውስጥ ካለው ከፍተኛ የአሲድ እንዲሁም የአልኮል ክምችት አንጻር ከሌሎች ምግቦች በተሻለ እርካታን ሊሰጠን ይችላል። ይህ ደግሞ ብዙ ጊዜ ሰዎች "እንጀራ ሱስ ያስይዛል" የሚል ድምዳሜ ላይ እንዲደርሱ አድርጓቸዋል ይላሉ ባለሙያው፤ አቶ አብነት። ለእንጀራ የሚከፈል ዋጋ በአሁኑ ሰዓት ኑሮዉን ቤልጂየም ያደረገው ወንድወሰን አሁን የሚኖርበት አካባቢ ለእንጀራ ቅርብ እንዳልሆነ ይገልጻል። ደረቅ እንጀራ ፍለጋ ከ1፡30 እስከ 2፡00 ሰዓት የሚፈጅ የባቡር ጉዞን ያደርጋል። እንጀራው ሉቨን ከሚባል ቦታ የሚመጣ ሲሆን ቀደም ብሎ ስልክ በመደወል ቀጠሮ ማስያዝ የግድ ነው። ቀድሞ መደወሉ ያስፈለገው ቀድመው ላዘዙ ብቻ ስለሚጋገር ነው። ክፋቱ ከዚህ ሁሉ እንክርት በኋላ የሚገኘው እንጀራ አንጀት አርስ አለመሆኑ ነው፤ "በመጠኑ ሰሐን የሚያክልና በጣም ትንሽ ነው። ጣዕሙ ደግሞ ኢትዮጵያ ካለው ጋር በጭራሽ አይወዳደርም" በማለት ምሬቱን ይገልፃል። እንዲያውም ወንድወሰን ''አእምሯችንን አሳምነን እንጀራ ነው ብለን እንበላዋለን እንጂ የጤፍ ስለመሆኑ በመጠራጠር ነገሩ እንጀራ ነው ለማለት ይከብደኛል" ይላል ጥርጣሬው ያለምክንያት አልተፈጠረም የሚለው ወንድወሰም የመለጠጥና መረር የማለት ባህሪ በመሆኑ ከጤፍ ይልቅ ለገብስ የቀረበ መሆኑን ይናገራል። "የማማረጥ ዕድል በሌለበት አቃቂር ማውጣት ቅንጦት ነው። ይህን ሁሉ እያወቅህ 'እንጀራ እየበላሁ ነው' የሚለው ነገር በራሱ ከፍተኛ የአእምሮ እርካታን ያጎናጽፍሃል" የሚለው። የሆነስ ሆነና እንጀራ ከሱስ ይመደባል? የሥነ ምግብ ባለሙያው ቀጥተኛ መልስ የላቸውም። ነገር ግን እንጀራ እንደ ኒኮቲን አልያም አልኮል ያሉ ሱስ አስያዥ ንጥረ ነገሮች፣ መጠጦች ወይም ተክሎች ዓይነት ሱስ የማስያዝ አቅም የሌልውና፤ ደካማ እንደሆነም ይገልፃሉ። ምናልባት እንጀራ ሲሠራ ሊጡ ከእርሾው እስኪብላላ ድረስ ሦስት ቀን ስለሚፈጅበት የአሲድ መጠኑ ከሌሎች አሲድ ያላቸው ምግቦች ከፍ ያለ ሊሆን ይችላል የሚሉት ባለሙያው የአሲድ መጠኑ ከፍ ማለቱና ጎምዘዝ ያለ ጣዕም መኖሩ መሠረታዊ ባይባልም መጠነኛ የሆነ ሱስ ሊያመጣ ይችላል ባይ ናቸው። እንጀራን የሚመገቡ ሰዎች ላይ ከሚከሰተው ፊዚዮሎጂካል ሱስ ይልቅ የሥነ አእምሯዊው ሱሱ የበለጠ ኃይል እንዳለውም አቶ አብነት ያስባሉ። "ብዙ ጊዜ ሰዎች እንጀራ ሳልበላ አንድ ቀን መቆየት አልችልም የሚሉት ሰውነታቸው እንጀራ ፈልጎ ሳይሆን ከልጅነታቸው ጀምሮ ያስለመዱት ነገር ስለሆነ ነው። ይህም ሱሱ ከአካላዊነቱ ይልቅ ሥነ አእምሯዊ ስለመሆኑ ሌላ አስረጅ እንደሆነም ይናገራሉ። እንጀራ በዓይን የዞረ 'ለት ወንድወሰን በድምሩ ለአራት ዓመታት ባሕር ማዶ በቆየባቸው ጊዜያት የእንጀራ ነገር በዓይኑ ይዞራል። በኖርዌይ ቆይታው ከዕለታት በአንዱ የእጀራ ሱሱ አየለበት፤ በአቅራቢያው በቀላሉ ማግኘት የሚታሰብ አልነበረም። ለምን ራሴ አልጋግርም የሚል ሐሳብ ብልጭ አለለት። ጤፍን የሚተካ ገብስ አመጣ፤ የገብሱ ዱቄት ውስጥ ጨው ጨመረ፤ በሞቀ ውሃ አቀላቀለው፤ ከገብሱ ዱቄት ውስጥ የገብሱን ገለባ ማጥለልና ከአራት እስከ አምስት ቀናት ድረስ በደንብ እስኪብላላ መጠበቅ ነበረበት፤ አዲስ መጥበሻ በመግዛት በመጥበሻው ውህዱን ጋገረው። ወንድወሰን የጋገረው የገብስ እንጀራ ውጤቱ እንደ አዲስ ሳይንሳዊ ግኝት አጓጊ ነበር። • የአገልግል ምግብ አምሮዎታል? "ለመጀመሪያ ጊዜ የጋገርኩት እንጀራ ምንም የእንጀራ መልክ የሌለውና ከእንጀራነት ይልቅ የላስቲክ ባሕሪን የተላበሰ ነበር ይላል" ከሳቅ ጋር እየታገለ። "ማባያ ይሁነኝ ብዬ ያዘጋጀሁትን ወጥ ስጨምርበት "እንጀራዬ" መያዝ እንኳ ተሳነው" ሲል ጀምሮት የነበረውን ሳቅ ይጨርሳል። ወንድወሰንን ያየ እንጀራ ሱስ አይደለም ማለት ይቻለዋል?
news-55914758
https://www.bbc.com/amharic/news-55914758
እነ አቶ ጃዋር መሐመድ የረሃብ አድማ ማድረግ ከጀመሩ ስድስት ቀናት እንዳለፋቸው ተነገረ
ፖለቲከኞቹ አቶ ጀዋር መሐመድ፣ አቶ በቀለ ገርባ፣ አቶ ሐምዛ አዳነ እና አቶ ሸምሰዲን ጠሃ የረሃብ አድማ ማድረግ ከጀመሩ 6 ቀናት እንዳለፋቸው ከጠበቆቻቸው መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ቱሊ ባይሳ ለቢቢሲ አረጋግጠዋል።
ጀዋር መሐመድ እንደ አቶ ቱሊ ከሆነ ደንበኞቻቸው የረሃብ አድማ እያደረጉ ያሉት የፖለቲከኞችን እስር እና በመገናኛ ብዙኃን ላይ የሚደርሰውን ጫና በመቃወም ነው። ጠበቃው ቱሊ ባይሳ ፖለቲከኞቹ እያደረጉት ያሉት የረሃብ አድማ እንዳደከማቸው ገልጸው፤ ደንበኞቻቸው ለማነጋገር በሄዱበት ወቅት ወጥተው ሊያነጋግሯቸው ስላልቻሉ "ተኝተው ባሉበት" ለማነጋገር ተገድደናል ሲሉ ለቢቢሲ ደንበኞቻቸው ያሉበትን ሁኔታ አብራርተዋል። ትናንት (ማክሰኞ ጥር 25) ደንበኞቻቸውን ሄደው ማነጋገራቸውን የሚያስረዱት አቶ ቱሊ፤ "የረሃብ አድማ ከጀመሩ ስድስተኛ ቀናቸው ነው። ከዚህ ቀደም ልንጠይቃቸው ስንሄድ መጠየቂያ ስፍራ ጋር መጥተው ነበር የሚያነጋግሩን። አሁን ግን ወደ እዛ እንኳን መጥተው ሊያነጋግሩን ስላልቻሉ በተኙበት ቦታ ሄደን ነው ያነጋገርናቸው። ድምጻቸውም፤ ሰውነታቸውም ተዳክሟል" ሲሉ ተናግረዋል። የታሰሪ ቤተሰቦችም ተከሳሾቹ እያካሄዱ ባሉት የረሃብ አድማ መዳከማቸውን ይናገራሉ። የአቶ ጃዋር መሐመድ እህት የሆነችው ራቢያ ሲራጅ፤ ትናንት እነ አቶ ጃዋርን ለመጎብኘት መሄዷን እና ያሉበትን ሁኔታ ከተመለከተች በኋላ መረበሿን ተናግራለች። "በጣም ተዳክመዋል። 'ትግል ላይ ነው ያለነው አንበላም' አሉኝ። መቆም እንኳን አይችሉም። ያሉበትን ሁኔታ ማየት አቅቶኝ ወጣሁኝ" ስትል ተናግራለች። አቶ ቱሊ እንደሚሉት ደንበኞቻቸው የሕክምና አገልግሎት ካስፈለገን በመረጥነው የሕክምና ስፍራ አገልግሎት ይሰጠን ማለታቸውን ተከትሎ የደንበኞቻቸውን አቤቱታ ተቀብለው ለማረሚያ ቤቱ አስተዳደር ማመልከቻ አስገብተው መውጣታቸውን ተናግረዋል። ይህንን የጠበቃውን መረጃ በተመለከተ የማረሚያ ቤቶች አስተዳደርን ተጨማሪ መረጃ እንዲሰጠን ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም፡፡ የረሃብ አድማ ለምን? እንደ ጠበቆቻቸው ገለፃ ከሆነ እን አቶ ጃዋር የረሃብ አድማ እያደረጉ ያሉት የፖለቲከኞችን እስር እና በመገናኛ ብዙኃን ላይ የሚደርሰውን ጫና በመቃወም ነው። እነ አቶ ጃዋር መሐመድ እና በቀለ ገርባን ጨምሮ በርካታ ፖለቲከኞች የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ ከተፈጠረው ሁከት ጋር ተያይዞ እጃችሁ አለበት ተብለው ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር መዋላቸው የሚታወስ ነው። "የዝነኛ ሰዎች ግድያን ተከትሎ ፖለቲከኞች ወደ እስር ቤት ተወረወሩ። መገናኛ ብዙኃኑም ተዘጉ። በርካታ የኦሮሞ ፖለቲካ ፓርቲዎች ተሰረዙ። የቀሩት ደግሞ አመራሮቻቸው እንዲታሰሩ ተደርጓል" የሚል ቅሬታ ደንበኞቻቸው እንደሚያሰሙ ጠበቃው ለቢቢሲ ተናግረዋል። ከዚህም በተጨማሪ "በወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር የዋሉ ሰዎች በዋስ እንዲወጡ ፍርድ ቤት ቢያዝም፤ አይለቀቁም። ቢለቀቁም ተመልሰው ይታሰራሉ። ሌሎች የፖለቲካ ፓርቲዎች ቢሮ ከፍተው ለምርጫ እንዲዘጋጁ ይደረጋል። በእኛ ላይ ግን ተቃራኒው ነው የሚፈጸመው" በሚል ምክንያት የረሃብ አድማ እያደረጉ እንደሆነ ጠበቃው ለቢቢሲ አስረድተዋል። ጠበቃው አቶ ቱሊ ባይሳ ለቢቢሲ እንደተናገሩት በገላን ከተማ ታስረው የሚገኙት እና ደንበኞቻቸው የሆኑት የኦነግ ከፍተኛ አመራሮች በተመሳሳይ የረሃብ አድማ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል። አቶ ሚካኤል ቦረን እና ኬነሳ አያና ፍርድ ቤት የዋስትና መብታቸው ተከብሮ ጉዳያቸው ከውጪ ሆነው እንዲከታተሉ ቢፈቅድላቸውም ፖሊስ እስረኞቹን አልለቅም በማለቱ የረሃብ አድማ ላይ ይገኛሉ ብለዋል፤ አቶ ቱሊ ባይሳ። የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ በቁጥጥር ሥር የዋሉት እነ አቶ ጃዋር ከቀረቡባቸው ተደራራቢ አስር ክሶች ስድስቱ እንዲቋረጡ ፍርድ መወሰኑ ይታወሳል። የሽብር ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ፤ የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀል አዋጅ ፤ የጦር መሳሪያ አስተዳደርና ቁጥጥር አዋጅ የመተላለፍ ክሶች ከተመሰረቱባቸው ክሶች መካከል ሲሆኑ፤ እንዲቋረጡ የተደረጉት ክሶች የጦር መሳሪያ አስተዳደር እና ቁጥጥር አዋጅ 1177/2021 ጋር የተያያዙ ናቸው። የዛሬ ሳምንት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የፀረ ሽብርና ሕገመንግሥታዊ አንደኛ ችሎት የተከሳሾችን የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሊቀበል ቀጠሮ ይዞ የነበረ ቢሆንም ቢጫ ቀለም ልብስ በለበሱ ግለሰቦች ምክንያት ችሎት ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱ ይታወሳል። የፍርድ ሂደቱን ለመከታተል ቢጫ ልብስ ለብሰው በፍርድ ቤት የተገኙ ሰዎች ወደ ፍርድ ቤቱ እንዳይገቡ በፖሊስ መከልከላቸውን ተከትሎ ተከሳሾች እና ጠበቆች ባሰሙት አቤቱታ ነው ተለዋጭ ቀጠሮ የተሰጠው። በማሕበራዊ ሚዲያዎች ላይ በርካቶች ቢጫ ልብስ የመልበስ ዘመቻ ሲያከናውኑ ቆይተዋል። ይህም ተከሳሾች በማረሚያ ቤት እና ፍርድ ቤት ሲቀርቡ የሚለብሱትን ባለ ቢጫ ቀለም ቱታ ለመወከል ነው። የእምነት ክህደት ቃል ለመስማት ተለዋጭ ቀጠሮ የተሰጠባቸው ተከሳሾች ነገ ጥር 27፣ 2013 ፍርድ ቤት ይቀርባሉ።
news-55444874
https://www.bbc.com/amharic/news-55444874
1ሺ ሄክታር የሚሰፋው የማይክል ጃክሰን የመኖርያ ግቢ በ22 ሚሊዮን ዶላር ተሸጠ
'ዘ ኔቨርላንድ' በሚል ስሙ የሚታወቀው የሟቹ ማይክል ጃክሰን መኖርያ ቤት መሸጡን ለጉዳዩ ቅርብ ነን የሚሉ ሰዎች ተናገሩ።
ይህ እጅግ ግዙፍ መኖርያ የሚገኘው ከሎስ ኦሊቮስ ከተማ ቀረብ ባለ ጫካ በካሊፎርኒያ ግዛት ውስጥ ነው። ንብረቱን የገዙት ቢሊየነር ቤቱ ያወጣል ተብሎ ከተጠበቀው አንድ አራተኛውን ብቻ ከፍለው ነው የራሳቸው ያደረጉት። ይህ የማይክል ጃክሰን የቀድሞ መኖርያ ግቢ እስከ 100 ሚሊዮን ዶላር ሊያወጣ ይችላል ተብሎ ተገምቶ ነበር። ቤቱን የገዙት ቢሊየነር ሮን በርከል የሚባሉ ሰው ናቸው ተብሏል። ዜናውን የዘገበው ዎል ስትሪት ጆርናል ሲሆን በዚህ ግዢኛ ሽያጭ በቀጥታ የተሳተፉ ሦስት ሰዎችን በምንጭነት ጠቅሷል። ይህ የማይክል ጃክሰን ግቢ ስፋቱ 2ሺ 700 ኤከር ወይም 1ሺ 100 ሄክታር የሚሸፍን እጅግ ግዙፍ መኖርያ ግቢ ነው። በካሊፎርኒያ ግዛት ከሳንታ ባራባራ ከተማ በስተ ሰሜን አቅጣጫ የሚገኘው ይህ እጅግ ግዙፍ መኖርያ ግቢ የማይክል ጃክሰንን ሞት ተከትሎ ሊሸጥ ዋጋ ሲወጣለት ለዓመታት ሲንከባለል ቆይቷል። በ2015 የቤቱ ግምት 100 ሚሊዮን ዶላር የነበረ ሲሆን ባለፈው ዓመት ግን በ31 ሚሊዮን ዶላር ሊሸጥ ነው የሚሉ ዜናዎች መውጣት ጀምረው ነበር። ማይክል ጃክሰን ቤቱን መጀመርያ ሲገዛው በ19 ሚሊዮን ዶላር ተኩል ነበር። የቤቱን ስምም በልጆች ዝነኛ የተረት ተረት ታሪክ ፒተር ፓን ውስጥ ባለው ደሴት ስም ሰይሞት ነበር። በተረቱ ዓለም ውስጥ ይህ ደሴት ልጆች የማያድጉበት ዓለምን የሚወክል ነው። ማይክል ይህንን ቤት የገዛው እንደነሱ አቆጣጠር በ1987 ነበር። በዚያ ጊዜ ትሪለር የተሰኘውን ሙዚቃ ያወጣበት እና በዝና ማማ ላይ የወጣበት ዘመን ነበር። ይህንን ቤቱን ወደኋላ ላይ የመዝናኛ ስፍራ አድርጎት ቆይቷል። ግቢው ከስፋቱ የተነሳ እጅግ ግዙፍ የእንሰሳት መጠበቂያ (zoo)፣ የአእዋፋት መናኸሪያ፣ የዲዝኒላንድ ሁሉም ዓይነት መጫወቻና መዝናኛዎች፣ በርካታ ሲኒማ ቤቶች፣ ሰው ሰራሽ ሐይቆች፣ መለስተኛ ባቡር መጓጓዣዎችና በናቱ ስም የተሰየመ የባቡር ጣቢያ ያሉት ምናልባትም አንድ አነስተኛ የገጠር ቀበሌን የሚያህል ስፋት ያለው ነው። በዚህ ስፍራ ሕጻናትና ቤተሰቦቻቸው እንዲዝናኑበት በማሰብ አካባቢውን በከፊል የመዝናኛ ማዕከል አድርጎትም ነበር ማይክል ጃክሰን። በኔቨርላንድ መኖርያ ቤቱ ተከፍተው የማያውቁ፣ አንድም ቀን አንድም ሰው አድሮባቸው የማያውቁ በርካታ ክፍሎች ያሉ ሲሆን በግቢው ውስጥ የመኖርያ ቤት ሕንጻዎች ቁጥር ግን 22 እንደሆነ ይታወቃል። በጊዜው ከ120 በላይ የቤት ሰራተኞች የነበሩት ማይክል ለደመወዝ ብቻ በዓመት ከአንድ ሚሊዮን ዶላር ያላነሳ የወጣ እንደነበር መረጃዎች ይጠቁማሉ። ማይክል በዚህ ስፍራ ይኖር የነበረው በርካታ ሕጻናት ጋር ሲሆን ፖሊስ ይህንን ግቢ ድንገት በመውረር ማይክል ይታማበት የነበረውን ከልጆች ጋር ጾታዊ ፍላጎት አለው በሚል ክስ መስርቶበት ነበር። ፖሊስ ማይክልን በዚህ ግቢ ውስጥ ሕጻናትን ያባልጋል፣ ምናባዊ ዓለም ሊፈጥር ፈልጓል በሚል ከሶት ነበር። ማይክል ድርጊቱን አለመፈጸሙን ክዶ ተከራክሯል። በ2005 ማይክል የ13 ዓመት ልጅን አባልገሀል በሚል ክስ ቀርቦበት ፍርድ ቤት ነጻ አድርጎት ነበር። ከዚህ በኋላ ይህንን ኔቨርላንድ ግቢ ጠልቼዋለሁ አልመስም ብሎ ስፍራውን ትቶት ኖሯል። እንዳለውም ማይክል ጃክሰን ወደ ኔቨርላንድ የተጠንጣለለ ቤቱ ሳይመለስ ነው የኖረው። ከአራት ዓመታት በኋላ በ2009 ማይክል ጃክሰን ሎስ አንጀለስ በሚገኘው ሌላ መኖርያ ቤቱ ውስጥ ከልብ ጋር በተያያዘ በሽታ፣ ከመጠን ያለፈ ብዙ መድኃኒት በመውሰዱ ለሞት መዳረጉ አይዘነጋም። ሞቱን ተከትሎ በርካታ የምርመራ ዘጋቢ ፊልሞች በዚህ ኔቨርላንድ መኖርያ ቤቱ ዙርያ ተሰርተዋል። ማይክል ጃክሰን በዚህ ግዙፍ ቤቱ ውስጥ ያልተገቡ ምናባዊ የሚመስሉ ድርጊቶችን ይፈጽም እንደነበረ የሚገምቱ ፊልም ሰሪዎች ጥርጣሪያቸውን የሚያንጸባርቁ መረጃዎችን አሰራጭተዋል። ኔቨርላንድ ግቢ የማይክል ጃክሰንን ሞት ተከትሎ ስሙን ወደ ሲካሞር ቫሊ በመቀየር እድሳት ተደርጎለት ነበር። አሁን ይህንን ታሪካዊና ግዙፍ ንብረት የግሉ ያደረጉት ቢሊየነሩ ሚስተር በርክል አካባቢውን ምን ሊሰሩበት እንደሆነ ይፋ አላደረጉም። ሆኖም ግን ይህንን ቤት ለመግዛት ሐሳቡ እንዳልነበራቸውና በዚያ ስፍራ በሄሊኮፕተር ሲንሸራሸሩ ከሰማይ ላይ ካዩት በኋላ ፍላጎት እንዳደረባቸው አብራርተዋል። የ68 ዓመቱ በርክል የዩዋኪፓ ኩባንያ መሥራችና ባለቤት ሲሆኑ ፎርብስ በያዝነው ወርና ዓመት ጠቅላላ ሀብታቸውን 1 ቢሊዮን ተኩል ገምቶታል።
news-45219095
https://www.bbc.com/amharic/news-45219095
እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች የላውሮ ግምት እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች የላውሮ ግምት
ሁለቱ የፕሪሚየር ሊጉ አዳዲስ አሰልጣኞች በዚህ ሳምንት እርስ በእርስ ይጫወታሉ። ቅዳሜ የቼልሲው ማውሪዚዮ ሳሪ በሜዳቸው የአርሴናሉን ኡናይ ኤምሬን ያስተናግዳሉ።
የቢቢሲው የእግር ኳስ ተንታኝ ማርክ ላውረንሰን አርሴናሎች ባለፈው ሳምንት በማንቸስተር ሲቲ ከደረሰባቸው ሽንፈት በኋላ "አራተኛ ሆነው ያጠናቅቃሉ ማለቴን በድጋሜ ላጤነው እችል ይሆናል" ብሏል። ላውሮ ዘንድሮም 380ዎቹንም የፕሪሚየር ሊጉን ጨዋታዎች በሙሉ ይገምታል። የላውሮ ግምቶች ቅዳሜ ካርዲፍ ከኒውካስል ካርዲፎች ባለፈው ሳምንት በበርንማውዝ ከደረሰባቸው ሽንፈት በኋላ ተሻሽለው እንደሚቀርቡ አስባለሁ። በቶተንሃም ቢሸነፉም ኒውካስሎች ጥሩ የተንቀሳቀሱ ሲሆን በዚህ ዓመት የሚቸገሩ አይመስለኝም። የላውሮ ግምት: 1-1 አፍሪካውያን በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውስጥ ሊቨርፑል ሞ ሳላህን ለፖሊስ አሳልፎ ሰጠ ኤቨርተን ከሳውዝሃምፕተን የኤቨርተን ደጋፊዎች ማርኮ ሲልቫ በሚመርጡት አጨዋወት ደስተኞች ሲሆኑ፤ በሜዳቸው በሚያደርጉት ጨዋታ ውጤቱ ምንም ይሁን በከፍተኛ ሁኔታ ይደግፋሉ። ከበርንሌይ ጋር በነበራቸው ጨዋታ አጥቂያቸው ዳኒ ኢንግስ በሁለተኛው አጋማሽ ተቀይሮ ከገባ በኋላ ጥሩ መንቃሳቀስ ቢችሉም ይህን ጨዋታ የሲልቫ ቡድን እንደሚያሸንፍ እገምታለሁ። የላውሮ ግምት: 2-0 ሌስተር ከዎልቭስ ሌስተሮች በመጀመሪያ ጨዋታቸው ከማንቸስትር ዩናይትድ ጋር ጥሩ የተንቀሳቀሱ ሲሆን ጂሚ ቫርዲም ጎል ማስቆጠር ችሏል። ዎልቭሶች በበኩላቸው በኤቨርተን ሁለት ጊዜ ከመመራት ተነስተው አቻ መለያየት ችለዋል። የላውሮ ግምት: 2-1 ቶተንሃም ከፉልሃም ቶተንሃሞች ጥሩ ተንቀሳቅሰው ኒውካስልን ያሸነፉ ሲሆን ላልተወሰነ ጊዜ በዌምብሌይ መጨዋታቸው የሚያሳስባቸው አይመስለኝም። ፉልሃሞች በዚህ ሳምንትም ሌላ ለንደን ክለብን ያገኛሉ። ባለፈው ሳምንት በክሪስታል ፓላስ የተሸነፉ ሲሆን በዚህ ሳምንትም ነገሮች ቀላል አይሆኑላቸውም። የላውሮ ግምት: 2-0 ዌስት ሃም ከበርንማውዝ አዲሱ የዌስት ሃም አሰልጣኝ ማኑዌል ፔሌግሪኒ ብዙ አጥቂዎችን ገዝተው ጥሩ ቡድን ለመስራት ቢጥሩም የተከላካይ መስመራቸው ግን አስጊ ነው። በርንማውዞች ከሜዳቸው ውጭ ጠንካሮች ባይሆኑም ነጥቦችን እያገኙ ነው። ከዚህ ጨዋታም አንድ ነጥብ ያገኛሉ ብዬ አስባለሁ። የላውሮ ግምት: 1-1 «ሳሸንፍ ጀርመናዊ ስሸነፍ ስደተኛ» ኦዚል ቀጣዩ የፕሪምየር ሊግ አሸናፊ ማን ይሆን? ቼልሲ ከአርሴናል የአርሴናሉ አሰልጣኝ ኡናይ ኤምሬ ምርጥ ቡድናቸውን ለማግኘት ብዙ መስራት አለባቸው። አርሴናሎች ባለፈው ሳምንት ከማንቸስተር ሲቲ ጋር በነበራቸው ጨዋታ ሲቸገሩ ቼልሲ በቡኩሉ በቀላሉ ነበር ሃደርስፊልድን ያሸነፈው። የላውሮ ግምት: 2-0 እሑድ በርንሌይ ከዋትፎርድ የሚያገኙትን ዕድሎች የሚጠቀሙ ከሆነ በርንሌይዎች ይህን ጨዋታ በጠባብ ውጤት የሚያሸንፉ ይመስለኛል። ዋትፎርዶች ወጥ አቋም ባያሳዩም ብዙ ቡድኖች ከእነሱ በታች ሆነው የውድድር ዓመቱን እንደሚያጠናቅቁ እገምታለሁ። የላውሮ ግምት: 1-0 ማንቸስተር ሲቲ ከሃደርስፊልድ ማንቸስተር ሲቲዎች በጉዳት ያጡትን ኬቪን ደ ብሩይንን የሚተኩላቸው ብዙ አማራጫችን ይዘዋል። ሃደርስፊልዶች ባለፈው ሳምነት በቼልሲ በሰፊ ውጤት የተሸነፉ ሲሆን በዚህ ሳምንትም ኢትሃድ ስታዲየም ላይ ከዚህ የተለየ ነገር ይጠብቃቸዋል ብዬ አልጠብቅም። የላውሮ ግምት: 3-0 ብራይተን ከማንቸስተር ዩናይትድ የብራይተኑ አሰልጣኝ ባለፈው ሳምንት በዋትፎርድ ሲሸነፉ ካልተጠቀሙባቸው አዳዲስ ተጫዋቾች መካከል አንዳንዶቹን በዚህ ጨዋታ ያሰልፋሉ። ማንቸስትር ዩናይትዶች ባለፈው ሳምንት ሌስተርን ለማሸነፍ በቂ ጨዋታ ያሳዩ ሲሆን ኮከብ ተጫዋቾቻው ወደ ሙሉ ብቃት ስለሚመለሱ እየተጠናከሩ ይሄዳሉ። የላውሮ ግምት: 1-2 ሰኞ ክሪስታል ፓላስ ከሊቨርፑል ሊቨርፑሎች ባለፈው ሳምንት የዌስት ሃም ተከላካይ መስመር የፈጠረላቸውን አይነት ክፍተት በደቡብ ለንደን አያገኙም። የፓላሱ አሰልጣኝ ሮይ ሆድሰን በሚመርጡት አጨዋወት መሠረት ምንም ክፍተት የማይፈጥሩ ሲሆን ጨዋታውንም ተቀራራቢ ያደርጉታል። የላውሮ ግምት: 1-1
45094420
https://www.bbc.com/amharic/45094420
"አብዲ ሞሃመድ ኡመር ስልጣን ለመልቀቅ በተደጋጋሚ ጠይቀው ነበር" አዲሱ የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት
የሶማሌ ክልል አዲሱ ፕሬዚዳንት አህመድ አብዲ መሀመድ የቀድሞው ፕሬዚዳንት አብዲ ሞሀመድ ኦማር ስልጣን እንዳስረከቡና ሽግግሩም በሰላም እንደተጠናቀቀ ለቢቢሲ ሶማልኛ ተናግረዋል።
የክልሉ አዲሱ ፕሬዚዳንት እንደተናገሩት የቀድሞው ፕሬዚዳንት ስልጣን ለመልቀቅ በመጠያቃቸው የሥራ አስፈፃሚው ኮሚቴ ጥያቄያቸውን ተቀብሎ አዲሱን የክልሉ ፕሬዚዳንት እንደመረጠም ገልፀዋል። ሰሞኑን ለብዙ ሰዎች ሞት፣ ለአብያተ-ክርስትያናት መቃጠልና ንብረት መውደም ጋር ተያይዞም በክልሉ የመከላከያ ሠራዊት የገባ ሲሆን፤ በክልሉ በነበረው አለመረጋጋት ጋር ተያይዞም በማዕከላዊ መንግሥት ግፊት ምክንያት እንደወረዱ ብዙዎች አስተያታቸውን ቢሰጡም አዲሱ ፕሬዚዳንት ሲንከባለል የነበረ ጥያቄ እንደሆነ ተናግረዋል። •በድሬዳዋ ከተማ በተከሰተ ግጭት የ10 ሰዎች ህይወት ጠፋ •በሶማሌ ክልል ከ10 የሚበልጡ አብያተ ክርስትያናት ጥቃት ደረሰባቸው .በሶማሌ ክልል በተከሰተ ቀውስ ህይወት ሲጠፋ አብያተ-ክርስትያናት ተቃጠሉ "ስልጣን ለመልቀቅ ባለፈው አራት ዓመት ጥያቄ ቢያቀርቡም በፓርቲያቸው ዘንድ ተቀባይነት አላገኘም ነበር" ብለዋል። ጨምረውም በትናንትናው ዕለት ይህ ጥያቄ ተቀባይነት እንዳገኘም ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት የቀድሞው ፕሬዚዳንት ጂግጂጋ በሚገኘው ቤታቸው ቤታቸው ውስጥ እንደሚገኙ ተናግረው ምንም እንኳን የሥራ አስፈፃሚነትን ስልጣን ቢያስረክቡም የፓርቲያቸው ሶህዴፓ ኃላፊ ሆነው ይቆያሉ ብለዋል።
news-56686729
https://www.bbc.com/amharic/news-56686729
ኮሮናቫይረስ ፡ህንድ እስከ መጪው ሃምሌ 250 ሚሊዮን ህዝብ እከትባለሁ አለች
ህንድ እስከ መጪው ሃምሌ 250 ሚሊዮን ህዝቧን የኮሮናቫይረስ መከላከያ የመክተብ እቅድ እንዳላት አስታውቃለች።
ለዚህም የሚሆን 500 ሚሊዮን መጠን (ዶዝ) ክትባት በዝግጅት ላይ እንደሆነም መንግሥት ከሰሞኑ አስታውቋል። አገሪቷ ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገባ ያለቻቸውን የማህበረሰብ ክፍል በከፍተኛ ፍጥነት እየከተበች ሲሆን እስካሁንም ድረስ ከ100 ሚሊዮን መጠን (ዶዝ) ያለው ክትባት ተከፋፍሎ መድረሱን አስታውቃለች። በሁለተኛው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ክፉኛ በተመታችው ህንድ ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ በየቀኑ በአማካኝ የምትመዘግበው የቫይረሱ ታማሚ ቁጥር ከ90 ሺህ በላይ ሆኗል ተብሏል። ከወረርሽኙ ጋር በመታገል ጎን ለጎን ክትባት እየከተበች ሲሆን ከ45 አመት በላይ የሆኑ ሰዎች በሙሉ መከተብ እንደሚችሉ ተገልጿል። ክትባቶቹንም ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀ ማዕከላትና ሆስፒታሎች በቀላሉ ማግኘት ይቻላል። እስካሁን ድረስ በከፍተኛ ደረጃ የተከተቡት ከ60 አመት በላይ የሆናቸው የእድሜ ባለፀጎችና የጤና ባለሙያዎች ናቸው። በአለም ላይ ካሉ አገራት 100 ሚሊዮን መጠን ያለው ክትባት በማዳረስ ቀዳሚዋ አገር ህንድ ስትሆን ይህንንም ለማድረግ የፈጀባት 85 ቀናት መሆኑን የአገሪቱ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። አሜሪካ ይህንን ያህል መጠን ከመክተብ 89 ቀናት የፈጀባት ሲሆን ቻይና ደግሞ 102 ቀናት መውሰዱን የጤና ሚኒስቴሩ አክሎ ገልጿል። ምንም እንኳን አገሪቷ በከፍተኛ መጠን እየከተበች ቢሆን በዚሁ ሳምንት በርካታ ግዛቶች የክትባት እጥረት እንዳጋጠማቸው ሪፖርት አድርገዋል። ሆኖም የፌደራል መንግሥቱ ከፍተኛ ክምችት አለኝ፤ እጥረት የሚለው መሰረት የሌለው ነው ብሏል። ከ40 ሚሊዮን መጠን በላይ ክትባት በማከማቻዬ ውስጥ አለኝ ብሏል። ሆኖም አገሪቷ እስከ መጪው ሃምሌ ድረስ 250 ሚሊዮን ዜጎቿን ለመክተብ የምታቅድ ከሆነ ፍጥነቷን ልትጨምር እንደሚገባ ባለሙያዎች ይናገራሉ። ወረርሽኙ ከተነሳ ጀምሮ 12 ሚሊዮን ሰዎች በኮሮናቫይረስ የታዩዙባት ህንድ 167 ሺህ ዜጎቿንም በሞት ተነጥቃለች።
news-45861919
https://www.bbc.com/amharic/news-45861919
በኢትዮጵያ እናቶችን የሚያገለግል 'ሁሉ በጤና' የተሰኘ መተግበሪያ ይፋ ሆነ
እናቶችን የሚያገለግል 'ሁሉ በጤና' የተሰኘ መተግበሪያ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴርና በጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ ትብብር ይፋ ተደርጓል።
ስለ እናቶችና ህፃናት ጤና በአጠቃላይ ቤተሰብ ሊያውቋቸው ስለሚገቡ መረጃዎችን ከዚህ ቀደም የቤተሰብ ጤና መምሪያ ተብሎ በፅሁፍ ይሰራጭ ነበር። ይሁን እንጂ ማንበብ የማይችሉና ያልተማሩ ቤተሰቦችን መድረስ ባለመቻሉ መተግበሪያው መሰራቱን ተመራጭ እንዳደረገው በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የእናቶችና ህፃናት ጤና ዳይሬክተር ዶ/ር አብርሃም ታሪኩ ይናገራሉ። • የዓለምፀሐይ፣ የፍስሃ እና የካሳሁን አዲስ ተስፋ • ስለ አንጀታችን የማያውቋቸው ስድስት አስገራሚ እውነታዎች በመሆኑም ማንበብ ለማይችሉት መተግበሪያውን ስልካቸው ላይ በመጫን በቅድመ ወሊድ፣ በወሊድ ወቅትና ከወሊድ በኋላ፣ በህፃናት ክትባት ጊዜ እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ የእናቶችና ህፃናት ጤናን የተመለከቱ መረጃዎችን በድምፅ ማግኘት እንዲችሉ ያስችላቸዋል። መተግበሪያው በአማርኛ ትግርኛና ኦሮምኛ የሚሰራ ሲሆን ለመጀመር ያህል በአማርኛ ተዘጋጅቶ ቀርቧል። የእናቶች ጤና ዘርፈ ብዙ በመሆኑ መተግበሪያው ምን ያህል ምሉዕ ነው ያልናቸው ዳሬይክተሩ ከቤተሰብ ጤና መመሪያ ውስጥ የተወሰዱ ዋና ዋና መረጃዎች ወደ መተግበሪያው የተቀየሩ እንደሆኑ ይናገራሉ። መተግበሪያውንም ማንም ሰው በቀላሉ መጠቀም እንዲችል የሚያስችል ነው ብለዋል። ምንም ዓይነት የኢንተርኔት አገልግሎት የማያስፈልገው ሲሆን በመተግበሪያው ላይ የተፃፈ ማውጫን በመጠቀም የሚፈልጉትን መረጃ በመምረጥ ማንበብም ሆነ በድምፅ መስማት የሚያስችላቸው ነው። ምን ያህል እናቶችን መድረስ አንደሚቻል ያነሳንላቸው ዳይሬክተሩ ከ50 በመቶ በላይ የሚሆኑ ቤተሰቦች የሞባይል ስልክ ተጠቃሚ መሆናቸውን፤ ከ60 ሚሊዮን በላይ ተጠቃሚዎች በመኖራቸው መተግበሪያው ተመራጭ እንዲሆንና የተሻለ ተደራሽ መንገድ ሞባይል ነው ከሚል ውሳኔ ላይ እንደደረሱ ከኢትዮ ቴሌኮም ያገኙትን መረጃ በመጥቀስ ተናግረዋል። • «የምታገለው ለማንም ብሔር የበላይነት አይደለም» አቶ በቀለ ገርባ • የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሠራዊት በተባበሩት መንግሥታት ተሸለመ በአብዛኛው የገጠር ቤተሰብ ውስጥ ስልክ የመጠቀም አዝማሚያው የወንዶች ቢሆንም መረጃውን ለትዳር አጋራቸውና ለልጆቻቸው ያጋራሉ ተብሎ ታሳቢ እንደተደረገም ይገልፃሉ። ቢሆንም ግን ከሁለት ዓመት በፊት ያለው መረጃ እንደሚያሳየው 27 በመቶ የሚሆኑ ሴቶች ተንቀሳቃሽ ስልክ ይጠቀማሉ በዚህም እነርሱንም ተደራሽ ማድረግ እንደሚቻል ያስረዳሉ። መተግበሪያው በማንኛውም ስልክ ላይ መጫን እንዲቻል ተደርጎ የተሰራ ሲሆን በተለይ በይበልጥ በዋጋም ቅናሽ ያላቸውና ቀላል ስልኮች ላይ መጠቀም እንዲቻል ተደርጎ የተሰራ ነው። በሌሎችም ዘመናዊ ስልኮች ላይ መጫን ይቻላል። ዳሬክተሩ የመተግበሪያው ስርጭት በቀጣይ የሚሰራ እንደሆነ ገልፀዋል። የባለፈው ዓመት የሥነ-ህዝብና ጤና ጥናት እንደገለፀው ከ100 ሺህ እናቶች 412 በወሊድ ወቅት ይሞታሉ፤ እድሜያቸው ከአምስት ዓመት በታች የሆኑ ጨቅላ ህፃናት ደግሞ ከ1000 ህፃነት 68ቱ ይሞታሉ።
52454420
https://www.bbc.com/amharic/52454420
ኮሮናቫይረስ፡ በአማራ ክልል “ህጋዊ አሰራርን ያልተከተሉ” 7ሺህ የሚሆኑ ንግድ ቤቶች ታሸጉ
የኮሮናወረርሽኝን ተከትሎ በአማራ ክልል በህገ ወጥ ተግባር ላይ ተሰማርተዋል የተባሉ 194 ነጋዴዎች ታስረው ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑ ተጠቆመ።
"ከወረርሽኙ መከሰት በኋላ ህገወጥ የንግድ ሥራ የሚሠሩ ነጋዴዎች" አሉ ያሉት የአማራ ክልል የንግድ እና ገበያ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ተዋቸው ወርቁ በህገወጥ ንግድ ከመሳተፍ "ጊዜው ችግር የምንካፈልበት ነው" ብለዋል። ነጋዴዎች ህጋዊ አሰራርን እንዲከተሉ ትምህርት ሲሰጥ እንደቆየ ምክትል ቢሮ ኃላፊው ለቢቢሲ ተናግረዋል። ከማስተማር ባሻገር ከማስጠንቀቂያ መስጠት እስከ ድርጅት ማሸግ የሚደርስ አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል። • እውን የትግራይ ክልል የራሱን ምርጫ ማካሄድ ይችላል? • ኢትዮጵያን ጨምሮ በርካታ አገሮችን እየረዳ ያለው ቢሊየነር ጃክ ማ ማነው? በክልሉ "49ሺህ በላይ ድርጅቶች ተፈትሽፈዋል። ወደ 21 ሺህ የሚደርሱት ችግር ተግኝቶባቸዋል። 7 ሺህ የሚሆኑት የታሸጉ ሲሆን 194 ግለሰቦች ታስረው ምርመራ እየተካሄደ ነው" በውለዋል። ቢሮው ከህገወጥ ንግድ በተጨማሪ በሽታውን ለመከላከልም እየሠራ መሆኑን አቶ ተዋቸው አስታውቀዋል። እንደኃላፊው ገለጻ ከሆነ በገበያ ቦታዎች ያሉትን ጥግግቶችን ለመቀነስ ከነበሩት የገበያ ቦታዎች በተጨማሪ አዳዲስ የገበያ ቦታዎችን በማስጀመር፤ በንግድ ሱቆች ውስጥ ገዢና ሻጭ ርቀታቸው እንዲጠብቁ በማድረግ እና የቤት ለቤት የሽያጭ አገልግሎትን በማስፋፋት ሰዎች ከቤታቸው አስገዳጅ ካልሆነ በቀር እንዳይወጡ ለማደረግ ቢሮው እየሰራ ነው። ቢሮው ወደ ገበያ ቦታዎች የሚሄዱ ሰዎችም የአፍና እፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል እንዲያደርጉ፤ በገበያ ቦታዎች ርቅተን እንዲጠብቁ፤ በገበያ ቦታዎች የንጽህና መጠበቂያዎችን እንዲጠቀሙ እና ገበያ ደርሰው ወደ ቤታቸው የሚመለሱ ሰዎች ከመግባታቸው በፊት እንዲታጠቡ ትምህርት እየሰጠ መሆኑም ተገልጿል። • የኤርትራውያን ስደተኞች ስጋት በኢትዮጵያ በገበያ ቦታዎች የአፍና እፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል ማድረግ አስገዳጅ ነው ወይ? ተብለው ከቢቢሲ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ ""እንደምክረ ሃሳብ ነው የቀረበው። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የአፍና እፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል አድርጉ አይልም። ገበያው ላይ ያለው ጥግግት በሽታውን ሊያስተላልፍ ይችላል። የገበያ ቦታዎች ጥግግቱ ከሁለት ሜትር የሚያንስበት አጋጣሚ ይበዛል። ከርቀት መጠበቅ ሌላ የአፍና እፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል ደግሞ የትንፋሽ ለትንፋሽ ልውውጥን ያስቀራል። በሽያጭ መካከል ያለው ቅርርብ ትንሽ በመሆኑ ነው አስገዳጅ ሳይሆን ምክረ ሃሳብ ነው ያቀረብነው" ሲሉ መልሰዋል። አዋጁ ሃገራዊ በመሆኑ ክልሉ ሌላ አዋጅ አያወጣም ያሉት ምክትል ቢሮ ኃፊው "በአዋጁ ገበያ የሚወጣ የአፍና እፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል ማድረግ አለበት አይልም፤ በደንቡም አልተካተተም። ስለዚህ ከማስገደድ በማስተማር የተሻለ በመሆኑ ምክረ ሃሳብ እናቀርባለን። የአፍና እፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል ባለማድረግ እርምጃ አንወስድም ግን ከበሽታ እንደሚከላከል እያስተማርን ነው" ብለዋል። የአፍና እፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል አቅርቦት ችግር መኖሩንም አቶ ተዋቸው ጠቁመው "ችግሩን ለመቅረፍ ብዙ ድርጅቶች እየሠሩ ነው። ህብረተሰቡ ትምህርቱን ተቀብሎ የአፍና እፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል እፈልጋለሁ እንኳን ቢል ምርቱ ላይም በደንብ እየሰራን ነው" ብለዋል።
news-43068770
https://www.bbc.com/amharic/news-43068770
ጃኮብ ዙማ ስልጣን ለቀቁ
ስልጣን አለቅም ብለው የነበሩት እምቢተኛው ዙማ ከራሳቸው ኤኤንሲ ፓርቲ ግፊት ሲበረታባቸው በመጨረሻ ስልጣን መልቀቅ ግድ ሆኖባቸዋል።
በቴሌቭዥን በተላለፈው ንግግራቸው ስልጣን መልቀቃቸውን ነገር ግን በፓርቲያቸው ውሳኔ እንደማይስማሙ ገልፀዋል። ፓርቲያቸው ኤኤንሲ ለ75 ዓመቱ ዙማ ለምክትል ፕሬዝዳንቱ ሲሪል ራማፎሳ ስልጣን አስረክቡ የሚል ጥሪ ሲያደርግላቸው ቆይቷል። እንደ አውሮፓውያኑ ከ2009 ጀምሮ ስልጣን ላይ የነበሩት ዙማ በርካታ የሙስና ውንጀላዎች ቀርበውባቸዋል። ከዙማ ጋር ቅርብ ግንኙነት አለው የተባለው የሃያሉ ጉፕታ ቤተሰብ የጆሃንስበርግ መኖሪያ ትናንት በፖሊስ ቀጥጥር ስር ውሎ ነበር። ዙማ የስልጣን ለቅቄያለሁ ንግግራቸውን የጀመሩት ለመቀለድ በመሞከርና ንግግራቸውን ለመታደም የተገኙ ጋዜጠኞችን ጥያቄ በመጠየቅ ነበር። ከዚያም ዙማ ላለፉት ዓመታት አብረዋቸው የሰሩ ሰዎችን በማመስገን በፓርቲያቸው ኤኤንሲ ውስጥ የተፈጠረው መከፋፈል ስልጣን የመልቀቅ ውሳኔ ላይ እንዲደርሱ እንዳደረጋቸው ተናገሩ። "በእኔ ስም ምንም አይነት ህይወት መጥፋት የለበትም።በእኔ ምክንያትም ኤኤንሲ ውስጥ መከፋፈል እንዲኖር አልፈልግም።ስለዚህም ስልጣን የመልቀቅ ውሳኔ ላይ ደርሻለው" ብለዋል ዙማ በመቀጠልም ምንም እንኳን በፓርቲያቸው የስልጣን ልቀቁ ውሳኔ ባይስማሙም ሁሌም ስርዓት የሚያከብር የፓርቲው አባል መሆናቸውን ገልፀዋል። በመጨረሻም "ስልጣን ብለቅም ህይወቴን ሙሉ ያገለገልኩትን የደቡብ አፍሪካ ህዝብና ፓርቲዬ ኤኤንሲን ማገልገሌን እቀጥላለሁ።"ብለዋል ዙማ።
52125409
https://www.bbc.com/amharic/52125409
ኮሮናቫይረስ፡ በአማራ ክልል ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች የትምህርት ተቋማት ለመጠለያነት ተዘጋጁ
በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች ለሚባሉት ለምኖ አዳሪዎች እና ጎዳና ተዳዳሪዎች ትምህርት ቤቶች ውስጥ እንዲጠለሉ ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩን የአማራ ክልላዊ መንግሥት የሠራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታውቋል።
የኮሮና ወረርሽኝ እየተስፋፋ ከመምጣቱ አንፃር ይህ የማህበረሰብ ክፍል ከለላ ሊሰጠው ይገባል ብሎ ያመነው ቢሮው ለዚህ የሚረዳውን ኮሚቴ ማቋቋሙንም የቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ጥላሁን መኳንንት በተለይ ለቢቢሲ ገልጸዋል። በክልሉ በተጋላጭነት ከሰላሳ ሺህ በላይ ለምኖ አዳሪዎች እና ጎዳና ተዳዳሪዎች ተለይተዋል። • ለኅዳር በሽታ ያልተበገሩት የ108 ዓመቷ አዛውንት ለኮሮና እጅ ሰጡ ለማህረሰቡ የሚሆን የቦታ መረጣ፣ የምግብ ዝግጅት፣ የብርድ ልብስ እና ንጽህና መጠበቂያዎች እንዲዘጋጅ መደረጉን ኃላፊው ተናግረዋል። በአማራ ክልል ሁለት ግለሰቦች የኮሮና ቫይረስ እንዳለባቸው መረጋገጡን ተከትሎ ከዛሬ እኩለ ቀን ጀምሮ በመላው አዲስ ቅዳም፣ እንጅባራ፣ ቲሊሊና በባ/ዳር ከተማ ብቻ የሚተገበር ለ14 ቀናት የሚቆይ ማንኛውንም አይነት የተሽከርካሪም ሆነ የህዝብ እንቅስቃሴ እንዳይደረግ የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የኮረና ቫይረስ መከላከልና መቆጣጠር ኮማንድ ፖስት መወሰኑ ይታወሳል። ነዋሪዎች እና በጐ አድራጊዎች ሁሉ መጠለያ ቦታ ላይ ለሚሠባሠቡ እና ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች የእለት የምግብ እርዳታ በሚያሠባስበው ግብረ ሃይልና የበጐ ፈቃደኛ አባላት አማካኝነት እንዲደግፉም ኮማንድ ፖስቱ ትላንት አስታውቆ ነበር። በዚህ መሠረት ከ1ሺህ 300 በላይ ጎዳና ተዳዳሪዎች ከዛሬ ጀምሮ ወደ ተዘጋጀላቸው ቦታ የማስገባት ሥራ ተጀምሯል። ከወጣቶች፣ የጤና ባለሙያዎች እና ከሌሎችም ጋር በመሆን ለሥራው እንዲሆን ጥምር ኮሚቴ መቋቋሙን የገለጹት አቶ ጥላሁን ለሥራው ሦስት ትምህርት ቤቶች መለየታቸውን አስታውቀዋል። የምግብ፣ የንጽህና መጠበቂያ እና ፍራሽ የመሳሰሉ ቁሳቁሶችን ማስገባት መጀመሩን ገልጸው ዛሬ የተለዩ ሰዎችንም የማስገባቱ ስራ ይጀመራል ብለዋል። በትምህርት ቤቶቹ 103 ክፍሎች የተለዩ ሲሆን በእያንዳንዱ ክፍል ስድስት ሰዎች እንዲቆዩ እንደሚደረግም አክለው አስረድተዋል።
news-49922349
https://www.bbc.com/amharic/news-49922349
ኔታኒያሁ እስራኤል ውስጥ ስላሉ ኤርትራዊያን ከጠ/ሚ ዐብይ ጋር መወያየታቸውን ተናገሩ
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታኒያሁ በቅርቡ ከኢትዮጵያው አቻቸው ጋር በተገናኙበት ወቅት ኤርትራዊያን ጥገኝነት ጠያቂዎችን በኢትዮጵያ መንግሥት ድጋፍ ከእስራኤል ለማስወጣት "አዲስ ዕቅድ" እንዳላቸው እንደተናገሩ 'ዘ ታይምስ ኦፍ ኢዝራኤል' የተባለ ጋዜጣ ዘገበ።
መስከረም ሰባት ቀን ከተደረገው የእስራኤል ምክር ቤት ምርጫ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ ለቅስቀሳ በሚል በሊክዊድ ፓርቲ የፌስቡክ ገጽ በወጣው ቪዲዮ ላይ ከኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር መገናኘታቸውን በማስታወስ የተነጋገሩትን ይጠቅሳሉ። በዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታኒያሁ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ሃገራቸው ከኤርትራ ጋር ከአንድ ዓመት በፊት ስለደረሱት የሠላም ስምምነት በማንሳት መልካም አጋጣሚዎች እንደተፈጠሩ እንዳነሱላቸው ይናገራሉ። • ኢትዮጵያውያን 'የሌሉበት' ስለ ኢትዮጵያ የሚዘክረው ሬድ ሲ ዳይቪንግ ሪዞርት ፊልም • "ኢትዮጵያዊነቴን ያገኘሁት ሙዚቃ ውስጥ ነው" አቨቫ ደሴ ጋዜጣው እንደጠቀሰው "አዲስ በሆነ ፕሮጀክት አማካይነት ሰዎቹ ወደ ኤርትራ እንዲመለሱ ለመርዳት የሚያስችል ጥሩ መንገድ አለኝ" እንዳሏቸው ኔታኒያሁ ተናግረዋል። ኔታኒያሁ አክለውም "ጠቅላይ ሚኒስትሩ [ዐብይ] ለመርዳት ያላቸው ፍላጎት ከዚህ በፊት ያላገኘነውን አጋጣሚ ይከፍትልናል" ብለዋል። በአጭር ቪዲዮው ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታኒያሁ የፓርቲያቸው የምክር ቤት አባል ከሆነችውና ጸረ ስደተኛ እንቅስቃሴ ውስጥ ተሳታፊ ከሆነችው ሜይ ጎላን ጋር ሲነጋገሩ ይታያሉ። በዚህ ወቅት ነው ከኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ስላደረጉት ውይይት ሲናገሩ የተደመጡት። ቢቢሲ ቪዲዮውን አግኝቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታኒያሁ በእብራይስጥ የሚናገሩትን አስተርጉሞ ነበር። በዚህ ተንቀሳቃሽ ምስል ላይም "መልካም ዜና አለ። የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ይፋዊ ጉብኝት ለማድረግ በመጡበት ጊዜ እንደነገሩኝ 'ከኤርትራ ጋር ሠላም ማውረዳችንን ታውቃለህ፤ እኔም በጣም ዘመናዊ በሆኑ ፕሮጀክቶች አማካይነት ሰዎቹ በጣም ጥሩ በሆነ ሁኔታ ወደ ኤርትራ እንዲመለሱ ለማድረግ በሚያስችሉ መንገዶች ልረዳህ እችላለሁ' ብለውኛል" ብለው ሲናገሩ ይደመጣል። ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታኒያሁ አክለውም "በእርግጥም በአፍሪካ ውስጥ ትኩረትን እየሳበ ባለው፣ ይህ ወጣትና ከፍተኛ ፍላጎት ያለው መሪ፣ እኛን ለመርዳት ያለው ዝግጁነት እስካሁን ያላገኘነውን መልካም አጋጣሚን ይከፍትልናል" በማለት ሲናገሩ ይሰማሉ። • "ወደ እናት ሃገራችን እስራኤል ውሰዱን" • እስራኤል ስደተኞችን የማስጠለሉን መርሃ ግብር አነሳች ጋዜጣው በዚህ ጉዳይ ላይ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤትን አስተያየት እንዲሰጥ ቢጠይቅም ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል። ቴል አቪቭ የሚገኘው የኤርትራ ኤምባሲም አስተያየት እንዲሰጥ በተደጋጋሚ ቢጠየቅም ምላሽ ከመስጠት ተቆጥቧል። አንድ በቴል አቪቭ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ውስጥ ያለ ሰራተኛን በፌስቡክ በኩል ለጋዜጣው እንደነገረው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ በእስራኤል ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት ስለኤርትራዊያን ጥገኝነት ጠያቂዎች ጉዳይ እንዳልተነሳ ገልጸዋል። "በውይይቱ ላይ ይህን ጉዳይ በተመለከተ የተነሳ ነገር የለም። ውይይቱ የሁለትዮሽ ግንኙነትን በተመለከተ ነበረ" ሲሉ የኤምባሲው ሰራተኛ የጽሁፍ መልስ ሰጥተዋል። በአሁኑ ጊዜ ከ23 ሺህ በላይ ጥገኝነት ጠያቂ ኤርትራዊያን እስራኤል ውስጥ የሚኖሩ ሲሆን፤ ከ16 ሺህ በላይ የሚሆኑት ይፋዊ የጥገኝነት ጥያቄን አቅርበዋል። ከእነዚህም ውስጥ እስካሁን 13ቱ ብቻ ተቀባይነት ሲያገኙ ከ5 ሺህ በላይ የሚሆኑት ደግሞ ጥያቄያቸው ውድቅ ተደርጓል። የቀሪዎቹ ማመልከቻዎች እስካሁን ድረስ ምላሽ አላገኘም።
51030551
https://www.bbc.com/amharic/51030551
እውን አውስትራሊያ ምስሉ ላይ እንደሚታየው እየተቃጠለች ነው?
