text
stringlengths
140
24k
summary
stringlengths
13
164
አዲስ አበባ፣ ሀምሌ አምስት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በሁለት ሺህ በጀት አመት በአስቸኳይ የሙስና መከላከል ስራ ከሁለት ነጥብ ስምንት ቢሊየን ብር በላይ ከሙስና እና ከምዝበራ ማዳን መቻሉን የፌደራል የስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን አስታወቀ ። በኮሚሽኑ የአስቸኳይ ሙስና መከላከል መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ገዛኸኝ ጋሻው በሁለት ሺህ በጀት አመት በተከናወኑ አበይት ጉዳዮች ዙሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም በተጠናቀቀው በጀት አመት ከአንድ መቶ ሰባ አምስት ሺህ በላይ አመራርና ሰራተኞች ሀብታቸውን ማስመዝገባቸውን አንስተዋል። በክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች አንድ ሺህ ሰማኒያ ሰባት አስቸኳይ የሙስና መከላከል ስራ መከናወኑን ነው የተናገሩት። በዚህም ሁለት ነጥብ ስምንት ቢሊየን ብር እና ስምንት ሺህ አራት መቶ ዘጠና የአሜሪካ ዶላር ማዳን መቻሉን ጠቁመው ከመሬት ጋር በተያያዘም ከአርባ ስድስት ሚሊየን ካሬ ሜትር የከተማና የገጠር ቦታ ከሙስና ምዝበራ ማዳን ተችሏል ብለዋል። አስቸኳይ የሙስና መከላከል ስራው ከግዥ፣ መሬት አሰጣጥ፣ ንብረት ማስወገድ፣ ገቢ አሰባሰብ ፣ እርዳታ አሰጣጥ እና ከማዳበሪያ ስርጭት ጋር የተያያዘ እንደሆነ መጥቀሳቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
በአስቸኳይ የሙስና መከላከል ስራ ሁለት ነጥብ ስምንት ቢሊየን ብር ከምዝበራ ማዳን ተቻለ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት ስድስት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በአዲስ አበባ ከተማ የተገነቡት ሶስት ትላልቅ የገበያ ማእከሎች በሙሉ አቅማቸው አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ አስታወቀ። አገልግሎት መስጠት የጀመሩት የኮልፌ እና ለሚ ኩራ የግብርና ምርቶች መሸጫ እንዲሁም የአቃቂ ቃሊቲ የሰብል ምርቶች መሸጫ ማእከላት መሆናቸው ተገልጿል። በአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ሰውነት አየለ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለፁት ሀምሳ ሰባት አምራች እና አቅራቢዎች ካባለፈው ሳምንት ጀምሮ በገበያ ማእከላቱ ምርት እያቀረቡ ይገኛሉ። በጨረታ ተለይተው ወደገበያ ማእከላቱ እንዲገቡ የተደረጉት የራሳቸው መሬት ኖሯቸው አመቱን ሙሉ ማምረት እና ማቅረብ የሚችሉ አምራቾች መሆናቸውንም ተናግረዋል። በተጨማሪም አንድ መቶ አርባ ሰባት ቸርቻሪ ነጋዴዎች ምርቶቻቸውን እያቀረቡ ሲሆን በመዲናዋ የሚገኙ ማህበራትም ምርት እንዲያቀርቡ ስምምነት ላይ መደረሱን ጠቁመዋል። በገበያ ማእከላቱ የሚቀርቡ ምርቶች ከመደበኛው ገበያ ጋር ሲነፃፀሩ ከ እስከ ሀያ በመቶ ቅናሽ እንዳላቸውም አንስተዋል። የዋጋ ንረትን ለመቋቋም የገበያ ማእከላቱ ድርሻ ከፍተኛ መሆኑንም አቶ ሰውነት አየለ ገልፀዋል። በመሳፍንት እያዩ
የመዲናዋ ሶስት የገበያ ማእከሎች በሙሉ አቅማቸው አገልግሎት መስጠት መጀመራቸው ተገለፀ
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ መተከል ዞን ማክሰኞ ሌሊት ለረቡእ አጥቢያ በሰላማዊ ሰዎች ላይ በተፈፀመ ጥቃት ከአንድ መቶ በላይ ሰዎች መገደላቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ኢሰመኮ እና አምንስቲ ኢንተርናሽናል ገለፁ።ጥፋተኞች በቁጥጥር ስር እየዋሉ ነውየግድያውን እውነተኛ መንስኤ የሚያጣራ ኮሚቴ ይቋቋምቢቢሲ በተጨማሪ በጥቃቱ አካባቢ የነበሩ የአይን እማኞችንና በአካባቢው በሚገኝ ሆስፒታል የሚሰሩ የጤና ባለሙያዎችን በማናገር ለመረዳት እንደቻለው አንድ መቶ ሀያ ሰዎች ሲገደሉ ሌሎች በርካቶች ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል። የክልሉ መንግስት ኮምዩኒኬሽን ሀላፊ አቶ መለሰ በየነ በጥቃቱ በትክክል ምን ያህል ሰዎች እንደተገደሉ ለመግለፅ ባይችሉም ቁጥሩ በጣም ከፍተኛ እንደሆ ለቢቢሲ አረጋገጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ዛሬ በይፋዊ የትዊተር ገፃቸው ላይ በመተከል ስለደረሰው ግድያ እየተፈፀመ ያለው ጭፍጨፋ እጅግ አሳዛኝ ሆኗል። በወገኖቻችን ላይ በተፈፀመው ኢሰብአዊ ተግባር በእጅጉ አዝኛለሁ ያሉ ሲሆን፣ መንግስት ችግሩን ከስሩ ለመፍታት አስፈላጊውን የተቀናጀ ሀይል እንዲሰማራ አድርጓል ብለዋል።ይህ ጥቃት በቤኒሻንጉል ክልል ውስጥ ያለው የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ በከፍተኛ ሁኔታ እየተዳከመ መሄዱን እንደሚያሳይም የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ ላይ አመልክቷል።የአምንስቲ ኢንተርናሽናል በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የተገደሉትን ሰዎች አስመልክቶ ባወጣው መለግጫ እጅግ አሰቃቂው ግድያ በክልሉ የሚኖሩ አማራዎች፣ ኦሮሞዎችና ሺናሻዎች ላይ ያነጣጠረ ነው። ይህ መንግስት ብሄር ተኮር የሆነ ግድያን ለማስቆም በፍጥነት ሊንቀሳቀስ እንደሚገባ የሚያሳይ ነው ብሏል።ኮሚሽኑ ጥቃቱን ተከትሎ ባወጣው መግለጫ ላይ እንዳመለከተው የታጠቁ ሀይሎች በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ፣ በኩጂ በተባለው ቀበሌ ውስጥ ጥቃቱን ከሌሊቱ አስር፡ ሰአት ላይ መሆኑንና ጠቅሷል። ለበርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች ሞት ምክንያት የሆነው ጥቃት የተፈፀመው የጥቃቱ ሰለባዎች በእንቅልፍ ላይ በነበሩበት ወቅት ቤቶችን በማቃጠልና በተኩስ መሆኑም ተገልጿል። አምንስቲ ከጥቃቱ ከተረፉ መካከል አምስት ሰዎች እንዳነጋገረና ከእነዚህ ሰዎች አንዱ የቡለት ዞን ነዋሪ እንደሆኑ አሳውቋል። በተጨማሪም ሁሉም ድርጅቱ ያነጋገራቸው ሰዎች የታጠቁ የጉሙዝ ብሄር ተወላጆች የአማራ፣ ኦሮሞና ሺናሻ ብሄር ተወላጆችን ቤት እየነጠሉ ጥቃት እንዳደረሱ ተናግረዋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ መንግስት በመተከል ዞን ከተፈጠረው የፀጥታ ችግር ጋር በተያያዘ እጃቸው አለበት የተባሉ አምስት አመራሮችን በህግ ቁጥጥር ስር ማዋሉን ትናንት ምሽት በክልሉ የመገናኛ ብዙኀን ላይ ይፋ አድርጓል።በቁጥጥር ስር ከዋሉት መካከል የኢፌዴሪ ሰራተኛ እና ማሀበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የማሀበራዊ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ የነበሩት አቶ ቶማስ ኩዊ፣ የቀድሞው የክልሉ ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ አድጎ አምሳያ፣ አቶ ሽፈራው ጨሊቦ፣ የቀድሞ የክልሉ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ ዳይሬክተር፣ የመተከል ዞን ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤትት ሀላፊ አቶ ባንዲንግ ማራ፣እንዲሁም አቶ አረጋ ባልቢድ የመተከል ዞን የቀድሞ አመራር የነበሩ መሆናቸው ተገልጿል።ኢሰመኮ ጥቃቱን በተመለከተ ተጎጂዎችንና ሌሎችንም በማነጋገር ባደረገው ማጣራት ጥቃቱ ለተፈፀመበት ቀበሌ የተመደበ የፖሊስ ወይም የፀጥታ ሀይል አለመኖሩን መረዳቱን አመልክቷል። ጥቃቱ የተፈፀመባት በኩጂ ቀበሌ ከወረዳው መቀመጫ ቡለን ከተማ ዘጠና ኪሎ ሜትር ርቃ የምትገኝ መሆኗን ጠቅሶ፤ በቀበሌው የሺናሻ፣ የኦሮሞና የአማራ ተወላጆች ይኖሩባታል። አምነስቲ እንዳነጋገራቸው አምስት ሰዎች ምስክርነት ከሆነ ደግሞ ጥቃት አድራሾቹ ቤቶችን አቃጥለዋል፤ ሰዎችን በስለትና በጥይት ገድለዋል። እስካሁን ድረስ ቢያንስ አንድ መቶ ሰዎች እንደተገደሉ ተዘግቧል። የሞት ቁጥሩ አሁንም ሊጨምር እንደሚችል አምነስቲ ያሳስባል። የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን የሚከታተለው ድርጅት መንግስት ይህን አሰቃቂ ግድያ እንዲመረምር ጥሪ አቅርቧል። ጥቃት አድራሾቹ ለፍትህ መቅረብ አለባቸው። የኢትዮጵያ መንግስት መሰል ድርጊቶች ድጋሚ እንዳይከሰቱ ሊከላከል ይገባል ብለዋል የድርጅቱ ሀላፊ። አምነስቲ ኢንተርናሽናል በግሉ የአጥቂዎችን ማንነት ማረጋገጥ ባይችልም፤ ጥቃቱ በስፍራው የሚኖሩ የሌላ ብሄር ተወላጆች ላይ ያነጣጠረ እንደሆነ ይገመታል። ከመስከረም ወር ጀምሮ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚኖሩ አማራዎች፣ ኦሮሞዎች፣ ሺናሻዎችና አገዎች ላይ ያነጣጠረ ተከታታይ ጥቃት እየተፈፀመ ነው። ኮሚሽኑ በበኩሉ በቡለን ሆስፒታል ስላሳ ስድስት ተጎጂዎች የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑና ከእነዚህ ውስጥ አብዛኞቹ በጥይት ሌሎቹ በቀስት የቆሰሉ መሆናቸውን አረጋግጧል። በተጨማሪም ጥቃት የደረሰባቸውን ሰዎች ሰዎች ሁኔታ የሚያሳዩና የሚረብሹ የፎቶግራፍ ማስረጃዎች ደርሰውኛል ሲል ገልጿል።በጥቃቱ በሰው ህይወትና በአካል ላይ ከደረሰው ጉዳት በተጨማሪ የደረሱና የተሰበሰቡ ሰብሎች በእሳት እንዲወድሙ መደረጋቸውን ኢሰመኮ አመልክቶ፤ ቢያንስ ያህል የእህል ክምሮች ሲቃጠሉ የተመለከቱ አንድ ተጎጂን በእማኝነት ጠቅሷል። ጥቃቱ ከበኩጂ ቀበሌ በተጨማሪ በጨላንቆና ዶሼ ቀበሌዎችም ቤቶች እየተቃጠሉ እንደሆነ ለኮሚሽኑ የተላኩ መረጃዎች እንዳሉ በመግለፅ፤ በድባጤ ወረዳ ዶንበን ቀበሌ ስጋት የገባቸው ነዋሪዎች ከጥቃቱ በኋላ ቀያቸውን ጥለው እየተሰደዱ እንደሆናቸው መረዳቱን አመልክቷል። ኢሰመኮ እንዳለው አካባቢው የተመደበው የመከላከያ ሰራዊት ከጥቃቱ ቀደም ብሎ የፌዴራልና የክልሉ አመራሮችን ለማጀብ ስፍራውን ለቆ መሄዱ ተከትሎ ጥቃት መፈፀሙናን እስከ እኩለ ቀን መቆየቱ ተነግሯል። ኮሚሽኑ ያነጋገራቸው ተጎጂዎች እንደሚሉት በጥቃቱ ከሞቱ ሰዎች መካከል አብዛኛዎቹ የሺናሻ ተወላጆች ናቸው። ነዋሪዎቹ ጨምረውም በጥቃቱ በስምና በመልክ የሚያውቋቸው የበኩጂ ቀበሌ ነዋሪዎች ጭምር መሳተፋቸውን ከጥቃቱ የተረፉ ተጎጂዎች ገልፀዋል። ኢሰመኮ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የሚከሰቱ ጥቃቶችን በተመለከተ የፌዴራሉና የክልሉን መንግስታት አስፈላጊውን ነገር ሁሉ እንዲያደርጉ ሲያሳስብ መቆየቱን ጠቅሶ ይሁንና ጥቃቶቹ በመልክና በስፋት እየተባባሱ መጥተዋል ብሏል።ኮሚሽኑ በጥቃቱ ላይ ተገቢው ማጣራትና ጥቃቱን ባለመከላከልም ሆነ በሌላ መልኩ ጥቃቱን የፈፀሙና ያባባሱ ሰዎችን ህግ ፊት የማቅረብ ሂደት ከወዲሁ እንዲጀመር አሳስቧል። ጨምሮም በአካባቢው የሚገኘውን የፀጥታ ሀይልና መዋቅር የሰዎችን ደሀንነት ሙሉ በሙሉ ለማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ በከፍተኛ ደረጃ በአፋጣኝ እንዲጠናከር ጥሪ አቅርቧል።የአካባቢው ባለስልጣናት ጥቃቱን የሚፈፅሙት ሀይሎችን ፀረ ሰላም ከማለት ውጪ ማንነታቸውና የጥቃቱ አላማ በግልፅ አይታወቅም። በተለያዩ ጊዜዎች በፀጥታ ሀይሎች በተወሰዱ እርምጃዎች የተለያየ ቁጥር ያላቸው በጥቃቶቹ ተሳትፈዋል የተባሉ ታጣቂዎች መገደላቸው ሲዘገብ ቆይቷል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሀበራዊ ፍትህ፣ ኢዜማ በመተከል የተፈፀመውን ጥቃት አስመልክቶ ባወጣው የሀዘን መግለጫ ላይ ክልሉ የዜጎች መሰረታዊ መብት የሆነውን በህይወት የመቆየት መብት ማስከበር ባለመቻሉ እና ድርጊቱ እየተደጋገመ በመምጣቱ፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እስካሁን የተፈፀሙት አሰቃቂ ወንጀሎችን ክልሉ ለምን ማስቆም እንዳልቻለ እውነተኛ መንስኤ የሚያጣራ ኮሚቴ አቋቁሞ በአፋጣኝ ተጠያቂነትን እንዲያሰፍን ጠይቋል።አክሎም የፌደራል መንግስት በህግ አግባብ ጣልቃ በመግባት የዜጎቹን ህይወት የመጠበቅ እና ህግ የማስከበር ስራውን ከማስጠበቅ በተጨማሪ አጥፊዎችን እና በክልሉ ያሉ ሀላፊነታቸውን በአግባቡ ያልተወጡ አመራሮችን ተጠያቂ እንዲያደርግ አሳስቧል።በአካባቢው ለወራት በዘለቀው ጥቃት ሳቢያ ፀጥታውን ለመቆጠጠርና በሰላማዊ ነዋሪዎች ላይ የሚፈፀሙትን ጥቃቶች ለማስቆም ባለፈው አመት መገባደጃ ላይ የፌደራል መንግስት ጦር ሰራዊትና የክልሉ የፀጥታ አካላት የተካተቱበት ኮማንድ ፖስት ተደጋጋሚ ጥቃት በሚፈፀምባቸው አካባቢዎች መዋቀሩ ይታወሳል። ነገር ግን አሁንም ድረስ የበርካታ ሰዎችን ህይወት የቀጠፉ ተከታታይ ጥቃቶች እየተፈፀሙ ነው። አሁን የተፈፀመውና ለበርካታ ሰዎች ሞት ምክንያት የሆነው ጥቃት በአካባቢው ከተፈፀሙት ሁሉ የከፋው እንደሆነ ይነገራል።
ቤኒሻንጉል ጉሙዝ መተከል ዞን በተፈፀመው ጥቃት ከአንድ መቶ በላይ ሰዎች መገደላቸውን የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ገለፁ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት ስድስት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ ኢትዮ ቴሌኮም በተያዘው በጀት አመት በመጀመሪያው ሩብ አመት አስር ነጥብ አንድ ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ።የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሪት ፍሬህይወት ታምሩ የኩባንያውን የመጀመሪያ ሩብ አመት ስራ አፈፃፀም በተመለከተ በዛሬው እለት መግለጫ ሰጥተዋል።ወይዘሪት ፍሬህይወት በመግለጫቸው ኢትዮ ቴሌኮም በተያዘው በጀት አመት መጀመሪያ ሩብ አመት ላይ የተለያዩ የአሰራር ማሻሻያዎች ሲያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል።ተቋሙ የእቅዱን ዘጠና ስምንት በመቶ ማሳካት መቻሉን የገለፁት ወይዘሪት ፍሬህይወት፥ ከተሰበሰበው ገቢ ውስጥ ሀምሳ ስድስት በመቶው ከድምፅ አገልግሎት ሀያ ዘጠኝ በመቶው ደግሞ ከሞባይል ዳታ የተገኘ መሆኑን አንስተዋል።እንዲሁም ከተሰበሰበው ገቢ ውስጥ አርባ አንድ ነጥብ አንድ ሚሊየን ዶላሩ ከአለም አቀፋ አገልግሎቶች የተገኘ መሆኑን ነው ተናገሩት።የተሰበሰበው ገቢ ከባለፈው ተመሳሳይ ሩብ አመት ጋር ሲነፃፀር የሀያ አንድ በመቶ ጭማሪ ማሳየቱንም ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ተናግረዋል።በሌላ በኩል በሩብ አመቱ የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር አርባ አራት ነጥብ አራት ሚሊየን የደረሰ ሲሆን ፥ የደንበኞች ቁጥርም አስር በመቶ መጨመሩ ተመላክቷል።በቤዛዊት ተፈሪ
ኢትዮ ቴሌኮም በመጀመሪያው ሩብ አመት አስር ነጥብ አንድ ቢሊየን ብር ገቢ ሰበሰበ
ነገረ ኢትዮጵያ ገዥው ፓርቲ የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችን ለማሰር ዝግጅት እያደረገ መሆኑን የነገረ ኢትዮጵያ ታማኝ ምንጮች ገለፁ። ሰሞኑን የኢህአዴግ ከፍተኛ አመራሮች ባደረጉት ስብሰባ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃልን ወይንስ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮችን ማሰር ያዋጣል በሚል ልዩነት እንደተፈጠረ የገለፁት ምንጮቻችን በስተመጨረሻም የኢንጅነር ይልቃል መታሰር ትኩረት የሚስብ በመሆኑ ንቁ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮችን ማሰር አዋጭ ነው የሚለው ቡድን ተደማጭነት እንዳገኘ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።በተመሳሳይ የሰማያዊና ሌሎች ፓርቲዎች አመራሮችን ከኢሳት ጋር ግንኙነት ያደርጋሉ በሚል በሽብር ስም ለመክሰስ ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነ ምንጮቻችን ገልፀዋል። የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችንም ሆነ ሌሎችን ከኢሳት ጋር ግንኙነት አላቸው በሚል ይከሰሳሉ የተባሉት እስከህዳር ወር መጨረሻ ሊታሰሩ ይችላሉ ሲሉ ምንጮቻችን ገልፀዋል። በሌላ በኩል በዚሁ ስብሰባ ኢንጅነር ይልቃል ወይንም ሌሎች ከፍተኛ አመራሮችን በማሰር ከተፈጠረው ልዩነት በተጨማሪ አመራሮችን በተለያዩ ሰበቦች ለማሰር በተዘጋጀውና በዚህ መንገድ መሄዱ እስከመቼ ያዋጣናል የሚሉ ጥያቄ በሚያነሱ ከፍተኛ የኢህአዴግ አመራሮች ልዩነት መፈጠሩንም ለማወቅ ተችሏል። ከዚህም ባሻገር በሌሎች የፓርቲው አካሄዶች ላይ ልዩነት በመፈጠሩ ፓርቲው ውስጥ አደጋ ተፈጥሯል ያሉት የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች በአቶ አባይ ፀሀዬ የሚመራ ቡድን ልዩነታችን ቢያንስ እስከ ምርጫው ድረስ ማቻቻል አለብን በሚል በሁለቱ ቡድን መካከል ያለውን ልዩነት ለመፍታት እየጣረ ነው ብለዋል። ሰማያዊ ፓርቲ ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር በመተባበር የአዳር ሰልፍን ጨምሮ የአንድ ወር መርሀ ግብር ቀርፆ እየተንቀሳቀሰ የሚገኝ ሲሆን የወሩ የመጀመሪያ መርሀ ግብር የሆነው የአደባባይ ስብሰባ ለማድረግ ሲቀሰቅሱ የተገኙ የፓርቲው አራት አመራሮች መታሰራቸው ይታወቃል።
ኢህአዴግ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችን ለማሰር መዘጋጀቱ ታወቀ የኢህአዴግ አመራሮች መካከል ልዩነት ተፈጥሯል