የአውስታራሊያ ሠደድ እሳትን የሚያሳዩ ፎቶዎች፣ ተንቀሳቃሽ ምስሎችና በማሕበራዊ ድር-አምባዎች ላይ እየተሠራጩ ነው።
ነገር ግን ከሰሞኑ የተሠራጨና አውስታራሊያ ስትንቦገቦግ የሚያሳይ የሳተላይት ምስል ብዙዎችን አጃኢብ አሰኝቷል። የብዙዎቹ ለጣፊዎች ዓላማ አውስትራሊያ እና የተፈጥሮ ሃብቷ፤ በተለይ ደግሞ የዱር እንስሳት ላይ እየደረሰ ያለው እልቂት አሳስቧቸው 'ኧረ እንደርስላቸው' ነው። ከጀመረ ወራትን ያስቆጠረው የአውስታራሊያ ሰደድ እሣት 25 ሰዎችን ሲገድል በሚሊዮን የሚቆጠሩ የዱር እንስሳትም ሰለባ ሆነዋል። አልፎም 2000 መኖሪያ ቤቶችን ከጥቅም ውጭ አድርጓል። ምንም እንኳ ባለፈው ቅዳሜና እሁድ የጣለው ዝናብ ሁኔታውን በትንሹም ቢሆን ጋብ ቢያደርገውም የእሣት አደጋ ሰዎች ቃጠሎው እንደ አዲስ ሊባባስ ይችላል የሚል ስጋር አላቸው። የሳተላይት ምስሉ ምስጢር ሪሃናን ጨምሮ በበርካታ ታዋቂ ሰዎች ትዊተርና ኢንስታግራም ገፃቸው ሲንሸራሸር የነበረው ከላይ የሚታየው ምስል ሰደድ እሣቱ ቢስፋፋ ምን ሊመስል እንደሚችል ምናባዊ እይታ እንዲሰጥ ተደርጎ በአንድ ግለሰብ የተሠራ እንጂ እውነተኛ አይደለም። አርቲስት አንተኒ ሃርሲ የተሰኘው ይህ ግለሰብ ባለፉት ወራት እሣት የተነሳባቸውን ቦታዎች ምስል ከሰበሰበ በኋላ ሰደዱ በአንድ ጊዜ ቢከሰት ይህን ይመስላል የሚል መረጃ ለመስጠት የሠራው ሥራ ነው። አርቲስቱ ፎቶው በማሕበራዊ ድር-አምባዎች እውቅና ካገኘ በኋላ በትዊተር ገፁ ባሰፈረው መልዕክት እርግጥ ነው የሳተለይት ምስል ግነት ይታይበታል፤ ቢሆንም እውነታን መሠረት አድርጌ ነው የሠራሁት ሲል ፅፏል። ሌላኛው በርካቶች ሲጋሩት የነበረው የአውስትራሊያን ካርታ የሚያሳየው ምስል አህጉሪቱ ስትንበለበል ያሳያል። ምስሉ የተገኘው ከአውስትራሊያ መንግሥት ድረ-ገፅ ሲሆን የሠደድ እሣቱን መስፋፋት የሚሳይ ሳይሆን የሙቀት መጠንን ለማሳየት የዋለ ነው። ካርታው ላይ የሚታዩት ቀያይ ነጥቦች ተፈጥሯዊውም ሆነ ሰው ሠራሽ ሙቀት በአካባቢው መኖሩን የሚያመላክቱ እንጂ ከእሣት ጋር ብቻ የተያያዙ እንዳልሆኑ መንግሥት አስታውቋል። እነዚህ ምስሎች ብቻ ሳይሆኑ ሌሎች በርካታ የሳተላይት ምስሎች የአውስትራሊያን ሠደድ እሣት ለማሳየት ጥቅም ላይ እየዋሉ ሲሆን ግማሾቹ አሳሳች ናቸው እየተባለ ነው።
news-55421937
https://www.bbc.com/amharic/news-55421937
በኮንሶ ዞን ኅዳር ላይ ባጋጠመ ግጭት ከ60 በላይ ሰዎች ተገድለዋል - ኢሰመኮ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኮንሶ ዞን ባለፈው ኅዳር ወር መጀመሪያ ላይ ዳግም ባገረሹ ግጭቶች ከስልሳ በላይ ሰዎች ሲገደሉ በርካቶች ደግሞ የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ።
ኮሚሽኑ ግጭቶቹን በተመለከተ ባደረገው ፈጣን ዳሰሳ ያገኘው ውጤት እንዳመለከተው ቢያንስ 66 ሰዎች ተገድለዋል፣ 39 ሰዎች የአካል ጉዳት ሲደርስባቸው በርካታ ቤቶችና ንብረቶች በእሳት ተቃጥለው ውድመት ደርሶባቸዋል። በተጨማሪም በተደጋጋሚ ባጋጠሙት ግጭቶች ሳቢያ ከ130 ሺህ በላይ የአካባቢው ነዋሪዎች ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውን ኢሰመኮ ገልጿል። የኮሚሽኑ ሪፖርት እንዳመለከተው የግጭቶቹ ሰለባዎች "በጥቃት ፈጻሚዎቹ በጭካኔና በአሰቃቂ ሁኔታ" መገደላቸውንና ከደረሱት ጉዳቶች በተጨማሪ "የተሰበሰበን እህልን ጨምሮ ንብረት እና የእርሻ ቦታዎች መሉ በሙሉና በከፊል በእሳት ወድመዋል" ብሏል። ጥቃቶቹ በተፈጸሙባቸው ጊዜያት "ለመሸሽ ያልቻሉ አቅመ ደካማ ሰዎች ቤታቸው ውስጥ እንዳሉ ተቃጥለው የሞቱ እንዳሉ" ማሳያ የሚሆኑ አሰቃቂ ክስተቶችን የሚዘረዝሩ ከጥቃት የተረፉ ሰዎች እማኝነት በሪፖርቱ የተካተተ ሲሆን፤ የት እንደደረሱ ያልታወቁም እንዳሉ አመልክተዋል። በኮንሶ ዞንና በአካባቢው ለረዥም ጊዜ የቆው ችግር ተገቢውን ትኩረት አላገኘም ያሉት የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር)፤ "በአካባቢው ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ ከመኖሪያው መፈናቀሉና ከመካከላቸው ለአምስተኛ ጊዜ የተፈናቀሉ ተጎጂዎች መኖራቸው አሳዛኝ የሰብአዊ መብቶች ቀውስ ነው" ብለዋል። ኮሚሽኑ በሪፖርቱ ላይ እንደጠቀሰው የጥቃቱን ፈጻሚዎች በተመለከተ ነዋሪዎችና የአካባቢው አስተዳዳሪዎች "የተለያየና የሚቃረን መረጃ" እንደሚሰጡ ገልጿል። በዚህም የአካባቢው መስተዳድር አካላትና ተጎጂዎች በአንድ በኩል ጥቃት ፈጻሚዎቹ "የጉማይዴ ልዩ ወረዳ መዋቅር ጠያቂ ታጣቂዎች" ናቸው ሲሉ፤ ሌሎች ደግሞ "እራሳቸውን "ኮንሲታ" ብለው የሚጠሩና በደቡብ ክልል ልዩ ኃይል የሚደገፉ የኮንሶ ታጣቂዎች ናቸው" የሚሉ አሉ። የደቡብ ክልል ልዩ ኃይልና የኮንሶ ዞን አስተዳደር በበኩላቸው አጥቂዎቹ "የጉማይዴ ወረዳ መዋቅር ጠያቂ ኃይል" ናቸው በማለት ያስረዳሉ። በተጨማሪም የዞኑ አስተዳደር የግጭቱ መነሻ የጉማይዴ ወረዳ መዋቅር ጠያቂ ኃይል በልዩ ኃይል ላይ የሰነዘረው "የትንኮሳ እርምጃ" መሆኑን ሲገልጽ፤ ልዩ ኃይሉ ደግሞ የደረሰበት ትንኮሳ እንደሌለ ይናገራል። የኮንሶ ዞን አስተዳደር ደግሞ በግጭቱ "የደራሼ ወረዳ፣ የኦነግ ሸኔና የህወሓት እጅ እንዳለበት" ሲገልጽ፣ የደራሼ ወረዳ አስተዳደር በበኩሉ "የኮንሶ ዞን አስተዳደርን" ይከስሳል። የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን እንደሚለው ጥቃቱ ሙሉ በሙሉ ብሔር ተኮር ነው ለማለት ባይቻልም ከአማሮ ወረዳ ቡኒቲ ቀበሌ የተፈናቀሉ የተወሰኑ ተጎጂዎች፣ "አማሮች በአማሮ መሬት ተቀምጠው የጉማይዴን መዋቅር ይደግፋሉ" በሚል ጥቃት የሚያደርሱባቸው አካላት እንዳሉ መግለጻቸውን አመልክቷል። ኮሚሽነር ዳንኤል (ዶ/ር) ስለ ግጭቶቹና በነዋሪዎች ላይ የደረሰውን ጉዳትና መፈናቀል በተመለከተ እንዳሉት "ለተፈናቃዮች በአፋጣኝ አስፈላጊውን ድጋፍ ከማቅረብ ባሻገር የፌዴራሉና የክልሉ መንግሥታት ሕዝቡን ባሳተፈ መልኩ ተቀናጅተው ዘላቂ ሰላም የሚያሰፍን መፍትሄ ሊሰጡ ይገባል" ብለዋል። ከሃምሳ በላይ ብሔሮች በሚገኙበት የደቡብ ክልል ውስጥ በሚገኘው የኮንሶ አካባቢ የሚፈጸመው ጥቃትና የሚደርሰው ጉዳት በተለያዩ ጊዜያት በተደጋጋሚ ሲያጋጥም የቆየ መሆኑ ይታወሳል። ዘላቂ መፍትሄ ሳያገኙ በቆዩት ከመሬት ይገባኛልና ከአስተዳደራዊ መዋቅር ጋር በተያያዘ በሚቀሰቀሱት ግጭቶችና ጥቃቶች ሳቢያ ከዚህ በፊትም በርካታ ሞትና የአካል ጉዳት ከማጋጠሙ ባሻገር ነዋሪዎች ለተደጋጋሚ ለመፈናቀል ተዳርገዋል። ኮንሶ በኢትዮጵያ ደቡብ ምዕራብ በሰገን ወንዝ አቅራቢያ የሚገኝና ወደ 300 ሺህ የሚገመት ሕዝብ የሚኖርበት አካባቢ ሲሆን በደቡብ ከቦረና፣ በምዕራብ ከአሌ ልዩ ወረዳና በሰሜን ከደራሼና ከአማሮ ወረዳዎች ጋር ይዋሰናል።
news-44977582
https://www.bbc.com/amharic/news-44977582
የደቡብ ሱዳን መንግሥት ለሕዝብ እንደራሴዎቹ መኪና መግዣ 16 ሚሊየን ዶላር ማውጣቱ ቁጣን ቀስቅሷል
ደቡብ ሱዳን ለ400 የሕዝብ እንደራሴ አባላቷ የመኪና መግዣ በሚል ለእያንዳንዱ የ40 ሺህ ዶላር ብድር መስጠቷ የሕዝብ ቁጣን ቀስቅሷል።
የፕሬዚዳንቱ ቃል አቀባይ 16 ሚሊየን ዶላር የወጣበትን ወጪ ባብራሩበት ወቅት "የሕዝብ እንደራሴዎች በሞተር ሳይክል መሄድ የለባቸውም" ሲሉ ተከራክረዋል። መንግሥትን የሚተቹ ወገኖች የሕዝብ እንደራሴዎቹ ፕሬዝዳንቱ እስከ 2021 ስልጣናቸውን ማራዘም የሚያስችላቸውን ውሳኔ ካፀደቁላቸው በኋላ ብድሩ የተሰጣቸው እንደ ሽልማት ነው ሲሉ ተችተዋል። • ማቻርና ሳልቫ ኪር ከፊል ስምምነት ላይ ደርሰዋል • የደቡብ ሱዳን የሰላም ድርድር አልተሳካም • በደቡብ ሱዳን ግጭት 170 ሰዎች ተገደሉ መንግሥት እየተካሄደ ባለው የእርስ በእርስ ጦርነት ምክንያት ምርጫ አይካሄድም ሲል አስታውቋል። ከግማሽ በላይ የሚሆኑት የደቡብ ሱዳን ዜጎች በረሃብ አለንጋ እየተሸነቆጡ ሲሆን ለምግብ ቀውሱ በ2013 በሳልቫ ኪር ታማኞች እና በሪክ ማቻር መካከል የተጀመረው ግጭት እንደሰበብ ተደርጎ ይጠቀሳል። ጦርነቱ 3.8 ሚሊየን ሰዎች ጨርቄን ማቄን ሳይሉ ቀያቸውን ጣጥለው እንዲሰደዱ ማድረጉን የአለም ምግብ ድርጅት ዘገባ ያሳያል። የደቡብ ሱዳን ዋና መዲና የሆነችው ጁባ ነዋሪዎች መንግሥት ከልማት ይልቅ መኪና ላይ ገንዘቡን ማዋሉ አስቆጥቷቸዋል። • የደቡብ ሱዳኑ ማቻር ሃገር ሊቀይሩ ነው "በነፍስ ወከፍ 40 ሺህ ዶላር በጣም ብዙ ገንዘብ ነው። ምን አይነት መኪና ቢሆን ነው?" ስትል የምትጠይቀዋ የከተማዋ ነዋሪ የሆነች ግለሰብ "መንግሥት ሕዝቡ ያለበት ሁኔታ ግድ እየሰጠው አይደለም። ይህ ሙስና ነው፤ የህዝብ እንደራሴዎቹ አፋቸውን እንዲዘጉ የተሰጣቸው ይሆን?"ስትል ከቢቢሲ ጋር ባደረገችው ቃለምልልስ ጠይቃለች። የፕሬዝዳንቱ ቃል አቀባይ አቴኒ ዌክ አቴኒ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ይህ በጀት የተያዘለት ጉዳይ ነው። የደቡብ ሱዳንን መንግስትም ገንዘብ አባካኝ ብሎ መውቀስ ''ፍትሃዊ አለመሆን" ነው። እንደ አቴኒ ከሆነ ይህ ብድር በ2005 እና በ2009 ለሕዝብ እንደራሴዎቹ መኪና ለመግዛት እንደተሰጣቸው ብድር አይነት ሲሆን ብድሩንም በአምስት ዓመት ውስጥ የሚመልሱ ይሆናል። "መንቀሳቀስ የህዝብ እንደራሴዎቹ መብት ነው" ሲሉም አክለዋል።
54136468
https://www.bbc.com/amharic/54136468
ኮሮናቫይረስ፡ ኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ ተቋርጦ የነበረውን የክትባት ሙከራ ሊጀምር ነው
ዓለምን ላሽመደመደው ኮቪድ-19 ክትባት ለማግኘት ሁሉም በየአቅሙ ላይ ታች እያለ ነው።
ከእነዚህ መካከልም አስትራዜኒካ እና ኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ እያበለፀጉ ያሉት ክትባት ከፍተኛ ተስፋ ተጥሎበታል። ለዚህም ነው ማክሰኞ ዕለት የክትባት ሙከራው ለጊዜውም ቢሆን መሰናከሉ ሲሰማ በበርካቶች ዘንድ ድንጋጤን የፈጠረው። ትናንት ግን የተመናመነውን ተስፋ መልሶ የሚያለመልም ዜና ተሰምቷል። ይሄው አስትራዜኔካና በኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ እየሰሩት ያለው ዓለም ተስፋ የጣለበት የኮቪድ-19 ክትባት ሙከራ ሊጀመር መሆኑ ተገልጿል። የክትባት ሙከራው እንዲቆም የተደረገው በዩናይትድ ኪንግደም በሚገኙ አንድ የሙከራው ተሳታፊ ላይ የጎንዮሽ ችግር በመታየቱ ነበር። ባሳለፍነው ማክሰኞም አስትራዜኔካ፤ ምርምሩ እንዲቆም የተደረገው በሙከራው ተሳታፊ ላይ የታየው የጤና ችግር ከክትባቱ ጋር ይያያዝ፤ አይያያዝ እንደሆነ ለመፈተሽ እንደሆነ ተናግሯል። ይሁን እንጅ ቅዳሜ ዕለት ኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ የክትባቱን ሙከራ መቀጠል እንደሚቻል አስታውቋል። የዩናይትድ ኪንግደም የጤና ሴክሬታሪ ማት ሃንኮክ ሙከራው እንደገና ሊቀጥል የመሆን ዜናውን በደስታ ተቀብለዋል። "ሙከራው እንዲቆም መደረጉ የሚያሳየው፤ ለደህንነት ቅድሚያ እንደምንሰጥ ነው። ተመራማሪዎቻችን በአፋጣኝና በተቻለ መጠን ውጤታማ የሆነ ክትባት እንዲያቀርቡም እንደግፋቸዋለን" ብለዋል። ዩኒቨርስቲው በበኩሉ "ልክ እንደዚህ ሰፊ የክሊኒካል ሙከራዎች በሚደረጉበት ጊዜ አንዳንድ የሙከራው ተሳታፊዎች ጤናቸው ሊታወክ ስለሚችል፤ ሙከራው ለጊዜው እንዲቆም መደረጉ የሚጠበቅ ነው" ብሏል በመግለጫው። ደህንነትን የሚመለከት ገለልተኛ ኮሚቴ እና የዩናይትድ ኪንግደም የመድሃኒትና እና የጤና መጠበቂያ ምርቶች ተቆጣጣሪ የሰጠውን ምክረ ሃሳብ ተከትሎም ምርምሩ አሁን ሊቀጥል እንደሚችልም አክሏል። የምርምሩ ተሳታፊ ያጋጠማቸውን የጤና እክል በተመለከተ ሚስጢር ለመጠበቅ ሲባል እንደማይገልፅ የተናገረ ቢሆንም፤ ኒው ዮርክ ታይምስ በዩናይትድ ኪንግደም የሚገኙት የሙከራው በጎፈቃደኛው በአንድ በኩል ያለው የአከርካሬ አጥንታቸው ላይ ያሉ ነርቮች መቆጣት እንዳጋጠማቸው ዘግቧል። በመላው ዓለም 180 የሚጠጉ የከትባት ሙከራዎች እየተካሄዱ ሲሆን እስካሁን ግን የክሊኒካል ሙከራቸውን አለማጠናቀቃቸውን የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል። ይህ ክትባት የመጀመሪያ እና ሁለተኛ የሙከራ ምዕራፉን በስኬት በማጠናቀቁ መጀመሪያ ላይ ገበያ ላይ ሊውሉ ይችላሉ ተብሎ ከፍተኛ ተስፋ ከተጣለባቸው ክትባቶች አንዱ ነው። ክትባቱ ወደ ሦስተኛው የሙከራ ምዕራፍ የተሸጋገረው በቅርብ ሳምንታት ሲሆን 30 ሺህ በጎ ፈቃደኞችን አሳትፏል። እነዚህ በጎ ፈቃደኞች በአሜሪካ፣ በዩናይትድ ኪንግደም፣ በብራዚል፣ በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ናቸው። በክትባት ማበልፀግ ሂደት ሦስተኛው ምዕራፍ በሺዎች የሚቆጠሩ በጎፈቃደኞች የሚሳተፉበት ሲሆን ዓመታትንም ሊወስድ ይችላል። የአገሪቷ መንግሥት የሳይንስ አማካሪ ፓትሪክ ቫላንስ፤ ሙከራው የመቋረጡ ዜና በተሰማ ማግስት "በኦክስፎርድ የሙከራ ሂደት ላይ ያጋጠመው ያልተለመደ አይደለም" ብለዋል።
46819694
https://www.bbc.com/amharic/46819694
ማህበራዊ ሚዲያዎችን መጠቀም የሌለብዎት ሰአት መቼ ነው?
ማህበራዊ ሚዲያዎች በአብዛኛዎቻችን እንቅልፍ ስርአት ላይ ከፍተኛ የሆነ ተጽእኖ እያሳደሩ ነው። ታዲያ እነዚህን ማህበራዊ ሚዲያዎች ገሸሽ ማደረግ ያለብን ሰአት የትኛው ነው?
የዘመኑ ወጣቶች በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚያጠፉትን ጊዜ ለተመለከተ ወዴት እየሄድን ነው የሚለውን ጥያቄ ያስነሳል? ባደጉት ሃገራት የሚገኙ ከ11 እስከ 15 ዓመት የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ወጣቶች በአማካይ ከ6 እስከ 8 ሰአታትን ማህበራሚዊ ሚዲያዎች ላይ ወሬዎችን ሲቃርሙ ያሳልፋሉ። • ፌስቡክ የምንጠቀምበት ሰዓት ሊገደብ ነው • ሶሻል ሚድያ በተጠቃሚዎች ላይ የሚያስከትለውን ጉዳት ያውቃሉ? አንድ የተሰራ ሌላ ጥናት ደግሞ በእንግሊዝ የሚገኙ እድሜያቸው ገፋ ያሉ ሰዎች በእንቅልፍ ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም ያሳልፋሉ ይላል። አሜሪካ ውስጥ ደግሞ ከ13 እስከ 18 እድሜ ክልል ውስጥ ካሉ ታዳጊዎች 70 በመቶ የሚሆኑት 'ስናፕቻት' የተባለውን የማህበራዊ ሚዲያ የሚጠቀሙ ሲሆን 'ኢንስታግራም' የተባለውም ማህበራዊ ሚዲያ ከፍተኛ ተከታዮች አሉት ተብሏል። በዓለማችን የማህበራዊ ሚዲያዎች ተጠቃሚ ቁጥር ከሶስት ቢሊየን በላይ እንደሚሆን ይገመታል። አብዛኛዎቻችን ደግሞ ከአንድ በላይ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮችን እንጠቀማለን። በአማካይም ከ2 እስከ 3 ሰአት በእነዚህ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ እናጠፋለን። በማህበራዊ ሚዲያዎችና በድብርት መካከል ያለውን ግንኙነት ስናስብ ሁለት አይነት ተጽእኖ አንዳለው ማስተዋል ይቻላል። የመጀመሪያው ድብርትን ለማራገፍ ማህበራዊ ሚዲያዎች የሚጫወቱት ሚና ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ማህበራዊ ሚዲያዎችን አብዝተን ስንጠቀም የሚፈጠርብን ድብርት ነው። ነገር ግን በቅርቡ 2000 ሰዎችን አሳትፎ በተሰራ አንድ ጥናት መሰረት ማህበራዊ ሚዲያዎች አሉታዊ ተጽእኗቸው ከፍ ያለ እንደሆነ ያሳያል። በጥናቱ መሰረት ማህበራዊ ሚዲዎችን አብዝተው እንዲጠቀሙ የተደረጉት ተሳታፊዎች ድብርት፣ ጭንቀትና በአካባቢያቸው ካሉ ሰዎች ጋር ምንም አይነት ግንኙነት አለመፈለግን የመሳሰሉ ምልክቶች ታይተውባቸዋል። ''ምናልባትም ማህበራዊ ሚዲያዎችን የሚጠቀሙ ሰዎች ከጓደኞቻቸው ጋር እየተገናኙ ወይም መልእክት እየተለዋወጡ ሊሆን ይችላል፤ ነገር ግን ከየትኛውም ጓደኛቸው ጋር ፊት ለፊት ተያይተው አያወሩም'' ይላሉ በፒትስበርግ ዩኒቨርሲቲ የመገናኛ ብዙሃን ጥናት፣ ቴክኖሎጂና ጤና ማዕከል ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ብራያን ፕሪማክ። ፕሪማክና የጥናት ቡድናቸው 1700 ወጣቶች ላይ በሰሩት ጥናት መሰረት ማህበራዊ ሚዲያዎችን የምንጠቀምት ሰአት የሚያሳድርብንን የጫና አይነት ይለያየዋል። እንቅልፍ ከመተኛታችን ከ30 ደቂቃ በፊት ማህበራዊ ሚዲያዎችን የምንጠቀም ከሆነ ጥሩ ያልሆነና በጣም አጭር እንቅልፍ እንድንተኛ ሊያደርገን ይችላል ይላሉ ፕሪማክ። ይህ የሚሆነው ደግሞ ከስልካችን የሚወጣው ሰማያዊ ጨረር 'ሜላቶኒን' የተባለውን በሰውነታችን ውስጥ የሚገኘውን ንጥረ ነገር ስለሚጎዳው ነው። ይህ ንጥረ ነገር ደግሞ ዋነኛ ስራው የእንቅልፍ ሰአት ሲደርስ እንድንተኛ ማድረግ ነው። • በአሁኑ ወቅት በጣም ተፈላጊ የሆኑ የዲጂታል ዘርፍ ሥራዎች የትኞቹ ናቸው? • ስልክዎ እንደተጠለፈ የሚያሳዩ ሰባት ምልክቶች ''ሌላኛው ምክንያት ደግሞ ከመተኛታችን በፊት በማህበራዊ ሚዲያዎች የምንመለከታቸው ዜናዎችና ሌሎች መረጃዎች ብዙ ሃሳብ ያመጡብናል። በመተኛችን ሰአት ስለመረጃዎቹ ማሰላሰል እንጀምርና እንቅልፋችን እያየነው ያመልጠናል'' ሲሉ ያብራራሉ ፕሪማክ። ከዚህ በተጨማሪ ከእንቅልፍ በፊት የሰውነት እንቅስቃሴ ማድረግ ጥሩ አንቅልፍ እንድንተኛ ማድረጉ እሙን ነው። ብዙ ጊዜያችንን በማህበራዊ ሚዲያ ባሳለፍን ቁጥር ደግሞ የእንቅስቃሴ ሰአታችን ይቀንሳል ማለት ነው። ይህም ሌላ ችግር ነው። ብዙ ተጠቃሚዎች ባሏቸው እንደ 'ፌስቡክና' 'ኢንስታግራም' ባሉ ማህበራዊ ሚዲያዎች ሰዎች ጥሩ ህይወት እየመሩ እንደሆነ የሚያሳዩ ምስሎችን በለጠፉ ቁጥርና ስለጎበኟቸው ቦታዎች ባወሩ ቁጥር፤ የእኛን ህይወት ከእነሱ ጋር እያወዳደርን የምንጨነቅ ከሆነ ወደ ድብርትና እነቅልፍ ማጣት መውሰዳቸው ደግሞ ሌላኛው የማህበራዊ ሚዲያ ጉዳት ናቸው። የእንቅልፍ ሰአታችን በቀነሰ ቁጥር ደግሞ ለልብ በሽታዎች ያለን ተጋላጭነት ይጨምራል፤ የስኳር በሽታና አላስፈላጊ ውፍረትን የመሳሰሉ ችግሮችንም አብሮ ይዞ ይዞ ይመጣል። • ከጥንት ሮማውያን እስከ ትዊተር የደረሰው የ# ምልክት በዚህ በጣም ተጎጂ የሚሆኑት ደግሞ ታዳጊዎቹ ናቸው። ምክንያቱም ሰውነታቸው ገና እድገቱን ያልጨረሰ እንደመሆኑ እንቅልፍ ማጣት ብዙ የሰውነት ስርአቶችን የማዳከምና የማጥፋት እድሉ ከፍተኛ ነው። ስለዚህ ይላሉ ባለሙያው፤ ቤተሰቦችና መምህራን ታዳጊዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ስለሚያጠፉት ጊዜ ሊጠይቁና ክትትል ሊያደርጉ ይገባል።
news-49290010
https://www.bbc.com/amharic/news-49290010
የኤርትራ ብሔራዊ አገልግሎት "ታዳጊዎችን ማብቂያ ለሌለው ለባርነት" እየዳረገ ነው ተባለ
ኤርትራ ምንም እንኳን ከኢትዮጵያ ጋር የሠላም ስምምነት ላይ ብትደርስም በብሔራዊ አገልግሎት ሰበብ ታዳጊዎችን ማብቂያ በሌለው ባርነት ውስጥ በማስገባት እየተከሰሰች ነው።
ሂማን ራይትስ ዎች ባወጣው ሪፖርት ላይ እንዳመለከተው በየዓመቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ትምህርታቸውን ሳያጠናቅቁ ጭምር ለግዴታ ወታደራዊ ስልጠና እንዲገቡ እንደሚገደዱ ገልጿል። ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የቆየውን የጦርነት ፍጥጫ ለማብቃት ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር የሠላም ስምምነት ካደረገች አንድ ዓመት ቢቆጠርም የብሔራዊ አገልግሎቷ እንደቀጠለ መሆኑ ይነጋራል። • ኤርትራ፡ ''እናቶች ከህጻናት ልጆቻቸው ጋር ታስረዋል'' • ኤርትራ በሳዋ ባደረገችው ወታደራዊ ትዕይንት ምን እያለች ይሆን? በተለያዩ ሃገራት የሚገኙ ኤርትራዊያንም ይህ የብሔራዊ አገልግሎት ተሳታፊዎች የሚሰለጥኑበት አስፈሪው የሳዋ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ማዕከል እንዲዘጋ የሚጠይቅ የመረጃ መረብ ዘመቻ ሲያካሂዱ ቆይተዋል። ሪፖርቱ ጨምሮም ሁሉም የመጨረሻ ዓመት የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች በጥብቅ ወታደራዊ ሥነ ሥርዓት በሚተዳደሩበትና ለቀላል ጥፋቶች አስከፊ ቅጣት ወደሚፈጸምበት ሳዋ ወታደራዊ ማዕከል እንዲገቡ ይደረጋል። ከስልጠናው በኋላም የተወሰኑት በሠራዊቱ ውስጥ እንዲቆዩ፣ ሌሎች ደግሞ በመምህርነት ወይም በሌላ የመንግሥት ሥራ ላይ ላልተወሰነ ጊዜ እንዲቆዩ ይደረጋል። መምህራንም በዝቅተኛ ክፍያ ማብቂያው ለማይታወቅ ጊዜ በሳዋ ማሰልጠኛ ማዕከል ውስጥ እንዲሰሩ እንደሚገደዱ ተጠቅሷል። ሂማን ራይትስ ዎች "እያስተማሩን ሳይሆን ባሪያ እያደረጉን ነው" በሚል ርዕስ በኤርትራ ስለሚካሄደው የግዳጅ ብሔራዊ አገልግሎት ላይ ባወጣው ሪፖርት ምልመላው ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው መምህራንና ተማሪዎች ኤርትራን ጥለው እንዲሰደዱ በማድረግ በሃገሪቱ የትምህርት ሥርዓት ጥራት ላይ ከባድ ጉዳትን የሚያስከትል ተጽእኖ እንዳለው አመልክቷል። "ማብቂያ የሌለው ብሔራዊ አገልግሎት ነው" ሲል በሳዋ ማሰልጠኛ ማዕከል ማስተማር የነበረበትና ባለፈው ዓመት ኤርትራን ጥሎ የተሰደደው የ25 ዓመቱ ወጣት ለሂማን ራይትስ ዋች ተናግሯል። • "መኖር የምፈልገው ልጆቼን ለማየት ብቻ ነው" • "አሁን ያገኘነው ሰላም ከሰው ሳይሆን ከአምላክ ነው"- ዘማሪ ሳሙኤል ተስፋሚካኤል "የፊዚክስ ትምህርትን ለማስተማር ከተመለመልክ፤ እድሜ ልክህን ሙሉ የፊዚክስ መምህር ሆነህ ትቀራለህ።" ባለፈው ሳምንት ኤርትራ የብሔራዊ አገልግሎቱ በከፍተኛ ደረጃ ሃገሪቱን እንደጠቀመ በመግለጽ የተጀመረበትን 25ኛ ዓመት ለቀናት በቆየ ደማቅ ሥነ ሥርዓት አክብራለች። ብሔራዊ አገልግሎቱ እንዲቆም የሚጠይቁ ዘመቻዎችን የሚያካሂዱ ሰዎች ግን ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ግንኙነት ስለተሻሻለ ለውጥ ማካሄድ አለባት ይላሉ። "አሁን ከኢትዮጵያ ጋር ያለው ችግር ተፈትቷል፤ ስለዚህ ከሃገሪቱ ወጣቶች መብትና ነጻነት በመጀመር በሰብአዊ መብቶች አያያዝ ላይ የሚደረጉ ለውጦች ተከትለው መምጣት አለባቸው" ሲሉ በሂማን ራይትስ ዎች ከፍተኛ የአፍሪካ ተመራማሪ በመግለጫው ላይ ሃሳባቸውን ሰጥተዋል።
news-54950902
https://www.bbc.com/amharic/news-54950902
በአሜሪካ የጥላቻ ወንጀሎች በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩ ተጠቆመ
በአሜሪካ የጥላቻ ወንጀሎች በከፍተኛ ሁኔታ መጨመራቸውንና በባለፉት አስር አመታትም ታይቶ በማያውቅ ደረጃ መድረሱን አንድ ሪፖርት ይፋ አድርጓል።
ሪፖርቱን ያወጣው የአሜሪካው የፌደራል ምርመራ ቢሮ (ኤፍቢአይ) ነው። በጥላቻ የተነሳሱ ግድያዎችም በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን የሚያሳየው ይህ ሪፖርት በባለፈው አመት 51 ሞቶች እንደተመዘገቡና ይህ ቁጥርም ከሁለት አመት በፊት ከነበረው ጋር ሲነፃፀር በእጥፍ ማደጉን ነው። በባለፈው አመት ነሐሴ በቴክሳስ ኤልፓሶ በሚገኘው የዋልማርት መገበያያ መደብር ውስጥ የሜክሲኮ ዜጎች ላይ ባነጣጠረ ጥቃት 22 ሰዎች ተገድለዋል። ከጎሮጎሳውያኑ 2014 ጀምሮም የጥላቻ ወንጀሎች በከፍተኛ ሁኔታ መጨመራቸውንም መረጃዎች ያሳያሉ። በርካታ ተሟጋቾችም አገሪቷ ውስጥ የሰፈነው የዘረኝነትና ሌሎች ጥላቻዎች እንደሚጨምሩም እያስጠነቀቁ ነው። የኤፍቢአይ አመታዊ የጥላቻ ወንጀሎች ሪፖርት እንደሚያሳየው በባለፈው አመት 7 ሺህ 314 ወንጀሎች የተመዘገቡ ሲሆን፣ ከሁለት አመት በፊት 7 ሺህ 120 ነበር። ከፍተኛ የተባለው ቁጥር የተመዘገበው በጎሮጎሳውያኑ 2008 ሲሆን ቁጥሩም 7 ሺህ 783 ነው። ሪፖርቱ የጥላቻ ወንጀል ብሎ የተረጎመው ወንጀሎች በዘር፣ በብሄር፣ በሃይማኖት፣ በፆታዊ አተያይ፣ በአካል ጉዳተኝነት፣ በፆታዊ ማንነትና ሌሎችም ጉዳዮች ተነሳስቶ ሲፈፀም ነው። መረጃው እንደሚያሳየው ከሃይማኖት ጋር በተያያዘ ወንጀሎች 7 በመቶ የጨመሩ ሲሆን በተለይም በይሁዲ እምነት ተከታዮችና ተቋማት ላይ ያነጣጠረ እንደሆነም ተገልጿል። ከዚህም በተጨማሪ ፀረ- ላቲን ወንጀሎችም እንዲሁም በአስር አመታት ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን መረጃው ጠቁሟል። በኤልፓሶ የተከሰተውና የ22 ሰዎች ህይወት የተቀጠፈበት በጥላቻ የተነሳሳ ጥቃትም ተካቶበታል። ሆኖም ከየትኛውም ቡድን ቢሆን የጥላቻ ወንጀል በትር በከፍተኛ ሁኔታ የሚያርፍባቸው ጥቁር አሜሪካውያን ናቸው። ምንም እንኳን በጥቁር አሜሪካውያን ላይ ያነጣጠረው የጥላቻ ወንጀል በትንሽም ቢሆን እንደቀነሰ የኤፍቢአይ ሪፖርት ቢያሳይም ከፍተኛ ቁጥሩን የሚይዙት እነሱ ናቸው። በኤፍቢአይ ውስጥ በዘር ወይም በብሄር ጥላቻ ምክንያት ከተመዘገቡት 4 ሺህ930 ጥቃት የደረሰባቸው መካከል 48.5 በመቶ በፀረ- ጥቁር ወይም አፍሪካ አሜሪካውያንን ጥላቻ ጋር የተያያዘ ነው። የኤፍቢአይ ሪፖርት መውጣቱን ተከትሎ በርካታ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች መረጃዎች በተጠናቀረ መልኩ እንዲሰባሰቡና የተሻለ ሪፖርት የሚደረግበት ዘዴ እንዲቀየስ ጥሪ አቅርበዋል። አንዳንድ የኤፍቢአይ ሪፖርት ሙሉ የጥላቻ ወንጀሉን መረጃ አያሳይም ብለዋል።
55258554
https://www.bbc.com/amharic/55258554
የቀድሞው የጣሊያን ኮከብ እግር ኳስ ተጫዋች ፓውሎ ሮሲ አረፈ
ጣሊያን በ1982 (እአአ) የዓለም ዋንጫን ባሸነፈችበት ወቅት ኮከብ የነበረው ፓውሎ ሮሲ በ64 ዓመቱ ማረፉን ቤተሰቦቹ አሳወቁ።
ስፔን ውስጥ በተካሄደው የዓለም ዋንጫ የጣሊያን ብሔራዊ ቡደን ዋንጫውን ባነሳበት ጊዜ ፓውሎ ሮሲ ኮከብ ግብ አግቢና ተጫዋች በመሆን የተመረጠ ሲሆን ዝናው በዓለም ዙሪያ ናኝቶ ነበር። ሮሲ በጣሊያን ሊግ ውስጥ እውቅናን ማግኘት የጀመረው ቪያቼንዛ ለተባለው ቡድን በተጫወተበት ጊዜ በርካታ ግቦችን በማስቆጠር የነበረ ሲሆን፤ ከዚያም ወደ ታዋቂዎቹ የጣሊያን ክለቦች ጁቬንቱስና ኤሲ ሚላን ተዘዋውሮ ተጫውቷል። የጣሊያን መገናኛ ብዙሃን ሮሲ ለረጅም ጊዜ በህመም ከቆየ በኋላ ሕይወቱ ማለፉን ገልጸዋል። የሮሲ ባለቤት ፌዴሪካ ካፔሌቲ ሞቱን ተከትሎ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጿ ላይ ከሮሲ ጋር አብረው የተነሱትን ፎቶ በመለጠፍ "ለዘላለም" የሚል ጽሁፍ አስፍራለች። ባለቤቱ፤ ፓውሎ ሮሲ በምን ምክንያት ለሞት እንደበቃ ምንም ያለችው ነገር ግን የለም። ሮሲ ለጣሊያን ብሔራዊ ቡድን በተጫወተባቸው 48 ጨዋታዎች ላይ 20 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን፤ በሴሪ አ ለቪያቼንዛ፣ ፔሩጂያ፣ ለጁቬንቱስ፣ ሚላንና ቬሮና በተጫወተባት ጊዜ ከ100 በላይ ግቦችን አስቆጥሯል። በ1077 (እአአ) ወደ ሴሪ አ እንዲያድግ ያደረገው ቪያቼንዛ ቡድን የሮሲ ሞት በክለቡ ላይ የፈጠረውን ስሜት "አንዳንድ ጊዜ ሁላችንም የተሰማንን ህመም የምንገልጽባቸው ቃላቶችን እናጣለን" በማለት ባወጣው መግለጫ ላይ አስፍሯል። ሮሲ በዓለም ዋንጫ የአገሩ ብሔራዊ ቡድን ዋንጫ እንዲያገኝ ካደረገ በኋላ በወቅቱ ለአውሮፓዊ የዓመቱ ምርጥ የእግር ኳስ ተጫዋች ይሰጥ የነበረውን የቦሎን ዶር ሽልማትን አግኝቶ ነበር። ፓውሎ ሮሲ እግር ኳስ መጫወት ካቆመ በኋላ ለስካይ፣ ሚዲያሴት እና ራይ ለተባሉ የመገናኛ ብዙሃን የእግር ኳስ ተንታኝ ሆኖ ሰርቷል።
news-53302605
https://www.bbc.com/amharic/news-53302605
በአማራ ክልል በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን በደረሰ ጥቃት ሰዎች መጎዳታቸው ተገለፀ
ሸኔ የተባለው ታጣቂ ቡድን ከሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር በተቀናጀ በአማራ ክልል ውስጥ ጥቃት መፈጸሙን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን ጥሩነህ መግለጻቸውን የአገር ውስጥ መገናኛ ብዙኀን ዘገቡ።
በአማራ ክልል በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ውስጥ በሚገኝ ደዌ አረዋ ወረዳ ላይና በባቲ ከተማ ላይ በተፈጸመው ጥቃት ወቅት በተደረገ የተኩስ ልውውጥ የቡድኑ መሪ መገደሉንና ሌሎች በጥቃቱ ተሳታፊ የነበሩ ታጣቂዎች ከነመሳሪያቸው መያዛቸውም በዚሁ ዘገባ ላይ ተገልጿል። ርዕሰ መስተዳደሩ ጨምረውም በባቲ ከተማ ውስጥ በአንድ ሆቴል ላይ በተፈጸመ የቦንብ ጥቃት አምስት ሰዎች ላይ የመቁሰል አደጋ መድረሱን ገልጸዋል። አቶ ተመስገን እንዳሉት ጥቃቱ በአዲስ አበባ ከተፈጸመው የድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር በተያያዘ በአካባቢው ሽብር ለመፍጠር በማቀድ የተፈጸመ መሆኑን ገልጸዋል። በብሔራዊው ቴሌቪዥን ላይ በቀረበው ዘገባ እንደታየው በእሳት የወደሙ ቤቶችና አንድ አውቶብስ ከደረሰበት ጥቃት መቃጠሉ ይታያል። አቶ ተመስገን የታጣቂ ቡድኑ ዓላማ አዲስ አበባ ከተፈፀመው ግድያ ር የተያያዘ ተልእኮ እንደተሰጣቸው አረጋግጠናል ብለዋል። ከታጣቂ ቡድኑ ጋር በነበረው የተኩስ ልውውጥ አንድ የጸጥታ አባል መቁሰሉን አቶ ተመስገን በሰጡት መግለጫ ላይ ጠቅሰዋል። የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ከዚህ በኋላ መንግሥት "የሸረሪቱ ድር ላይ ብቻ ሳይሆን ሸረረቷ ላይም አተኩሮ ይሰራል" ብለዋል። አክለውም ክልላቸው በየትኛውም መልኩ ከፌደራል መንግሥት ጎን እንደሚቆሙ ተናግረዋል። ከድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በኋላ በተፈጠረ ግርግር ፖለቲከኞች ጋዜጠኞችና የተለየዩ ከተማ ነዋሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ይታወቃል። እንዲሁም በአዲስ አበባ በደረሱ ጥቃቶች ሁለት ፖሊሶችን ጨምሮ ቢያንስ አስር ሰዎች ህይወታቸው መጥፋቱ የተገለጸ ሲሆን በተመሳሳይ በተለያዩ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች ውስጥም 11 የጸጥታ ኃይሎችን ጨምሮ 156 ሰዎች ሞተዋል። ከማክሰኞ ጀምሮ በነበሩት ተከታታይ ቀናት በኦሮምያ በተፈጸሙ ግድያዎችና የንብረት ውድመቶች የተጠረጠሩ 1084 ሰዎችን መያዙን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ሲያስታውቀ፣ በአዲስ አበባና በድሬዳዋም በርካታ ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተነግሯል።
news-55349590
https://www.bbc.com/amharic/news-55349590
ራሷን ጎዳና ላይ ያዋለደችው እናት በአዳማ
ይህ የሆነው አዳማ ከተማ ነው። ታሪኩ ደግሞ የአንዲት ወጣት። ወጣቷ ኑሮዋን መስርታ የነበረው ጎዳና ላይ ነው።
የጎዳና ላይ ኑሮ ደግሞ በችግሮች የተሞላ ነውየምትለው ጠይባ እርሷና ጨቅላ ልጇ ወደሚኖሩባት አዳማ የመጣችው የእለት ጉርስ ለማግኘት፣ ሰርቶ ለማደር በመሻት ነበር። ጠይባ በሥራ ምክንያት ከጭሮ ወደ አዳማ የመጣችው ከጥቂት ዓመታት በፊት ነው። "አባትና እናት የለኝም። ትምህርት ስለጨረስኩ ሥራ ይገኛል መባሉን በመስማቴ ነው ወደ አዳማ የመጣሁት" ስትል ለቢቢሲ ቃሏን ሰጥታለች። ጠይባ አዳማ ላይ ሥራ ስትፈልግ በሌላ በኩል ፍቅር የልቧን ደጃፍ አንኳኳ እናም የወንድ ጓደኛ ይዛ አብረው መኖር ጀመሩ። በዚህ መካከል ነፍሰጡር መሆኗን አወቀች። ጓደኛዋ በተለያዩ ሱሶች ውስጥ ያለ ወጣት እንደነበር የምትናገረው ጠይባ የተለያዩ ጥቃቶች ያደርስባት እንደነበር ትናገራለች። በየዕለቱ የሚደርስባት ድብደባ ስለበዛባት የሰባት ወር ነፍሰጡት ሆና ወደ ጎዳና ወጣች። "እዚሁ አዳማ ኃይለማርያም ሆስፒታል አጠገብ ሳድር ነበር፤ ሲገኝ በልቼ ሳጣ እንዲሁ ጦሜን እያደርኩ ከረምኩ። የሰባት ወር ነፍሰጡር ሆኜ እስክወልድ ድረስ እዚያው ነው የኖርኩት።" ደራሽ ምጥ ጎዳና ላይ ጠይባ ሕይወቷን የአዳማ ጎዳናዎች ላይ ከማድረጓ በፊትም ሆነ ከዚያ በኋላ የእርግዝና ክትትል ለማድረግ ወደ ሕክምና ተቋም ሔዳ እንደማታውቅ ለቢቢሲ ተናግራለች። በተወለደችበት አካባቢ እናቶች ሲወልዱ ምን እንደሚያስፈልጋቸውና ምን ማድረግ እንዳለባት ስትሰማ ስለነበር ይህንኑ እራሷ ላይ ለመተግበር እንደወሰነች ታስረዳለች። ድንገት ምጧ መጥቶ የሚያዋልዳት በዙሪያዋ ባይኖር፣ የጤና ተቋም የሚያደርሳት ቢጠፋ፣ የልጇን እትብት የምትቆርጥበት ምላጭ ማዘጋጀቷን ገልጻለች። " እናቶቻችን ነፍሰጡር ሴት ምላጭ ከእጇ ማጣት እንደሌለባት ሲናገሩ እሰማ ነበር። እኔም ቀድሜ ምላጭ ገዝቼ ቦርሳዬ ውስጥ አስቀመጥኩኝ" ጠይባ የገመተችው ከመሆን ያገደው አንዳች ነገር የለም። የመውለጃዋ ቀን በተቃረበበት ሰሞን ልብስ ለማጠብ ውሃ ወዳለበት ሰፈር እየሄደች ሳለች ሕመም ጀመራት፤ ምጧ መምጣቱን አልተጠራጠረችም። " . . .የሕመም ስሜት ሲሰማኝ፣ በአቅራቢያዬ ወደነበረው የመኪና ማጠብዬ ተጠግቼ፣ መኪና የሚያጥቡ ሰዎች የሚያርፉበት ክፍል ገባሁኝ" በማለት ሁኔታውን ታስታውሳለች። እርሷ እንደምትለው ከሆነ፣ በክፍሉ ውስጥ የነበሩ ሰዎች፣ እርሷ ምጥ ላይ መሆኗን ሲያውቁ፣ ክፍሉን ለቅቀው የሄዱ ሲሆን እርሷም ብቻዋን ልጇን በሰላም ተገላግላለች። " ምጥ መሆኑን እንዳወቅኩኝ ቶሎ ብዬ ምላጩን ከቦርሳ ውስጥ አወጣሁኝ፤ ትንሽ ቆይቼ ልጁ ልክ እንደተወለደ ራሴን ሳልስት እትብቱን በጣቶቼ ሰፍሬ ቆረጥኩኝ። ከልብሴ ላይም ክር ቆርጬ የልጄን እትብት አበትኩኝ። ከዚያ በኋላ የማስታውሰው ከላይ የለበስኩትን ለልጄ ማልበሴን ብቻነው፤ ወዲያው ራሴን ሳትኩ" ከአንድ ሰዓት በኋላ ሰዎች መጥተው ከስፍራው እንዳነሷት እና የሕክምና ተቋም እንደወሰዷት የምትናገረው ጠይባ፣ በአሁኑ ሰዓት እዚያው አዳማ ከተማ የተወሰኑ ሰዎች ባደረጉላት ድጋፍ ቤት ተከራይታ መኖር ጀምራለች። "ያኔ የነበረውን ነገር ሳስታውስ እንቀጠቀጣለሁ፤ ነገር ግን እንኳንም ሁለት ሆንን በልጄ ደስተኛ ነኝ። ካሁን በኋላ ምንም ብቸገር ልጄን አሳድገዋለሁ። የልጄ ጤንነት በጥሩ ሁኔታ ላይ ነው ያለው። እርሱም ከጠነከረ ስራ እጀምራለሁ" በማለት ያላትን ተስፋ ትገልጻለች። የአዳማ ከተማ የጎዳና ተዳዳሪዎች ከሚበዙባቸው የኢትዮጵያ ከተሞች መካከል አንዷ ናት። በአዳማ ከተማ አስተዳደር የሴቶች እና ሕጻናት ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ባለሙያ የሆኑት አቶ ኢደኦ ደዋኖ በአዳማ በጎዳና ላይ የሚኖሩ ሕጻናትና እናቶች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ነው ብለዋል። በተለያየ ችግር ከአጎራባች ዞኖች የሚመጡ ሰዎች ወደ ጎዳና ኑሮ ይገባሉ ሲሉም ይናገራሉ። ምን ያህል ሰዎች በጎዳና ላይ እንደሚኖሩ ግን የከተማ አስተዳደሩ በቁጥር የተደገፈ መረጃ እንደሌለው በመግለጽ አዳማ ጎዳና ላይ ሁሌም አዳዳስ ፊቶች ኑሮ ጀምረው እነደሚታዩ ተናግረዋል። ከዚህ ቀደም በከተማይቱ ጎዳና ላይ የሚኖሩ ሰዎችን የማንሳት ስራ የተጀመረ ቢሆንም፣ አዳዲስ ሰዎች በሚነሱ ሰዎች በመተካት እንዲሁም የተነሱ ሰዎች ቦታ በመቀየር ወደ ጎዳና በመመለሳቸው፣ ችግሩ መፍትሔ እንዳያገኝ አድርጎታል ብለዋል። የጎዳና ተዳዳሪዎችን በዘላቂነት በመደገፍ እና መልሶ በማቋቋም ላይ በቋሚነት የሚሰሩ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ባለመኖራቸውም ችግሩ እንዳይፈታ ምክንኣት ሆኗል ሲሉ ሃሳባቸውን አጠናቅቀዋል።
51505693
https://www.bbc.com/amharic/51505693
የሉሲዎቹና የአዳማ ክለብ ጎል አዳኝ ሴናፍ ዋቁማ
የሉሲዎቹና የአዳማ ክለብ ጎል አዳኝ የፊት መስመር ተጫዋች ነች፤ ሴናፍ ዋቁማ። ትውልድና እድገቷ በነቀምት ነው።
ለእግር ኳስ ያላትን ፍቅር ስትገልጽ "ትምህርት ቤት እያለሁ ለኳስ ካለኝ ፍቅር የተነሳ እጫወት የነበረው ከወንዶቹ ጋር ነበር" ትላለች። ትኩረቷን ሙሉ በሙሉ ለኳስ ከሰጠች በኋላ ነቀምት በሚገኙ የእግር ኳስ ፕሮጀክቶች ውስጥ ታቅፋ ስልጠናዎችን ወስዳለች። ከዚያም በነበራት አቋም ተመርጣ ወደ አሰላ በመሄድ ለአራት ዓመታት ስልጠና ወስዳለች። • "በሀገራችን ከሶስት ሴቶች አንዷ ላይ ጾታዊ ጥቃት ይደርሳል" • በወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር እየዋሉ መሆኑን አቃቤ ሕግ አስታወቀ • የሕዝብ እንደራሴዎችን ጎራ አስለይቶ ያሟገተው ሕግ "የሰዎች አመለካከት ጥሩ አልነበረም" የምትለው ሴናፍ፤ በእግር ኳስ ህይወቷ ማህበረሰቡ ሴቶች እግር ኳስ መጫወታቸውን በበጎ አለመመልከቱ የእግር ኳስ ህይወቷን ፈታኝ አድርጎባት እንደነበረ ታስረዳለች። "ሴቶች ከቤት መውጣት የለባቸውም የሚል አመለካከት ነበር። እግር ኳስ መጫወት ደግሞ እንደ ሃፍረት ነበር የሚቆጠረው" የምትለው ሴናፍ፤ የማህብረሰቡ አመለካከት በወላጆቿ ላይ ጭምር ጫና በማሳደሩ ወላጆቿ እግር ኳስ መጫወት ማቆም እንዳለባት ሲነግሯት እንደነበረ ታስታውሳለች። "እኔ ግን ይህ ሁሉ አመለካከት ወደ ኋላ አላስቀረኝም። ዓላማዬ አድርጌ ይዤው ስለነበረ ማንም ሊያስቆመኝ አልቻለም። ቤተሰቦቼም ይህን ሲረዱ እኔን መደገፍ ጀመሩ" ትላለች። ሴናፍ ተማሪ እያለች ፍቅሯ ለእግር ኳስ እንጂ ለትምህርት አልነበረም። በዚህም ብዙ ጊዜዋን የምታሳለፍው ኳስ በመጫወት ነበር። "አገርን ወክሎ እንደመሳተፍ የሚያስደስት ነገር የለም" የምትለው ሴናፍ፤ በ2011 በሁለት ዘርፎች የውድድር አሸናፊ ነበረች። በኢትዮጵያ የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 21 ጎሎችን በማሰቆጠር ኮከብ ግብ አግቢ እና የውድድር ዓመቱ ኮከብ ተጫዋች ተብላ ተሸልማለች። ክለቧ አዳማም፣ የውድድሩ ሻምፒዮን ሆኖ እንዲጨርስ የራሷን አስተዋጽኦ አበርክታለች። የ25 ዓመቷ እግር ኳሰኛ ሴናፍ፤ ወደፊት በእግር ኳሱ ዓለም ፕሮፌሽናል ተጫዋች ሆና መቀጠል ምኞቷ ነው። "አንድ ሰው ከቆረጠ እና በያዘው ላይ ካተኮረ ያሰበበትን ማሳካት አይሳነውም" በማለት ከራሷ የህይወት ተሞክሮ በመነሳት የፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋችነት ህልሟን እንደምታሳካ በልበ ሙሉነት ትናገራለች። አንድነት ነገር ማሳካት እንደማይቻል የምናስብ ከሆነ ከስኬት መድረስ እንችልም ስለዚህ ያሰብነው እንዲሳካ በቁርጠኝነት መስራት ይኖርብናል ትላለች። ሴናፍ የኔይማር ጁኒየር አድናቂ መሆኗን ትናገራለች።
news-42233452
https://www.bbc.com/amharic/news-42233452
የዶናልድ ትራምፕ የጉዞ እገዳ ዕቅድ ተግባራዊ ሊሆን ነው
የአሜሪካ ጠቅላይ ፍድርድ ቤት ትራምፕ ከስድስት ሙስሊም ከሚበዛባቸው ሃገራት የሚመጡ ሰዎች ወደ ሃገራቸው እንዳይገቡ ያወጡት የጉዞ እገዳ ተግባራዊ እንዲሆን አዟል።
ውሳኔው ከቻድ፣ ኢራን፣ ሊቢያ፣ ሶማሊያ፣ ሶሪያና የመን የሚመጡ ሰዎች ወደ ሃገሬ አይገቡም ሲሉ ትራምፕ የገቡትን ቃል ተፈፃሚነት እንደሚያረጋግጥላቸው እየተነገረ ይገኛል። እገዳው ትራምፕ ወደ ሥልጣን ከመጡ ወዲህ ለሦስተኛ ጊዜ ያወጡት የጉዞ ማገጃ ዕቅድ ሲሆን ብዙ ተቃውሞ ገጥሞትም እንደበረ ይታወሳል። ዕቅዱ ላይ ብይን ለመስጠት ከተቀመጡት ዘጠኝ ዳኞች መካከል ሰባቱ ዕቅዱ እንዲፀድቅ የደገፉ ሲሆን የተቀሩቱ ተቃውሟቸውን ገልፀዋል። በቀጣይ. . .? ምንም እንኳ ዕቅዱ ተግባራዊ እንዲሆን ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ብይን ይስጥ እንጂ እገዳው አሁንም ብዙ እክሎች ከፊቱ እንዳሉ እየተነገረ ነው። ሳን ፍራንሲስኮ፣ ካሊፎርንያ፣ ሪችሞንድና ቨርጂኒያ ግዛቶች ብይኑን በመቃወም ይግባኝ የጠይቁ ሲሆን የየግዛቶቹ ፍርድ ቤቶች ይግባኙን በዚህ ሳምንት ቀጠሮ ይዘዋል። ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ይግባኞቹ ተሰምተው ውሳኔ እንዲሰጥባቸውም አዟል። የይግባኝ መስማት ሂደቱ ከተከናወነ በኋላ በስተመጨረሻም ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ብይን ይሰጥበታል። የዕለተ ሰኞ ውሳኔ የአሜሪካ ከፍተኛ የሕግ አካል የሆነው ጠቅላይ ፍርድ ቤት አሁን ሥልጣን ላይ ያለውን አስተዳደር ሊደግፍ እንደሚችል ፍንጭ ሰጭ ነው ይላሉ ዳቪድ ሌቪን የተባሉ የካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ፕሮፌሰር። የዋይት ሃውስ ቃል-አቀባይ ሆጋን ጊድሌይ የትራምፕ አስተዳደር በውሳኔው አለመገረሙን ተናግራዋል። የአሜሪካው ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ጄፍ ሴሺንስ በበኩላቸው ውሳኔውን "ለአሜሪካውያን ደህንነት እጅግ አስፈላጊ ብይን" ሲሉ አሞካሽተውታል። የአሜሪካው ሲቪል ሊበርቲስ ሕብረት ግን ትራምፕ ለሙስሊሞች የመረረ ጥላቻ ያላቸው ናቸው ሲል ይኮንናል፤ ባለፈው ሳምንት የእንግሊዝ ቀኝ ዘመም አክራሪ ሃይል በበይነ መረብ የለቀቀውን ምስል ፕሬዚደንቱ በትዊተር ገፃቸው ላይ ማጋራታቸውን በማስታወስ። በቅርቡ በለንደን፣ ፓሪስ፣ ብራሰልስና በርሊን የደረሱትን አደጋዎች በማስታወስ፤ ትራምፕ ፖሊሲው አሜሪካንን ከሽብርተኞች በትር ይታደጋታል ሲሉ ይከራከራሉ። የሕግ ሰዎች ግን ፖሊሲው በደህንነት ሽፋን ሙስሊሞች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ የሚደረግ ሤራ ነው ሲሉ ይሞግታሉ። በአብዛኛዎቹ ግዛቶች ያሉ ዝቅተኛ ፍርድ ቤቶች ዕቅዱን እንደተቃወሙትም የሚዘነጋ አይደለም።
news-55992967
https://www.bbc.com/amharic/news-55992967
እነ አቶ ጃዋር የረሃብ አድማ እንዲያቆሙ በሃይማኖት አባቶች እና ፖለቲከኞች ተጠይቀው ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀሩ
ከ12 ቀናት በላይ በረሃብ አድማ ላይ የሚገኙት እነ አቶ ጃዋር መሐመድ የረሃብ አድማውን እንዲያቆሙ በሃይማኖት አባቶች እና ፖለቲከኞች ቢጠየቁም ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀሩ።
ከድምጻዊ ሃጫሉ በኋላ በቁጥጥር ስር ዋሉት እና ክስ ተመስርቶባቸው በእስር የሚገኙት እነ አቶ ጃዋር መሐመድ፣ በቀለ ገርባ፣ ሸመሰዲን ጠሃ እና ሃምዛ አዳነ በፖለቲከኞች እና በቤተሰብ አባላቶቻቸው ላይ የሚደርሰውን እስር እና ወከባ በመቃወም የረሃብ አድማ ማድረግ ከጀመሩ 12 ቀን አልፏቸዋል። ከአራቱ ተከሳሾች በተጨማሪ በአቶ ጃዋር መሐመድ የክስ መዝገብ ሥር የሚገኙት የአቶ ጃዋር መሐመድ ጠባቂዎች እና የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ ጋዜጠኛ መለሰ ዲሪብሳ የረሃብ አድማውን ተቀላቅለዋል። ከእነ አቶ ጃዋር ጠበቆች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ከድር ቡሎ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ከዚህ ቀደም ጠበቆች እና የቤተሰብ አባላት ምግብ እንዲበሉ ሲጠይቋቸው ቢቆዩም ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል። ዛሬ ታዋቂ ፖለቲከኞች እና የሃይማኖት አባቶች ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ተገኝተው ተከሳሾች የረሃብ አድማቸውን እንዲያቆሙ ቢጠይቋቸውም ፈቃደኛ ሳይሆኑ መቅረታቸውን አቶ ከድር ለቢቢሲ ተናግረዋል። "ከፖለቲከኞች የኦነግ ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ፣ አቶ ሌንጮ ለታ፣ አቶ ባቴ ኡርጌሳ፣ ከሃይማኖት አባቶች ደግሞ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ ቃሊቲ ተገኝተው ቢለምኗቸውም ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል" ሌላኛው የእነ አቶ ጃዋር ጠበቃ አቶ ሙስጋኑ ሙለታ፤ ፖለቲከኞቹ እና የሃይማኖት አባቶች የረሃብ አድማውን እንዲያቆሙ ሲጠይቁ በስፍራው እንደነበሩ ይናገራሉ። "እነ አቶ ጃዋር በጣም ተዳክመዋል። ብዙ መናገር እና መራመድ አይችሉም። ሰውነታቸው ዝሏል። ሃኪሞችም ብዙ አታውሩ ብለዋቸዋል" ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። "ለሽምግልና የሄዱት ሰዎች 'ምግብ ብሉ። በራሳችሁ ላይ ጉዳት አታደርሱ' ሲሉ ነበር የጠየቋቸው። ይሁን እንጂ ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል" ሲሉ አቶ ምስጋኑ ተናግረዋል። አቶ ከድር ቡሎ በበኩላቸው የረሃብ አድማ እያደረጉ ካሉ ተከሳሾች መካከል የሕክምና እርዳታ አስፈልጓቸው ወደ ጤና ተቋም እየተወሰዱ ያሉ ተከሳሾች መኖራቸውን ተናግረዋል። ባሳለፍነው እሁድ የእነ አቶ ጃዋር መሐመድ ሃኪሞች "ምርመራ ካደረጉላቸው በኋላ ውሃ ካልወሰዱ አንዳንድ የሰውነት አካላቸው ሥራ ሊያቆም እንደሚችል ከነገሯቸው በኋላ ነው በግድ ውሃ እየወሰዱ ነው ያሉት። ምግብ የሚባል ነገር አፋቸው ጋር እየደረሰ አይደለም" ሲሉ ከእነ አቶ ጃዋር ጠበቆች መካከል አንዱ የሆኑት ምስጋኑ ሙለታ ለቢቢሲ ተናግረው ነበር። የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ በቁጥጥር ሥር የዋሉት እነ አቶ ጃዋር ከቀረቡባቸው ተደራራቢ አስር ክሶች ስድስቱ እንዲቋረጡ ፍርድ መወሰኑ ይታወሳል። የሽብር ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ፤ የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀል አዋጅ ፤ የጦር መሳሪያ አስተዳደርና ቁጥጥር አዋጅ የመተላለፍ ክሶች ከተመሰረቱባቸው ክሶች መካከል ሲሆኑ፤ እንዲቋረጡ የተደረጉት ክሶች የጦር መሳሪያ አስተዳደር እና ቁጥጥር አዋጅ 1177/2021 ጋር የተያያዙ ናቸው። የረሃብ አድማ ለምን? እነ አቶ ጃዋር መሐመድ የረሃብ አድማውን እያደረጉ ያሉት በፖለቲከኞች ላይ የሚደርሰውን እንግልት እና እስር፣ እነሱን ለመጠየቅና የችሎት ሂደታቸውን ለመከታተል ወደ ፍርድ ቤት በሚመጡ ሰዎች ላይ የሚፈጸም እስር እና ወከባ እንዲቆም ለመጠየቅ ነው። እነ አቶ ጃዋር መሐመድ እና በቀለ ገርባን ጨምሮ በርካታ ፖለቲከኞች የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ ከተፈጠረው ሁከት ጋር ተያይዞ እጃችሁ አለበት ተብለው ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር መዋላቸው የሚታወስ ነው። ከእነ አቶ ጃዋር በተጨማሪ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ከፍተኛ አመራሮች በተመሳሳይ የረሃብ አድማ ላይ ይገኛሉ። አቶ ሚካኤል ቦረን እና ኬነሳ አያና ፍርድ ቤት የዋስትና መብታቸው ተከብሮ ጉዳያቸው ከውጪ ሆነው እንዲከታተሉ ቢፈቅድላቸውም ፖሊስ እስረኞቹን አልለቅም በማለቱ የረሃብ አድማ ላይ እንደሚገኙ ጠበቃቸው አቶ ቱሊ ባይሳ ለቢቢሲ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) የረሃብ አድማው ተከሳሾችን የከፋ አደጋ ላይ እንዳይጥል የቅርብ ክትትል ማድረግ እንደሚያስፈልግ መግለጻቸውን ኮሚሽኑ ባሳለፍነው አርብ ባወጣው መግለጫ አስነብቧል። "ለታሳሪዎች ምክንያታዊ የሆኑ ጥያቄዎች ተገቢውን አፋጣኝ ምላሽ መስጠትና የእስረኞችን ጠያቂዎች በማረሚያ ቤቱም ሆነ በፍርድ ቤቶች በአግባቡ ማስተናገድ ይገባል" ስለማለታቸው በመግለጫው ሰፍሯል።