በአዲስ አበባ ከተማ በ ሚሊዮን ብር ወጪ የተገዙ ሀምሳ አራት የደረቅ ቆሻሻ አንሺ መኪኖች ለበርካታ ወራት ወደ ስራ ሳይገቡ መቆየታቸው ተገለፀ ።በአዲስ አበባ እሳት እና ድንገተኛ አደጋ መከላከልና መቆጣጠሪያ ባለስልጣን ግቢ እና ሌሎች ቦታዎች ቆመው የቆዩ እነዚህ መኪኖች በአዲስ አበባ ፅዳት አስተዳደር ስር የተደራጁ የደረቅ ቆሻሻ አንሺ ማህበራት ለስራቸው እንዲገዛ ያዘዛቸውና በሚፈልጉበት ደረጃ ባለመገዛታቸው ነው የተባለው።ስላሳ አምስት ኩንታል የሚጭን የደረቅ ቆሻሻ ማንሻ መኪኖች እንዲገዛ ያዘዙት እነዚህ ማህበራት ካዘዙት ውጪ ኩንታል የሚጭኑ መኪኖች በመገዛታቸው እንደነበረ ነው የተጠቆመው።የነዚህ መኪኖች መቆምን አስመልክቶ ዋልታ ያነጋገራቸው በአዲስ አበባ እሳት እና ድንገተኛ አደጋ መከላከልና መቆጣጠሪያ ባለስልጣን መኪኖቹ በግቢያቸው ለበርካታ ግዜ በመቆሙ የአደጋ መከላከያ ማሽኖችን ለማቆም የቦታ ጥበት እንዳጋጠማቸውና እክል እንደሆነበት ገልፀዋል።ተሸከርካሪያዎቹ የህዝብ ሀብት በመሆኑ የሚመለከታቸው አካላት ቶሎ ወደ ስራ ቢያስገባቸው የተሻለ ነው ሲሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።የአዲስ አበባ ከተማ ፅዳት እስተዳደር ኤጄንሲ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኢቢሬ ኢስማኤል የመኪኖቹ ከመጫን አቅም ጋር ተያይዞ በአሰመጪ በላይአብ ሞተርስ እና አዲስ ካፒታል መካከል በተፈጠረው ውዝግብ እና አለመግባባት ወደ ስራ ሳይገቡ መቆየታቸውን አስታውቋል።ማህበራቱ የፈለጋቸው መኪኖች እና የተገዙት መኪኖች የመጫን አቅም አለመመጣጠኑ በባለሙያ ተረጋግጠው በውሉ መሰረት በአስመጪው ላይ የአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር ቅጣት እንደተጣለም አቶ ኢቢሬ ገልፀዋል ።ከማህበራቱ ጋር ወደ መግባባት እንደተደረሰ የተናገሩት ስራአስኪያጁ ተሸከርካሪዎች በቅርቡ ወደ ስራ እንደሚገቡም አረጋግጠዋል ።
ሀምሳ አራት የደረቅ ቆሻሻ አንሺ መኪኖች ለበርካታ ወራት ወደ ስራ ሳይገቡ መቆየታቸው ተገለፀ
የአለም አቀፍ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማሀበር አይኤኤኤፍ በወርቅ ደረጃ ከሚመድባቸው የጎዳና ውድድሮች የለንደን ማራቶን ተጠቃሽ ነው። ከተመሰረተ አራት አሰርታት ያስቆጠረው ለንደን ማራቶን እንግሊዛውያን ከማንነታቸው ጋር የሚያይዟቸውን ታሪካዊ ቅርሶቻቸውን ለአለም ህዝብ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚያስተዋውቁበት መድረክ እንደሆነ ይታመናል። ውድድሩ ባለፈው እሁድ ሲካሄድ ኬንያዊ ኤሊዩድ በአሸናፊነት ሲያጠናቅቅ፣ ሙስነት ገረመው ሁለተኛ በመሆን አጠናቋል። ሙሌ ዋሲሁን ሶስተኛ የነሀስ ሜዳሊያ ባለቤት ሆኗል። በሴቶች የኢትዮጵያውያን የምንጊዜም ተቀናቃኝ በመሆን የሚታወቁት ኬንያውያኑ ብሪግድ ኮስጊና ቪቪያን ቼሪዮት አንደኛና ሁለተኛ በመሆን ሲያጠናቅቁ፣ ኢትዮጵያዊቷ ሮዛ ደረጃ ሶስተኛ ሆናለች። የለንደን ማራቶን አዘጋጅ ለአሸናፊ አትሌቶች በአጠቃላይ ሶስት መቶ ዶላር ያዘጋጀ ሲሆን፣ ኬንያውያኑ ከፍተኛውን የገንዘብ ሽልማት በማግኘት ቀዳሚ ሆነዋል። እስከ ውድድሩ ፍፃሜ የኤሊዩድ ኪፕቾጌ ጠንካራ ተፎካካሪ ሆኖ የሁለተኛ ደረጃ ይዞ ያጠናቀቀው ሙስነት ገረመው ያስመዘገበው ሰአት ለኢትዮጵያውያንም ሆነ ለለንደን ማራቶን ክብረ ወሰን ሲሆን፣ አብረውት ከተወዳደሩት ኬንያውያኑ ኪፕቾጌና ዊልሰን ኪፕሰንግ ከሙስነት የተሻለ ሰአት የነበራቸው ናቸው። በአለም ከአንድ መቶ ዘጠና ስድስት በላይ አገሮች የቀጥታ ስርጭት እንደነበረው በተነገረለት የለንደን ማራቶን አሸናፊው ኪፕቾጌ ርቀቱን ለማጠናቀቅ ሁለት፡ሁለት፤ ስላሳ ሰባት ጊዜ ሲወስድበት፣ ሁለተኛ የወጣው ሙስነት ገረመው ሁለት፡ሁለት፤ ሀምሳ አምስት እና ሶስተኛ የወጣው ሙሌ ዋሲሁን ሁለት፡ ሶስት፤ በሆነ ጊዜ አጠናቀው መሆኑ ታውቋል። በሴቶች በተደረገው ተመሳሳይ ውድድር ኬንያውያኑ ብሪግድ ኮስጊና ቪቪያን ቼሪዮት ሁለት፡ ፤ ሀያ እና ሁለት፡ ሀያ፤ ሲያጠናቅቁ፣ ሶስተኛ የወጣችው ሮዛ ደረጀ በበኩሏ ሁለት፡ ሀያ፤ ሀምሳ አንድ የገባችበት ሰአት ሆኖ ተመዝግቧል። በሌላ በኩል በአለም አቀፍ ተቋማት ተመሳሳይ እውቅና ካላቸው የጎዳና ውድድሮች አንዱ በሆነው ሀምቡርግ ማራቶን፣ በሁለቱም ፆታ ኢትዮጵያውያኑ አሸናፊ የሆኑበትን ሰአት አስመዝግበዋል። በዚሁ መሰረት በሴቶች አንደኛ የወጣች ዲባባ ኩማ ስትሆን የገባችበት ሰአት ሁለት፡ ሀያ አራት፤ አርባ አንድ ሲሆን፣ በወንዶች ያሸነፈው ታዱ አባተ ደግሞ ሁለት፡ ስምንት፤ ሀያ አምስት በሆነ ጊዜ አጠናቆ መሆኑ ከአለም አቀፉ ተቋም ድረ ገፅ ለማወቅ ተችሏል። በስፔን ማድሪድ በተደረገው የማራቶን ውድድርም ኢትዮጵያውያኑ እንስቶች የተሰጣቸውን የአሸናፊነት ቅድመ ግምት ሲያሳኩ፣ ወንዶቹ ድል ሳይቀናቸው ቀርቷል። በዚሁ መሰረት በሴቶች ከአንደኛ እስከ አራተኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ ያጠናቀቁት ኢትዮጵያውያቱ የወርቅ ሜዳሊያው በበሻሾ ኢንሰርሙ የበላይነት ተጠናቋል። የአሸናፊነቱን ክብር የተቀዳጀችው በሻሾ ርቀቱን ለማጠናቀቅ ሁለት፡ሀያ ስድስት፤ ሀያ አራት ሲፈጅባት፣ ፈታሌ ደጀን ሁለት፡ሀያ ሰባት፤ ስድስት፣ እንዲሁም በሻዱ በቀለና ገበያነሽ አየለ ሁለት፡ስላሳ ሁለት፤ አስር እና ሁለት፡ስላሳ ሁለት፤ ሆነ ጊዜ በማጠናቀቅ አሸናፊዎች ሆነዋል። በወንዶች ኬንያውያኑ በበላይነት ማጠናቀቃቸውም ታውቋል።
ለቶኪዮ ኦሊምፒክ ተስፋ የተጣለበት ሙስነት ገረመው
የሰብአዊ መብት ጥሰት ተጠርጣሪዎች ተቋማትም ተጠያቂ መሆን አለባቸው አሉየፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን በብሄራዊ መረጃና ደሀንነት አገልግሎት ውስጥ አደገኛ መርዝ ማግኘቱን አስታወቀ። የመርዙን አይነትና የጉዳት መጠን በባለሙያ ለማስመርመር እየሰራ መሆኑን በመግለፅ፣ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንደሚያስፈልገውም ገልጿል። መርማሪ ቡድኑን በመቃወም ተጠርጣሪዎች ለፍርድ ቤቱ በተቋሙ ውስጥ መርዝ እንዳለ የተናገሩት እነሱ መሆናቸውን አስረድተው፣ ይኼንንም ያደረጉት መርዙ አደገኛ በመሆኑ ዜጎች ሳያውቁ ቢነኩት ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል በማለት አስበው መሆኑን ገልፀዋል። ነገር ግን መርማሪ ቡድኑ ራሱ በምርመራ እንዳገኘው አድርጎ ለፍርድ ቤቱ በማቅረብና በማስረዳት፣ የተጨማሪ ጊዜ መጠየቂያ ማድረጉ ተገቢ አለመሆኑንና ፍርድ ቤቱ ሊቀበለው እንደማይገባ አሳስበዋል። ፍርድ ቤቱ በማጣሪያ ጥያቄ መርማሪ ቡድኑ መርዙን ያገኘው የፍርድ ቤት መበርበሪያ ትእዛዝ ወስዶ ባደረገው ብርበራ መሆን አለመሆኑን ሲጠይቀው፣ በተጠርጣሪዎቹ ጥቆማ ነው፤ ብሏል። በከባድ የሰብአዊ መብት ጥሰት ወንጀል ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት ተጠርጣሪዎች፣ እነሱ በወንጀል ከተጠረጠሩ ይሰሩባቸው የነበሩ ተቋማትም ስለሚመለከት፣ እነሱም መጠየቅ እንዳለባቸው ለፍርድ ቤት ተናገሩ። በአቶ ጐሀ አፅብሀ የምርመራ መዝገብ የተካተቱ የብሄራዊ መረጃና ደሀንነት አገልግሎት፣ የፌዴራል ፖሊስ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስና የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር አባላት የነበሩ ስላሳ ሶስት ተጠርጣሪዎች ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አስረኛ ወንጀል ችሎት እንዳስረዱት፣ ተጠርጥራችኋል የተባሉት ህጋዊ ሆነው ሲሰሩባቸው በነበሩበት ተቋማት ውስጥ በመሆኑ፣ ተቋማቱም ሊጠየቁ እንደሚገባ አስረድተዋል። ተጠርጣሪዎቹ ብቻቸውን ተጠያቂ ሊሆኑ እንደማይገባ ለፍርድ ቤቱ የገለፁት፣ የተጠረጠሩበትን የወንጀል ድርጊት በማጣራት ላይ የሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን፣ ቀደም ብሎ ተፈቅዶለት በነበረው ቀናት ውስጥ የሰራውን የምርመራ ስራና በቀጣይ ለሚሰራው የምርመራ ሂደት ተጨማሪ ቀናት እንዲፈቀድለት ፍርድ ቤቱን በመጠየቁ ነው። መርማሪ ቡድኑ በተፈቀደለት ቀናት ውስጥ ምርመራውን ያደረገው፣ ተጠርጣሪዎቹን አራት ቦታ በመለየት መሆኑን ጠቁሟል። በርካታ ዜጎችን የኦነግና የአርበኞች ግንቦት ሰባት አባል ናቸው በማለት አፍኖ በመያዝና አይናቸውን አስሮ ወደ ድብቅ እስር ቤት በመውሰድ፣ በጨለማ ቤት ውስጥ በማስቀመጥ እስከ አምስት ወራት ድረስ በማቆየት የተለያዩ ማሰቃያ ዘዴዎችን በመጠቀምና በማሰቃየት የአካል ጉዳት፣ ማምከንና ህይወታቸው እንዲያልፍ ማድረጋቸውን በማስታወስ፣ ድርጊቱ የተፈፀመባቸውን የሀምሳ አንድ ምስክሮች ቃል መቀበሉን ለፍርድ ቤቱ ተናግሯል። በክልል የሚገኙና በደረሰባቸው ግርፋት ወደ አዲስ አበባ መጥተው የምስክርነታቸውን ቃል መስጠት የማይችሉትን ባሉበት ተገኝቶ የሚቀበል መርማሪ ቡድን በማቋቋም መላኩንም አክሏል። በደረሰባቸው ድብደባ ህይወታቸው ያለፈ የሁለት ሰዎች አስከሬን ምርመራ ሁለት አይነት ውጤት በመቀመጡ፣ ጥርት ያለ መረጃ ለማግኘት በድጋሚ ጠይቆ እየተጠባበቀ መሆኑንም መርማሪ ቡድኑ አስረድቷል።ራሳቸው ባቆሟቸው ጠበቆችና መንግስት በመደበላቸው ተከላካይ ጠበቆች አማካይነት የመርማሪ ቡድኑን የምርመራ ሂደት የተቃወሙት ተጠርጣሪዎቹ፣ መርማሪ ቡድኑ በቡድን ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት በማለት የመመርመር ስልጣን የተሰጠውንና ያልተሰጠውን ተቋም ተጠርጣሪ አንድ ላይ መፈረጁ ተገቢ እንዳልሆነ ተናግረዋል። ፍርድ ቤቱ ቀደም ብሎ በነበረ ችሎት ማን በምን እንደተጠረጠረና ስንት ምስክሮች እንደመሰከሩበት፣ ስንት እንደቀሩና የተገኙ ማስረጃዎችን ለይቶ እንዲያቀርብ የሰጠውን ትእዛዝ አለማክበሩን አስረድተዋል። መርማሪ ቡድኑ በጥቅል ስለሚያቀርብ መከራከር እንዳልቻሉ ጠቁመው፣ ለምን የፍርድ ቤቱን ትእዛዝ እንዳላከበረ እንዲጠየቅላቸው አሳስበዋል። መርማሪ ቡድኑ በተደራጀ መልኩ በማለት በጥቅል የሚያቀርበውን መከራከሪያ ሀሳብ በተናጠል እንዲያቀርብ ጠይቀው፣ ከአምስት ወራት በላይ ምርመራ ሲያደርግ እንደነበር ሲገልፅ ከርሞ በየቀጠሮው ተጨማሪ ቀናት የምርመራ ጊዜ መጠየቁ፣ የመንግስትንም ተአማኒነት የሚያሳጣ መሆኑን ተናግረዋል። ፍርድ ቤቱ የተጠርጣሪውን መብት ማስከበርና ፍትህ እንዳይጓደል መርማሪ ቡድኑ የተሰጠውን ትእዛዝ እንዲያከብር ማድረግ እንዳለበትም ተናግረዋል። ከህገ መንግስቱና አለም አቀፍ ድንጋጌዎች አንፃር የእነሱም ሰብአዊ መብት ሊከበር እንደሚገባ ጠቁመው፣ እንደተያዙ የተጠረጠሩበት የወንጀል ድርጊት ሊነገራቸውና ቃላቸውንም መስጠት ሲገባቸው በአርባ ስምንት ቀናት ውስጥ ቃላቸውን ያልሰጡ ተጠርጣሪዎችም እንዳሉ ተናግረዋል። የመርማሪ ቡድኑ አባላት የተጠርጣሪዎቹን የወንጀል ተሳትፎ መለየት ያቃታቸው በሁለት ምክንያት መሆኑን ጠቁመው፣ የመለየት ችሎታ ስለሌላቸው ወይም ወንጀል ስለሌለ መሆኑን ገልፀዋል። አንዳንዶቹ ተጠርጣሪዎች እንዳስረዱት፣ በተቋማቸው ውስጥ እየተመሰገኑና እድገት እየተሰጣቸው ስራቸውን በአግባቡ ሲሰሩ ከመቆየታቸው ባለፈ ምንም የፈፀሙት የወንጀል ድርጊት እንደሌለ ተናግረው፣ መርማሪ ቡድኑ አርባ ስምንት ቀናት ካሰራቸው በኋላ አዲስ ወንጀል ፍለጋ አዲስ መርማሪ ቡድን በማዋቀር ወደ ክልል እየላከ መሆኑን ለፍርድ ቤቱ መግለፁ ተገቢ ካለመሆኑ በተጨማሪ፣ እነሱን ስለማይመለከታቸው የጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ውድቅ ተደርጎ የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው ጠይቀዋል። አንዳንዶቹ ተጠርጣሪዎች የተጠረጠሩበት የወንጀል ድርጊት ተለይቶ ባይነገራቸውም ቃላቸውን መስጠታቸውን፣ ፎቶግራፍ መነሳታቸውንና አሻራ መስጠታቸውን ገልፀው የቀራቸው ነገር ስለሌለ ዋስትና እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል። አንዳንዶቹ ደግሞ የሰብአዊ መብት ጥሰት የሚባል ወንጀል የለም። በህግም የተደነገገ አይደለም። ነገር ግን የሰብአዊ መብት ጥሰት ፈፅማችኋል ከተባለ በመረጃና በማስረጃ ሊቀርብብን ይገባል፤ በማለት ፎቶግራፍ ተነሱ መባላቸውንና አሻራ ስጡ መባላቸውን ተቃውመዋል።፡ አሻራና ፎቶ የሚያስፈልገው ወንጀሉን ለመመዝገብ በመሆኑ፣ እነሱ ደግሞ በቡድን ከማለት ባለፈ በግል የፈፀሙት ወንጀል ተለይቶ እስካልተነገራቸው ድረስ አስፈላጊ አለመሆኑን አስረድተዋል። እያስጠየቃቸው ያለው ህጋዊ ሆኖ በሚሰራ ተቋም ውስጥ ሲሰሩ በነበረ ድርጊት በመሆኑም፣ ተቋማቱም ሊጠየቁ እንደሚገባ ደጋግመው ተናግረዋል። የወንጀል ህግ አላማ ማስተማር መሆኑን ተጠርጣሪዎቹ ተናግረው የወንጀል ድርጊት በራሱ የሚመጣ እንጂ በፍለጋ እንደማይገኝ፣ ነገር ግን መርማሪ ቡድኑ ባልተሰራ ወንጀል እነሱን አስሮ ወንጀል ፍለጋ ላይ እንደሆነ በማስረዳት ተቃውሞአቸውን አሰምተዋል። ሲሰሩ የኖሩት በመመርያና በደንብ መሆኑን ጠቁመው አንድ ተጠርጣሪ ላይ በምን ያህል ቀናት ምርመራ ተሰርቶ መጠናቀቅ እንዳለበትና ወንጀሉ ከባድ ከሆነም ምን ያህል ጊዜ እንደሚወስድ እንደሚታወቅ በመናገር፣ በእነሱ ላይ ግን እየተንዛዛ መሆኑን አስረድተዋል። የሰው ምስክርነት ከአንድ ማስረጃ ጋር ከተጣረሰ ወንጀል የለም ማለት ነው በማለት የሰብአዊ መብት ጥሰት ተፈፅሟል እየተባለ፣ እነሱም ላይ ባልተጨበጠ የወንጀል ድርጊት ሰብአዊ መብታቸው እየተጣሰ መሆኑን ገልፀዋል። የግራ ቀኙን ክርክር የሰማው ፍርድ ቤቱ አቶ ጐሀ አፅብሀን ጨምሮ ተጠርጣሪዎች ያቀረቡትን ተቃውሞና የጠየቁትን ዋስትና ባለመቀበል መርማሪ ቡድኑ የጠየቀውን ቀናት ፈቅዶ፣ ለታሀሳስ ስላሳ ቀን ሁለት ሺህ አመተ ምህረት ቀጠሮ ሰጥቷል። ምክትል ኮማንደር አለማየሁ ሀይሉን ጨምሮ ተጠርጣሪዎችም ያቀረቡትን ተቃውሞ በማለፍ መርማሪ ቡድኑ ከጠየው ቀናት ውስጥ አስር ተጨማሪ የምርመራ ቀናት በመፍቀድ ለታሀሳስ ሀያ ስድስት ቀን ሁለት ሺህ አመተ ምህረት ቀጠሮ ሰጥቷል። ፍርድ ቤቱ ትእዛዙን የሰጠው የምርመራ መዝገቡን አስቀርቦ ከተመለከተ በኋላ ነው። ከህፃን ልጇ ጋር ታስራ በምትገኘው ዋና ሳጅን እቴነሽ አረፈአይኔ ላይ መርማሪ ቡድኑ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ጠይቆ የተፈቀደለት ቢሆንም፣ ፍርድ ቤቱ መዝገቡን አስቀርቦ ሲመለከተው የተሰራ ምርመራ አለመኖሩን በማረጋገጡ በስላሳ ብር ዋስ እንድትፈታና ከአገር እንዳትወጣ ለኢሚግሬሽንና የዜግነት ጉዳዮች ዋና መምርያ እንዲፃፍ ትእዛዝ ሰጥቷል። በደሀንነት ተቋም ውስጥ ተገኘ የተባለው መርዝ ከተጠርጣሪዎቹ ጋር የሚያገናኘው ነገር ስለሌለ እንዳልተቀበለው አስታውቋል።በተመሳሳይ የወንጀል ጥርጣሬ በእስር ላይ የሚገኙት የብሄራዊ መረጃና ደሀንነት አገልግሎት የዋና ዳይሬክተሩ ፅህፈት ቤት ሀላፊ ነበሩ የተባሉት አቶ መአሾ ኪዳኔና በተቋሙ የስምሪት፣ የአትክልትና የፅዳት ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ሀዱሽ ካሳ ላይም ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተጠይቆ አስር ቀናት ተፈቅዷል። መርማሪ ቡድኑ ቀደም ብሎ በነበረው ችሎት በተሰጠው ጊዜ የአምስት ሰዎች ምስክርነት ቃል መቀበሉን፣ ሀላፊነታቸውን ከተቋማቸው ጠይቆ መቀበሉን፣ የአቶ ሀዱሽ ባለቤት ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ በንግድ ባንክ ተቀማጭ ብር እንዳላቸው ማረጋገጡንና በተጠርጣሪው ስም የተለያዩ የቤት ሽያጭ ውል ስምምነት ሰነድ ማግኘቱን ተናግሯል። ተጨማሪ ድብቅ እስር ቤትም ማግኘቱን ገልጿል። ተጨማሪ የተጎጂ ምስክሮች ቃል መቀበል፣ የህክምና ማስረጃ ሰነድ ማሰባሰብና የምርመራ ቡድን አቋቁሞ ወደ ክልል ሊልክ መሆኑን አስረድቶ የጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንዲፈቀድለት ጠይቋል። የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዱት፣ ደንበኞቻቸው የተጠረሩት የኦነግና የግንቦት ሰባት አርበኞች አባል የነበሩ ዜጎችን በማሰርና በማሰቃየት መባሉ በወቅቱ ህጋዊ አሰራር ነበር። ምክንያቱም በህግ አውጪው ምክር ቤት የተወገዙ ድርጅቶች ስለነበሩ መሆኑንም ተናግረዋል። በቡድን እያለ የሚናገረው መርማሪ ቡድኑ ማን ከማን ጋር ተቧድኖ ምን እንደሰራ የገለፀው ስለሌለ ግልፅ አለመሆኑን አክለዋል። በመሆኑም የወንጀል መነሻ ጥርጣሬ ስለሌለ ምርመራ መጀመር እንደሌለበትም ገልፀዋል። አቶ ሀዱሽ በባለቤታቸው ስም ገንዘብ ተቀምጧል መባሉ ከተጠቀሱት ሴት ጋር ህጋዊ የሆነ የጋብቻ ሰነድ ስለሌላቸው፣ እሳቸውን እንደማይመለከትም አስረድተዋል። እነሱ ከአዲስ አበባ ወጥተው የማያውቁ መሆናቸው እየታወቀ፣ መርማሪ ቡድን በማቋቋም ወደ ክልል እንደሚልክ መናገሩ ተገቢ እንዳልሆነም ገልፀዋል። በመሆኑም መርማሪ ቡድኑ የጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ውድቅ ተደርጎ የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው ጠይቀዋል።የግራ ቀኙን ክርክ ያዳመጠው ፍርድ ቤት የተጠርጣሪዎቹን የመቃወሚያና ዋስትና ጥያቅ ውድቅ በማድረግ ከተጠየቀው ቀናት ውስጥ በአብላጫ ድምፅ አስር ቀናት በመፍቀድ ለታሀሳስ ሀያ ስድስት ቀን ሁለት ሺህ አመተ ምህረት ቀጠሮ ሰጥቷል።
በብሄራዊ መረጃና ደሀንነት አገልግሎት ውስጥ አደገኛ መርዝ መገኘቱን የፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ
በተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽነር ዘይድ ራአድ አል ሁሴን ከሚያዝያ ሀያ አራት ሀያ ስድስት ሁለት ሺህ ዘጠኝ አመተ ምህረት ኢትዮጵያን ይጎበኛሉ።ኮሚሽነሩ የኢፌዴሪ መንግስት ባደረገላቸው ግብዣ መሰረት ነው ሀገሪቱን የሚጎበኙት።እግረ መንገዳቸውን ከአፍሪካ ህብረት መሪዎች ጋር እንደሚወያዩም ታውቋል።በኢትዮጵያ ቆይታቸው የሀገሪቱን የሰብአዊ መብት ሁኔታና የመንግስታቱን ድርጅት የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ተግባራት በተመለከተ ከጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ፣ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ አባዱላ ገመዳና ከሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ጋር ምክክር ያደርጋሉ።ከዚህ በተጨማሪ ኮሚሽነሩ ከኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር አዲሱ ገብረእግዚአብሄር፣ ከኢትዮጵያ ሲቪል ሶሳይቲ ድርጅቶችና ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ተገናኝተው እንደሚነጋገሩም ታውቋል።ኮሚሽነር ዘይድ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሀማትን ጨምሮ ከህብረቱ የሰላምና ደህንነት ኮሚሽነር ስማይል ቼርጉይና ከህብረቱ የፖለቲካ ጉዳዮች ኮሚሽነር ሴሱማ ሚናታ ሳማቴ ጋር ተገናኝተው የሁለቱን ተቋማት ሰብአዊ መብቶች ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት መንገድ ምክክር ያደርጋሉ።ከዚህ በተጨማሪ ትብብራቸውን ለማጠናከር በቅርቡ በሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ የተጠናከረ ትብብር ለማድረግ በኒዮርክ የተፈረመው ስምምነት ትግበራና መሰል የትብብር ዘርፎች የውይይታቸው አጀንዳዎች እንደሚሆኑም ተገልጿል። ኮሚሽነሩ በጉብኝታቸው ማጠቃለያ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የስብሰባ አዳራሽ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጡም በተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽን ቢሮ ይፋ አድርጓል ኢዜአ ።
በተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽነር ኢትዮጵያን ሊጎበኙ ነው
ላለፉት አመታት ከተለያዩ የአለም አገራት የባኞ ቤት የህንፃ ማጠናቀቂያ የሳውና የጃኩዚና መሰል የሴራሚክ ምርቶችን በማስመጣት ለአገር ውስጥ ገበያ ሲያቀርብ የቆየው ኢትዮ ሴራሚክስ አምስተኛውን ትልቅና ዘመናዊ የሴራሚክስ መሸጫ ማእከል ቦሌ ኖቪስ ሱፐር ማርኬት ፊት ለፊት አዲስ በገነባው ህንፃ ላይ ከፈተ። ከትላንት በስቲያ በይፋ ስራ የጀመረው ይሄው መደብር ከሌሎቹ መደብሮች በተለየ የተደራጀና እቃዎች ተገጣጥመው ዲስፕሌይ የተደረጉበት ሲሆን ማንኛውም ደንበኛ እቃዎቹን ሲገዛ ምን እንደሚመስሉና ምን ቅርፅ እንደሚኖራቸው በማየት የሚገዛውን ለመወሰን እንዲችል የሚረዱ መሆናቸው በእለቱ ተገልጿል።ከዱባይ ስፔይን ጣሊያን ፈረንሳይ ጀርመንና ከቻይና የመጡ የሴራሚክስ እቃዎች እንደየመጡበት አገርና ሁኔታ ተለይተው የተቀመጡ ሲሆን በአገራችን የቤት ውስጥ ዲዛይነር ህንፃው ላይ ተሰርተው ተቀምጠዋል። በኛና ኛ ፎቅ ላይ በአይነት በአይነት የተደረደሩ የተለያዩ አገራት የሴራሚክስ ውጤቶች የቀረቡ ሲሆን ኛ እና ኛ ፎቅ ላይ ደረጃቸውን የጠበቁ ሶፋዎች አልጋዎች የቢሮና የመመገቢያ ወንበርና ጠረጴዛዎች ቁም ሳጥኖች ይገኙበታል ይህ የሽያጭ ማእከሉ አደረጃጀት አንድ ሰው ቤት ሰርቶ ሲያጠናቅቅ ቤቱን ለመጨረስና ሁሉንም እቃ በአንድ ቦታ ለማግኘት እንዲችል የሚያግዝ መሆኑን የኢትዮ ሴራሚክስ የሽያጭና ግብይት መምሪያ ሀላፊ አቶ ሚፍታህ አክመል ገልፀዋል። እያንዳንዱ የሴራሚክስ እቃዎች አዳዲስና የ ስሪት እንደሆኑ የገለፁት ሀላፊው የጥራት ደረጃቸውን የጠበቁ በመሆናቸው ከመላላጥና ከኬሚካል ጉዳት የፀዱ ናቸው ብለዋል። ደንበኞችን በአግባቡ ለማስተናገድና ስለ እቃዎቹ ስሪትና ምንነት በቂ መረጃ እንዲሰጡ የሰለጠኑ ከ በላይ የሽያጭ ሰራተኞች መኖራቸውን የድርጅቱ የሽያጭና ደንበኞች አገልግሎት ሀላፊ አቶ መሀመድ ሳሌህ ጨምረው ገልፀዋል። በሽያጭ ማእከሉ የአልጋ ትልቁ ዋጋ ሺህ ብር ሲሆን ሶፋ ትልቁ ዋጋ ሺህ ብር መሆኑም ታውቋል። የአልጋ መሸጫ ትንሹ ዋጋ ሺህ ሲሆን የሶፋ ትንሹ ዋጋ ሺህ ብር እንደሆነ አቶ መሀመድ ጨምረው ገልፀዋል።
ኢትዮ ሴራሚክስ ኛውን ትልቅና ዘመናዊ ሾውሩም በቦሌ ከፈተ
መጋቢት ፳ ሀያ ቀን ፳፻፰ አመተ ምህረት ኢሳት ዜና በደቡብ ክልል ሰሜናዊ ዞን በሀላባ ማረቆ ወረዳ የተከሰተው መጠነ ሰፊ የርሀብ አደጋ አስከፊ መሆኑን ዩኒሴፍ አስታውቀዋል። በደቡብ ክልል ከሚገኙ አንድ መቶ ስላሳ ስድስት የገጠር ወረዳዎች ውስጥ በክልሉ ትርፍ አምራች የነበሩት ሰባ ሶስት ወረዳዎች ከፍተኛ አደጋ ይንዣበባቸው ሲሆን፣ ከእነዚህም ውስጥ አርባ አምስትቱ ወረዳዎች በዝናብ እጥረት ምክንያት አስጊ ሁኔታ ውስጥ መሆናቸውን ዩኒሴፍ አመልክቶአል። ድርቁን ተከትሎ የተፈጠረው የውሀ እጥረት እንስሳት ላይም ከፍተኛ እልቂት አስከትሏል። በማረቆ ወረዳ የዋሻ ፈቃ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርእሰ መምህር ሰልፋ ደሎኮ ተማሪዎቹ በባዶ ሆዳቸው ወደ ትምህርት ቤት ይመጣሉ። ስለሚርባቸው አትኩሮት ሰጥተው ትምህርታቸውን መከታተል ተስኗቸው በጊዜ ትምህርት አቋርጠው ወደ ቤታቸው ይሄዳሉ። ሲሉ ርሀቡ በማማር ማስተማሩ ሂደት ላይ አደጋ መደቀኑን አስረድተዋል። መምህሩ ሀያ የሚሆኑ ተማሪዎች በድርቁ ሳቢያ ትምህርታቸውን አቋርጠው እቤት ለመዋል መገደዳቸውንም አስረድተዋል። አንድ የአካባቢው ነዋሪ የ አመቱ ታዳጊ ተማሪ በበኩሉ በቀበሌው አቅራቢያ ያለው የውሀ ምንጭ በመድረቁ የቤት እንስሳትን ውሀ ለማጠጣትና ለመጠጥ ውሀ ለማግኘት ሲል ረዥም መንገድ ለመጓዝ በመገደዱ ትምህርቱን አቁሞዋል። ተማሪው አክሎም፣ ትምህርት እንደሚጠቅመኝ ባውቅም ቤተሰቤን ማገዝም ግዴታዬ ነው። በዚህም ምክንያት አርፍጄ እመጣለው ወይም በጭራሽ ሳልማር እቀራለሁ ብሎአል። የደቡብ ክልል መስተዳድር ለአካባቢው አርሶ አደሮች የመጠጥ ውሀ ችግሮች ምንም አይነት የመፍትሄ እርምጃዎችን እስካሁን አልወሰደም። በተመሳሳይ በአማራ፣ትግራይ፣ ኦሮሚያና አፋር ክልሎች ላይ በደረሰው ድርቅ ምክንያት ከሶስት ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ትምህርት ለማቆም ተገዷል። በኢትዮጵያ የተከሰተውን አስከፊ የርሀብ አደጋ ጉዳተኞች ለመታደግ አለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች ዘመቻ መጀመራቸውን ዩኒሴፍ አስታውቋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብት እርዳታ ክፍል እንዳስታወቀው፣ አለማቀፍ እርዳታ እየቀረበ ቢሆንም፣ በወደብ መጨናነቅ ምክንያት በጅቡቲ ወደብ ሰማኒያ ሺ ቶን የሚሆን ምግብ አልተራገፈም። መንግስት ለእርዳታው ቅድሚያ እንዲሰጥ ካላደረገ የሁለተኛውን ዙር ምግብ የማከፋፈል ስራ አደጋ ላይ ይጥለዋል።
በደቡብ ክልል ማረቆ ወረዳ በእርሀቡ ምክንያት ታዳጊ ተማሪዎች ትምህርታቸውን ለማቋረጥ ተገደዱ
አዲስ አበባ፣ ነሀሴ ስምንት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ እነ አቶ እስክንድር ነጋ በተጠረጠሩበት የእርስ በርስና የሀይማኖት ግጭት ማስነሳት ወንጀል አራት ምስክሮችን ችሎት አቅርቦ አሰምቷል።በዚህም ሶስትኛ፣ አምስትኛ፣ ስድስትኛ እና ሰባትኛ ተራ ቁጥር ላይ የተመዘገቡ ምስክሮች ቀርበው ቃላቸውን ሰጥተዋል።እነ አቶ እስክንድር በነሀሴ ስድስት ቀን ጠበቆቻችንን አንፈልግም ብለው ማሰናበታቸውን ተከትሎ ፍርድ ቤቱ ህገ መንግስታዊ መብታቸው እንዲጠበቅ የመንግስት ተከላካይ ጠበቃ ያቆመላቸውና በዛሬው እለት ምስክርን ለመስማት ተለዋጭ ቀጠሮ የሰጠ ሲሆን እነ አቶ እስክንድር ግን ዛሬም የቆመላቸውን ተከላካይ ጠበቃ አንፈልግም ሲሉ አሰናብተዋል።ተከላካይ ጠበቃው ተጠርጣሪወቹን ለማማከር ብሞክርም አንፈልግም ጠበቃ የማቆም አቅም ስለሌለን አይደለም ፤ ፍርድ ቤቱም ይህን ሰምቶ ያሰናብተኝ ሲል ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ ያቀረበ ሲሆን ፍርድ ቤቱም አሰናብቶታል።አቃቤ ህግ ያቀረባቸው አራት ምስክሮች ቃላቸውን የሰጡ ቢሆንም አቶ እስክንድር ነጋ በምስክሮቹ ላይ መስቀለኛ ጥያቄ ካለዎት ተብለው ለቀረበላቸው ጥያቄ ብዙ ጥያቄ ቢኖረኝም ምንም አይነት መስቀለኛ ጥያቄ ማቅረብ አልፈልግም ብለዋል።ፍርድ ቤቱም ቀሪ የአቃቤ ህግ ምስክሮችን ለመስማት ለነሀሴ ቀን ሁለት ሺህ አመተ ምህረት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።በታሪክ አዱኛ
አቃቤ ህግ በእነ አቶ እስክንድር ነጋ ላይ የቅድመ ምርመራ ምስክሮችን አሰማ
ኔልሰን ማንዴላ የደቡብ አፍሪካ የፀረአፓርታይድ የዘርመድሎ ተዋጊ አርበኛ መሆናቸው ይታወቃል። በደቡብ አፍሪካ ዘረኛ መንግስትለእስር የተዳረጉት ኢትዮጵያ ውስጥ ወታደራዊ ስልጠና ወስደው እንደተመለሱ ነበር። እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ አም ማንዴላ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ኢትዮጵያ ፓስፖርት በመስጠት አጋርነቷን የገለፀች ብቸኛ ሀገር ነበረች።ከዘመናት በሀላ ማንዴላ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ወቅት የግድያ ሙከራ ሴራ ተደርጎ እንደነበር ሚስጥሩን ከግማሽ ክፍለዘመን በላይ ይዘው የቆዩ በቀዳማዊ አፄ ሀይለስላሴ ዘመን የኢትዮጵያ ፖሊስ መኮንን ዛሬ ጥቅምት አም ለመጀመርያ ጊዜ በሸገር ራድዮ የዜና እወጃ ላይ ገልፀዋል።ሻምበል ጉታ ዲንቃ በንጉሱ ዘመን የፖሊስ መኮንን ነበሩ። ማንዴላን በከፍተኛ ሚስጥር እንዲጠብቁ ሀላፊነት ከተሰጣቸው ጄኔራል ታደሰየማንዴላ አሰልጣኝ በወቅቱ ኮል የነበሩኮል ፍቃደ እና ሻምበል ፈቃደ ውስጥ ነበሩ።ዛሬ የ አምቱ የእድሜ ባለፀጋ ሻምበል ጉታ ዲንቃ ለሸገር ሲናገሩ እንዲህ አሉ።ማንዴላን እንድጠብቅ ሀላፊነት የተሰጠኝ እኔ ነበርኩ።ማንዴላ የሚያድሩበት እና ወታደራዊ ስልጠና የሚወስዱበት የኮልፌ የፖሊስ ማሰልጠኛ ቦታነበር።በተለይ እርሳቸው የሚገኙበት ቦታ የፈንጅ ወረዳ ነበር የሚባለው።ከአራታችን በቀር ማንም ወደ እርሳቸው ቦታ ዝር ማለት አይችልም። ሲተኙ መስኮት ከፍተው ነው የሚተኙት።አንድ ቀን ታድያ አብሮኝ ከሚሰራው የፖሊስ ባልደረባዬ በጥብቅ እንደሚፈልገኝ ነገረኝ።ጣይቱ ሆቴል ተቀጣጠርን እና ሀሳቡን ገለፀልኝ። ካሉ በሀላ አሁን አዲስ አበባ ላፍቶ አካባቢ ነዋሪ የሆኑት ሻምበል ጉታ በመቀጠል እንዲህ ብለዋልጣይቱ ሆቴል የወሰደኝ ሰው ለጊዜው ፓውንድ በወቅቱ አስቡት ፓውንድን እና ሰጥቶ እንዲህ አለኝ ሁለት እድል ከፊታችን ተቀምጧል።ሊያመልጠን አይገባም።ከፍተኛ ገንዘብ እናገኛለን።ቀጥሎም ወደ ውጭ ሀገር የመሄድ እድል አለን።ከአንተ የሚጠበቀው ማንዴላ በተኛበት ዛሬ ሌሊት በመስኮት ገብተህ በገመድ አንቀህ ግደል እና ውጣ እንደወጣህ መኪና ተዘጋጅቶ ይጠብቅሀል ከእዚህ የውትድርና ህይወት እንገላገላለን አለኝ። እኔም ጉዳዩን ከሰማሁ በሀላ በጉዳዩ የተስማማሁ መስዬ ቀጥታ ለጀኔራል ታደሰ ነገርኩኝ። ጉዳዩ በሚስጥር ተይዞ ይህንን ያደረጉት ሰዎች ተደረሰባቸው እና ከሀገር እንዲወጡ እንዲባረሩተደረጉ ይህ ሚስጥር ለዘመናት ከእኔ ጋር የኖረ ነው።ጉዳዩን ማንዴላም አያውቁትም። ብለዋል።ኢትዮጵያ ለኔልሰን ማንዴላ የሰጠቻቸው ፓስፖርትኔልሰን ማንዴላ በወቅቱ እንደ ሻምበል ጉታ ዲንቃ አይነት ታማኝ የኢትዮጵያ የፖሊስ መኮንን ባይገጥማቸው ኖሮ የደቡብ አፍሪካ የነፃነት ታሪክ ሂደትም ሆነ የነፃነት ትግሉ ታሪክ ሌላ መልክ በያዘ ነበር።ይህ ጉዳይ እጅግ ትልቅ ጉዳይ ነው።የኢትዮጵያ ፖሊስ ለአፍሪካ ያደረገው አስተዋፆ የሚያጎላ በመሆኑ በኢትዮጵያ የዜና አገልግሎቶች ሁሉ ትኩረት ተሰጥቶት የአለም አቀፍ የዜና ሽፋን እንዲያገኝ ጥረት ማድረግ ለኢትዮጵያ ፋይዳው ብዙ ይመስለኛል። እስካሁን ድረስ ማንዴላ በኢትዮጵያ ምን ያህል ድጋፍ ተደርጎላቸው እንደነበር የማያውቅ አፍሪካዊም ሆነ ደቡብ አፍሪካዊ እንዲሁም የአለም ህዝብ አለ። በመሆኑም ይህ ጉዳዩን ለማጮህ የሚረዳ ወርቃማ አጋጣሚ ነው።በመሆኑም ቢያንስ ለሻምበል ጉታ ዲንቃ የኢትዮጵያ ፖሊስ ጠርቶ ማእረግ እና ሽልማት ከእዚህ ባለፈም ጋዜጣዊ መግለጫ መስጠት እና ማንዴላ በህይወት ዘመናቸው ሳሉ ሻምበል ጉታ ደቡብ አፍሪካ ድረስ ሄደው እንዲያገኟቸው ማድረግተገቢ ይመስለኛል። ጉዳዩ የደህንነት ሚስጥር የነበረ በመሆኑ በወቅቱ ግድያውን ሊፈፅም የሞከረው አካል ወይንም ሀገር ማንነቱን ሻምበል ጉታ የተባረሩት ዜጎች የየት ሀገር እንደነበሩ አልገለፁም ዛሬ ከደቡብ አፍሪካ ጋር ለሚኖረው ግንኙነት ላይጥላ እንዳያጠላ ስጋት ስለሚሆን ዜናው በተፈለገው ደረጃ ለአለም ህዝብ እንዳይደርስ የሚደረጉ ስውር ስራዎች እንደማይጠፋ ማጤን ሌላው ስራ ሊሆን ይችላል።በመጨረሻም ሻምበል ጉታ ዲንቃ ለህዝብ ወጥተው ዛሬ ላይ ምንም ምስጢርነት የሌለውን ጉዳይ ለህዝብ በመንገራቸው ሊመሰገኑ ይገባል።ምንጭ ሸገር ራድዮ ቅንብር ጉዳያችን ጡመራ ቀን አርብ ጥቅምት አም
ማንዴላን በተመለከት ለግማሽ አመታት የተደበቅ ምስጢር
ባሌ ሮቤ፦ የሰብል ማጨጂያና መውቂያ ማሽን ኮምባይነር እጥረት ምርትን በወቅቱ ለመሰብሰብ ስጋት እንደፈጠረባቸው በኦሮሚያ ክልል የባሌ ዞን አርሶ አደሮች ገለፁ። የባሌ ዞን አጋርፋ ወረዳ አርሶ አደሮች ሰሞኑን ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለፁት፤ በአካባቢያቸው በኮምባይነር ሰብልን ማጨድና መውቃት የተለመደ ነው። ይሁን እንጂ በዘንድሮ የምርት ዘመን የኮምባይነር አቅርቦት እጥረት በማጋጠሙ ምርታቸውን በወቅቱ ሰብስበው ለማስገባት ስጋት ፈጥሮባቸዋል። የኮምባይነር ተጠቃሚ ከሆኑት አንዱ አርሶ አደር አብዱል ሀኪም አማን እንደገለፁት፤ የሲናና ግብርና ማእከልና የአጋርፋ ወረዳ ግብርና ቢሮ በሚያደርጉላቸው እገዛ በየጊዜ የግብርናቸው አሰራር ዘምኗል። ምርታቸውም ጨምሯል። የዘንድሮው ምርታቸው ደግሞ ከመቼውም ጊዜ በላይ ጥሩ እንደሆነ ይገልፃሉ። ነገር ግን ባጋጠመው የኮምባይነር አቅርቦት እጥረት ሰብላቸውን በወቅቱ መሰብሰብ እንዳልቻሉ አመልክተዋል። ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በደረሱ ሰብሎች ላይ ጉዳት ከማድረሱ በፊት የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት የማጨጂያና መውቂያ ማሽኖችን እንዲያቀርቡላቸው ጠይቀዋል። የአጋርፋ ወረዳ ግብርና ኤክስቴንሽን ስራ አስኪያጅ አቶ አማን አብዱል ቃዲር እንዳስረዱት፤ በሰብል መሰብሰብ ወቅት ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ኮባይነሮችን በማስመጣት ምርት የመሰብሰቡ ሂደት ይከናወን ነበር። በአሁኑ ጊዜ በአንዳንድ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተከሰተው የሰላም ችግር ኮባይነሮችን ወደ አካባቢው ማምጣት አላስቻለም። ችግሩን ለመፍታትም ኮሚቴ ተዋቅሮ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የአካባቢው አርሶ አደሮች የሲናና ግብርና ምርምር ማእከል በሚያደርገው ድጋፍ ምርታማነታቸው መጨመሩንና በምርት ዘመኑም አብዛኛው መሬት በተለያዩ የስንዴ ሰብሎች መሸፈኑን የጠቆሙት አቶ አማን፣ የኮምባይነር እጥረት ሰብሉን በወቅቱ ሰብስቦ ምርት ለማስገባት እንቅፋት እንደሆነ ገልፀዋል። ችግሩን ለመፍታት የተለያዩ አካላት ድጋፍ ያስፈልጋል ብለዋል። በባሌ ዞን የአጋርፋ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሶፊያን ተማም የአካባቢው አርሶ አደሮች በትራክተር የማረስ እና በኮምባይነር የማሳጨድ ልምዳቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ጠቅሰው፤ በምርት ዘመኑ የሰብል ማጨጂያና መውቂያ ኮምባይነር ማግኘት የተቻለው ጥቂት ብቻ መሆኑን አመልክተዋል። ችግሩን ለመፍታት ከተለያዩ አካላት ጋር በሚደረጉ ምክክሮች በተያዘው ወር አቅርቦቱን ለማስተካከል ጥረት እንደሚደረግ አስታውቀዋል። የአጋርፋ ወረዳ በአመት ሁለት ጊዜ የሚመረትበት አካባቢ ሲሆን በመኸር ወቅቱም አንድ ሺ ሀያ ስምንት ሄክታር መሬት በሰብል እንደተሸፈነ እና ከዚህም አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ ኩንታል ምርት ይሰበሰባል ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ሶፊያን ገልፀዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ ዘጠኝ ሁለት ሺህ ኢያሱ መሰለ
የሰብል ማጨጂያና መውቂያ ማሽንእጥረት ስጋት ፈጥሯል
ፀረ አረም መድሀኒቶችን ለውጭ ገበያ ለማቅረብ አቅዷልበፕራይቬታይዜሽንና የመንግስት የልማት ድርጅት ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ ከሚያስተዳድራቸውና ለሽያጭ አቅርቧቸው ከነበሩ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ውስጥ አንዱ የሆነው አዳሚ ቱሉ ፀረ ተባይ ማዘጋጃ አክሲዮን ማህበር ከ ሚሊዮን ብር በላይ ያስገነባውን አዲስ ማምረቻ በማጠናቀቅ ስራ ጀመረ።ከአዲስ አበባ በ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ዝዋይ ከተማ የተገነባውና ስራ የጀመረው ማምረቻ የተባለውን ፀረ አረም መድሀኒት የሚያመርትና በተለያዩ መጠን ባላቸው መያዥያዎች የሚያሽግ ፋብሪካ ነው።ባለፈው ቅዳሜ በይፋ የተመረቀው አዲሱ ፀረ አረም ማምረቻ አክሲዮን ማህበሩ የተለያዩ ፀረ አረምና በሽታ ተከላካይ መድሀኒቶችን ከሚያመርትበት ፋብሪካ ጋር ተያይዞ የተሰራ ነው። እንደ አክሲዮን ማህበሩ የስራ ሀላፊዎች ገለፃ አዲሱ ምርቱ በአክሲዮን ማህበሩ የሚመረቱ ፀረ አረም መድሀኒቶችን ቁጥር ወደ ያሳድግለታል። ከዚህም ሌላ አገሪቱ በአመት እስከ ሚሊዮን ብር በላይ የውጭ ምንዛሪ ታወጣበት ነበር የተባለውን ፀረ አረም በአገር ውስጥ መመረቱ ለፀረ አረም መድሀኒቱ ግዥ ይውል የነበረውን የውጭ ምንዛሪም በመቀነሱ ረገድ ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል ተብሏል።በኢትዮጵያ ውስጥ ፀረ ተባይ መድሀኒቶችን በማምረት የሚታወቀው አዳሚ ቱሉ ፀረ ተባይ አክሲዮን ማህበር የማስፋፊያ ስራዎችን እያከናወነ ያለው በዘርፉ የተሰማራ የግል ባለሀብት ባለመኖሩ ጭምር ነው። የአክሲዮን ማህበሩ መረጃ እንደሚገልፀው በኢኮኖሚው ዘርፍ የግል ባለሀብቱ በተሟላ መልኩ ባልተሳተፈባቸው እንዲህ ባሉ ምርቶች መንግስታዊው አክሲዮን ማህበር ድርሻውን እየተወጣ ነው።ከአክሲዮን ማህበሩ የተገኘው ተጨማሪ መረጃ እንደሚያስረዳው ከዚህም በኋላ ፋብሪካውን የማስፋፋት ስራ የሚቀጥል መሆኑን ነው። ለዚህም የአምስት አመት እቅድ ተነድፏል። በእቅዱ መሰረት አሁን በመመረት ላይ ያሉትን የተለያዩ ፀረ አረም ምርቶች ቁጥር ወደ ለማሳደግ የሚለው ይገኝበታል።በቀጣዩ አምስት አመታት የፀረ አረም ምርቶችን ቁጥር ከማሳደግ ባሻገር አራት ፀረ አረም ምርቶችን በመለየት ለጎረቤት አገሮች ለመሸጥና ፋብሪካው የውጭ ምንዛሪ ማስገኛ እንዲሆን ጭምር መታቀዱን ያመላክታል።የውጭ ምንዛሪ የሚጠይቁና ከተለያዩ አገሮች የመጡ የነበሩ ፀረ አረም መድሀኒቶችን በአገር ውስጥ የማምረት የሚያስችል ውጥን መያዙንና አሁን በአገር ውስጥ በሚመረቱ ፀረ አረም መድሀኒቶች የሚሆኑ ጥሬ እቃዎችን በአገር ውስጥ ለመተካት የሚሰራ መሆኑንም አስታውቋል። በ በጀት አመትም የአንዳንድ የፀረ ተባይ ማምረቻ የሚሆኑ ጥሬ እቃዎችን በአገር ውስጥ የሚያዘጋጅ መሆኑን ጠቅሷል።በሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን የእቅድ ዘመን አክሲዮን ማህበሩ አከናውናቸዋለሁ ካላቸው ዋና ዋና ተግባራት መካከል ከአራት የተለያዩ ኩባንያዎች ጋር በጥምረት ለመስራት የሚያስችለው እቅድ አለው ተብሏል።ኩባንያው በ በጀት አመት ከታክስ በፊት ሚሊዮን ብር ያተረፈ ሲሆን ይህን ትርፍ በ በጀት አመት በ በመቶ በማሳደግ ሚሊዮን ብር ለማትረፍ የሚያስችለውን ስራ በመስራት ላይ ነው ተብሏል። ወደዚህ ደረጃ ለመድረስም በጆይንት ቬንቸር ከሌሎች ኩባንያዎች ጋር ለመስራት እቅድ አለው።አክሲዮን ማህበሩ በ በጀት አመት ሚሊዮን ሊትር ፈሳሽ ሚሊዮን ኪሎ ግራም ጠጣር ፀረ ተባይ ምርቶችን በማምረት ከ ሚሊዮን ብር ሽያጭ አከናውኗል። በ በጀት አመት ግን የሽያጭ መጠኑን ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ማድረስ የሚያስችለውን ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ተጠቅሷል። የአክሲዮን ማህበሩ ባለፉት አምስት አመታት ስላከናወናቸው ተግባራት የሚያመለክተው መረጃም ስድስት ሚሊዮን ሊትር ፈሳሽ ሚሊዮን ኪሎ ግራም ፀረ ተባይ መድሀኒቶችንና የአልጋ አጎበር በማምረት ማሰራጨቱ ነው። አዳሚ ቱሉ የፀረ ተባይ ማዘጋጃ አክሲዮን ማህበር በ አመተ ምህረት ወደ ስራ የገባ ሲሆን በ አመተ ምህረት በ ሚሊዮን ብር ካፒታል በአክሲዮን ኩባንያ ደረጃ እንዲዋቀር ተደርጓል። በወቅቱ ያመርታቸው የነበሩ ፀረ ተባይ መድሀኒቶች አስር ብቻ ነበሩ አሁን ግን ደርሷል። በአሁኑ ወቅት ሰራተኞች ያሉት ሲሆን ቱ ቋሚ ናቸው።በፕራይቬታይዜሽንና የመንግስት የልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ ስር ከሚተዳደሩና በአትራፊነታቸው ከሚጠቀሱ ተቋማት መካከል አንዱ ነው። እንደሌሎች የመንግስት የልማት ድርጅቶች ወደ ግል ለማዛወር ሁለት ጊዜ ጨረታ ወጥቶ በግዥ እጦት ሳይዛወር ቀርቷል። ሆኖም የማስፋፊያ ስራ ያስፈልጋቸዋል ከተባሉ ተቋማት ውስጥ አንዱ በመሆን የማስፋፊያ ስራውን እያከናወነም ነው።