41855492
https://www.bbc.com/amharic/41855492
ትምህርት ዕድሜን እንደሚያስረዝም በጥናት ተረጋገጠ
ሰዎች በትምህርት ላይ የሚያሳልፉት እያንዳንዱ ዓመት በእድሜያቸው ላይ በአማካይ 11 ወራትን እንደሚጨምር ሳይንቲስቶች አረጋገጡ።
እድሜን ከሚያራዝሙ ነገሮች በተጨማሪ የሚያሳጥሩ በርካታ ምክንያቶች እንዳሉም አመልክተዋል። አጥኚዎቹ እንደሚሉት አንድ ሰው ከልክ በላይ በሚጨምረው በእያንዳንዱ ኪሎ ግራም ከእድሜው ላይ ሁለት ወርን ሲቀንስ በቀን አንድ ፓኮ ሲጋራ የሚያጨስ ሰው ደግሞ ከዕድሜው ላይ ሰባት ዓመታትን ያሳጥራል። የኤደንብራ ዩኒቨርሲቲ የጥናት ቡድን እዚህ ውጤት ላይ የደረሰው ባልተለመደ ሁኔታ የሰዎችን የዘረ-መላዊ መለያዎችንና የዘር ቅንጣቶችን ልዩነት በመተንተን ነው። ተመራማሪዎቹ እንደሚያስቡት ውጤቱ ሰዎች ረጅም ዕድሜን እንዲኖሩ የሚያስችል አዲስ መንገድን ለማወቅ ያስችላል ብለዋል። የአጥኚዎቹ ቡድን ግዙፍ በሆነው ተፈጥሯዊ የጥናት ሙከራ ላይ የተሳተፉ ከ600 ሺህ የሚበልጡ ሰዎችን ዘረ-መላዊ መለያዎችን ተጠቅመዋል። አንድ ሰው በተመሳሳይ የሚያጨስ፣ የሚጠጣ፣ ትምህርቱን ያቋረጠ ከሆነና ከልክ ያለፈ ክብደት ካለው፤ ጤናማ ያልሆነውን የአንዱን ነገር ተፅዕኖ ለይቶ ለማወቅ አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል። ከዚህ ይልቅ አጥኚዎቹ ተፈጥሯዊ ወደሆነው ሙከራ ፊታቸውን መልሰዋል። አንዳንድ ሰዎች በዘር ቅንጣታቸው ውስጥ ምግብን አብዝተው እንዲመገቡ የሚያደርግ ወይም ለውፍረት የሚያጋልጥ ተፈጥሮ ሊኖራቸው ይችላል። ስለዚህም አጥኚዎቹ አብዝተውና በልኩ የሚመገቡ ሰዎችን ተጨማሪ የሕይወት ዘይቤዎችን ሳያካትት ለማነፃፀር ችለዋል። ዶክትር ፒተር ጆሺ እንደሚሉት ''ክብደት መጨመር በቀጥታ በዕድሜ ላይ የሚያስከትለውን ውጤት በተመለከተ ለማወቅ ይቻላል። ይህም ትንተናውን አያፋልሰውም'' ብለዋል። ተመሳሳይ የተፈጥሮ ይዘቶችም ሰዎች በትምህርት ላይ የሚያሳልፉትን ዓመታትና በማጨስ ወይም በመጠጣት ከሚያገኙት እርካታ ጋር እንዲያያዙ ተደርገዋል። የጥናት ቡድኑ በተጨማሪም በዘር ቅንጣቶች ውስጥ ዕድሜ ላይ ተፅዕኖ ያላቸው የተለዩ ይዘቶችን ማግኘታቸውን ሳይንሳዊ ጥናት በሚቀርብበት መጽሔት ላይ አስፍረዋል። ዶክተር ጆሺ እንደሚሉት እነዚህ የዘረ-መል ይዘቶች ላይ የሚታዩ ልዩነቶች ''በጣም ትንሽ ጉዳዮች ናቸው'' ብለዋል። በእድሜ ላይ ለውጥን ከሚያስከትሉ ልዩነቶች ውስጥ 20 በመቶ የሚሆኑት በዘር የሚመጡ ሊሆኑ ይችላሉ። ነገር ግን አስካሁን ተለይተው የታወቁት 1 በመቶው ብቻ ናቸው። ዶክተሩ እንደሚሉት ዘረ-መል በምንኖረው እድሜ ላይ ተፅዕኖ ያለው ቢሆንም ''እያንዳንዳችን በአኗኗር ዘይቤያችን ላይ በምናደርገው ምርጫ መሰረት የበለጠ ተፅዕኖ የማድረግ አቅም አለን'' ብለዋል። ዶክተር ጆሺ ለቢቢሲ እንደገለፁት ''እድሜ ላይ ተፅዕኖ ያላቸውን ቀዳሚ የዘር ቅንጣቶችን በመለየት ስለእርጅናና መፍትሄው አዳዲስ መረጃዎችን እናገኛለን ብለን ተስፋ እንደርጋለን''ብለዋል። ረጅም ዕድሜ እንዳንኖር የሚያደርጉ የበሽታ አይነቶችም እንዳሉ ባለሙያዎቹ ጠቁመዋል።
news-52171488
https://www.bbc.com/amharic/news-52171488
ኮሮናቫይረስን፡ በአዲሱ የሞባይል ቴክኖሎጂ ላይ የተነዛው ሐሰተኛ ወሬ ጉዳትን አስከተለ
የሞባይል ስልክ አገልግሎትን ፈጣንና ዘመናዊ ያደርገዋል ተብሎ የታመነበት የአምስተኛው ትውልድ [5ጂ] ቴክኖሎጂ የኮሮናቫይረስን እያሰራጨ ነው በሚል በተናፈሰው ወሬ ምክንያት በንብረት ላይ ጉዳት እየደረሰ ነው።
በማኅበራዊ መገናኛ መድረኮች በስፋት ሲዘዋወሩ በነበሩ ቪዲዮዎች ላይ እንደታየው ብሪታኒያ ውስጥ በሚገኙት በርሚንግሐምና መርሲሳይድ ከተሞች ውስጥ የሞባይል ግንኙነት ማማዎች በእሳት ሲጋዩ ታይተዋል። ይህንን ተከትሎ የሴራ ንድፈ ሐሳብን በመመርኮዝ ዘመናዊው የአምስተኛው ትውልድ [5ጂ] ቴክኖሎጂ ለኮሮናቫይረስ መሰራጨት ምክንያት ሆኗል የሚለው ክስ በሳይንስ ባለሙያዎች ሐሰት ተብሎ ተወግዟል። አዲሱ ቴክኖሎጂ በሽታውን እያስተላላፈ ነው የሚሉ መላምቶችን የያዙ መልዕክቶች ዕውቅና ባገኙና በመቶ ሺህዎች ተከታይ ባሏቸው የፌስቡክ፣ የዩቲዩብና የኢንስታግራም አካውቶች በኩል ሳይቀር በስፋት ሲሰራጩ ነበር። ነገር ግን ሳይንቲስቶች ይህ በኮቪድ-19 እና በ5ጂ አገልግሎት መካከል አለ የተባለው ግንኙነት "ፍጹም የማይረባ" ከመሆኑ በተጨማሪ ከሥነ ፍጥረት እሳቤ አኳያም ሊሆን የማይችል ነው ሲሉ አጣጥለውታል። የሴራ ንድፈ ሐሳብን የሬዲዮ ሞገዶችን በመጠቀም ለሞባይል ስልክ አገልግሎት የሚውለውን የ5ጂ ቴክኖሎጂ በስፋት እየተሰራጨ ላለው የኮሮናቫይረስ ተጠያቂ በማድረግ ይህንን ሐሰተኛ መረጃ በስፋት እያሰራጩ ያሉት ሰዎች የሴራ ንድፈ ሐሳብን መሰረት አድርገው ነው። ይህ ወሬ መሰራጨት የጀመረው በጥር ወር መጨረሻ አካባቢ የመጀመሪያው የኮሮናቫይረስ ታማሚ አሜሪካ ውስጥ በተገኘበት ሰሞን ሲሆን፤ ክስተቱ ከ5ጂ ጋር ግንኙነት እንዳለው በፌስቡክ በኩል ነበር ሲወራ የነበረው። የሚሰራጨውም ወሬ ሁለት ገጽታ የነበረው ሲሆን አንደኛው 5ጂ የተፈጥሮ በሽታን የመከላከያ አቅምን በመቀነስ ሰዎችን ለኮሮናቫይረስ ተጋላጭ ያደርጋል የሚሉ ናቸው። ሌሎቹ ደግሞ ቫይረሱ በቀጥታ በ5ጂ ቴክኖሎጂ በኩል ይተላለፋል ሲሉ ያልተረጋገጡ መልዕክቶችን በስፋት አሰራጭተዋል። በሬዲንግ ዩኒቨርስቲ የሥነ ህይወት ተባባሪ ፕሮፌሰር የሆኑት ዶክትር ሳይመን ክላርክ ግን እነዚህን ሁለት ሐሳቦች "ሙሉ ለሙሉ የማይረቡ" ሲሉ አጣጥለዋቸዋል። "5ጂ የሰዎችን በሽታን የመከላከል አቅም ይቀንሳል የሚለው ሐሳብም ለንግግር የሚበቃ አይደለም" ይላሉ ዶክተር ክላርክ። "የተፈጥሮ በሽታን የመከላከል አቅማችን በተለያዩ ምክንያቶች ዝቅ ሊል ይችላል፤ አንድቀን ሲደክመን ሌላ ጊዜ ደግሞ ጥሩ ምግብ ሳናገኝ ስንቀር መዋዠቁ አይቀርም። ይህም ትልቅ ነው የሚባል ባይሆንም በቫይረሱ ለመያዝ ተጋላጭ ሊያደርግን ይችላል። "በእርግጥ የራዲዮ ሞገዶች ጠንካራ በሚሆኑበት ጊዜ የሰውነታችን በሽታን የመከላከል ሥርዓት በአግባቡ ሥራውን ሊያከናውን አይችልም። ነገር ግን የ5ጂ የራዲዮ ሞገድ በጣም ዝቅተኛ ስለሆነ በሽታን የመከላከል ሥርዓታችንን ሊያስተጓጉል የሚችልበት አቅም የለውም። በዚህም ዙሪያ በርካታ ጥናቶች ተሰርተዋል።" የቫይረሱ ተፈጥሮና ባህሪይ በብሪስቶል ዩኒቨርስቲ የህጻናት ህክምና ፕሪፌሰር የሆኑት አዳም ፊን እንደሚሉት ደግሞ የ5ጂ ቴክኖሎጂ ቫይረሱን ያስተላልፋል የሚባለው ነገር ፈጽሞ የማይሆን ነገር እንደሆነ ተናግረዋል። "ኮሮናቫይረስ ከአንድ ሰው ወደ ሌላ ሰው የሚተላለፍ መሆኑ ይታወቃል። ቫይረስና ለሞባይል እንዲሁም ለኢንትርኔት ግንኙነት የሚያገለግለው ኤሌክትሮማግኔቲክ ሞገድ በአሰራራቸው የተለያዩ ነገሮች ናቸው" ብለዋል። ከ5ጂ ቴክኖሎጂ ጋር በተያያዘ የሚወራው ነገር ትክክል እንዳልሆነ እንደማሳያነት ከተጠቀሱት ምሳሌዎች መካከል፤ በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ የኮሮናቫይረስ በስፋት የተሰራጨባቸው ከተሞች ገና የ5ጂ አገልግሎትን ያላገኙ ናቸው። በተጨማሪም በበሽታው ክፉኛ ከተጠቁት አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢራን ቴክኖሎጂውን ሥራ ላይ ለማዋል ገና ጥረት እያደረገች ነው። የ5ጂ ቴክኖሎጂን በተመለከተ የኮሮናቫይረስ ከመምጣቱ ቀደም ብሎ አንስቶ እጅግ አስፈሪ የሆኑ ነገሮች ሲወሩ ቆይተዋል። ከወራት በፊት ይፋ የተደረገ አንድ ጥናት ከሞባይል ስልክ አማካይነት የሚከሰት የጤና ችግርን በተመለከተ ምንም አይነት ማስረጃ እንዳልተገኘ አመልክቷል። የተለያዩ ተቋማትም በ5ጂ ቴክኖሎጂና በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መካከል ግንኙነት አለ እየተባለ የሚናፈሰው ወሬ "እንደሚያሳስባቸው" ገልጸው፤ እስካሁንም በሁለቱ መካከል ምንም አይነት የሚያሳምን ማስጃ እንዳልተገኘ ተገልጿል። ቫይረሶች በተፈጥሯቸው የሰውን ወይም የእንስሳትን ህዋሳትን በመውረር ለመራባት ይጠቀሙባቸዋል፤ በዚህም ሳቢያ በሽታ ይከሰታል። ቫይረሶች ከሰውነት ውጪ ለረጅም ጊዜ ሊቆዩ አይችሉም ለዚህም ነው በአብዛኛው በሳልና በማሽነጠስ ጊዜ በሚወጡ ፈሳሽ በሆኑና በጥቃቅን ብናኝ መልክ ወደ ሰውነት ለመግባት መንገድ የሚፈልጉት። የዚህ የኮሮናቫይረስ ተፈጥሯዊ አወቃቀር እንደሚያመለክተው ቫይረሱ ከእንስሳት ወጥቶ ወደ ሰው የተሸጋገረ ሲሆን፤ ከዚያም ከሰው ወደ ሰው በመተላለፍ አሁን ካለበት ደረጃ ላይ ደርሷል።
48237006
https://www.bbc.com/amharic/48237006
"ሥልጣን በአማራና በኦሮሞ መካከል የሚደረግ ቅርጫ መሆን የለበትም" ወ/ሮ አዳነች አቤቤ
ሰሞኑን የገቢዎች ሚኒስትር ለአንድ ብሔር ያደላ ሹመት ይሰጣል በሚል በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ቅሬታ ሲነሳበት ነበር።
የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የገቢዎች ሚኒስትሯ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ፤ የተነሳውን ቅሬታ በሚመለከት ሲመልሱ፤ "ሠራተኞች በብሔር ላይ ቅሬታ አላነሱም" ይላሉ። አንድ ሠራተኛ በችሎታው ተመዝኖ ለቦታው ብቁ ሲሆን ብቻ እንደሚመደብም ተናግረዋል። "አመራሩን በተመለከተ አብዛኛው የጉሙሩክ ቅርንጫፎች ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ነው ያሉት" የሚሉት ወ/ሮ አዳነች፤ ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ሞጆ፣ አዳማ፣ ጅማና ሞያሌ የፌደራል ጉሙሩክ ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤቶች መኖራቸውን በማስታወስ፤ በነዚህ ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤቶች የክልሉን ቋንቋና ባህል የሚያውቅ አመራር መመደቡን አረጋግጠዋል። • "ከመቶ ምናምን ፓርቲ ሴት የምናገኘው አንድ ወይም ቢበዛ ሁለት ሊሆን ይችላል" ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ አክለውም በፖለቲካ ወይም በሌሎች መስፈርቶች ይሰጡ የነበሩ የኃላፊነት ቦታዎች እንደቀሩ አሳውቀው፤ ብቃት ዋነኛው መስፈርት መሆኑን አረጋግጠዋል። ሃገሪቷ ፌዴራላዊ አሠራር ስለምትከተል በክልል ያለንም አሠራር ልክ እንደዚያው ሕብረ ብሔራዊ አሠራርን የማንፀባረቅ ዓላማ እንዳላቸውም አብራርተዋል። "ሥልጣን በአማራና በኦሮሞ መካከል የሚደረግ ቅርጫ መሆን የለበትም። የማንኛውም ብሔር ተወላጅ ለማንኛውም ሥራ ተወዳድሮ ብቃት ካለው ማግኘት ይችላል።" በኦሮሚያ ክልል ብቻ ሳይሆን በሌሎች ክልሎችም በተመሳሳይ መልኩ እንደሚሠራም ለቢቢሲ ተናግረዋል። እንደ ምሳሌም ኮምቦልቻ፣ ባሕር ዳር እና መቀሌን ጠቅሰው "በሁሉም ቅርንጫፎች ያሉት ኃላፊዎች ከባህሉም ከወጉም እንዲተዋወቁ አድርገናል" ብለውናል። ቅሬታ አቅራቢዎች እንደ ምሳሌ የጠቀሷቸው ውስንና የተመረጡ ቅርንጫፎች በመሆናቸውም የመሥሪያ ቤቱን አሠራር እውነታ አያንፀባርቅም በማለት ሥራው በሂደት ላይ ቢሆንም የቅርንጫፎቹን አመራር ዝርዝር በፌስቡክ ገፃቸው ማግኘት እንደሚቻል ጠቁመዋል። "በኦሮምያ ክልል ያሉት ቅርንጫፎች ውስጥ የሚሠሩት ሦስት ምክትል ኃላፊዎችም እንኳ ከሌላ ብሔር የተውጣጡ እንዲሆኑ ተደርጎ ነው መዋቀሩ የተሠራው" በማለት ሃሳባቸውን አብራርተዋል። ሚኒስትሯ "በኦሮሚያ ክልል ውስጥ በሚገኙ በእነዚህ ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤቶች አብዛኞቹ ምክትል ኃላፊዎች የሌላ ብሔር ተወላጆች ናቸው። ስለዚህ በሚኒስትር መሥሪያ ቤቱ ስልጣን ላይ ኦሮሞ በዝቷል የሚለው ሐሰት ነው" በማለት ቅሬታውን ያጣጥላሉ። "አመራር ስንመድብ የመጀመሪያው መስፈርታችን ብቃትና ችሎታ ነው" የሚሉት ወ/ሮ አዳነች፤ ሀገሪቷ በፌደራሊዝም ስርዓት የምትደዳር እንደመሆኗ የተመጣጠነ የብሔር ተዋፅኦ እንዲኖር እናደርጋለን ብለዋል። • በስህተት የተሰጣቸውን 1 ሚሊየን ብር የመለሱት መምህር የገቢዎች ሚኒስትር ባለፉት ዘጠኝ ወራት የሰበሰበው ገቢ ካለፉት ዓመታት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የተሻለ እንደሆነ ያስታወቁት ሚኒስትሯ፤ "ዘንድሮ የሰበሰብነው 145 ቢሊየን ብር ሲሆን፤ ካለፈው ዓመት በ13 ቢሊየን ብር ይበልጣል" ብለዋል። ይህንንም በመቶኛ ሲያስቀምጡት የዘጠኝ ነጥብ አምስት እድገት ማሳየቱን ይናገራሉ። አክለውም እንሠራለን ብለው ካቀዱት ጋር በማነጻጸር "አሁንም ጉድለቶች አሉ" ይላሉ ሚኒስትሯ። "የሀገሪቱን ገቢ የማመንጨት አቅም ስናየው የሚያኮራ ሥራ ሠርተናል ብለን አናስብም። ነገር ግን የተሠራው ሥራ በቀላሉ ያሳካነው አይደለም። በመሥሪያ ቤቱ ትልልቅ የመዋቅር ማስተካከያዎችና ሪፎርሞች አድርገናል። ግብር ከፋዩ ዜጋ በፈቃደኝነት ተነሳስቶ መጥቶ እንዲከፍል ሁኔታዎችን አመቻችተናል። የሰው ኃይልን በማብቃት፤ አገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን እንዲሁም የግብር ከፋዮችን ለማነቃቃት የተለያዩ ሕዝባዊ መድረኮች ስናካሂድ ነበር። ያገኘነው ስኬት የነዚህ ድምር ውጤት ነው።" • "በራሷ ገቢ የምትተማመንና መቆም የምትችል ሀገር ማየት እሻለሁ"ወ/ሮ አዳነች አቤቤ መሥሪያ ቤቱ ውስጥ የነበረው ብልሹ አሠራር የንግዱ ማህበረሰብ በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ ተስፋ እንዲቆርጥና ግብር በአግባቡ እንዳይከፍል አድርጎት ነበር የሚሉት ሚኒስትሯ፤ በተሠሩት የለውጥ ሥራዎች ይህንን ማስተካከል መቻላቸውን ይገልፃሉ። "በዚህ አመት ለመሰብሰብ ያቀድነው 170 ቢሊየን ብር ነበር" ያሉት ወ/ሮ አዳነች፤ ሀገሪቱ ወደ ውጪ ከምትልካቸውና ወደ ሀገር ውስጥ ከምታስገባቸው እቃዎች ታክስና ቀረጥ በሚፈለገው መጠን መሰብሰብ አለመቻሉን ገልጸዋል። የውጪ ምንዛሬ እጥረትም ግባቸውን እንዳያሳኩ ካደረጉ ምክንያቶች መካከል እንደሚጠቀስ ተናገረዋል። • ዘረኝነት ለእናቶች ሞት ምክንያት እየሆነ ነው? "ከሀገር ውስጥ የምንሰበሰበውን ገቢ ከ80 በመቶ በላይ አሳክተነዋል፤ ትልቁ ፈተና ከውጪ ከሚገቡ እቃዎች የምንሰበስበው ገቢ ነው።" በማለት የኮንትሮባንድ እቃዎች ግብይት እንዲሁም ሕገ ወጥ የውጪ ሀገራት ገንዘብ ዝውውር በሀገሪቱ ውስጥ ሕገ ወጥ ንግድ እየተስፋፋ እንደሆነ ያመላክታል ሲሉ ያስረዳሉ። በየክልሎቹ የሚገኙ የኮንትሮባንድ እቃዎች ክትትል የሚደረግባቸው የፍተሻ ጣቢያዎችን መዋቅር በማጠናከር ችግሩን ለመቅረፍ ሙከራ እንደሚያደርጉም ተናገረዋል።
news-53578164
https://www.bbc.com/amharic/news-53578164
በሕንድ ሙምባይ የድሃ ሰፈሮች የሚኖሩ ከግማሽ በላይ ነዋሪዎች በኮቪድ-19 ተይዘዋል
በሕንድ ሙምባይ በድሆች መንደር ውስጥ በሚገኙ ሦስት አካባቢዎች በሚኖሩ ሰዎች ላይ በተደረገ ምርመራ በርካቶች በኮቪድ-19 መያዛቸውን መረጋገጡ ተገለፀ።
በዚሁ አካባቢ በድህነት ከተጎሳቆሉ መንደሮች ውጪ በሚኖሩ ሰዎች መካከል ደግሞ ለቫይረሱ የተጋለጡት 16 በመቶዎቹ ብቻ ናቸው ተብሏል። ይህ ውጤት የተገኘው ከተወሰደው የ7000 ሰዎች ናሙና መሆኑ ሲገለጽ ቦታዎቹም በጣም ጥግግት ከሚበዛባቸው ሦስት የተለያዩ አካባቢዎች ነው ተብሏል። በሙምባይ እስከ ትናንት ማክሰኞ ድረስ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 110 ሺህ ሰዎች ሲሆኑ ከእነዚህም መካከል 6187 ሰዎች ሞተዋል። የዳሰሳ ጥናቱ የተሰራው በከተማ አስተዳደሩ እንዲሁም በመንግሥት አማካሪዎች ቡድንና በታታ መሰረታዊ ምርምር ተቋም በኩል ነው። ጥናቱ ይፋ እንዳደረገው ናሙናቸው ከተወሰዱባቸው ሰዎች መካከል 57 በመቶ ያህሉ ለኮቪድ-19 የተጋለጡ ናቸው። በከተማዋ ምዕራብ፣ ምሥራቅና ማዕከላዊ አካባቢ የሚኖሩ 1.5 ሚሊዮን ሰዎች ይኖራሉ ተብሎ ይገመታል። በጥናቱ ላይ የተሳተፉ ተመራማሪዎች ለቢቢሲ እንደተናገሩት በቫይረሱ ክፉኛ የተጎዳችው በዚህች ከተማ ላይ የተሰራው ጥናት ስለቫይረሱ ስርጭት የሚናገረው ነገር አለ ሲሉ ገልፀዋል። መጀመሪያ ቫይረሱ ቀድሞ ከታሰበው በላይ በከተማዋ 12.5 ሚሊየን ሰዎች በሚኖሩበት የምንዱባኖች መንደር ውስጥ በሰፊው መሰራጨቱን ነው። ከፍተኛ ሆነው ስርጭት የሚያሳየው በእነዚህ አካባቢዎች የሚኖሩ ሕንዳውያን በጋራ በሚጠቀሟቸው መጸዳጃ ቤቶችን የመሳሰሉ በመኖራቸው ነው ተብሏል። "ውጤቱ የሚያሳየው ከፍተኛ ጥግግት ያለበት ኑሮ እንዴት ለቫይረሱ እንደሚያጋልጥ ነው" ያሉት በታታ የምርምር ተቋም ውስጥ የሚሰሩት ሳንዲፕ ጁኔጃ ናቸው። ጥናቱ ሌላው ያሳየው ነገር በርካታ ቁጥር ያላቸው ሰዎች በቫይረሱ ተይዘው ምንም ምልክት ሳያሳዩ መዳናቸውን ነው። ይህም በአካባቢው የተከሰተውን የሞት ቁጥር አነስተኛ ያደረገው ሲሆን ይህ ደግሞ በከተማ ደረጃ በኮቪድ-19 ምክንያት የሚሞቱ ሰዎች ቁጥርን ዝቅተኛ አድርጎት ቆይቷል ተብሏል። በዚህ ጥናት ሌላው የተረጋገጠው ነገር በድሆች መንደር የሚኖሩም ሆነ ከዚያ ውጪ መኖሪያቸው የሆነ በርካታ ሴቶች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው መገኘታቸውን ነው። ተመራማሪ ዶ/ር ኡላስ ኤስ ኮልቱር ለቢቢሲ እንደገለፁት "ምክንያቱን አላወቅነውም። ከማኅበራዊ ጠባይ እስከ አካላዊ ልዩነት ድረስ ሊሆን ይችላል" ብለው ለቢቢሲ አስረድተዋል። በሙምባይ ያለው አዳዲስ በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየቀነሰ መምጣት ሌላ ጥያቄ አጭሯል። ምናልባት በከተማዋ ስርጭቱ ተስፋፍቶ ሰዎች የመከላከል አቅማቸውን አዳብረው ይሆን? ወይስ የወል ተፈጥሯዊ መከላከያ [ኽርድ ኢሚዩኒቲ ]ተገንብቶ ለሚለው ከጥርጣሬ ውጪ ምላሽ አልተገኘም። ሙምባይ ማክሰኞ እለት ብቻ 717 አዲስ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን የመዘገበች ሲሆን ከባለፉት ሦስት ወራት ወዲህ ትንሹ ነው ተብሏል። የተመራማሪዎቹ ቡድን ጥርት ያለ መልስ ላይ ያልደረሰ ሲሆን ድጋሚ የዳሰሳ ጥናቱ እስካልተደረገ ድረስ ማኅበረሰቡ ውስጥ የወል ተፈጥሯዊ መከላከያ ዳብሯል የሚለውን መናገር እንደማይቻል ዶ/ር ኮልቱር ገልፀዋል። የዳሰሳ ጥናቱ ከሦስት ወር በኋላ የሚደገም መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዚህም ወቅት ስርጭቱ መስፋፋቱ አልያም መቀነሱ የሚታይ ይሆናል። ይህም በከተማዋ የቫይረሱ ስርጭት ያለበት ሁኔታን ማወቅ ያስችላል ተብሏል። "የመረጥናቸው ሦስት አካባቢዎች ላይ የተገኘው የኮሮናቫይረስ መጠን ይለያያል፤ አንዳንድ አካባቢዎች በድህነት ተጠጋግተው የሚኖሩ ሲሆኑ የተወሰኑ አካባቢዎች ደግሞ ለብቻቸው የሚኖሩ አካባቢዎች ነው፤ ሃሳቡ በአንድ አካባቢ መኖር ለስርጭቱ መስፋፋት አስተዋጽኦ አድርጓል? የሚለውን ለማየት ነው" ያሉት ደግሞ ዶ/ር ኮልቱር ናቸው። ተመራማሪዎች የዳሰሳ ጥናቱ የመላ ከተማዋን ሁኔታ እንደማያሳይም ተናግረዋል። "ነገር ግን የስርጭቱ መጠን ከዚህ እጅግ በጣም የራቀ ነው ብለን አናምንም" ያሉት ደግሞ ዶ/ር ጁንጃ ናቸው። በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ መንግሥት በደልሂ ከአራት ነዋሪዎች መካከል አንዱ ለኮሮናቫይረስ የተጋለጠ መሆኑን ገልጿል።
48376790
https://www.bbc.com/amharic/48376790
ቦትስዋና ዝሆን ማደን ፈቀደች
ቦትስዋና ዝሆንን ለማደን የሚከለከለውን እገዳ ማንሳቷን አስታውቃለች። ምክንያት ብላ ያቀረበችውም በሰዎችና በእንስሳቱ መካከል በተደጋጋሚ የተፈጠረውን ግጭት እና ዝሆኖቹ ሰብል ወደ ማውደም መሸጋገራቸውን ነው።
ዝሆኖችን ማደን የሚከለክለው ህግ የወጣው እ.ኤ.አ በ2014 ሲሆን ክልከላው ገበሬዎችንና ከዚህ በፊት በማደን ገቢ ያገኙ የነበሩ ግለሰቦችን እየጎዳ ነው ብለዋል። በዓለም ላይ ከፍተኛ ቁጥር ዝሆኖች የሚገኙት ቦትስዋና ሲሆን 130 ሺህ ያህል ዝሆኖች እንዳሏት ይገመታል። • ኬንያዊው ፀሀፊ ቢንያንቫንጋ ዋይናይና ሲታወስ • በጉጂ አስር ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ • "የከተማ መስፋፋት የኢትዮጵያን ብዝሀ ሕይወት አደጋ ላይ ጥሏል" ዶ/ር መለሰ ማርዮ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ሞክግዌትሲ ማሲሲ ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር ላይ ነበር በቀድሞው ፕሬዝዳንት የተጣለውን እገዳ ለመመርመር ኮሚቴ ያዋቀሩት። በዚህ ዓመት የካቲት ወር ላይም ኮሚቴው እገዳው እንዲነሳ የሚል ምክረ ሀሳብ ማቅረቡ ተሰምቶ ነበር። "የዝሆኖቹ ቁጥር መጨመር፣ በዝሆኖቹና በሰው ልጆች መካከል የሚፈጠር ግጭት መበራከት፣ ዝሆኖቹ በሰውና በእንስሳት ላይ የሚያደርሱት ጥቃት መጨመር" ወደ እዚህ ውሳኔ እንደገፋቸው በመግለጫቸው ላይ የገለፁት የአካባቢ፣ የተፈጥሮ ኃብት እንክብካቤ እንዲሁም የቱሪዝም ሚኒስትሩ ናቸው። አክለውም "አደን ሲፈቀድ ሕግን በተከተለ እና ስርዓት ባለው መልኩ እንዲሆን እናደርጋለን" ብለዋል። የክልከላው መነሳት እርምጃው ፖለቲካዊ ነው ብለው በማያምኑ የአካባቢ ጥበቃ ተሟጋቾች ዘንድ ብስጭትን ይፈጥራል። ሀገሪቱም በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን የአካባቢ ጥበቃ ስም የሚያጠለሽ ሲሆን ለሀገሪቱ ከዳይመንድ ማዕድን ማውጣት ቀጥሎ ሁለተኛ የገቢ ምንጭ የሆነው የቱሪዝም ሀብቷንም ይጎዳል ተብሏል።
news-53126753
https://www.bbc.com/amharic/news-53126753
ቀለበታዊው የፀሐይ ግርዶሽ በላልይበላ
ቀለበታዊ የፀሐይ ግርዶሽ በዛሬው ዕለት ዕሁድ ሰኔ 14/ 2012 ዓ.ም ጥዋት በኢትዮጵያ ታይቷል።
በብዙዎች ዘንድ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ቀለበታዊ የፀሐይ ግርዶሽ ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የምሥራቅና መካከለኛው አፍሪካ ይታያል። በተለይም በላልይበላ አካባቢዎች ጨለምለም ብሎ የነበረ ሲሆን ቀለበታዊ የፀሐይ ግርዶሹም መታየቱን ቢቢሲ አረጋግጧል። በአብዛኛው የኢትዮጵያ ክፍል ፀሐይ ከ80 በመቶ ተሸፍና በከፊል ግርዶሽነት የታየች ሲሆን በተወሰነው የደቡብ ኢትዮጵያ ክፍል ደግሞ ፀሐይ ከ60- 80 በመቶ ተሸፍና ግርዶሹ ታይቷል። ዋናው ግርዶሽ ግን ከምዕራብ ኢትዮጵያ አንስቶ እስከ ሰሜን ምስራቅ ድረስ የሚዘልቀው ነው። ክስተቱም ወለጋ ጀምሮ፣ በከፊል ጎጃምንና ጎንደርን አቆራርጦ ነው ወደ ወሎ በመሻገር ላሊበላንም ያዳረሰ እንደሆነም የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አስታውቋል። በእነዚህ ቦታዎች ፀሐይ እስከ 98 በመቶ ተሸፍና ቀለበታዊውን ግርዶሽም ማየት ተችሏል። ይህንን ቀለበታዊ ግርዶሽ ማየት ከቻሉ አካባቢዎች መካከልም ላሊበላን ጨምሮ ቆቦ፣ ኮረም፣ አላማጣ፣ በጊ፣ ሜቲ፣ እንጅባራ፣ ቡሬ፣ አገው ግምጃ ቤት፣ጋይንት፣ ንፋስ መውጫ፣ ግሽ አባይ የተወሰኑት ናቸው። ግርዶሹ ከጥዋቱ 12፡45 ጀምሮ እስከ ስድስት ሰዓት ተኩል የቆየ ነበር ተብሏል። ቀለበታዊው የፀሐይ ግርዶሽ በላልይበላ ቀለበታዊ ግርዶሽ የሚከሰተው ጨረቃ በፀሐይና በምድር መካከል ስትሆን እንዲሁም ፀሐይ ሙሉ በሙሉ ተጋርዳ ብርሃን መስጠት ሳትችል ነው። ጨረቃ በፀሐይና መሬት መካከል ስትሆን የሚፈጠረውንም ክስተት ለማየት ብዙዎችም ወደ ላልይበላ ተጉዘዋል። እንዲህ አይነት ታሪካዊ ክስተት በድጋሚ የሚያጋጥመው ከ18 ዓመታት በኋላ ሲሆን ሙሉ የፀሐይ ግርዶሽ የሚኖረው ከ146 ዓመታት በኋላ እንደሆነ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ከለሰሞኑ አስታውቋል። ቀለበታዊ የፀሐይ ግርዶሽ ከኮንጎ ተነስቶ፣ ማዕከላ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ኢትዮጵያንና ኤርትራን አዳርሶ ወደ መካከለኛው ምሥራቅም ይሻገራል።
news-55003274
https://www.bbc.com/amharic/news-55003274
ኮሮናቫይረስ ፡ ስንት ተስፋ ሰጪ የኮቪድ-19 ክትባቶች ተገኝተዋል?
የተለያዩ ተቋሞች የኮቪድ-19 ክትባትን ለማግኘት መቃረባቸውን እያስታወቁ ነው። ይህም ለመላው ዓለም ተስፋ የሰጠ ዜና ሆኗል።
ከሳምንት በፊት ፋይዘር እና ባዮቴክ የተባሉ ተቋሞች ውጤታማነቱ አስተማማኝ የሆነ ክትባት ማግኘታቸውን ማሳወቃቸው ይታወሳል። አሁን ደግሞ ሞዴርና የተባለ ድርጅት ውጤታማ የኮቪድ-19 ክትባት ሙከራ ማድረጉን ይፋ አድርጓል። በኦክስፎርድ የሚካሄደው የክትባት ምርምር በ60ዎቹ እና 70ዎቹ እድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ሰዎች ላይ በሽታ የመከላከል አቅምን ከማዳበር አንጻር ውጤታማ መሆኑ ተገልጿል። ሌለው በክትባት ምርምር ውጤታማ እየሆነ የሚገኘው የቤልጄሙ ጃንሰን ሲሆን፤ ዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ ሦስተኛ ደረጃ ሙከራ ላይ ይገኛል። ክትባት ሰውነት በሽታ የመከላከል አቅም እንዲያዳብር በማገዝ፤ ሕይወት ወደቀደመው ገጽታ እንዲመለስ ይረዳል። ሰዎች በወረርሽኙ እንዳይያዙም ያግዛል። ወይም ደግሞ የበሽታውን አደገኛንት ይቀንሳል። ክትባቶቹ ምን ልዩነት አላቸው? ክትባት የሚሠራው ሰውነት በሽታውን የሚከላከልበትን አቅም ለማዳበር ሲሆን፤ ሰውነት ቫይረሱ እንግዳና አደገኛ እንደሆነ ተገንዝቦ እንዲዋጋ ያግዛል። ፋይዘር እና ባዮቴክ እንዲሁም ሞዴርና ያገኙት አርኤንኤ የተባለ ክትባት ነው። ይህም የቫይረሱን የዘረ መል ቅንጣቶች ሰውነት ውስጥ በመክተት፤ ሰውነት በሽታውን ለይቶ የመከላከል አቅም እንዲያዳብር የሚደረግበት መንገድ ነው። በጃንሰን የሚሠራው ክትባት ደግሞ ዘረ መሉ የተሻሻለ የጉንፋን ቫይረስን በመጠቀም፣ ኮሮናቫይረስን እንዲመስል አድርጎ ጎጂነቱን ለመቀነስ ይሞክራል። በዚህ መንገድ ሰውነት በሽታን የመከላከል አቅም አዳብሮ ወረርሽኙን እንዲከላከል ይደረጋል። በኦክስፎር እና በሩስያ የሚሠሩት ክትባቶች ጉዳት አልባ ቫይረስን ዝንጀሮ ላይ ይሞክራሉ። ከዚያም ዘረ መሉን አሻሽሎ ከኮሮናቫይረስ ጋር እንዲመሳሰል በማድረግ ውጤት ለማግኘት ይሞከራል። በቻይና የተሠሩት ሁለት ክትባቶች የተጠቀሙት ራሱን ቫይረሱን ነው። ቫይረሱ ጉዳት እንዳያስከትል ካከሰሙት በኋላ ነው ምርምሩ የተሠራው። ሰዎችን ለቫይረሱ በማጋለጥ የሚሠሩ ምርምሮች የትኛው ክትባት የተሻለ ውጤታማ እንደሆነ ለመረዳት ያግዛሉ። ክትባት መቼ እናገኛለን? ፋይዘር በዚህ ዓመት መጨረሻ 50 ሚሊዮን ጠብታዎችን በመላው ዓለም እንደሚያከፋፍል ተናግሯል። በሚቀጥለው ዓመት ደግሞ 1.3 ቢሊዮን ጠብታዎች ይገኛሉ። ለምሳሌ ዩናይትድ ኪንደም በዓመቱ መጨረሻ 10 ሚሊዮን የክትባት ጠብታ እንደምታገኝ ይጠበቃል። ተጨማሪ 30 ሚሊዮን ክትባቶች ማዘዟንም አስታውቃለች። ሌለው ጥያቄ ክትባቱን በቅድሚያ ማን ያገኛል? የሚለው ነው። ይህ የሚወሰነው ወረርሽኙ በከፍተኛ ሁኔታ በሚሰራጭባቸው እና የበለጠ ውጤታማ በሆነባቸው አካባቢዎች ነው። ዩናይትድ ኪንግደም በቅድሚያ ክትባቱን የምትሰጠው በከፍተኛ ሁኔታ ተጋላጭ ለሆኑት በእድሜ የገፉ ሰዎችና እንክብካቤ ሰጪዎቻቸው ነው። ክትባቱ ውጤታማ መሆኑ የሚታወቀው ሁሉም የሙከራ ደረጃዎች ታልፈው ክትባቱ በሽታን እንደሚከላከል ወይም በበሽታው ሳቢያ የሚሞቱ ሰዎችን ቁጥር እንደሚቀንስ ሲታወቅ ነው። ክትባቶች ፍቃድ አግኝተው፤ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ጠብታዎች መመረትም አለባቸው። ቫይረሱን ከምድር ላይ ለማስወገድ ከ60 እስከ 70 የሚሆነው የዓለም ሕዝብ በሽታውን የመካከል አቅም ማዳበር አለበት።
54280349
https://www.bbc.com/amharic/54280349
ሰብዓዊ መብት፡ ታዋቂው ሱዳናዊ የፊልም ባለሙያ በእስር ቤት እንደተገረፈ ተናገረ
ታዋቂው ሱዳናዊ የፊልም ባለሙያና የአለም አቀፉ የኦስካር ሽልማት ዳኛው ሃጆጅ ኩካ በእስር ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ ከሰሞኑም እንደተገረፈ ተናግሯል።
የአካባቢውን ደህንነት አደጋ ጥላችኋል እንዲሁም ረብሻችኋል በሚል ወንጀል ነው እሱን ጨምሮ ስድስት አርቲስቶች ባለፈው ሳምንት በካርቱም የሚገኘው ፍርድ ቤት የሁለት ወር እስር የፈረደባቸው። ከዚህም በተጨማሪ 90 ዶላርም እንዲከፍሉ ቅጣት ተጥሎባቸዋል። ጠበቃቸው ግን ክሱ ትርጉም አይሰጥም በሚል ተከራክሯል። ከእስር ቤት ሆኖ ከቢቢሲ ፎከስ ኦን ሬድዮ ጋር ቃለ መጠይቅ ያደረገው የፊልም ባለሙያው፣ ሃጆጅ በመጀመሪያ እስር ቤት እንደገባ ይዞታው መጥፎ እንደነበርና ሁለት ጊዜም እንደተገረፈ አስረድቷል። የእስር ቤቱ ሁኔታ በጣም መጥፎ ከመሆኑ አንፃር የአልጋ እጥረትም ነበር ብሏል። ነገር ግን በአለም አቀፍ ሁኔታ አርቲስቶቹ እንዲለቀቁ የሚል ጥሪና የትብብር ዘመቻ መከፈቱን ተከትሎ የእስር ሁኔታቸው እንደተሻሻለና ስልክም ማግኘት እንደቻለ አስረድቷል። ሆኖም መታሰራቸውን "በጣም ተስፋ አስቆራጭና አሳዛኝ" ያለው ሲሆን በህዝብ አብዮት ከስልጣን የተገረሰሱት የፕሬዚዳንት ኦማር አልበሽር ስርአትም በተወሰነ መልኩ እንዳለ ማሳያ ነው ብሏል። ለእስር የበቁት ነሐሴ ወር ላይ ሲሆን የአንድ ቲያትር ልምምድ ሲጨርሱ ጥቃት መድረሱን ተከትሎ ነው። ፖሊስ በአካባቢው ደርሶ በቁጥጥር ስር ባዋላቸውም ወቅት እየዘፈኑና እየዘመሩ አካባቢውን ረብሸውታል የሚልም ክስ ቀርቦባቸዋል። ጥቃት የፈፀሙት ግለሰቦች ግን በቁጥጥር ስር አልዋሉም። የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በበኩላቸው የሱዳን የፍትህ ስርአትም ሆነ ፖሊስ አሁንም ቢሆን ከቀድሞው ስርአት ነፃ አለመሆኑን እየተናገሩ ነው። የመናገርና የማሰብ ነፃነትን የሚከለክሉ ጨቋኝ የሚባሉ ህጎችም አሁንም ተግባራዊ እየሆኑ እንዳሉም እስሩ ማሳያም ነው ተብሎም እየተተቸ ነው።
news-56277302
https://www.bbc.com/amharic/news-56277302
ሙዚቃ፡ ድንገት ብቅ ያለችው ትውልደ ኢትዮጵያዊት የቤልጂየም ሙዚቃ ኮከብ
ለመጀመሪያ ጊዜ ሙዚቃዋን ለሰማ የማይረሳ ትዝታን ታሳርፋለች ይላሉ ሙዚቃዋን የሰሙ። መድረክ ላይ ባላት የመዝፈን ችሎታም ሆነ ለስለስ ብሎ በሚስረቀረቀው ድምጿ የብዙዎችን ቀልብም መሳብ ችላለች።
መስከረም ሜስ የሙዚቃ ተችዎችም በሙዚቃ ኢንዱስትሪው ውስጥ ብሩህ ተስፋ ሊኖራት እንደሚችሉም ከወዲሁ እየተናገሩ ነው። መስከረም ሜስ ትባላለች። በጥቅምት ወር ይህች ዝናን እያተረፈች ሙዚቀኛ በሮክ ባንዶች መካከል የሚደረገውን የሁሞ ሮክ ራሊ ውድድር ማሸነፍ ችላለች። ውድድሩ ከአውሮፓውያኑ 1978 ጀምሮ በቤልጂየሙ መፅሔት ሁሞ የሚካሄድ ነው። የመድረክ አያያዟ፣ ጊታር አጨዋወቷና ድምጿ ብዙዎችን ያስደመመ ሲሆን፤ በሙዚቃው ኢንዱስትሪ አዲስ ኮከብ ልትወጣ መሆኑ ማሳያ ነው ተብሏል። ዓመታዊው ሮክ ራሊ የዘንድሮው ዝግጅት በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ጥቂቶች የታደሙበት ሆኗል። መስከረም በጓደኞቿና በቤተሰቦቿ ታጅባ ይህንን ውድድር ማሸነፏ ዝናን እንድትጎናጸፍ ከማድረጉ በላይ ህይወቷንም ቀይሮታል። መስከረም ሜስ ማን ናት? ትውልዷ ኢትዮጵያ ሲሆን ገና የአስር ወር ጨቅላ እያለች የቤልጂየም ዜግነት ባላቸው ቤተሰቦቿ በማደጎ ወደ መሄዷን ከቢቢሲ ጋር ባደረገችው ቆይታ ተናግራለች። ያደገችውም በወደብ ከተማዋ ጌንት አቅራቢያ በምትገኝ ሜሬንድሬ በምትባል ትንሽ ከተማ ነው። ገና በጨቅላነቷ ከኢትዮጵያ በመውጣቷ የአፏን የፈታችው በደች ቋንቋ ነው፤ ስለ ኢትዮጵያም የምታስታውሰው ምንም ነገር የለም። "ከህፃናት ማሳደጊያ ቤት ነበር ወደ ቤልጂየም በማደጎ የመጣሁት" የምትለው መስከረም የወላጇቿንና ቤተሰቦቿን ማንነትም አታውቅም። በጉዲፈቻ ያሳደጓት ቤተሰቦቿ የነገሯት ነገር ቢኖር አዲስ አበባ ከሚገኝ የማሳደጊያ ቤት መወሰዷን ነው። ህይወት በማደጎ በወሰዷት ቤተሰቦቿ ቤት ውስጥ በእንክብካቤ የተሞላና የልጅነት ህይወቷም "መልካም መሆኑንም" ታስረዳለች። ካደገችም በኋላ ቢሆን ይህ ነው የሚባል ግንኙነት ከኢትዮጵያ ጋር እንደሌላት ትናገራለች። መስከረም ከሙዚቃ ችሎታዋም በተጨማሪ ደች፣ እንግሊዝኛና ፈረንሳይኛ አቀላጥፋ የምትናገር ሲሆን "የትኛውንም የኢትዮጵያ ቋንቋዎች መረዳትም ሆነ መናገር አልችልም" ትላለች። ሆኖም ስሟ መስከረም ምን ማለት እንደሆነ ታውቅ እንደሆነ ከቢቢሲ ለቀረበላት ጥያቄ ምላሿ "አዎ" ነበር። ስሟን የምትናገርበት የቋንቋ ቅላፄም ለየት ያለ ነው። መስከረም (ከቀኝ መጀመሪያዋ) ወደ ኢትዮጵያ በጣችበት ጊዜ መስከረም ታዳጊ እያለች በጉዲፈቻ ከወሰዷት ቤተሰቦቿና ከሁለት ወንድሞቿ ጋር ወደ ኢትዮጵያ የመምጣት እድሉን አግኝታ ነበር። ስለነበራትም ቆይታ መስከረም እንዲህ ትላለች "በጣም ነው ኢትዮጵያን የወደድኳት። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ያየሁዋቸውን ቆንጆ አበቦች አሁንም ፊቴ ላይ ድቅን ይላሉ። ህንፃው ራሱ ገራሚ ነው። በእውነቱ የኢትዮጵያ ጉብኝቴ ለየት ያለ ነበር" ትላለች። ኢትዮጵያን ስትጎበኝ የመጀመሪያ ጊዜዋ እንደመሆኑ "የቱሪስት አይነት ጉብኝት የነበረ ሲሆን" እንዲሁም ገና ታዳጊ በመሆኗም ከአገሪቷ ጋር ይህ ነው የሚባል ግንኙነት እንዳትመሰርት ምክንያት እንደሆነ ትጠቅሳለች። ነገር ግን መቼም ቢሆን የማትዘነጋው ጉዳይ "የሕዝቡ ደግነት፣ ቀናነትና እንግዳ ተቀባይነትን ነው" ትላለች። የመስከረም የሙዚቃ ህይወት የመስከረም የሙዚቃ ህይወት የሚጀምረው ገና በልጅነቷ ነው። ተማሪ እያለች ነበር የአውሮፓውያኑን ክላሲካል ሙዚቃ ተብሎ የሚጠራውን ነው ያጠናችው። ስመ ጥር የሚባሉ የሙዚቃ አቀናባሪ የሆኑትን የባህ፣ የሞዛርትና የቤትሆቨንን ሥራዎችን አጥንታለች። ይህም የራሷን የሙዚቃ ስልት እንድታዳብር መነሻ እንደሆናት ትናገራለች። ምንም እንኳን ትምህርቷ የክላሲካል የሙዚቃ ስልት ቢሆንም ስታድግ አባቷ ይጫውተው የነበረው የ40ዎቹና የ50ዎቹ ፎክሎር የተሰኘው የሙዚቃ ስልት ከፍተኛ ተፅዕኖ አሳርፎባታል። በተለይም በ1960ዎቹ በማኅበራዊ ፍትህ ዘርፍ ትልቅ ሚና የተጫወተው እንደ አሜሪካዊው ቦብ ዲለን ያሉ ሙዚቀኞች በእሷ የሙዚቃ ህይወት ትልቅ ስፍራ እንዳላቸው ትናገራለች። የራሷን የሙዚቃ ስልት በተመለከተም እንዲህ በአንድ የማይወሰን እንደሆነና ሰፊ መሆኑንም ትገልጻለች። "ስዘፍን ራሴን የተለየ ዓለም ውስጥ አገኘዋለሁ። ሙዚቃ ውስጤን የምገልፅበት፣ ከህሊናዬ ጋር የማወራበት ነው" ትላለች። መስከረም መሰንቆ ለመጫወት ስትሞክር መስከረም በራሷ የሙዚቃ ምህዋር ላይ ብቻ የምትዞር ሳይሆን ለአንዳንዶች ምናልባት 'አይዲያሊስት' ትመስላለች። "'አይዲያሊስት' ነኝ ብለሽ ታስቢያለሽ?" ከቢቢሲ የቀረበላት ጥያቄ ነበር "ምን ማለት እንደሆነ አላውቀውም። ትልቅ ቃል ነው። ገና 21 ዓመቴ ነው። ገና ዓለምን መፈተሽ መጀመሬ ነው" ትላለች። መስከረም በአሁኑ ወቅት መኖሪያዋን በትልቋ ከተማ ጌንት አድርጋለች "ነፃነቴን ምናልባት በከፍተኛ ሊባል በሚችል ሁኔታ እየተደሰትኩበት ነው። የምመለስ አይመስለኝም። ዓለምን ለማየት ተዘጋጅቻለሁ፤ ዓለምም እየጠበቀኝ ነው" ትላለች። ነገር ግን ከእሷ ጋር በሃሳብም የሚመሳሰሉ ሰዎችን ማግኘት ቀላል እንዳልሆነ ታስረዳለች። "የእኔ ዓለም ከሌሎች ጋር የሚገጣጠመው እንዴት ነው" በማለት ራሷን በተደጋጋሚ የምትጠይቅ መሆኑንም ትገልጻለች። በተለይም በአሁኑ ወቅት ባገኘችው ድንገተኛ ዕውቅና፣ ታዳሚዎቿን ማግኘት፣ ሕዝቡን ማየት እንዲሁም ሚዲያው እንደሚያስፈራት አልደበቀችም። "አስፈሪ እንዲሁም አስደሳች ሆኖ ነው ያገኘሁት። ቀላል አይደለም። እንደነዚህ አይነት እሳቤዎች ያነሳሱኛል። ሙዚቃየም ከእነዚህ ሃሳቦች ነው የሚነሱት" ትላለች። በኢንተርኔት ላይ ብዙ ስለ መስከረም መረጃ የሌለ ሲሆን ምናልባት ይህ ሆን ብላ ያደረገችው እንደሆነ በቢቢሲ ተጠይቃ ምላሿም ትንሽ እንደምታፍርና የግል ህይወቷንም ብዙ በማኅበራዊ ሚዲያ እንደማታጋራ ትናገራለች። መስከረም እንደምትለው በፀጥታ የተሞላና የተገለለ ህይወትን ትመርጣለች። ሆኖም በአሁኑ ወቅት ባለው የዓለም ሁኔታ እንዲሁም በጥበብ ኢንዱስትሪው ውስጥ ላሉ እንደሷ አይነት ሰዎች ከማኅበራዊ ሚዲያ መራቁ እንደማይቻልም ታስረዳለች። ከወረርሽኙ በኋላ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን ለማዘጋጀት አስባ እንደሆነ ስትጠየቅ "አዎ! በእንግሊዝ በተለይ የሙዚቃ ዝግጅቶችን ማድረግ እፈልጋለሁ፤ ምክንያቱም የሙዚቃዎቼ መነሻ ስለሆነ" ትላለች። መስከረም ከኢትዮጵያ ቋንቋዎች በአንደኛው ምናልባትም በአማርኛ ወደፊቱ ለትዘፍን ሃሳቡ እንዳላት ስትጠየቅ በሰጠችው ምላሽ "ይሄ ለኔ በጣም አስቸጋሪ ነው፤ ነገር ግን ምናልባት አንድ ቀን የማልሞክርበት ምክንያት የለም" ብላች። ዩቲዩብ ላይ የሚገኙትን የመስከረምን ሙዚቃዎች ለሰማ የምትዘፍነውን የሙዚቃ ስልት በአንድ አይነት ማስቀመጥ ከባድ ይሆናል። ሙዚቃዋ ከፎክ፣ ጃዝ፣ ፖፕና ክላሲካል የተጣመሩ ስልቶችን የያዘ ሲሆን፤ ለሰስ ያለና የመንቆርቆር ስሜት አለው። ግጥሞቿም ጥልቅ ናቸው። ለስለስ ባለ ድምጿና በጊታሯ ለየት ያሉ ዜማዎችን መፍጠር ችላለች። "ጆ" በተሰኘው ዘፈኗ የሙዚቃ ሰንጠረዥን መቆጣጠር የቻለችው መስከረም በቅርቡ አልበሟን ለማውጣት በዝግጅት ላይ እንደሆነችና ከሌሎች አርቲስቶችም ጋር የመጣመር እቅድ እንዳላት ታስረዳለች።
45327509
https://www.bbc.com/amharic/45327509
ዘጠኝ አየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ታሰሩ
አለም አቀፍ በረራዎችን በማስተጓጎል የተጠረጠሩና የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎችን ስራ ማቆም አድማ አስተባብረዋል የተባሉ 9 አየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች መታሰራቸውን ፌደራል ፖሊስን በመጥቀስ ፋና ዘግቧል።
አየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎቹ ካለፈው ሳምንት ሰኞ ጀምሮ የስራ ማቆም አድማ ላይ እንደነበሩ ይታወቃል። አድማውን ተከትሎ ባለፈው ሳምንት አጋማሽ ላይ ከአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ማህበር እንዲሁም የስራ ማቆም አድማውን ካስተባበሩ ሰራተኞች በጥቅሉ ዘጠኝ ባለሙያዎች ከትራንስፖርት ሚኒስቴር ተወካዮችና ከኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ጋር ድርድር ላይ እንደነበሩ ምንጮች ለቢቢሲ አማርኛ ገልፀዋል። ባለፈው ሳምንት የአዲስ አበባ፣ ባህር ዳርና መቀሌ አውሮፕላን ማረፊያ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች የስራ ማቆም አድማ መትተው ነበር። የትራፊክ ተቆጣጣሪዎቹ ከደሞዝ ጭማሬ፣ ከስራ ምዘና ፣ እውቅናና ከጥቅማጥቅም ጥያቄ ጋር በተያያዘ ነው ከላይ በተጠቀሱት አውሮፕላን ማረፊያዎች አድማ የመቱት። ተመስገን ቂጤሳ በአዲስ አበባ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪ ነው። የነበረባቸውን አስተዳደራዊ ጫና ተቋቁመው ለሙያቸው የሚገባው እውቅና እንዲሰጥና ጥቅማጥቅም እንዲጠበቅ ጥያቄ ሲያቀርቡ ቢቆዩም ምላሽ ሳያገኙ መቆየታቸውን ለቢቢሲ ገልፆ ነበር። ለጥያቄያቸው አለመመለስ መሰረታዊ ምክንያት የሆነው በኢትዮጵያ ሲቪል አቬየሽን ባለስልጣን ያለው የመልካም አስተዳደር ችግር እንደሆነ ተናግሯል። ተመስገን ባለስልጣኑ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎችን ጥያቄ ለመመለስ ልሞክር የሚልበት መንገድ ሙያውን በትክክል ካለመረዳትና የሚገባውን እውቅና ካለመስጠት የሚነሳ እንደሆነ አስረድቷል። "ዛሬ ላይ የተደረሰው በዚህ ምክንያት ነው" ብሏል። በረራዎች በአድማው ምንም እንዳልተስተጓጎሉ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ቢገልጽም ተመስገን ግን ክፍተቱን ለመሙላት የተሞከረው ከስራው ርቀው የቆዩ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎችን እንዲሁም ስልጠናቸውን ያልጨረሱ ተቆጣጣሪዎችን በማሰማራት መሆኑ አግባብ እንዳልሆነ ገልፆ ነበር። ድምፃቸውን ለማሰማት አስበው የነበረው ሙሉ በሙሉ ስራ አቁመው ሳይሆን የተወሰኑ ስራዎችን ( ቪ አይ ፒ ፣ አምቡላንስ እና ወታደራዊ በራራዎችን) ብቻ እየሰሩ ከስራ ገበታቸው ላይ ሆነው እንደነበር ነገር ግን ጠዋት ላይ ወደ ስራ ቦታቸው ሲሄዱ እንዳይገቡ መደረጉን ተመስገን ተናግሯል። ተመስገን እንደሚለው ከአድማው አንድ ቀን ቀደም ብሎም አንድ ፎርም እንዲሞሉ ፤ እሱን ካልሞሉ ግን የስራ ውላቸው እንደሚቋረጥ ማሳሰቢያም ተሰጥቷቸው ነበር። አድማው መቼ እንደሚያበቃ የቀረበለትን ጥያቄ በማስመልከት "ከባለስልጣኑ በላይ እንዲሁም በለውጥ ላይ ያለ መንግሥት አለ እንዲሰማን እንፈልጋለን"ብሏል። አስር እጥፍ ወይም 1 ሺህ በመቶ ደመወዝ ጭማሪ የጠየቃችሁት ደመወዛችሁ ስንት ቢሆን ነው? የሚልጥያቄ ለተመስገን አንስተን ነበር። በመጀመሪያ ኢትዮጵያ የአለም አቀፉን ስራ ድርጅት (አይ ኤል ኦ) ሰነድ የፈረመች አገር በመሆኗና ሰነዱም የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ካለባቸው የስራ ጫናና ስራው ከሚጠይቀው ሙያዊ አቅም አንፃር ከመርከብ ካፒቴን እንዲሁም ከኮሜርሻል ፓይለት እኩል እንዲከፈለው ማስቀመጡን ተመስገን ተናግሯል። "አገሪቱ ለፓይለት ትከፍላለች ። እኛ የሚከፈለን ግን አንድ መካከለኛ ፓይለት ከሚከፈለው ከአንድ ሃያኛ ያነሰ ነው። ለምሳሌ እኔ ሰባት ዓመት ሰርቻለው የሚከፈለኝ በወር 380 ዶላር ነው። የምሰራው ስራ ግን ከዚህ በላይ ዋጋ ያወጣል። የማገኘው ሌላ ምንም ዓይነት ጥቅማጥቅም የለም።" በማለት ሁለተኛውን ነጥቡን ያስቀምጣል። በሶስተኛ ደረጃ የሚያነሳው ነጥብ የጎረቤት አገር አየር መንገዶችን ተሞክሮ ነው። ''ኬንያ ከኢትዯጵያ ጋር ተመጣጣኝ ኢኮኖሚ ነው ያላት። የኬንያ አየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ከእኛ አምስት በመቶ እጥፍ ደመወዝ ያገኛሉ። ጥቅማጥቅም ሳይጨመር" በማለት ያለጥናት እንዲሁ አስር እጥፍ ይጨመርልን አለማለታቸውን አስረድቷል ተመስገን። ያላግባባቸው ባለስልጣኑ የአየር ትራፊክ ቁጥጥር ሙያን ሲመዝን ከዚህ ቀደም የሰራውን ጥናት መሰረት በማድረግ ጥያቄአቸውን ለመመለስ በመሞከሩ እንደነበርም ተመስገን ያስረዳል። የኢትዮጵያ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት የሆነው አቶ ፍፁም ጥላሁንም የባለሙያዎቹ ጥያቄ ከዓመታት በፊት በ45 ቀን ይመለሳል ተብሎ ስምንት ዓመታት እንዲሁ ማለፋቸውን ለቢቢሲ ገልፆ ነበር። የኢትዮጵያ ሲቪል አቪየሽን ባለስልጣን ዳይሬክተር ጀነራል ኮሎኔል ወሰንየለህ ሁነኛው «እስከዛሬ ድረስ በመሰል ደረጃ የወጣ ጥያቄ አልነበረም» ሲሉ ምላሽ ሰጥተው ነበር። «ከዚህ ቀደም የነበሩት ጥያቄዎች ከደረጃ አሰጣጥ (ሬቲንግ) ጋር የተያያዙ ነበሩ፤ እኒህ ጥያቄዎች ደግሞ በዓለም አቀፍ አሰራር መሰረት የሚመለሱ ናቸው። ለዚህ ኮሚቴ ተቋቁሞ እነሱንም የኮሚቴ አባል አድርገናቸዋል» በማለት ኮሎኔል ወሰንየለህ ሁኔታውን አስረድተዋል። «እውቅና የመስጠት ጉዳይም ሌላው ነገር ነው፤ በዚህ በኩል ደግሞ መንግሥት የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎችን ሥራ እውቅና በመስጠት በተወሰነ መልኩ ከፍ ያለ ደሞዝ እየከፈለ ነው ያለው።» በማለት እዚህ ጉዳይ ላይ መግባባት ያልተቻለው የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎቹ እውቅናን ከገንዘብ ጋር ስላያያዙት እንደሆነ ለማስረዳት ይሞክራሉ። «ሃገሪቱ ልትከፍል በምትችለው አቅም ጥናት አስደርገን ኮሚቴ አቋቁመን እነሱም የኮሚቴው አባል ሆነዋል። ነገር ግን እነሱ እየጠየቁ ያሉት 1 ሺህ በመቶ (አስር እጥፍ) የደሞዝ ጭማሪ ይደረግልን ነው።»ብለዋል። ኃላፊው ጨምረውም «ደመወዛችን አንሷል፤ መንግሥት እኛ በፈለግነው መጠን ካልከፈለን አድማ እንመታለን ብሎ መንግስትን ማስገደድ ተገቢ ነው ወይ? በሌላው ዓለምስ ይሄ ያስኬዳል ወይ?»በማለት ጥያቄም አንስተዋል። • «ወይዘሮ ጎሜዝ፤ እርስዎ አያገባዎትም! አርፈው ይቀመጡ በልልኝ» • አብዲ ሞሃመድ ያለመከሰስ መብታቸው ተገፈፈ • የብአዴን መግለጫ፡- ከስያሜ መቀየር እስከ ኢትዮ ሱዳን ድንበር የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎቹ ላለፉት ዓመታት አለብን የሚሉትን ችግር ሲያሰሙ እንደነበር በማስመልከት ጥያቄ ያቀረብንላቸው ኃላፊው መንግሥት በሚያደርገው የደሞዝ ጭማሪ መሠረት ባለሙያዎቹ ተጠቃሚ ሲሆኑ እንደነበር ነገር ግን የ1 ሺህ በመቶ ጭማሬ ጉዳይ ሲነሳ ሲሰሙ የመጀመሪያ ጊዜ እንደሆነ ገልፀዋል። «ምንም እንኳ መንግሥት አንድ ሺህ በመቶ (አስር እጥፍ) የሚለውን ኃሳብ ባይቀበለውም በተቋቋመው ኮሚቴ አማካይነት ጥናት እያካሄደ ነው» የባለሙያዎቹ አድማ መምታት በረራ ላይ የፈጠረው ተፅዕኖ ካለ በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ኃላፊው «በአድማው ተሳታፊ ያልሆኑ ባለሙያዎች ፣ ከዚህ ቀደም የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪ የነበሩና በሌላ ስራ ላይ ተመድበው የነበሩ ሌሎች ሥልጠና እንዲወስዱ ተደርጎ እንዲሁም ባለሙያዎችን ከውጭ አገር አየር መንገዶች በማምጣት ሥራው ያለ አንዳች እንከን እንዲካሄድ እያደረግን ነው» በማለት መልስ ሰጥተዋል። ይህ ዘላቂ መፍትሄ መሆን ይችላል ወይ ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ «እንግዲህ ከመንግሥት አቅም በላይ የሆነ የደሞዝ ጭማሪ የጠየቀን ባለሙያ ሌላ የምንይዝበት መንገድ የለም፤ ሌላም አማራጭ የለም፤ ስለዚህ ይህ ብዙ ችግር አይሆንብንም» ብለዋል።
news-57035751
https://www.bbc.com/amharic/news-57035751
በልብስዎ ቀለም እና በጣትዎ የ’V’ ምልክት በማሳየትዎ የሚታሰሩባት ቤላሩስ
የቤላሩስ ባለሥልጣናት የተቃዋሚዎችን ቀይ እና ነጭ ባንዲራ የሚውለበለቡትን ብቻ ሳይሆን በእነዚህን ቀለሞች የተሠሩ ካልሲዎችን ያደረጉትንም ሰዎችን እየቀጡ ነው፡፡