አዳሚ ቱሉ አዲሱን ፀረ አረም ማምረቻውን ስራ አስጀመረ
በስደት ምክንያት ከኢትዮጵያ ወጥተው በሳኡዲ አረቢያ፣ በግብፅና በሊባኖስ ይኖሩ የነበሩ ኢትዮጵያውያን፣ ከፍተኛ የአካል ጉዳት እየደረሰባቸው በግድ እንዲወጡ እየተደረገ መሆኑ ታወቀ።ከሳኡዲ አረቢያ ተመላሾች የአቀባበልና አሸኛኘት ኮሚቴ አባልና የብሄራዊ የአደጋ መከላከልና ስጋት አመራር ኮሚሽን ተወካይ አቶ አስመላሽ ገብረ ህይወት ሀሙስ ሀምሌ ሀያ ቀን ሁለት ሺህ ዘጠኝ አመተ ምህረት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ላይ እንደተናገሩት፣ ከሰኔ ሀያ ስድስት እስከ ሀምሌ ሀያ ቀን ሁለት ሺህ ዘጠኝ አመተ ምህረት ብቻ ከፍተኛ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ሶስት ስድስት መቶ ሀምሳ ሶስት ኢትዮጵያዊያን ከሳኡዲ አረቢያ፣ ግብፅና፣ ሊባኖስ በግድ እንዲወጡ ተደርጓል። ከእነዚህ መካከልም አንዳንዶች እጃቸውና እግራቸው ተሰብሮ የመጡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።በአንድ ወር ውስጥ ብቻ ይህን ያህል መጠን ያላቸው ኢትዮጵያዊያን በግድ ከአረብ አገሮች እንዲወጡና ከፍተኛ እንግልት እንዲደርስባቸው መደረጉን የገለፁት አቶ አስመላሽ፣ አብዛኛዎቹ ኢትዮጵያዊያን ከሳኡዲ አረቢያ የሚመጡ መሆናቸውንም አስረድተዋል። በአሁኑ ጊዜም ሳኡዲ አረቢያ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው ዜጎች እንዲወጡ ከማወጇ በፊት፣ ታስረውና ህገወጥ ተብለው ተይዘው የነበሩ ኢትዮጵያዊያን በግድ እንዲወጡ እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።እነዚህ ታስረው የሚመጡ ዜጎች ጫማ እንኳን የሌላቸውና ከፍተኛ የሆነ የሞራልና የአካል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑንም ለማወቅ ተችሏል።ከእነዚህ የአረብ አገሮች በግድ የሚመጡ ዜጎችን መንግስት እየተቀበለና ወደየመጡበት አካባቢ እየመለሰ እንደሚገኝም ተወካዩ አስረድተዋል። እነዚህ በግድ እንዲወጡ የሚደረጉ ዜጎች ቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖርት ሲደርሱ ብሄራዊ የአደጋ መከላከልና ስጋት አመራር ኮሚሽን ተቀብሎ ብርድ ልብስ፣ ብስኩትና ውሀ እንደሚሰጣቸው ተናግረዋል።ሳኡዲ አረቢያ ሰነድ አልባ ኢትዮጵያዊያን ወደ አገራቸው እንዲመለሱ የሰጠችው ተጨማሪ አንድ ወር ከተጠናቀቀ በኋላ ይህ ችግር እየባሰ እንደሄደ አክለዋል። ከአዋጁ መጠናቀቅ በኋላም የሳኡዲ አረቢያ መንግስት ቤት ለቤት በማሰስና በመያዝ ወደ ኢትዮጵያ በግድ እንደሚመልሳቸው ተመላሾች ገልፀዋል። ንብረት ይዘው እንደማይወጡና በተደጋጋሚ አሻራ ተነስተው ወደ ኢትዮጵያ እንደሚላኩ አስረድተዋል።
በርካታ ኢትዮጵያዊያን ከሳኡዲ አረቢያና ከግብፅ በግዳጅ እንዲወጡ እየተደረገ ነው
አዲስ አበባ፣ ሀምሌ ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በደቡብ ክልል ባለፈው በጀት አመት ከማእድን ልማት ዘርፍ ከአንድ መቶ ሀያ አምስት ነጥብ ሁለት ሚሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱ ተገለፀ። በክልሉ በማእድን ልማት የተሰማሩ ባለሀብቶች ከ ሺህ በላይ ለሆኑ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠራቸውም ተመላክቷል። የክልሉ የማእድን ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ አፀደ አይዛ በክልሉ ለኢንዱስትሪ ግብአት አንድ መቶ ሀያ አምስት ሺህ አራት መቶ አርባ ቶን ማእድናትን ማምረት መቻሉን ተናግረዋል። ከተመረተው ማእድን አንድ መቶ ዘጠኝ ቶን የድንጋይ ከሰል ለሲሚንቶ ፋብሪካዎች ማቅረብ ስለመቻሉም ዋና ዳይሬክተሯ አብራርተዋል። በበጀት አመቱ ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ ተተኪ ምርቶችን ለሀገር ውስጥ የኢንዱስትሪ ግብአት በማቅረብ የውጭ ምንዛሬን ማሳደግ የተቋሙ ዋና አላማ መሆኑንም ዋና ዳይሬክተሯ ተናግረዋል። በክልሉ ከአርባ ምንጭ፣ ከወላይታ፣ ከዲላ እና ከዋቻሞ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመቀናጀት የማእድን ጥናት እየተካሄደ መሆኑም ተጠቁሟል። የድንጋይ ከሰል፣ ዶሎማይት፣ ካኦሊን የብረት ማእድናት እና ሌሎች ተዛማጅ የማእድን አይነቶችን በጥናት መለየት መቻሉም ተብራርቷል። ማእድናቱ ለሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች እና ለወጭ ንግድ የሚሆኑ የጌጣጌጥ ማእድናትን እንደሆኑ በጥናት መረጋገጡን ወይዘሮ አፀደ አይዛ መናገራቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።
በደቡብ ክልል ከማእድን ልማት ዘርፍ ከአንድ መቶ ሀያ አምስት ነጥብ ሁለት ሚሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱ ተገለፀ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት ሶስት ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ስኬት የወጣቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ማሳደግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አለው ሲሉ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሀር ገለፁ። የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የወጣቶች የሰላም ጉባኤ ማጠናቀቂያ መርሀ ግብር በዛሬው እለት ተካሂዷል። በመድረኩ የተገኙት ከንቲባ ከድር ጁሀር በሰላም እሴት ግንባታ ጉልህ ሚና የሚጫወቱ ሚዛናዊ ወጣቶችን ማፍራትና ማብቃት ይኖርብናል ብለዋል። ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ስኬት የወጣቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ማሳደግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳለውም አስረድተዋል። በድሬዳዋ ውስጥ በባህልና ኪነ ጥበብ፣ በፊልም፣ በሙዚቃ፣ በስፖርት እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ለሚንቀሳቀሱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል። በቀጣይ ወጣቶችን ከመደገፍ ተግባር ጎን ለጎን ተተኪዎችን ለማፍራት ጠንክረን እየሰራን ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ እድገት የወጣቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ማሳደግ ከፍተኛ ሚና አለው ከንቲባ ከድር ጁሀር
የህዋ ተመራማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ የብላክ ሆል ምስልን በጣም ሩቅ ካለ የክዋክብት ስብስብ ውስጥ ማንሳት ችለዋል። አርባ ቢሊየን ኪሎሜትር ይረዝማል የተባለው ብላክ ሆል ምድርን በሶስት ሚሊየን እጥፍ ይበልጣታል ተብሏል። የዘርፉ ባለሙያዎች ትልቅ አውሬ የሚል ስያሜ ሰጥተውታል። ይህንን አስገራሚ የብላክ ሆል ምስል ለማንሳት አገልግሎት ላይ የዋሉትን ስምንት ቴሌስኮፖች በማጣመር አንድ ወጥ ምስል እንዲገኝ ያደረገችው ደግሞ የሀያ ዘጠኝ አመቷ ሳይንቲስቷ ኬቲ ቦውማን ነች። ጨረቃን የሚረግጠው የመጀመሪያው ጎብኚ ታወቀ በሳተላይቶች ዙሪያ ሰባት አስደናቂ እውነታዎች በዚህ ስራዋም በመላው አለም የሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎችና ሌሎች ሰዎች አድናቆታቸውን እያጎረፉላት ይገኛሉ። ብላክ ሆል ከምድር አምስት መቶ ሚሊየን ትሪሊየን ኪሎሜትሮች ርቀት ላይ ሲሆን በመላው አለም የሚገኙ ኢቨንት ሆራይዝን የተባሉ ስምንት ቴሌስኮፖችን በመጠቀም ነው ምስሉን ማንሳት የተቻለው። ጥቁሩ ቀዳዳ ፕሮግራሙን ደግሞ በዋነኛነት ስትመራው የነበረችው ኬቲ ነበረች። ሙሉውን ምስል ባገኘችበት ወቅትም እስካሁን ድረስ የመጀመሪያውን የብላክ ሆል ምስል ማግኘቴን አላመንኩም ስትል በፌስቡክ ገጿ ላይ አስፍራለች። ኬቲ በመላው አለም ተበታትነው የሚገኙትን ቴሌስኮፖች እንደ አንድ አድርጎ ለመጠቀም የሚያስችል ዘዴ ለማበጀት የማሳቹሴትስ ቴክኖሎኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የመጨረሻ አመት ተማሪ ከነበረችበት ጊዜ አንስቶ ሶስት አመታት ፈጅቶባታል። ይህንን የሙከራ ሀሳብ ያቀረቡትና ከኔዘርላንድስ ሬድባውንድ ዩኒቨርሲቲ የመጡት ፕሮፌሰር ሄይኖ ፋልኬ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ብላክ ሆል የተገኘው ሰማኒያ ሰባት በተባለ የክዋክብት ስብስብ ውስጥ ነው። ክብደቱ ከፀሀይ ስድስት ነጥብ አምስት ቢሊየን እጥፍ ሲሆን እስከዛሬ ድረስ አሉ ብለን ከምንገምታቸው ሁሉ እጅግ የላቀ ሆነ አግኝተነዋል። የብላክ ሆሎች ሁሉ ታላቅ እንደሆነ አስባለሁ። ብለዋል። የብላክ ሆልን ምስል ለማንሳት በተደረገው ጥረት ከአንታርክቲካ እስከ ቺሊ ድረስ ከሁለት መቶ በላይ ተመራማሪዎች ተሳትፈዋል። ማንም ሰው ብቻዬን አደርገዋለው ብሎ የሚያስበው ነገር አይደለም። ጥረታችን ወደ እውነታ የተቀየረው ሁሉም ተሳታፊ ባደረገው ትልቅ አስተዋፅኦ ነው። ለዚህም በስራው ላይ የተሳተፉትን በሙሉ ማመስገን እፈልጋለሁ። ብላለች ኬቲ። በታሪክ የመጀመሪያው የብላክ ሆል ምስል ስለ ብላክ ሆል እስካሁን የታወቀው የሀምዛ ሀሚድ ገመድ አልባ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ በህይወት ከሌለች እናት የተወለደችው ህፃን በምድራችን ላይ የሚገኝ የትኛውም ቴሌስኮፕ ብቻውን የብላክ ሆልን ምስል መውሰድ አይችልም። ለዚህም ነው በመላው አለም የሚገኙ ስምንት ቴሌስኮፖችን በማጣመር አስር ቀናት የፈጀ ፎቶ ማንሳት ግድ ያለው። ቴሌስኮፖቹ ያነሷቸውን ምስሎች ደግሞ በመቶዎች በሚቆጠሩ የመረጃ ማጠራቀሚያዎች ውስጥ በመሰብሰብ በየእለቱ ወደ አሜሪካና ጀርመን በአውሮፕላን ይላኩ ነበር። የዶክተር ኬቲ ቦውማን ስራም እዚህ ላይ ነበር እጅግ ጠቃሚ የነበረው። እሷ የፈጠረችው መረጃዎችን የማቀናጀት መንገድ ውጤታማ ሆኖ አለምን ያስደመመ ምስል ማግኘት ተችሏል።
ከመጀመሪያው የብላክ ሆል ምስል ጀርባ ያለችው ሴት
ስልሳ ሰባት በዛብህ መለዮ ሰማኒያ አንድ አብዱልከሪም መሀመድተጠናቀቀ ጨዋታው አንድ አንድ በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቋል።ተጨማሪ ደቂቃ ሶስትየተጫዋች ለውጥ ድቻአማኑኤል ተሾመ ወጥቶ ዮሴፍ ድነንገቱ ገብቷል።ጎልልል ቡናሰማኒያ አንድ ኤልያስ ማሞ ያሻማውን ኳስ አብዱልከሪም መሀመድ በግንባሩ በመግጨት ቡናን አቻ አድርጓል።የተጫዋች ለውጥ ድቻበዛብህ መለዮ ወጥቶ ዳግም በቀለ ገብቷል።ጎልልል ድቻ ስልሳ ሰባት በዛብህ መለዮ በግሩም ቅብብል ግብ አስቆጥሮ ድቻን ቀዳሚ አድርጓል። ሀምሳ አምስት ከመጀመርያው አጋማሽ በተሻለ ሁኔታ ደጋፊዎች ቡድናቸውን እያበረታቱ ጨዋታው ተሟሙቆ ቀጥሏል።የተጫዋች ለውጥ ድቻአናጋው ባደግ ወጥቶ ያሬድ ዳዊት ገብቷል።የተጫዋች ለውጥ ቡናሳሙኤል ሳኑሚ ወጥቶ ሳዲቅ ሴቾ ገብቷል።ተጀመረ ሁለተኛው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ተጀመረ።እረፍት የመጀመርያው አጋማሽ ያለ ግብ ተጠናቋል።ተጨማሪ ደቂቃ ሁለት መቶ ስላሳ ስምንት ኤልያስ ማሞ በቮሊ የመታው ኳስ ለጥቂት በግቡ አናት በላይ ወጥቷል።ስላሳ ሶስት ጨዋታው ውጥረት የተሞላበት ሲሆን በሁለቱም በኩል የተደራጀ እንቅስቃሴ እየተመለከትን አይደለም። ሁለቱም ቡድኖች በራሳቸው የሜዳ ክልል ኳስ ከመቀባበል ባለፈ ወደ ተጋጣሚ የሜዳ ክልል መዝለቅ አልቻሉም።ስድስት ኢትዮጵያ ቡናዎች የተሻረው ግብ አግባብ አይደለም በሚል ጨዋታውን አቋርጠው ክስ በማስመዝገብ ላይ ይገኛሉ።ሶስት ከመስመር የተሻገረውን ኳስ ኢትዮጵያ ቡናዎች ቢያስቆጥሩም ከጨዋታ ውጪ ተብሎ ተሽሯል።ተጀመረ ጨዋታው በኢትዮጵያ ቡና አማካኝነት ተጀምሯል።የወላይታ ድቻ አሰላለፍአንድ ወንድወሰን ገረመውስድስት ተክሉ ታፈሰ ሀያ ሰባት ሙባረክ ሽኩር ሶስት ቶማስ ስምረቱ አምስት ዳግም ንጉሴ ስምንት አማኑኤል ተሾመ በዛብህ መለዮ ሀያ አንድ መሳድ አጪሶ ሰባት አናጋው ባደግ አላዘር ፋሲካ ሀያ ሶስት ፀጋዬ ብርሀኑተጠባባቂዎች ወንድወሰን አሸናፊ ሀያ አብዱልሰመድ አሊ አራት ዮሴፍ ድንገቱ ቴዎድሮስ ዳግም በቀለ ሲሳይ ማሞ ዘጠኝ ያሬድ ዳዊትየኢትዮጵያ ቡና አሰላለፍዘጠና ዘጠኝ ሀሪስን ሄሱ አብዱልከሪም መሀመድ ኤፍሬም ወንድወሰን አራት ኤኮ ፌቨር አህመድ ረሽድዘጠኝ ኤልያስ ማሞ ሀያ አምስት ጋቶች ፓኖም ስምንት አማኑኤል ዮሀንስ እያሱ ታምሩ ሀያ ስምንት ያቡን ዊልያም ሳሙኤል ሳኑሚተጠባባቂዎችሀምሳ ጆቤድ ኡመድ ሳለአምላክ ተገኝ ሰባት ሳዲቅ ሴቾ አምስት ወንድይፍራው ጌታሁን ሀያ ሰባት ዮሴፍ ዳሙዬ አብዱልከሪም ሀሰን ሀያ አንድ አስናቀ ሞገስ
ወላይታ ድቻ ከ ኢትዮጵያ ቡና ቀጥታ የፅሁፍ ስርጭት
የወሰን ማካለሉ ስራ በሁለት ወራት ውስጥ የተከናወነ ሲሆን በሁለቱ ክልሎች መካከል ቀሪ ስልሳ ሶስት ቀበሌዎችን የማካለሉ ስራም እየተሰራ ነው ተብሏል።የሁለቱ ክልሎች ርእሳነ መስተዳደሮች ሚያዚያ ሀያ ስምንት ሁለት ሺህ ዘጠኝ የድንበር ማካለሉን ስራ በሶስት ወራት ውስጥ ለማከናወን ስምምነት ፈፅመው እንደነበር ይታወሳል።በስምምነቱ መሰረት ከዚህ ቀደም ሳይከለሉ የቀሩትን ጨምሮ በምእራብ እና ምስራቅ ሀረርጌ፣ ባሌ፣ ጉጂ እና ቦረና ዞኖች በሀያ አራት ወረዳዎች የሚገኙ አንድ መቶ አርባ ስምንት ቀበሌዎች መካለል አለባቸው።የኦሮሚያ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አዲሱ አረጋ፥ እስካሁን ሰማኒያ አምስት ቀበሌዎች መካለላቸውን ገልፀዋል።የፌዴራል እና አርብቶ አደር ልማት ጉዳዮች ሚኒስቴር በበኩሉ እስካሁን የተሰራውን የማካለል ስራ በቁጥር ለመገለፅ መረጃዎችን አጠናቅሮ አለማጠናቀቁን አሳውቋል።ከአቶ አዲሱ በተገኘው መረጃ መሰረት ግን ባለፉት ሰማኒያ ስድስት ቀናት ውስጥ በተከናወነው የአስተዳደር ወሰን ማካለሉ ስራ ያልደረሰባቸው ቀሪ ስልሳ ሶስት ቀበሌዎች አሉ።በሚኒስቴሩ የግጭት ቅድመ ማሰጠንቀቂያ እና ዘላቂ መፍትሄ ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ መለሰ፥ ቀሪዎቹን ቀበሌዎች ለማካለል ተጨማሪ ጊዜ ያሰፈልጋል ብለዋል።በእስካሁኑ የድንበር ማካለለ ስራ የዘላቂ ሰላም ዋስትና የሆነው የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ማጠናከር ተግባር መከናወኑን ያነሱት ዳይሬክተር ጀነራሉ፥ ይህም በአካባቢው አስተማማኝ ሰላም ለማስፈን የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።በአሁኑ ወቅት በሁለቱ ክልሎች አጎራባች አካባቢዎች ሰላም እና መረጋጋት መሰፈኑንም አቶ ሲሳይ አመላክተዋል።በድንበሩ ምክንያት ድፍርሶ የነበረው የሁለቱ ወንድማማች ህዝቦች ማህበራዊ ግንኙነት ወደ ቀድሞው እየተመለሰ፣ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትም እየተጠናከረ ነው ያሉት አቶ አዲሱ፥ ወሰን ከማካለል ጎን ለጎን በመሰረተ ልማት የማስተሳሰሩበ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።በኦሮሚያ እና በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልሎች ያሉ አራት መቶ ሀያ ሁለት አዋሳኝ ቀበሌዎችን ለማካለል የሚያስችል ውሳኔ ከተላለፈ አመታት ቢቆጠሩም የአስተዳደር ወሰን ማካለል ስራ እስከ ዛሬ አልተጠናቀቀም።እስከ ሁለት ሺህ ስድስት አጋማሽ ድረስ በህዝበ ውሳኔው መሰረት ሁለት መቶ ሰባ አራትቱን ማካለለ ተችሏል፤ ቀሪዎቹን ቀበሌዎች የማካለሉ ስራ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ አልተጠናቀቀም ነበር።ይህንን ተከትሎ ባልተካለሉት አካባቢዎች ግጭት ተከሰቶ የሰው ህይወት አልፏል ኤፍ ቢ ሲ ።
በኦሮሚያና ኢትዮጵያ ሶማሌ ክልሎች ሰማኒያ አምስት አጎራባች ቀበሌዎችን ወሰን የማካለል ስራ ተሰራ
አዲስ አበባ፣ መስከረም ሰባት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በደቡብ ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ከ ሶስት ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ መሰማራታቸው ተገለፀ።እየተካሄደ ያለውን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግም በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር አስታውቋል።የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ፍቅሬ አማን እንደገለፁት በዞኑ ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት በተደረገ ጥረት ከ ሶስት ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች በግብርና፣ በኢንዱስትሪ እና በአገልግሎት ዘርፎች ተሰማርተው እየተንቀሳቀሱ ነው።እንደ ዋና አስተዳዳሪው ገለፃ በርካታ የኢንቨስትመንት አማራጮች ያሉት የቤንች ሸኮ ዞን በግብርናው ዘርፍ፣ በቡና እና በቅመማቅመም ፣በማር ምርት፣ በቅባት እህሎች፣ በሩዝ እርሻ ልማት ፣በሆርቲካልቸር እና መሰል ገበያ ተኮር በሆኑ ዘርፎች ላይ የባለሀብቱን ተሳትፎ ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።በቀጣይም የባለሀብቱን ተሳትፎ ለማሳደግ እና ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት በትኩረት ይሰራል ሲሉ መናገራቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
በደቡብ ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ከ ሶስት ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ መሰማራታቸው ተገለፀ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት ሰባት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የኢትዮጵያ የሀይማኖት ተቋማት የጋራ መርህ ላይ ተመስርተው ጠንካራ ተቋም እንዲፈጥሩ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አቢይ አህመድ አሳሰቡ።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን፣ ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት፣ ከኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን እና ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል የእምነት መሪዎች ጋር ዛሬ ተወያይተዋል።በዚህ የውይይት መድረክ ላይ የጋራ እሴቶችን በመጠቀም ፈጣሪን የሚፈራ፣ ለሀገርና ለህዝብ የሚጠቅም ትውልድ መፍጠር ይገባል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።ይህንንም የሚያስችል ዘመን የሚሻገር ተቋም የሀይማኖት ተቋማቱ እንዲፈጥሩም ነው ያሳሰቡት።ኢትዮጵያ በሁሉም እምነት ውስጥ በአለማዊም ሆነ በመንፈሳዊ እውቀት የዳበሩ፣ በታሪክ እና በእድሜ የበሰሉ መሪዎች ቢኖሯትም ጠንካራ ተቋም ባለመኖሩ በአግባቡ እንዳልተጠቀመች አንስተዋል።የሚፈጠረው ተቋምም ዋነኛ አላማው ሀገራዊ ሀብትን በትክክል አውቆና አቅምን አሰባስቦ ሀገር እንድትጠቀም ማስቻል ነው ብለዋል።በተጨማሪም ተቋሙ ድምፅ ለሌላቸው ሰዎች ድምፅ የሚሆን፣ በሰላም ግንባታ ላይ የሚሳተፍ ፣ በአደጋ ጊዜ ተባብሮ የሚሰራ እና የህዝቡን ማህበራዊ ደህንነት ለማረጋገጥ የሚተጋ እና የማገልገል ልምድን ለወጣቱ የሚያስተላልፍ ይሆናልም ብለዋል።የሀይማኖት መሪዎቹ ጠንካራ ተቋም መመስረቱ ላይ በመስማማት በቀጣይ ውይይት እንደሚያስፈልገው ጠቁመዋል። በአልአዛር ታደለ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አቢይ የኢትዮጵያ የሀይማኖት ተቋማት የጋራ መርህ ላይ ተመስርተው ጠንካራ ተቋም እንዲፈጥሩ አሳሰቡ
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን የዋጋቸውን እጥፍ የሚሆን የተጠየቀባቸውን ሀያ ተሽከርካሪዎች ታክስና ቀረጥ ከፍሎ ለመረከብ፣ የባለስልጣኑ የተለያዩ ከፍተኛ ሀላፊዎች እየተወዛገቡ መሆኑን ታወቀ። አውቶሞቢሎቹን ቶዮታ ያሪስ ለማቅረብ በወጣው ጨረታ ከተሳተፉት ተሽከርካሪ አቅራቢ ድርጅቶች መካከል፣ በላይ አብ ሞተርስና ሞኤንኮ የሞተርና ኢንጂነሪንግ አክሲዮን ማሀበር በባስልጣኑ የቀረበውን መስፈርት በማሟላት የመጨረሻዎቹ ተወዳዳሪዎች እንደነበሩ ሰነዶቹ ያሳያሉ። በላይ አብ ሞተርስ ሀያ ቶዮታ ያሪስ አውቶሞቢሎች ታክስና ቀረጥን ጨምሮ በ አምስት መቶ ሰማኒያ ሶስት ስድስት መቶ ስላሳ አራት ብር ሲያቀርብ፣ ሞኤንኮ ደግሞ ባለስልጣኑ ለኤልሲ የከፈለውን ሳይጨምር በ አምስት መቶ ስላሳ ብርና የኤልሲውን ጨምሮ ሀያ ስድስት አንድ መቶ ስድስት መቶ አርባ ዘጠኝ ብር ማቅረቡን ሰነዶቹ ያስረዳሉ።ጨረታውን ሞኤንኮ እንዲያሸንፍ በመደረጉ ባለስልጣኑ በወቅቱ በነበረው የውጭ ምንዛሪ መጠን፣ የአውቶሞቢሎችን ጠቅላላ ዋጋ ታክስና ቀረጥን ሳይጨምር ዘጠኝ አምስት መቶ ሰማኒያ ሁለት ስምንት መቶ ሀምሳ አምስት ብር ክፍያ መፈፀሙ ታውቋል። አስመጪው ኩባንያ ሀያዎቹን አውቶሞቢሎች አስጭኖና አጓጉዞ ገላን ደረቅ ወደብ ድረስ ማምጣቱም ተረጋግጧል። ተሽከርካሪዎቹን በስምምነታቸው መሰረት ታክስና ቀረጥ አምስት መቶ ስላሳ ሰባት መቶ ዘጠና አራት ብር ከፍሎ ባለስልጣኑ መረከብ ቢኖርበትም፣ ልዩነቱን ሊከፈል አልቻለም። በወደቡ ከተፈቀደው ሀያ አምስት ቀናት በላይ ማቆየት ተጨማሪ የደሜሬጅ ክፍያ ስለሚያስከትል፣ ሞኤንኮ ተሽከርካሪዎቹን ከወደቡ በማውጣት በራሱ መጋዘን ቦንድድ ዌር ሀውስ ውስጥ አስቀምጧቸው እንደሚገኝም ተረጋግጧል።ሞኤንኮ የሞተርና ኢንጂነሪንግ ኩባያ አክሲዮን ማሀበር ለአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በፃፈው ደብዳቤ እንዳስታወቀው፣ በገቡትና ባሰሩት ውል መሰረት ተሽከርካሪዎቹን አምጥቷል። በተስማሙበትና ባሰሩት ውል መሰረት የታክስና ቀረጥ ክፍያ የሚፈፀመው በባለስልጣኑ ነው። በመሆኑም ታክስና ቀረጥ ክፍያውን በመፈፀም አውቶሞቢሎች እንዲረከብ አሳስቧል። ያ ሳይሆን ቀርቶ በተሽከርካሪዎቹ ላይ ጉዳት ወይም ተጨማሪ ችግር ቢፈጠር ሀላፊነቱን እንደማይወስድ፣ የማሀበሩ የመኪኖችና የጨረታ ሽያጭ ስራ አስኪያጁ አቶ ሙሉጌታ ሰይፉ ለዋና ስራ አስኪያጁ ሞገስ ጥበቡ ኢንጂነር ግልባጭ ያደረጉት ደብዳቤ ያስረዳል።የሞኤንኮን ጥያቄና ማሳሰቢያ የተመለከቱት የከተማው መንገዶች ባለስልጣን የለውጥና ዘርፍ ድጋፍ ሰጪ ዳይሬክቶሬት፣ የእቃ ግዥ አቅርቦትና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት፣ ከህግ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ጋር እየተወዛገቡ መሆናቸውን ሰነዶች ያስረዳሉ።የተቋሙ የለውጥና ድጋፍ ሰጪ ዘርፍ ከህግ ክፍሉ በጠየቀው አስተያየት እንደገለፀው፣ የጉምሩክ ኮሚሽን ክፍሉን በተመለከተ የአውቶሞቢሎቹ ግዥ ኤልሲ በባለስልጣኑ ተከፍቷል። ንብረቶቹንም በአስቸኳይ እንዲወስድ ሞኤንኮ ጠይቋል። ከሶስት ቀናት በኋላ ወደቡ ዴመሬጅ ስለሚያስከፍል እልባት እንዲሰጠው የህግ አስተያየት ጠይቋል።የህግ ማማከርና የኮንትራት ጉዳይ ቡድን በሰጠው አስተያየት እንዳስረዳው፣ በተሽከርካሪዎቹ የቀረጥና ታክስ ክፍያ ላይ ውዝግብ የተነሳው ከጨረታው ሰነድ ዝግጅት ጀምሮ ነው።ዝግጅቱም ተቋሙን የሚጎዳ በመሆኑና የጨረታው ምዘና በአግባብ ባለመከናወኑ ተሸናፊ ተጫራች የአሸናፊነት አክሊል ተሰጥቶታል በማለት ጉዳዩ የተጠየቀውን ቀረጥና ታክስ ከመክፈል በላይ የመንግስትን ጥቅም በከፍተኛ ሁኔታ የሚጎዳ በመሆኑ፣ የሂደቱ ተሳታፊዎች ተጠያቂ መሆን እንዳለባቸው ገልፆ አስተያየቱን ለህግ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት አሳውቋል። የህግ ዳይሬክቶሬቱም የህግ ማማከርና ኮንትራት ጉዳይ ቡድንን አስተያየት በመደገፍና በማጠናከር፣ ለእቃ ግዥ ንብረት አቅርቦትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በፃፈው አስተያየት፣ የተፈፀመውን የህግ ጥሰት በመመርመር መንግስትን ከጉዳት እንዲታደጉና የህግ የበላይነት እንዲሰፍን ጠይቋል።በግልባጭም ለከተማው አስተዳደር ከንቲባ ፅህፈት ቤት፣ ለፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ፣ ለፌዴራል ፖሊስና ለአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ እንዲሁም ለሚመለከታቸው አካላት አሳውቆ ምላሽ እየተጠባበቀ መሆኑን ሪፖርተር ካገኛቸው ሰነዶች አረጋግጧል።
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን ሀላፊዎች በተሽከርካሪዎች ግዥ እየተወዛገቡ ነው
አቶ መላኩ ፋንታ እና አቶ ገዋህድ ወጊዮርጊስ በ መዝገቦች ተከሰዋልሶስት ተጠርጣሪዎች በነፃ ተለቀዋልየፌደራሉ የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን አቃቤ ህግ ከ በላይ በሚሆኑ የገቢዎችና ጉምሩክ መስሪያ ቤት ባለስልጣናት እና የቅርንጫፉ ፅህፈት ቤት ሰራተኞች እንዲሁም ከባለስልጣናቱና ሰራተኞች ጋር ተመሳጥረው ከባድ የሙስና ወንጀል ፈፅመዋል በተባሉት ባለሀብቶች ላይ የክስ መዝገቦች አደራጅቶ ከፈተ። በምርመራ ቀጠሮ ላይ የቆዩ ተጠርጣሪዎች በነፃ ሲለቀቁ ቀደም ሲል በዋለው ችሎት ምርመራቸው አልተጠናቀቀም ተብለው እንደገና ወደ ምርመራ ቀጠሮ የተመለሱት ተጠርጣሪዎች ባሉበት ሆነው እስከ ጳጉሜ ቀን የምርመራ ስራው እንዲቀጥል ተብሏል። የኮሚሽኑ አቃቤ ህግ በተከሳሾቹ ላይ የከፈታቸው መዝገቦች በሚኒስትር ማእረግ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ መላኩ ፋንታ እና አቶ ገዋህድ ወጊዮርጊስ በሶስት መዝገቦች ክስ ቀርቦባቸዋል። የተከሳሽ ጠበቆች በየደንበኞቻቸው ላይ የቀረበው የክስ ጭብጥ እንዲሰጣቸው የጠየቁ ቢሆንም ፍቤቱ እስከቀጠሮ ባለው ጊዜ ውስጥ እንዲደርሳችሁ ይደረጋል የሚል ምላሽ ሰጥቷል። ተከሳሾችም በቀጣይ ቀጠሮ ሲቀርቡ የክሱ ጭብጥ እንደሚነበብላቸው ተገልጿል። የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን የባለስልጣኑ ሰራተኞች በነበሩት በአቶ ንጉሴ ክብረት አቶ ጌታቸው አሰፋ እና አቶ ምሳሌ ወስላሴ ላይ ሲያካሂድ የነበረውን ምርመራ በማጠናቀቁና ክስ እንደማይመሰረትባቸው በማረጋገጡ በነፃ እንዲለቀቁለት ጠይቆ ፍቤቱ እንዲለቀቁ ትእዛዝ ሰጥቷል። በሌላ በኩል በእነ አቶ ገዋህድ መዝገብ ተካተው ምርመራ ሲካሄድባቸው የነበሩት አቶ ሙሌ ጋሻው በመሀንዲስነት ሲሰሩ በነበሩበት የኦሮሚያ ክልል ፍቤት ጉዳያቸው እንዲታይ አቃቤ ህግ አመልክቷል። ተጠርጣሪውም ፈቃደኛነታቸውን በመግለፃቸው ፍቤቱ የአቃቤ ህግን ጥያቄ ተቀብሎ ጉዳያቸው በክልሉ ፍቤት እንዲታይ ትእዛዝ ሰጥቷል። በሌላ በኩል የኦዲት ምርመራው ባለመጠናቀቁ አቃቤ ህግ በአቶ ተክለአብ ዘረአብሩክ አቶ ምህረተአብ አብርሀ አቶ በእግዚአብሄር አለበል እና አቶ ፍፁም ገማርያም ላይ የ ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ የጠየቀ ቢሆንም ፍቤቱ ከተጠየቀው ጊዜ ቀጠሮ ቀን ብቻ በመፍቀድ ተጠርጣሪዎች ባሉበት ማረፊያ ቤት ቆይተው ለጳጉሜ ቀን እንዲቀርቡ ቀጠሮ ሰጥቷል። የክስ መዝገብ የተከፈተባቸውን ተጠርጣሪዎች በኛ ወንጀል ችሎት በኩል ክሳቸው እንዲታይ ለጥቅምት እና ቀን ቀጠሮ ሰጥቷል።
በገቢዎችና ጉምሩክ ተጠርጣሪዎች ላይ የክስ መዝገቦች ተከፈቱ
ለክቡር አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ጉዳዩ፡ በኢፌዲሪ ህገ መንግስት አንቀፅ ስላሳ ሰባት አንድ መሰረት ፍትህ ለማግኘት ለሁለተኛ ጊዜ የቀረበ አቤቱታ፤ አንድ በኢፌዲሪ ህገ መንግስት አንቀፅ ሀምሳ አንድ አንድ ህገ መንግስቱን መጠበቅና መከላከል የፌዴራል መንግስት ስልጣንና ተግባር በመሆኑ፤ ሁለት በኢፌዲሪ ህገ መንግስት አንቀፅ ሰባ አራት ህገ መንግስቱን ማክበርና ማስከበር የጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልጣንና ተግባር በመሆኑ፤ አቤቱታዬን እነሆ ለሁለተኛ ጊዜ ለክቡርነትዎ ለማቅረብ ተገድጃለሁ፡ ጅቡቲ በስደተኞች ሰፈር በምኖርበት ቤት ውስጥ ታህሳስ ሀያ ስድስት ቀን አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ አምስት አመተ ምህረት ከምሽቱ ሶስት ሰአት በቅጥር ነፍሰ ገዳዮች በተፈፀመብኝ የመግደል ሙከራ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶብኝ፣ በጅቡቲ ሆስፒታል ለአንድ አመት ከሶስት ወራት በህክምና ስረዳ ቆይቼ በእግዚአብሄር ቸርነት ከሞት ልተርፍ ችያለሁ። በወቅቱ በጭካኔ ከተደበደብኩባቸው ዘጠኝ ጥይቶች መካከል አንዱ ጥይት አሁንም በሰውነቴ ውስጥ ስለሚገኝ ከሳምባዬ ጋር በሚያደርግው ንክኪ በየጊዜው ለከባድ የሳል ህመም የሚዳርገኝ መሆኑን በሀኪም ተረጋግጦ ተነግሮኛል። ለዚህ የወንጀል ድርጊት ተጠያቂ የሆኑት ሰዎች ግን ዛሬም የመንግስት ስልጣናቸውን መከታ አድርገው ከእስር እንዳልፈታ የተለመደ የበቀል እርምጃ በመውሰድ ላይ ናቸው። አልፎ ተርፎም ከማረሚያ ቤት ብወጣም ህይወቴ በእነሱ እጅ እንደሆነና የሚፈልጉትን ማድረግ እንደሚችሉ ዛቻዎቻቸው እየደረሰኝ ነው። ይሁን እንጂ ደምን በደም ቢያጥቡት ተመልሶ ደም ነው። የሆነው ሆነ ይህንን ማመልከቻ ልፅፍልዎ የተነሳሁበት ዋና ምክንያት፣ በኢፌዲሪ ህገ መንግስት አንቀፅ ሀያ አምስት እና በኢፌዲሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ አራት ሁሉም ሰዎች በህግ ፊት እኩል ናቸው የሚለውን ድንጋጌ በሚቃረን መልኩ በዜግነቱ በእኩልነት የመታየትና የመዳኘት ህገ መንግስታዊ መብቴ በመጣሱ የተነሳ ከፍተኛ ጉዳት ስለደረሰብኝ፤ ፍትሀዊ ውሳኔ ይሰጡኛል በሚል እምነት ሰኔ ሰባት ቀን ሁለት ሺህ ስድስት አመተ ምህረት አቤቱታዬን በፅሁፍ ለክቡርነትዎ ማቅረቤን ያስታውሱታል ብዬ አምናለሁ። እንደሚታወቀው በኢፌዲሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ ሁለት መቶ ሁለት አንድ ማንኛውም ተቀጪ ፍርዱ የእድሜ ልክ እስራት ከሆነና ታሳሪው ሀያ አመት ከታሰረ፣ ፍርድ ቤቱ ጥፋተኛው በአመክሮ እንዲፈታ እንደሚወስን ተደንግጓል። በዚህ መሰረት እኔም በተከሰስኩበት ጉዳይ እጄ ከተያዘበት ከሀያ ሁለት ስምንት አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ ስድስት አመተ ምህረት አንስቶ የተፈረደብኝን የእድሜ ልክ እስራት ሀያ አመት በሀያ ሁለት ስምንት ሁለት ሺህ ስድስት አመተ ምህረት ጨርሻለሁ። ሆኖም ከሀያ ሶስት ስምንት ሁለት ሺህ ስድስት አመተ ምህረት ጀምሮ በማላውቀው ጉዳይ ህገ መንግስታዊ መታግቼ አሁንም በአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት ቃሊቲ ዞን አራት ውስጥ በእስር ላይ እገኛለሁ። ማረሚያ ቤቱ የአመክሮ መብትን ለማክብር ታራሚው በእስር ቤት ቆይታው ያለውን ባህሪ መገምገም እንዳለበት አውቃለሁ፤ በዚህ መሰረትም እኔ ሀያ አመት በእስር በቆየሁበት ጊዜ የነበረኝ ጠባይ ተገምግሞ ያገኘሁት ውጤት እጅግ የሚያስመሰግነውን ዘጠና አምስት ከመቶ ዘጠና አምስት ነው። ይህም በማረሚያ ቤቱ ሀላፊ በአቶ አብርሀም ወልዷረጋይ ፊርማ ተረጋግጦ፣ ለፍቺ ከሌሎች ታራሚዎች ሰነዶች ጋር በዘጠኝ ስምንት ሁለት ሺህ ስድስት አመተ ምህረት ለፍርድ ቤት ተልኮ የነበረ ቢሆንም፤ በ ስምንት ሁለት ሺህ ስድስት አመተ ምህረት ለፍርድ ቤት ከተላኩት ሰነዶች መካከል የእኔን ብቻ ነጥለው መለሰው በማስመጣ ራሳቸው አቶ አብርሀም ወልዷጋይ በእጃቸው እንደያዙት በማረሚያ ቤቱና በፍርድ ቤቱ ሰራተኞች ተረጋግጦ ተነግሮኛል። ይህን የሚያስረዳ የፍርድ ቤቱ ማረጋገጫ ሰነድም ከዚህ ጋር ተያይዟል። እኔም ሆንኩ ቤተሰቤ፣ አቶ አብርሀም ወልዷረጋይን ለማነጋገር ያደረግነው ጥረት ሊያነጋግሩን ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሊሳካልን አልቻለም። በኢፌዲሪ ህገ መንግስት አንቀፅ ሶስት በወንጀል ተጠርጥረው የተያዙ ሰዎች በአርባ ስምንት ሰአታት ውስጥ ፍርድ ቤት የመቅረብ መብት እንዳላቸው የተደነገገ ቢሆንም፤ እኔ ግን የተፈረደብኝን ቅጣት ጨርሼ ያለአንዳች ምክንያት ህገ መንግስቱን በመጣስ እስከ ዛሬ ነሀሴ ቀን ሁለት ሺህ ስድስትአመተ ምህረት ድረስ አንድ መቶ ቀናት ወይም ሁለት ሺህ ሰባት መቶ ስልሳ ሰአታት ታግቼ እገኛለሁ። ክብሩ ጠቅላይ ሚኒስትር በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር ሶስት መቶ ስልሳ አምስት አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ዘጠኝ አንቀፅ ስላሳ ዘጠኝ አንድ መሰረት በወጣው የፌዴራል ታራሚዎች አያያዝ የሚኒስቴሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር አንድ መቶ ስላሳ ስምንት አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ዘጠኝ አንቀፅ አርባ አራት አንድ ስለማረሚያ ቤቱ ግዴታ እንደሚከተለው ተደንግጓል። ማንኛውም ታራሚ የእስራት ጊዜውን ሲጨርስ፣ ይቅርታ ወይም ምህረት ሲያገኝ ወይም ፍርድ ቤት በአመክሮ እንዲፈታ ትእዛዝ ሲሰጥ ማረሚያ ቤቱ ታራሚውን ወዲያው የመፍታት ግዴታ አለበት ። ነገር ግን እኔን ለመጉዳት ሲባል ብቻ ይህ ደንብ ሊጣስ መቻሉን ክብሩነቶ እንዲያውቁት ነው። እንዲሁም በኢፌዲሪ ህገ መንግስት አንቀፅ ዘጠኝ አንድ የህገ መንግስቱ የበላይነት እንደሚከተለው ታውጇል፡ ህገ መንግስቱ የበላይ ህግ ነው። ማንኛውም ህግ፣ ልማዳዊ አሰራር፣ እንዲሁም የመንግስት አካል ወይም ባለስልጣን ውሳኔ ከዚህ ህገ መንግስት ጋር የሚቃረን ከሆነ ተፈፃሚነት አይኖረውም ተብሎ የተደነገገ ቢሆንም አሁንም እኔን ለመጉዳት ሲባል ብቻ ይህ የሀገሪቱ ህገ መንግስት ተጥሷል። ስለዚህም እስከ ዛሬ ድረስ ከነቤተሰቤ የደረሰብኝን የረዥም ጊዜ ተደራራቢ ችግር በጥሞና ተረድተውልኝ በህገ መንግስቱ የበላይነት ከእስር እንድፈታ ክቡርነትዎ ለማረሚያ ቤቱ ሀላፊ ለአቶ አብርሀም ወልዷረጋይ ትእዛዝ እንዲሰጡልኝ በማክበር አመለክታለሁ። ሻለቃ መላኩ ተፈራ ይመር
ይድረስ አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ህገ መንገስቱ ተጣሰ፣ ሻለቃ መላኩ ተፈራ ታገተ
አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት አስር ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በኢትዮጵያ አሁን ላይ በኮቪድ ከሚያዙ ሰዎች ውስጥ ነጥብ ዘጠኝ በመቶዎቹ ወደ ፅኑ ህሙማን ክፍል እንደሚገቡ ተገለፀ። በኢትዮጵያ የኮቪድ ስርጭት ያለበት ሁኔታ እና ከመነሻው ጀምሮ እስካሁን ን ምላሽ በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሀን ገለፃ ተደርጓል። የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አስቻለው አባይነህ እንዳሉት ኮቪድ በአለም ጤና ድርጅት የአለም የጤና ስጋት መሆኑንና ሀገራት ቅድመ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ከመገለፁ አስቀድሞ በቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ በመግቢያና መውጫ በሮች የሙቀት ልየታና ክትትል በማድረግ ቫይረሱ ሊያስከትለው የነበረውን ችግር በእጅጉ መቀነስ ችሏል። አሁን ላይ አዲስ አበባ በስርጭቱ ቀዳሚ መሆኗ የተገለፀ ሲሆን ኦሮሚያና ትግራይ ክልሎች ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ተጠቁሟል። በኢትዮጵያ ያለውን የቫይረሱን ስርጭት ለማወቅ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደ የአንድ ወር ሀገር አቀፍ የምርመራ ዘመቻ ከሰባ ሶስት በመቶ በላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ተለይተዋል ብለዋል። አሁን ላይ የምርመራ መጠን የቀነሰ ቢሆንም ቫይረሱ የሚገኝባቸው እና ለህልፈት የሚዳረጉ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑም ተነስቷል፤ ባለፉት ሁለት ሳምንት ውስጥ እንደሀገር ያለው የቫይረሱ ስርጭት አስር ነጥብ አራት በመቶ መሆኑም ተገልጿል። የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በበኩላቸው ኮቪድ ኝን ለመከላከል አስፈላጊውን የቅድመ ዝግጅትና መከላከል፣ የህክምናና የላቦራቶሪ ማእከላትን የማደራጀት ስራዎች መሰራታቸውን ጠቅሰው ቫይረሱ በሀገሪቱ ከተከሰተ በኋላ የተወሰዱ ጥብቅ እርምጃዎችና የአስቸኳይ አዋጅ መታወጁ ሊከሰት የነበረውን ችግር መቀነስ አስችሏል ነው ያሉት። ኮቪድ ኝን ለመከላከል ተወስደው የነበሩ ጠንካራ ክልከላዎችና እገዳዎች እንደሀገር ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተፅእኖ ማሳደራቸውን ያነሱት ሚኒስትሯ፥ ይህን ከግምት በማስገባት ቫይረሱን የጥንቃቄ ን ተግባራዊ በማድረግ ክልከላዎቹ እንዲላሉ ተደርጓል ብለዋል። ከመጋቢት ወር ጀምሮ የተዘጋው ትምህርትም እንዲከፈት የተደረገው ያለውን ተፅእኖ ከግምት በማስገባት ነው ብለዋል ዶክተር ሊያ። ነገር ግን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መነሳቱና የነበሩ ክልከላዎች መላላታቸው በማህበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ የሆነ መዘናጋትን መፍጠሩንም ጠቁመዋል። አሁን ላይ የተነሱትና የላሉት ክልከላዎች ብሎም ትምህርት መከፈቱ አስፈላጊ በመሆኑ አሁንም ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግም ጥሪ አቅርበዋል። የኮቪድ በኢትዮጵያ አሁንም ስጋት በመሆኑ የወጡ መመሪያዎችን ተግባራዊ ከማድረግ ጋር ተያይዞ የፀጥታ አካላት ሀላፊነታቸውን እንዲወጡም ጠይቀዋል። በመግለጫው ላይ የተገኙት በኢትዮጵያ የአለም ጤና ድርጅት ተወካይ ቦሬኢማ ሀማ ሳምቦ ኢትዮጵያ ለኮቪድ የሰጠችው ምላሽ የሚበረታታ መሆኑን በማንሳት አሁን ላይ ትምህርት እንዲከፈት መወሰኑ አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል። ተማሪዎች ለረጅም ጊዜ ቤት ውስጥ መቀመጣቸው ቫይረሱ ከሚያስከትለው በላይ የአእምሮና የስነ ልቦና ቀውስ እንደሚያስከትልባቸው በመጥቀስም ትምህርት መጀመሩ አስፈላጊ ነው ብለዋል። በሀይማኖት ኢያሱ
በኢትዮጵያ በኮቪድ ከሚያዙ ሰዎች ውስጥ በመቶ የሚሆኑት ወደ ፅኑ ህሙማን ክፍል ይገባሉ
ህዳር ቀን አመተ ምህረት ከቀትር በኋላ በ ሲኖትራክ ተሽከርካሪዎች ግምቱ ከ ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ ለ ቤቶች ግንባታ የሚውል የአርማታ ብረት ዘርፈዋል ተብለው የታሰሩ ሰባት ግለሰቦች ላይ ክስ ተመሰረተባቸው።የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ታህሳስ ቀን አመተ ምህረት ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ኛ ወንጀል ችሎት ያቀረበው ክስ እንደሚያስረዳው ተከሳሾቹ የዝርፊያ ወንጀሉን የፈፀሙት ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቁጠባ ቤቶች ልማት ኢንተርፕራይዝ መጋዘን ነው። መጋዘኑ የሚገኘው በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስድስት ውስጥ ሲሆን ተከሳሾቹ ድርጊቱን የፈፀሙት ህዳር ቀን አመተ ምህረት ከቀኑ ሰባት ሰአት እስከ ሰአት ባለው ጊዜ ውስጥ መሆኑን አቃቤ ህግ በክሱ ገልጿል።ተከሳሾቹ የኢንተርፕራይዙ የግብአት ክምችትና ስርጭት ኦፊሰር ተስፋለኝ በቀለ ነጋዴ መሆናቸው የተገለፀው ዳርሰማ ጃኦ ስንታየሁ ተስፋዬ አበበ ተስፋዬ ልኡል ፈቃዱ አሸናፊ ረታና ኢዮስያስ አለሙ ናቸው።ኦፊሰሩ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘትና ለሌሎቹም ለማስገኘት በማሰብ ግምቱ ብር የሆነ ባለ ስድስት ዲያሜትር ጥቅልና ባለ ስምንት ዲያሜትር ጥቅል የመንግስት ብረት በ ሲኖትራኮች በማስጫን እንዲዘረፍ ማድረጉ በክሱ ተገልጿል። ዳርሰማና ስንታየሁ በ ሲኖትራኮች የተጫነውን ብረት ሞጆ ሳይት ፋሪ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኘውና ዳርሰማ በተባለው ተከሳሽ መጋዘን ውስጥ እንዲራገፍ ማድረጋቸውም ተጠቁሟል። ብረቱን ከመጋዘን በማውጣት ከኢንተርፕራይዙ ያወጡት በፎርጅድ ሰነድ ተጠቅመው መሆኑም ተጠቁሟል።ተከሳሾቹ የብረቱን ምንጭና የባለቤትነት መብት እንዳይታወቅ ከማድረጋቸውም በተጨማሪ ዳርሰማ ከህግ ተጠያቂነት እንዲያመልጥ ስንታየሁ ሞጆ ሳይት ከሚገኘው መጋዘን የተራገፈውን ብረት በ ሲኖትራኮች በማስጫን ሰበታ በሚገኘው የግሉ ፕላስቲክ ፋብሪካ መጋዘን ውስጥ ማስተላለፉን ክሱ ያብራራል።አበበ ተስፋዬ የወንጀሉ ድርጊት እንዲፈፀም ሲያመቻች አሸናፊ ደግሞ በሁለት ሲኖትራኮች የቀረበለትን ብረት በመግዛት አዳማ ናዝሬት በሚገኘው የግል የንግድ ድርጅቱ ውስጥ ማስቀመጡን ክሱ ይጠቁማል። ኢዮስያስ ደግሞ የተሸጠለትን ኩንታል ብረት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ጭድ ተራ በሚገኘው ንግድ ድርጅቱ ውስጥ ማስቀመጡን ክሱ ያብራራል።በአጠቃላይ ተከሳሾቹ የወንጀል ህግ አንቀፅ ሀ እና ለን እና የሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር አንቀፅ ን ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር እና አዋጅ ቁጥር አንቀፅ ሀ ላይ የተደነገገውን ተላልፈው በመገኘታቸው በፈፀሙት ከባድ የእምነት ማጉደል ሙስና ወንጀል በወንጀል ድርጊት የተገኘን ገንዘብ ንብረት ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ የሙስና ወንጀልና መንግስታዊ ሰነዶችን አስመስሎ ማዘጋጀትና መገልገል የሙስና ወንጀል ክስ እንደተመሰረተባቸው አቃቤ ህግ ያቀረበው ክስ ያስረዳል።ተከሳሾቹ ዋስትና እንዲፈቀድላቸው ባቀረቡት የመብት ጥያቄ ላይ ተገቢ ምላሽ ለመስጠትና ከጠበቆቻቸው ጋር ተመካክረው የቅድመ ክስ መቃወሚያ ካላቸው ለመጠባበቅ ለታህሳስ ቀን አመተ ምህረት ቀጠሮ ተሰጥቷል።ምንጭ ሪፖርተር
ከ ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ የ ቤቶችን ብረት ዘርፈዋል የተባሉ ክስ ተመሰረተባቸው
ጀማል ባለፈው ማክሰኞ በቱርክ ኢንስታንቡል የሳኡዲ ቆንስላ ቀጠሮ ነበረው። የጋብቻ ጉዳዮችን ለመጨራረስ፤ የቀድሞው ባለቤቱን የፍቺ ጉዳይ ለመዝጋት አዲሷን ቱርካዊት ባለቤቱን አስከትሎ ወደዚያ ሄደ። ደጅ ጠብቂኝ መጣሁ አላት። በዚያው አልተመለሰም። የመጀመርያው ጥርጣሬ ሳኡዲ አፍና ወደ አገሯ ልካዋለች የሚል ነበር። አሁን እየወጡ ያሉ መረጃዎች ግን እዚያው ቆንስላው ውስጥ በምስጢር እንደተገደለ ፍንጭ የሚሰጡ ናቸው። የማትተነፍሰው ከተማ አዲስ አበባ የጠፉት የኢንተርፖል ሹም ቻይና ውስጥ ተገኙ ሳኡዲያዊው ጀማል ካሹጊ ቀደም ባሉት ዘመናት የንጉሳዊው ቤተሰብን እስከማማከር የደረሰ ሰው ነበር። የኋላ ኋላ ግን የመብት ጥያቄዎችን በማንሳቱ ጥርስ ውስጥ ገባ። ነገሩ አላምር ሲለው ወደ ቱርክ ሸሸ። ላለፉት አመታት የሳኡዲን አፋኝ አስተዳደር ሲነቅፍ ቆይቷል። የቱርክ ባለስልጣናት ከሳኡዲ ጋር ያላቸውን የዲፕሎማሲ ግንኙነት ላለማቆርፈድ ዝምታን መርጠው የነበረ ሲሆን ትናንት ግን ዝምታውን ሰብረውታል። ጀማል በቆንስላው ሳለ ተገድሏል ብለዋል ለቢቢሲ። ሳኡዲ ግን ዜጋዬን እየፈለኩት ነውና አፋልጉኝ ስትል ፌዝ የሚመስል መግለጫን አውጥታለች። አቶ ጀማል ካሹጊ ስመ ጥር ፀሀፊ ሲሆን በተለይም ለዋሺንግተን ፖስት አምደኛ በመሆን ይታወቃል። አብራው ወደ ሳኡዲ ቆንስላ ሄዳ የነበረችውን ባለቤቱ ምናልባት ካልተመለስኩ በዚህ ስልክ ቁጥር የረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ረዳት ለሆነ ሰው ደውለሽ ተናገሪ ብሏት እንደነበር ገልፃለች።
በገዛ አገሩ ኤምባሲ ውስጥ የተገደለው ጋዜጠኛ
አዲስ አበባ፣ ሀምሌ አስር፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በተለያዩ ሀገራት የሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች እና ሰራተኞች ዛሬ እየተከናወነ በሚገኘው በአንድ ጀንበር አምስት መቶ ሚሊዪንችግኝ የመትከል መርሀ ግብር ላይ ተሳተፉ። በጂቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በትዊተር ገፁ የአየር ንብረት ለውጥ ድንበር እንደማይገድበው ሁሉ የአረንጓዴ አሻራም ወሰን የለውም ብሏል። ኢትዮጵያ እና ጂቡቲ በአረንጓዴ ልማት ዘርፍ በጋራ እየሰሩ መሆኑን የጠቆመው ኤምባሲው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን በጂቡቲ አረጓዴ አሻራቸውን ማሳረፋቸውን አስታወሷል። በተመሳሳይ በጋና የኢትዮጵያ ኤምባሲ ነገን ዛሬ እንትከል በሚል መሪ ቃል በሀገር ደረጃ እየተከናወነ ባለው የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ተሳትፏል። በህንድ የኢትዮጵያ ኤምባሲም አምባሳደሮች፣ ዲፕሎማቶችና የኤምባሲው ሰራተኞችን በማሳተፍ አረንጓዴ አሻራ ማኖር እንደተቻለ በትዊተር ገፁ አመልክቷል። በተጨማሪም በአንድ ጀምበር አምስት መቶ ሚሊዮን የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር በጣሊያን የኢ ፌ ዴ ሪ ኤምባሲ ሰራተኞች ተከናውኗል። አምባሳደር ደሚቱ ሀምቢሳ በመርሀ ግበሩ እንዳሉት የአረንጓዴ አሻራ ምርሀ ግብር ትልቅ አለም አቀፋዊ እውቅናን ያተረፈ ተግባር መሆኑን ገልፀዋል።
በተለያዩ ሀገራት የሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች በአንድ ጀንበር አምስት መቶ ሚሊዪን ችግኝ የመትከል መርሀ ግብር ላይ ተሳተፉ
የጥቃቅንና አነስተኛ አሰሪዎች ፌዴሬሽን ራሱን ችሎ በፌዴሬሽን ደረጃ የተቋቋመው አምና ሁለት ሺህ ዘጠኝ አመተ ምህረት ነበር። በመላው አገሪቱ በጥቃቅን፣ ታዳጊና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በተደራጁ ሁለት ሺህ ማሀበራት አማካይነት የተመሰረተ ነው። ራሱን ችሎ የተቋቋመበት ምክንያት ኢንተርፕራይዞችን የሚወክሉ ማሀበራት በመበራከታቸውና በስራቸው የሚያቅፏቸው ሰራተኞችም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ በመምጣታቸው የአሰሪና ሰራተኛ ግንኙነት ሰላማዊ ለማድረግ ከወዲሁ ማሀበራትን ወደ ፌዴሬሽን ደረጃ ማሳደግ አስፈላጊ በመሆኑ ነበር። በአሁኑ ወቅት ከሁለት አምስት መቶ በላይ አባላት ያፈራው የኢትዮጵያ ጥቃቅንና አነስተኛ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ አሰሪዎች ፌዴሬሽን ህጋዊ ሰውነት አግኝቶ ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ ምን እየሰራና ወደፊት ሊሰራ ያቀዳቸውን ነገሮች በተመለከት የፌዴሬሽኑን ፕሬዚዳንትና የትንሳኤ ኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራ አስኪያጅ አቶ ጌታቸው ሀይሌን ታምራት ጌታቸው አነጋግሯቸዋል። ሪፖርተር፡ አባሎቻችሁ በምን አይነት መስክ የተሰማሩ ናቸው ፌዴሬሽኑ ምን ያህል አባላትስ አሉት አቶ ጌታቸው፡ በኢትዮጵያ በጠቅላላው ወደ ስድስት መቶሺ ኢንተርፕራይዞች ማሀበሮች አሉ። ከነዚህ ውስጥ በኛ ስር ያሉት ሁለት አምስት መቶዎቹ ናቸው። ይኼ ብቻ የሆነው ጥቃቅንና አነስተኛ ሲደራጁ በየክልሉ ሆኖ መሰረታዊ ማሀበሮች በመሆናቸው ነው። እነዚህን ማሀበራት በቅርቡ በክልል ደረጃ በማሳደግ በክልሉ የኢትዮጵያ ጥቃቅንና አነስተኛ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ አሰሪዎች ፌዴሬሽን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ይሆናሉ ማለት ነው። በተመሳሳይ በሌሎችም ክልሎች እንደዚህ አይነት አደረጃጀቶች እየፈጠርን ነው። እንግዲህ ስሙ ራሱ እንደሚያመለክተው ጥቃቅንና አነስተኛ ሆነው ለምሳሌ እንጀራ በመጋገር ተነስተው ወደ ባለ ሆቴልነት የተቀየሩት፣ ከቀን ስራ ጀምረው ትልልቅ ኮንስትራክሽን ስራ የሚሰሩ በተለያዩ የሙያ ዘርፍ ያሉትን ያጠቃልላል። አሰሪ እነዚህ ሁለት አምስት መቶ ማሀበሮች በትንሹ እያንዳንዳቸው ከአስር እስከ ስላሳ የሚደርሱ ቋሚና ጊዜያዊ ሰራተኛ ቀጥረው የሚያስተዳድሩ ናቸው። ሪፖርተር፡ ከኢትዮጵያ አሰሪዎች ፌዴሬሽን ጋር ያላችሁ ግንኙነት ምን ይመስላል አቶ ጌታቸው፡ መጀመሪያ እኛን ያቋቋመን ራሱ የኢትዮጵያ አሰሪዎች ፌዴሬሽን ነው። ሌሎች በአገሪቱ ካሉ አምስት አሰሪ ፌዴሬሽኖች ጋር በጋራ ለመስራት በወሰነው መሰረትም እየሰራን እንገኛለን። ለኢትዮጵያ አሰሪዎች ፌዴሬሽንም አብረን ለመስራት ጥያቄ አቅርበን መልስ እየጠበቅን እንገኛለን። ሪፖርተር፡ ራሳችሁን ለማደራጀት በየክልሉ እየተንቀሳቀሳችሁ ነው። በስራችሁ የገጠማችሁ ችግር ካለ አቶ ጌታቸው፡ ማደራጀቱ ገና ቀጣይ ስራ ነው። በቅርቡም በደቡብ ክልል በአምስት ዞኖች ላይ በወልቂጤ፣ በወላይታ ሶዶ፣ በአርባ ምንጭ በተጨማሪም ለማደራጀት ዝግጅት የጨረስን ነው። እንደዚሁ ደግሞ በትግራይ ክልል በምስራቃዊ ዞን አዲግራትን ጨምሮ ዘጠኝ ወረዳዎችን ለማደራጀት ወደዚያው የምናቀና ይሆናል። በመቐለም በተመሳሳይ ሁኔታ የምናጠናክር ይሆናል። በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል በጅማ፣ በአዳማ፣ በቢሾፍቱ ያደራጀን ሲሆን፣ በቀጣይ በነቀምቴ፣ በአምቦና በሌሎች ከተሞች ለማደራጀት እንቅስቃሴ ላይ ነን። እነዚህን ስራ ስንሰራ እየገጠሙን ያሉ ችግሮች በዋናነት የገንዘብ እጥረት ነው። ሁለተኛ ከኢትዮጵያ አሰሪዎች ፌዴሬሽን ጋር ልዩነታችሁ ምንድነው በሚል የሚገጥመን ሙግት ነው። ሪፖርተር፡ አባሎቻችሁን ለማብቃት ምን እያከናወናችሁ ነው አቶ ጌታቸው፡ መንግስት እነዚህ ኢንተርፕራይዞች ወደፊት የአገርን ፍላጎት አሟልተው ወደ ውጭ በመላክ የውጭ ምንዛሪ ያመጣሉ ብሎ የሚያምንባቸው የወደፊት ኢንዱስትሪውን ይረከባሉ ተብለው የሚጠበቁ ናቸው። ስለዚህ ዛሬ ራሳቸውን አዘጋጅተው መጠበቅ ስላለባቸው የመደራጀት ጥቅሙ ምንድን ነው፣ በመደራጀት ችግሮች እንዴት ተፈቱ የሚለው አንዱ ሲሆን፣ ዛሬም የአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ህጉን ባለማወቅ እሰጥ አገባ ውስጥ በመግባት የገንዘብ፣ የጊዜና የንብረት ብክነት እየመጣ በመሆኑ አዋጁን በማስተማር ምልከታ መስጠት፣ ሌላው ደግሞ የስራ ፈጠራን በሚመለከት ነው። አንዱ ገንዘብ ይዞ ምን እንደሚሰራ ግራ ይገባዋል። አንዱ እውቀት ይዞ የት እንደሚሰራ ፈጠራውን የት መሸጥ እንዳለበት ባለማወቅ እየተላለፈ ይኖራል። እነዚህን እንዴት ማገናኘት እንደሚቻል የጠለቀ እውቀት የሚገኝበት መድረክን በየጊዜው እያዘጋጀን ነው። ተሳታፊዎችም ያገኙትን እውቀት በቀላሉ ለሌሎች እንዲያካፍሉ ይደረጋል። እኛም ይኼንን መሳይ ትምህርት በማዘጋጀት ወደፊት በስፋት የምንሄድበት ይሆናል። ይኼም የኢንዱስትሪውን ሰላም ለማስጠበቅ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል። ሪፖርተር፡ ማሀበሩ ያሉበት ችግሮች ምንድናቸው ወደፊትስ ምን ሊሰራ አስቧል አቶ ጌታቸው፡ ለጊዜው ያለብን የገንዘብ ችግር ነው። አባላት መዋጮዋቸውን በጊዜው ስለማይከፍሉ ለሰራተኞችና ለቤት ኪራይ ከመክፈል ውጪ ባለፈ የሚተርፍ አይደለም። ሌላውና ትልቁ ችግር ፌዴሬሽኑ የራሱ ህንፃ የለውም። አሁን ያለው በኪራይ ቤት ነው። ቋሚ የሆነ ቢሮ ስለሌለው ቋሚ አድራሻም የለውም። ከየትኛውም የመንግስት አካል ድጋፍ እያገኘንም አይደለም። በራሳችን ነው የምንንቀሳቀሰው። ፌዴሬሽኑ ግን እጁን አጣጥፎ አልተቀመጠም። ከሁለት ወር በኋላ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሚገኙበት የእውቅናና የምስጋና ፕሮግራም ከከተማው የምግብ ዋስትና ፕሮግራም ጋር በመሆን አገር አቀፍ ንቅናቄን ለመፍጠር እየተዘጋጀን ነው። በዚሁ ፕሮግራም ላይ መንግስት ለጥቃቅንና አነስተኛው ዘርፍ ከአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና አራት አመተ ምህረት ጀምሮ ሳይሰለች ላደረገልን ድጋፍ ምስጋና የምናቀርብ ይሆናል። ሌላው ፌዴሬሽኑ ከማሀበሩ ምስረታው ጀምሮ ነገ ምን መድረስ አለበት በሚል ጥናታዊ ፅሁፍ በማቅረብ በዚያው የሰራቸውን ስራዎች የሚገመገምበት፣ ያሉበትን ችግሮችም ዘለቄታዊ መፍትሄ የሚያገኙበት ይሆናል ብለን እንጠብቃለን። ሌላው የረዥም ጊዜ እቅዶቻችን ከእነዚህ ከስድስት መቶሺ በላይ የሆኑትን ማሀበሮችን በማሰባሰብ ባንክ ማቋቋም ነው። ምክንያቱም አሁን ለኢንተርፕራይዙ ትልቅ ችግር እየሆነ ያለው የብድር አቅርቦት ነው። የሚቋቋመው ባንክም ያለውን ችግር መቅረፍ የሚችል እንዲሆን ታቅዷል። ለጊዜው በዚህ በኩል ያለብንን ችግር ለመፍታት ከልማት ባንክ ጋር እየተነጋገርን እንገኛለን።