ወደ መንጃ ፈቃድ ትምህርት ቤት የምታቀና አንዲት ሴት በዋና ከተማዋ ሚኒስክ ውስጥ በአራት ሰዎች በቁጥጥር ስር ዋለች፡፡ ያልተፈቀደ ልብስ ለብሰሻል በሚል መያዟ ተነገራት፡፡ ምክንያቱ ምን ይሆን? የተከለከለውን ባንዲራ የሚመስል በቀይ መስመሮች ያሉት ነጭ ካልሲዎችን በልበሷ ነበር፡፡ የድል ምልክት የሆነውን የ'V' ምልክት ለሚያልፉ ተሽከርካሪዎች አሳይተሻል ተብላለች። ተመሳሳይ ምላሽ የሰጧት አሽከርካሪዎችም ከባድ የገንዘብ ቅጣት ተላለፈባቸው። ቀይ መስመር ያለው ነጭ ባንዲራ በ20 ኛው ክፍለዘመን የቤላሩስ ብሔረተኞች ባንዲራ ሆኖ ለአጭር ጊዜ አገልግሏል፡፡ በኋላም የሶቪዬት ኮሚኒስቶች መዶሻ እና ማጭድ ባለው በቀይ እና አረንጓዴ ባንዲራ ተክተውታል፡፡ ባንዲራው በድጋሚ በፕሬዚዳንት አሌክሳንደር ሉካሽንኮ እአአ በ 1995 እንደገና ተዋወቀ። በዚህ ጊዝ ግን ከኮሚኒስት ውድቀት በኋላ በመሆኑ መዶሻውን እና ማጭዱን ቀንሶ ነበር የቀረበው፡፡ ናታሊያ ሲቮቶቫ-ሴዱሽኪና 2,320 906 ዶላር እንድትቀጣ ተፈረደባት ፡፡ ያልተፈቀዱ የተቃውሞ ሰልፎችን በሚከለክሉ ህጎች መሰረት ነው ክስ ተመሰረተባት፡፡ በወቅቱ አጭር ጂንስ በመልበሷ የተከሰሰችበትን ካልሲዎችና ቀይ ቱታ በቀላሉ የሚታዩ ነበሩ፡፡ ካልሲዎቹን የገዛችበት የበይነመረብ ሱቅ ተመሳሳይ ቀለም ያለው ምርት መሸጥ ቢያቆምም ተመሳሳይ ነጭ ካልሲዎችን በጥቁር መስመር እየሸጠ ይገኛል። ሲቮቶቫ-ሴዱሽኪና በረንዳዋን በቀይ እና በነጭ ሪባን በማስጌጧ ከዚህ ቀደምም ተመሳሳይ የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባታል፡፡ ባለፈው ዓመት በአስር ሺህዎች የሚቆጠሩ ሰልፈኞች ወደ ሚንስክ አደባባዮች ወጥተዋል። ፕሬዚዳንቱ ሉካሼንኮ በነሐሴ ወር በተካሄደው ምርጫ አጭበርብረው በድጋሚ ተመረጥኩ ማለታቸው ነበር ሰልኞቹን ያስቆጣው፡፡ ሰልፎቹን ለመበተን ፖሊስ አስለቃሽ ጭስና ሃይል ተጠቅሞ በሺህዎች የሚቆጠሩትን ደግሞ አስሯል፡፡ ብዙ የፖሊስ የጭካኔ እርምጃዎች የተሰነዱ ሲሆን ሉካሼንኮ ከሩሲያ ውጭ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ተገልለዋል፡፡ ዋናዎቹ የተቃዋሚ መሪዎች በስደትም ሆነ በእስር ቤት ያሉ ተቃዋሚ መንግሥታት ተቃዋሚዎች በአብዛኛው ሞተዋል፡፡ በዚህ አመት ከ 2700 በላይ ሰዎች በፀረ-ሉካሼንኮ እንቅስቃሴ ክስ ተመስርቶባቸዋል፡፡ በሌሎች ፀረ-ተቃዋሚ ክሶች፡ * በሞጊሌቭ ነዋሪ የሆኑት ማሪያ ቮይኖቫ ፊርማዋ የ"ፅንፈኛውን" መፈክር እንዲመስል አድርገዋል በሚል 115 ዶላር ተቀጥታለች፡፡ * በተመሳሳይ በሞጊሊቭ ኦልጋ ክሊምኮቫ እና ሰርጌይ ስኮክ አሌክሳንደር ሉካሼንኮን በመሳደብ ጥፋተኛ ተብለው የሦስት ዓመት እስር ተላልፎባቸዋል ክሊምኮቫ እና ስኮክ በሚንስክ ውስጥ በፍርድ ሂደት ላይ * አንድሬ ፓርኮሜንኮ በረንዳ ላይ በቀይ እና በነጭ ያስቀመጠው "የወረቀት ባነር" ተቃዋሚዎችን ይደግፋል በሚል በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡ ግለሰቡ ቀለሞቹ አዲስ ቤት ሲቀየር ቴሌቪዥን ያመጣበት ካርቶን ቀለም መሆኑን እና በቅርቡ ወደ ቤቱ ስለገባ እንዳላስወገደው አስታውቋል፡፡ * ዩሊያ ያኩቦቪች በሚንስክ ውስጥ የፖለቲካ ሃሳብ ለማስተላለፍ መንገድ ዘግታለች በሚል ሁለት ዓመት ተፈርዶባታል፡፡ መንገዱ የተዘጋው ቀይ መብራት በመብራቱ ነው ስትል አስተባብላለች፡፡
55735400
https://www.bbc.com/amharic/55735400
ፑቲን ቅንጡ ቤተ መንግሥት ማስገንባታቸውን 'የሚያጋልጠው' ቪድዮ
የሩስያው ፕሬዘዳንት ቭላድሚር ፑቲን ቅንጡ ቤተ መንግሥት ለመገንባት በሕገ ወጥ መንገድ ገንዘብ ማፍሰሳቸውን የሚያሳየው የምርመራ ቪድዮ በተለቀቀ በጥቂት ቀናት ውስጥ ከ20 ሚሊዮን በላይ ተመልካች አግኝቷል።
ቪድዮው የተለቀቀው በሩስያዊው ተቃዋሚ አሌክሴ ናቫልኒ ቡድን ነው። ናቫልኒ ሩስያ፣ ሞስኮ ሲደርስ በቁጥጥር ስር የዋለው ከቀናት በፊት ነበር። የምርመራ ቪድዮው እንደሚያሳየው፤ ቤተ መንግሥቱ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር ወጥቶበታል። "በታሪክ ትልቁ ጉቦ ነው" በማለት በቪድዮው ተገልጿል። ክሬምሊን ቤተ መንግሥቱ የፑቲን አይደለም ብሏል። በደቡብ ሩስያ ብላክ ሲ አካባቢ የሚገኘው ቤተ መንግሥት የሞኖኮ 39 እጥፍ ስፋት እንዳለው ተገልጿል። ቪድዮው የተለቀቀው ናቫልኒ ከጀርመን ወደ ሩስያ ከሄደ ከሁለት ቀን በኋላ ነበር። ናቫልኒ በቅድመ ምርመራ ለ30 ቀናት የታሰረ ሲሆን፤ ገንዘብ በመበዝበር የቀረበበትን ክስ በመጣሱ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል። እሱ ግን እስሩ ፖለቲካዊ ነው ይላል። የ44 ዓመቱ ተቃዋሚ ባለፈው ነሐሴ ተመርዞ ለሞት ተቃርቦ ነበር። ለመመረዙ ተጠያቂው ፑቲን እንደሆኑ ቢናገርም፤ የሩስያ መንግሥት እጁ እንደሌለበት አስታውቋል። ቪድዮው ምን ያሳያል? የምርመራ ቪድዮው እንደሚያሳው ቤተ መንግሥቱ የተሠራው በፑቲን የቅርብ ሰዎች ሕገ ወጥ የገንዘብ ድጋፍ ነው። የነዳጅ ምርት ባለሥልጣኖች እና ቢሊየነሮች ከነዚህ መካከል ናቸውም ተብሏል። ናቫንሊ በቪድዮው "በዚህ ገንዘብ ለአለቃቸው ቤተ መንግሥት ሠርተዋል" ብሏል። የሩስያ ብሔራዊ የምርመራ ተቋም ቤተ መንግሥቱ ዙርያ ያለው 27 ስኩዌር ማይል መሬት ባለቤት እንደሆነም በቪድዮው ተጠቁሟል። ሕንጻው ውስጥ ካዚኖ (መቆመሪያ)፣ የበረዶ ሆኪ መጫወቻና ወይን ማቀነባበሪያ ይገኛል ተብሏል። "ለመጣስ የሚከብድ አጥር አለው። ራሱን የቻለ ወደብና ቤተ ክርስቲያን አለው። በረራ ማድረግ ክልክል ነው። የድንበር ላይ ጥበቃ ኃይልም አለው። ሩስያ ውስጥ ያለ ራሱን የቻለ አገር ነው" ሲል ናቫንሊ ተናግሯል። ናቫንሊ በጸረ ሙስና ንቅናቄው ይታወቃል። እአአ 2018 ላይ ፑቲን ተቀናቃኝ ሆኖ ምርጫ ሊወዳደር ሲል ገንዘብ የመበዝበዝ ክስ ተመስርቶበታል። ታዋቂው ሩስያዊ ተቃዋሚ ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተከታዮች አሉት። የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፐስኮቭ በቪድዮው ላይ የተባሉት ነገሮች "ሐሰት ናቸው" ብለዋል። ፕሬዘዳንቱ "ምንም ቤተ መንግሥት የላቸውም" ሲሉም ቃል አቀባዩ አስተባብለዋል። 22 ሚሊዮን ተመልካቾች ያገኘው የምርመራ ቪድዮ የሚገባደደው፤ ሕዝቡ ተቃውሞውን በአደባባይ እንዲገልጽ በማሳሰብ ነው። "ከተበሳጩ ሰዎች 10 በመቶው እንኳን የተቃውሞ ሰልፍ ቢያደርጉ መንግሥት ምርጫውን ለማጭበርበር አይደፍርም" ሲል ናቫንሊ ተናግሯል። ናቫንሊ የተመረዝኩት በፑቲን ነው ብሎ ወደ ሩስያ መመለሱ በርካቶችን አስገርሟል። ሆኖም ግን ማረሚያ ቤት ሆኖ ቪድዮው ከተለቀቀ በኋላ ደጋፊዎቹ ተቃውሞ እንዲካሄድ እያነሳሱ ነው። የናቫንሊ እጣ ፈንታ ምን ይሆናል? የካቲት 2 ናቫንሊ ፍርድ ቤት ይቀርባል። 2014 ላይ በፍርድ ቤት የተወሰነበት የሦስት ዓመት ተኩል እስር ስለመጽናቱም ውሳኔ ይተላለፋል። ከሦስት ቀናት በኋላ በድጋሚ ፍርድ ቤት ቀርቦ የሁለተኛው ዓለም ጦርነት ጀግኖችን ስም የማጥፋት ክሱ ይታያል። ናቫንሊ ከተመረዘ በኋላ ጀርመን ውስጥ ህክምና ሲከታተል ነበር። ወደ ሩስያ ከተመለሰ እንደሚታሰር ማስጠንቀቂያ ቢሰጠውም ወደ አገሩ ከመመለስ ወደኋላ አላለም። የቀረበበትን ክስ "ፍትሕ ላይ መቀለድ ነው። ሕገ ወጥነት መንሰራፋቱን ያሳያል" ሲል ተችቷል። 2018 ላይ የአውሮፓ የሰብአዊ መብት ፍርድ ቤት፤ የናቫንሊ ክስ "የዘፈቀደ ነው" ብሎ ነበር። መታሰሩ ከዚህ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ጋር የሚቃረን ነው የሚል ጥያቄ ተነስቷል።
news-55120402
https://www.bbc.com/amharic/news-55120402
ኮሮናቫይረስ፡ ጳጳሳቷን በኮቪድ-19 እያጣች ያለችው የሰርቢያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን
የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ እንደ ሰርቢያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጉዳትና ጫና ያሳረፈባቸው የእምነት ተቋማት በጣም ጥቂት ናቸው።
በባለፉት ሁለት ወራት ውስጥ በሰርቢያና ሞንቴኔግሮ የሚገኙ የቤተክርስቲያኗ ከፍተኛ ኃላፊዎችን በኮሮናቫይረስ አጥታለች። የቤተክርስቲያኗ ኃላፊዎች ከኮሮናቫይረስ መከሰት በኋላ በተለመደው መንገድ የአምልኮና ሌሎች አገልግሎቶችን በመቀጠላቸው ለወረርሽኙ መዛመትና ለሞቱ ምክንያት እንደሆነ ታዛቢዎች ይናገራሉ። ባለፉት ወራትም በቤተ ክርስቲያኗ የተከሰተው ተከታታይ ሞት አስደንጋጭ ሆኗል። የቤተ ክርስቲያኗ አመራሮች በኮሮናቫይረስ የታመሙም ሆነ የሞቱ ቢኖሩም በአሁኑ ወቅት ቤተክርስቲያኗ በአብዛኛው ሰርቢያውያን ዘንድ የህይወታቸው ማዕከል ናት። በሰርቢያ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች የማስተማር ሥራውን በወረርሽኙ ምክንያት በበይነ መረብ እንዲያደርጉ መመሪያ ቢወጣም ቤተክርስቲያኗ የቁርባን ሥርዓቷን አልተወችም። የአገሪቱ መንግሥት ወረርሽኙን ለመቆታጠር ከአምስት በላይ ሰዎች በአንድ ቦታ ላይ እንዳይሰባሰቡ ያስተላለፈውን ትእዛዝ በመተላለፍ ቤተ ክርስቲያኗ የአምልኮ ሥነ ሥርዓት ማካሄዷን ቀጥላለች። "ምንም እንኳን የምዕመናን ቁጥር በተወሰነ መልኩ መቀነስ ቢያሳይም አሁንም ቢሆን በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያኖች የሚደረገው የቅዳሴ ሥነ ሥርዓት አልተስተጓጎለም፤ በየጊዜው ይደረጋል" በማለት የእምነት ጉዳዮች ተንታኝ ዜልጅኮ ኢንጃክ ይናገራሉ። "በሰርቢያውያን ዘንድ ቤተ ክርስቲያኗ ትልቅ ክብር አላት። ከአገሪቷም ሆነ ከየትኛው ብሔራዊ ተቋማት በበለጠ ትልቅ ክብር አላት" ይላሉ ተንታኙ። "በባልካን አገራትም ሆነ በምሥራቅ አውሮፓ የአስተዳደር ሥርዓት፣ ፖለቲካዊ ሁኔታዎች፣ ርዕዮተ ዓለማትም ሆነ መንግሥት በተደጋጋሚ ቢቀያየርም ሕዝቡ በፖለቲካውም ሆነ በምጣኔ ሀብቱ ይህ ነው የሚባል ማሻሻያ አላሳየም። ለሕዝቡ ቋሚና ዋነኛዋ ነገር ቤተ ክርስቲያኗ ናት" በማለትም ያስረዳሉ። ሆኖም ሁለት ትልልቅ ጳጳሳት የቀብር ሥነ ሥርዓት ጋር ተያይዞ በቤተ ክርስቲያኗ አሰራር ላይ ትችቶች እየተሰሙ ነው። በሞንቴግሮ መዲና ፖዶጎሪጋ ለቅስተኛ ምዕመናን የኤጲስ ቆጶስ አምፊሎሂጄ ራዶቪች አስከሬን እጅና ግንባር በመሳምና በመሳለም ሲሰናበቱ ነበር። ኤጲስ ቆጶሱ በኮሮናቫይረስ ተይዘው ህይወታቸው ከማለፉ በፊት የእምነት ተግባራት "የአምላክ ክትባት" ናቸው ብለው ነበር። ለቀስተኛ ምዕመናን በቤልግሬድ ሴይንት ሳቫ ቤተክርስቲያን የተካሄደውን ፓትርያርክ ኢሪነጅ የቀብር ሥነ ሥርዓት በርቀት እንዲከታተሉት ተደርገዋል። ሆኖም ከቀብራቸው በፊት በነበረው የፓትርያርኩ የስንብት ሥነ ሥርዓት ላይ መመሪያዎች አልተከበሩም ተብሏል፤ የእምነቱ ተከታዮች የሬሳ ሳጥኑ ላይ የተገጠመውን መስታወት በመሳምና በመሳለምም ክብራቸውን ሲገልፁም ነበር። በነበረውም የቅዳሴ ሥነ ሥርዓት ቁርባኑ ሲፈፀም የነበረው በአንድ ማንኪያ እንደሆነም ተገልጿል። ይህም ሁኔታ ለኮሮናቫይረስ የማጋለጥ እድሉም ከፍተኛ እንደሆነም የተላላፊ በሽታዎች አጥኚ ዶክተር ጁሪክ ለቢቢሲ ሰርቢያ ተናግረዋል። ቤተ ክርስቲያኗ ሥነ ሥርዓቷንና አሰራሯን እንድታሻሻልና ካልሆነም መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ ባለሙያው ጥሪ አድርገዋል። ዶክተር ጁሪክ በተጨማሪም ስብሰባዎች የታገዱበት መመሪያ ወጥቶ ባለበት ሰዓት በቤተ ክርስቲያኗ ለምን ይህ ተግባራዊ እንደማይሆን ይጠይቃሉ። "ሕግና መመሪያዎች ለአንዳንዶች ተግባራዊ እንደማይደረግ መጥፎ መልዕክትን አስተላልፏል። ይህ ሁኔታ መመሪያዎችን ተግባራዊ እንዲያደርጉ በተጠየቀው ሕዝብ ዘንድ አመኔታን ያሳጣልም" ይላሉ። ከፓትርያርኩ የስንብት ፕሮግራም ጋር ተያይዞ ከፍተኛ የሆነ የወረርሽኙ መዛመት ሊኖር ይችላል በሚልም የጤና ባለሙያዎች ዝግጅት እያደረጉ ነው። በቅርብ ቀናት ውስጥ በሰርቢያ በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱንም በመጥቀስ ሁኔታው የሚያሳዝን ነው ተብሏል። የአገሪቱ ፕሬዚዳንት አሌክሳንደር ቩሲክ በበኩላቸው "ሁላችንም ቢሆን ኃላፊነታችን ካልተወጣን ለሚያሳዝን ከፍተኛ አደጋ መጋለጣችን አይቀርም" በማለት አስጠንቅቀዋል። ቤተ ክርስቲያኗ አገልግሎት መቀጠሏን በማስመልከት ምንም ከማለት የተቆጠበች ቢሆንም የቤተ ክርስቲያኗ ኃላፊዎችም ሆኑ ቁሶች ከቅዱስ ሲኖዶሱ አቅጣጫ እንዲቀመጥላቸው እየጠበቁ መሆኑን አሳውቀዋል። ምንም እንኳን የፓትርያርኩን ሞት እንዲሁም የኤጲስ ቆጶስ ዴቪድን ሆስፒታል መግባት ተከትሎ አገልግሎት የሚሰጡ ኃላፊዎች ቁጥር ቀንሷል። ነገር ግን አሁንም ዝርዝር አቅጣጫ ይሰጣል በሚል እየተጠበቀ ነው ያለው። እስከዚያው ግን ቤተ ክርስቲያኗ ፓትርያርኳን ለማስታወስ የምታደርገውን የሰባት ቀን እንዲሁም ሌሎች አገልግሎቶች ቀጥለዋል። በዚህ ሳምንት መጨረሻ አርብ በነበረው ስነ ስርአትም ቄሶች ጭምብል አላጠለቁም ነበር።
56087297
https://www.bbc.com/amharic/56087297
"የተማረ ወንድ አይደፍርም" ያሉት ሚኒስትር ከፍተኛ ውግዘትን አስተናገዱ
"የተማረ ወንድ አይደፍርም" በማለት የተናገሩት የደቡብ አፍሪካ የትምህርት ሚኒስትር ከፍተኛ ውግዘትን እያስተናገዱ ነው ተባለ።
ሚኒስትሯ አንጂ ሞትሼክጋ ስለ ትምህርት ጠቃሚነት እያስረዱ በነበረበት ወቅት ነው ይህንን አስተያየት የሰጡት ተብሏል። በያዝነው ሳምንት ሰኞ እለት ሚኒስትሯ ለሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች እንደተናገሩት ግለሰቦች በትምህርታቸው የላቀ ደረጃ ላይ ከደረሱ መድፈርን ጨምሮ ሌሎች ነውረኛ ተግባራት ላይ የመሳተፍ እድላቸው አነስተኛ ነው ብለዋል። በርካቶች የሚኒስትሯ አስተያየት መሰረታዊ የሆነውን የፆታዎች የኃይል ሚዛን ልዩነትን ያላገናዘበ ነው ሲሉ ተችተዋቸዋል። በቦታው የነበሩት ተማሪዎች በሚኒስትሯ አስተያየት ባለመስማማት ሲያጉረመርሙ የተሰማ ሲሆን ሚኒስትሯም ለዚሁ ምላሽ በሚመስል መልኩ "የተማሩ ወንዶች በእንደዚህ አይነት ወንጀለኛ ድርጊቶች መሳተፋቸው በጣም አሳዛኝ ነው" ብለዋል። የተወሰነ ንግግራቸው ተቀንጭቦ በማህበራዊ ሚዲያዎች የተጋራ ሲሆን በርካቶችንም አስቆጥቷል። የመድፈር ባህል በተንሰራባት ደቡብ አፍሪካ የተማሩ ወንዶች አይደፍሩም ምን ማለት ነው በሚልም ብዙዎች ተችተዋል። ሚኒስትሯ በበኩላቸው አስተያየታቸው ከአውድ ውጭ እንደተወሰደ ተናግረዋል። "መድፈር ከስልጣንና ኃይል ጋር የተገናኘ ነው። በወንዶችና በሴቶች መካከል ያለውን የኃይል ሚዛን ልዩነት ለማስረዳት ወንዶችን ከህፃንነታቸው ጀምሮ እንዲያውቁ በማለት በትምህርተ ስርአቱ ቀርፀን እያስተማርን እንገኛለን። ወንዶች የኃይል ሚዛንን በተመለከተ፣ አባታዊ ስርአትን እንዲሁም የተሳሳተ የወንድነት ትርጉምን በተመለከተ ሊማሩ ይገባል። በተለይ ወሲባዊ ጥቃትን ለመታገል ወንዶች በፆታዎቹ መካከል ስላለው የኃይል ሚዛን ሊማሩ ይገባል" በማለት ከሚኒስትሯ የወጣው መግለጫ አስፍሯል። በአውሮፓውያኑ 2019 ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ ወሲባዊ ጥቃቶች የአገሪቱ ብሔራዊ ቀውስ ነው በማለት አውጀው ነበር። በየአመቱም 40 ሺህ ወሲባዊ ጥቃቶች ሪፖርት የሚደረጉ ሲሆን ይህም በአገሪቷ ካለው ቁጥር አንፃር ኢምንት ነው ይላሉ።
news-51534366
https://www.bbc.com/amharic/news-51534366
ሐማስ የአማላይ ሴቶችን ፎቶ በመጠቀም የእስራኤል ወታደሮችን ስልክ ጠለፈ
የሚሊሻ ቡድኑ ሐማስ የበርካታ የእስራኤል ወታደሮችን ስልክ መጥለፉን የእስራኤል ጦር አስታወቀ።
ሐማስ የወታደሮቹን ስልክ ለመበርበር ከተጠቀማቸው የሴቶች ፎቶግራፍ መካከል አንዱ። ቡድኑ ጾታዊ ግንኙነት ፈላጊ ሴት በመምሰል የአማላይ ሴቶች ምሥል በመጠቀም ወደ ወታደሮች ስልክ መልእክት ይልካል፤ ከዚያም የጦሩ አባላት ሳያውቁ በስልካቸው ላይ ስለላ ለማድረግ የሚጠቅም መተግበሪያ (አፕ) ይጭናል። የእስራኤል ጦር እንዳለው ሐማስ ከፍተኛ ጉዳት ሳያስከትል ብርበራው እንዲከሽፍ ተደርጓል ብሏል። ጋዛን ተቆጣጥሮ የሚገኘው ሐማስ ከእስራኤል ጋር ለዓመታት ባላንጣ ሆኖ ቆይቷል። የእስራኤል ጦር ከፍተኛ አዛዥ የሆኑት ሊውተኔት ኮሎኔል ጆናታን ኮንሪከስ እንደሚሉት ከሆነ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ሐማስ ተመሳሳይ ጥረቶችን ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰው፤ ይህ ሙከራው ግን ከዚህ ቀመድ ሲጠቀምባቸው ከነበሩት ስልቶች የተለየ እና የቴክኖሎጂ ይዘቱም የተራቀቀ መሆኑን ጠቁመዋል። "እራሳቸውን እያስተማሩ እና እየሰለጠኑ መምጣቻቸውን አስታውለናል" ብለዋል። ሊውተኔት ኮሎኔል ጆናታን እንደሚሉት ከሆነ የሐማስ በርባሪዎች ሂብሩ ቋንቋ የማይችሉ እና ወደ እስራኤል በቅርብ የመጡ ሴት የጾታ ግንኙነት ፈላጊ በመምሰል ወንድ ወታደሮችን ዒላማ ሲያደርጉ ቆይተዋል። ቋንቋ እንደማይችሉ እና በቅርብ ወደ እስራኤል እንደመጡ ማስመሰላቸው በጦሩ አባላት ዘንድ እንዲታመኑ አድርጓቸዋል ብለዋል የጦር አዛዥ። "ግንኙነቱን ከተጀመረ በኋላ 'ፎቶግራፋችንን ተመልከቱ' በማለት ሊንክ ይልካሉ። ሊንኩን ሲጫኑት ግን ስልካቸውን መበርበር የሚያስችል መተግበሪያ ይጫናል" ብለዋል። በርባሪዎቹ ይህን ሲያደርጉ በስልካችው ላይ የሚገኙትን የሰዎች ስም እና አድራሻን ጨምሮ ሙሉ መረጃ ማግኘት ያስችላቸዋል ተብሏል። ከዚህ በተጨማሪ ያለ ስልኩ ባለቤት ዕውቅና የተጠለፈበት ሰው ስልክ ድምጽ እና ምሥል እንዲቀርጽ ማድረግ ይቻላቸዋል ተብሏል። የእስራኤል መከላከያ ኃይል ወታደሮቹ ዘመናዊ ስልኮችን ሲጠቀሙ የበርባሪዎች ዒላማ እንዳይሆኑ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲወስዱ የሚያስችል ስልጠናዎችን ሲሰጥ እንደነበረ ተነግሯል።
news-55802353
https://www.bbc.com/amharic/news-55802353
በአዲስ አበባ ከ21 ሺህ በላይ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በሕገ-ወጥ መንገድ ተይዘው ተገኙ
በአዲስ አበባ 21,695 የጋራ መኖርያ ቤቶች በሕገ-ወጥ መንገድ ተይዘው መገኘታቸውን ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ተናገሩ።
የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በሕገ-ወጥ የመሬት ወረራና ባለቤት አልባ ህንፃዎች እንዲሁም ኮንዶሚኒየምና የቀበሌ ቤቶች ዙሪያ የተደረገ የማጣራት ውጤት ላይ በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም 1,338 ሄክታር መሬት በሕገ-ወጥ የተወረረ መሆኑን፣ 21,695 የጋራ መኖርያ ቤቶች በተለያየ በሕገ-ወጥ ሁኔታ ላይ የሚገኙ መሆኑን፣ 322 ግንባታቸው ያለቀና ያላለቀ ህንፃዎች ባለቤት አልባ ሆነው መገኘታቸውን፣ 14,641 መኖርያና ለንግድ የተከራዩ የቀበሌ ቤቶችን ያለ አግባብና በሕገ-ወጥ ይዞታነት የሚገኙ መሆኑን አስታውቀዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ም/ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ዛሬ ማክሰኞ እለት፣ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በአጠቃላይ በአዲስ አበባ 13 ሚሊየን 389 ሺህ 955 ካሬ ወይም 1 ሺህ 338 ሄክታር መሬት በሕገ-ወጥ መያዙን አስታውቀዋል። ወይዘሮ አዳነች በዚህ መግለጫቸው ላይ እንዳሉት በአዲስ አበባ በሕገ-ወጥ መንገድ ከተያዙት 21 ሺህ 695 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ውስጥ 15 ሺህ 891 የሚሆኑት የባለቤትነት መረጃ አልቀረበባቸውም። 850 ቤቶች ደግሞ ዝግ ሆነው ሲገኙ 4 ሺህ 530ዎቹ ደግሞ ባዶ ሆነው ተገኝተዋል ብለዋል ምክትል ከንቲባዋ። እንደ ምክል ከንቲባዋ መግለጫ ከሆነ 424 በሕገ-ወጥ መልኩ በግለሰቦች ተይዘው የሚገኙ ሲሆን በዕጣ ሳይሆን በተለያዩ አግባቦች ወደ ተጠቃሚው ግለሰቦች የተላለፉ ደግሞ 51 ሺህ 64 ቤቶች ሆነው ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በአዲስ አበባ ከተማ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች እየተባባሰ የመጣ፣ የመንግሥታዊ መዋቅሮች ድጋፍ ያለው ሕገ-ወጥ የመሬት ወረራ እና የጋራ መኖሪያ ቤቶች ኢፍትሃዊ ዕደላ እንዳለ ባካሄድኩት ጥናት ደርሼበታለሁ ሲል ማስታወቁ ይታወሳል። በቤቶች ኮርፖሬሽን ተመዝግቦ የሚገኘው ባለዕጣዎች የስም ዝርዝር እና በመስክ በተገኘው የተጠቃሚዎች የስም ዝርዝር መካከል ልዩነት ያላቸው ቤቶች 132 ሺህ 678 እንደሆኑና 18 ሺህ 423 ቤቶች ደግሞ የቤት ባለቤት ስም የሌላቸው መሆኑን በጥናቱ መለየቱንም አስታውቀዋል። በእነዚህ ቤቶች ውስጥ የሚኖሩ ግለሰቦች መረጃቸውን እንዲያቀርቡ በተደጋጋሚ ቢጠየቁም መረጃ ማቅረብ ያልቻሉ ወይም ያልፈለጉ በመሆናቸው ቤቶቹ በህገወጥ መንገድ የተያዙ መሆናቸውም በጥናቱ መለየቱን አስታውቀዋል። እንደ ምክትል ከንቲባዋ በአዲስ አበባ ካሉ 121 ወረዳዎች ውስጥ በ88ቱ ወረዳዎች በተፈጸመ የመሬት ወረራ 1 ሺህ 338 ሄክታር መሬት ሲወረር፣ በተደረገው የህንጻ ቆጠራም 322 ህንጻዎች እና ቤቶች ባለቤት አልባ ሆነው ተገኝተዋል። ከ1997 ጀምሮ በከተማዋ በተለያየ አግባብ ሕገ-ወጥ የመሬት ወረራው ሲፈፀም ነበረ ያሉት ምክትል ከንቲባዋ፣ በ2010 ሀገራዊ ለውጥ ከመምጣቱ በፊት ሰፋ ባለ መልኩ የመሬት ወረራው የነበረና ከለውጡ በኋላም አጠቃላይ አመራሩ ህገወጥነትን በተገቢው ባለመከላከሉ ችግሩ እንዲደራረብ አድርጎታል ነው ያሉት። ባለቤት አልባ ቤቶችና ህንፃዎች በተመለከተም ባለቤት አልባ በሚል የተለዩት ቤቶችና ህንፃዎች በድምሩ 322 ሲሆኑ፣ የቦታ ስፋታቸው ደግሞ 229 ሺህ 556 ካሬ መሆኑ መለየቱ ተገልጿል። እንደ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ መግለጫ ከሆነ፣ ከየወረዳ ቤቶች ልማት ጽህፈት ቤቶች በተገኘ መረጃ መሰረት አጠቃላይ በከተማ አስተዳደሩ ስር የሚተዳደሩ 150 ሺህ 737 የቀበሌ መኖሪያ እና ንግድ ቤቶች አሉ። በዚህ ጥናት ተደራሽ መሆን የተቻለው 138 ሺህ 652 የመኖሪያ እና የንግድ ቤቶችን መሆኑም ተገለጿል። በከተማዋ 10 ሺህ 565 የቀበሌ ቤቶች በቁልፍ ግዥ፣ ሰብሮ በመግባት፣ እና በሌሎች ህጉ ከሚፈቅደው ውጪ በሕገ-ወጥ መንገድ ተይዘዋል ብለዋል ምክትል ከንቲባዋ። በጥናቱ ተደራሽ ከተደረጉ የቀበሌ መኖሪያ ቤቶች ውስጥ 7 ሺህ 723 ቤቶች ውል በሌላቸው ሰዎች ተይዘዋል። 2ሺህ 207 የቀበሌ ቤቶች ደግሞ ወደግል የዞሩ ሲሆን፣ 265 በሶስተኛ ወገን የተያዙ፣ 164 ኮንደምንየም በደረሳቸው/የራሳቸው ቤት ባላቸው ሰዎች የተያዙ የቀበሌ መኖሪያ ቤቶች መኖራቸው ነው፡፡ 137 ለመኖሪያነት የሚያገለግሉ የቀበሌ ቤቶች በሽያጭ ወደ ግል የተላለፉ፤ 1 ሺህ 243 ታሽገው/ተዘግተው የተቀመጡ፣ 5 ሺህ 43 የፈረሱ፤ 180 አድራሻቸው የማይታዎቁ/የጠፉ የቀበሌ መኖሪያ ቤቶች እንዳሉ ተረጋግጧል። የቀበሌ ንግድ ቤቶችን በተመለከተ በሰጡት መግለጫ በአጠቃላይ የንግድ ቤቶች ብዛታቸው 25 ሺህ 96 ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ በሕገ-ወጥ መንገድ የተያዙ የቀበሌ የንግድ ቤቶች ብዛት 4 ሺህ 76 ናቸው። በከተማዋ ሕገ ወጥ የመሬት ወረራ ባህሪያት ጋር በተያያዘ በህገወጥ መንገድ ባዶ የሆነ የመንግስትን መሬት በወረራ በመያዝ የተፈፀመ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ይህ ድርጊት በግለሰብ ደረጃና በሀይማኖት ተቋማትም ጭምር የተፈፀመ መሆኑ ምክትል ከንቲባዋ ተናግረዋል።
news-47938529
https://www.bbc.com/amharic/news-47938529
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሴት ሰራተኞች ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ ቅርንጫፍ ከፈተ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአዲስ አበባ፣ አትላስ አካባቢ በሴት ሠራተኞች ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ ቅርንጫፍ መክፈቱን አስታወቀ።
ቅርንጫፉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1400ኛው ቅርንጫፍ ሲሆን ከሥራ አስኪያጅ ጀምሮ በባንኩ አገልግሎት የሚሰጡት ሁሉም ሠራተኞቹ ሴቶች ብቻ መሆናቸው ተገልጿል። • ኢንጅነር አይሻ መሃመድ የሃገር መከላከያ ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ • ሴቶች የተቆጣጠሩት የስፔን ካቢኔ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ በልሁ ታከለ ሴቶች በአንድ አገር ሁለንተናዊ እድገት ከፍተኛ ድርሻ ቢኖራቸውም የሚገባቸውን ቦታ ባለማግኘታቸው የሴቶችን ተሳትፎ ለማጎልበትና ለማበረታታት ሲባል ቅርንጫፉ እንደተከፈተ ለቢቢሲ ገልፀዋል። "ሴቶች ከወንዶች በተሻለ ደንበኞችን በጥሩ እንክብካቤ በማስተናገድ ከደንበኞቻችን ጋር ያለንን ግንኙነት ሲያጠናክሩ በተግባር አይተናል" የሚሉት አቶ በልሁ በሴቶች ብቻ የተቀላጠፈና የተደራጀ አገልግሎት መስጠት እንደሚቻል ማሳየትም ሌላኛው ዓላማው ነው ብለዋል። ቅርንጫፉ ከሌሎች ባንኮች የተለየ አገልግሎት ባይሰጥም የሴቶችን የሥራ ፈጠራና የፋይናንስ አቅም ለማጠናከር የሴቶች የብድር አገልግሎት ለመጀመር ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። ሠራተኞቹ ከተለያዩ የባንኩ ቅርንጫፎች የተውጣጡ እንደሆነም ታውቋል። ቅርንጫፉ በኢንዱስትሪው ውስጥ ትልቅ ድርሻ ባላቸው አንጋፋ የባንክ ባለሙያ አቶ ለይኩን ብርሃኑ ተሰይሟል።
news-50142851
https://www.bbc.com/amharic/news-50142851
ኢትዮጵያ እና ኬንያ ድንበር ላይ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ የሁለት ሰዎች ህይወት አለፈ
ኢትዮጵያ እና ኬንያ ድንበር ላይ በከባድ ዝናብ ሳቢያ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ለሁለት ሰዎች እና ለበርካታ የቤት እንስሳት ሞት ምክንያት ሆነ።
መርሰቢት በሚባለው የኬንያ ግዛት ውስጥ የድርቅ መከላከል ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ጉዮ ጎሊቻ ከዚህ ቀደም በአከባቢው በከባድ ዝናብ ሳቢያ የሚደርስ የጎረፍ አደጋ የተለመደ ቢሆንም የዘንድሮው ግን የተለየ ነው ብለዋል። • የውሃ እጥረት ዋነኛው የዓለማችን ስጋት • ምድር በአስፈሪ ሁኔታ እየሞቀች ነው ሳናውቀው እያለቁብን ያሉ ስድስት ነገሮች በጎርፉ አደጋ የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉንና ወደ 9 ሺህ የሚጠጉ የቤት እንስሳት መሞታቸውን አቶ ጎዮ ለቢቢሲ ተናግረዋል። "ከዝናብ በኋላ የተከሰተው ጎርፍ ከኢትዮጵያ ከሚመጣው ውሃ ጋር ተጨምሮ በሶሎሎ፣ ጎልቦ እና ዋጂራ ተብለው በሚጠሩ አከባቢዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት አስከትሏል" ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። በጎርፍ አደጋው ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች የሚያስፈልጓቸው ድጋፎች እየተደረጉላቸው እንደሆነ ጨምረው ተናግረዋል። ወደ 6ሺህ የሚጠጉ ፍየሎች እና ከ3ሺህ በላይ ከብቶች ሳይሞቱ እንዳልቀሩ ግምት አለ የሚሉት አቶ ጉዮ፤ 200 እስከ 300 የሚሆኑ መኖሪያ ቤቶችም ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰ ያስረዳሉ። • ዓለምን ሊመግብ የሚችለው የስንዴ ዘር • ዛፎች ከምድር ቢጠፉ ምን ይፈጠራል? የቀይ መስቀል የመርሰቢት ግዛት ተወካይ የሆኑት ሞውሪስ አኒያንጎ "እስካሁን 226 ቤተሰብ መርዳት ችለናል" ያሉ ሲሆን የቀይ መስቀል እርዳታ ሰጪዎች በጎርፉ ሳቢያ እንደልብ በየብስ እየተንቀሳቀሱ እርዳታ መስጠት ስላልቻሉ በአየር ብቻ የተደረገፈ እርዳታ እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል። "ከአሁን በኋላ እንኳ ለቀጣዮቹ ሁለት ወራት ዝናብ መዝነቡን ይቀጥላል። ተጨማሪ አደጋ ሊደርስ ስለሚችል ለህዝቡ የማስጠንቀቂያ መልዕክቶችን ማስተላለፍ ላይ ትኩረት አድርገውን እየሰራን ነው" ያሉት አቶ ጉዮ ናቸው።
news-47939679
https://www.bbc.com/amharic/news-47939679
በጦላይ የኦነግ ሠራዊት አባላት ላይ የተከሰተው ምንድን ነው ?
ከባለፈው እሁድ ጀምሮ የጤና እክል ገጥሟቸው ሆስፒታል እየገቡ ያሉ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ወታደሮች ቁጥር እየጨመረ ነው።
ወታደሮቹ ቁርስ ተመግበው ሲነሱ ብዙ እራሳቸውን እየሳቱ መውደቅ መጀመራቸው መነገሩ ይታወሳል። ወታደሮቹ ጨምረውም የቀረበላቸው ሻይ ውስጥ ነጭ ባዕድ ነገር መመልከታቸው እና የተለየ ጠረን እንዳለው ጨምረው ተናግረዋል። "ሻይ በምንጠጣበት ብርጭቆ ስር ነጭ ዱቄት የሚመስል ነገር አግኝተናል፤ ይህንንም ለማሰልጠኛው አስተዳደሮች አሳይተናል" ሲል አንድ ስሙ እንዲጠቀስ ያልፈለገ የኦነግ ሠራዊት አባል ለቢቢሲ ተናግሯል። • ትጥቅ የፈቱ የኦነግ ወታደሮች የረሃብ አድማ ላይ ናቸው የጤና እክል በገጠማቸው የሠራዊቱ አባላት ላይ የሚታዩበት ምልክት ምን እንደሆነ ሲናገር "የአፍ ድርቀት፣ የሆድ ቁርጠት፣ ሆድ የማቃጠል ስሜት፣ ከደም ጋር የተቀላቀለ ትውከትና የፊት መገርጣት ናቸው" ብሏል። የኦሮሚያ ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ረታ በላቸው፤ በጦላይ በሚገኙ የኦነግ ወታደሮች ላይ ያጋጠመው የጤና ችግር መንስዔ እየተጣራ ነው ያሉ ሲሆን የደረሰባቸው የጤና እክል ግን ለህይወት አስጊ አይደለም ብለዋል። እንደ ምክትል ኮሚሽነሩ ከሆነ 134 የኦነግ ወታደሮች በወሊሶ ቅዱስ ሉቃስ ሆስፒታል የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው እንደነበር ተናግረዋል። ምክትል ኮሚሽነሩ የጦላይ ማሰልጠኛ አስተዳደሮች ጉዳት አስከተለ የተባለውን ሻይ ቀምሰው ምን የደረሰባቸው ነገር የለም ብለዋል። ''እኛ የቀረበላቸው ሻይ ውስጥ መርዝ ተጨምሯል ብለን አናምንም፤ ምርመራ እየተካሄደ ነው። እንደተባለው መርዝ ተጨምሮ ከተገኘ ግን ጠፋተኛው ላይ እርምጃ ይወሰዳል።'' በዚሁ ሆስፒታል እየታከመ የሚገኘው ሌላኛው የሠራዊቱ አባል ኢብሳ በበኩሉ የተሰጣቸውን ሁሉ ተመግበው ቢሆን ኖሮ ጉዳቱ ከፍ ያለ ሊሆን እንደሚችል ገልፆ "ሁላችንም እናልቅ ነበር" በማለት ተናግሯል። • «ኦነግ ሀገር ለመገንጠል ነው የምሠራው ብሎ አያውቅም» ሽጉጥ ገለታ (ዶ/ር) "ይሄ ነገር የመርዝ ሽታ አለው ብዬ ስላስቆምኩዋቸው ሻዩን አልጨረሱትም ነበር። ገሚሱ ቀምሰው ብቻ ስለሆነ የተዉት በዚያ መንገድ ነው የተረፍነው" ይላል። "እከሌ ብለን ማንም ላይ ጣታችንን ባንቀስርም ህብረታችንን የማይወዱ ሰዎች እንዳሉ እንጠረጥራለን። ነገር ግን ግቢው ውስጥ ካሉ ሰዎች ጋር ምንም አይነት ግጭት የለንም" ብሏል። የህክምና ባለሙያዎች ምን ይላሉ? ወሊሶ በሚገኘው የቅዱስ ሉቃስ ሆስፒታል ሃኪም የሆኑት ዶ/ር አብዱላቲፍ ይሲያቅ እስከ ዛሬ ማክሰኞ ከሰዓት ድረስ 154 የኦነግ ሠራዊት አባላት ህክምና እየተደረጋለቸው መሆኑን ተናግረዋል። "በእኛ ምርመራ መሰረት የምግብ መበከል (መመረዝ) ሳይሆን ራሱን የቻለ መርዝ ተጨምሮበት እንደሆነ ነው የሚያሳየው። የሠራዊቱ አባላትም መርዝ እንደሸተታቸው ተናግረዋል" ብለዋል። ዶ/ሩ ጨምረውም ታካሚዎች ራስ ምታት፣ የሆድ ቁርጠት፣ ሆድ የማቃጠል ስሜት፣ ከደም ጋር የተቀላቀለ ትዉከትና የፊት መገርጣት ምልክቶች እንደታየባቸው በመናገር እነዚህም የመርዝ ምልክቶች መሆናቸውን ተናግረዋል። •“ኢትዮጵያ አዲስ የጥላቻ ንግግር ህግ አያስፈልጋትም” አቶ አብዱ አሊ ሂጂራ የክልሉ የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ አድማሱ ዳምጠው በበኩላቸው 136 የኦነግ ሠራዊት አባላት በጤና እክል ምክንያት በወሊሶ ሉቃስ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑንና የከፋ የጤና ችግርም እንደሌለ ለመንግሥት ሚዲያዎች በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። በመግለጫቸው ጨምረው በሠራዊቱ አባላት ላይ የምግብ መመረዝ ደርሶባቸዋል፤ ሠራዊቱ ላይም ይህ ሆን ተብሎ የተደረገ ነው እየተባለ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰት ነው ብለዋል። ያጋጠመውን የጤና እክል መንስኤም ለማጣራት ፖሊስና የሚመለከታቸው አካላት ምርመራ እያደረጉ መሆናቸውን ገልፀው መንስኤውም ሲታወቅ ውጤቱ ለህዝብ ይፋ እንደሚሆን ነው።
news-57222403
https://www.bbc.com/amharic/news-57222403
ኮሮናቫይረስ፡ በሕንድ ኮቪድ-19 የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ300ሺህ አለፈ
ከኮቪድ-19 ተህዋሲ ጋር በተያያዘ በሕንድ የሟቾች ቁጥር በድምሩ ከ300ሺህ ማለፉን መንግሥት ይፋ አደረገ።
አንዲት ሴት በአስከሬን ማቃጠያ አቅራቢያ የጤና ባለሙያዎች በበኩላቸው ይህ አሐዝ በቅርብ ወራት ውስጥ በአያሌው ሊጨምር እንደሚችል ይተነብያሉ። ይህም ብቻ ሳይሆን የሟቾች ቁጥር መንግሥት ይፋ ካደረገውና በቅጡ ካመነው በበለጠ እንዲያውም በሦስት እጥፍ እንደሚሆን ግምት ሰጥተዋል። በሕንድ በተህዋሲው በድምሩ 300ሺህ ሰዎች ሕይወታቸውን ያጡ መሆኑ ይፋ ሲደረግ፤ በተህዋሲው የተያዙ ሰዎች ደግሞ 26 ሚሊዮን እንደሆኑም ተመላክቷል። ይህም አሐዝ ሕንድን ከአሜሪካ ቀጥሎ በዓለም ብዙ ዜጎቿ በተህዋሲው በመያዝ ብልጫ ያላት 2ኛዋ ትልቅ አገር ያደርጋታል። በሟቾች ብዛትም ከሄድን ሕንድ በዓለም ከአሜሪካና ብራዚል ቀጥላ በርካታ ዜጎቿን በተህዋሲው ያጣች 3ኛዋ አገር ናት። የሚገርመው ሕንድ ከ100ሺህ ሰዎች ሞት ወደ 300ሺህ ዜጎች ሞት የተሸጋገረችው አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ መሆኑ ነው። ሁለተኛ ዙር ወረርሽኝ በሕንድ የተከሰተው ባለፉት ሳምንታት ሲሆን ተህዋሲው እጅግ በሚያስደነግደጥ ፍጥነት የብዙዎቹን ሕንዳዊያንን ቤት አንኳኩቶ የ200ሺህ ዜጎችን ሕይወት ነጥቋል። ሆስፒታሎች በህሙማን መጨናነቃቸው ሳያንስ የሟቾችን አስከሬን ለማስወገድ እንኳ ፈተና ሆኖ በወንዞች ዳርቻ በመቶዎች የሚቆጠሩ አስክሬኖች መገኘታቸው ዓለምን ያነጋገረ ጉዳይ ሆኖ ሰንብቷል። የአስክሬን ማቃጠያ ቦታዎች እጥረት በመከሰቱም ጊዜያዊ የአስክሬን ማቃጠያ ድንኳኖችን በፓርኮች ውስጥ መትከል አስገድዶ ነበር። በሕንድ ድህነት ክንዱን ባበረታባቸው ገጠራማ ቀበሌዎች የሞት ምዝገባ የሚታወቅም የሚታሰብም ጉዳይ አይደለም። ይህን እውነታ ከግምት ውስጥ በማስገባት በሕንድ በተህዋሲው የሞቱት ሰዎች ቁጥር መንግሥት ካመነው በብዙ ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ይገመታል። አንዳንድ የሟቾችን ቁጥር በሌሎች ዘዴዎች ግምት ለማግኘት የሞከሩ ባለሙያዎች እንደሚሉት በሕንድ በኮቪድ-19 ምክንያት ቢያንስ አንድ ሚሊዮን ሰው ሳይሞት አልቀረም።
news-48545494
https://www.bbc.com/amharic/news-48545494
የሕክምና ባለሙያው ታካሚዎችን በመግደል ዘብጥያ ወረደ
ጀርመናዊው የቀድሞ ነርስ የ85 ታካሚዎችን ነብስ በማጥፋት ወንጀል ጥፋተኛ ተባለ።
በምስራቅ ጀርመን በሚገኙ ሁለት ሆስፒታሎች ይሠራ የነበረው ነርስ የ85 ታካሚዎችን ነብስ አጥፈተሃል ተብሎ ተፈርዶበታል። ኒየልስ ኾግል የተባለ ግለሰብ በሁለት ሰዎች ግድያ የእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበት ማረሚያ ነበር የሚገኘው። ግለሰቡ በጀርመን የቅርብ ዓመታት ታሪክ በርካታ ሰዎችን የገደለ ሰው እንደሆነ ይገመታል። • የባህል ሃኪሙ የተማመነበት ጥይት ማርከሻ ባለመስራቱ ሞተ • 'የሴቶች ቫያግራ' በአፍሪካዊቷ ሃገር እ.ኤ.አ ከ1999 እስከ 2005 ባለው ጊዜ የልብ መድኃኒት ከሚፈቀደው በላይ በመስጠት ነው ታካሚዎች እስከወዲያኛው እንዲያሸልቡ ያደረገው ተብሏል። ሰውዬው ግድያውን የፈፀመው ታካሚዎችን ለማዳን ነው ቢልም ታማሚዎቹ ከፈውስ ይልቅ ሞት እጣ ፈንታቸው ሆኗል። የፍርድ አደባባይ ላይ የቀረበው የ42 ዓመቱ ኾገል የታካሚዎችን ቤተሰቦች ይቅር በሉኝ ሲል ተማፅኗል። ''ባለፉት ዓመታት ላደረስኩባችሁ በደል በሙሉ ከልብ ይቅርታ እንድታደርጉልኝ እጠይቃለሁ'' ቢልም በርካቶች የአዞ እንባ ሲሉ ኮንነውታል። ቀድሞ ማረሚያ ቤት ከገባበት የሁለት ሰዎች ግድያ ጋር በድምሩ 100 ሰዎችን ገድሏል። ፖሊስ ግን ቁጥሩ ሳይልቅ አይቀርም የሚል ጥርጣሬ አለው። የኒየልስ ኾግል ሰዎችን የመግደል አባዜው እንዲገታ የሆነው እ.ኤ.አ 2005 ላይ በሃኪም ያልታዘዘ መድሃኒት ለታካሚው ሲሰጥ በመገኘቱ ነበር። በዚህም ተግባሩ በግድያ ሙከራ 7 ዓመታትን በእስር እንዲያሳልፍ ተፈርዶበታል። በሌሎች ተመሳሳይ ክሶች ደግሞ እ.ኤ.አ 2015 ላይ የእድሜ ልክ እስራት ተበይኖበት ነበር። ሰውዬው 55 ሰዎችን መግደሉን ፍርድ ቤት ፊት ቀርቦ አምኗል። ዜናውን የሰሙ ጀርመናዊያን እስካሁን ከድንጋጤ የወጡ አይመስሉም።
news-55541617
https://www.bbc.com/amharic/news-55541617
የአሜሪካ ምርጫ 2020፡ በጆርጂያ ምርጫ ዲሞክራቶችና ሪፐብሊካን አንገት ለአንገት ተናንቀዋል
ትናንት በተጀመረው የጆርጂያ ግዛት ለሕግ መወሰኛው ምክር ቤት ውክልና ምርጫ ዲሞክራቶችና ሪፐብሊካን ተናንቀዋል።
ዴሞክራቶቹ ጆን ኦሶፍ እና ራፋኤል ዋርኖክ እስከአሁን ያሉ ቆጠራዎች እንደሚያሳዩት የሁለቱ ፓርቲ ዕጩዎች በጣም በተቀራረበ ውጤት ላይ ናቸው። ሪፐብሊካን ፓርቲን የወከለችው ኬሊ ሎፍለር እንዲሁም ሌላኛው ዕጩ ዴቪድ ፐርዲዩ ከዲሞክራቶቹ ራፋኤል ዋርኖክና ጆን ኦሶፍ ጋር እልህ አስጨራሽ ትግል ላይ ናቸው። ተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ፓርቲያቸው የጆርጂያን ውክልና ማሸነፉ እጅግ ቁልፍ ጉዳይ ነው ሲሉ ተደምጠዋል። ተሰናባቹ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላቸው "ይህ ምርጫ የመጨረሻው የሪፐብሊካኖች ምሽግ ነው" ሲሉ መራጮች ነገሩን እንደዋዛ እንዳይመለከቱት ቀስቅሰዋል። የጆርጂያ ግዛት ምርጫ በዚህ ደረጃ ትኩረት ሊስብ የቻለው በሚቀጥሉት ዓመታት የአሜሪካንን የፖለቲካ መልክአ ምድር የመቀየር አቅም ስላለው ነው። በጆርጂያ የዲሞክራቶች ማሸነፍ በአሜሪካ የፖለቲካ፣ የፖሊሲና የአስተዳደር መዋቅር ውስጥ የጆ ባይደንና የቡድናቸውን ጉልበት የሚጨምር ይሆናል። ሪፐብሊካኑ ከሁለቱ እጩዎች አንዱን እንኳ ማሸነፍ ከቻሉ በሴኔት ጠባብ የበላይነትን ይጎናጸፋሉ። ሴኔቱ ላለፉት ዓመታት በሪፐብሊካን የበላይነት መቆየቱ ይታወሳል። ዲሞክራቶች ግን የጆርጂያን 2 እንደራሴዎች ምርጫ ማሸነፍ ከተቀናቃኞቻቸው ሪፐብሊካን ጋር እኩል 50 ወንበሮች እንዲያገኙ ያስችላቸዋል። ይህ እኩሌታውን ወንበር የማግኘቱ ነገር እንደ ድል የሚቆጠረው በካምላ ሐሪስ ምክንያት ነው። የሕግ መወሰኛው ምክር ቤት የሚመራው በምክትል ፕሬዝዳንት ስለሚሆን እኩል 50=50 እንደራሴዎች ድምጽ ሲሰጡ ምክር ቤቱን የሚመሩት ቀጣይ ምክትል ፕሬዝዳንት ካምላ ሐሪስ ስለሚሆኑ የእርሳቸው ድምጽ በሸንጎው ወሳኝ የመለያ ድምጽ ሆኖ እንዲቀጥል ያስችላል። በዚህም የተነሳ ዲሞክራቶች በጆርጂያ ሁለት እንደራሴዎች ቢያሸንፉላቸው ሴኔትን መቆጣጠር ያስችላቸዋል ማለት ነው። ናንሲ ፔሎሲ የሚመሩት የሕግ መምሪያው ምክር ቤት በዲሞክራቶች የበላይነት የተያዘ ሸንጎ ነው። አሁን ቆጠራ ላይ የሚገኘው የጆርጂያ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት የእንደራሴዎች ምርጫ ባለሀብቷ ሚስ ኬሊ ሎፍለር ከጥቁሩ የመብት ታጋይ ሚስተር ራፋኤል ዋርሎክ ጋር ተናንቀዋል። ሚስተር ፐርዲዩ ደግሞ ከሚስተር ኦሶፍ ጋር አንገት ለአንገት ተያይዘዋል። ሪፐብሊካኖቹ ኬሊ ሊዮፍለር እና ዴቪድ ፐርዱ በጆርጂያ 159 የምርጫ ወረዳዎች ሲኖሩ ከነዚህ ውስጥ እስከ አሁን 88 ከመቶው ድምጽ ተቆጥሯል። ሆኖም አሸናፊው አልተለየም። ለጊዜው ሁለቱ የሪፐብሊካን ዕጩዎች በትንሽ ቁጥር እየመሩ እንደሆነ የአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን እየዘገቡ ነው። ነገር ግን በሺህ የሚቆጠሩ ድምጾች ገና በመቆጠር ላይ ናቸው። በተለይም ከአትላንታ ከተማ ወጣ ብለው በሚገኙ ትንንሽ የምርጫ ጣቢያዎች በርካታ የዲሞክራቲክ ፓርቲ ደጋፊዎች በመኖራቸው የሪፐብሊካን ዕጩዎች መሪነት ሊቀለበስ ይችላል ተብሎ ተገምቷል። ከትናንት ማክሰኞ በፊት ብቻ 3 ሚሊዮን የሚሆኑ የጆርጂያ ነዋሪዎች ድምጽ ሰጥተዋል፤ ይህም ድምጹን ለመስጠት ከተመዘገበው ጠቅላላ ሕዝብ 40 ከመቶው ነው። በአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እንደታየው ከምርጫ ቀን በፊት ድምጽ የሚሰጡት በብዛት የዲሞክራቲክ ፓርቲ ደጋፊዎች ናቸው። በፕሬዝዳንትነት ውድድር መሸነፋቸውን ለመቀበል ዳገት የሆነባቸው ዶናልድ ትራምፕ በጆርጂያ የእንደራሴዎች ምርጫ ላይም እምነትን የሚሸረሽሩ መልዕክቶችን በትዊተር ሰሌዳቸው ላይ መጻፋቸውን ቀጥለውበታል። ከሰሞኑ ዶናልድ ትራምፕ የጆርጂያ ግዛት ምርጫ አስፈጻሚን በስልክ ድምጽ እንዲያጭበረብርላቸው ሲወተውቱ የሚያስደምጥ የተቀዳ የስልክ ልውውጥ በዋሺንግተን ፖስት ይፋ ተደርጎባቸው ትልቅ ውግዘትን ሲያስተናግዱ እንደነበር አይዘነጋም። የጆርጂያ ግዛት የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት የእንደራሴዎች ምርጫ አሁን እየተደረገ ያለው በድጋሚ ለ2ኛ ጊዜ ነው። ለመጀመርያ ጊዜ የተደረገው ባለፈው ኅዳር ከአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ጎን ለጎን ነበር። ድጋሚ ምርጫ የተጠራበት ምክንያት ደግሞ በጆርጂያ ግዛት የምርጫ ደንብ መሰረት ዕጩዎች ከ50 ከመቶ በታች ድምጽ ካገኙ ድጋሚ የውክልና ምርጫ እንዲደረግ ስለሚያዝ ነው። በአሜሪካ ፖለቲካዊ መዋቅርና አካሄድ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤትን በበላይነት መያዝ ለተመራጩ ፕሬዝዳንት ቁልፍ ጉዳይ ነው የሚሆነው። ምክንያቱም ተቀናቃኞቻቸው ለሚያወጡት ሕግና ፖሊሲዎች ተግባራዊ እንዳይሆኑ ማነቆ እንዳይሆኑባቸው ይረዳል። ለምሳሌ ሪፐብሊካኖች በጤና መድኅን፣ በአየር ንብረት ለውጥና በሌሎች ቁልፍ አገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚወጡ ሕጎችን በሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ድምጽ በመስጠት ውድቅ ሊያደርጓቸው ይችላሉ። ይህ ሸንጎ በዲሞክራቶች ከተያዘ ግን በቀላሉ አስፈላጊ ፖሊሲዎችንና ሕጎችን ለማሳለፍ እንዲሁም ለከፍተኛው ፍርድ ቤትና ለከፍተኛው የአገሪቱ ሥልጣን ካቢኔ ባይደን የሚያጯቸውን ሰዎች ያለ ድካም ለማጸደቅ ይረዳል። በጆርጂያ ግዛት የዲሞክራቲክ ፓርቲ እጩዎቹ ኦሶፍ እና ዋርኖክ ሁለቱም ቢያሸንፉ የሕግ መምሪያውን፣ የሕግ መወሰኛውና ነጩ ቤተመንግሥት ሙሉ በሙሉ በዲሞክራቶች ቁጥጥር ሥር እንዲወድቅ ያደርገዋል። ይህ ሆኖ የሚያውቀው በ2008 ባራክ ኦባማ ባሸነፉበት ዓመት ብቻ ነው። ጆርጂያ በአመዛኙ ለሪፐብሊካን የምታደላ ናት። አንድ ዲሞክራት የሕዝብ እንደራሴ ላለፉት 20 ዓመታት በጆርጂያ አሸንፎ አያውቅም። ጆ ባይደንም ግዛቷን ሲያሸንፉ ከ30 ዓመት በኋላ የመጀመርያው ሰው ናቸው። የዲሞክራቱ ዕጩ ራፋኤል ዋርኖክ የጆርጂያን ውክልና ካሸነፈ የመጀመርያው የግዛቲቱ ጥቁር የሴኔት ሸንጎ እንደራሴ በመሆን አዲስ ታሪክ ያስመዘግባል ተብሎ ይጠበቃል።
news-57251174
https://www.bbc.com/amharic/news-57251174
አሜሪካ የኮሮናቫይረስ መነሻ 'በግልጽ' እንዲመረመር ጠየቀች
የዓለም ጤና ድርጅት የኮቪድ-19 አመጣጥን በተመለከተ የሚያደርገው ቀጣይ ምርመራ 'ግልጽ' መሆኑን እንዲያረጋግጥ አሜሪካ ጠየቀች።
በሚኒስቴር ደረጃ በተደረገው የድርጅቱ ስብሰባ ላይ ንግግር ያደረጉት የአሜሪካው የጤና ሚንስትር ዣቪየር ቢሴራ ዓለም አቀፍ ባለሙያዎች የኮሮናቫይረስ ምንጭ ምን እንደሆነ እንዲገመግሙ ሊፈቀድላቸው ይገባል ብለዋል። የአሜሪካ የመገናኛ ብዙሃን ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት ቫይረሱ ቻይና ከሚገኝ ቤተ ሙከራ ስለማፈትለኩ የሚያሳዩ መረጃዎች እየጨመሩ ነው። ኮቪድ-19 በማዕከላዊ ሁቤይ አውራጃ በምትገኘው ውሃን ከተማ ለመጀመሪያ ጊዜ እአአ በ2019 ተገኝቷል። ከዚያን ወዲህ በዓለም ዙሪያ ከ167 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ ከ3.4 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ደግሞ ሕይወታቸው ማለፉ ሪፖርት ተደርጓል። በመጋቢት ወር የዓለም የጤና ድርጅት ከቻይናውያን ሳይንቲስቶች በኮቪድ-19 አመጣጥ ላይ በጋራ ባቀረቡት ዘገባ ቫይረሱ ከቤተ ሙከራ የመነሳት ዕድሉ "እጅግ በጣም የማይታሰብ ነው" ብለው ነበር። ሆኖም የዓለም ጤና ድርጅት ተጨማሪ ጥናት እንደሚያስፈልገው አስታውቋል። ነገር ግን ጥያቄዎች እንደቀጠሉ ናቸው። ከአሜሪካ የስለላ ምንጮች ጋር የሚያያዙ ሪፖርቶች እንደሚሉት ቻይና በማኅበረሰቡ ውስጥ አዲሱ በሽታ መኖሩን ይፋ ከማድረጓ ከሳምንታት በፊት የዉሃን ቫይረሶች ምርም ተቋም ሦስት አባላት ሆስፒታል ገብተው ነበር። ቤይጂንግ በተደጋጋሚ ሪፖርቶቹን ውድቅ ያደረገች ሲሆን ይልቅም ቫይረሱ ከአሜሪካ ቤተ ሙከራ የመጣ ሊሆን ይችላል ስትል ደጋግማ ትናገራለች። የአሜሪካ የጤና እና ሰብዓዊ አገልግሎት ሚንስትሩ ዣቪየር ቤሴራ፤ ማክሰኞ ለዓለም ጤና ድርጅት ባደረጉት ንግግር ቻይናን በስም አልጠቀሱም። ነገር ግን አሜሪካ ከቀጣዩ ምርመራ ጥብቅ አካሄድ እንደምትጠብቅ ግልጽ አድርገዋል። በድርጅቱ በተዘጋጀው የዓለም የጤና ስብሰባ ላይ ባደረጉት ንግግርም "የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ከሕይወታችን አንድ ዓመት መውሰድ ብቻ ሳይሆን በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳጥቶናል" ብለዋል። አክለውም "የቫይረሱን አመጣጥ የሚመለከተው የምዕራፍ 2 ጥናት ግልጽ፣ ሳይንስን መሠረት ያደረገ እና ለዓለም አቀፍ ባለሙያዎች የቫይረሱን ምንጭ እና የወረርሽኙን የመጀመሪያ ቀናት ሙሉ በሙሉ የመገምገም ነፃነት የሚሰጥ መሆን አለበት" ብለዋል። ዋይት ሐውስ ማክሰኞ ዕለት ከዓለም የጤና ድርጅት "ከጣልቃ ገብነት ወይም ከፖለቲካዊ ወገንተኝት የፀዳ የወረርሽኙን አመጣጥ በባለሙያ የሚመራ ግምገማ" እንደሚጠብቅ ገልጿል። የብሔራዊ የአለርጂ እና ተላላፊ በሽታዎች ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር እና የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የህክምና ዋና አማካሪ አንቶኒ ፋውቺ ቫይረሱ ከእንስሳት ወደ ሰው ተላልፏል ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል። በዚህ ወር ግን ኮቪድ-19 በተፈጥሯዊ መንገድ ስለመጀመሩ ሙሉ ለሙሉ እርግጠኛ አለመሆናቸውን አስታውቀዋል። የቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቫይረሱ መነሻ የዉሃን የቫይሮሎጂ ተቋም እንደሆነ ከተናገሩ በኋላ ቫይረሱ ከቤተ ሙከራ ነው የወጣው የሚለው የሴራ ትንተና ውድቅ ተደርጓል። አብዛኛዎቹ የአሜሪካ የመገናኛ ብዙሃን እንደዚህ ያሉትን ጥያቄዎች ሐሰት ሲሉ ገልጸዋል። ማክሰኞ ትራምፕ ለኒው ዮርክ ፖስት በተላኩት ኢሜል ባለቤትነቱን ለመውሰድ ፍላጎት አሳይተዋል። "ይህ ከመጀመሪያ ጀምሮ ለእኔ ግልጽ ነበር። ግን እንደተለመደው በጣም ብዙ ተነቅፌበታለሁ። አሁን ሁሉም 'እሱ ትክክል ነበር' ይላሉ" ብለዋል።
news-54308135
https://www.bbc.com/amharic/news-54308135
ቲክቶክ ላይ የተጣለውን እገዳ ፍርድ ቤት በጊዜያዊነት ሻረ
ቲክቶክ ከትናንት ምሽት ጀምሮ በአሜሪካ ሰዎች አውርደው እንይጠቀሙበት ገደብ ተጥሎበት ነበር።
ይሁን እንጂ የዋሽንግትን ዲሲ ዲስትሪክት ፍርድ ቤት ዳኛ ካርል ኒኮላስ እግዱን ላልተወሰነ ጊዜ ሽረውታል። ዳኛው ይህን ውሳኔ ባያስተላልፉ ኖሮ በአሜሪካ የሚገኙ አዲስ ተጠቃሚዎች ቲክቶክን ከአፕል እና ጉገል ፕለይ ስቶር ላይ አውርደው መጠቀም አይችሉም ነበር። መተግበሪያው በስልኮቻቸው ላይ ጭነው የሚገኙ ተጠቃሚዎችም መተግበሪያውን ማሻሻል አይችሉም ነበር ተብሏል። ዳኛ ካርል ኒኮላስ ትናንት ምሽት የአሜሪካ መንግሥት ያስተላለፈውን ውሳኔ የሻሩት ለ90 ደቂቃ የዘለቀ አቤቱታ ካደመጡ በኋላ ነው። ዳኛውን ይህን ውሳኔ እንዲወስኑ ያበቃቸው ምክንያት ግን ይፋ አልተደረገም። ቲክቶክ የፍርድ ቤት ውሳኔውን አድንቆ ምብቱን ለማስጠበቅ ጥረቱን እንደሚቀጥል አስታውቋል። "ፍርድ ቤቱ ካቀረብናቸው ሕጋዊ መከራከሪያዎች ጋር መስማማቱ አስደስቶናል" ብሏል ቲክቶክ ባወጣው የጽሑፍ መግለጫ። ቲክቶክ ከአፕል እና ጉግል ፕለይ ስቶር ላይ መተግበሪያውን ማንሳት ከአሜሪካ ሕገ-መንግሥት ጋር የሚቃረን ነው ብሎ አጥብቆ ሲከራከር ቆይቷል። ሰዎችም ቲክቶክን እንዳይቀላቀሉ መከልከሉ የሰዎች የመናገር መብት የሚጥስ ነው ይላል። የአሜሪካ መንግሥት ጠበቆች በበኩላቸው ቲክቶክ የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ጉዳይ አስፈጻሚ ነው ሲሉ ይከሱታል። ብሔራዊ ደህነት በአሁኑ ወቅት ቲክቶክ በአሜሪካ የሚኖረው የወደፊት እጣ ፈንታ ግልጽ አይደለም። በቻይናው ኩባንያ ባይቴንዳንስ ባለቤትንት የሚተዳደረው ቲክቶክ ለአሜሪካ ብሔራዊ ስጋት ነው የሚል ክስ ይቀርብበታል። የፕሬዝደንት ትራምፕ አስተዳደር ባይቴንዳንስ የአሜሪካውያንን ግላዊ መረጃ እየሰበሰበ ለቻይናው ኮሚኒስት ፓርቲ ያቀርባል ይላል። ባይቴንዳንስ በበኩሉ የመተግበሪያው ተጠቃሚ ሰዎች መረጃ በአሜሪካ እና በሲንጋፖር የሚከማች መሆኑን እና ለቻይና ሕጎች ተገዢ አልመሆኑን ይጠቅሳል። ቲክቶክ በአሜሪካ የሚኖረው እጣ ፈንታ ጥያቄ ውስጥ ወድቆ በሚገኘበት ወቅት፤ ቲክቶች ኦራክል እና ዎልማርት ለተሰኙት ሁለት ግዙፍ የአሜሪካ ጉባንያዎች የ20 በመቶ ድርሻውን ሊሸጥ መሆኑን አስታውቋል። ትራምፕ ግን ባይቴንዳንስ የበለይነትን የሚወስድበት ስምምነት በአስተዳደራቸው ውስጥ ተቀባይነት እንደሌላው ተናግረዋል።
news-54886519
https://www.bbc.com/amharic/news-54886519
ትግራይ፡ ከጦርነቱ ጋር ተያየዞ እየተሰራጩ ያሉ ሐሰተኛ ምሥሎችና መረጃዎች
ከጦርነቱ ጋር በተያያዘ በርካታ ሐሰተኛ ምስሎች በማኅበራዊ ሚዲያው ላይ እየተጋሩ ይገኛሉ።
የኢትዮጵያ መንግሥት በትግራይ ክልል ላይ በከፈተው ወታደራዊ ዘመቻና ይህንኑ ተከትሎ እየወጡ ባሉ ዘገባዎች በርካታ ሰዎች ሐሳዊ መረጃዎችን ያጋራሉ፥ ይጋራሉ። ማኀበራዊ ሚዲያውም በዚህ ተሞልቷል። የቢቢሲ አንዳንዶቹን ሐሳዊ ምሥሎች ነቅሶ አውጥቷቸዋል። ምሥሎቹ በጭራሽ ከዚህ ጦርነት ጋር ተያያዥ አይደሉም። አንዳንዶቹ እውነት እንዲመስሉ ሆን ተብለው በልዩ ጥበብ የተቀናበሩ መሆናቸውን ተገንዝቧል። ከእነዚህም መካከል በስፋት የተጋሩ የተጭበረበሩ 4 ፎቶዎች የሚከተሉት ናቸው። 1ኛ፦ የሚሳይል መቃወሚያ (ሚሳይል ዲፌንስ ሲስተም) በማኀበራዊ ሚዲያው በርካታ ሰዎች ሩሲያ ሰራሽ ኤስ-400 (S-400) የሚሳይል መቃወሚያ (ሚሳይል ዲፌንስ ሲስተም) ምሥልን አጋርተዋል። ምሥሉን የተጠቀሙት ደግሞ የትግራይ ክልል ከኢትዯጵያ መንግሥት የሚሰነዘርበትን የአየር ጥቃት የሚከላከልበት አድርገው ነው። ከዚህም ባሸገር የሩሲያ ሰራሽ እሳት (አረር) የሚተፋ መሣሪያ (flamethrower system) አገልግሎት ላይ አንደዋለ አድርገው አሰራጨተዋል፤ አጋርተዋል፤ ተጋርተዋል። ከእነዚህ ሐሳዊ ምሥሎች ስርም እንዲህ የሚል የምሥል ማስታወሻን አስፍረዋል፦ "ይህ የምትመለከቱት ፎቶ እንደሚያመለክተው ኢትዮጵያ እንደ አገር እንኳ እኛ በክልል ደረጃ ያለን የጦር መሣሪያ እንደሌላት ነው" ይላል። "ትግራዊያን ራሳቸውን ከአየር ጥቃት ለመከላከል እየተጠቀሙበት ነው" ሲልም ያክላል። ከመሣሪያው ፎቶ አጠገብ ደግሞ የትግራይ ልዩ ኃይል አባል የደንብ ልብስ የለበሰ የሚመስል ሰው ቆሞ ይታያል። ቢቢሲ እንዳረጋገጠው ይህ ምሥል ተቀናብሮ የተሠራ ነው። ከመሣሪያው ፎቶ ጋር የትግራይ ልዩ ኃይል አባል ፎቶ ሆን ተብሎ ተጨምሮበት የታተመ ነው። ለዚህም በቂ ማስረጃዎችን ማቅረብ ይቻላል። ከአካባቢው ካሉ የምሥል ጥላዎች በተቃራኒ የቅንብር ፎቶዎቹ ጥላ ወደ ተቃራኒ አቅጣጫ ማሳየቱ አንዱ ለፎቶ ሐሳዊነቱ ማሳያ ነው። አንዳንዶቹ የአካባቢው ምሥሎችም ከሌላው ጨለም ያሉ ናቸው። የብርሃን ምጣኒያቸው ልዩነትም ይህን ያሳብቃል። ከዚህም ባሸገር በአንደኛው ፎቶ ላይ ወታደሩ ከከባቢያዊ ምሥሎች በተለየ የሱ ፎቶ ምጣኔ የተለጠጠ ሆኖ ይታያል። የፎቶው ምንጭ በተደረገ የኦንላይን ፍተሻ ከየት እንደሆነ ተደርሶበታል። በደቡብ ሩሲያ አስትራካን ክልል ወታደሮች ልምምድ ከሚያደርጉበት ሥፍራ የተወሰደ ነው። በሩሲያ ቋንቋ የተደገፈ ቪዲዯ ይህንኑ የሚያረጋግጥ ነው። በመስከረም ወር የተወሰደው ይህ ተመሳሳይ ምሥል ተመሳሳይ የአየር መቃወሚያ አገልግሎት ላይ ሲውል ያሳያል። ኤስ-400 (S-400) የአየር መቃወሚያ ሲስተም እጅግ ዘመናዊ የሚባል ከምድር ወደ አየር ተምዘግዛጊ የሚሳይል ሲስተም ሲሆን ከሩሲያ ሌላ ጥቂት የውጭ አገራት እጅ ውስጥ ካልሆነ እንደ ኢትዯጵያ ያለ አገር በእጁ የሚያስገባው መሣሪያ አይደለም። ኢትዮጵያ ይህን መሣሪያ ከሸመቱ አገራት ተርታ የለችበትም። "ኢትዮጵያ ኤስ-300 ዝርያዎችንም ሆነ ኤስ-400 መቃወሚያዎች ገዝታ አታውቅም። የአካባቢው አገራትም ይህ የላቸውም" ይላሉ ጀስቲን ብሮንክ። ጀስቲን በሎንዶን የሮያል ዩናይትድ ሰርቪስ ኢንስቲትዩት ባልደረባ ናቸው። 2ኛ፦ ተመትቶ ወደቀ የተባለው ተዋጊ ጄት ብዙዎች የፌስቡክ ተጠቃሚዎች አንድ በትግራይ ክልል ተመትቶ ወደቀ የተባለ የጦር ጄት ምስል በስፋት ተጋርተውታል። አንደኛው የፌስቡክ ገጽ ላይ "የትግራይ ልዩ ኃይል ከሰማይ ጥቃት እየደረሰበት ነው፤ ልዩ ኃይሉ የኢትዮጵያን የጦር ጄት አውድሞታል። ሌሎች ልዩ ኮማንዶ አባላትንም ገድሏል፣ ጦርነቱም እንደቀጠለ ነው" ይላል። ነገር ግን የቢቢሲ ምርመራ እንደሚያስረዳው ይህ ምሥል ከቶውኑም ከኢትዮጵያ አይደለም። በሪቨርስ ኢሜጅ የፍለጋ ዘዴ ተመሳሳይ ምሥሎች ሌሎች ቦታዎች ተገኝተዋል። በሐምሌ 2018 በኢራኑ ፕሬስ ቲቪ ሪፖርት ላይ የሳኡዲ የጦር ጄት በየመን መመታቱን የሚያሳይ ምሥል እንዲሁም በግንቦት 2015 የትዊተር ሰሌዳ ምሥል ሚግ 25 ፕሌን በሊቢያ ዚንታን ከተማ አቅራቢያ ያሳያል። 3ኛ፦ የተጭበረበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን አደጋ ፎቶ አንዳንድ ሰዎች ከተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመንገደኞች አውሮፕላን ፎቶን ከሰሞኑ ጦርነት ጋር አስተሳስረው ሲጠቀሙበት ነበር። ይህም ከዚህ ቀደም መንገደኞችን ጭኖ ወደ ናይሮቢ ሲያቀና ቢሾፍቱ አቅራቢያ የተከሰከሰውንና ከ150 ሰዎች በላይ የሞቱበትን ቦይንግ 737 ማክስ 8 ምሥል ጋር የተያያዘ ነው። ይህን ምሥል የተጠቀሙበት ከጎረቤት አማራ ክልል የመጡ ወታደሮች ሬሳ በትግራይ የተገደሉ በማስመሰል ነው። ነገር ግን ሌሎች ይህ ምሥል ምንም ከዚህ ውጊያ ጋር የሚያይዘው ነገር እንደሌለ ተረድተው ይህንኑ አጋልጠዋል። በዚህም የተነሳ ብዙዎች ይህንን ምሥል እየሰረዙት ይገኛሉ። 4ኛ፦ ሚኒስትሯ ወታደሮችን ጭምብል አጥልቁ ብለዋል? የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ሪፓብሊክ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሚኒስትር የሆኑት ወ/ሮ ሊያ ታደሰ በትዊተር ሰሌዳቸው ላይ ወታደሮች የአፍ እና አፍንጫ ጭንብል እንዲያጠልቁ ሲያበረታቱ የሚያሳይ ምሥል (ስክሪንሾት) በማኅበራዊ ሚዲያ ተጋርቷል። ይህ ምሥል ሚኒስትሯ የኮቪድ ጥንቃቄ መመርያዎችን ለወታደሮች ያስተላለፉ ተደርጎ በማስመሰል ነው የተሰራጨው። ከዚህ ሐሳዊ ምሥል ጋር የተጻፈው መልእክት እንዲህ ይነበባል፡ "ርቀታችንን ጠብቀን ሳኒታይዘር እና ማስካችንን በጥንቃቄ በማድረግ ጦርነቱ በሰላም እንዲጠናቀቅ የበኩላችንን አስተዋጽኦ እንድናበረክት ለማሳሰብ እወዳለሁ።" ይህ የሚኒስትሯ የትዊተር ሰሌዳ መልዕክት የተፈበረከ እንጂ እውነት አይደለም። በሚኒስትሯ የትዊተር የግል አካውንት ሰሌዳ ዝርዝርም ላይ የሚገኝ አይደለም። ትክክለኛው የሚኒስትሯ የትዊተር መልዕክቶች ሚንስትሯ ትዊተር የሚጠቀሙት በአይፎን ስልክ እንጂ በአንድሮይድ ስልክ እንዳልሆነ ይጠቁማል።
news-55235542
https://www.bbc.com/amharic/news-55235542
ትግራይ፡ በመቀለ አይደር ሆስፒታል ያለው ሁኔታ አስጊ ደረጃ ላይ መድረሱ ተገለፀ
በመቀለ ከተማ የሚገኘው ዋነኛው የህክምና ተቋም አይደር ሪፈራል ሆስፒታል ሁኔታ አስጊ ደረጃ ላይ መድረሱን የዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ማህበር አስታወቀ።
ሆስፒታሉ መደበኛ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስፈልጉት የነበሩት አቅርቦቶች በከፍተኛ ደረጃ በመሟጠጣቸው ህክምና ለሚፈልጉ ሰዎች አገልግሎቱን ለመስጠት አዳጋች ደረጃ ላይ መድረሱ ተገልጿል። እስከ ትናንት ባለው መረጃ አይደር ሆስፒታል ድንገተኛና ህይወት አድን የሚባሉ ለምሳሌ ቀዶ ጥገናና የፅኑ ህሙማን ህክምና ለማቋረጥ መገደዱን የዓለም አቀፉ ቀይመስቀል የምሥራቅና የአፍሪካ ቀንድ ቀጠና ቃለ አቀባይ ክሪስታል ዌልስ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ቃለ አቀባይዋ ለዚህ እንደ ምክንያትነትም ያስቀመጡት መድኃኒቶች፣ የህክምና መገልገያ ቁሳቁሶችና ነዳጅ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በማለቃቸው ነው ብለዋል። የተፈጠረውንም ችግር ለመቅረፍም ከመንግሥት ባለስልጣናት ጋር እየተወያዩ መሆኑንም አስረድተዋል። "የህክምና ግብአቶችን ጨምሮ አስፈላጊ የሚባሉ ቁሳቁሶችን አዲስ አበባ ካለው ክምችታችን ወደ መቀለ እንዲሄድ ከመንግሥት ባለስልጣናት ጋር በመነጋገር ላይ ነን። ይህንም በቅርቡ እንደሚፈፀም ተስፋ አለን" በማለትም ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪ በመቀለ ከተማ ከፍተኛ የውሃ እጥረት እንዳጋጠመ ቀይ መስቀል በትዊተር ገፁ አስታውቋል። የዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ማኅበር ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበርም ጋር በመሆን ውሃ በከተማዋ ማከፋፈል መጀመራቸውን የገለፀው ድርጅቱ ይህም ሁኔታ ዋነኛው የውሃ አቅርቦት መስመር ሥራ እስኪጀመር ድረስ ይቀጥላል ብሏል። "በእርግጠኝነት ይሄ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጠውን የማኅበረሰቡን ህይወት የማዳን ተግባር ነው። ሁኔታውም አስጊ ደረጃ ላይ ነው" የሚል መልዕክት ድርጅቱ አስተላልፏል። ባለፈው ሳምንት ዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል በግጭቱ ሳቢያ ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች ህክምና እየሰጠው ያለው አይደር ሆስፒታል አሳሳቢ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝም ገልፆ ነበር። ድርጅቱ እንዳለው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር አምቡላንሶች በግጭቱ ሳቢያ የተጎዱና ሕይወታቸው ያለፈ ሰዎችን ወደ አይደር ሪፈራል ሆስፒታል እያጓጓዙ ነው። ሆስፒታሉን የጎበኙ የድርጅቱ ባልደረቦች "80 በመቶው ታካሚዎች በግጭቱ ጉዳት የደረሰባቸው ናቸው። ሌሎች ሕክምናዎች ቆመው ለድንገተኛ አደጋ ብቻ አገልግሎት እየተሰጠ ነው" በማለትም ገልፆ ነበር። የማኅበሩ የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ኃላፊ ማሪያ ሶልዳድ "ቁስል ለመስፋት የሚውል መገልገያ፣ ጸረ ተህዋሰ መድኃኒት፣ የህመም ማስታገሻ እና ሌሎችም መድኃኒቶች በአሳሳቢ ሁኔታ እያለቁ ነው" ሲሉ ተናግረዋል። የሞቱ ሰዎችን አስክሬን ማቆያ ፕላስቲኮች እየጨረሱ መሆኑንም ኃላፊዋ ተናግረዋል። ማኅበሩ ምን ያህል ሰዎች እንደተጎዱና እንደሞቱ ምንም መረጃ አልሰጠም። ተጎጂዎቹ ወታደሮች ይሁኑ ሲቪሎችም መሆናቸውም በወቅቱ አልተገለጸም። ከሰሞኑም በትግራይ ክልል በተለያዩ ቦታዎች በቀጠለው ውጊያ ምክንያት እርዳታ ለማቅረብ የሚያደርገው ጥረት እንደተስተጓጎለበትም የተባበሩት መንግሥታት ማስታወቁ የሚታወስ ነው። በክልሉ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች የሚያስፈልጋቸው የምግብና የመድኃኒት ክምችት እተሟጠጠ መሆኑም ተነግሯል። የተባበሩት መንግሥታት ባለስልጣናት ለፈረንሳይ ዜና ወኪል እንደተናገሩት፤ ምንም እንኳን ያልተቋረጠ የሰብአዊ እርዳታ ለማቅረብ ከመንግሥት ጋር ስምምነት ላይ ቢደረስም ወደ አካባቢዎቹ መድረስ እንዳልቻሉ ገልጸዋል። በትግራይ ክልል ውስጥ ጭምር ጥቂት የማይባሉ ሰዎች ሠብአዊ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሲሆን፤ ለዚህም ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ "ነጻ የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት መስመር" እንዲመቻች ጠይቀዋል። ባለፈው ሳምንት የኢትዮጵያ መንግሥት ባለስልጣናት ለእርዳታ አቅርቦት ሠራተኞች የሚያገለግል መተላለፊያ መስመር እንደሚከፍቱ አስታውቀው ነበር። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ፍሰት ቃል አቀባይ የሆኑት አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በበኩላቸው ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የተደረሰው ስምምነት የሚደረጉት የእርዳታ አቅርቦት ሥራዎች ሙሉ ለሙሉ በመንግሥት እንዲመራ ታሳቢ በማድረግ መሆኑን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ አስረድተዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በትናንትናው ዕለት 18 ሺህ 200 ኩንታል የምግብ አቅርቦት የጫኑ 44 ከባድ የጭነት መኪኖችም ሽረ ከተማ መግባታቸውን ሰላም ሚኒስቴር በትዊተር ገፁ አስታውቋል። ድጋፉ በሽረና በአቅራቢያው ባሉ ቦታዎችም እንደሚካሄድ መረጃው ጠቁሟል። መንግሥት በትግራይ ክልል ህግ የማስከበር ያለው ወታደራዊ ዘመቻ ከተጀመረባት ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም በክልሉ የመብራት የስልክና ኢንተርኔት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ መቋረጡ የሚታወስ ነው። ለሳምንት አገልግሎቱ ተቋርጦባቸው ከነበሩት አካባቢዎች መካከል አንዱ በሆነው በአላማጣ ሙሉ በሙሉ የቴሌኮም አገልግሎት መጀመሩንና ኢትዮ ቴሌኮም ከሰሞኑ አስታውቋል። ከዚህም በተጨማሪ በምዕራብ በኩል በዳንሻ፣ በተርካን፣ ሁመራ፣ ሽራሮ፣ ማይካድራና ማይፀብሪም አገልግሎቱ በከፊል እንደተጀመረ ተገልጿል። ወታደራዊ ግጭቱ ከተቀሰቀሰ በኋላ ተቋርጠው የሚገኙትን የኤሌክትሪክ ኃይልና የቴሌኮም አገልግሎቶች መልሶ ለማስቀጠል እየተሰራ መሆኑን አምባሳደር ሬድዋን ተናግረዋል። በዚህም መሠረት እነዚህን አገልግሎቶች መልሶ ለማስጀመር መቀለን፣ አክሱምና አዲግራትን ጨምሮ ወደ ሌሎች አካባቢዎች ቡድን መላኩን ጠቁመዋል።
news-49856008
https://www.bbc.com/amharic/news-49856008
ሁሌም አብሮን ያለው 'የመስቀል ወፍ'
የመስቀል ወፍ ለወራት ጠፍቶ ቆይቶ አዲስ ዓመት ሲገባ በተለይ ደግሞ መስከረም ሲጋመስ እንደሚከሰት በብዙዎች ዘንድ ይታመናል።
በአባባልም አንድ ሰው ለረጅም ጊዜ ጠፍቶ ቆይቶ ድንገት ሲከሰት ' ምነው የመስቀል ወፍ ሆንክ' ይባላል። ይህም ለረጅም ጊዜ ሳይታዩ ወይም ጠፍቶ ቆይቶ መታየትን ለማመልከት ማህበረሰቡ የሚጠቀምበት አባባል ነው። አእዋፋትን በቅርበት የሚያጠኑት አቶ ይልማ ደለለኝ ግን "እነዚህ የመስቀል ወፍ ተብለው የሚታወቁት አእዋፋት እንደሚባሉት ለረጅም ጊዜ ተሰውረው ቆይተው በመስቀል ሰሞን የሚከሰቱ ሳይሆኑ ዘወትር አብረውን የሚኖሩ ናቸው" ይላሉ። • ላሊበላ፡ የመፍትሔ ያለህ የሚለው ብሔራዊ ቅርስ እንደባለሙያው ከሆነ በኢትዮጵያ በመስቀል ወፍ ስም የሚታወቀው አንድ አይነት ዝርያ ያለው ወፍ ብቻ ሳይሆን ቁጥራቸው ከአራት በላይ የሆኑ የተለያዩ ዝርያ ያለቸው አእዋፋት እንደሆኑ ይናገራሉ። ለዚህም እንደምሳሌ የሚጠቅሱት ቁራ በሚል የሚጠሩ አእዋፋት ቢኖሩም በውስጣቸው የተለያዩ ዝርያዎች እንዳሉት ሁሉ የመስቀል ወፍ ውስጥም የተለያዩ የወፍ አይነቶች መኖራቸውን ነው። ከእነዚህ የመስቀል ወፎች መካከልም አዘውትረን የምናያቸው በቅርብ የምናውቃቸው ትንንሽዬዎቹና ድንቢጥ ተብለው የሚታወቁት አእዋፋትም በመስቀል ወፍነት ከሚጠሩት ውስጥ ይካተታሉ። • በወለደች በ30 ደቂቃ ውስጥ የተፈተነችው ተማሪ ስንት አስመዘገበች? እንደየቋንቋውና እንደየአካባቢው እነዚህ ወፎች የየራሳቸው ስያሜና መጠሪያ ሊኖራቸው እንደሚችል የሚጠቅሱት አቶ ይልማ የመስቀል ወፍ የሚለው ግን በርካታ አይነት ወፎች በውስጡ አካትተዋል ይላሉ። በእንግሊዝኛው እነዚህ አዕዋፋት ኢንዲጎ በርድስ፣ ዋይዳ፣ ቢሾፕ ወይም ዊዶ በርድ ተብለው እንደሚታወቁ በእነዚህ ውስጥም የተለያዩ ዝርያዎች መኖራቸውን ያስረዳሉ። ወፎቹ የሚታዩበት ጊዜ እነዚህ የመስቀል ወፍ ተብለው የሚጠሩት አእዋፋት በስፋት ታይተው በበርካቶች ዓይን ውስጥ የሚገቡት የክረምቱ ወራት አብቅቶ የበጋው ወቅት በሚጀምርበት ጊዜ ነው። አእዋፋቱ በአብዛኛው ዘር በል በመሆናቸው በዚህ ወቅት ደግሞ የሚደርሱ ሰብሎች በስፋት የሚገኙበትና ወፎቹም የሚራቡበት አመቺ ወቅት በመሆኑ በስፋት እንደሚታዩ አቶ ይልማ ይናገራሉ። እነዚህ አእዋፋት ባሕሪያቸው ከአንድ አካባቢ ወደሌላ አካባቢ ወቅቶችንና የአየር ሁኔታዎችን እየተከተሉ የሚሰደዱ በመሆናቸው በሌሎች ሃገራት ውስጥም ይገኛሉ። • የ40 ሺህ ብር ጉቦ አልቀበልም ያለው ፖሊስ ምን ይላል? አቶ ይልማ እንደሚሉት የተለያዩ አእዋፋት በተለያዩ ወቅቶች በተለይ ከሰሜናዊ ንፍቀ ክበብ ወደ አፍሪካ የሚመጡ ሲሆን በሌላ ጊዜ ደግሞ ወደዚያው የሚሄዱም አሉ። ወደኢትዮጵያ ወቅቶችን ጠብቀው የተለያዩ ወፎች ከመካከለኛው ምሥራቅ፣ ከስካንዴኔቪያን ሃገራት፣ ከምስራቅ አውሮፓ ሃገራት እንዲሁም ከሩሲያ የሚመጡ እንዳሉና እነዚህም በስደተኛ ወፍነት በባለሙያዎች እንደሚታወቁ ይገልጻሉ። የመስቀል ወፍ ተብለው የሚታወቁት አብዛኞቹ ግን በኢትዮጵያ ውስጥና በዙሪያዋ ባሉ ሃገራት ውስጥም እንደሚገኙ ይነገራል። ስለዚህ አእዋፋቱ ከኢትዮጵያ ባሻገር በኬንያ፣ በኡጋንዳና በታንዛንያ ውስጥ እንደሚገኙ ይጠቅሳሉ። አብረውን ያሉ ግን እንግዶች አቶ ይልማ እንደሚሉት በልምድ እንደምንለው የመስቀል ወፍ ለረጅም ጊዜ ጠፍተው ቆይተው በመስቀል ወቅት የሚከሰቱ እንዳልሆኑና በዙሪያችን አብረውን የሚኖሩ ናቸው። አእዋፋቱ አዲስ የሚሆኑብን አብረውን በዙሪያችን በሚቆዩበት ጊዜ የሚኖራቸው ገጽታ በመስከረም ወር ላይ በተፈጥሯዊ ሂደት ቀለማቸው ተለውጦ አይነ ግቡ ስለሚሆኑ የዚያ ወቅት አዲስ ክስተት እንደሆኑ ስለሚታሰብ ነው። "ለዚህም የአዕዋፋቱን ተፈጥሮ መረዳት ያስፈልጋል" የሚሉት አቶ ይልማ እነዚህ ወፎች ላይ ይህ ተፈጥሯዊ ለውጥ የሚታየው በዋናነት በመስከረም ወር ላይ የሚራቡበት ጊዜ በመሆኑ ነው። ይህ ደግሞ ከመስቀል በዓል ጋር ተቀራራቢ በመሆኑ የተለየ ገጽታን ተላብሰው እንዲታዩ ያደርጋቸዋል። የተፈጥሮ ሂደት በመስከረም ወር ላይ እንስት አእዋፋቱ እንቁላል ለመጣል የሚዘጋጁበት በመሆኑ ተባዕቱ ለእሱና ለተጣማሪው እንዲሁም ለሚፈለፈሉት አእዋፋት የሚያስፈልገውን ምግብና መጠለያን በሚያገኝበት ቦታ ላይ አንድ የተወሰነ አካባቢን ከልሎ ይይዛል። የመራቢያ ጊዜ በመሆኑ ወንዱ ይህንን በሚያደርግበት ወቅት የላባው መጠን ይረዝማል ቀለሙም ይቀየራል። ቀለሙ ደማቅና ውብ ስለሚሆን የሰዎችን አይን በመሳብ እንደ አዲስ ወፍ ሊታይ ይችላል ይላሉ አቶ ይልማ። ይህ ቀለምም ከሩቅ የሚታይ እንደሚሆን የሚናገሩት ባለሙያው በተለይ ፀሐይ በሚያገኘው ጊዜ በማንጸባረቅ ትኩረት የመሳብ አቅም አለው። በተጨማሪም ለውጡ የሚከሰተው በመራቢያ ጊዜ በመሆኑ እንስት ወፎችን ለመሳብና ለማማለል ከመጥቀሙ በተጨማሪ በአንጸባራቂ ውበቱ በቀላሉ ስለሚታይ፣ እንዲሁም በዚህ ላይ ዝማሬን ስለሚጨምር ሌሎች አእዋፋት የእርሱን አካባቢ እንዲርቁ ያስችለዋል። • "ለስልጣን ተብሎ የሚፈጠር ውህደትን ህወሓት ፈጽሞ አይቀበለውም" አቶ ጌታቸው ረዳ እንግዲህ ይህ የአእዋፋቱ ሥነ አካላዊ ለውጥ ነው በሌለው ጊዜ በአካባቢያችን ይኖሩ የነበሩትን እነዚህን አእዋፋት ለረጅም ጊዜ ጠፍተው በመስቀል ወቅት ብቅ ያሉ እንዲመስሉ ያደረጋቸው ይላሉ አእዋፋቱን በቅርበት የሚያጠኑት አቶ ይልማ ደለለኝ። ባለሙያው እንደሚሉት "በአካባቢያችን ያሉትን አእዋፋት በቅርበት የመከታተል ልምድ ስለሌለንና ክረምቱ አልፎ መስከረም አጋማሽ ላይ አእዋፋቱ ላባቸው በቀለማት አሸብርቆ በቀላሉ አይናችን ውስጥ ሲገቡ በዙሪያችን የነበሩት ወፎች ሳይሆኑ ጊዜ እየጠበቁ ብቅ የሚሉ ይመስሉናል።" ቀለማቸውና ዝማሬያቸው ከአዲስ ዓመትና ከመስከረም የፀሐይ ወቅት ጋር ተዳምሮ ከሚፈጠረው መልካም ስሜት ጋር የሁሉንም ቀልብ ስለሚስቡ ሁሉም ይመለከታቸዋል ሁሉም አዲስ ወፍ የመስቀል ወቅትን ጠብቆ እንደመጣ ይታመናል። የመስቀል ወፍ ብለን የምንጠራቸው አእዋፋት ከሌሎች ለየት የሚሉት ተባዕቶቹ በጣም ደማቅ ቀለም ሲኖራቸው፣ ሴቷ ግን ቡኒ ወይም ወደ ግራጫ የሚያደላ ቀለም ነው ያላት፤ በመራቢያ ወቅት ወንዱ ከበርካታ እንስት አእዋፋት ጋር የመሆን ባሕሪ እንዳለውም አቶ ይልማ ይጠቅሳሉ። ስለዚህ የአእዋፋት አጥኚ የሆኑት አቶ ይልማ ደለለኝ እንደሚሉት የመስቀል ወፎች ለረጅም ጊዜ ሳይታዩ ቆይተው መስከረም ወር ላይ የሚከሰቱ ዓመታዊ እንግዶች ሳይሆኑ አብረውን ቆይተው በተፈጥሮ ሂደት የላባቸው ቀለም የሚቀየር ቤተኛ አእዋፋት ናቸው ማለት ነው።
news-53364760
https://www.bbc.com/amharic/news-53364760
በሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በቀጥታ ተሳትፈዋል የተባሉ ግለሰቦችና ቡድን በዐቃቤ ሕግ ይፋ ተደረጉ
ድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ውስጥ እጃቸው አለበት ተብለው የተጠረጠሩ ሦስት ሰዎች መለያታቸውንና ሁለቱ በቁጥጥር ስር እንደዋሉ የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ይፋ አደረገ።
የአገሪቱ ጠቅላይ አቃቤ ዐቃቤ ሕግ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ዛሬ አርብ በሰጡት መግለጫ ላይ ላይ እንዳስታወቁት በግድያው ውስጥ በቀጥታ እጃቸው አለበት ያሏቸውን የሦስት ሰዎች ማንነትና ከግድያ ጀርባ አለ የተባለውን ቡድንም ገልጸዋል። በዚህም መሰረት በድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ውስጥ ቀጥተኛ ተሳታፊ ናቸው ብለው በስም የጠቀሷቸው ሦስት ግለሰቦችን፤ ጥላሁን ያሚ፣ አብዲ አለማየሁና ከበደ ገመቹ የተባሉ ናቸው። ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጓ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ እንዳሉት ሃጫሉ ሁንዴሳን በጥይት ተኩሶ የገደለው ጥላሁን ያሚ የተባለው ግለሰብ እንደሆነና ቀሪዎቹ ግለሰቦች አብዲ አለማየሁና ከበደ ገመቹ ደግሞ በግድያው ውስጥ ቀጥተኛ ተሳታፊ መሆናቸውን አመልክተዋል። ጨምረውም ሦስቱ ግለሰቦች የግድያውን ተልዕኮ ኦነግ-ሸኔ ከተባለው ቡድን ተቀብለው ማስፈጸማቸውን በመግለጽ፤ ቡድኑ ከግድያው ጀርባ እጁ እንዳለበት ዐቃቤ ሕጓ ተናግረዋል። ድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳን ተኩሶ የገደለው ጥላሁን ያሚ የተባለው ግለሰብ እንደሆነ ያመለከቱት ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጓ ተልዕኮውንም ኦነግ-ሸኔ እንደተቀበለና ድምጻዊውን ኢላማ ማድረግ ለምን እንዳስፈልገ በሰጠው ቃል መግለጹን ተናግረዋል። የግድያ ተልዕኮውን እንዲፈጽም ከሸኔ ቡድን በሰኔ ወር ውስጥ ሦስት ጊዜ ተገናኝተው እንዳሳመኑትና በመጀመሪያ ላይ ግድያው የሚፈጸምበት ግለሰብ ሃጫሉ መሆኑን እንዳልተነገረው ነገር ግን የተለያዩ የግድያ ኢላማ የሆኑ ሰዎች እንዳሉ እንደተነገረው ጠቅሰዋል። ግድያውንም መፈጸም አስፈላጊ የሆነው "መንግሥት በመዳከሙና ይህ ካልተፈጸመ የኦሮሞ ሕዝብ አደጋ ላይ ሊወድቅ እንደሚችል" በመግለጽ ለእራሱም ድርጊቱ ጥቅም እንደሚያስገኝለት ጥላሁን ያሚ ለፖሊስ በሰጠው ቃል ማመኑን ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ተናግረዋል። ከግድያው ጀርባ ሌሎች ቡድኖች ሊኖሩበት ስለሚችሉና የተደራጀና ሰፋ ያለ ትስስር ያለው በመሆኑ ምርመራው እንደሚቀጥልና ዘርዝር ሁኔታዎች በቀጣይነት ለሕዝቡ ይፋ እንደሚደረግ አመልክተዋል። በግድያው ውስጥ ቀጥተኛ ተሳትፎ እንዳላቸው ከተነገረው ግለሰቦች መካከል ጥላሁን ያሚና አብዲ አለማየሁ እንደተያዙ የተገለጸ ሲሆን ሦስተኛ ተጠርጣሪ ከበደ ገመቹ ግን አለመያዙ ተነግሯል። ከዐቃቤ ሕግ የቀረበው መረጃ እንደሚያመለክተው ከድምጻዊው ግድያ ጋር የቀጥታ ተሳትፎ ያላቸው ሦስቱ ግለሰቦች መለየታቸውን አመልክቶ የድርጊቱ አቀናባሪና አስፈጻሚ ደግሞ ኦነግ-ሸኔ የተባለው ቡድን መሆኑን ከተጠርጣሪዎቹ መታወቁ ተገልጿል። ሰኔ 22 ምሽት አዲስ አበባ ውስጥ በጥይት ተመትቶ የተገደለው የታዋቂው ድምጻዊ የሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በመላ አገሪቱ ድንጋጤን የፈጠረ ሲሆን ግድያውን ተከትሎም በአዲስ አበባ ከተማና በኦሮሚያ ክልል ውስጥ በተፈጠረ አለመረጋጋት ወደ 200 የሚጠጉ ሰዎች ህይወት ማለፉ ይታወቃል። ግድያውን ተከትሎ በድርጊቱ የተጠረጠሩ ከአስር በላይ ሰዎች በፖሊስ ተይዘው ምርምራ እየተደረገባቸው እንደሆነ አቃቤ ሕግ ተገልጾ ነበር።
news-52851207
https://www.bbc.com/amharic/news-52851207
ኮሮናቫይረስ ያቃወሰው የዓለም አቀፍ የትምህርት ዕድል
የ29 ዓመቱ ራውናቅ ሲንግ ከሁለት ዓመታት በፊት በቢዝነስ አስተዳደር ሁለተኛ ዲግሪውን ለመማር ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር መነጋገር ጀምሮ ነበር።
በአውሮፓውያኑ ጥር 2020 ላይ ደግሞ ካሊፎርኒያ ውስጥ የሚገኘው የባርክሌይስ ዩኒቨርስቲ ኮሊጅ ፤'ስ ስኩል ኦፍ ቢዝነስ’ ማመልከቻውን ተቀብሎ ተጨማሪ መረጃዎችን እንዲልክ ጠይቆት ነበር። "ዩኒቨርሲቲው ሙሉ በሙሉ ማመልከቻዬን እንዲቀበለኝ በማሰብ ለአምስት ዓመታት ስሰራበት የነበረውን መስሪያ ቤት ለቅቄ አዲስ የተመሰረተ ሌላ ንግድ ነክ ድርጅት ውስጥ ገባሁ።’’ ሲንግ ይህንን ያደረገው ለመማር ካሰበው ትምህርት ጋር የሚቀራረብ ሥራ ለመስራት ብሎ ነበር። ክፍያውም ቢሆን ከቀድሞው ጋር ሲነጻጸር እዚህ ግባ የሚባል አይደለም። ጥረቱ ውጤት አስገኝቶለት የባርክሌይ ዩኒቨርሲቲ ማመልከቻውን ሙሉ በሙሉ ተቀብሎት በመጪው መስከረም ትምህርት ለመጀመር በዝግጅት ላይ ነበር። ነገር ግን ሳይታሰብ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ዓለምን እንዳልነበረች አደረጋት። ሲንግ ብቻውን አይደለም፤ በኮሮናቫይረስ ምክንያት በተለያዩ የዓለማችን ትልልቅ ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር ዝግጅታቸውን አጠናቀው በመጠባበቅ ላይ ከነበሩ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሕንዳውያን መካከል ነው። ሁሉም ወደፊት ምን እንደሚሆን አያውቁም፤ ኮሮናቫይረስ መድኃኒት አልያም ክትባት ተገኝቶለት ነገሮች ወደቀድሞው ሁኔታቸው ይመለሱ አይመለሱ በእርግጠኝነት ማወቅ አይችሉም። ከቻይና በመቀጠል ሕንድ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ተማሪዎችን ወደ ውጭ አገራት በመላክ ትታወቃለች። እንደ አገሪቱ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት መረጃ ከሆነ በአውሮፓውያኑ 2019 ብቻ ከአንድ ሚሊየን በላይ ሕንዳውያን በተለያዩ የውጭ አገራት ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ነበር። በየዓመቱ ሰኔ እና ግንቦት በሕንድ የሚገኙ ተማሪዎች የትምህርት ቪዛ ለማግኘት በአገራት ቆንስላ እና ኤምባሲዎች በር ላይ ተሰብስበው ይታዩ ነበር። የዘንድሮው ሁኔታ ግን ከሌላ ጊዜው ለየት ያለ ይመስላል። ዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ ጋዜጠኝነት ለመማር ፍላጎት ያላት የ23 ዓመቷ ባሩዋ ሌላኛዋ ለትምህርት ወደ ውጭ ለመሄድ ተዘጋጅተው ከነበሩት ተማሪዎች መካከል ናት። "በአሁኑ ሰዓት ከፍተኛ ጭንቀትና ውጥረት ይታያል፤ ዓለም አቀፍ እንቅስቃሴ እንዴት እንደሚሆን አናውቅም፤ የትምህርት ቪዛ ይሰጠን አይሰጠን የምናውቀው ነገርም የለም" ብላለች። ኬምብሪጅ ዩኒቨርስቲ በትምህርት አሰጣጡ ላይ ለውጥ አድርጓል በርቀት መማር አንዳንድ በዩናይትድ ኪንግደም እና አሜሪካ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎች የመጀመሪያውን ሴሚስተር ወደሚቀጥለው ዓመት እንዲያስተላለፉ አማራጭ እያቀረቡ ይገኛሉ። ግሪንዊች የተባለው ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከፈለጉ የፊት ለፊት ለፊት ትምህርት ከኦንላየን ትምህርት እያሰባጠሩ መማር የሚችሉበትን ሁኔታ አመቻችቷል። ከሌሎች አገራት የሚመጡት ተማሪዎች ደግሞ የዘንድሮውን የመጀመሪያ ሴሚስተር ወደሚቀጥለው ዓመት ማስተላለፍ እንደሚችሉ አስታውቋል። ታዋቂው ኬምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ እስከሚቀጥለው ዓመት ድረስ ትምህርት በኦንላየን ይቀጥላል ብሏል። ሲንግ ለአንድ ዓመት ተኩል ያህል በጉጉት ሲጠብቀውና ሲዘጋጅለት የነበረው የውጭ አገር ትምህርት በኮሮናቫይረስ ምክንያት መሰናከሉ እንዳበሳጨው ይናገራል። ባሩዋ በበኩሏ "እኛ ዋነኛው በእነዚህ ዩኒቨርሲቲዎች የምናመለክትበት ምክንያት በካምፓሶች ተገኝተን መማር ስለምንፈልግ ነው። በእነዚህ አገራት ዕድል ካገኘን መስራትም እንፈልጋለን። ስለዚህ ባህሉንና አኗኗሩን በቦታው ሄደን ማየት አለብን። በኦንላየን የሚባለው ትምህርት ከምንም ቢሻልም ምርጫዬ ግን አይደለም" ትላለች። ወደ ውጭ አገራት ሄዶ መማር ቀላል የማይባል ወጪ አለው። ተማሪዎች ለተለያዩ ሥራ ማስኬጃዎች በዶላርና በፓውንድ ነው የሚከፍሉት። የቪዛ እና የአውሮፕላን ጉዞ ወጪም አለ። ስለዚህ ተማሪዎች በኦንላየን የሚማሩ ከሆነ የቪዛ እና የአውሮፕላን ቲኬት ወጪ ይቀርላቸዋል ማለት ነው። ነገር ግን አብዛኞቹ ከነወጪው በውጭ አገራት ሄዶ መማሩን ነው የሚመርጡት። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የሚነሳው ሌላ ጉዳይ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አጠናቀው ሲመረቁ በውጭ አገራት ሥራ እንደሚያገኙ ተስፋ ማድረጋቸው ነው። ከኮሮናቫይረስ ጋር በተያያዘ የበርካታ አገራት ኢኮኖሚ መድቀቁን ተከትሎ ደግሞ ከዚህ በፊት ሠራተኞችን በብዛት ይቀጥሩ የነበሩ ትልልቅ ድርጅቶች እንደውም ሠራተኞቻቸውን እየቀነሱ ነው። በሚቀጥሉት ዓመታት ነገሮች ቢስተካከሉ እንኳን እነዚህ ድርጅቶች በቶሎ ሠራተኞችን ይቀጥራሉ ብሎ ማሰብ ከባድ ነው። ያላቸውን ጥሪት አሟጠው በአሜሪካና በዩናይትድ ኪንግደም ዩኒቨርሲቲዎች ዲግሪያቸውን የሚይዙ ተማሪዎች ወደአገራቸው ተመልሰው መስራት አዋጪ አይሆንላቸውም። በዚህም ምክንያት በተማሩበት አገር ሥራ ማፈላለግን ይመርጣሉ። አሜሪካ ውስጥ ከተለያዩ አገራት የሚመጡ ዓለም አቀፍ ተማሪዎች ለኢኮኖሚው እስከ 45 ቢሊየን ዶላር ድረስ በየዓመቱ ያበረክታሉ። በእንግሊዝ ደግሞ ከእነዚሁ ተማሪዎች ብቻ ዩኒቨርሲቲዎች እስከ 7 ቢሊየን ፓውንድ ያገኛሉ። ስለዚህ በኮሮናቫይረስ ምክንያት ችግር ውስጥ የሚገቡት ተማሪዎች ብቻ ሳይሆኑ ከተማሪዎቹ ይህን ያህል ገንዘብ የሚሰበስቡት አገራትና የትምህርት ተቋማቱም ጭምር ናቸው። ሲንግ ምንም እንኳን የወደፊቱን መተንበይ ባይችልም በሚቀጥለው ዓመት ወደ አሜሪካ ሄዶ ትምህርቱን መከታተል እንደሚጀምር ተስፋ ያደርጋል።
news-55374923
https://www.bbc.com/amharic/news-55374923
ኮሮናቫይረስ፡ አሜሪካ የሞደርና ክትባት ጥቅም ላይ እንዲውል ፈቀደች
አሜሪካ ሞደርና ሰራሹ የኮቪድ ክትባት ጥቅም ላይ እንዲውል ፍቃድ ሰጠች።
ከአንድ ሳምንት በፊት የአሜሪካ የምግብ እና መድሃኒት ተቆጣጣሪ የፋይዘር/ባዮንቴክ ክትባት ጥቅም ላይ እንዲውል ፍቃድ መስጠቱ ይታወሳል። ይህን ተከትሎ የሞደርና ክትባት በአሜሪካ ጥቅም ላይ እንዲውል ፍቃድ ያገኘ ሁለተኛው ክትባት ሆኗል። ባለስልጣናቱ 200 ሚሊዮን የሞደርና ክትባትን ለመገዛት ከስምምነት የደረሱ ሲሆን ከዚህም መካከል 6 ሚሊዮን የሚሆነው ለስርጭት ዝግጁ መሆኑ ተነግሯል። አሜሪካ በቫይረሱ ክፉኛ ጉዳት ደረሰባት አገር ናት። እንደ ጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ አሃዝ ከሆነ 313 ሺህ 500 ሰዎችን በቫይረሱ ምክንያት ሕይወታቸውን ያጡ ሲሆን ከ17.5 ሚሊዮን ሕዝብ በላይ ደግሞ በቫይረሱ ተጠቅቷል። የምግብ እና መድሃኒት አስደተዳደር ኮሚሽነር ስቴፋን ሃን ሞደርና ሰራሹ ክትባት በአሜሪካ ጥቅም ላይ እንዲውል መፈቀዱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎችን ያጠቃውን በሽታ ለመቆጣጠር ትልቅና ጉልህ ሚና ይጫወታል ብለዋል። ሞደርና ሰራሹ ክትባት ጥቅም ላይ እንዲውል ፍቃድ ያገኘው የአሜሪካ መንግሥት የጤና አማካሪ ቡድን ክትባቱ ጥቅም ላይ እንዲውል ፍቃድ እንዲሰጠው ምክረ ሃሳባቸውን ካቀረቡ በኋላ ነበር። የሞደርና ክትባት ደህንነቱ የተጠበቀ እና 94 በመቶ ሰዎችን ከበሽታ የመከላከል አቅም ያለው እንደሆነ ተጠቁሟል። ፕሬዝደንት ትራምፕ በትዊተር ገጻቸው ላይ ክትባቱ ጥቅም ላይ እንዲውል ፍቃድ መሰጠቱን ገልጸው ክትባቱን የማከፋፈሉ ሥራ መጀመሩን አስታውቀዋል። “እንኳን ደስ ያላችሁ ሞደርና ክትባት አሁን ይገኛል!” ሲሉም ፕሬዝደንት ትራምፕ ጽፈዋል። የፊታችን ሰኞ ክትባት እንደሚወስዱ የተገለጸው ተመራጩ ፕሬዝደንት ጆ ባይደን የፋይዘር/ባዮንቴክ እና ሞደርና ክትባቶች ጥቅም ላይ መዋላቸው ወደፊት የተሻለ ሕይወት እንደሚጠብቀን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። የሞደርና ክትባት ከፋይዘር በምን ይለያል? ሁለቱ ክትባቶች የሚለዩበት አንድ መሠረታዊ ጉዳይ ሲከፋፈሉ እና ሲከማቹ የሚቆዩበት የቅዝቃዜ መጠን ነው። የአሜሪካው ፋይዘር እና የጀርመኑ ባዮንቴክ የሰሩት ክትባት ሲጓጓዝም ሆነ ሲከማች የቅዝቃዜ መጠኑ ከዜሮ በታች 75 ዲግሪ ሴንቲግሬድ በሆነ ስፍራ መቀመጥ ይኖርበታል። ይህም የሎጂስቲክ ስራውን ከባድ ያደርገዋል። በሌላ በኩል የሞደርና ክትባት መከማቸት እና መጓጓዝ ያለበት ከዜሮ በታች 20 ዲግ ሴንቲግሬድ በሆነ ቅዝቃዜ ውስጥ ነው። ሁለቱም ክትባቶች ሰዎች በቀናት ልዩነት ሁለት ጊዜ መውሰድ ይኖርባቸዋል። ሞደርና ሰራሹ ክትባት ሁለት ጊዜ መወሰድ ያለበት በ28 ቀናት ልዩነት ሲሆን የፋይዘር/ባዮንቴክ ክትባት ግን በ21 ቀናት ልዩነት ነው። ሞደርና ክትባቶቹን የሚያመርተው በአሜሪካ ማሳቹሴትስ ግዛት ነው። ፋይዘር በበኩሉ ክትባቱን የሚያመርተው ጀርመን እና ቤልጄም በሚገኙ ፋብሪካዎቹ ነው። ካናዳ፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ የአውሮፓ ሕብረት፣ ደቡብ ኮሪያ እና ጃፓን የሞደርና ክትባት ለዜጎቻቸው እንዲሰጡ ውሳኔ ባያስተላልፉም ክትባቱን ለመግዛት ግን ቀድመው ውል አስረዋል።
55147189
https://www.bbc.com/amharic/55147189
ሐሰተኛ በተባለው ምስል ሰበብ ቻይና አውስትራሊያን ይቅርታ አልጠይቅም አለች
ቻይና በመንግሥቷ ማኅበራዊ ሚዲያ ገጽ ላይ አንድ የአውስትራሊያ ወታደርን የሚያሳይ አሰቃቂ ምስል በማውጣቷ ይቅርታ እንደማትጠይቅ አስታውቃለች።
ቻይና ጨምራም አውስትራሊያ የተፈጸመውን ድርጊት እንደጦር ወንጀል እንዳይታይ ለማድረግ እየሞከረች ነው ስትልም ከሳለች። የአውስትራሊያ ወታደሮች ንጹሀን የአፍጋኒስታን ዜጎችን መግደላቸውን የሚጠቁም ሪፖርት ከወጣ በኋላ ምርመራ እየተደረገ ነው። የቻይና ከፍተኛ ባለሥልጣን በትዊተር ገጻቸው የአውስትራሊያ ወታደር የአፍጋኒስታን ታዳጊ በስለት ሲገድል የሚያሳይ ፎቶ መለጠፋቸውን ተከትሎ፤ የተቆጣችው አውስትራሊያ ቻይና ይቅርታ ትጠይቀኝ ብላ ነበር። በማኅበራዊ ገጾች ላይ የተሰራጨው ምሰል ሐሰተኛ ነው ስትልም አውስትራሊያ ከሳለች። ቻይና በበኩሏ፤ በሁለቱ አገራት መካከል ያለው ግንኙነት ለመሻከሩ ተጠያቂው አውስትራሊያ ናት ስትል ወንጅላለች። የአውስትራሊያ መከላከያ እአአ ከ2009 እስከ 2013፤ የአውስትራሊያ 25 ወታደሮች 39 የአፍጋን ንጹሀን ዜጎችን ስለመግደላቸው ተአማኒ መረጃ አግኝቻለሁ ብሏል። ቻይና ሪፖርቱ እንደወጣ አውስትራሊያን ኮንናለች። የውጪ ጉዳይ ሚንስትር ቃል አቀባዩ ሊጃን ዛሆ፤ የተቀናበረ የአውስትራሊያዊ ወታደር ምስል በትዊተር ገጻቸው ለጥፈዋል። ጠቅላይ ሚንስትር ስኮት ሞሪሰን "ቤጂይንግ አስቀያሚ ምስል በመለጠፏ ልታፍር ይገባል" በማለት ቻይና ይቅርታ ትጠይቀን ብለው ነበር። በአውስትራሊያ የቻይና ኤምባሲ ግን ይቅርታ ሳይጠይቅ እንዲያውም የጠቅላይ ሚንስትሩን ንግግር ተችቷል። "እኛን የሚወቅሱት የአውስትራሊያ ወታደሮች ከፈጸሙት አሰቃቂ ተግባር የሕዝቡን ትኩረት ለመውሰድ ነው" ሲል ኤምባሲው መግለጫ አውጥቷል። አውስትራሊያ እና ቻይና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ገብተዋል። አውስትራሊያ ስለኮቪድ-19 መነሻ ምርመራ ይደረግ ማለቷን ተከትሎ ደግሞ ነገሮች ተባብሰዋል። ባለፉት ጥቂት ወራት ሁለት በቻይና ይሠሩ የነበሩ የአውስትራሊያ መገናኛ ብዙሃን ባልደረቦች እንዲወጡ ተደርጓል። በቅርቡ ሁለት የአውስትራሊያ ምሁራን ቻይና ከመግባት ታግደዋል። ቻይና የአውስትራሊያ ወይን ላይ 200% ቀረጥ መጣሏ ደግሞ ወደ ምጣኔ ሀብት ሽኩቻ ከቷቸዋል።
56867424
https://www.bbc.com/amharic/56867424
የቀድሞው የማንቸስተር ተጫዋች ሪያን ጊግስ በሴቶች ላይ ጥቃት በመሰንዘር ተከሰሰ
የዌልስ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ እና የቀድሞው የማንቸስተር ዩናይትድ ተጫዋች ሪያን ጊግስ ሁለት ሴቶችን ላይ ጥቃት በመሰንዘር ክስ ተመሰረተበት።
ሪያን ጊግስ ጊግስ ባለፈው ኅዳር ወር ሳልፎርድ ውስጥ በ30 ዎቹ እና በ20ዎቹ የዕድሜ ክልል ውስጥ ባሉ ሴቶች ላይ ጥቃት በማድረስ ተከሷል። በመጪው ረቡዕ በማንቸስተር ዩናይትድና በሳልፎርድ ፍርድ ቤቶች እንዲቀርብ ዋስትና አስይዟል። የ47 ዓመቱ ሪያን ጊግስ በሰጠው መግለጫ በፍርድ ቤት ለቀረበበት ክስ ጥፋተኛ አይደለሁም ብሏል። "ለሕግ ሙሉ አክብሮት አለኝ። በተጨማሪም የቀረቡብኝን ውንጀላዎች ከባድነት ተረድቻለሁ" በማለት "ስሜን ለማጽዳት ዝግጁ ነኝ" ሲል ገልጿል። ዘ ግሬትማንቸስተር ፖሊስ እንደገለጸው የፖሊስ መኮንኖቹ ከወራት በፊት በዎርስሊ የተፈጠረን ረብሻ ተከትሎ ጥሪ ቀርቦላቸዋል። ፖሊስ እንዳመለከተው በ30 ዎቹ ዕድሜ ላይ ያለች አንዲት ሴት በቦታው ለደረሰባት ቀላል የአካል ጉዳት ህክምና አግኝታ ነበር። ጊግስ እአአ በታኅሣሥ 2017 እና በኅዳር 2020 መካከል ባሉት ጊዜ ውስጥ የማስገደድ ወይም ጫና የማሳደር ባህሪ በማሳየት ተከሷል። የዌልስ እግር ኳስ ማኅበር የአውሮፓ ዋንጫ ላይ የዌልስን ብሔራዊ ቡድንን የሚመራው ረዳት አስልጣኙ ሮበርት ፔጅ እንደሆነ አረጋግጧል። "ጉዳዩ በማኅበሩ እና በብሔራዊ ቡድኑ ላይ ስላለው ተፅዕኖ ለመወያየት" የቦርድ ስብሰባ እንደሚኖር ማኅበሩ ገልጿል። ጊግስ በመግለጫው አክሎም "ለሮበርት ፔጅ፣ ለአሰልጣኞቹ፣ ለተጫዋቾቹ እና ለደጋፊዎች በውድድሩ ስኬታማ እንዲሆኑ ምኞቴን ማስተላል እፈልጋለሁ" ብሏል። የቀድሞው የማንቸስተር ዩናይትድ የክንፍ መስመር ተጫዋች ጊግስ 24 ዓመት የተጫዋችነት ዘመኑ በሽልማቶች የተሞላ ነበር። እአአ በ2007 የቢቢሲን የዓመቱ ምርጥ የስፖርት ሰው አሸናፊም ሆኗል። ለዌልስ ብሔራዊ ቡድን በ64 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ ተጫውቷል። ጥር 2018 ደግሞ የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ሆኖ የተሾመ ሲሆን ቡድኑንም ለዩሮ 2020 አብቷል። ጊግስ በሊግ ሁለት ተወዳዳሪ የሆነው የሳልፎርድ ሲቲ ቡድን ባለቤቶች መካከል አንዱ ነው።
news-53414877
https://www.bbc.com/amharic/news-53414877
"ሴት ምንም ብትማር፤ ባል የሚስት ራስ ነው" ያሉት ፓስተር ክፉኛ እየተተቹ ነው
ናይጄሪያዊው ፓስተር ኢኖች አደቦይ ከሰሞኑ በትዊተር ላይ መነጋገሪያ ከሆኑ ሰዎች መካከል ግንባር ቀደም ሆነዋል። ባለፉት 24 ሰዓታት ብቻ ከ34 ሺህ ጊዜ በላይ በትዊተር ላይ ስማቸው ተጠቅሷል።
ናይጄሪያዊው ፓስተር ኢኖች አደቦይ ከባለቤታቸው ጋር ይህ የሆነው ፓስተሩ በኢንስታግራም ገፃቸው ላይ ከ50 ዓመታት በላይ የትዳር አጋራቸውን ፎሉኬ ልደትን በማስመልከት ያጋሩትን ፅሁፍ ተከትሎ ነው። ፅሁፉ "ዛሬ የባለቤቴ ልደት ነው፤ በተለይ አዲስ ተጋቢዎች ከእርሷ ብዙ ነገር ሊማሩ ይገባል። በጣም ጠንካራ ሴት ናት . . . " ሲል ይጀምራል። ከዚያም "እቅዷ ምንም ይሁን ምን ከእርሷ ጋር የሆነ ቦታ መሄድ እንደምፈልግ ከነገርኳት፤ ስትሰራው የነበረውን ነገር ሁሉ ጥላ ከእኔ ጋር ትመጣለች" ይላሉ። አገልጋዩ በዚህ ብቻ አላበቁም "ሴቶች ምንም ያክል ቢማሩና ስኬታማ ቢሆኑ ባል የሚስት ራስ ነው፤ በመሆኑም ሁል ጊዜም ባልን ማክበር አለባችሁ" ሲሉም ዘለግ ባለው ፅሁፋቸው አትተዋል። ይህንን ፅሁፍ በርካቶች የሴቶችን መብት የሚፃረር ሲሉ በትዊተር ላይ ተቃውመውታል። በርካታ ሰዎችም ቃላቶቹን 'አስቀያሚ' ሲሉ በመጥራት ፓስተሩ ላይ ትችት ሰንዝረዋል። የባለቤታቸውን የልደት በዓልም በእርሷ ላይ ያለውን የበላይነት ለማሳየት መጠቀም አልነበረባቸውም ሲሉም ወቅሰዋል። በሌላ በኩልም ለአምስት አስርት ዓመታት የዘለቀውን ትዳራቸውንም ያወደሱ አልጠፉም። አንዲት ሴት የሌላውን ሰው የበላይነት አውቃ ከተቀበለች ምን ችግር አለው፤ ሁለት ካፒቴኖች አንድ መርከብ አይዘውሩም ሲሉ ለጥንዶቹ ያላቸውን ክብር ገልፀዋል።
news-47689766
https://www.bbc.com/amharic/news-47689766
የኒውዚላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር አድናቆት እየጎረፈላቸው ነው
የኒውዚላንዱ ክራይስትቸርች ግድያን ተከትሎ የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ጃሲንዳ አርደን ለሁኔታው ምላሽ የሰጡበት መንገድና ለተጎጅዎች ያሳዩት ፍቅር የብዙዎችን ልብ የነካ ነበር።
በተለይም "አንድ ነን፤ እነሱ እኛ ናቸው" በሚል ያደረጉት ንግግርም እንዲሁ የብዙዎችን ስሜት ነክቷል። ጠቅላይ ሚኒስትሯ ለዚህ ፈታኝ ሁኔታ ምላሽ የሰጡበት መንገድና መላ ሃገሬውን በአንድ ላይ እንዲቆም ያደረጉበት ሁኔታ ዓለም አቀፍ አድናቆትን እያስገኘላቸው ነው። የቢቢሲ ከፍተኛ የፖለቲካ ተንታኝ የሆነው ሮቢን ለስቲግ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያሳዩት ብቃት ከብዙ ነገሮች አንፃር ቢታይ የላቀ የፖለቲካ ብቃት ውጤት እንደሆነ ይናገራሉ። "ያሉት ብቻም ሳይሆን ያሉበት መንገድም ጭምር ነው ቁም ነገሩ። አገሪቱ ምን እንደሚያስፈልጋት በመረዳትና ምሳሌ በሚሆን መልኩ ነው ምላሽ የሰጡት" ይላል። • በኒውዚላንዱ የመስጊዶች ጥቃት 50 ሰዎች ተገደሉ • "አደጋውን ስሰማ ክው ነበር ያልኩት..." አቶ ተወልደ ገ/ማርያም • አደጋው ስፍራ በየቀኑ እየሄዱ የሚያለቅሱት እናት ማን ናቸው? እንዲህ ያለ አገራዊ አደጋ ሲያጋጥም እንዲህ ባለና በተሳካ መንገድ ለገጠመው ችግር ምላሽ በመስጠት አገርን አንድ ላይ እንዲቆም ማስቻል እንደ ኒውዚላንዷ ጠቅላይ ሚኒስትር አርደርን ያሉ ጥቂቶች ብቻ የሚችሉት ነው። የዋሽንግተን ፖስቱ ኢሻን ታሮር "አርደርን የአገራቸው ሐዘንና ስቃይ ገፅታ ሆነዋል" በማለት የፃፈ ሲሆን ሌሎችም በርካታ ታዋቂ ዓለም ዓቀፍ መገናኛ ብዙኃን ጠቅላይ ሚኒስትሯን 'ድንቅ መሪ' በማለት ዘግበዋል። የቱርኩ ፕሬዘዳንት ጣይብ ኤርዶዋንም ጠቅላይ ሚኒስትሯ ያሳዩት ነገር ለዓለም ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ ተናግረዋል።
news-48381381
https://www.bbc.com/amharic/news-48381381
ኮንዶም መጠቀም እያቆምን ይሆን?