ባንክ ለማቋቋም የሰነቀው የጥቃቅንና አነስተኛ አሰሪዎች ፌዴሬሽን
ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ ከጋዜጠኛ መአዛ ብሩ ጋር ያደረጉትን ቃለምልልስ አዳመጥኩት።ግሩም ነበርጋዜጠኛዋ ወይዘሮ መአዛ ብሩ የሚያነሷቸው ጥያቄዎች እንደተለመደው በሳል እና ሰፋ አድርጎ ለመናገር የሚመቹ እና የሚጋብዙ ነበሩ።ከጠቅላይ ሚኒስተርው ተፈጥሮ የምወድላቸው ለህዝብ ቀረብ የማለት ሰዋዊነት ለጠያቂ ጋዜጠኛም ምቾት መስጠቱ አይቀርም።መደብ ላይ እየተኛሁኩራዝ የሚበራበት ቤት ውስጥ ያደግኩ ነኝ ሲሉ አድማጭ ከእኛ እንደ አንዱ እንጅ ከሰማይ ዱብ ብለው ዙፋን ላይ ያረፉ አለመሆናውን ይረዳልይህ አይነቱ ሰው ሰው የሚል ነገር ከመሪ አንደበት ሲወጣ አንዳች ህዝብን እና መሪን የሚያቀራርብ መስህብ አለው።የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስተር ከሰው ይልቅ ለእግዜር የመቅረብ ሁኔታ ከእለታት አንድ ቀን ለጥያቄ ፊታቸው የሚኮለኮሉ ጋዜጠኞችን እጅ ሲያንቀጠቅጥቃላትን ሲሰባብርትንፋሽ ሲቆራርጥ ተመልክቼ አውቃለሁና ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ ከጋዜጠኛ ጋር ሲገናኙ የሚያሳዩት ሰዋዊ ትህትና ከትልቅነት የምመዘግብላቸው ማንነታቸው ነው።ከሸገር ጋር በነበራቸው ረዘም ያለ ቆይታ ካነሷቸው ሀሳቦች የመደመር ፍልስፍናቸውን በተመለከተ ያቀረቡት ሀተታ በዚሁ ፍልስፍና ዙሪያ የነበረኝን ግርታ በመጠኑ ያቃለለ ነው። መደመር የሚለው አመት ሙሉ ሾላ በድፍን ሆኖ የኖረ ነገር መፍታታቱ ደግ ነው። በፍልስፍናው ዙሪያ ይታተማል ያሉትን መፅሀፍ ለማንበብም ጉጉ ነኝ። በመደመር ፍልስፍናቸው ውስጥ ትብብር እና ውድድርን እንዴት አብሮ ማስኬድ እንደሚቻል በአዞው እና በወፏ መስለው ያነሱትን ጭብጥ የበለጠ ወድጄዋለሁ።የተጠናወተን በሁሉነገር በብሄረሰባችን አንፃር የመወዳደር አባዜ በቀላሉ ይለቀናል ብየ ለመገመት ቢቸግረኝም ይህ ፍልስፍና ሲብራራመፅሀፍ ሆኖ ሲመጣ የሚያቀለው ችግር ቀላል አይሆንም። ከሁሉም በላይ ከባህር ማዶ ፍልስፍና ለማድረግ ዘምቢል ይዘን ከምንባዝን እንደ ሁኔታችንበችግራችን ልክ እና ተፈጥሮ በተሰፋ ሀገር በቀል ፍልስፍና ደግሞ ከፖለቲካችን ደዌ የምንፈወስ ከሆነ መሞከሩ አይከፋም።የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስተር በመሆናቸው ለሁሉም ኢትዮጵያዊ እንደሚሰሩኦሮሞም ለብቻው በተለየ ሁኔታ እንዳይጎዳ እንደታገሉበተለየ ሁኔታ እንዲጠቀምም እንደማይሰሩ የተናገሩት ንግግር ለጆሮ ቢጥምም በተግባር ከሚታየው ጋር ግን አይገጥምም። ሊቀመንበር ሆነው የሚመሩት ፓርቲ በአዲስ አበባ ላይ ልዩ ጥቅም ይገባኛልልዩ ጥቅሜ ደግሞ አዲስ አበባን ፊንፊኔ ብሎ የኦሮሞ ግዛት ማድረግ ነው ሲል ልዩ ጥቅም ከማለት አልፎ ጠቅልሎ የመውሰድ ትግል እንደሚያደርግ መግለጫ አውጥቶ በታከለ ኡማ በኩል ከሚያደርገው ርብርብ ጋር አይገጥምም።እንደ እኔ ላለ ቃል ከተግባር ጋር ማመሳከር ለሚወድ ዜጋ ይህች ንግግር መኮስኮሷ አይቀሬ ነው። በዚህ ረገድ ከአብይ አለፍ ብሎ ኦህዴድ ላይ ትኩረት ማድረጉ ደግ እንደሆነ አውቃለሁና ጠቅላይ ሚኒስተርውን በግል ልከሳቸው አልሻም። ለምን ቢባል ኦህዴድ ውስጥ ያለው የኦነግ መንፈስበአጠቃላይ በኦሮሞ ብሄርተኛው ጎራ ያለው የማይጠረቃ የኬኛ ጥያቄየኦህዴድም ከዚህ የማይጠረቃ ጥያቄ አለመዋጀት ጠቅላይ ሚኒስተርው የሚፈልጉትን ብቻ ሳይሆን የማይፈልጉትን የመናገር የመስራት ውድድር ውስጥ እንደሚከታቸው አላጣውም። ዋናው ለጥያቄ ግን አስከመቼ እንዲህ ሆነው ይዘልቁታል የሚለው ነውጠቅላይ ሚኒስተርው ሀገራቸውን የሚወዱበትን ውድ የገለፁበት መንገድ ልቤን ነክቶታል።ኢትዮጵያን በጣም ከሚወዱ ዜጎች አንዱ እንደሆኑ ገልፀው ስለ ኢትዮጵያ ሲሆን እንደሌላ ጊዜ ጠንከር ብሎ መቆም እስኪቸግራቸው ድረስ ስለኢትዮጵያ ሲሆን ስስ እንደሆኑ ገልፀዋል። እንዲህ ሲሉ እኔን እኔን መስለውኝ ነው መሰለኝ ምን እያሉ እንደሆነ በደንብ ተረድቻለሁ እንዲህ የሚል ጠቅላይ ሚኒስተር በማኘታችንም ደስተኛ ነኝ። ይህን ያሉት አብይ ነገ ሌላ ጥፋት ሊያጠፉ ይችላሉ ግን ከዚህ ኢትዮጵያን ከመውደዳቸው ከፍታ እስካልወረዱ ድረስ ከነቃርሚያው ተስፋ እንዳደርግ ያደርጉኛል።ባለቤታቸውን ከእናታቸው ጋር እያናፀሩ የገለፁበት መንገድበተለይ ቀዳማዊት እመቤቷ በመጠን መኖርን የሚውቁ ቀጥብ ግን ደግሞ ሀይለኛ ሴት መሆናቸውን የገለፁበት መንገድ ወይዘሮ ዝናሽ ከሚያበዙ የአፍሪካ ቀዳማዊ እመቤቶች ወገን አለመሆናቸውን ያሳያልይህም መልካም ነው ሀይለኝነቱም አይጠላምሴት ሀይለኛ ካልሆነች ይህን የወንድ አለም እንዴት ትዘልቀዋለች በስተመጨረሻም ጠቅላይ ሚኒስተርው ለጥበብ ቀረብ ያለች ነፍስ እንዳለቻቸው ግጥም አብዝተው እንደሚወዱ የሚያደንቋቸውን ገጣሚያንን በመዘርዘር ተናግረዋል። ጥበብን መውደድ ሀገርን የመረዳት መንገድ ነውበጥበብ በር ገብቶ የማይፈተሸ የህይወት ገፅ የለምና
ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ ከጋዜጠኛ መአዛ ብሩ ጋር ያደረጉትን ቃለምልልስ መስከረም አበራ
በአዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖርት የተፈጠረውን መጨናነቅ ለመቀነስ፣ መደበኛ ያልሆነ የበረራ አገልግሎት ለሚሰጡ የግል አየር መንገዶች ብቻ የሚያገለግል ኤርፖርት ለመገንባት ጥናት እየተካሄደ እንደሆነ ተጠቆመ። የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣንና የኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ድርጅት በጋራ ከባለድርሻ አካላት ጋር የካቲት ሀያ ስድስት ቀን ሁለት ሺህ ሰባት አመተ ምህረት ባካሄዱት ስብሰባ፣ መንግስት በአዲስ አበባ አነስተኛ አውሮፕላኖች የሚስተናገዱበት የተለየ ኤርፖርት እንዲገነባ የግል አየር መንገዶች በተደጋጋሚ ያቀረቡትን ጥያቄ እያጤነው እንደሆነ ተገልጿል። በስብሰባው ላይ ማብራሪያ የሰጡት የኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ድርጅት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ቴዎድሮስ ዳዊት፣ ድርጅታቸው ሁለት አማራጮችን በመመልከት ላይ እንደሆነ ጠቁመዋል። አንደኛው አማራጭ የግል አየር መንገዶች በአነስተኛ አውሮፕላኖች መደበኛ ያልሆነ የበረራ አገልግሎት የሚሰጡ የሚጠቀሙበት መንደርደሪያና የተለየ የመንገደኞች ተርሚናል በአዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖርት ግቢ ውስጥ መገንባት ሲሆን፣ ሁለተኛው አማራጭ ራሱን የቻለ አነስተኛ ኤርፖርት ከአዲስ አበባ ወጣ ብሎ በሚገኝ ስፍራ መገንባት የሚል እንደሆነ አቶ ቴዎድሮስ ተናግረዋል። በከፍተኛ ወጪ በክልል ከተሞች ላይ የተገነቡና ከአቅም በታች የሚሰሩ ኤርፖርቶችን መጠቀም የሚል አማራጭ ሀሳብ ቢኖርም፣ የቻርተር በረራ አገልግሎት ገበያ በአብዛኛው ያለው አዲስ አበባ በመሆኑ ተግባራዊ ማድረግ ሊያስቸግር እንደሚችል አቶ ዳዊት አስረድተዋል። በተጠቀሱት አማራጮች ላይ ድርጅታቸው ጥናት በማካሄድ ላይ መሆኑንም ተናግረዋል። የኤርፖርት ግንባታ ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅ በመሆኑ ያለው ፍላጎትና የግል አየር መንገዶች አቅም በሚገባ መጠናት እንዳለበት ሀላፊው ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የተመዘገቡ የግል አየር መንገዶች ሲኖሩ በትክክል የቻርተር በረራ አገልግሎት የሚሰጡት ከስድስት አይበልጡም። እነዚህ የግል አየር መንገዶች የተጋረጡባቸው በርካታ ችግሮች እንዳሉባቸው ይገልፃሉ። አየር መንገዶቹ ብሶታቸውን በተለያዩ መድረኮች ለኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣንና ለኤርፖርቶች ድርጅት ሲያቀርቡ ቆይተዋል። አየር መንገዶቹ ከሚያቀርቧቸው በርካታ ጥያቄዎች መካከል ለጄኔራል አቪዬሽን የሚያገለግል የተለየ ኤርፖርት ግንባታ ዋነኛው ነው። የአዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖርት አንድ መንደርደሪያ ብቻ ያለው ሲሆን በቀን ከአንድ መቶ ሀምሳ በላይ በረራዎች ያስተናግዳል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በከፍተኛ ፍጥነት በማደግ ላይ በመሆኑና ወደ አዲስ አበባ የሚበሩ አለም አቀፍ አየር መንገዶች ቁጥር በመጨመሩ ኤርፖርቱ በመጨናነቅ ላይ ይገኛል። የግል አየር መንገዶች ቀላል አውሮፕላኖችን የሚያንቀሳቅሱ በመሆናቸው፣ በአንድ መንደርደሪያ ላይ እንደ ድሪምላይነርና ቦይንግ ሰባት መቶ ሰባ ሰባት ከመሳሰሉ ግዙፍ አውሮፕላኖች ጋር ተጋፍተው መስራት እንደተቸገሩ ሲገልፁ ከርመዋል። በተፈጠረው መጨናነቅ ምክንያት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የፓይለት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የተግባር ልምምድ በከፊል ድሬዳዋና ደብረ ዘይት ለማካሄድ ተገዷል። የግል አየር መንገዶች ያሉባቸውን ችግሮች ለኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣንና ለኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ድርጅት ሲያቀርቡ መቆየታቸው ይታወሳል። በተለይ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን በአመት ሁለት ጊዜ በሚያዘጋጀው የምክክር መድረክ ላይ የግል አየር መንገዶችን ችግር በማዳመጥ መፍትሄ በመስጠት ይታወቃል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ድርጅትም ምላሽ በመስጠት ላይ ይገኛል። ትራንስፖርት ሚኒስቴር በበኩሉ ለግል አየር መንገዶች አቤቱታ ጆሮ መስጠት ጀምሯል። የትራንስፖርት ሚኒስትሩ አቶ ወርቅነህ ገበየሁ ለመጀመሪያ ጊዜ የግል አየር መንገዶችን፣ የአውሮፕላን ነዳጅ አቅራቢዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን በአንድነት ታህሳስ ሁለት ሺህ ሰባት አመተ ምህረት አነጋግረዋቸው ነበር። አቶ ወርቅነህ በተለይ የግል አየር መንገዶች ያሰሙትን ብሶት በጥሞና ያዳመጡ ሲሆን፣ የሚመለከታቸው አካላት ለቀረቡት ችግሮች የመፍትሄ ሀሳብ እንዲያቀርቡ ትእዛዝ ሰጥተዋል። የግል አየር መንገዶች ያቀረቧቸውን ሀያ አንድ ያህል ጥያቄዎች የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኮሎኔል ወሰንየለህ ሁነኛው፣ ባለፈው ሀሙስ በዝርዝር አቅርበዋል። ከሚኒስትሩ ጋር ከተካሄደው ስብሰባ በኋላ የተወሰዱ እርምጃዎችንና የቀረቡ የመፍትሄ ሀሳቦች ላይ ውይይት ተካሂዷል። የአውሮፕላን ጥገና ሀንጋር አለመኖር፣ የአውሮፕላን መቀመጫ ብዛት ገደብ፣ የኤርፖርት መጨናነቅ፣ የመንገደኞች ማስተናገጃ ካውንተር አለመኖር፣ የሻንጣ ማጓጓዣ ቀበቶ ኮንቬየር ችግር፣ የነዳጅ አቅርቦት፣ በኤርፖርት የሚከራይ ቢሮ አለማግኘታቸውና የጉምሩክና የኢሚግሬሽን አሰራር ለሚኒስትሩ ካቀረቧቸው ሀያ አንድ ጥያቄዎች መካከል በዋነኛነት የሚጠቀሱ ናቸው። መንግስት ለጄኔራል አቪዬሽን ተገቢውን ትኩረት መስጠት መጀመሩን የተናገሩት ኮሎኔል ወሰንየለህ፣ የግል አየር መንገዶች ለሚኒስትሩ ያቀረቧቸው አብዛኛዎቹ ጥያቄዎች እንደሚመለሱ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል። ረዥም ጊዜ የወሰደው ብሄራዊ የአየር ትራንስፖርት ፖሊሲ ለውይይት በቅርቡ እንደሚቀርብና በአጭር ጊዜ ውስጥ ይፀድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ አስረድተዋል። በውይይቱ ላይ ተሳታፊዎች ወደ አገር በሚገቡ አውሮፕላኖች እድሜና በአብራሪዎች እድሜ ላይ በተጣሉ ገደቦች ላይ ጥያቄ አንስተዋል። አየር መንገዶች ወደ አገር ውስጥ ማስገባት የሚችሏቸው አውሮፕላኖች እድሜ ከሀያ ሁለት አመት እንዳይበልጥ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ይከለክላል። ባለስልጣኑ ፓይለቶች እድሜያቸው ከስልሳ አምስት ካለፈ አውሮፕላን እንዳያበሩም ይከለክላል። የአቢሲኒያ የበረራ አገልግሎት ባለቤትና ማኔጂንግ ዳሬክተር ካፒቴን ሰለሞን ግዛው የካበተ ልምድ ያላቸው ፓይለቶች በየካፌው ማኪያቶ ከሚጠጡ፣ ያላቸውን እውቀት ለወጣት አብራሪዎች ቢያካፍሉ ምን አለበት ሲሉ ጠይቀዋል። በአውሮፕላን እድሜ ላይ የተጣለውን ገደብ በተመለከተ ህጉ ተፈፃሚ የሚሆነው በአገር ውስጥ አየር መንገዶች ላይ ብቻ እንደሆነ ካፒቴን ሰለሞን ተናግረዋል። የአገር ውስጥ ኩባንያዎች አዲስ አውሮፕላኖች እንዲያበሩ ሲገደዱ፣ የውጭ አየር መንገዶች ያረጁ አውሮፕላኖች አምጥተው እንዲሰሩ ይፈቀድላቸዋል። ይህ ፍርደ ገምድል ውሳኔ ይመስለኛል፤ ብለዋል። ለጥያቄው ምላሽ የሰጡት ኮሎኔል ወሰንየለህ በአውሮፕላኖችና በፓይለቶች እድሜ ላይ የተጣለው ገደብ ለበረራ ደሀንነት በማሰብ እንደሆነ፣ መመርያው የወጣው የአለም አቀፍ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት ደንብ ተከትሎና የሌሎች አገሮች ልምድን በማገናዘብ እንደሆነም አስረድተዋል። የውጭ ኩባንያዎች ያረጁ አውሮፕላኖችን እንደልባቸው አስገብተው ይሰራሉ በማለት ካፒቴን ሰለሞን ያቀረቡትን ቅሬታ፣ ባለስልጣኑ ሙሉ በሙሉ የሚቀበለውና የማስተካከያ እርምጃ እንደሚወስድበት ገልፀዋል። የናሽናል ኤርዌይስ ባለቤትና ዋና ስራ አስፈፃሚ ካፒቴን አበራ ለሚ በበኩላቸው፣ ተመሳሳይ ወቀሳዎችን በየጊዜው ደጋግመው መናገራቸው እያሳፈራቸው እንደመጣ ተናግረዋል። መንግስት የግል አየር መንገዶች የሚጠቀሙባቸው አውሮፕላኖች መቀመጫ ብዛት ላይ የጣለው ገደብ ሁሌም እንደሚያሳዝናቸው የገለፁት ካፒቴን አበራ፣ የጥገና ሀንጋር መገንቢያ መሬት በመከልከላቸው የግል አየር መንገዶች አውሮፕላኖቻቸውን በጠራራ ፀሀይና ዶፍ ዝናብ ለመጠገን እንደሚገደዱ ተናግረዋል። መንግስት የግል አየር መንገዶች እንዲያድጉ ከፈለገ አስፈላጊውን ድጋፍ ሊሰጥ እንደሚገባ ካፒቴን አበራ ጠይቀዋል። ምላሽ የሰጡት አቶ ቴዎድሮስ ቀደም ሲል መንግስት ለአቪዬሽን መስክ ቅድሚያ እንዳልሰጠ፣ መንግስት ቅድሚያ ሰጥቶ ሲሰራ የነበረው በሌሎች አንገብጋቢ የድህነት ቅነሳ ፕሮግራሞች ላይ መሆኑን ጠቅሰው፣ ይህ ግን እየተለወጠ እንደመጣ ተናግረዋል። የአገሪቱ ኢኮኖሚ በፍጥነት በማደግ ላይ እንደሆነና የአየር ትራንስፖርት ፍላጎት ከኢኮኖሚ እድገቱ ጋር ተያይዞ በማደግ ላይ በመሆኑ፣ በአሁኑ ወቅት መንግስት ለአቪዬሽን ዘርፍ ተገቢውን ትኩረት መስጠቱን ገልፀዋል። የግል አየር መንገዶች ለኢኮኖሚው ያላቸው አስተዋፅኦ አነስተኛ ቢሆንም፣ መንግስት በአሁኑ ወቅት ተገቢውን ትኩረት እየሰጣቸው እንደሚገኝ የገለፁት አቶ ቴዎድሮስ፣ ለኢኮኖሚው ያላቸው አስተዋፅኦ አነስተኛ ነው ብለን አንንቅም። ከቅርብ አመታት ወዲህ እየተጠናከሩ መጥተዋል። እኛ የምናየው ያለውን ያልተነካ ትልቅ እምቅ አቅም ጭምር ነው፤ በማለት ገልፀዋል። አቶ ቴዎድሮስ የካውንተርና የቢሮ ጥያቄ በአዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖርት የተጀመረው የማስፋፊያ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ ሙሉ በሙሉ መፍትሄ እንደሚያገኝ፣ እስከዚያው ግን ባለው አቅም ለማስተናገድ ጥረት እንደሚደረግ፣ የጥገና ቦታን በተመለከተ በቅርቡ ምላሽ እንደሚሰጥበት ተናግረዋል። የአውሮፕላን መቀመጫ ብዛት ገደብና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች በተመለከተ በአየር ትራንስፖርት ፖሊሲው ምላሽ እንደሚያገኙ ኮሎኔል ወሰንየለህ አስረድተዋል። የግል አየር መንገድ ተወካዮች የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣንና ኤርፖርቶች ድርጅት፣ እንዲሁም ትራንስፖርት ሚኒስቴር ለሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠታቸው ምስጋና አቅርበዋል።
ለግል አየር መንገዶች የሚያገለግል ኤርፖርት ለመገንባት ታስቧል
አዲስ አበባ ፣ ነሀሴ ሀያ አምስት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ ባለፉት ሀያ አራት ሰአታት ውስጥ በተደረገ ሺህ ሶስት መቶ ስልሳ አራት የላቦራቶሪ ናሙና ምርመራ አንድ ሺህ ዘጠኝ ሰዎች ላይ የኮሮና ቫይረስ መገኘቱን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ ። ሚኒስቴሩ በእለታዊ መግለጫው በአጠቃላይ እስካሁን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ሀምሳ ሁለት ሺህ አንድ መቶ ስላሳ አንድ ደርሷል። በሌላ በኩል ስድስት መቶ ሰዎች ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ እስካሁን ድረስ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና አራት ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል። በሀያ አራት ሰአታት ውስጥም የ ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን ያንንም ተከትሎ በሀገሪቱ በቫይረሱ ህይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥር ስምንት መቶ ዘጠኝ ደርሷል። እንደ ሚኒስቴሩ መግለጫ በአሁኑ ወቅት ሶስት መቶ አርባ አራት ሰዎች በቫይረሱ ምክንያት በፅኑ የታመሙ ሲሆን እስከ አሁን በአጠቃላይ ለዘጠኝ መቶ አስር ሺህ ሁለት መቶ ዘጠና ሶስት ሰዎች የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጓል።
ባለፉት ሀያ አራት ሰአታት አንድ ሺህ ዘጠኝ ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው የ ሰዎች ህይወት አልፏል