ሄይሊ የ24 ዓመት ወጣት ነች። ውጪ ከምታሳልፋቸው ምሽቶች በአንዱ ወደ መጠጥ ቤት ጎራ ብላ ነበር። ሌሊቱ ሊጋመስ ጥቂት ሲቀረው ከዚህ በፊት ትምህርት ቤት አብሯት የተማረ ሰው በድንገት አገኘች።
አብረው ሲጠጡ አምሽተው ተያይዘው ወደቤት ገቡ። ያለምንም መከላከያም ግብረ ስጋ ግንኙነት ፈጸሙ። ጠዋት ከእንቅልፌ ስነሳ ሰክሬ ባደረግኩት ነገር ባልደሰትም ይበልጥ ያሳሰበኝ ግን ያለኮንዶም ግብረ ስጋ ግንኙነት መፈጸሜ ነው ትላለች። ሄይሊ እንደምትለው፤ በግብረ ስጋ ግንኙት ወቅት ኮንዶም ስለመጠቀም ለማውራት ምቾት አይሰጣትም። ''አንዳንዴም መከላከያ ስለመጠቀም ባወራ ጓደኛዬ ምን ይለኛል? ብዬ እተወዋለው።'' • ስለኤች አይ ቪ /ኤድስ የሚነገሩ 8 የተሳሳቱ አመለካከቶች • የሚያስወርዱ ሴቶች ቁጥር ከሚወልዱ ሴቶች የሚበልጥባት ሀገር የእንግሊዙ የማኅበረሰብ ጤና ቢሮ በቅርቡ በሠራው ጥናት መሰረት፤ እድሜያቸው ከ16 እስከ 24 የሆኑ ወጣቶች አብዛኛዎቹ ከፍቅር ጓደኛቸው ጋር ያለኮንዶም የግብረ ስጋ ግንኙነት መፈጸማቸውን ተናግረዋል። ከአስር ወጣቶች አንዱ ደግሞ እስከነጭራሹ ኮንዶም ተጠቅመው አያውቁም። በአውሮፓውያኑ 2003 በተደረገ ጥናት መሰረት ግን እድሜያቸው ከ16 እስከ 24 ከሆኑ ወጣቶች መካከል 43 በመቶ የሚሆኑት ኮንዶም እንደሚጠቀሙ ተናግረው ነበር። ከአስር ዓመት በኋላ ያሉትን ቁጥሮች ያመሳከሩት ባለሙያዎች እንግሊዝ ውስጥ ብቻ ኮንዶም የሚጠቀሙ ሰዎች ቁጥር 36 በመቶ ቀንሷል ብለዋል። አሜሪካ ውስጥ ኮንዶም ይጠቀሙ የነበሩ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ቁጥር 2007 ላይ ከነበረው 62 በመቶ፤ በ2017 ወደ 54 በመቶ ቀንሷል። በዚሁ ጥናት ላይ እንደተጠቆመው፤ በግብረ ስጋ ግንኙት የሚተላለፉ በሽታዎች በብዛት የሚታዩት እድሜያቸው ከ16 እስከ 24 ዓመት ክልል ውስጥ ባሉ ወጣቶች መሆኑ ነገሮችን ይበልጥ አሳሳቢ አድርጓቸዋል። እንግሊዝ ውስጥ እንደ ጨብጥና ቂጥኝ ያሉ በግብረ ስጋ ግንኙነት የሚተላለፉ በሽታዎች የተያዙ ወጣቶች ቁጥር 2017 ላይ 20 በመቶ ጨምሮ የነበረ ሲሆን፤ ዋነኛ የመተላለፊያ መንገዱ ያለመከላከያ የሚደረግ የግብረ ስጋ ግንኙነት ነው። የኮንዶም ተወዳጅነት የቀነሰበት ዋነኛ ምክንያት ተብሎ የሚገመተው እርግዝናን የሚከላከሉ የተለያዩ አይነት ዘመን አመጣሽ አማራጮች ቁጥር መጨመር ነው። እንግሊዝ ውስጥ የእርግዝና መከላከያ መድሃኒቶችን የሚገዙ ወጣት ሴቶች ቁጥር ከምን ጊዜውም በላይ ጨምሯል። በ1950ዎቹ መተዋወቅ የጀመረው ኮንዶም ምንም አይነት ለውጥ ሳይደረግበት እስካሁን ድረስ አለ። ምናልባትም ከኮንዶም ጋር የተያያዙ ብዙ ለውጦች አለመኖራቸው ሰዎች በቀላሉ እንዲሰለቹትና ወደሌሎች አማራጮች እንዲሄዱ ሳያደርጋቸው እንዳልቀረ ይገመታል። ቤት ሠራሽ ኮንዶሞች ለመጀመሪያ ጊዜ አገልግሎት ላይ መዋል የጀመሩት በጥንት ዘመን ሲሆን፤ የዛኔ የነበሩ ሰዎች የበግ አልያም የፍየል አንጀትና የሽንት ፊኛ ይጠቀሙ ነበር። ከኤችአይቪ ጋር ተያይዘው የሚሠሩ ማስታወቂያዎችና መልእክቶች መቀነስ በራሱ ለኮንዶም ጥቅም ላይ አለመዋል የራሱን የሆነ አስተዋጽኦ አለው። በተለይ ደግሞ ባደጉት አገራት የኤችአይቪ ስርጭት እጅጉን የቀነሰና ጠፍቷል በሚባል ደረጃ መሆኑ በተለይ ወጣቶች ኮንዶም ለመጠቀም የሚያስገድዳቸው ነገር እንደሌለ እንዲያስቡ አድርጓቸዋል። • ወንዶች የማያወሯቸው አምስት አሳሳቢ ነገሮች • ኤምአርአይ ምንድነው? ከነዚህ ነገሮች ሁሉ ወጣ ስንል ደግሞ ያልተፈለገ እርግዝና መረሳት የለበትም። ብዙ ወጣት ሴቶች በግብረ ስጋ ግንኙነት ከሚተላለፉ በሽታዎች ይልቅ ያልተፈለገ እርግዝናን ይፈራሉ። ኮንዶም መጠቀም ካለባቸውም እርግዝናን ለመላከል እንደሆነ እያሰቡ ነው የሚያደርጉት። የሥነ ተዋልዶ ጤና ባለሙያ የሆኑት ፕሮፌሰር ሲንቲያ ግራሃም እንደሚሉት፤ በተለይ ደግሞ ወጣቶች ኮንዶም መጠቀም ከግብረ ስጋ ግንኙነት የሚገኘውን ደስታ ይቀንስብናል ብለው ያስባሉ። አብዛኛዎቹ ወንዶች ደግሞ ኮንዶም ሲጠቀሙ ብልታቸው በተገቢው ሁኔታ እንደማይነቃቃላቸው ይናገራሉ። ፕሮፌሰር ሲንቲያ ግን ወጣም ወረደም ኮንዶም መጠቀምን የመሰለ ቀላልና ጠቃሚ አማራጭ የለም ብለው ያምናሉ።
news-53935480
https://www.bbc.com/amharic/news-53935480
በህዳሴው ግድብ ድርድር ላይ ውጤት እየታየ መሆኑ ተገለጸ
በታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ በኢትዮጵያ፣ በሱዳንና በግብጽ መካከል ባለፉት ሁለት ሳምንታት ሲካሄድ በነበረው ድርድር ላይ የተወሰነ ውጤት መታየቱን የኢትዮጵያ ውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ገለጹ።
ሚኒስትሩ ስለሺ በቀለ (ዶ/ር) በትዊተር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት ላይ እንዳሉት ምንም እንኳን በድርድሩ ውጤቶች እየታዩ ቢሆንም የሚጠበቀውን ረቂቅ የስምምነት ሰነድ ለማቅረብ ፍጻሜ ላይ አልደረሰም ብለዋል። የ Twitter ይዘት መጨረሻ, 1 በተጨማሪም የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ላይ እንዳመለከተው የሦስቱ አገራት የውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች ትናንት አርብ ውይይት መካሄዱንና ባለፉት ቀናት በባለሙያዎች መካከል ሲካሄድ የነበረው ድርድር ውጤት ሪፖርት መቅረቡን ገልጿል። መግለጫው የኢትዮጵያ፣ የሱዳንና የግብጽ ባለሙያዎች ከነሐሴ 15/2012 ዓ.ም ጀምሮ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አሞላልና የውሃ አለቃቀቅ ደንብ ላይ ድርድር ሲያካሂዱ እንደነበር አመልክቶ፤ የዚሁ ውጤት ለአገራቱ ሚኒስትሮቹ ቀርቧል ብሏል። በሚኒስትሮቹ ስብሰባ ላይም የደቡብ አፍሪካ፣ የአውሮፓ ሕብረትና የአሜሪካ ተወካዮች ታዛቢ ሆነው የተገኙ ሲሆን የአፍሪካ ሕብረት የወከላቸው ባለሙያዎችም እንደነበሩ ተጠቅሷል። በአገራቱ መካከል እየተካሄደ ያለውን ድርድር ቀጣይ ሂደት በተመለከተም ለደቡብ አፍሪካ ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር እንዲሁም ለአፍሪካ ሕብረት የአስፈጻሚ ምክር ቤት ሊቀ መንበር በደብዳቤ ለማሳወቅ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። የዚህ የሦስቱ አገራት ድርድር ሂደት ከሱዳን በኩል የሚሰጥ ማረጋገጫን መሰረት በማድረግ መስከረም 04/2012 ዓ.ም እንደሚቀጥል ተገልጿል። ኢትዮጵያ ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት በቢሊየን ዶላሮች አውጥታ እየገነባችው ባለው የታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ በሦስቱ አገራት መካከል ሲካሄድ የነበረው ድርድር በተለያዩ ጊዜያት ለመካሄድ የቻለ ቢሆንም ያለመቋጫ ሲቋረጥ መቆየቱ ይታወሳል። በተለይ በግድቡ የውሃ አሞላልና አጠቃላይ የሥራ ሂደትን በተመለከተ አገራቱ ለመስማማት ተቸግረው የቆዩ ሲሆን በተለይ ኢትዮጵያ በዚህ ዓመት የግድቡን የመጀመሪያ ዙር የውሃ ሙሌት ለመጀመር የነበራትን ዕቅድ ካሳወቀች በኋላ ለመስማማት አዳጋች ሁኔታ ተፈጥሮ ነበር። ነገር ግን ኢትዮጵያ በነበረው ከፍተኛ የክረምት የዝናብ መጠን ታግዛ የመጀመሪያውን ዙር የውሃ ሙሌት ዕቅዷን ማሳካቷን ካሳወቀች በኋላ በቀሪ ጉዳዮች ላይ ድርድሩ ቀጥሏል።
news-53595983
https://www.bbc.com/amharic/news-53595983
በቤንሻንጉል ጉሙዙ ጥቃት የተጠረጠሩ 20 ታጣቂዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ
ሐምሌ 20/2012 በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ጉባ ወረዳ ጥቃት የፈጸሙ 20 ታጣቂዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ።
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግሥት ሠላም ግንባታ እና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱላዚዝ መሃመድ በተለይ ለቢቢሲ እንደገለጹት ግለሰቦቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ትናንት ነው። እንደ ምክትል ቢሮ ኃላፊው ከሆነ ታጣቂዎቹ ጥቃቱን ከመፈጸማቸው በፊት የመንግሥት የጸጥታ ኃይል እርምጃ እየወሰደባቸው ነበር። እርምጃውን ተከትሎ ተበታትነው በመንቀሳቀስ 13 ሰዎች ላይ ግድያ መፈጸማቸውን ጠቁመዋል። ከጥቃቱ በኋላ በተደረገ የክትትልና የቁጥጥር ሥራ 20 ሰዎች ትናንት መያዛቸውን አቶ አብዱላዚዝ አስታውቀዋል። ግለሰቦቹ ሲጠቀሙባቸው የነበሩ 12 መሣሪያዎችም መያዙን ነው የተናገሩት። በአሁኑ ጊዜ አካባቢው ወደ ሠላማዊ ሁኔታ መመለሱን የገለጹት አቶ አብዱላዚዝ የክልሉን የሠላም ግንባታ እና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊን እና የክልሉን የፖሊስ ኮሚሽነር ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮችም ወደ ቦታው በማቅናት ሕዝብን የማራጋጋት እና ችግር ፈጣሪዎቸን በቁጥጥር ስር እያዋሉ ነው ብለዋል። በጥቃቱ ላይ የተሳተፉ ሁሉም ተጠርጣሪዎች ስለመያዘቸው በተመለከተም፤ የምርመራ ቡድን ተቋቁሞ እየሠራ መሆኑን ተናግረው በውጤቱ መሠረት ተጨማሪ ሰዎች በቁጥጥር ስር ሊውሉ ይችላሉ ብለዋል። ቢቢሲ ያነጋገራቸው እና ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ አንድ የአካባቢው ነዋሪ በበኩላቸው፤ ጥቃቱን ተከትሎ ከሁለት ቀበሌዎች 200 የሚጠጉ ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው መሸሻቸውን አስታውቀዋል። ለተፈናቃዮቹ የአካባቢው ነዋሪ እና መንግሥት ድጋፍ እያደረገላቸው መሆኑንም ተናግረዋል። አንዳንድ ቤታቸው ዘግተው የሸሹ ግለሰቦች ቤት ተሰብሮ ንብረታቸው እንደተዘረፈም ግለሰቡ ጠቁመዋል። ከጥቃቱ ጋር በተያያዘም በቁጥጥር ስር የዋሉ ግለሰቦች መኖራቸውን እንደሰሙ የገለጹት ነዋሪው፤ ኅብረተሰቡ ውስጥ ሆነው ታጣቂዎችን ሲረዱ የነበሩ ሰዎች አሁንም አለመያዛቸውንም ገልጸዋል። በአሁኑ ጊዜ የጉባ ከተማ ሠላማዊ ቢሆንም ወጣ ብለው በሚገኙ ቀበሌዎች ስጋት መኖሩን አልሸሸጉም። ከፌደራል እና ከክልል የመጡ ከፍተኛ አመራሮች ትናንት እና ዛሬ ከአካባቢው የአገር ሽማግሌዎችና ወጣቶች ጋር በመወያየት ላይ ናቸውም ብለዋል። የቤንሻንልጉ ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሌ ሀሰን ትላንት ምሽት ከብሔራዊው ቴሌቪዝን ኢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ ድርጊቱን የፈጸሙት "በክልሉ እና ሱዳን ድንበር አካባቢ ስልጠና ሲወስዱ የነበሩ ቡድኖች ናቸው" ሲሉ ተናግረዋል። ቡድኖቹ ላይ ባለፉት ሁለት ሳምንታት በተከታታይ በተወሰዱ እርምጃዎች 12ቱ መገደላቸውን እና 30 የሚጠጉት መያዛቸውንም ጠቁመዋል። በአካባቢው ቀደም ሲል የተፈጠረውን ዓይነት ችግር ለመፍጠር ቢታቀድም ከአማራ ክልል እና ከፌደራል መንግሥት ጋር በመሆን እንደከዚህ ቀደሙ የማስተካከያ እርምጃ እንንደሚወሰድ ገልጸዋል። በአሁን ሰዓት አካባቢው ወደ ቀድሞ ሠላሙ መመለሱን ተናግረው የሕግ በላይነትን ለማስከበር በሚደረገው ሥራ ውስጥ ኃላፊነታቸውን ያልተወጡ አመራሮች ላይ ጭምር ሕጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ ይወሰዳል ብለዋል።
news-48987775
https://www.bbc.com/amharic/news-48987775
በባህር ዳሩ የተኩስ ልውውጥ ሦስት ሰዎች ሞቱ
ትናንት እሁድ ባህር ዳር ከተማ ውስጥ አባይ ማዶ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ በአካባቢው ሚሊሻዎችና ሲፈለግ በነበረ በአንድ ግለሰብ መካከል በተደረገ የተኩስ ለውውጥ የሦስት ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገለጸ።
ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ አንድ የባህር ዳር ፖሊስ አባል ለቢቢሲ እንደተናገሩት ከዚህ ቀደም ተፈጸሞ ከቆየ ሌላ የግድያ ወንጀል ጋር በተያያዘ ተጠርጥሮ ሲፈለግ የቆየ ነው የተባለን ግለሰብ ሊይዙ ሲከታተሉት የነበሩ የአካባቢው ሚሊሻዎች ላይ ተኩስ በመክፈቱ ነው ጉዳት የደረሰው። ሸፍቶ ነበር የተባለውን ግለሰብ ሲከታተሉ የቆዩት ሁለት የሚሊሻ አባላት፤ እሁድ ምሳ ሰዓት አካባቢ ተጠርጣሪው አለበት ወደተባለው ቤት በሄዱበት ጊዜ ተተኩሶባቸው ህይወታቸው ሲያልፍ ተጠርጣሪው በሌሎች የጸጥታ አባላት እንደተተኮሰበት ለማወቅ ተችሏል። • “የኢህአፓና መኢሶን ነገር አማራ ክልል ላይ ሊከሰት ይችላል ብዬ ነበር” • "መግለጫ የምንሰጠው ሰዎችም ልንታሰር እንችላለን" የአማራ ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በተኩስ ለውውጡ የተመቱት ሁለቱ ሚሊሻዎች ወዲያው ህይወታቸው ሲያልፍ ተፈላጊው ግለሰብ ግን ከቆሰለ በኋላ ወደ ሆስፒታል ተወስዶ ነው ህይወቱ ያለፈው ተብሏል። ከሳምንታት በፊት መንግሥት የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ነው ካለው ግድያ ጋር በተያያዘ ከገባችበት ድንጋጤ በማገገም ላይ በምትገኘው የባህር ዳር ከተማ ውስጥ እሁድ ዕለት ያጋጠመው የተኩስ ልውውጥ በነዋሪዎች ላይ ስጋትን ፈጥሮ ነበር። ስለክስተቱ ከክልሉም ሆነ ከባህር ዳር ከተማ የፖሊስ ኃላፊዎች ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ኃላፊዎቹ ስብሰባ ላይ በመሆናቸው ምክንያት አልተሳካም።
news-46111195
https://www.bbc.com/amharic/news-46111195
የማይናማር ግጭትን ለማባባስ ፌስቡክ ጥቅም ላይ መዋሉን ሪፖርት ጠቆመ
ፌስቡክ የማይናማር ግጭትን ለማባባስ ጥቅም ላይ እንዳይውል መከላከል ተስኖታል የሚለውን ሪፖርት ፌስቡክ እንደሚስማማበት ገልጸ።
የማይናማር ግጭትን ለማባባስ ፌስቡክ ጥቅም ላይ ውሏል በፌስቡክ የተዋቀረው ገለልተኛ ሪፖርት እንደጠቆመው በማይናማር የመብት ጥሰቶችን እና ግጭቶችን ለማባባስ ፌስቡክ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። የተባበሩት መንግሥታት፤ በሮሂንጋ ማኅበረሰብ ላይ የደረሰውን ጥቃትና የሰብዓዊ መብት ጥሰት "ለዘር ማጥፋት የቀረበ" ሲል ፈርጆት ነበር። • ቢቢሲ ከእንግሊዝ ቀጥሎ ግዙፉን ቢሮውን አስመረቀ • ዲሞክራቶች ቢያሸንፉ ትራምፕ ሊከሰሱ ይችላሉ? ፌስቡክ በማይናማር ከ18 ሚሊዮን በላይ ተጠቃሚዎች አሉት። ፌስቡክ ለበርካቶች ዋነኛው ወይም ብቸኛው የመረጃና የዜና ምንጭ ነው። የፌስቡክ አስተዳደሮች "በማይናማር እየገጠመን ያለውን ችግር ለመቅረፍ እየሠራን ነው። ሆኖም ብዙ ይቀረናል'' ብለዋል። ባለፈው ዓመት የሮሂንጋ ታጣቂዎች ፖሊስ ጣቢያዎች ላይ ጥቃት መሰንዘራቸውን ተከትሎ የሃገሪቱ ጦር ራክሂን በምትባለው ግዛት ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት ሰንዝሮ ነበር። በሺዎች የሚቆጠሩ ህይወታቸውን ሲያጡ፤ ከ700 ሺህ በላይ ሰዎች ደግሞ ወደ ጎረቤት ሃገር ባንግላዲሽ ተሰደዋል። በሮሂንጋውያን ላይ የአስገድዶ መድፈር፣ የእርሻ መሬትን መቃጠልና መሰል በደሎች ደርሶባቸዋል። • የጀማል ኻሾግጂን ግድያ ለመሸፈን 'ባለሙያዎች ተልከዋል' • በካሜሮን ከ70 በላይ ተማሪዎችና መምህራን ታገቱ ሮሂንጋውያን በማይናማር (በርማ ተብላ ትጠራ በነበረው) ሃገር ውስጥ እንደ ስደተኛ ይቆጠራሉ። በመንግሥት እና በተቀረው ሕዝብ ለበርካታ አስረት ዓመታት ተገልለዋል። ቢዝነስ ፎር ሶሻል ሪስፖንሲቢሊቲ (Business for Social Responsibility -BSR) ያቀረበው ባለ 62 ገጽ ገለልተኛ ሪፖርት ''በማይናማር ግጭትና ጥላቻን ማባባስ ለሚፈልጉ ቡድኖች ፌስቡክ መጠቀሚያ ሆኗል'' ይላል። ሪፖርቱ፤ ፌስቡክ የጥላቻ ንግግርን በተመለከተ ያለውን ፖሊሲ እንደገና ሊከልሰው ይገባል ሲልም አክሏል።
news-53216682
https://www.bbc.com/amharic/news-53216682
ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን የሙከራ በረራ ሊያደርግ ነው
ቦይንግ ማክስ 737 አውሮፕላን በዚህ ሳምንት ወሳኝ የፍተሻ በረራ ያደርጋል።
በዓለም ዙሪያ ያሉ ቦይንግ 737 አውሮፕላኖች እንዲቆሙ ተደርገዋል ምናልባትም ከዛሬ ሰኞ ጀምሮ ለሦስት ቀናት የሚቆየው የማክስ 737 የበረራ ሙከራ የፋይናንስና የመልካም ስም እጦት ለገጠመው ቦይንግ አንድ እመርታ ተደርጎ ተወስዷል። ሆኖም የዚህ የሙከራ በረራ ስኬታማነት ማክስ 737 ወደ ገበያ የመመለስ ዋስትናን አይሰጠውም። አውሮፕላኑ ወደ ገበያ ለመመለስ ገና በርካታ ሌሎች ፈተናዎችን ማለፍ ይጠበቅበታል። በቦይንግ ታሪክ ከፍተኛ ገበያ የነበረው ይህ የአውሮፕላን ሞዴል ሁለት ተከታታይ አደጋዎች ከደረሱበትና ተሳፋሪዎችም ከሞቱ በኋላ ከፍተኛ ችግር ውስጥ መግባቱ ይታወሳል። በኢንዶኒዢያና በኢትዮጵያ አየር መንገዶች አውሮፕላኖች ላይ የደረሱ አደጋዎችን ተከትሎ የዚህ የማክስ 737 አውሮፕላን ግዢን የፈጸሙ፣ አውሮፕላኑን ሲጠቀሙ የነበሩ፣ አውሮፕላኑን ለመረከብ ሲጠባበቁ የነበሩና አዲስ ግዥ ለማድረግ ቀብድ የከፈሉ ጭምር ምርቱ ላይ ጥያቄ በማንሳታቸው ቦይንግ ከፍተኛ ችግር ውስጥ ገብቶ ቆይቷል። ከዛሬ ጀምሮ ለሦስት ቀናት የሚደረጉ በበራዎች ስኬታማ ቢሆኑ እንኳ ማክስ 737 ወደ ሰማይ ለመመለስ ገና በርካታ የደኅንነትና የምህድስና ፍተሻዎችን ማድረግ ይጠበቅበታል። ይህም ሂደት ከዚህ በኋላ በርካታ ወራትን ሊወስድ ይችላል ተብሏል። የአቪየሽን ተቆጣጣሪዎች ማክስ 737 ቦይንግ አውሮፕላንን ከበረራ ያገዱት የዛሬ 15 ወር ገደማ ሲሆን ይህም የላየን እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላኖች ላይ በአምስት ወራት ልዩነት የደረሰውን እጅግ አሰቃቂ አደጋን ተከትሎ ነበር። በሁለቱ አደጋዎች በድምሩ 346 ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። የበረራ እግዱን ተከትሎ የ103 ዓመቱ አንጋፋው የቦይንግ ኩባንያ ላይ የካሳና የደኅንነት ጥያቄዎች አንዲነሱበት አድርጓል። በዚህም ሳቢያ ኩባንያው የከፋ ችግር ውስጥ ገብቶ እንደቆየ ይታወሳል። በተለይም የአሜሪካ የፌዴራል አቪየሽን አስተዳደር የአውሮፕላኖችን የበረራ ደኅንነት የሚፈትሽበት መንገድ ላይ በአጠቃላይ ጥያቄ እንዲነሳ ማድረጉ አይዘነጋም። ቦይንግ መጀመርያ አካባቢ የአደጋዎቹን ችግሮች ከራሱ ለማራቅ ከፍተኛ ሙከራ ሲያደርግ ቆይቶ ነበር። አደጋውን ተከትሎ የተደረጉ ጥብቅ ምርመራዎች ግን የማክስ 737 አውሮፕላኖች ስሪት ላይ የበረራ መቆጣጠሪያ ሥርዓታቸው አንዳች ግድፈት እንዳለበት የጠቆሙ ነበሩ። አሁን ማክስ 737 እነዚህ የበረራ መቆጣጠሪያ ሥርዓቶቹ ላይ ያደረገውን የምህንድስና ማሻሻያ ተከትሎ ማሻሻያው ምን ያህል ስኬታማ እንደሆነ ለማረጋገጥ መለስተኛ የበረራ ሙከራዎችን በዚያው በቦይንግ ማምረቻ ሲያትል አካባቢ እንደሚያደርግ ይጠበቃል። በዚህ የሙከራ በረራ አብራሪዎች ሆን ብለው የማክስ 737 ግድፈት ነበረበት የተባለውን የኤምካስ ሶፍትዌር ቁልፍን በመጫን አውሮፕላኑ ራሱን በራሱ መቆጣጠር ይችል እንደሆን ይመለከታሉ ተብሏል። የአሜሪካ የበረራ ተቆጣጣሪ መሥሪያ ቤት ለአሜሪካ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት በላከው ደብዳቤ ዛሬ ለሚጀመረው የሙከራ በረራው ይሁንታ መስጠቱን አስታውቋል። በዚህ ደብዳቤ ተቆጣጣሪ መሥሪያ ቤቱ እንደገለጸው የማክስ አውሮፕላኖች ወደ ሥራ እንዲመለሱ ገና ፈቃድ አልሰጠም። ይህ እንዲሆን ገና ብዙ የሙከራ ሂደቶች መታለፍ አለባቸው ብሏል። ይህ የሙከራ በረራ ይካሄዳል ተብሎ ቀጠሮ ተይዞለት የነበረው ባለፈው ዓመት ሲሆን በመሀሉ በአውሮፕላኑ ላይ አንዳች ሌላ ያልተጠበቀ ግድፈት በመገኘቱ ነበር በድጋሚ ሙከራው እንዲዘገይ የተደረገው። ይህ የሙከራ መለስተኛ በረራ ከተደረገ በኋላ በበራው ሂደት የተገኙ ቴክኒካዊ ነጥቦች አንድ በአንድ ይተነተናሉ፣ ይጠናሉ ተብሏል። ሙከራው እንከን አልባ ሆኖ ቢጠናቀቅ እንኳ ይህ አውሮፕላን በቀጥታ ወደ ሥራ ይመለሳል ማለት አይደለም። አብራሪዎችን ከአውሮፕላኑ ጋር እንዲዋሀዱ ለማድረግ የስልጠና መርሀ ግብር ይዘረጋል፣ የአውሮፓና የካናዳ የበረራ ተቆጣጣሪዎች ደግሞ ለዚህ አውሮፕላን እውቅናና ይሁንታ መስጠት ይኖርባቸዋል። የአውሮፓ አቪየሽን ኤጀንሲ እንዳስታወቀው ማክስ 737 ከአሜሪካ የአቪየሽን አስተዳደር የጤናማነት እውቅና ተሰጥቶት ወደ ሥራ መመለስ ይችላል የሚል ሰርተፍኬት ቢሰጠው እንኳ ይህ አውሮፕላን በአውሮፓ ሰማይ ላይ ለመብረር ያስችለዋል ማለት አይደለም ብሏል። ከአውሮፓ የኖርዌይ አየር መንገድ፣ ቲዩአይ እና አይስላንድ አየር መንገድ ይህን የቦይንግ ምርት የሆነውን ማክስ 737 አውሮፕላን ይጠቀሙ የነበሩ ሲሆን ሌሎች አገሮች ደግሞ አውሮፕላኑ እንዲመረትላቸው አዘው ሲጠባበቁ የነበሩ ናቸው።
news-52597597
https://www.bbc.com/amharic/news-52597597
የአቶ ለማ መገርሳ ድምጽ አየር ላይ እንዳይውል ተደርጓል ስለመባሉ ይጣራል ተባለ
የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ (ኦቢኤን) የቦርድ አባል እና የክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታቸው ባልቻ፤ የአቶ ለማ መገርሳ ድምጽ በኦቢኤን እንዳይተላለፍ ስለመደረጉ የሚያውቁት ነገር እንደሌለና ስለጉዳዩ እንደሚጣራ ተናገሩ።
ኃላፊው አቶ ጌታቸው ለቢቢሲ እንደገለጹት የማንም ድምጽ በድርጅቱ እንዳይተላለፍ የተወሰነ ነገር እንደሌለ አመልክተው ተከስቷል ስለተባለው ጉዳይም መጣራት እንደለበት ተናግረዋል። በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የሚተዳደረው የመገናኛ ብዙሃን ድርጅት የሆነው ኦቢኤን ላይ የክልሉ የቀድሞ ፕሬዝዳንትና የወቅቱ የአገሪቱ የመከላከያ ሚንስትር የሆኑትን የአቶ ለማ መገርሳ ድምጽ እንዳይተላላፍ ተደርጓል በሚል የድርጅቱ ጋዜጠኞች ቅሬታ ማሰማታቸውን መዘገባችን ይታወሳል። ቢቢሲ ከድርጅቱ ጋዜጠኞች ባገኘው መረጃ መሰረት ረቡዕ እለት በአዳማ ከተማ በተፈጸመው የታዋቂው ባለሃብት በአቶ ከቢር ሁሴን ቀብር ላይ አቶ ለማ ተገኝተው ያደረጉት ንግግር 'ከላይ በመጣ ትዕዛዝ' በሚል በድርጅቱ ኃላፊዎች ድምጻቸው አየር ላይ እንዳይውል መደረጉ ተገልጿል። ይህንንም ተከትሎ ቢቢሲ በጉዳዩ ላይ የድርጅቱ ዳይሬክተር ከሆኑት አቶ ዝናቡ አስራት እና ምክትላቸውን አቶ ቦጃ ገቢሳ ምላሽ ለማግኘት በስልክ ተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርግም የሁለቱም የእጅ ስልክ ባለመነሳቱ ሳይሳካ ቀርቷል። ከዚህም በኋላ የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ (ኦቢኤን) የቦርድ አባል እና የክልሉ ኮሚኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታቸው ባልቻ "ይህ ሊሆን የሚችልበት ምንም መመዘኛ የለም" ሲሉ ለቢቢሲ የተናገሩ ሲሆን ጨምረውም "ይህ ጉዳይ መጣራት አለበት" ብለዋል። ከዚህ ባሻገርም ስለክስተቱ ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት የኦቢኤን ቦርድ ሰብሳቢ እና የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ ዋና ጸሐፊ አቶ አዲሱ አረጋን ለማግኘት ያደረግነው ጥረትም ሳይሳካ ቀርቷል። አቶ ጌታቸው ከድርጅቱ እና ከቦርድ አባላት ጋር የዘወትር ሥራዎች እየተከናወኑ መሆን አስታውሰው፤ ይህ ጉዳይ ግን በቦርዱ ስብሰባ ላይ እስካሁን አለመነሳቱን ለቢቢሲ ተናግረዋል። "ሙያው በሚፈቅደው መሠረት አርትኦት ይሰራል እንጂ የዚህ ሰው ድምጽ ይተላለፍ' የዚህ ይከልከል የሚል ሰው የለም" ብለዋል። የአቶ ለማ ድምጽ አየር ላይ እንዳይውል እንዴት ተከለከለ? የአቶ ለማ ንግግርን የያዘው የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ዘገባ ረቡዕ ዕለት ምሳ ሰዓት ላይ ስድስት እና ሰባት ሰዓት ላይ እንደሚሰራጭ በዕለቱ የጣቢያው መርሃ ግብር ላይ ተይዞ የነበረ ቢሆንም፤ ዜናው ወደ ምሽት እንዲተላለፍ መወሰኑን የድርጅቱ ሠራተኞች ለቢቢሲ ተናግረዋል። ነገር ግን በዕለቱ ምሽት 12 እና 1 ሰዓት ዜናዎች ላይ ከዘገባው የአቶ ለማ መገርሳ ድምጽ እንዲወጣ ተደርጎ፤ የክልሉ የፕሬዝደንት አቶ ሽመልስ አብዲሳን ድምጽ በማካተት እንዲተላለፍ ተደርጓል። አቶ ለማ በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ ያሉት ምን ነበር? በታዋቂው ባለሃብት የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ከተገኙት የክልሉና የፌደራል መንግሥቱ ባለስልጣናት አንዱ የነበሩት አቶ ለማ መገርሳ በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ ንግግር ለማድረግ ወደ መድረክ ሲያመሩ ለቀብር ከታደመው ሕዝብ ከፍ ባለ ጭብጨባ ነበር የተቀበላቸው። የአቶ ለማ ንግግር ትኩረቱ የነበረው ሟቹ የንግድ ሰው በሁሉም ዘንድ ያላቸውን ታዋቂነትና ያበረከቱትን አስተዋጽኦ የሚዘክር እንደነበር በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ የታደሙ ሰዎች ለቢቢሲ ገልጸዋል። አቶ ለማ ሟች ከቢር ሁሴንን እንደ አባትና ጓደኛቸው ይመለከቷቸው እንደነበር በማስታወስ "ትልቅ ትንሹ የሚያውቀው ሰው ነበረ። በንግድ ብቻ ሳይሆን ለወገኑ የሚጨነቅ ለኦሮሞ ብሎ ንብረቱን ያጣ ሰው ነው። ገንዘብ ቢኖረውም አንድም ቀን ለራሱ ጊዜ ያልነበረው ሰው ነበር። ኦሮሞ ዛሬ ትልቅ ሰው ነው ያጣው" የሚል ይዘት ያለው ንግግር ነበር ያደረጉት።
news-46176341
https://www.bbc.com/amharic/news-46176341
በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያገረሸው የኢቦላ ወረርሽኝ በታሪኳ ታይቶ አይታወቅም
በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በቅርቡ ያገረሸው ኢቦላ ወረርሽኝ በአገሪቷ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና አሰከፊ ነው ሲሉ የአገሪቷ ጤና ጥበቃ ሚንስትር አስታውቀዋል።
የህክምና ባለሙያዎች የኢቦላ ሥርጭትን ለመግታት ክትባት እየሰጡ ነው። ከባለፉት አራት ወራት ጀምሮ ቢያንስ 200 ሰዎች በወረርሽኙ ሕይወታቸው ሲያልፍ ወደ 300 የሚሆኑ የተጠረጠሩ ህመምተኞች ተገኝተዋል። ወረርሽኙን ለመግታት የተለያዩ ጥረቶች እየተደረገ ሲሆን እስካሁን 25 ሺህ ለሚሆኑ ሰዎች ክትባት ተሰጥቷል። ይሁን እንጂ የአገሪቱ ፖለቲካዊ አለመረጋጋትና የጤና ባለሙያዎች ላይ በተለያየ ጊዜ ጥቃት በመድረሱ ለዓመታት ወረርሽኙን ለመቆጣጠር የሚደረገውን ጥረት ተፈታትኖታል። • ኢቦላ በኮንጎ እየተዛመተ ነው • ኢቦላ ለምን አገረሸ? • "ቀጣዩን ምርጫ ከዳር ሆኜ ባልታዘብም ተወዳዳሪ ግን አልሆንም" ብርቱካን ሚደቅሳ የጤና ጥበቃው ሚንስትር ኦሊ ኢሉንጋ በዚህ ሰዓት 319 በበሽታው የተያዙና 198 ሞት መመዝገቡን ገልፀዋል። "ቤተሰቦቻቸውን ላጡ፣ ያለ አሳዳጊ ለቀሩ ሕፃናትና ለተበተኑ የቤተሰብ አባላት የተሰማኝን ሀዘን እገልፃለሁ ፤ መፅናናትን እመኛለሁ፤ በፀሎትም አስባቸዋለሁ" ሲሉም ተናግረዋል። ባለስልጣኑ እንደተናገሩት ግማሽ ያህሉ ተጎጂዎች 800 ሺህ ህዝብ ከሚኖርባት የሰሜናዊ ኪቩ ግዛት ቤኒ ነዋሪዎች ናቸው። አገሪቱ በአውሮፓውያኑ 1976 ካጋጠማት ስሙ በውል ካልታወቀው ወረርሽኝ በኋላ የአሁኑ በጣም አሰቃቂውና አስፈሪው ነው። ኢቦላ ከሰውነት ከሚወጣ ፈሻሽ እና ሌሎች ኢንፌክሽኖች አማካኝነት ይተላለፋል፤ ምልክቱም ጉንፋን መሳይ ህመም፣ ማስታወክ፣ ተቅማጥ፣ ውስጣዊና ውጫዊ መድማት ናቸው።
44027224
https://www.bbc.com/amharic/44027224
ፑቲን ለ4ኛ ጊዜ ዛሬ ቃለ መሐላ ፈጸሙ
ተቃዋሚዎቻቸው ከ"ዛር" የአፄዎቹ ንጉሣዊ አገዛዝ ጋር የሚያመሳስሏቸው ቭላድሚር ፑቲን 18 ዓመታትን በሥልጣን ላይ ቆይተዋል። ዛሬ ለአራተኛ ጊዜ አገሪቱን በፕሬዝዳንትነት ለመምራት ቃለ-መሐላ ፈጽመዋ።
ከትናትን በስቲያ የእርሳቸውን ወደ ሥልጣን መምጣት ለመቃወም አደባባይ የወጡ ሩሲያዊያን ከፖሊስ ጋር ተጋጭተዋል። ዛሬም ቃለ-መሐላ በሚፈጽሙበት ዕለት አንዳች ተቃውሞ ይከሰታል የሚል ፍርሃት በመኖሩ ጠበቅ ያለ የጸጥታ ጥበቃ እንዳለ እየተዘገበ ነው። ፖሊስ ቅዳሜ ዕለት በተጠራው "ሕገ-ወጥ" ተቃውሞ ተሳትፋችኋል ያላቸውን ከአንድ ሺህ በላይ ዜጎች በቁጥጥር ሥር አውሏል። ተቃዋሚዎቹ በ19 ከተሞች ነበር ድምጻቸውን ያሰሙት። ፑቲን በድጋሚ የተመረጡት የ76 በመቶ የመራጩን ይሁንታ በመግኘት ነው። ሆኖም የምርጫው ተአማኒነት ጥያቄ ውስጥ የሚገባ ስለመሆኑ ታዛቢዎች በስፋት ይናገራሉ። እንደ ታዛቢዎቹ አመለካከት ከሆነ የአገሪቱ ሁነኛው የተቃዋሚ መሪ አሌክሲ ናቫልኒ በምርጫው እንዳይሳተፉ አሻጥር ተሰርቶባቸው ነበር። የተቃማዊው መሪ ናቫልኒ በቅዳሜው የተቃውሞ ሰልፍ በመሳተፋቸው በአሁነ ሰዓት በፖሊስ ቁጥጥር ውለዋል። የተቃውሞ ሰልፉ "ፑቲን ዳግማዊ አጼ ሊሆን አይገባውም" በሚል መሪ መፈክር የተካሄደ ነው። ፑቲን ለመጀመርያ ጊዜ ወደ ሥልጣን የመጡት ከዛሬ 18 ዓመት በፊት ነበር። በ2008 ከፕሬዝዳንትነት ሥልጣን ለይስሙላ ዞር በማለት በጠቅላይ ሚኒስትርነት ቆይተው እንደልነባቸው የሚዘውሯቸውን ዲሜትሪ ሜድቬዴቭን ወደ መንበሩ አምጥተዋቸው ነበር። ይህን ያደረጉት ከ2 ጊዜ በላይ በፕሬዝዳንትነት መቆየት በሕገ-መንግሥቱ ባለመፈቀዱ ነበር። በ2012 በድጋሚ ወደ ሥልጣን ሲመጡ ግን ሕገ-መንግሥቱን በማሻሻል የሥልጣን ቆይታቸውን ወደ 6 ዓመታት ከፍ በማድረግ በአዲስ መልክ ሩሲያ መምራት ጀምረዋል። ፑቲን እስከ 2024 በስልጣን ላይ የሚቆዩ ከሆነ ለሩብ ምዕተ-ዓመት ሩሲያን ይመራሉ ማለት ነው። ይህ ከጆሴፍ ስታሊን ቀጥሎ ከንጉሣዊያኑ የአፄዎች አገዛዝ ውጪ ረዥሙ የሥልጣን ቆይታ ይሆናል ማለት ነው። አምባገነኑ መሪ ጆሴፍ ስታሊን ለ31 ዓመታት አገሪቱን መምራቱ ይታወቃል።
news-51780954
https://www.bbc.com/amharic/news-51780954
የኢትዮጵያው አውሮፕላን አደጋ ረቂቅ ሪፖርት ቦይንግን ተጠያቂ አደረገ
ከአንድ ዓመት በፊት የተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን አደጋ ምክንያት የአውሮፕላኑ የዲዛይን ችግር እንደሆነ መርማሪዎች ለአሜሪካ መንግሥት መስሪያ ቤቶች ያዘጋጁት የአደጋው ረቂቅ ሪፖርት አመለከተ።
ሮይተርስ እንደዘገበው የአሜሪካ ብሔራዊ የትራንስፖርት ደህንነት ቦርድ በረቂቅ ሪፖርቱ ላይ ቅሬታ ወይም እንዲለወጥ የሚያቀርበው ሃሳብ ካለው ዕድል እንደተሰጠው፤ ሪፖርቱ ይፋ ስላልተደረገ ማንነታቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ ሰዎች ተናግረዋል። የቦርዱ ቃል አቀባይ ኤሪክ ዌይስ ጊዜያዊው ረቂቅ ሪፖርትን እንደተቀበሉ ቢገልጹም ድርጅታቸው ለውጥ እንዲደረግ ይጠቅ እንደሆነ አስተያየት ከመስጠት ተቆጥበዋል። ቦይንግ ሪፖርቱን በተመለከተ ምላሹ ምን እንደሆነ በሮይተርስ ቢጠየቅም ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል። ረቂቅ ሪፖርቱን ቀድሞ ይፋ ያደረገው ብሉምበርግ ኒውስ እንዳለው የሪፖርቱ ማጠቃለያ ስለኢትዮጵያ አየር መንገድም ሆነ የበረራ ሰራተኞቹ አሰራርን በተመለከተ ውስን ወይም ምንም ነገር ባለማለቱ በምርመራው ላይ በተሳተፉ አንዳንድ ሰዎች ዘንድ ጥያቄን አስነስቷል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት በነበረው አውሮፕላን ላይ የደረሰውን አደጋ በተመለከተ የተዘጋጀው ረቂቅ ሪፖርት፤ በአውሮፕላኑ የበረራ መቆጣጠሪያ ሶፍትዌር ላይ በነበረ ችግርና በአብብራሪዎች ስህተት እንደተከሰከሰ በተነገረለት በተመሳሳዩ የኢንዶኔዢያው የላየን ኤር አውሮፕላን ሪፖርት ጋር መነጻጸሩ ተገልጿል። ከአንድ ዓመት በፊት ወደ ጎረቤት አገር ኬንያ ለመጓዝ ከአዲስ አበባ ከተነሳ ከስድስት ደቂቃዎች በኋላ የተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን የበረራ ቁጥር 302 የአውሮፕላኑ ሰራተኞችን ጨምሮ 157 ሰዎች ሞተውበታል። ከዚህ አሰቃቂ አደጋ በኋላም በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖች ከበረራ ውጪ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የበላይ ተቆጣታሪነት ስር ካናዳ ሞንትሪያል በሚገኘው የአቪዬሽን ኤጀንሲ ደንብ መሰረት፤ ኢትዮጵያ አደጋውን በተመለከተ የመጨረሻውን ሪፖርት በአደጋው አንደኛ ዕለት ይፋ ማድረግ ይኖርባታል። 32 ኬንያዊያን፣ 18 ካናዳዊያን፣ 18 ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ የ33 አገራት 157 ዜጎች ህይወታቸው ያለፈበትን የዚህን አደጋ አንደኛ ዓመት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመጪው ማክሰኞ አስቦት እንደሚውል ቢቢሲ አረጋግጧል።
news-50450488
https://www.bbc.com/amharic/news-50450488
ደግነት ለጤንነት ብቻ ሳይሆን ለረዥም እድሜ ይጠቅማል
ደግነት ምን ያስገኛል? ምናልባት ደስ የሚል ስሜት? . . . አዎ በእርግጥም መልካምነት በሕይወታችን ጥሩ ነገሮችን ያስከትላል። ተመራማሪዎች ደግነት ከሚፈጥርልን አወንታዊ ስሜት ባሻገር እድሜያችንንም እንደሚያረዝም ደርሰንበታል ይላሉ።
በእርግጥ ደግነት ስንል ምን ማለታችን ነው? ለምንስ አስፈላጊ ነው? የሚለውን ጥያቄ ተመራማሪዎቹ አንስተው በዝርዝር ለመረዳት ሲነሱ ነገሩ በሰው ሕይወት ውስጥ ወሳኝ ነገር ሊሆን እንደሚችል እርግጠኛ ሆነው ነበሩ። ምርምሩን የመሩት ዳንኤል ፌስለር በተለይ ሌሎች መልካም ሲያደርጉ የሚመለከቱ ሰዎች እንዴት ደግ ለመስራት ሊነሳሱ እንደሚችሉ በቅርበት በመፈተሽ "ተላላፊ ደግነት" ያሉት ክስተት ማንን በተለይ በአወንታዊ መልኩ እንደሚነካ መርምረዋል። • በፌስቡክና በዩቲዩብ ብዙ ተከታይ ያላቸው ሰዎች ምን ያህል ገንዘብ እንደሚያገኙ ያውቃሉ? ተመራማሪው "በአሁኑ ዘመን ደግነት በራቀው ዓለም ውስጥ እንገኛለን" በማለት በዓለም ዙሪያ በፖለቲካ አመለካከትና በሐይማኖት ሰበብ በሰዎች መካከል የሚከሰተው ግጭት እየጨመረ መሆኑን ይናገራሉ። ደግነት ሌሎችን ለመጥቀም ከሚደረጉ አስተሳሰቦችን፣ ስሜቶችንና እምነቶችን ከሚያንጸባርቁ ተግባራት ጋር የተያያዙ እንደሆኑ በመግለጽ፤ እነዚህም በውጤታቸው ሌሎችን የሚጠቅሙ ሲሆኑ ሌላ ውጤት ለማምጣት የምንጠቀምበት እንዳልሆነ ተመራማሪው ይናገራሉ። በተቃራኒው ደግ ወይም መልካም አለመሆን "ሌሎችን ያለመቀበል፣ ለሌሎች ደህንነት ዋጋ ያለመስጠት ማሳያ ነው" ይላሉ። • መጻሕፍትን ማንበብና መጻፍ ለአዕምሮ ጤና ይህ በደግነት ላይ የተደረገው ምርምር ያስፈለገው "ደግነት ስለምን በዘመናዊው ዓለም ተጓደለ የሚለውን ለመረዳት" እንደሆነ ለጥናቱ የገንዘብ ድጋፍ የሰጠው ተቋም ባለቤቶች ተናግረዋል። ተመራማሪው ዳንኤል ፌስለር እንደሚሉት ደግነት ብዙ ገጽታዎች አሉት "የደግነት ተግባር ለሰው ስናደርግና ለእኛም ሲደረግልን በሁሉም መልኩ ለጤናችን ጠቃሚ ነው። አደገኛ የሆነን ውጥረት ወይም ጭንቀትን በማስወገድ በጎ ውጤት አለው" ይላሉ። ደግነት ወይም መልካምነት ትልልቅ ድርጊቶች በመፈጸም ብቻ የሚገለጹ ሳይሆኑ ቀላል የሚባሉ ንግግሮችና የሰላምታ ልውውጦችም ከዚሁ አንጻር ሊታዩ ይችላሉ። ለራሳችን ይልቅ ለሌሎች በጎ ማድረግ ቀላል ነው ብዙም ግድ ባንሰጠውም በመደብር ውስጥ የሚገኙ አስተናጋጆች የሚያሳዩን ፈገግታና የሚሰጡን ሰላምታ በአጠቃላይ ጤናችን ላይ የእራሱ የሆነ አውንታዊ ውጤት እንዳለው ጥናቱ አመልክቷል። "ለሌሎች መልካም ስለመሆን ማሰብና በደግነት ድርጊቶች ውስጥ መሳተፍ የደም ግፊትን ዝቅ ያደርጋል። በተጨማሪም ድብርትና ጭንቀትን የማከም ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው።" • እውን ቡና መጠጣት እድሜ ይጨምራል? በኮለምቢያ ዩኒቨርስቲ ዶክትር የሆኑት ኬሊ ሃርዲንግ በቅርብ ባሳተሙት መጽሐፋቸው ላይ እንዳሰፈሩት መልካምነት የሰውነታችንን በሽታን የመከላከል አቅም ይገነባል፣ የደም ግፊትን ዝቅ በማድረግ ሰዎች በረጅም እድሜ የተሻለ ሕይወት እንዲኖራቸው ያደርጋል ብለዋል። ጠቃሚ ነጥቦች ደግነት ለተሞላበት ሕይወት 1. የሚሰሙ መስለው መልስ ለመስጠት እራስዎን ከማዘጋጀት ይልቅ በሐቅ ሌሎች የሚሉትን ማድመጥ ይጀምሩ 2. በመጥፎ ሁኔታ ምላሽ ለሚሰጥዎት ሰው በመልካምነት ይመልሱ። (የሚያመነጫጭቅዎትን ሰው ያስቡና ወዳጅነት በተሞላበት ሁኔታ "ቀንህ/ሽ ጥሩ አልነበረም?" ብለው ይጠይቋቸው። በዚህም ውጥረት የተሞላበትን ሁኔታ በቀላሉ ማርገብ ይችላሉ) 3. በሰዎች ሕይወት ውስጥ ከሚያጋጥሙ ነገሮች ሁሉ ችላ መባል፣ አለመፈለግና አለመፈቀር የሰውነትን ክብር የመግፈፍ ያህል ስለሆነ ችላ የተባለን ሰውን ያቅርቡ። ይህን ሲያደርጉ ለሰዎች ዋጋን ይሰጣሉ። 4. ከመልካምነት የራቀ ድርጊት ሲፈጸም ሲገጥምዎ የእርሶ ችግር አለመሆኑን ይረዱ። ለድርጊቱ ምላሽ እንዲሰጡ ሲገፋፉም እራስዎን ይቆጥቡና በጥልቀት ትንፋሽ ወስደው እራስዎን ያርቁ። ዶክትር ኬሊ "ደግነት በዙሪያችን ያሉ ነገሮችን በመለወጥ በዓለም ላይ ያሉ ነገሮችን እንድንፈትሽ ይረዳናል" በማለት "በአብዛኛው ከእራሳችን ይልቅ ለሌሎች ሰዎች መልካም ለመሆን ይቀለናል" ሲሉ አክለዋል። ለእራሳችንም ሆነ ለሌሎች ደግ መሆንን ለማበረታታት በርካታ መንገዶች አሉ። "በሥራ ቦታ፣ በትምህርት ቤትና በቤታችን ውስጥ ደግና ሩህሩህ በመሆን መልካም ውጤትን ለማግኘት እንችላለን" ይላሉ። በህክምና በኩል ቴክኖሎጂው እየተሻሻለ ሊሆን ይችላል፤ ነገር ግን የተንከባካቢን ደግነት ያህል ትልቅ ነገርን ግን መፍጠር አይቻለንም ይላሉ ዶክተሯ። በተለይ ደግሞ በአእምሮ ጤናና አካላዊ ጤና መካከል ያለው ትስስር እጅግ ወሳኝነት በመጥቀስ። • ትምህርት ዕድሜን እንደሚያስረዝም በጥናት ተረጋገጠ ሰዎች ሌሎች የደግነት ተግባርን ሲፈጽሙ ሲመለከቱ ተመሳሳዩን ለመፈጸም ይነሳሳሉ ይላሉ ባለሙያዎች። ስለዚህ የምንፈጽማቸው በጎ ነገሮች በእኛ ድርጊት ላይ ብቻ የሚቆሙ ሳይሆኑ በሌላ ጊዜ ለሌሎች ሰዎች ለሌሎች እንዲፈጸሙ እያገዝን መሆኑን መረዳት ያስፍለጋል። ግጭቶችና ጥላቻ በተበራከተበት ዓለም የመልካምነት ድርጊቶች ጎልተው ይሰማሉ፤ ያዩ የሰሙ እንዲሁም የተደረገላቸው ጭምር ሳይቀሩ ደግ ማድረግን ይለምዳሉ፤ ለሌሎችም ያስተላልፋሉ። በአንደኛው የዓለም ክፍል የሚፈጸም የደግነት ተግባር አየርና ባሕሩን አቋርጦ ከአድማስ ባሻገር በመጓዝ በሌላ ቦታ ይሰማል ይፈጸማል። ለዚህ ነው ደግንት/መልካምነት ተላላፊ ነው የሚባለው።
news-55401206
https://www.bbc.com/amharic/news-55401206
ትግራይ ፡ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ልጅ ሰምሃል መለቀቋን እናቷ አዜብ መስፍን ገለጹ
የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ልጅ ሰምሃል መለስ ትግራይ ውስጥ በጸጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር ከቆየች በኋላ መለቀቋን እናቷ ወይዘሮ አዜብ መሰፍን ለቢቢሲ ገለጹ።
ወ/ሮ አዜብ እንዳሉት ሰምሃል ከእሁድ ጀምሮ አስከ ሰኞ ምሽት ድረስ ለ36 ሰዓታት ተይዛ መቆየቷን ገልጸው፤ ትናንት ምሽት እራሷ ደውላ መለቀቋን እንደገለጸችላቸው ለቢቢሲ ዛሬ [ማክሰኞ] ጠዋት ተናግረዋል። ወ/ሮ አዜብ ልጃቸው ሰምሃል በምን ምክንያት ለእስር እንደተዳረገች የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ለቢቢሲ ተናገረው፣ ወደ መቀለ የሄደችው ወታደራዊ ግጭቱ ከመጀመሩ በፊት እንደሆነ ገልጸዋል። አዲስ አበባ የሚገኙት ወ/ሮ አዜብ ጨምረውም ሰምሃል ወደ መቀለ ያቀናችው በአባቷ የህይወት ታሪክ ላይ የተጻፈ መጽሐፍን ተንተርሶ የተዘጋጀን ቲያትር ለማስመረቅ በርካታ ሰዎች ካሉበት ቡድን ጋር መሆኑን አመልክተዋል። ሰምሃል "የፖለቲካ አቋም ሊኖራት ይችላል። ነገር ግን የፖለቲካ ፓርቲ አመራርም፣ አባልም፣ ደጋፊም አልነበረችም" ያሉት እናቷ ወ/ሮ አዜብ መስፍን የእስሯ ምክንያት ምን እንደሆነ እንደማያውቁ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ከሰምሃል በተጨማሪ ከሁለት አስርት ዓመታት በፊት አዲስ አበባ ውስጥ የተገደሉት ጀነራል ኃየሎም አርአያ ልጅ የሆነው ብርሐነመስቀል ኃየሎምም በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል። ወ/ሮ አዜብ ከቀናት በፊት ልጃቸው ሰምሃል እየተፈለገች እንደሆነ በመስማታቸው አርብ ዕለት ወደ መቀለ ለመሄድ ፈልገው የነበረ ቢሆንም ፈቃድ ባለማግኘታቸው እንደቀሩና እሁድ ዕለት በቁጥጥር ሰር እንደዋለች መስማታቸውን ለቢቢሲ አብራርተዋል። ሰምሃል በየትኛው አካል እንደተያዘችና ምክንያቱ ምን እንደሆነ ከአንዳንድ አካላት ለማወቅ ጥረት ማድረጋቸውን የሚናገሩት ወ/ሮ አዜብ ነገር ግን ምላሽ ለማግኘት እንዳልቻሉ ጠቅሰዋል። ቢቢሲ ሰምሃል መለስ በቁጥጥር ስር ስለዋለችበት ምክንያትና ለማወቅ ከጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ፕሬስ ሴክሬታሪያት አወል ሱልጣን እና የፌደራል ፖሊስ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጄይላን አብዲን ቢጠይቅም ስለጉዳዩ የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ተናግረዋል። ሰምሃል መለስ የኢህአዴግ ሊቀ መንበርና ከ20 ዓመታት በላይ አገሪቱን የመሩት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እና የወይዘሮ አዜብ መስፍን የበኩር ልጅ ስትሆን አስከ አባቷ ህልፈት ድረስ ስለእርሷ ብዙም የሚታወቅ ነገር አልነበረም። የ32 ዓመቷ ወጣት ሰምሃል የተወለደችው አባቷ በኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማሪያም የሚመራውን መንግሥት ለመጣል ህወሓትን በመምራት የሽምቅ ውጊያ በሚያደርጉበት ጊዜ ሱዳን ካርቱም ውስጥ ነበር። ሰምሃል ከአባቷ ህልፈት በኋላ የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስትር ለመዘከር በሚካሄዱ እንቅስቃሴዎችና በፖለቲካዊ መድረኮች ላይ አልፎ አልፎ በመቅረብ ሃሰብ ስትሰነዝር ከመታየት ውጪ በፖለቲካው መድረክ ጎልቶ የታየ ተሳትፎ አልነበራትም። ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም በትግራይ ክልል ውስጥ በሚገኘው የአገሪቱ የመከላከያ ሠራዊት የሠሜን ዕዝ ላይ ጥቃት ከተፈጸመ በኋላ መንግሥት በህወሓት ኃይሎች ላይ ወታደራዊ ዘመቻ አካሂዶ የህወሓት አመራሮችን ከክልሉ የስልጣን መንበር ላይ ማስወገዱ ይታወሳል። በትግራይ ክልል ውስጥ ለሦስት ሳምንታት ያህል ከተካሄደ ወታደራዊ ዘመቻ በኋላ ኅዳር 19/2013 ዓ.ም የፌደራል መከላከያ ሠራዊት የክልሉን ዋና ከተማ መቀለን ተቆጣጥሮ ይፈለጋሉ ያላቸውን ከፍተኛ የህወሓት አመራሮችን ለመያዝ ክትትል እያደረገ መሆኑን ገልጿል።
news-51582936
https://www.bbc.com/amharic/news-51582936
በአሜሪካና ካናዳ ድንበር ላይ የሰው አንጎል ተገኘ
የአሜሪካ ጉምሩክ ኃላፊዎች በካናዳ ፖስታ አመላላዥ መኪና ውስጥ የሰው አንጎል ማግኘታቸውን ገለጹ።
በአሜሪካ ድንበር ላይ የተገኘው የሰው አንጎል ሰፋ ባለ ጠርሙስ ውስጥ የተቀመጠው አንጎል የተገኘው በአሜሪካዋ ሚችጋን እና በካናዳዋን ቶሮንቶ መካከል በሚገኘው ብሉ ዋተር በተባለ ድልድይ ነው። ጠርሙሱ የተገኘው "Antique Teaching Specimen" (የጥንታዊ አስተምሮ ናሙና) የሚል መግለጫ ተጽፎበት ሲሆን፤ መነሻውን ቶሮንቶ አድርጎ ወደ ዊስኮንሰን እንዲደረስ የተላከ ነበር። የጉምሩኩ ኃላፊዎች እንደተናገሩት፤ ስለ ጠርሙሱ ባለቤት እንዲሁም አንጎሉ ወደ አሜሪካ እንዲገባ የተፈቀደበትን ሰነድ አላገኙም። • የ 'ኮፒ ፔስት' ፈጣሪ ሞተ • ፓስፖርት፡ የሰዎችን እንቅስቃሴ የወሰነ ሰነድ • ኬንያዊውን ገርፈዋል የተባሉት ቻይናውያን አሰሪዎች ከሃገር እንዳይባረሩ ፍርድ ቤቱ አዘዘ የጉምሩኩ ዳይሬክተር ማይክል ፎክስ "የአሜሪካ የማኅበረሰብ ጤና ተቋም እና የበሽታ ቁጥጥር ድርጅትም እንዲህ አይነት ነገሮች እንዳይዘዋወሩ የሚከለክል ጥብቅ ሕግ አላቸው" ብለዋል። የአሜሪካ ጉምሩክ ኃላፊዎች ድንበር ላይ እንግዳ ነገር ሲይዙ ይህ የሰው አንጎል የመጀመሪያቸው አይደለም። እንደ ጎርጎሮሳውያኑ በ2014 የሎስ አንጀለስ አውሮፕላን ማረፊያ ሠራተኞች ከናይጄሪያ ወደ ካሊፎርንያ የተላኩ 67 ቀንድ አውጣዎች አግኝተው ነበር። 2006 ላይ ደግሞ የዳይኖሰር እንቁላልን ጨምሮ ስምንት ቶን ጥንታዊ ቅሪተ አካል ተይዞ ነበር። ቅሪተ አካሉ ከአርጀንቲና ወደ አሪዞና የተላከ መሆኑ ይታማናል።
54673732
https://www.bbc.com/amharic/54673732
ስደት፡ ሕይወት ከአሰቃቂው የሳዑዲ አረቢያ እስር ቤት በኋላ
የ39 ዓመቷ ዘውድነሽ በቀለ በ2013 ዋዜማ ከሳኡዲው የስደተኞች እስር ቤቶች ወደ ኢትዮጵያ ከሚመለሱ 147 ሴቶች እና ሕፃናት መካከል አንዷ መሆኗን ስታውቅ ደስታውን መቆጣጠር አልቻለችም ነበር። ይህን ያክል እደለኛ መሆኔንም አላመንኩም ነበር ትላለች።
ጥሪት ቋጥራ ባትሸጉጥም፤ እንደ ውጥኗ ድህነትን ድል ባትነሳም፤ ባዶ እጇን ቢሆንም ወደ አገር ቤት የመመለስ ጉዟዋ ደስታ እንዲፈጠርባት ካደረጉ ምክንያቶች መካከል ቀዳሚው ያለፉትን ስድስት ወራት በሳዑዲ እስር ቤት ያሳለፈችበት ሰቆቃ ነው "እግዚያብሄር የተመሰገነ ይሁን ለአገሬ በቅቻለሁ፤ ለልጆቼም በህይወት ገብቻለሁ" ትላለች ለቅሶ ባጀበው ድምፅ። ከመቶ በላይ ሰዎች በአንድ ላይ በታጎሩበት የእስር ቤት ቆይታዋ "ብዙ የታመሙ አሉ፤ ብዙ ያበዱ አሉ። የአዕምሮ ጭንቀት [የገጠማቸው] አሉ። በሕገ-ወጥ መንገድ እየሄዱ፤ ሕገ-ወጥ ደላላ እየወሰዳቸው።" ዘውድነሽ ከሰባት ዓመት በፊት ሕጋዊ በሆነ መንገድ ነበር ሕይወቷን ልታቀና ወደ ሳዑዲ አረቢያ ያቀናችው። ቆይታዋ ግን ቀድማ እንደተመኘችው፤ ተስፋም እንዳደረገችው አልጋ በአልጋ አልሆነላትም። ከመነሻው የቋንቋ ማነቆ ነበረባት፤ የቤት ሠራተኛነት ከምታገለግላት ቀጣሪዋ ጋር መስማማት አልቻለችም፤ በደልንም ማሰተናገደን ያወቀችው ገና ከማለዳው ነበር። የሥራ ፈቃዷ ካለቀም በኋላ እዚያው የቆየችው ዘውድነሽ ከሥራ ሥራ ተዟዙራቸለች፤ ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሳለች፤ በየመንገዷም እንግልትን ቀምሳለች። "ሕፃን ልጅ ዳልዬ ላይ በጩቤ ሁሉ ወግቶኛል" ትላለች። "በቃ በሽተኛ ሆኛለሁ።" ባለፈው ዓመት አጋማሽ ገደማ ግን የባሰው ዱብ ዕዳ ተከሰተ። በርካታ ኢትዮጵያዊያን ስደተኛ ሠራተኞች ተጋርተው የሚኖሩበት ቤት በሳዑዲ የፀጥታ ኃይሎች ተከበበ። "ገላዬን ታጥቤ በፒጃማ ነበር ያለሁት። ልብስ መቀየሪያ እንኳን ሳልይዝ አፋፍሰው ወሰዱን።" ዘውድነሽ በሳዑዲ ፖሊስ ከተያዘች በኋላ የተወሰደችው በሰብአዊ መብቶች ጥሰት እና በአያያዝ ጉድለት ወደሚታወቀው እስር ቤት ነበር። መገናኛ ብዙሃን እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ዘውድነሽ የነበረችበት እስር ቤት ውስጥ የሚፈጸሙ በደሎችን አጋልጠው ነበር። በእነዚህ እስር ቤቶቹ ውስጥ ድብደባ ይፈፀማል፤ ታሳሪዎች በሰንሰለት ይታሰራሉ፤ ከመጠን በላይ ይተፋፈጋሉ የሚሉ ወቀሳዎች በመገናኛ ብዙሃን እና የሰበዓዊ መብት ተሟጋቾች ቀርቦ ነበር። የሳኡዲ መንግስት ትችቶቹን ተከትሎ ጉዳዩን እየመረመርኩ ነው ማለቱ ይታወሳል። ዘውድነሽ (ቀኝ) እና ጓደኛዋ ገነት ዘውድነሽ የነበረችበት እስር ቤት አስከፊ እንደነበር ትጠቅሳለች። ከመጠን ባላይ ከመታጨቅም በላይ፤ ለታማሚዎች የሚደረግ በቂ የህክምና አገልግሎት አልነበረም ትላለች። ከእንክብካቤ ንፈገቱ የተነሳም በእስር ቤቱ ውስጥ የሞተች ስደተኛ እንደነበረች ታወሳለች። ስለዚህም አዲስ አበባ የሚመልሳት አውሮፕላን ውስጥ ስትገባ ደስታዋ ወደር አልነበረውም። አዲስ አበባ ከደረሰች በኋላም በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ለአስራ አንድ ቀናት ያክል በአንድ የዩኒቨርስቲ ካምፓስ ውስጥ እራሷን ለይታ እንድትቆይ ተደርጋ ነበር። ከለይቶ ማቆያው ስትወጣ የመጓጓዣ ወጭ 250 ብር ተሰጥቷት ወደ መኖሪያ ተጉዛለች። ይህ ከሆነ ከአንድ ወር በኋላ ዘውድነሽ የድጋፍ ያለህ ትላለች። ሥራ ማግኘት አልቻለችም። ህይወቷን ዳግም ለመገንባትም በአዲስ አበባ ምስራቃዊ ጫፍ በሚገኘው የእናቷ ቤት ውስጥ ኑሮን ጀምራለች። ከአካባቢዋ ወረዳ ድጋፍ እንደሚደረግላት ቃል ተገብቶላት ጥሪ እንድትጠብቅ ተነግሯታል። ጥሪው ግን እስካሁን አልመጣም። የባንክ ደብተር ቁጥሯን እንድትሰጥም እንዲሁ ተነግሯት እርሱን ሰጥቻለሁ ትላለች። ለተመላሽ ስደተኞች የሚደረገው የማቋቋሚያ ድጋፍ ፍፁማዊ ነው ባይባልም ባለፉት ዓመታት መሻሻል ታይቶበታል የሚሉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ድዔታ ፅዮን ተክሉ ናቸው። "ስለ ሳኡዲ አረቢያ ካወራን [እ.ኤ.አ] ከግንቦት 2017 ጀመሮ እስከ መጋቢት 2020 ድረስ ወደአራት መቶ ሺህ ኢትዮጵያዊያንን መልሰናል" ይላሉ ሚኒስትር ድኤታዋ ከቢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ። "እነዚህ በሙሉ ነፍስ ወከፍ ግለሰቦች ናቸው ብለህ ከጠየቅከኝ አይደሉም ነው የምለው፤ ምክንያቱም ከመካከላቸው አስር ጊዜ አስራ አምስት ጊዜ የተጓዘ ሰው ታገኛለህ። ስለዚህ ማድረግ የምትችለው ጉዞዎቹን መቁጠር ነው።" ይህን የድግግሞሽ ጉዞ ለማስቀረት ስነ ህይወታዊ መረጃ መሰብሰብ መጀመራቸውን ይገልፃሉ። ተመላሽ ስደተኞቹ አዲስ አበባ በሚደርሱበት ወቅት መጠነኛ የስነ ልቦና ህክምና እንደሚደረግላቸው የሚናገሩት ሚኒስትር ድኤታዋ፤ "ከዚያ በኋላ ከክልል ቢሮዎች ጋር እንሰራለን" ይላሉ። ከጤና ሚኒስቴር፣ ከሰላም ሚኒስቴር እና ከሠራተኛ እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዲሁም መንግሥት በዚህ ክንውን አጋር ከሚላቸው ከአፍሪካ ኅብረት፣ ከአውሮፓ ኅብረት እና ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በመሆን ተመላሾቹን መልሶ ወደማኅበረሰብ ለመቀላቀል እንዲሁም ሕይወታቸውን ዳግም እንዲገነቡ ለማድረግ እንሠራለን ሲሉ ያስረዳሉ። "መሻሻል ታይቷል? አዎ። ሥራውን እንከን አልባ ፍፁም ነው? አይደለም። [ተመላሾቹን] ወደማኅበረሰብ በመቀላቀል ጉዳይ የበለጠ መስራት አለብን" ይላሉ ፅዮን። በርካቶቹ ተመላሾች በሳዑዲ አረቢያ ካጋጠማቸው ሰቆቃ አሻራ ጋር እንደሚኖሩ ከሚያስረዱት ተመላሾች መካከል ገነት ታከለ አንዷ ናት። ገነት ለአስራ ዓመታትን ያህል በሳዑዲ አረብያ ቆይታለች። የመጨረሻዎቹን ሦስት ወራት አሰቃቂ ነበር ባለችው እስር ላይ ነው ያሳለፈችው። እንደ ዘውድነሽ ሁሉ እርሷም የጳጉሜ 2012 ተመላሾች መካከል አንዷ ናት። በእስር ቤት ከተዋወቀቻት ዘውድነሽ ጋር አሁን የቀረበ ወዳጅነትን መስርታለች። በእስር ቆይታዋም በሽታ እንዳጋጠማት ትናገራለች። "እግሬን መሽመቀቅ [ጀምሮኛል]። ጊዜው ደግሞ የብርድ ሰዓት ነው" ትላለች። በተመለሰች ከአንድ ወር በኋላ ለቢቢሲ በሰጠችው ቃለ መጠይቅ። "የሚለበስ ደግም ምንም የለም። እዚያ [ገብተው] ጥለውት የሄዱት ካለ እንጅ። አንድ ብርድ ልብስ ነበር፤ ስሚንቶ ላይ ነው የምንተኛው።" በእስር ቤቱ ውስጥ ወደአስር አካባቢ ክፍሎች እንደነበሩ የምታስታውሰው ገነት፤ አንደኛው ክፍል ውስጥ ብቻ ከስድሳ በላይ ሕፃናት ነበሩ ትላለች። "አኔ የነበርኩበት ክፍል ውስጥ አስራ ሁለት ልጆች አሉ።" ከተመለሰች በኋላ ወደህክምና መስጫ ስፍራ አዘውትራ ማቅናቷን የምትናገረው ገነት፤ ሻል እያላት ቢመጣም ጨርሶ አለመዳኗንም ጨምራ ትገልፃለች። እንደ ዘውድነሽ ሁሉ ገነት ከኮሮናቫይረስ ለይቶ ማቆያ ስትወጣ ለመጓጓዣ የሚሆን ነው ተብሎ ጥቂት መቶ ብሮች እንደተሰጣት ለቢቢሲ ትናግራለች። ከዚያ በኋላ ግን የድጋፍ ቃል ኪዳን ካልሆነ በስተቀር በተጨባጭ ያገኘችው ነገር ያለመኖሩን ታስረዳለች። እርሷ እና መሰል ተመላሾች ምናልባትም ቀደም ብለው ሳኡዲ አረቢያ እያሉ እየላኩ ያስቀመጡት ገንዘብ ወይንም ጥሪት ከሌላቸው በስተቀር ህይወትን ከዜሮ መጀመር ግድ እንደሚላቸው ነው የምትገልፀው ገነት። እርሷም ሆነች ገነት ዳግም ወደመካከለኛው ምስራቅ የመጓዝ ኃሳብ ጨርሶም የለንም ይላሉ፤ ነገር ግን የገንዘብም ሆነ የሙያ ስልጠና አሊያም በአንዳች መልኩ እንዲደራጁ የሚደረግበትን መፍትሄ ይናፍቃሉ። መጪው ጊዜ ምን ይዞ እንደሚመጣ እርግጠኞች አይደሉም፤ ቢያንስ ለአሁኑ ግን ከወዳጅ ቤተሰብ ጋር የመገናኘትን እንደሁም የደህንነታቸው መጠበቅን ትሩፋት እያጣጣሙ ይገኛሉ።
news-57118262
https://www.bbc.com/amharic/news-57118262
የእስራኤልና ፍልስጥኤም ግጭት ከዬት ወደዬት
ከሰሞኑ በእየሩሳሌም በተነሳው ግጭት በመቶዎች የሚቆጠሩ ፍልስጥኤማውያን ተጎድተዋል። 20 የሚሆኑ የእስራኤል ፖሊሶችም እንዲሁም በግጭቱ ጉዳት ደርሶባቸዋል ተብሏል።
ለወራት ያህል ተፋጠው የነበሩት እስራኤልና ፍልስጥኤም ለአስርት አመታት ያህልም በማያባራ ግጭት ውስጥ ናቸው። እንዴት ተጀመረ? ቤተልሔም በሃያኛው ክፍለ ዘመን ከመቶ አመት በላይ ያስቆጠረው ጉዳይ ፍልስጥኤም ተብሎ የሚታወቀውን መካከለኛ ምስራቅ ይገዛ የነበረው የኦቶማን ኢምፓየር በአንደኛው አለም ጦርነት በብሪታንያ ተሸነፈ። ብሪታንያም ግዛቱን ተቆጣጠረች። በቦታውም ይኖሩ የነበሩት በዋነኝነት አረቦች ሲሆን አነስ ያለ ቁጥር ያላቸው ይሁዳውያን ነበሩ። በሁለቱ ህዘቦች መካከል ያለው ውጥረት መነሻም አለም አቀፉ ማህበረሰብ በተለያዩ አገር የነበሩ ይሁዳውያን ወደ ፍልስጥኤም እንዲመለሱ መሆኑ ነበር። ይህንንም ስራ በበላይነት የምትሰራው ብሪታንያ ሆነች። ይሁዳውያን መሬቱ የጥንት መኖሪያችን ብለው የሚያስቡ ሲሆን ለፍልስጥኤማውያንም እንዲሁ ግዛታችን የኛ ነው በሚል ውሳኔውን ተቃወሙ። በአውሮፓውያኑ 1920-40ዎቹ ወደ ፍልስጥኤም የሚመጡ ይሁዳውያን ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ጨመረ። አብዛኛዎቹ በሁለተኛው አለም ጦርነት አውሮፓ ውስጥ የነበረውን ጭፍጨፋን አምልጠው የተረፉ ናቸው። በይሁዳውያንና በአረቦቹ መካከል የነበረው ፍጥጫ እንዲሁም የብሪታንያ ግዛት ተቃውሞ ታክሎበት ሁኔታዎች መጋጋል ጀመሩ። በአውሮፓውያኑ 1947 የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ፍልስጥኤም ለሁለት እንድትከፈልና የይሁዳውያንና የአረብ ግዛቶች እንዲመሰረቱ እንዲሁም እየሩሳሌም አለም አቀፍ ከተማ እንድትሆን ውሳኔ አስተላለፈ። ውሳኔው በአይሁድ መሪዎች መካከል ተቀባይነት ቢያገኝም በአረቦች መካከል ግን ውድቅ ተደረገ እንዲሁም ተግባራዊ አልሆነም። የእስራኤል መፈጠርና "ከፍተኛው ጥፋት" ችግሩን መፍታት ያልቻሉት እንግሊዛውያን በአውሮፓውያኑ 1948 ለቀው ሲወጡ የአይሁድ አመራሮች የእስራኤል ሃገር ምስረታን አወጁ። ሁኔታውን በርካታ ፍልስጥኤማውያን ተቃወሙት፤ ጦርነትም ተከተለ። የአካባቢው አረብ አገራት ወታደሮችም ተሳተፉበት። በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ፍልስጥኤማውያን ከቤታቸው ተፈናቀሉ፤ የተወለዱበትን ቀዬ ለቀው ወጡ። ይህም ሁኔታ አል ናቅባ ወይም ከፍተኛ ጥፋት ተብሎ ይጠራል። ጦርነቱ ቆሞ በአመቱ የተኩስ አቁም ስምምነት ሲፈረም እስራኤል በርካታ ግዛቶችን ተቆጣጠረች። ዮርዳኖስ ዌስት ባንክ የሚባለውን ግዛት እንዲሁም ግብፅ ጋዛን ተቆጣጠሩ። እየሩሳሌምም በምዕራብ በኩል በእስራኤል ኃይሎች ቁጥጥር ስትገባ በምስራቅ በኩል ደግሞ የዮርዳኖስ ኃይሎች ተቆጣጠሯት። የሰላም ስምምነትም መደረስ ስላልተቻለ ሁሉም ወገኖች እርስ በርስ መወነጃጀላቸውን ቀጠሉ፤ በመጪዎቹ አስርት አመታትም በርካታ ጦርነቶች ተደረጉ። በቀጣዩና በአውሮፓውያኖቹ 1967 በተደረገው ጦርነት እስራኤል ምስራቅ እየሩሳሌምን፣ ዌስት ባንክን እንዲሁም አብዛኛውን የሶሪያ የጎላን ሃይትን፣ ጋዛንና የግብፅን ሲናይ ፔኒንሱላን ተቆጣጠረች። በርካታ የፍልስጥኤም ተፈናቃዮቻቸውና ልጆቻቸው በአሁኑ ወቅት በጋዛና በዌስት ባንክ እንዲሁም በጎረቤት አገራት ዮርዳኖስ፣ ሶሪያና ሊባኖስ ይኖራሉ። ፍልስጥኤማውያን ተፈናቃዮችም ሆኑ ልጆቻቸው ወደ አገራቸውም ሆነ ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ እስራኤል አልፈቀደችላቸውም። እስራኤል እንደምትለው ፍልስጥኤማውያኑ ለእስራኤል አገር ሆና መመስረት አደጋ ደቅነዋል ትላቸዋለች። የስድስቱ ቀን ጦርነት ወታደሮች እስራኤል አሁንም ቢሆን ዌስት ባንክን እንደያዘች የምትገኝ ሲሆን ከጋዛ ወጥቻለሁ ብትልም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በበኩሉ ግዛቱ በእስራኤል ቁጥጥር ስር ነው ይላል። እስራኤል መላው እየሩሳሌም መዲናዬ ናት የምትል ሲሆን ፍልስጥኤማውያን በበኩላቸው ምስራቅ እየሩሳሌም የወደፊቷ ፍልስጥኤም መዲና ናት ይላሉ። እስራኤል መላው እየሩሳሌም የኔ ናት የሚለውን የይገባኛል ጥያቄ እውቅና ከሰጡ ጥቂት አገራት መካከል አሜሪካ አንዷ ናት። በባለፉት አምሳ አመታትም እስራኤል በነዚህ ቦታዎች ቤቶች የሰራች ሲሆን 600 ሺህ የሚሆኑ ይሁዳውያንም ይኖራሉ። ፍልስጥኤማውያን የአለም አቀፍ ህጎችን በመጥቀስ የእስራኤል ድርጊት ህገወጥ ነው ለሰላሙም እንቅፋት ነው ቢሉም እስራኤል ይህንን ትክዳለች። በአሁኑ ወቅት ምን እየተከናወነ ነው? በእስራኤልና በፍልስጥኤማውያን መካከል ከፍተኛ ውጥረት ያለ ሲሆን በተለይም በምስራቅ ኢየሩሳሌም፣ በጋዛና በዌስት ባንክ በሚኖሩት መካከል ደግሞ ሁኔታው የከፋ ነው። ጋዛን እያስተዳደራት ያለው የፍልስጥኤማውያኑ ታጣቂ ቡድን ሃማስ ሲሆን ከእሰራኤል ጋር በርካታ ጊዜያት ተዋግቷል። እስራኤልና ግብፅ በጋራ ለሃማስ የጦር መሳሪያ እንዳይደርስ በሚል የጋዛ ድንበርን ይቆጣጠራሉ። እስራኤል በጋዛና ዌስት በምታደርገው ድርጊትና ክልከላዎች በርካታ ፍልስጥኤማውያን እየተሰቃዩ እንደሆነ ይናገራሉ። እስራኤል በበኩሏ ይህንን የምትፈፅመው ራሷን ከፍልስጥኤማውያን ጥቃት ለመከላከል ነው ትላለች። በቅርቡም የረመ ን ፆም መግባቱን ተከትሎ በፖሊስና በፍልስጥኤማውያን ያለው ግጭት ተባብሶ ነበር። በተለይም በምስራቅ እየሩሳሌም የሚኖሩ ፍልስጥኤማውያን ከቤታችሁ እናስወጣችኋለን የሚለው ማስፈራሪያ በርካቶችን አስቆጥቷል። ዋነኛ ችግሮቹ ምንድን ናቸው? እስራኤልና ፍልስጥኤማውያን የማይስሟሙባቸው በርካታ ጉዳዮች አሉ። ከነዚህም መካከል የተፈናቃይ ፍልስጥኤማውያን እጣ ፈንታ፣ በእስራኤል ቁጥጥር ስር ያለው ዌስት ባንክ የሰፈሩት ይሁዳውያን እዚያው ይቆዩ ወይስ ወደሌላ ቦታ ይሂዱ እንዲሁም እየሩሳሌምን የመጋራት ጥያቄዎች ይገኙበታል። ከሁሉም በላይ ግን ፍልስጥኤም ከእስራኤል ጎን ለጎን ሃገር ሆና ትመስረት የሚለው ዋነኛ ጥያቄ ነው። የሰላም ውይይት ጉዳዮች ለባለፉት 25 አመታት የተነሱ ሲሆን እስካሁን ግጭቶቹን መፍታት አልቻሉም። የወደፊቱ ምንን ይዞ ይመጣ ይሆን? በአጭሩ የእስራኤልና የፍልስጥኤም ሁኔታ ባጭሩ አይቋጭም። በቅርቡ በተሰናባቹ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ተዘጋጅቶ የመጣውና በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ "የክፍለ ዘመኑ ስምምነት" የተባለው የሰላም እቅድ በፍልስጥኤማውያን ለአንድ ወገን ያደላ በሚል ውድቅ ተደርጓል። ለወደፊቱም የሚመጡ የሰላም ስምምነቶች ሁለቱ አካላት የሚስማሙበትና ውስብስብ ችግሮችን የሚፈቱ መሆን አለባቸው። እስከዚያ ድረስ ግጭቱ የሚቀጥል ይሆናል።
news-53564190
https://www.bbc.com/amharic/news-53564190
ዚምባብዌ የአሜሪካ አምባሳደርን አገሪቷን አበጣብጠዋል በሚል አባርራለሁ አለች
የዚምባብዌ ገዢ ፓርቲ ዛኑ ፒኤፍ በባለፈው ሳምንት በአገሪቱ የተደረገውን የተቃውሞ ሰልፍ ድጋፍ በማድረግ የአሜሪካ ኤምባሲን ወንጅለዋል። አምባሳደሩን ከአገር አባርራለሁ በማለትም አስፈራርተዋል።
ምንም እንኳን ተቃውሞው በአገሪቱ ውስጥ የተንሰራፋውን ሙስና ለመቃውም ነው ቢባልም የፓርቲው ቃለ አቀባይ ፓትሪክ ቺናማሳ እንዳሉት መንግሥትን ለመገልበጥ የተደረገ ነው ብለዋል። ተቃዋሚዎቹ በዚህ ተግባራቸው የሚቀጥሉም ከሆነ ተመጣጣኝ ኃይል መንግሥት እንደሚጠቀምም አስጠንቅዋዋል። ቃለ አቀባዩ አክለውም የአሜሪካ አምባሳደር ብሪያን ኒኮልስንም የዱርዬ ተግባር ነው ያሳዩት በማለትም ወርፈዋቸዋል። በሁለቱ አገራት መካከል ያለው ግንኙነትም ለመበላሸቱም ማሳያ ነው ተብሏል። አሜሪካ በዚምባብዌ ውስጥ ያለው ሰብዓዊ መብት አያያዝ ጋር በተያያዘ የኢኮኖሚ ዕቀባ መጣሏ የሚታወስ ነው። ከዚህ ቀደምም በአገሪቱ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ አገሪቷን ለማበጣበጥ ይሰራል መባሉን ውንጀላ ነው በማለት ክዷል። የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በአገሪቷ ውስጥ ጭማሬ ማሳየቱን ተከትሎ መንግሥት የተለያዩ መመሪያዎችን አስተላልፏል። እነዚህ መመሪያዎችንም በተመለከተ መንግሥት ወረርሽኙን በመጠቀም መሰረታዊ የሚባሉ መብቶችን እየጣሰ ነው በማለት ተቃዋሚዎች እየወነጀሉ ነው። በባለፈው ሳምንት አንድ ተቃዋሚ ፖለቲከኛ ሰልፍ በማስተባበር በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን ጋዜጠኛም እንዲሁም በተቃውሞ ሰልፉ በመሳተፍ ታስሯል። የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብት ቢሮ ወረርሽኙ ነፃነትን ለመገደብ እንደ ሽፋን ሊጠቀሙበት አይገባም ብለዋል።
50371542
https://www.bbc.com/amharic/50371542
ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ከደረሰው ግጭት ጋር በተያያዘ 13 ተማሪዎች መታሠራቸው ተነገረ
ባለፈው ቅዳሜ ምሽት ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ከደረሰው እና የሁለት ተማሪዎችን ሕይወት ከቀጠፈው ግጭት ጋር በተያያዘ 13 ተማሪዎች መታሠራቸው ተነገረ።
የሰሜን ወሎ ዞን ፀጥታ እና ሰላም ቢሮ ኃላፊ ኮሎኔል ኃይለማርያም አምባዬ ሌሎች ተጨማሪ ተማሪዎች በግጭቱ ተሳትፎ እንደነበራቸው ተጠርጥረው እየተፈለጉ መሆኑን ለቢቢሲ ተናግረዋል። ቅዳሜ ምሽት በወልዲያ ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎች መካከል በተፈጠረ ግጭት ቢያንስ ሁለት ተማሪዎች መሞታቸውን መዘገባችን ይታወሳል። የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች እና መምህር የብሄር መልክ በያዘው ግጭት የሁለት ተማሪዎች ህይወት ማለፉን እና በርካቶች መቁሰላቸውን አረጋግጠውልን ነበር። ትናንት የአማራ መገናኛ ብዙሃን የሰሜን ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ወልደትንኤ መኮንን በመጥቀስ ቅዳሜ ምሽት ግጭት የተከሰተው፤ ተማሪዎች በጋራ እግር ኳስ በቴሌቪዝን ተመልክተው ሲመለሱ በተፈጠረ ግጭት መሆኑን እና በዚህም ሁለት ተማሪዎች መገደላቸውን እና ስምንት ተማሪዎች ላይ ደግሞ ጉዳት መድረሱን ዘግቦ ነበር። የሰሜን ወሎ ዞን ፀጥታ እና ሰላም ቢሮ ኃላፊ ኮሎኔል ኃይለማርያም አምባዬ የአገር መከላከያ እና የፌዴራል ፖሊስ አባላት ወደ ዩኒቨርስቲው ቅጥር ግቢ መግባታቸውን እና ይሄም እርምጃ መረጋጋትን ማምጣቱን ለቢቢሲ ተናገግረዋል። ኮሎኔል ኃይለማርያም በዛሬው ዕለት ዩኒቨርሲቲው "የተረጋጋ ሁኔታ ላይ ነው" ያሉ ሲሆን፤ በፀጥታው ሁኔታ ስጋት ገብቷቸው ወደየቀያቸው ለመመለስ የፈለጉ ተማሪዎች እንደበሩ አልካዱም። ነገር ግን ከአገር ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የዞኑ አመራሮች እና ከአካባቢው ነዋሪዎች እንዲሁም ከወልዲያ ከተማ ከንቲባ ጋር ውይይት በማድረግ ደህንነት ተሰምቷቸው ትምህርታቸውን አንዲቀጥሉ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በሌላ በኩል ቢቢሲ ያነጋገረው ከሌላ ስፍራ ወደ ዩኒቨርሲቲው ያቀና ተማሪ ከሃገር ሽማግሌዎች አና የአካባቢው ነዋሪዎች አለንላችሁ እያሉን ቢሆንም ጥቃት አድራሾቹ ሲጋለጡ አላየንም ይላል።አሁንም ቢሆን ስጋት እንዳልተለየው የሚገልፀው ይሄው ተማሪ ወደትውልድ ቀዬው የመመለስ ፍላጎቱን እንዳልቀየረ ይናገራል። ግጭቱን ተከትሎ የደህንነት ስጋት የገባቸው ተማሪዎች ከዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ለመውጣት ሲሞክሩ መከልከላቸውን ተናግረዋል። [ፎቶ፡ ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ እሁድ ጠዋት] እሁድ ዕለት ስሙ እንዳይጠቀስ የጠየቀ አንድ ተማሪ ለቢቢሲ "ትናንት [ቅዳሜ ምሽት] የተፈጸመውን አይተን እንዴት ነው ዶርም ውስጥ የምንተኛው?" ሲል ተናግሯል። ጨምሮም "ትናንት የተፈጸመው ዳግም ላለመከሰቱ ምንም ማረጋገጫ የለንም" በማለት ከዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ እንዳይወጡ መደረጉ አግባብ አለመሆኑን ጠቁሟል። ትላንት [እሁድ] የአማራ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባዔ ላይ ተገኘተው ንግግር ያደረጉት የክልሉ የሰላምና ሕዝብ ደህንነት ቢሮ ኃላፊ አቶ አገኘሁ ተሻገር፤ በተማሪዎች መካከል የተነሳውን ግጭት የብሔር ለማስመሰል የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች አሉ ሲሉ ተደምጠው ነበር። "በግጭቱ ተማሪዎች ተጎድተዋል። በአሁኑ ሰዓት ጉዳዩን አረጋግተነዋል። በዚህ ወንጀል ላይ የተሳተፉ ሰዎችን በቁጥጥር ሥር አውለናል። አልፎም አማራ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በሙሉ ሰላም ለማደፍረስ የሚሠሩ አካላትን ለይተን እርምጃ ለመውሰድ እየተንቀሳቀስን ነው።" ብለው ነበር። የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ትናንት በወልዲያ ዩኒቨርሲቲ የተፈጸመውን ክስተት ማውገዙም አይዘነጋም። የክልሉ ምክት ፕሬዝደንት አቶ ሽመልስ አብዲስ ትናንት ከሰዓት በጽሁፍ በሰጡት መግለጫ፤ "አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች በአቋራጭ ስልጣን ለመያዝ እና አስተሳሰቦቻቸውን በኃይል ህዝብ ላይ ለመጫን ጥረት እያደረጉ ነው" ብለዋል። አክለውም ለክስተቱ ተጠያቂ ናቸው የተባሉት ለፍርድ እንዲቀርቡ ከፌደራል እና ከአማራ ክልል መንግሥት ጋር አብረው እንደሚሰሩ አሳውቀዋል።
news-53075007
https://www.bbc.com/amharic/news-53075007
ፖሊስ ሆን ብለህ በአደባባይ 'ፈስተሃል' ያለውን ግለሰብ 550 ዶላር ቀጣ
ከታች አየር ማስወጣት ማኅበራዊ ነውር እንደሆነ ይታሰብ ይሆናል እንጂ በሕግ ያስቀጣል ተብሎ አይጠበቅም።
በኦስትሪያ ግን ፖሊስ ነገሩ ላይ አምርሮ "አላግባብ ፈስተሃል" ያለውን ግለሰብ 564 ዶላር መቀጮ ጥሎበታል። መቀጮው ይህን ያህል ተመን የተደረገበት ባስከተለው መጥፎ ጠረን ወይም ርዝማኔ አልያም የድምጽ ምጣኔ ይሁን የታወቀ ነገር የለም። ሰውየው ድርጊቱን የፈጸመው ፖሊሶች ፊት መሆኑ ቅጣቱን ሳያከብድበት አልቀረም። የቪይና ፖሊስ ግን ሰውየው የተቀጣው "ጋዝ በታች በኩል በማስወጣቱ" ብቻ አይደለም ሲል በትዊተር ሰሌዳው ተከላክሏል። "መቼስ በታች በኩል ለምን ተነፈስክ ብለን ዜጋችንን አንቀጣም. . . " ይላል የፖሊስ የትዊተር መግለጫ። ፖሊስ ሰውየው ላይ ያቀረበው ክስ ግልባጭ በማኅበራዊ ድር አምባው ከታተመ በኋላ ኦስትራዊያን ነገሩን ማኅበራዊ ቧልት አድርገውት ቆይተዋል። የክሱ ርዕስ "የሥነ ምግባር ጥሰት እና ሥርዓት ማጣት" የሚል ሲሆን ድርጊቱ የተፈጸመው በሰኔ 5 እንደሆነ ይገልጻል። ፖሊስ ግን ተከሳሹ ድምጽ ያለው ጋዝ ከማስወጣቱም በላይ ለፖሊስ ተባባሪ አልነበረም ብሏል። ተከሳሹ ድርጊቱን የፈጸመው ፖሊስ በቁጥጥር ሊያውለው ወደ ነበረበት የሕዝብ መናፈሻ በመጣ ጊዜ ከተቀመጠበት የሕዝብ መናፈሻ አግዳሚ ወንበር ተነስቶ ነገርየዋን ሆን ብሎ፣ አስቦና አቅዶ፣ ድምጽ እንዲኖረው በማድረግ "ከባድ ጋዝ ማስወጣቱ" ተብራርቷል። ተከሳሹ የተጣለበትን ቅጣት ይክፈል አይክፈል፣ አልያም ይግባኝ ስለማለቱ የተባለ ነገር የለም።
49722056
https://www.bbc.com/amharic/49722056
የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ራማፎሳ በሌሎች አፍሪካውያን ላይ በደረሰው ጥቃት ማፈራቸውን ገለፁ
የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ሲሲል ራማፎሳ በቅርቡ መጤ ጠል በሆኑ የአፍሪካ ዜጎች ላይ የደረሰው ጥቃት እጅግ አድርጎ እንደሚያሳፍራቸው ለቢቢሲ ተናግረዋል።
የንግድ መናሃሪያ በሆነችው ጆሃንስበርግ መተዳደሪያቸው ንግድ የሆኑ ከሌሎች አፍሪካ አገር የመጡ ዜጎች ላይ የተደራጁ ቡድኖች ጥቃት አድርሰውባቸዋል፤ ንብረታቸውም ወድሟል። ጥቃቱ በሌሎችም ከተሞች ቀጥሎ ለብዙ ቀናት ቀጥሎ ነበር። የሃገሪቱ ባለስልጣን እንደገለፁት አስራ ሁለት ሰዎች ሲገደሉ፤ ከነሱም መካከል አስሩ ደቡብ አፍሪካውያን ናቸው ብለዋል። •በጆሀንስበርግ ፖሊስ ባካሄደው አሰሳ ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ 1200 ሰዎች ታሰሩ •ታዋቂ አፍሪካውያን ወደ ደቡብ አፍሪካ አንሄድም አሉ የቢቢሲው ዘጋቢ ሚልተን ኒኮሲ ፕሬዝዳንቱ "በጥቃቱ አፍረዋል ወይ ብሎ" ለጠየቃቸው ጥያቄ ሲመልሱ፤ "እንዴት አላፍርም፤ እኛ ደቡብ አፍሪካዊያን በአፓርታይድ ጊዜም ሆነ ከዚያ በኋላ ብዙ አገሮች አስጠልለውን እኛ በምላሹ እነሱን ስናጠቃ እንዴት አላፍርም" ብለዋል። አክለውም " ይህ ደቡብ አፍሪካ ከምትቆምበት እሴት የሚፃረር ነው፤ ህዝባችን ሌሎች የአፍሪካ ዜጎችን አይጠላም። አሁንም ቢሆን የሌሎች አገር ዜጎች መጥተው መስራት ይችላሉ። ዜጎቻችንም የሃገሪቱን ህግ እንዲያከብሩ እንፈልጋለን" ብለዋል። •በደቡብ አፍሪካው ዝርፊያ ከአርባ በላይ ሰዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ ራማፎሳ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ አሁንም ቢሆን የአፍሪካውያንነትና የፓን አፍሪካዊነት መንፈስ እንዳለም ለማስረዳትም መልዕክተኞችን ወደ ሰባት ሃገራት ልካለች። በቅርቡ የደረሰው ጥቃት ደቡብ አፍሪካ በአህጉሪቷ ላይ ያለውን ስሟን አጠልሽቶታል። በዚምባብዌ መዲና ሐራሬ ለቀድሞው ፕሬዚዳንት ስርአተ ቀብር የተገኙት ራማፎሳ ንግግር በሚያደርጉበትም ወቅት ከዚምባብዌውያን ዘንድ ተቃውሞ ገጥሟቸዋል።
54954051
https://www.bbc.com/amharic/54954051
ኮሮናቫይረስ ፡ የኮቪድ-19 ክትባት መሰጠት ሲጀምር ዓለም ወደ መደበኛ ኑሮው ይመለሳል ተባለ
በቅርቡ ይፋ ይደረጋል ተብሎ የሚጠበቀው የኮሮናቫይረስ ክትባት ከፍተኛ አውንታዊ ውጤት ስለሚኖረው በበሽታው ተጽእኖ የተመሳቀለው የዓለም ሕዝብ ህይወትን ከወራት በኋላ ወደ መደበኛው መስመር እንዲመለስ ያደርጋል ተባለ።
ክትባቱን ካዳበሩት ተቋማት መካከል አንዱ የሆነው ባዮኤንቴክ መስራች ከሆኑት አንዱ ፕሮፌሰር ኡጉር ሳሂን እንዳሉት፤ ክትባቱ የበሽታውን መስፋፋት በግማሽ እንደሚቀንሰው ተስፋ ከማድጋቸው በተጨማሪ፤ "በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሰዋል።" ባለፈው ሳምንት ባዮኤንቴክ እና አብሮት የሚሰራው ፋይዘር የተባለው የመድኃኒት አምራች ኩባንያ እንዳሉት፤ የመጀመሪያ ደረጃ የተደረገው ትንተና ክትባቱን ካገኙ ሰዎች መካከል ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑትን ከበሽታው እንደሚከላከል አመልክቷል። በሙከራው 43 ሺህ የሚደርሱ ሰዎች በክትባቱ ሙከራ ላይ መሳተፋቸውም ተገልጿል። ፕሮፌሰር ሳሂን ለቢቢሲ እንደተናገሩት ከትባቱ ወረርሽኙ ከሰው ወደ ሰው የመተላለፍ ሁኔታውን እንደሚቀንሰውና በተከተቡት ላይ የበሽታው ምልክቶች እንዳይከሰት የማድረጉን ሁኔታ ለመረዳት ተጨማሪ ክትትል ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል። ዩናይትድ ኪንግደም ከአንድ ወር በኋላ 10 ሚሊዮን የሚደርስ የባዮኤንቴክ/ፋይዘር ክትባትን የያዙ ብልቃጦችን የምታገኝ ሲሆን፤ በተጨማሪም 30 ሚሊዮን ብልቃጥ ክትባትም አዛለች። በሦስት ሳምንት ልዩነት ሁለት ጊዜ የሚሰጠው ክትባት በስድስት አገራት ውስጥ ተሞክሯል። በቀዳሚነት በአዛውንቶች መንከባከቢያዎች ውስጥ ያሉ በዕድሜ የገፉ ሰዎችና እንክብካቤ የሚሰጧቸው ሠራተኞች የሚያገኙ ሲሆን፤ በተከታይነትም የጤና ባለሙያዎችና ከ80 ዓመት በላይ የሚሆኑ ሰዎች ክትባቱን ያገኛሉ የተባለ ሲሆን፤ ከዚያም ሌሎች እንደየዕድሜያቸው ክትባቱ ይሰጣቸዋል ተብለወል። በዓለም የኮሮናቫይረስን በመከላከል ረገድ ውጤታማ ነው የተባለው ይህ ክትባት ይፋ ከተደረገ በኋላ፤ በኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ ታዋቂ የሕክምና ፕሮፌሰር የሆኑት ሰር ጆን ቤል፤ ከወራት በኋላ ህይወት ወደ መደበኛ ፍሰቷ ትመለሳለች ሲሉ ተስፋቸውን ገልጸዋል። "ምናልባትም ይህንን ያለ የመጀመሪያው ሰው ሳልሆን አልቀርም፤ ነገር ግን ይህንን የምለውም ባለኝ መተማመን ምክንያት ነው" ብለዋል። ክትባቱን በማዘጋጀት ሂደት ሰፊ ተሳትፎ ያላቸው ፕሮፌሰር ሳሂን ግን ረዘም ያለ ጊዜ ሊያስፈልግ ይችላል ብለዋል። ጨምረውም ሁሉም ነገር እንደታሰበው ከሄደ በሁለት ወራት ውስጥ ክትባቱ ለስርጭት ቀረወቦ አገልግሎት ላይ መዋል ይጀምራል። በተያዘው ዕቅድ መሰረትም አስከ መጪው ሚያዝያ ድረስም ከ300 ሚሊዮን በላይ የሚሆን ክትባት በዓለም ዙሪያ የሚሰራጭ ሲሆን "በዚህም ውጤት ማየት የሚጀመርበት ሁኔታ ይፈጠራል" ብለዋል። በሚቀጥለው የፈረንጆች ዓመትም ከወራት በኋላም የክትባቱ ውጤት የሚታይበት ሲሆን ክትባቱም በስፋት ቀርቦ በርካታ ሰው ለመከተብ የሚቻል ይሆናል ተብሏል።
news-55984270
https://www.bbc.com/amharic/news-55984270
የመረጃ መረብ ሰርሳሪዎች የፎሎሪዳን ውሃ ለመመረዝ ሞክረው ነበር ተባለ
በአሜሪካ የመረጃ መረብ ሰርሳሪዎች (ሃከርስ) የፍሎሪዳን የውሃ ሲስተም ዒላማ በማድረግ አደገኛ ኬሚካል ሊጨምሩ እንደነበር የአገሪቱ ባለሥልጣን ገለፁ።
እነዚህ የመረጃ መረብ ሰርሳሪዎች ፍሎሪዳ በሚገኘው ኦልድስማር የውሃ ማጣሪያ ውስጥ የጨመሩት አደገኛ ኬሚካል ሶዲየም ሃይድሮ ኦክሳይድ (lye) ሲሆን የድርጅቱ ሰራተኞቹ በፍጥነት የተከሰተውን በማስተዋል እርምጃ መውሰዳቸው ተገልጿል። ሶዲየም ሃይድሮ ኦክሳይድ (lye) በውሃ ውስጥ ያለውን አሲድ ለመቆጣጠር በአነስተኛ መጠን የሚጨምር ሲሆን ነገር ግን ከመጠን በላይ ከተጨመረ የጤና እክል ያስከትላል። የኦድስማር ከንቲባ የሆኑት ኤሪክ ሴይደል "መጥፎ ሰዎች አሉ" ብለዋል። ድርጊቱን ፈጽመዋል ተብለው ከተጠረጠሩ መካከል እስካሁን ድረስ በቁጥጥር ሥር የዋለ የሌለ ሲሆን የመረጃ መረብ መንታፊዎቹም መቀመጫቸውን አሜሪካ ይሆኑ በሌላ አገር የታወቀ ነገር የለም። የኦልድስማር የውሃ ማጣሪያ ቁጥጥር የሚደረግለት በኮምፒውተር በተደራጀ ስርዓት ሲሆን አርብ ዕለት ከርቀት ይህንን ስርዓቱን ዒላማ ያደረጉ መንታፊዎች ነበሩ ተብሏል። አርብ ማለዳ የማጣሪያው ሰራተኛ ከሆኑ ሰዎች መካከል አንዱ ይህንን በሌላ አካል የተደረገ ሙከራ ሲያስተውል የድርጅቱ ተቆጣጣሪዎች መስለውት እንደነበር ታምፓ ቤይ ታይምስ የተሰኘ መገናኛ ብዙኀን ዘግቧል። ነገር ግን ከሰዓት ሌላ ሙከራ የተካሄደ ሲሆን በዚህ ወቅት የመረጃ መረብ ሰርሳሪዎቹ የማጣሪያውን ሶፍትዌር ውስጥ በመግባት የሶዲየም ሃይድሮኦክሳይድ ይዘቱን እጅግ በጣም ከፍ እንዲል አድርገዋል። ወድያውኑ በወቅቱ ሥራ ላይ የነበሩ ተቆጣጣሪዎች መጠኑን ወደ መደበኛው እንዲቀንስ አድርገውታል። ሶዲየም ሃይድሮኦክሳይድ በዋነኛነት ፈሳሽ ማጽጃዎችን ለማምረት ያገለግላል። ይህ ኬሚካል በጣም አደገኛ ሲሆን ከተዋጠ አፍ፣ ጉሮሮ እና ሆድ እቃ ላይ ጉዳት በማድረስ ማስመለስ፣ ማቅለሽለሽ እንዲሁም ተቅማጥን ያስከትላል። በተጨማሪም ቆዳ እና አይንን የማቃጠል ባህሪ አለው። የፒኔላስ ካውንቲ ፖሊስ የሆኑት ቦብ ጉዋልቲየሪ " እኔ የኬሚስትሪ ባለሙያ አይደለሁም። ነገር ግን የማውቀውን እነግራችኋለሁ. . .ከፍተኛ መጠን ያለው ኬሚካል [ሶዲየም ሃይድሮኦክሳይድ] ውሃ ውስጥ ከጨመራችሁ ለጤና ጠንቅ ነው" ብለዋል። የኦልድስማር ውሃ ማጣሪያ ለ15 ሺህ ነዋሪዎች እንዲሁም ለተለያዩ የንግድ ተቋማት ውሃ ያቀርባል። በአሁኑ ወቅት በጊዜያዊነት የውሃውን ስርዓት ከርቀት መቆጣጠር የሚያስችለው ስርዓት እንዳይሰራ ተደርጓል። በ2016 ቨሪዞን የተሰኘ ተቋም ያወጣው ሪፖርት እንደሚያሳየው በአሜሪካ አንድ ስሙ ያልተገለፀ የውሃ ማጣሪያ ላይ ተመሳሳይ ጥቃት ተሰንዝሮበት ነበር። በ2020 ደግሞ በእስራኤል የውሃ ማጣሪያዎች ላይ የመረጃ መዝባሪዎች ተደጋጋሚ ሙከራ አድርገዋል። አሁን በፍሎሪዳ የደረሰው ጥቃት ለዓመታት "ወሳኝ በሆኑ የሕዝብ መገልገያዎች ላይ" ጥንቃቄ እንዲደረግ ሲወተውቱ ለነበሩ የመረጃ ደህንነት ተቋማትና ባልደረቦችን የበለጠ የሚያስጨንቅ ነው። ውሃ፣ መብራት፣የኒውክለር ማብላሊያዎች እና መጓጓዣዎች ጊዜያቸው ያለፈባቸው የኢንፎርሜሽን ቴክነሎጂዎችን በብዛት ስለሚጠቀሙ የመረጃ መረብ ደህንነታቸው ደካማ እና ተጋላጭ ነው፤ ይህ ደግሞ በእንድ ጊዜ የአገልግሎት መቋረጥ እንዲገጥም ያደርጋል ተብሎ ተሰግቷል።
news-54852596
https://www.bbc.com/amharic/news-54852596
የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ፅህፈት ቤት ሀላፊ ማርክ ሚዶውስ በኮሮና ተያዙ
የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ፅህፈት ቤት ሀላፊ ማርክ ሚዶውስ የኮቪድ-19 ምርመራ አድርገው ቫይረሱ እንደተገኘባቸው ባለስልጣናት ለአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን ገለጹ፡፡
የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ሳያደርጉ ሕዝብ በሚሰበሰብባቸው ዝግጅቶች ላይ ብዙ ጊዜ የሚታዩት ሚዶውስ እንዴት ቫይረሱ እንደያዛቸው ግልጽ አልሆነም፡፡ ኃላፊው በትራምፕ አስተዳደር ውስጥ ከሚሠሩ እና በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች መካከል አንደሱ ሲሆኑ በአሜሪካ 230,ሺህ የሚሆኑ ሰዎች በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸው አልፏል፡፡ አሜሪካ አርብ ከ127 ሺህ በላይ አዲስ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ያስመዘገበች ሲሆን ይህም ለሦስተኛ ተከታታይ ቀናት ከፍተኛ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ቁልፍ ርዕስ የነበረ ሲሆን ሰዎች ድምጻቸውን በፖስታ እና ቀደም ብለው በአካል እንዲሰጡ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ ከቀናት በፊት ሚዶውስ ከሲኤንኤን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ አሜሪካ "ወረርሽኙን ለመቆጣጠር አትችልም" ያሉ ሲሆን ኮቪድ-19 ማሸነፍ የሚቻለው በክትባት እና ህክምና ብቻ እንደሆነ አስታውቀዋል። ኃላፊው ቫይረሱ መጀመሪያ መቼ እንደተገኘባቸው ወይም የበሽታውን ምልክቶች ስለማሳየታቸው ግልጽ አልሆነም፡፡ እሳቸውም እስካሁን አስተያየት አልሰጠም፡፡ ሜዶውስ በምርጫ ዘመቻው የመጨረሻ ቀናት ከፕሬዚዳንቱ ጋር የተጓዙ ሲሆን በኋይት ሃውስ በደርዘን የሚቆጠሩ የትራምፕ ደጋፊዎች በተገኙበት የምርጫ ምሽት ግብዣ ላይም ነበሩ፡፡ ፕሬዝዳንት ትራምፕ፣ ባለቤታቸው ሜላኒያ እና ልጃቸው ባሮን ከኮቪድ-19 ተገኝቶባቸው እንዳገገሙ ይታወሳል። የብሄራዊ ደህንነት አማካሪው ሮበርት ኦብሪየን፣ ከፍተኛ አማካሪው ስቲፈን ሚለር እና የኋይት ሃውስ አማካሪ ሆፕ ሂክስም በተመሳሳይ ከቫይረሱ አገግመዋል፡፡
46901930
https://www.bbc.com/amharic/46901930
ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፡ "በብሔር ግጭት ወደ 900 ገደማ ሰዎች ተገድለዋል"
የተባበሩት መንግሥታት ባወጣው መረጃ መሰረት፤ በምዕራብ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በብሔር ግጭት ሳቢያ ቢያንስ 890 ሰዎች ተገድለዋል።
በግጭቱ ወደ 900 ሰዎች ገደማ መሞታቸውን የተባበሩት መንግሥታት ተናግሯል ባኑኑ እና ባቴንዴ በተባሉ ማኅበረሰቦች መካከል ግጭት የተከተሰተው ዩምቢ በሚባለው አካባቢ በሚገኙ አራት መንደሮች ውስጥ ነው። • በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የጤና ባለሙያዎች ጥቃት ደረሰባቸው የተባበሩት መንግሥታት እንዳለው፤ አብዛኞቹ የአካባቢው ነዋሪዎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል። ዩምቢ አካባቢ ባለው ግጭት ሳቢያ ለዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ሀገራዊ ምርጫ ድምጽ የሚሰጡት መጋቢት ላይ ይሆናል። የተባበሩት መንግሥታት እንዳለው፤ 465 ቤቶችና ህንጻዎች ተቃጥለዋል፤ ፈራርሰዋልም። ከነዚህ መካከል ሁለት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ የጤና ተቋም፣ ገበያ እና የሀገሪቱ ገለልተኛ የምርጫ ኮሚሽን ቢሮ ይገኙበታል። • ኮንጎ በታሪኳ አስከፊ በሆነው የኢቦላ ወረርሽኝ እየተናጠች ነው ከተፈናቀሉት ሰዎች 16,000 የሚሆኑት የኮንጎ ወንዝን ተሻግረው በኮንጎ ብራዛቪል ተጠልለዋል። የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብት ኮሚሽነር ሚሼል ባቼት፤ "ይህ አስደንጋጭ ግጭት ተመርምሮ ጥፋተኞቹ ለፍርድ መቅረብ አለባቸው" ብለዋል። ኮሚሽኑ ምርመራ መጀመሩም ተመልክቷል። ዩምቢ ለወትሮው ሰላማዊ ግዛት ነበር። በማኅበረሰቦቹ መካከል ግጭት የተቀሰቀሰው፤ የባኑኑ ማኅበረሰብ አባላት ባህላዊ መሪያቸውን በባቴንዴ መሬት ለመቅበር በመሞከራቸው ነበር። የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ምርጫን ፌሊክስ ቲስኬዲ ማሸነፋቸው ቢነገርም ሌላው ተቀናቃኝ ማርቲን ፋያሉ "አሸናፊው እኔ ነኝ" ማለታቸው ይታወሳል። • ኢቦላ በኮንጎ እየተዛመተ ነው ማርቲን ፋያሉ እንደሚሉት ከሆነ፤ ፌሊክስ ቲስኬዲ ምርጫውን ያሸነፉት ከቀድሞው ፕሬዘዳንት ጆሴፍ ካቢላ ጋር ተመሳጥረው ነው። ሕዝቡ የሰጠው ድምጽ ዳግመኛ ይቆጠር ሲሉም ለፍርድ ቤት አቤቱታ አሰምተዋል። የአፍሪካ ኅብረት የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን ጉዳይ በተመለከተ ዛሬ አዲስ አበባ ላይ ይመክራል።
news-48934581
https://www.bbc.com/amharic/news-48934581
ሲፒጄ ለኢትዮጵያዊያን ጋዜጠኞች መስጋቱን ገለጸ
ኢትዮጵያ ውስጥ እየታየ ያለው የመገናኛ ብዙሃንን የመቆጣጠርና ጋዜጠኞች የማሰር ሁኔታ ቀድሞ ወደነበረው ጭቆና እንዳይመለስ ስጋት እንዳለው ለጋዜጠኞች መብት የሚሟገተው ሲፒጄ ባወጣው ሪፖርት አመለከተ።
ሲፒጄ "ለውጥ እየተካሄደ ባለበት ወቅት የኢትዮጵያ ፕሬስን ለመቆጣጠር አሮጌውን ዘዴ እየተጠቀመች ነው" በሚል ባወጣው ሪፖርት የኢንትርኔት አገልግሎትን ማቋረጥና ጋዜጠኞችን ማሰርን እንደምክንያትነት ጠቅሷል። • አምነስቲ በቅርቡ የታሰሩ ጋዜጠኞች ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ መንግሥትን ነቀፈ ሰኔ 15 አማራ ክልል ውስጥ ተሞከረ የተባለውን መፈንቅለ መንግሥት ተከትሎ የኢንትርኔት አገልግሎት እንዲቋረጥ መደረጉና ሲፒጄ ጨቋኝ ነው ባለው የጸረ ሽብርተኛነት ሕግ አማካይነት ቢያንስ ሁለት ጋዜጠኞች መታሰራቸው ከግንቦት ወር ወዲህ እየታየ ያለ ክስተት መሆኑን አመልክቷል። ከኢንትርኔት መቋረጥ በተጨማሪ ባለፉት ሁለት ወራት ባለስልጣናት በርካታ ጋዜጠኞችን እንዳሰሩ የጠቀሰው ሲፒጄ ሐምሌ አንድ ደግሞ የመከላከያ ሚኒስቴር "በሠራዊቱና በሕዝቡ መካከል አለመተማመንን በሚፈጥሩ ባላቸው ግለሰቦችና የመገናኛ ብዙሃን ላይ ክስ ለመመስረት እንዳቀደ መግለጹን ጠቅሷል። በአሁኑ ወቅት በእስር ላይ ይገኛሉ ያላቸውንና ቀደም ሲል የታሰሩ ጋዜጠኞችን በሪፖርቱ ላይ በስም የጠቀሰው የሲፒጄ ሪፖርት በመንግሥት በኩል እየተወሰደ ያለውን እርምጃ በተመለከተም በጋዜጠኝነት የተሰማሩና ለሙያው ቅርብ የሆኑ ሰዎች የተፈጠረባቸውን ስሜት አካቷል። • የሴቶች የቆዳ ክሬሞች የደቀኑት አደጋ መንግሥት ከቆየው ልማዱ ለመላቀቅ እየታገለ ወይም በጋዜጠኞች ላይ አዲስ ዙር ጥቃት እየከፈተ ሊሆን እንደሚችል በመጥቀስ በርካታ ጋዜጠኞች ስጋታቸውን ገልጸዋል። በተጨማሪም ይህ ሁኔታ በዚሁ የሚቀጥል ከሆነ የሃገሪቱ መገናኛ ብዙሃን የወደፊት ዕጣ ፈንታን አሳሳቢ ያደርገዋል ብለዋል። ጉዳዩን በተመለከተ ሲፒጄ ምላሽ እንዲሰጡት ያናገራቸው የመንግሥት ቃል አቀባይ ስለታሰሩት ጋዜጠኞች ዝርዝር መረጃ እንደሌላቸው ተናግረው ነገር ግን ተሞክሯል ከተባለው መፈንቅለ መንግሥት ጋር በተያያዘ በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ውስጥ የተለያዩ ሰዎች ላይ ባለስልጣናት ምርመራ እያደረጉ እንደሆነ ገልጸዋል። ቢለኔ ስዩም በተወሰኑ የታሰሩ ሰዎች ጉዳይ ላይ አስተያየት ያልሰጡ ቢሆንም ግን የታሰሩ ጋዜጠኞችን በተመለከተ ሁሌም ከሥራቸው ጋር በቀጥታ የተገናኘ እንዳልሆነ ጠቅሰው፤ መንግሥት ለመገናኛ ብዙሃን በከፍተኛ ደረጃ አመቺ ሁኔታን ለመፍጠር ቁርጠኛ መሆኑን እንደገለጹ ሲፒጄ በሪፖርቱ ላይ ጠቅሷል።
news-57230081
https://www.bbc.com/amharic/news-57230081
ኮሮናቫይረስ፡ የሕንዱ ድርጅት በኮቪድ-19 ለሞቱ ሠራተኞቹ ቤተሰቦች ካሳ ሊከፍል ነው
በሕንድ አንድ የብረት ማምረቻ ድርጅት በኮቪድ-19 ሳቢያ ለሞቱ ሠራተኞቹ ቤተሰቦች ካሳ እንደሚከፍል አስታወቀ።
ይህን ያለው በሕንድ ከትላልቅ የብረት ፋብሪካዎች አንዱ የሆነው ታታ ስቲል ነው። ድርጅቱ የሞቱ ሠራተኞቹ የጡረታ እድሜ [60 ዓመት] እስከሚደርስ ደመወዝ፣ የቤትና የሕክምና ጥቅማ ጥቅም እከፍላለሁ ብሏል። ከዚህም በተጨማሪ ለግንባር ቀደም ሠራተኞቹ ልጆች እስከሚመረቁ ድረስ የትምህርት ክፍያ እንደሚከፍል ቃል ገብቷል። ሕንድ ወረርሽኙ ከተከሰተ አንስቶ 300 ሺህ ሰዎችን በቫይረሱ አጥታለች። ባለሙያዎች ግን ቁጥሩ ከዚህም ሊበልጥ እንደሚችል ይናገራሉ። ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ ታታ ስቲል በዚህ አስፈሪ ወረርሽኝ ወቅት በተቀጠፉ ውድ ሠራተኞቹ ማዘኑን ገልጾ ከቤተሰቦቻው ጎን እንደሚቆም ገልጿል። በእርግጥ ታታ ስቲል ይህን ያለ የመጀመሪያው ድርጅት አይደለም። ባለፈው ሳምንት የሆስፒታል ግሩፕ ኦዮ ሩምስ በኮሮናቫይረስ ሳቢያ የሞቱ ሠራተኞቹን ቤተሰቦች በተለያየ መንገድ እንደሚረዳ ገልጾ ነበር። ኦዮ ሩምስ ቃል የገባው ድጋፍ የስምንት ወር ደመወዝ ክፍያን እና የአምስት ዓመት የልጆቻቸውን የትምህርት ክፍያ ይጨምራል ብሏል። የድርጅቱ መሥራች ሪተሽ አጋርዋል በትዊተር ገጻቸው ላይ በተከታታይ ባሰፈሩት ጽሁፍ "ኮቪድን ለመከላከል የሚደረገው ትግል ከአቅም በላይ ሆኗል፤ ነገር ግን እንዲህ ዓይነት በጎ ተግባራት የቤተሰቦቻቸውን ችግር ያስወግዳሉ" ብለዋል። በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ብርጭቆ አምራች ድርጅቱ- ቦሮሲል በኮቪድ-19 ለሞቱ ሠራተኞቹ ለሁለት ዓመታት ደመወዝ እንደሚከፍል ቃል ገብቷል። የድርጅቱ ዳሬክተር ሽሪቫር ኬሩራ በሊንክድን ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ ድርጅቱ በኮቪድ-19 በሞት ለተለዩዋቸው ሠራተኞቻቸው ልጆች የትምህርት ወጪ እንደሚከፍል ገልጸዋል። እነዚህ ድርጅቶች ይህንን ያስታወቁት አገሪቷ በበሽታው በርካታ ዜጎቿን በማጣቷ ምጣኔ ሀብታዊ ቀውስ ውስጥ መግባቷን ተከትሎ ነው። ሁለተኛው ዙር የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ባለፉት ጥቂት ሳምንታት በአገሪቷ የጤና ሥርዓት ላይ የከፋ ጉዳት አድርሷል። ከአቅማቸው በላይ የተጨናነቁት የሕክምና ተቋማትም በቫይረሱ ተይዘው ወደ ተቋማቸው የሚመጡ ህሙማንን ለመመለስ ተገደዋል። በበርካታ ቦታዎች ወሳኝ የሆኑ መድሃኒቶችና የኦክስጅን አቅርቦት የለም። የአስክሬን ማቃጠያ ቦታዎችም ሞልተዋል። በዚህ ሳምንት ሕንድ በአጠቃላይ ከ300 ሺህ በላይ ሞት በመመዝገብ ከአሜሪካና ከብራዚል ቀጥሎ ከዓለም ሦስተኛዋ አገር ሆናለች። በሕንድ 26 ሚሊየን ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሲሆን ከአሜሪካ ቀጥላ በሁለተኛነት ተቀምጣለች። አሁን ላይ ሕንድ የዓለማችን የወረርሽኙ ማዕከል ሆናለች።
news-47664119
https://www.bbc.com/amharic/news-47664119
የፌስቡክ ተጠቃሚዎች የይለፍ ቃል ደህንነት አስተማማኝ አይደለም ተባለ
በሚሊዮን የሚቆጠሩ የፌስቡክ ተጠቃሚዎችን የይለፍ ቃል 20 ሺህ በሚሆኑ ፌስቡክ ውስጥ በሚሰሩ ሰዎች ይታወቁ እንደነበር ይፋ ሆነ።
የኢንተርኔት ደህንነት ተመራማሪው ብሬይን ክሬብስ ፌስቡክ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ ረገድ ችግር እንዳለበት አጋልጧል። በጥናቱ መሰረት 600 ሚሊዮን የሚሆኑ የደንበኞች የይለፍ ቃል ምንም አይነት ጠጥበቃ ሳይደረግላቸው እንዲሁ ተጽፎ ለማንም ግልጽ በሆነ መልኩ እንደሚገኝ ተናግሯል። እነዚህ የይለፍ ቃሎች ከፈረንጆቹ 2012 ጀምሮ የተከፈቱ ናቸውም ብሏል። ፌስቡክ ይህን ተከትሎ ሁሉንም የይለፍ ቃሎች በአንድ ቋት ውስጥ ለማስቀመጥ እየሰራሁ ነው በማለት ለማስተባበል ሞክሯል። • ፌስቡክ የተጠቃሚዎችን ግላዊ መረጃ መበርበሩን አመነ ክሬብስ ከፌስቡክ ሰራተኛ አገኘሁት ባለው ተጨማሪ መረጃ መሰረት፤ እንደዚህ አይነት ችግሮች ያጋጠሙት መተግበሪያውን የሚያበለጽጉት ሰዎች መጀመሪያውኑ የይለፍ ቃሉ ወደ ሚስጥራዊ ኮድ እንዳይቀየር አድርገው ስለሚያዘጋጁት ነው ብሏል። የፌስ ቡክ ኢንጂኔር ሰኮት ሬንፍሮ እንደሚሉት ችግሮቹ ምን እንደሆኑ ለመለየት ጥረት አድርገናል መፍትሄውንም እናመጣለን ብለዋል። መረጃው እንደሚያሳው አብዛኛዎቹ የዚህ ችግር ተጋላጮች የፌስቡክ ላይት ተጠቃሚዎች ናቸው። ኩባንያው ለሮይተርስ በሰጠው ቃል መሰረት "በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠሩ የፌስቡክ ላይት ተጠቃሚዎች፣ በአስር ሚሊዮን የሚቆጠሩ የሌላ ፌስቡክ ተጠቃሚዎችና በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የኢንስታግራም ተጠቃሚዎች የችግሩ ተጋላጮች ናቸው።" • ፌስቡክ የምንጠቀምበት ሰዓት ሊገደብ ነው ቢሆንም ግን ቀጥሎ ሊመጣ የሚችለው መፍትሄ የይለፍ ቃልን እንደገና መቀየር ሊሆን ይችላል ተብሏል። የፌስቡክ መግቢያ (Log in) ደህንነቱ የተጠበቀ አይደለም በማለት ባለፉት ጊዜያት የተለያዩ የዜና ምንጮች ሲተቹት ቆይተዋል። መስከረም ወር ላይ የ50 ሚሊዮን ፌስቡክ ተጠቃሚዎች መረጃ ተጋላጭ ሆኖ እንደነበርም ይታወሳል። በ2018 መጀመሪያ አካባቢም በሚሊዮን የሚቆጠሩ የፌስ ቡክ ተጠቃሚዋች መረጃ በካምብሪጅ የመረጃ ሳይንስ ኩባንያ እየተጠና መሆኑንም ፌስቡክ ገልጾ ነበር። ፌስቡክ ላይ ያለን ግላዊ መረጃን እንዴት መጠበቅ ይቻላል?
news-41847186
https://www.bbc.com/amharic/news-41847186
ለካ እንቅልፍ እንዲህ ጠቃሚ ነገር ኖሯል?
ስለ እንቅልፍ ጥቅምና ጉዳት ምን ያህል እናውቃለን? ከጤናችን፣ ከባህሪያችን እንዲሁም ከዕድሜያችን ጋር ስላለው ግንኙነትስ? እስቲ ስለእንቅልፍ እኒህን አስር ጠቃሚ ነጥቦች እንንገርዎ. . . 1. ለ 8 ሰዓታት መተኛት
ብዙ ጊዜ በአንድ ቀን ቢያንስ ለስምንት ሰዓታት መተኛት እንዳለብን ሲነገር እንሰማለን። ግን ይህ መረጃ ከየት የመጣ ነው? የእንቅልፍ እጥረት አለባቸው የምንላቸው ከስድስት ሰዓት ያነሰ እንቅልፍ የሚያገኙ ሰዎችን ሲሆን ከልክ በላይ የሆኑቱ ደግሞ ከዘጠኝ እስከ አስር ሰዓት የሚያንቀላፉ ሰዎች ናቸው። ጥናቶች እንደሚያመለከቱት የእንቅልፍ እጥረት ያለባቸው ሰዎችም ሆኑ ከልክ በላይ እንቅልፍ የሚያገኙ ሁለቱም ለተለያዩ በሽታዎች ተጋላጭ ናቸው። ታዳጊዎች እስከ 11 ሰዓታት ድረስ እንዲተኙ ሲመከር ጨቅላ ሕፃናት ግን በተለየ ሁኔታ እስከ 18 ሰዓታት ድረስ እንዲተኙ ይመከራል። የደብሊን ስላሴ ኮሌጅ ፕሮፌሰር ሼን ኦማራ እንደሚናገሩት "እንዳንድ ጊዜ እንቅልፍ እጦት ለጤና መቃወስ ምክንያት ይሁን ወይስ ምልክት መለየት እጅግ አዳጋች ነው።" የማይካደው ሐቅ ግን በተከታታይ የእንቅልፍ እጦት የሚያጋጥማቸው ሰዎች ለጤና መቃወስ እጅጉን የተጋለጡ ናቸው። 2. እንቅልፍ እጦት እና ሰውነታችን እንቅልፍ እጦት ለጤና መታወክ ብቻ ሳይሆን ለበርካታ መዛባቶች የሚያጋልጥ እንደሆነ በርካታ ጥናቶች ይጠቁማሉ። 5 ሚሊዮን ያህል ሰዎች የተሳተፉባቸው153 ጥናቶች እንዳመለከቱት በቂ እንቅልፍ የማያገኙ ሰዎች ለስኳር በሽታ፣ ደም ግፊት፣ ከልብ ጋር ለተያያዙ በሽታዎች እንዲሁም ከልክ ላለፈ ውፍረት ተጋላጭነታቸው የሰፋ ነው። በጥናቱ ላይ ከተሳተፉት መካከል ከሰባት ሰዓታት ያነሰ እንቅልፍ እንዲያገኙ የተደረጉ ሰዎች ለብርድ በሽታ የመጋለጥ ዕድላቸው ከፍ ብሎ ተገኝቷል። ቁጣ ቁጣ ማለት፣ የአዕምሮ ችግር፣ እንዲሁም ከልክ በላይ ውፍረት ዋነኞቹ ችግሮች ሆነው ተገኝተዋል። እንቅልፍ ያጠራቸው ሰዎች ሁኔታውን በመድሃኒት ለመመከት በሞከሩ ቁጥር ሰውነታቸው በሽታን ለመቋቋም ያለው አቅም እንደሚዳከምም ነው ጥናቶች የሚያስረዱት። ከልክ በላይ እንቅልፍ መተኛትም የራሱ የሆኑ መዘዞች እንዳሉት አጥኚዎቹ ያሰምራሉ። ትልቁ የእንቅልፍ ማብዛት መዘዝ የማመዛዘን ችግር እንደሆነ ፕሮፌሰር ሼን ኦማራ ያስረግጣሉ። 3. እንቅልፍ በደረጃ እንቅልፍ ከ60 እስከ 100 ደቂቃዎች ርዝማኔ ያላቸው ደረጃዎች አሉት። የመጀመሪያው ደረጃ በመተኛት እና አለመተኛት መካከል የሚገኝ ሰውነታችን ቀስ በቀስ ለቀቅ እያለ የሚመጣበት ክፍል ነው። ሁለተኛው ክፍል ደግሞ በዝግመት ሙሉ በሙሉ ወደ እንቅልፍ የምንገባበት ነው። ሶስተኛው ደረጃ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ የምንተኛበት ክፍል ሲሆን ሰውነታችን ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ከሌሎች እንቅስቃሴዎች ውጭ የሚሆንበትና መነሳት የሚባል ነገር የማይታሰብበት ወቅት ነው። ሰዎች በየዕለት ዕለት የእንቅልፍ ጊዜያቸው በእነዚህ ደረጃዎች ሥር የሚያልፉ ሲሆን የደረጃዎቹ መዛባት ለጤና መታወክ ሚና እንዳለውም ይነገራል። 4. የፈረቃ ሥራ እና እንቅልፍ የፈረቃ ሥራ ብዙ ጊዜ ለበርካታ የጤና እክሎች ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ይነገራል። አጥኚዎች እንደሚሉት ከልክ በታች እንቅልፍ የሚያገኙ የፈረቃ ሠራተኞች ከልክ ላለፈ ውፍረትና ለስኳር በሽታ ራሳቸውን አሳልፈው እየሰጡ ነው። እንዲያም ሆኖ በፈረቃ ሥራ ሕይወታቸውን የሚመሩ ሰዎች ሙሉ በመሉ ለበሽታ የተጋለጡ ናቸው ማለት አይደለም። ለረዥም ጊዜ ያለምንም በሽታ መጠቃት የሚቆዩ እንዳሉም ጥናት ይዘግባል። 5. ከጊዜ ጊዜ የእንቅልፍ እጦት እያጠቃን ነው ወይስ. . .? እንቅልፍ እጦት እያስቸገረዎት ነው ተብለው ቢጠይቁ ምላሽዎ በእርግጥ ሊሆን እንደሚችል አያጠራጥርም። በ15 ሃገራት የተደረገው ጥናት ግን ከዚህ ተቃራኒ የሆነ መረጃ ይዞ ብቅ ብሏል። ስድስት ሃገራት የእንቅልፍ ጊዜ ማጠር ሲስተዋልባቸው ሰባቱ ሃገራት ውስጥ ሰዎች የተሻለ እንቅልፍ እያገኙ ነው፤ የተቀሩት ሁለት ሃገራት ዜጎች ደግሞ የተመጣጠነ እንቅልፍ ያገኛሉ። 2ሺህ እንግሊዛውያን ወጣቶችን አካቶ የተደረገ ጥናት እንደሚያሳየው ሴቶች ከወንዶች በተለየ የእንቅልፍ እጦች ችግር አለባቸው። አልፎም ካፌይን እና አልኮልም የራሳቸውን አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደሩ እንደሆነ ሳይረሳ። በተለምዶ ምሽት ላይ የምናደርጋቸው እንደ ቴሌቪዥን መመልከት፣ ተንቀሳቃሽ ስልክ መጠቀም እና ወጥቶ መዝናናት ያሉ እንቅስቃሴዎችም በቂ እንቅልፍ ላለማግኘት ትልቅ ሚና አላቸው። 6. ወደኋላ "ከመቶ ዓመታት በፊት የነበረው ትውልድ በአንድ ቀን ውስጥ ሁለት የመኝታ ጊዜዎች ነበሩት" ሲሉ በቨርጂኒያ የታሪክ ፕሮፌሰሩ ሮጀር ኤክሪች ያስረዳሉ። በፕሮፌሰሩ ሃሳብ የማይስማሙ ሳይንቲስቶች ግን የኤሌክትሪክ ብርሃን በሌለበት ጊዜ የኖሩ አዳኝ ሰዎች በቀን አንድ ጊዜ ብቻ ነበር የሚተኙት ሲሉ ይከራከራሉ። ይህም የሰው ልጅ ከቀደመው ጊዜ ጀምሮ የእንቅልፍ ሥነ-ሥርዓቱ ተመሳሳይ እንደነበርና ብዙም እንዳልተለወጠ ያሳያል። 7. ተንቃሳቃሽ ስልክ፣ እንቅልፍና ታዳጊዎች የእንቅልፍ ባለሙያዎች እንደሚያስረግጡት በአስራዎቹ ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ታዳጊዎች በአንድ ቀን ቢያንስ የ10 ሰዓታት እንቅልፍ ማግኘት አለባቸው። እውነታው ግን ቢያንስ ግማሽ የሚያህሉት እንኳ በዚህ መጠን እንቅልፍ እያገኙ አይደለም። መኝታ ክፍሎች እንቅልፍ በሥርዓቱ የምናገኝባቸው ቦታዎች ሊሆኑ ሲገባ ተንቀሳቃሽ ስልክና ላፕቶፕ የመሳሰሉ ቴክኖሎጂዎች እንቅልፍ እያሳጡን ነው። በተለይ ደግሞ በአስራዎቹ ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ታዳጊዎችን። 8. የእንቅልፍ መዛባት ሕክምና አሁን አሁን በርካታ ሰዎች በእንቅልፍ መዛባት ችግር ምክንያት እርዳታ በመሻት ወደ ሕክምና መስጫ ቦታዎች እየነጎዱ አንደሆነ ይነገራል። ምክንያቱ በርካታ ሊሆን ቢችልም ዋነኛው ግን ከልክም በላይ ውፍረት እንደሆነ ነው አጥኚዎቹ አሁንም አጽንዖት ሰጥተው የሚናገሩት። ዶክተሮች ከጊዜ ወደ ጊዜ ለታካሚዎች የእንቅልፍ መድሃኒቶችን ማዘዝ ማቆም ጀምረዋል። ከዛ ይልቅ ተከታታይ ሕክምና አዋጭ መላ ሆኖ ተገኝቷል። ሆኖም አሁንም በርካቶቸ የእንቅልፍ መድሃኒቶችን ለችግሩ መከላከያ መላ አድርገው ይጠቀማሉ። 9. በሃገራት መካከል ያለው ልዩነትስ. . . ? ኢንዱስትሪ በተስፋፋባቸው 20 ሃገራት የተካሄደ ጥናት እንደሚያትተው ከሞላ ጎደል በሃገራቱ መካከል ያለው የእንቅልፍ ዘይቤ ተመሳሳይነት አለው። ጥናቱ እንደሚጠቁመው የሥራ ሰዓት፣ ትምህርት ቤት፣ እና የመዝናኛ ጊዜ ከተፈጥሯዊው የብርሃን ዑደት በበለጠ ሁኔታ የሰዎች የእንቅልፍ ስርዓት ላይ ተጽዕኖ አለው። የኤሌክትሪክ አቅርቦት በሌለባቸው የታንዛኒያ፣ ናሚቢያ እና ቦሊቪያ አካባቢዎች የተደረገ ሌላ ጥናት ደግሞ ሰዎች በአማካይ 7.7 ሰዓት እንቅልፍ ያገኛሉ። ይህም ኢንዱስትሪ ከተስፋፋባቸው ሃገራት ብዙም ልዩነት ያለው አይደለም። 10. የምሽት ወይስ የጠዋት ሰው ኖት. . . ? በጥዋት ነቅተው ቀናቸውን የሚጀምሩ ሰዎች መኖራቸውን ያህል ሌሊቱን ሙሉ እንቅልፍ በዓይናቸው ሳይዞር የሚነጋ ሰዎች ደግሞ ያጋጥሙናል። መብራት እንቅልፍ ሳይተኙ ሌሊቱን ለሚያሳልፉ ሰዎች ትልቅ እፎይታን ፈጥሯል። ለጥናት ታስቦ መብራት ወደሌለበት ሥፍራ የተወሰዱ ሰዎች በ48 ሰዓታት ጊዜ ውስጥ ቀድመው ከሚተኙበት ጊዜ በሁለት ሰዓታት አስቀድመው ወደ መኝታቸው አምርተዋል። ጊዜ በገፋ ቁጥርም ሰዎች ፀሓይ ስታዘቀዝዝቅ ወደ መኝታቸው መሄድ ተያያዙት። ዋናው ነጥብ ሰውነታችን የሚከተለውን ተፈጥራዊ ሂደት በሰው ሰራሽ አምፖል መመከቱ የሚመከር አይደለም ሲሉ አጥኚዎቹ ያሰምራሉ።
news-46265538
https://www.bbc.com/amharic/news-46265538
ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው ከጠበቃቸው ጋር ፍርድ ቤት ቀረቡ
መንግሥት ጠበቃ ያቁምልኝ የሚለውን ጥያቄ ያልተቀበለው ፍርድ ቤት የራሳቸውን ጠበቃ እንዲያቆሙ በወሰነው መሠረት ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው ከጠበቃቸው ጋር ዛሬ ከሰዓት በኋላ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 10ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበዋል።
ጠበቃቸው ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዱት ደንበኛቸውን በፖሊስ ታጅበው ካልሆነ ለብቻቸው ማግኘት ስላልቻሉ ለብቻቸው እንዲያገኟቸው እንዲያደርግ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል። ዳኛው በበኩላቸው ጠበቃው ያለ ፖሊስ ደንበኛቸውን ሊያገኙ እንደሚገባና፤ የፖሊስ ሚና ደህንነትን የማስጠበቅ ብቻ እንደሆነ ገልፀዋል። ጠበቃቸው ከሜጀር ጀነራሉ ጋር በፍርድ ቤቱ ውስጥ ለብቻቸው እንዲወያዩም ፈቅደውላቸዋል። የአቶ ክንፈ ጠበቃ የደንበኛቸው ጉዳዩ በፍርድ የተያዘ ሆኖ ሳለ እስከ ትናንት ድረስ በዶክመንተሪና በተለያዩ መንገዶች በሚዲያ መተላለፉ ፍትሀዊ ዳኝነት የማግኘት ዕድላቸውን በሚያጠብ መልኩ እንደሆነና አሁንም አግባብ ባልሆነ መንገድ ሚዛናዊ ያልሆኑ የሚዲያ ሽፋኖች እየተሰጡ እንደሚገኙ አውስተዋል። ፍርድ ቤቱ በበኩሉ ዘገባዎችን በተመለከተ ዝርዝር ማስረጃ በማቅረብ ራሱን የቻለ ክስ ሊቀርብ ይችላል፤ በዚህ ችሎት ግን የሚታይ አይሆንም ሲል ምላሽ ሰጥቷል። • ሜጀር ጄኔራል ክንፈ: ‘‘ቤት የለኝም፣ መኪና የለኝም፣ ንብረት የለኝም፤ ያለኝ ሰውነቴ ብቻ ነው’’ • ኤርትራ ላይ የተጣለው ማዕቀብ ተነሳ • የህግ የበላይነት ሳይሸራረፍ እንዲተገበር የሚጠይቀው የትግራይ ክልል መግለጫ አቶ ተስፋዬ ኡርጌ በሰኔ 16ቱ የቦምብ ፍንዳታ የተጠረጠሩት አቶ ተስፋዬ ኡርጌ አዲስ የሙስናና የሰብዓዊ መብት ጥሰት ክሶች ቀርበውባቸዋል። ከቀረቡባቸውም የሰብአዊ መብት ጥሰቶች መካከል ሰዎች በካቴና እየታሰሩ ቆሻሻ ቦታ ላይ እንዲጣሉ፣ በጉንዳን እንዲበሉ፣ በሽብርተኝነት ተጠርጥራችኋል በሚል ከግለሰቦች ገንዘብ በመውሰድ፤ መልምለው ወደ ኤርትራ በመላክ ሽብርተኛ ማስባል ወንጀሎች ተጠቅሰውባቸዋል። ከዚህም በተጨማሪ ግለሰቦችን ከአምስት ወር ላላነሰ ጊዜ በይፋ የማይታወቁ ሕገወጥ ስውር ቤቶች ውስጥ እንዲታሰሩ አድርገዋል የሚል ተጨማሪ ክስ ቀርቦባቸዋል። ግለሰቦች ታስረውም ሰብዓዊ መብታቸው እንዲገፈፍ በማድረጋቸው፤ ብዙዎች አካል ጉዳተኛ ከመሆን በተጨማሪ እንዲሞቱ ምክንያት እንደሆኑም ተገልጿል። አቶ ተስፋየ ኡርጌ በበኩላቸው ማንንም አስረውም ሆነ ገርፈው እንደማያውቁና፤ ሀብትም ቢሆን ሕገ መንግሥት ከፈቀደላቸው ሀብት የማፍራት መብት በላይ ሌላ የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ገልፀዋል። የግራ ቀኙን ክርክር ያዳመጠው ፍርድ ቤት በአቶ ተስፋዬ ኡርጌ ላይ ፖሊስ የጠየቀውን 14 ተጨማሪ ቀናት ፈቅዷል። ሰዎችን በማስፈራራት በቁጥጥር ሥር የዋሉት የኢትዮቴሎኮም የሴኪውሪቲ ዲቪዥን ኃላፊ ኮሎኔል ጉደታ ኦላናም የመንግሥት ሠራተኛ በመሆናቸው በራሳቸው ጠበቃ ማቆም እንደማይችሉ ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል። አራተኛው ተከሳሽ የሆኑት ኮሎኔል ሰጠኝ ካህሳይም በወር የሚያገኙት 5ሺህ ብር መሆኑን ጠቅሰው ጠበቃ ማቆም እንደማይችሉ ተከራክረዋል። አቶ ኢሳያስ ዳኘው ከዚህ ቀደም በራሳቸው ጠበቃ ማቆም እንደማይችሉ ለተናገሩት የሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው ወንድም አቶ ኢሳያስ ዳኘው ፖሊስ አለኝ ያለውን ማስረጃም አቅርቦ ለፍርድ ቤቱ አሰምቷል። በራሳቸው ስም በፀረ ሙስና ኮሚሽን የሐብት መዝገብ ቅፅ ላይ ራሳቸው ያስመዘገቡት ዝርዝር 2 ሚሊየን ብር የሚያወጣ ባለ አንድ ፎቅ ቤት በራሳቸው ስም የተመዘገበ፣ በባለቤታቸው ስም የተመዘገበ 6 ክፍል ያለው ቤት፣ 115 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ የጋራ ሕንጻ፣ 240ሺህ ብር የሚያወጣ ቶዮታ ኮሮላ፣ ግምቱ 1 ሚሊዮን ሁለት መቶ ሺ የሆነ ሎደር፣ የአንበሳ ባንክ ባለድርሻ፣ በንግድ ባንክ፣ በዳሸንና በአዋሽ ባንክ በርካታ ገንዘብ መቆጠባቸውን ማረጋገጡን ፖሊስ ተናግሯል። ፖሊስ ግለሰቡ ከሀገር ሊሸሹ ሲሉ አየር መንገድ ላይ በቁጥጥር ሥር እንዳዋላቸው ጠቅሷል። የተከሳሽ ጠበቃ በበኩላቸው ሀብቱ የተመዘገበው በ2003 ዓ.ም መሆኑን ጠቅሶ አሁን ሀብቱ ለሌላ ተላልፎ ወይም ተሽጦ መሆን አለመሆኑን በተጨባጭ ስለማያሳይ የተከላካይ ጠበቃው አገልግሎት መቀጠል አለበት ሲል ተከራክሯል። ባለቤታቸው በንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩ እንደሆኑና ሎደሩም የባለቤታቸው ነው በማለትም አስረድቷል። ፖሊስ በበኩሉ ሀብቱ በ2003 ቢመዘገብም በየሁለት ዓመቱ ሀብቱ መኖር አለመኖሩን የማሳወቅ ወይም የማደስ ኃላፊነት ነበረባቸው፤ ይህንን ካላደረጉ ንብረቱ እንዳለ ነው የሚቆጠረው በማለት ተከራክሯል። በተጨማሪም የባልና ሚስት ሐብት የጋራ ሀብት ነው ይህንንም ራሳቸው መዝገብ ያሰፈሩት በፈቃዳቸው ነው ሲል አስረድቷል። ፍርድ ቤቱም ተከሳሽ በቂ ሀብት ስላላቸው ከዛሬ ጀምሮ መንግሥት ያቆመላቸው ጠበቃ ተነስቶ በራሳቸው ጠበቃ በማቆም እንዲከራከሩ ውሳኔ አስተላልፏል። ፖሊስም በፍርድ ቤቱ ፊት በሀሰት ምለው የግል ጠበቃ ለማቆም ገንዘብ የለኝም በማለታቸው አስተማሪ ቅጣት እንዲጣልባቸውም ጠይቋል። ፍርድ ቤቱ መርማሪ ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜን ፈቅዷል።
56954702
https://www.bbc.com/amharic/56954702
ቢያንስ 15 ሰዎች በተገደሉበት ጥቃት ታጣቂዎች "ሰዎችን በቋንቋ ችሎታ ለይተዋል"
ትናንት ቢያንስ 15 ሰዎች በተገደሉበት ጥቃት ሰዎች ከአውቶብስ ወርደው በቋንቋ ችሎታቸው መለየታቸውን አንድ የዓይን እማኝ ለቢቢሲ ተናገሩ።
ቡሬ ከተማ ከፍኖተ ሰላም ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ ትገኛለች ከምዕራብ ጎጃም ቡሬ ከተማ ወደ ነቀምት መስመር ሲጓዝ በነበረ የሕዝብ ማመላለሽ አውቶብስ ላይ በተፈጸመ ጥቃት ቢያንስ 15 ሰዎች መገደላቸውን ኢቢሲ ፖሊስ ጠቅሶ ዘግቧል። የሆሮ ጉዱሩ ዞን ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ብርሃ የባሳ ለብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያው፤ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ተሳፋሪዎችን ከአውቶብስ እንዲወርዱ ካደረጉ በኋላ ቢያንስ 15 ሰዎች ተገድለዋል ሲሉ ተናግረዋል። ከሟቾች በተጨማሪ በጥቃቱ የተጎዱ ሰዎች ስለመኖራቸው ጠቅሰው፤ ድርጊቱ እየተጣራ ነው ብለዋል። የፖሊስ አዛዡ ከሟቾቹ መካከል የኦሮሞ እና የአማራ ብሔር ተወላጆ ይገኙበታል ብለዋል። የዓይን እማኙ ምን ይላሉ? ቢቢሲ ያነጋገራቸው የዓይን እማኝ በአውቶብሱ ተሳፍረው የነበሩት አብዛኛዎቹ ተሳፋሪዎች መዳረሻቸው ምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ ውስጥ ወደምትገኝ ጉትን ከተማ መሆኑን ያስረዳሉ። ጉትን ከተማ ከነቀምቴ ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ የምትገኝ ሲሆን በርካታ የአማራ ብሔር ተወላጆች የሚኖሩባት አስተኛ ከተማ ነች። የዓይን እማኙ ረፋድ ላይ በባለ ሁለት በር የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ተሳፍረው ከቡሬ ከተማ መነሳታቸውን ያስታውሳሉ። የአባይ በረሃን ጨረሰው እንደወጡ ወደ 20 የሚሆኑ እና የተለያዩ አይነት መሳሪያዎችን የታጠቁ ሰዎች አውቶብሱን እንዳስቆሙት ይናገራሉ። "ግማሹ ቦታ ቦታ ይዘው ቆመዋል። ግማሹ ደግሞ ከመኪናው አስወረዱን። ከዛ የሰዎችን ዘር መለየት ጀመሩ" ይላሉ ይህ የዓይን እማኝ። ታጣቂዎቹ ተሳፋሪዎችን በኦሮምኛ 'ማን ነህ?' 'ወዴት ነው የምትሄደው?' የሚሉ ጥያቄዎችን መጠየቅ መጀመራቸውን የዓይን እማኙ ያስረዳሉ። "ኦሮምኛ የምንችል ኦሮምኛ ተናግረን አለፈን። ኦሮምኛ የማይችሉትን ለይተው ወደ ጫካ ይዘው ሄዱ። ብዙ ሰው ይዘው ሄደዋል"። የዓይን እማኙ እንደሚያስረዱት ተሳፋሪዎች ከአውቶብሱ እንዲወርዱ ተደርጎ ታጣቂዎቹ ተሳፋሪዎችን እየጠየቁ ሳለ አራት ሰዎች ለማምለጥ ሲሮጡ ታጣቂዎቹ ተኩሰው እንደገደሏቸው ይናገራሉ። ከአራቱ ሰዎች ውጪ ግን የተለዩት ሰዎች ሲገደሉ አለማየታቸውን አስረድተዋል። "ወደ ጫካ ይዘዋቸው ሲሄዱ ነው ያየሁት። ጉቲን ከተማ ከደረሰን በኋላ ነው የወሰዷቸውን ሰዎች እንደገደሏቸው የሰማነው" ይላሉ። ታጣቂዎቹ ተሳፋሪዎቹን ከአውቶብሱ ካስወረዱ በኋላ፤ አውቶብሱ ወደ ቡሬ መመለሱን ይህ የዓይን እማኝ ይናገራሉ። "በአውቶብሱ ከነበርነው ውስጥ 26 ሰዎችን ነው ለይተው የለቀቁን። ሁለት ረዳቶች እና ሹፌሩ ወደ ቡሬ ተመልሰዋል። አራቱን ገድለው የተቀሩትን ወደ ጫካ ይዘው ሄደዋል" ይላሉ የዓይን እማኙ። ይህ የዓይን እማኝ ታጣቂዎች በትክክል ስንት ሰው ለይተው እንደወሰዱ ባያውቁም ከ30 የማያንሱ ሰዎችን ወደ ጫካ ይዘው ስለመሄዳቸው ይናገራሉ። አውቶብሱ ወደ ቡሬ ዞሮ ከተመለሰ በኋላ ወደ ነቀምት መስመር በእግር ጉዞ መጀመራቸውን ገልጸዋል። "አውቶብሱ ከተመለሰ በኋላ በእግር ጉዞ ጀመርን። መንገድ ላይ አይሱዙ መኪና አግኝተን አጋምሳ እስከሚባል ቦታ አደረሰን" በማለት ያስረዳሉ። ይህ የዓይን እማኝ ኦሮምኛ መናገር መቻላቸው ከጥቃቱ እንዲያመልጡ ቢያስችላቸውም፤ በርካቶች በብሔራቸው ምክንያት ተለይተው መገደላቸው ከፍተኛ የሆነ ድናጋጤን እንዳሳደረባቸው ይናገራሉ። "ከድንጋጤ የተነሳ ትናንት መናገር ሁሉ አልቻልኩም ነበር። ምንም ቃል ማውጣት ተስኖኝ ነበር። ዛሬ ነው መናገር የጀመርኩት ሲሉ" ገጠመኛቸውን ለቢቢሲ አስረድተዋል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ ማንነት መሠረት ያደረጉ ጥቃቶች በተደጋጋሚ እየተፈጸሙ ይገኛሉ። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ኦሮሚያ እና አማራ መሰል ጥቃቶች ተፈጽመዋል። በተመሳሳይ በዚህ ሳምንት አጋማሽ ላይ ወደ አማራ ክልል እየጓዙ በነበሩ የአይሱዙ የጭነት መኪኖች ላይ በተፈጸመ ጥቃት አምስት ሰዎች መገደላቸውን የአከባቢው ባለስልጣናት ማስታወቃቸው ይታወሳል።
news-56884281
https://www.bbc.com/amharic/news-56884281
በሞቃዲሾ የተከሰተው ውጊያ የለየለት ጦርነት እንዳይቀሰቅስ አስግቷል
በሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ በሁለት ተጻራሪ ኃይሎች መካከል ውጊያ ተካሄደ።
ትናንት እሁድ ከአገሪቱ ቤተ መንግሥቱት አቅራቢያ የባባድ መሣሪያዎች ድምጽና የተኩስ ልውውጥ እንደነበረ ከስፍራው የሚወጡ መረጃዎች አመላክተዋል። ሞርታር ጭምር የፕሬዝዳንቱ መቀመጫ ወደሆነው ቤተ መንግሥት ስለመተኮሱ ተሰምቷል። ውጊያው ምናልባትም ፕሬዝዳንት ፋርማጆን በሚደግፉና በሚቃወሙ የሠራዊት አካላት አልያም በታጣቂዎች መካከል ሳይካሄድ እንዳልቀረ ተጠርጥሯል። ባለፈው ሳምንት ፕሬዝዳንት መሐመድ አብዱላሂ መሐመድ ወይም (ይበልጥ የሚታወቁበት ስማቸው ፋርማጆ) የሥልጣን ዘመናቸውን በሁለት ዓመት ማራዘማቸው እያነጋገረ ነበር። የፋርማጆ የሥልጣን ዘመን ባለፈው የካቲት ወር ማብቃት ነበረበት። የፋርማጆ ሥልጣናቸውን ማራዘም በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ እየተወገዘ ይገኛል። የአፍሪካ ሕብረትም ሆነ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፋርማጆ ውሳኔ እንዳሳሰባቸው ከመግለጽ አልተቆጠቡም። ትናንት እሁድ በወጡ አንዳንድ ዘገባዎች እንደተመላከተው በአንዳንድ አካባቢዎች የተነሱ አለመግባባቶች እየሰፉ ሄደው ማዕከላዊ ሞቃዲሾን ሲያምሱ ውለዋል። አንዳንድ የአገሬው መገናኛ ብዙሃን እንደዘገቡት ከሆነ ግጭቱ በዋናነት የፋርማጆን መንግሥት በሚደግፉና በሚቃወሙ ታጣቂ ኃይሎች መካከል የተደረገ ነበር። የጎሣ መሪዎችም በግጭቱ ተሳትፎ ነበራቸው። እስከአሁን በትናንቱ ግጭት ስለደረሰው ጉዳት የተባለ ነገር የለም። የግል የሆነው 'ካሲማዳ' የወሬ ድረ ገጽ እንዳለው ጸረ ፋርማጆ ሰልፈኞች ወደ ጎዳና ወጥተው ጎማ ያቃጠሉ ሲሆን፤ አማጺ ወታደሮችም የተወሰኑ የሞቃዲሾ ሰሜናዊ ሰፈሮችን መቆጣጠር ችለው ነበር። የቀድሞው የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ማህሙድ እና የተቃዋሚ መሪው አብዱራህማን አብዲሺኩር የመንግሥት ደጋፊ ታጣቂዎች ቤቶቻቸው ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን ተናግረዋል። በተለይ አብዱሺኩር በትዊተር ሰሌዳቸው ላይ እንደጻፉት መከላከያ ኃይሉን ፖለቲካ ውስጥ ማስገባት አደጋ አለው ሲሉ አስጠንቅቀዋል። ትናንት ከሰዓት የሶማሊያ ደኅንነት ሚኒስትር ሐሰን ሐነደበይ ጂማሌ ስማቸውን ያልጠቀሷቸው አገሮች ከግጭቱ ጀርባ እንዳሉ አስታውቀዋል። እጃቸውን እንዲሰበስቡም አሳስበዋል። የደኅንነት ሚኒስትሩ በቴሌቪዥን ወጥተው እንደተናገሩት ታጣቂ ቡድን ወደ ሞቃዲሾ ተሰማርቶ አገሪቱን ለማመስ ተልዕኮ ተሰጥቶት ነበር። ሆኖም አክሽፈነዋል ብለዋል። ሶማሊያ ለአስርታት በጦርነት ስትታመስ የቆየች አገር ናት። ከፈረንጆቹ 2011 ጀምሮ ግን የመረጋጋት ዝንባሌን ስታሳይ ቆይታለች። የፋርማጆ መንግሥትም የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ድጋፍ ያለው ሆኖ ቆይቷል። ሆኖም የፋርማጆ ሕጋዊ የግዛት ዘመን በየካቲት ማብቃቱን ተከትሎ ምርጫ መዘግየቱ ያቺን አገር ወደለየለት ግጭት ውሰጥ እንዳይከታት ተሰግቷል። በሶማሊያ ምርጫ የሚካሄድበት መንገድ ከተመለደው ወጣ ያለና የተወሳሰበ ነው። በሶማሊያ የቀጥታ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ሳይሆን የሚደረገው የጎሳ መሪዎች የሕዝብ ተወካዮችን ከመረጡ በኋላ የተመረጡት የሕዝብ ተወካዮች ናቸው ፕሬዝዳንቱን የሚመርጡት።
news-46589722
https://www.bbc.com/amharic/news-46589722
የግብፅ መካነ መቃብር፡ ሳቃራ ፒራሚድ ኮምፕሌክስ አቅራቢያ አዲስ ግኝት ይፋ ተደርጓል
በግብፅ ቄሶች ያረፉበትና ላለፉት 4400 ዓመታት ተነክቶ የማያውቅ መካነ መቃብር ማግኘታቸውን አርኪዮሎጂስቶች አስታወቁ።
ባለሙያዎች በጣም የተለየና ተጠብቆ የቆየ ያሉትን መካነ መቃብር ጋዜጠኞች ገብተው እንዲያዩ ተፈቅዶላቸው ነበር። በግብፅ የአንቲኪዩቲስ ምክር ቤት ዋና ፀሃፊ የሆኑት ሙስጠፋ ዋዚሪ ባለፉት አስርት ዓመታት ታይቶ የማይታወቅ አስደናቂ ግኝት ነው ሲሉ ገልፀውታል። • በጥቅም ላይ የዋሉ የጥንታዊ ግብፅ የህክምና ጥበባት • ሀና እና ጓደኞቿ የሰሩት የእናቶች ምጥ መቆጣጠሪያ • የአለማየሁ ተፈራ ፖለቲካዊ ካርቱኖች በካይሮ አቅራቢያ ሳቃራ ፒራሚድ የተገኘው ይህ መካነ መቃብር በቀለማት ያሸበረቁ ሥዕላዊ መግለጫዎች፣ የፈርኦን ሐውልቶች እንዲሁም ዋህትይ የተባሉት የንጉሣዊ ቄስ ከእናታቸው፣ ከሚስታቸው እና ከዘመዶቻቸው ጋር በሚያሳይ ምስል የተሞላ ነው። አርኪዮሎጂስቶች የመካነ መቃብሩ ባለቤት የመቃብር ክዳን ማግኘታቸውን ተከትሎ ሌሎች አዳዲስ ግኝቶችን ለመፈለግ በአውሮፓውያኑ ታህሳስ 16 ቁፋሮ መጀመራቸው ታውቋል። የግብፅ ፒራሚድ በሚገኝበት ሳቃራ ጥንታዊው ኔክሮፖሊስ ሰፊው መካነ መቃብር የተገኘበት ቦታ የመካነ መቃብሩ ውጫዊ ክፍል የሚያሳየው በድንጋይ የተሰራውን ረዥም ግድግዳ በጥንታዊ የግብፅ ጽሁፍ እንዲሁም በሥዕላዊ መግለጫዎች የተሸፈነው መካነ መቃብር በመካነ መቃብሩ ላይ የተሰሩ የሰዎች ሐውልት የቁፋሮው ፕሮጀክት መሪ የሆኑት ሙስጠፋ አብዶ፤ መካነ መቃብሩ 10 ሜትር ርዝመት፣ 3ሜትር ስፋትና 3ሜትር ከፍታ አለው በጥንታዊቷ ግብፅ ቄሶች ልዩ ክብር ይሰጣቸው ነበር የመካነ መቃብሩ ቀለም ላለፉት 4400 ዓመታት በጥሩ ሁኔታ ይገኛል ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ 2500 - 2350 ድረስ ግብፅን ሲመሩ የነበሩት ዋህቲይ ሐውልት ዋናውን ቄስና ቤተሰቦቹን የሚያሳየው በቀለም ያጌጠው ግድግዳ አርኪዮሎጂስቶች መካነ መቃብሩ ላይ ተጨማሪ ምርምር ለማድረግ አቅደዋል።
news-46436548
https://www.bbc.com/amharic/news-46436548
በእስራኤሏ ከተማ ሲሳሪያ 900 ዓመታትን ያስቆጠሩ የወርቅ ሳንቲሞች ተገኙ
የወርቅ ሳንቲሞቹ ስብስብ በእስራኤል የጥንት ወደብ ከተማ ሲሳሪያ በአርኪዎሎጂስቶች ቁፋሮ ከ900 ዓመታት በኋላ የተገኘ ነው።
የወርቅ ሳንቲሞቹ ከአንድ የጆሮ ሎቲ ጋር በነሐስ ማሰሮ በድንጋዮች መካከል የተገኙ ሲሆን በቁጥር 24 ናቸው። ምን አልባትም አንድ ቀን አውጥቼ እጠቀምበታለሁ በሚል በአንድ ግለሰብ የተቀበሩ ሳይሆኑ እንዳልቀረና ሳይጠቀሙበት እንደቀሩ ተነግሯል። • "ወደ እናት ሃገራችን እስራኤል ውሰዱን" • እስራኤል ስደተኞች የማስወጣት ዕቅዷን ሰረዘች የሳንቲሞቹ ባለቤት በአውሮፓውያኑ 1101 በነበረው የጅምላ ጭፍጨፋ ሳይገደሉ እንዳልቀሩ አርኪኦሎጂስቶቹ ያስረዳሉ። እንዚህ ሳንቲሞች በሲሰሪያ የዓለም ቅርስ ጥበቃ ለመስራት በተደረገ ቁፋሮ ወቅት የተከሰቱ ሲሆን በሁለት ድንጋዮች መካከል ተቀብረው ነው የተገኙት። ይህም በሲሰሪያል አስገራሚ ታሪክ የመስቀል ጦርነት በድል ለመጠናቀቁ ግኝቱ አንዱ ማሳያ እንደሆነ የእስራኤል የጥንት ቅርሶች ጥበቃ ባለስልጣናት አስረድተዋል። ባለስልጣናቶቹ የተፃፉ መረጃዎችን ጠቅሰው በአውሮፓውያኑ ከ1100 እስከ 1118 ባሉት ዓመታት አብዛኞቹ የሲሰሪያ ነዋሪዎች በእየሩሳሌም የመስቀል ጦርነት መሪ በባልድዊን መጀመሪያ ተገድለዋል። በመሆኑም "የእቃዎቹ ባለቤት እና ቤተሰቦቹ በዘር ጭፍጨፋው እንደተገደሉ አሊያም በባሪያ ንግድ እንደተሸጡና ወርቁን ማውጣት እንዳልቻሉ በምክንያታዊነት ማሰብ ይቻላል" ይላሉ የቁፋሮው ዳሬክተሮች ዶክተር ፒተር ግንደልማን እና ሞሃመድ ሃታር። • ". . . ጥፍር መንቀል ሕጋዊ አይደለም ስንለው ብሔሩ ውስጥ ለመደበቅ ይሞክራል" ጠ/ሚ ዐብይ • "ፓስፖርት መስጠት አልተከለከለም" የኢሚግሬሽንና የዜግነት ጉዳዮች ተቋም የቅርብ ግኝት እንደሚያስረዳው በሁለት ተቀራራቢ ቦታዎች ሌሎች ሐብቶችም ተገኝተዋል። አንደኛው የወርቅ ማሰሮና የብር ጌጣጌጦች ሲሆን በአውሮፓውያኑ 1960 የተገኘ ነው ሁለተኛው ደግሞ በ1990 የተገኘው የነሐስ ዕቃ ነው። እነዚህ ግኝቶች በቅርቡ በእየሩሳሌም በሚገኘው የእስራኤል ሙዚየም ውስጥ ተጠብቀው ይገኛሉ። በአውሮፓውያኑ 2015 እንዲሁ በእስራኤል ሜዲትራኒያን ባህር ዳርቻ ጠላቂዎች ረጂም እድሜ ያስቆጠሩ የወርቅ ሳንቲሞች ቁርጥራጮችን አግኝተዋል። ሳንቲሞቹ በቁጥር 2000 ሲሆኑ ከ1000 ዓመት በላይ አስቆጥረዋል፤ በባህር ጠላቂ ቡድኖች ተቀብረው የቆዩ ሳይሆን እንዳልቀረ ተነግሯል።
news-54851970
https://www.bbc.com/amharic/news-54851970
የአሜሪካ ምርጫ፡ ቆጠራው በቀጠለበት ምርጫ ባይደን እንደሚያሸንፉ ተንብየዋል
የማክሰኞውን የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ተከትሎ ዶናልድ ትራምን ለማሸነፍ ከጫፍ የደረሱት ጆ ባይደን እንደሚያሸንፉ በመተማመን በድጋሚ ተናግረዋል ፡፡
የዴሞክራቲክ ፓርቲው ዕጩ ኋይት ሐውስ ለመግባት ከሚያስፈልጉት 270 የኤሌክቶራል ኮሌጅ ድምፆች 253ት ያህሉ አግኝተዋል፡፡ በተጨማሪም ባይደን ወሳኝ ግዛቶች በሆኑት በጆርጂያ፣ ኔቫዳ፣ ፔንሲልቬንያ እና አሪዞና እየመሩ ነው፡፡ የባይደን ድል ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከአራት ዓመት በኋላ በመጪው ጥር ስልጣናቸውን እንዲለቁ ያደርጋቸዋል፡፡ ባይደን ምን አሉ? ባይደን አርብ ምሽት ዊልሚንግተን ደላዌር ለነበሩ ደጋፊዎቻቸው ሲናገሩ "ይህንን ውድድር እናሸንፋለን" ብለዋል፡፡ መድረኩ ላይ የባይደን ምክትል በመሆን የሚወዳደሩት የካሊፎርኒያ ሴናተር ካማላ ሃሪስ ተገኝተዋል፡፡ ከ 300 በላይ የኤሌክቶራል ኮሌጅ ድምጾችን ለማሸነፍ በትክክለኛው መንገድ ላይ እንደሆኑ ተናግረዋል። በታሪክ ውስጥ ከማንኛውም የአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ዕጩ በላይ በምርጫ ከ74 ሚሊዮን በላይ በሆኑ ሰዎች ተመርጠዋል፡፡ አሜሪካውያን የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን፣ የተዳከመውን ኢኮኖሚ፣ የአየር ንብረት ለውጥን እና ዘረኝነትን እንዲዋጉ ስልጣን እንደተሰጣቸው ባይደን ተናግረዋል፡፡ የሪፐብሊካኑን ዶናልድ ትራምፕን ያልጠቀሱት ባይደን "እኛ ተቃዋሚዎች ልንሆን እንችላለን ግን ጠላቶች አይደለንም እኛ አሜሪካውያን ነን" ብለዋል፡፡ ባይደን የማሸንፊያ ንግግራቸውን እንደሚያቀርቡ የታቀደ ቢሆንም በምርጫው ውጤት ላይ የመገናኛ ብዙሃን አሸናፊ መሆናቸውን አለመጥቀሳቸውን ተከትሎ አጠቃላይ መረጃ ለመስጠት መርጠዋል። ዴሞክራቱ በድጋሚ ለአሜሪካኖች ንግግር እንደሚያደርጉ ተስፋ እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡ ከዚህ ቀደም ሁለት ጊዜ ለዋይት ሀውስ በአውሮፓውያኑ 1988 እና በ2008 የተወዳደሩት ባይደን በ78 ዓመታቸው ከተመረጡ አንጋፋው ፕሬዝዳንት ይሆናሉ፡፡ በዚህ ሳምንት መጨረሻ አሸናፊ እንደሆኑ ከተነገረ ሰኞ የሽግግር ሂደቱ ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የአሜሪካው የደህንነት አገልግሎት የባይደንን ደህንነት ለማጠናከር አንድ ቡድን ወደ ደላዌር ማጠናከሪያ ልኳል፡፡ የፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር በዊልሚንግተን አየር ክልል ላይ በረራዎችን አግዷል፡፡ ትራምፕ ግን በአጭር ጊዜ ውስጥ ሽንፈታቸውን እንደሚቀበሉ የሚያሳይ ምንም ፍንጭ የለም፡፡ ትራምፕ አርብ ከሰዓት በኋላ በትዊተር ገጻቸው ላይ "ጆ ባይደን የፕሬዚዳንቱን ቢሮ እንዳገኘ ተሳስቶ መግለጽ የለበትም። እኔም ያንን ማድረግ እችል ነበር፡፡ የህግ ሂደቶች አሁን በመጀመር ላይ ናቸው!" ብለዋል። ትራምፕ በምርጫ መጭበርበር ላይ ማስረጃ የሌላቸውን ጥያቄዎችን ሲያቀርቡ ቆይተዋል። በኋይት ሀውስ ውስጥ ያለው መንፈስ ምን ይመስላል? ፕሬዚዳንት ትራምፕ ብዙ አጋሮቻቸው በቴሌቪዥንም ሆነ በጎዳናዎች ላይ ደግፈዋቸው አለመቆማቸው ተቆጥተዋል፣ ቅር ተሰኝተዋልም ሲሉ የዋይት ሃውስ ባለስልጣናት አርብ አስታውቀዋል። ትራምፕ ቴሌቪዥን እየተመለከቱ፣ ለምርጫ የዘመቻ ቢሮዎች የስልክ ጥሪ በማድረግ ጊዜያቸውን በ'ኦቫል' ቢሮ እና በመኖሪያ ቤታቸው መካከል ሲያሳልፉ ቆይተዋል፡፡ በርካታ ረዳቶቻቸው ሥራ ላይ አልተገኙም። ዋይት ሀውስም "ባዶ" እና የሃዘን ድባብ ያጠላበት ነው ተብሏል፡፡ ዜናውን ይበልጥ አሳዛኝ የሚያደርገው አርብ ማታ የ 61 አመቱ የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ፅህፈት ቤት ሀላፊ ማርክ ሚዶውስ በኮሮናቫይረስ በሽታ መያዛቸው ሪፖርት መደረጉ ነው። ይህ የሆነው አሜሪካ በቀን ክብረ ወሰን የሆነ ከ125 ሺህ በላይ አዲስ ኮሮናቫይረስ ያለባቸውን ሰዎች ባስመዘገበችበት ዕለት ነው፡፡ ፕሬዚዳንቱ ለከፍተኛ አማካሪዎቻቸው በውጤቱ ላይ የሕግ ጥያቄዎች እንደሚቀጥሉ ቢያመለክቱም ለእንዲህ ዓይነቱ ሙግት የሚሆን ጠንካራ መረጃ አልቀረበም።
news-48429703
https://www.bbc.com/amharic/news-48429703
246 የኮኬይን ከረጢቶችን የዋጠው ግለሰብ አውሮፕላን ላይ ሞተ
ከሜክሲኮ ከተማ በተነሳው አውሮፕላን ተሳፋሪ የነበረው ጃፓናዊ 246 ከረጢት ኮኬይን በመዋጡ ሕይወቱ ሊያልፍ ችሏል።
በዚህም ምክንያት በረራው በጃፓኑ ናሪታ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍ የሚጠበቅበት ቢሆንም በሜክሲኮዋ ሶኖራ ግዛት ለማረፍ ተገዷል። ባለስልጣናት እንዳሉት ዩዶ ኤን የተባለው ግለሰብ ሆዱ ውስጥ በደበቀው ዕፅ ምክንያት ጭንቅላቱ ውስጥ ባጋጠመው የፈሳሽ መጠራቀም ሳቢያ ሊሞት ችሏል። • “ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ ከደወሉልን በኋላ ተረጋግተናል” የናዝራዊት አበራ እህት ይህ ግለሰብ ከኮሎምቢያ ዋና ከተማ ቦጎታ የጀመረውን ጉዞ ቀይሮ ወደዚህ በረራ እንደገባም ታውቋል። የሶኖራ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ በሰጠው መግለጫ መሠረት የእፅ ከረጢቶቹ 2.5 ሴንቲ ሜትር ርዝመትና 1 ሴንቲ ሜትር ስፋት አላቸው። በግለሰቡ ላይ በተደረገው የውስጥ አካል ምርመራም እነዚህ ከረጢቶች በግለሰቡ ሆድና አንጀት ውስጥ እንደታዩ ተነግሯል። አውሮፕላኑ በህረሞሲሎ ከተማ በድንገት ካረፈ በኋላ ቀሪዎቹ 198 ተሳፋሪዎች ጉዟቸውን እንደገና መቀጠላቸውም ተገልጿል። የሜክሲኮ ባለስልጣናት ጉዳዩን በመመርመር ላይ ይገኛሉ።
48250848
https://www.bbc.com/amharic/48250848
አፍጋኒስታናዊቷ ጋዜጠኛና የፖለቲካ አማካሪ መገደል ቁጣ ቀሰቀሰ
የአፍጋኒስታን ፖለቲከኞችና የሴቶች መብት ተሟጋቾች የቴሌቪዥን ጋዜጠኛዋ በጠራራ ፀሐይ መገደል አስቆጥቷቸዋል፤ ተገቢውን ፍትህም እንድታገኝ እየጠየቁ ነው።
ሚና ማንጋል ወደ ፖለቲካው ከመምጣቷ በፊት የቴሌቪዥን ጋዜጠኛ የነበረች ሲሆን ቅዳሜ ዕለት ካቡል ውስጥ ከቅርብ ርቀት በተተኮሰባት ጥይት ነበር የተገደለችው። የአፍጋን የመንግሥት ባለስልጣናት ገዳዮቿን ይዞ ለፍርድ ለማቅረብ ቃል ገብተው ፖሊስ ምርመራውን እያደረገ መሆኑንና እስካሁን ከግድያው ጀርባ ማን እንዳለ አልታወቀም ብለዋል። ቅዳሜ ዕለት የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትሩ በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት ለአፍጋን የሕዝብ እንደራሴ የባህል ጉዳዮች ኮሚሽን አማካሪ የነበረችው ማንጋል ወደ ስራ ገበታዋ እየሄደች በነበረችበት ተገድላለች ሲሉ ተናግረዋል። • "ምርጫው እንዲራዘም እንፈልጋለን" አቶ አንዷለም አራጌ • "ይህንን ሐውልት የኢትዮጵያ ሕዝብ አሠሩላቸው" • አውሮፕላን ያለ ፊት ጎማው ያሳረፈው አብራሪ የአፍጋኒስታን ከፍተኛው ፍርድቤት፣ የሲቪል ሶሳይቲ ቡድኖች እና የፀረ ፆታዊ ጥቃት ኮሚሽኑ ጥብቅ ክትትል እንዲደረግ ጠይቀዋል። ማንጋል በፌስ ቡክ ገጿ ላይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ማስፈራሪያ ዛቻዎች እየደረሷት መሆኑንና ለሕይወቷ እንደምትሰጋ ፅፋ እንደነበር የሴቶች መብት ተሟጋች የሆነችው ዋዝማ በቲውተር ገጿ ላይ አስፍራለች። የፖሊስ ቃል አቀባዩ ለሮይተርስ "የዛቻው ዓይነት ግልፅ አይደለም፤ የቤተሰብ ግጭቶችንም ማየታችን አይቀርም" ብለዋል ። ሞቷ ከተሰማበት ጊዜ አንስቶ አፍጋኒስታናውያን በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በሀገሪቱ ሴቶች ላይ ስለሚደርስ ጥቃት እየፃፉ ይገኛሉ። አንዳንዶች ጥቃቱ በጠራራ ፀሐይ መፈፀሙን ሲፅፉ ሌሎች ደግሞ ጥቃቱ በካቡል አንፃራዊ ደህንነትና ሠላም አለ በሚባልበት ሥፍራ መከሰቱን በመጥቀስ ስጋታቸውን ገልፀዋል። ሪፖርተርስ ዊዝ አውት ቦርደርስ በ2018 አፍጋኒስታንን ለጋዜጠኞች ፍፁም አደገኛ የሆነች ሃገር ሲል ፈርጇታል።