ኢሳት ነሀሴ አራት ሁለት ሺህ ስምንት የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን በሳምንቱ መገባደጃ በኦሮሚያና አማራ ክልሎች የተፈፀሙ ግድያዎችን በገለልተኛ አለም አቀፍ ታዛቢ ቡድን ማጣራት እንዲደረግበት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ውይይት በማካሄድ ላይ መሆኑን ረቡእ ይፋ አደረገ። በአለም ዙሪያ የሚፈፀመው የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን የሚከታተለው ይኸው አካል የኢትዮጵያ መንግስት ከአለም አቀፍ ገለልተኛ አካል በሯን ክፍት እንድታደርግ በይፋ መጠየቁን ሮይተርስ ከጄኔቭ ዘግቧል። ከቀናት በፊት ከአንድ መቶ ለሚበልጡ ሰዎች ግድያ ምክንያት የሆነው ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ በጉዳዩ ዙሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ መግለጫን የሰጡት የኮሚሽኑ ሀላፊ ዘይድ ራድ አል ሁሴን በሁለቱ ክልሎች በሳምንቱ መገባደጃ የተፈፀሙ ግድያዎች ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት እጅግ አሳሳቢ መሆኑን አስታውቀዋል። የተለያዩ አለም አቀፍ አካላት በድርጊቱ ስጋታቸውን በመግለፅ ላይ እንደሚገኙ የገለፁት ሀላፊው፣ ይህንኑ ዘመቻ ተከትሎ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ግድያውን ማጣራት እንዲካሄድበት መወሰኑን ይፋ አድርገዋል። በኦሮሚያ ክልል ለወራት ዘልቆ ከቆየው ተቃውሞ ጋር በተገናኘ በተመሳሳይ ሁኔታ ግድያ ተፈፅሞ በገለልገኛ አካል ማጣራ አለመካሄዱን ያወሱት የሰብአዊ መበት ኮሚሽኑ ሀላፊ በሀገሪቱ በአጠቃላይ ስለተገደሉ ሰዎች ቁጥር ትክክለኛ መረጃ አለመገኘቱን አክለው አስታውቀዋል። ከተቃውሞው ጋር በተገናኘ ለእስር የተዳረጉ ሰዎች በአስቸኳይ እንዲፈቱ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ዋናው ፅህፈት ቤትቱ ከሚገኝበት ጄኔቭ ከተማ ጥሪውን አቅርቧል። ሂውማን ራይትስ ዎች ከተለያዩ አካላት የሰበሰባቸውን ማስረጃዎች ዋቢ በማድረግ በኦሮሚያ ክልል ብቻ ከአራት መቶ በላይ ሰዎች መገደላቸውን በቅርቡ ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ በአስርሺ የሚቆጠሩ ሰዎችም ለእስር መዳረጋቸው አመልክቷል። የሰብአዊ መብት ኮሚሽኑ ሰላማዊ ሰልፎችን ለማጀብ የሚሰሩ የፀጥታ ሀይሎች ለግድያ የሚያበቁ መሳሪያዎችን መጣጠቅ እንደሌለባቸው አክሎ አሳስቧል። በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ የአውሮፓ ህብረት በክልሉ የተፈፀመውን ግድያ በአለም አቀፍ ገለልተኛ አጣሪ ቡድን ማጣሪያ እንዲካሄድበት ማሳሰቡ ይታወሳል። የህብረቱ ፓርላማም የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ላይ ያለውን አቋም እንዲያስተካክልና እርምጃን ለመውሰድ የሚያስችለውን የውሳኔ ሀሳብ ከወራት በፊት ማፅደቁ የሚታወስ ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ለኢትዮጵያ መንግስት ያቀረበውን ጥያቄ በተመለከተ እስካሁን ድረስ የተሰጠ ምላሽ የሌለ ሲሆን በርካታ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማትና ግለሰቦችም ተመሳሳይ ጥያቄን እያቀረቡ እንደሆነ ለመረዳት ተችሏል።
የተመድ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን በኦሮሚያና አማራ ክልሎች የተፈፀሙ ግድያዎችን በገለልተኛ አለም አቀፍ ታዛቢ ቡድን ማጣራት እንዲደረግበት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር እየተወያየ እንደሆነ ገለፀ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የዚምባብዌ የፀረ ሙስና ኮሚሽን በሀገሪቱ ሀብታሞች የገንዘብ ምንጭ ላይ ምርመራ ጀመረ። ምርመራው በሀገሪቱ ባለ ፀጎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር በማድረግ የሀብት ምንጫቸውን ማጣራትና እነርሱ የሚያንቀሳቅሱት ድርጅት ግብር መክፈል አለመክፈሉን የሚያካትት መሆኑን የፀረ ሙስና ኮሚሽነሩ ማታንዳ ሞዮ ተናግረዋል። በዚህ ሂደት መሰረትም ባለ ፀጎቹ የሀብት ምንጫቸውን በሀገሪቱ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበው አሳማኝ በሆነ መልኩ ማስረዳት ይጠበቅባቸዋል ነው ያሉት። ይህ ሳይሆን ቢቀርና የሀብት ምንጫቸውን በአግባቡ ማስረዳት ካልቻሉ ግን ያካበቱት ሀብት በመንግስት ይወረሳል ነው የተባለው። ባለሀብቶቹ ከፍርድ ቤት ከሙስና ነፃ ናቸው የሚል ማስረጃ ቢያገኙም እንኳን የገንዘብ ምንጫቸውን አሳማኝ በሆነ መልኩ ካላስረዱና ማስረጃ ካላቀረቡ ሀብት ንብረታቸው ይወረሳልም ተብሏል። የሀገሪቱ ፀረ ሙስና ኮሚሽን ባለፈው የፈረንጆቹ አመት ሀምሌ ወር ላይ ይህን የሀብት ምንጭ የማጣራት ሂደት እንዲያከናውን ስልጣን ተሰጥቶታል። ሀገሪቱ ለአመታት በከፋ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ ትገኛለች። የሀገሬው ዜጎችም ሙስና እና የተበላሸ አሰራር ባስከተለው የኑሮ ጫና ምክንያት ተቃውሞ እያሰሙ ነው። በሀገሪቱ ለኮሮና ቫይረስ በሚል የተካሄደው የመድሀኒትና ቁሳቁስ ግዢም ለሙስና የተጋለጠ ነበር ተብሏል። ከዚህ ጋር ተያይዞም የሀገሪቱ ጤና ሚኒስትር ኦባዲያህ ሞዮም ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ክስ ቀርቦባቸዋል። በዚምባብዌ ስልሳ ሶስት በመቶው የሀገሬው ዜጎች ከድህነት ወለል በታች ሲገኙ ሀያ ሶስት በመቶ ህፃናት ደግሞ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ካስቀመጠው የህፃናት እድገት መለኪያ በታች መሆናቸውን መረጃዎች ያመላክታሉ። ምንጭ፡ ቢቢሲ
ዚምባብዌ በሀገሪቱ ሀብታሞች የገንዘብ ምንጭ ላይ ምርመራ ጀመረች
በሳውዲ ንጉስ ጥብቅ ትእዛዝ በተጀመረው የፀረሙስና ማፅዳት ዘመቻ ሽህ መሀመድ ሁሴን አልአሙዲ መታሰራ ቸውን ከሳውዲ መንግስት በወጣ መረጃ አላረጋገጥኩም ። መታሰራቸው ግን በተለያዩ ታዋቂ አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሀንን ጨምሮ የአረብ መገናኛ ብዙሀን ዜናውን በሰፊው በዝርዝር እየተዘቡት ነው በሪያድ የጀርመን ራዲዮ ዘጋቢ ጋዜጠኛ ስለሽ ሽብሩ ምንጩን ባይጠቅስም የሸሁን በሪያድ መታሰር አረጋግጧል ።እንደኔ እንደኔ መረጃዎችን ቀስ ብሎ ማጣራትና ማረጋገጥ ይገባል። ይህ መሰሉን ከፍተኛ የፀረ ሙስና እስር በሚመለከ ት የሚወጡ መረጃዎች ከሳውዲ መንግስት መረጋገጥ ይኖ ርባቸዋል ። ከሳውዲ መንግስት መረጃ ባለፈ እስሩን ለማረጋ ገጥ በስራ ቦታዎችን ከቅርብ ሰዎቻቸው የሚገኙ መረጃዎች ግብአት ሊሆኑ የሚችሉበት አጋጣሚ ቢኖርም በሸህ መሀመ ድ ሁሴን አልአሙዲን መታሰር ዙሪያ የተጨበጠ መረጃ አላገኘሁም ። በእኔ በኩል እስካሁን ያለው መረጃ ይህው ነው ። በተረፈ የመረጃ አቀራረቤን በሚመለከት ለምትሰጡት አስተያየት አክብሮቴ ከፍ ነው። በተለይ በሳውዲ ከባቢ ዙሪያ በማቀርበው መረጃ ቅድሚያ የምሰጠው መረጃው ተአማኒ ከመሆኑ ላይ እንደሆነ ትረዱ ዘንድ ማስገንዘብ እወዳለሁ ቸር ያሰማንነቢዩ ሲራክጥቅምት ቀን አም
የመረጃ ግብአት በሸህ አልአሙዲን እስር ዙሪያ ነቢዩ ሲራክ
የመንግስት ባለስልጣናትን ሀብት በመጪው መስከረም ወር ለህዝብ በይፋ እንደሚያሳውቅ የፌደራል ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ናስታወቀ።የፌደራል ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ እዬልኝ ሙሉ አለም እንደገለፁት የኮሚሽኑ ተግባር ሀብትን መመዝገብ ብቻ ሳይሆን ፣ ሹመኛው ወይም ሰራተኛው ያስመዘገበው ሀብት ትክክል ነው ወይስ አይደለም የሚለው መረጋገጥ ጭምር እንደሆነ በመጥቀስ፤ መዝግቦ እና ማጣራት አድርጎ ያረጋጠውን ሀብት ለህዝቡ በግልፅ ይፋ ማድረግ በአዋጅ የተደነገገ ተግባሩ መሆኑን አስረድተዋል። እንደ ኮሚሽነርቱ ገለፃ፣ ህዝቡ በመንግስት ስልጣን ላይ ያሉ እና የመንግስት ሰራተኞች የሆኑ ሰዎችን ሀብት የማወቅ መብት አለው። ባለስልጣናቱና ተሻሚዎቹ ከገቢያቸው በላይ ከፍተኛ ሀብት አፍርተው ሲገኙ ለፍርድ ማቅረብ ከኮሚሽኑ ተልእኮዎች መካከል አንዱ ነው። ይህ ሀብትን አጣርቶ በይፋ ማሳወቅ በሁለት መንገድ ጠቃሚ መሆኑን ኮሚሽነሩ ያስረዳሉ። የመጀመሪያ ጠቀሜታው በሀሰት ሀብት ሳይኖራቸው እንዳላቸው ሲወራባቸው በነበሩ ተሿሚዎች ዙሪያ ያለውን እውነታ ግልፅ በማድረግ በአመራሮቹና በህዝቡ መካከል የነበረውን ጥርጣሬ ማጥፋት ሲሆን፣ሁለተኛ ጠቀሜታው ደግሞ ሀብትን በማከማቸትና በመደበቅ የተጋለጠን አመራር ህዝቡ እንዲታገለው ይረዳል። በዚህ መሰረት በመጀመሪያው ዙር የተደረገውና ሹመኞች ላይ ያነጣጠረው የሀብት ምዝገባና ቁጥጥር የፊታችን መስከረም ይፋ እንደሚሆን ያስታወቁት ኮሚሽነሩ፣ በሁለተኛው ዙር ደግሞ የመንግስት ሰራተኞችን ሀብት የመመዝገቡና የማሳወቁ ስራ እአራትንደሚቀጥል አሳውቀዋል። የባለስልጣናቱን ሀብት በኮሚሽኑ ድረ ገፅ ይፋ ለማድረግ ከአንድ የህንድ ድርጅት ጋር እየሰሩ መሆናቸውን ያመለከቱት ኮሚሽነሩ፣ ይህ ካልተሳካ ራሱን የቻለ መፅሄት እንደሚያዘጋጁ አስታውቀዋል።
የመንግስት ባለስልጣናትን ሀብት በመጪው መስከረም ወር ለህዝብ በይፋ እንደሚያሳውቅ የፌደራል ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ናስታወቀ።
መንግስት ሁለተኛውን የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ለመጀመር ታሳቢ ካደረጋቸው መስፈርቶች መካከል አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት በነጠላ አሀዝ ውስጥ ይሆናል የሚል ቢሆንም፣ በሀምሌ ወር የጀመረው ባለሁለት አሀዝ የዋጋ ግሽበት በነሀሴ ወርም ነጥብ ስድስት በመቶ ማደጉ ተገለፀ። ማእከላዊ ስታትስቲክስ ባለስልጣን ነሀሴ ሀያ ስምንት ቀን ሁለት ሺህ ሰባት አመተ ምህረት ያወጣው የነሀሴ ወር አገር አቀፍ የሸማቾች ዋጋ መመዘኛ ኢንዴክስ እንደሚያሳየው፣ የነሀሴ ወር አገር አቀፍ ጠቅላላ የችርቻሮ ዋጋ ኢንዴክስ ከሁለት ሺህ ስድስት አመተ ምህረት ነሀሴ ወር ጋር ሲነፃፀር ነጥብ ስድስት በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። ለዚህ ጭማሪ ምክንያት የሆኑት የምግብና አልኮል ያልሆኑ መጠጦች ነጥብ ሰባት ከመቶ፣ መጠጥ፣ ሲጋራና ትምባሆ ሰባት ነጥብ ስምንት በመቶ፣ ልብስና መጫሚያ ስምንት ነጥብ ዘጠኝ በመቶ፣ የቤት ኪራይ፣ የቤት መሳሪያ እቃዎች፣ ውሀና ኢነርጂ ነጥብ አንድ በመቶ ዋጋቸው በመጨመሩ እንደሆነ ኢንዴክሱ ያስረዳል። በተጨማሪም የቤት እቃዎች፣ የቤት ማስጌጫዎች፣ የቤት ቁሳቁስና የቤት ሰራተኛ ደመወዝ ሰባት ነጥብ ከመቶ፣ ህክምና አራት ነጥብ አንድ ከመቶ፣ ኮሙዩኒኬሽን መገናኛ ሁለት ነጥብ ሰባት ከመቶ፣ ሬስቶራንትና ሆቴሎች ሰባት ነጥብ ሰባት በመቶና ሌሎች እቃዎችና አገልግሎቶች አራት ነጥብ ሶስት ከመቶ ጭማሪ በማሳየታቸው አጠቃላይ የዋጋ ግሽበቱ ነጥብ ስድስት በመቶ ሊሆን መቻሉን ባለስልጣኑ ያስረዳል። በአገር አቀፍ ደረጃ ለታየው የ ነጥብ ስድስት በመቶ የዋጋ እድገት ምክንያት ከሆኑት መካከል ዋነኛው አብዛኞቹ የምግብ አይነቶች ጭማሪ በማሳየታቸው መሆኑን፣ የባለስልጣኑ የነሀሴ ወር የዋጋ መመዘኛ ኢንዴክስ ሪፖርት ይገልፃል። ከእነዚህም መካከል ስጋ አስር ነጥብ ሰባት በመቶ፣ ወተት፣ አይብና እንቁላል በ ነጥብ ዘጠኝ በመቶ፣ አትክልት፣ ጥራጥሬ፣ ድንችና ሌሎች የስራ ስር ምግቦች ሀያ ስድስት ነጥብ ሰባት በመቶ፣ ስኳር፣ ማርና ቸኮሌት ሁለት ነጥብ አራት በመቶ፣ እንዲሁም ሌሎች ምግቦች ስልሳ አንድ ነጥብ አራት ከመቶ እድገት በየኢንዴክሶቻቸው ላይ ማስመዝገባቸውን ሪፖርቱ ያስረዳል። በሌላ በኩል ዳቦና እህል ነጥብ አንድ በመቶና አልኮል ያልሆኑ መጠጦች ነጥብ አራት ከመቶ ቅናሽ አሳይቷል። የነሀሴ ወር ሁለት ሺህ ሰባት አመተ ምህረት የአገር አቀፍ ጠቅላላ ችርቻሮ ዋጋ መመዘኛ ኢንዴክስ ከሁለት ሺህ ስድስት አመተ ምህረት ነሀሴ ወር ሲነፃፀር በ ነጥብ ስድስት በመቶ ጭማሪ ለማሳየቱ አስተዋፅኦ ካደረጉት መካከል አዲስ አበባ ነጥብ አምስት በመቶ፣ አፋር ነጥብ አምስት በመቶ፣ አማራ አስር ነጥብ በመቶ፣ ቤንሻንጉል ጉሙዝ ዘጠኝ ነጥብ በመቶ፣ ድሬዳዋ ሶስት ነጥብ ዘጠኝ በመቶ፣ ጋምቤላ ስድስት ነጥብ ስምንት በመቶ፣ ደቡብ ክልል ስድስት ነጥብ ስምንት በመቶ፣ ሶማሌ ስምንት ነጥብ ሶስት በመቶና ትግራይ ስድስት ነጥብ በመቶ አስተዋፅኦ አድርገዋል። መንግስት ሁለተኛውን የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ግቦችን ሲያቅድ መነሻ ካደረጋቸው ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች መካከል አንዱ የዋጋ ግሽበት በነጠላ አሀዝ ስር መሆኑን ነበር። በእርግጥም የዋጋ ግሽበት ላለፉት ሁለት አመታት ባለሁለት አሀዝ እድገት ጭማሪ አድርጎ አያውቅም። ይሁን እንጂ በሁለት ሺህ ሰባት አመተ ምህረት ሀምሌ ወር የዋጋ ግሽበቱ ወደ ነጥብ ዘጠኝ በመቶ ከፍ ብሎ ነበር። ከስታትስቲክስ ባለስልጣን መረጃ ማየት እንደሚቻለው፣ የነሀሴ ወር የዋጋ ግሽበት መጠነኛ ቅናሽ አሳይቷል።
የነሀሴ ወር የዋጋ ግሽበት ነጥብ ስድስት በመቶ ማደጉን ስታትስቲክስ ባለስልጣን አስታወቀ
አዲስ አመት ደመና ጭጋጉ ሲገፍለት በተራው ሲፈካ ሰማይ ምድሪቱ በቀለማት ህብር ስትደምቅ ስትሞሸር ባደይ አትምጪ ይቅርብሽ ከኔ አትምጪ ነገን ሰንቀሽ እሰይ መስከረም ጠባ አዲስ ቀን ነው ብለሽ ይልቁን የውስጤ ዝናብ ሲያባራ የመንፈሴ ሰማይ ሲጠራ የልቤ አደይ ሲፈካ የተስፋ ፀሀዬ ስትበራ ያኔ ነይልኝ በሰኔ ነይልኝ ባምሌ ነሀሴው ነይልኝ ለእንቁጣጣሽ አዲስ ቀን አዲስ አመት ነው። ታዬ አስፋው፣ ሀጢሾ ሁለት ሺህ ስምንት መኖሪያ ቤት ውስጥ የገባው ፔንጉዊን በቁጥጥር ስር ዋለ በብዛት በደቡባዊ ንፍቀ ክበብ ውስጥ የሚገኙት ፔንጉዊኖች የሚኖሩት በውሀማ አካባቢዎች መሆኑ ይታወቃል። እንደ አሳና ሌሎች ባህር ውስጥ የሚገኙ እንስሳትና ነፍሳትን ይመገባሉ። በደቡብ አሜሪካ በሀምቦልት ግዛት ውስጥ የሚገኘው አንድ ፔንጉዊን ግን የተለመደውን ምግቡን ወደ ጐን ብሎ የሚበላ ነገር ፍለጋ ወደ አንድ መንደር አቀና። ምሽት ስለነበር ልብ ያለው አልነበረም። በአካባቢው ወደሚገኝ አንድ ቤትም ጐራ ይላል። ቢቢሲ እንደዘገበው የቤቱ ባለቤት ከወደ ማድቤታቸው የእቃ ካካታ መስማታቸው ሌባ ገብቷል የሚል ስሜት ነበር ያሳደረባቸው። በፍጥነት ወደ ማድቤታቸው ሲገቡ ግን ያልጠበቁት ነበር ያጋጠማቸው። ምግብ ፍለጋ ጐራ ያለውን ፔንጉዊን የአካባቢው ፖሊስ ክፍል ደርሶ ወደ ነበረበት መልሶታል። አነጋጋሪዋ ተሳፋሪ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ አካባቢ በአውሮፕላን በሚደረግ ጉዞ መንደገኞች የተለያዩ ነገሮች ያጋጥማቸዋል። አጠገባቸው ከተቀመጠ ሰው ጋር ቃል ሳይነጋገሩ በረራውን የሚጨርሱ፣ ቦታ የማይበቃቸው ሌላም ሌላም የተለመዱ ገጠመኞች ናቸው። ከኪንሳንቲ ወደ ኬንታኪ ይበር በነበረው አውሮፕላን የታየው ግን ከዚህ የተለየ ነበር። ዘ ቴሌ ግራፍ እንዳስነበበው ባለፈው ሰኞ ወደ ኬንታኪ ሲበሩ ከነበሩ መንገደኞች መካከል አንደኛው ከጐኑ ባለው መቀመጫ ላይ አሻንጉሊት አስቀምጧል። ሁኔታው ያስገረማት ሳራ ኖቪክ የተሰኘችው አንዲት ሴትም ስለ ሁኔታው በትዊተር ገጿ አሰፈረች። ተከታዮቿም ሰውየውን እንደሚያውቁት፣ ከዚህ ቀደምም ባርባራ በሚል ስም ያወጣውን ፎርጂድ ፓስፖርት በመጠቀም እንደ ጓደኛው ለሚቆጥራት ለአሻንጉሊቱ የአየር ቲኬት እንደቆረጠ፣ ሁኔታው የደህንነት ስጋት በመፍጠሩ ከፍተኛ ፍተሻ እንደተካሄደበትና ባርባራ አሻንጉሊቷ እንጂ ሌላ ሰው አለመሆኑን ደርሰውበት በዚህ እንደተቋጨ አስረዷት። ለሳራ መረጃውን ከሰጧት ተከታዮቿ መካከል አንደኛው የአሻንጉሊቷንና የሰውየውን ፎቶ በትዊተር ገጿ ላይ ለጥፎታል። በኮኬይን የተሞላ ቦርሳውን ፖሊስ እንዲያፋልገው የጠየቀ በአደንዛዥ እፅ የተሞላ ቦርሳው የጠፋበት የ አመት ወጣት፣ የጠፋ ቦርሳውን ፖሊስ እንዲያፋልገው በጠየቀበት ቅፅበት በቁጥጥር ስር ዋለ። የሲያትል ፖሊስ ዲፓርትመንትን ጠቅሶ ዩፒአይ እንዳሰፈረው፣ የጠፋውን የወጣቱን ቦርሳ ያገኘ ሰው፣ ቦርሳውን ለፖሊስ አስረክቦ ነበር። በቦርሳው ውስጥ አራት ትላልቅና ሀያ ሰባት ትናንሽ እሽግ ኮኬይን፣ ጥቂት ማሪዋናና፣ ሰዎች ከሱስ ወይም ከሌላ ህመም ጋር ተያይዞ ጭንቀት ውስጥ ሲገቡ ሊያነቃቃ የሚችል ሀምሳ እንክብል መድሀኒት፣ የ አመቱ ወጣት መታወቂያና የእጅ ስልክም ነበር። ቦርሳ ጠፍቶብኛል ብሎ ፖሊስን የጠየቀው ወጣትም፣ በአደንዛዥ እፅ አዘዋዋሪነት በቁጥጥር ስር ውሏል። በመጥፋት ላይ ያሉት የአለም ቅርሶች ዩኔስኮ በአያያዝ ችግርና በእድሜ ብዛት በመጥፋት ላይ የሚገኙ ዘጠኝ የአለም ቅርሶችን ዝርዝር አወጣ። ዘ ኢንዲፔንደንት እንዳቀረበው ስጋት ውስጥ የገቡት ቅርሶች የሚከተሉት ናቸው። በፍሎሪዳ የሚገኘው ኤቨር ግላድስ ናሽናል ፓርክ የቀድሞ የኢየሩሳሌም ከተማና ግንቦች በአሜሪካ የሚገኘው ብሌይዝ ቤሪየር ሪፍ ሪሰርቭ ሲስተም የግብፁ አቡ ሜና የኢንዶኔዥያው ትሮፒካል ሬይን ፎረስት ሄሪቴጅ ኦፍ ሱማትራ የጆርጂያው ባጋርቲ ካቴድራልና ጄላቲ ገዳም በፔሩ የሚገኘው ቻንቻን የአርኪዮሎጂ ዞን በማዳጋስጋር የሚገኘው አስናና ደን በሊቨርፑል የምትገኘው ማሪታይም መርካንታይል ከተማ ናቸው።
የዘንድሮው የመስቀል በአል ደመራ መስከረም ቀን ሁለት ሺህ ዘጠኝ አመተ ምህረት በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ሲከበር
ርእሰ መስተዳድር አገኘሁ ተሻገር በማእከላዊ ጎንደር ዞን በላይ አርማጭሆ ወረዳ እየተከናወኑ ያሉ የችግኝ ዝግጅትና የተፋሰስ ልማትን እየጎበኙ ነው።ባህር ዳር፡ ጥር አራት ሁለት ሺህ አመተ ምህረት አብመድ ርእሰ መስተዳድሩ በወረዳው በሹማራ ሎምየ ቀበሌ የባንብላ ተፋሰስ ልማትን ተመልክተዋል።ባለፉት አመታት በተከናወነው የተፋሰስስ ልማት ስራ ቡና፣ ማንጎ፣ ሙዝ፣ጌሾና ሌሎች ገበያ ተኮር አትክልትና ፍራፍሬ በአካባቢው አርሶ አደሮች እየለማ ይገኛል።አርሶ አደር ተስፋ ሀይሌና ብርሀን ፈንቅለው እንዳሉት እነርሱን ጨምሮ በርካታ አርሶ አደሮች ተግባራዊ ባደረጉት የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው።ርእሰ መስተዳድሩ የሁለት ሺህ አመተ ምህረት የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ስራንም በማእከላዊ ጎንደር ዞን በላይ አርማጭሆ ወረዳ በይፋ ያስጀምራሉ።
ርእሰ መስተዳድር አገኘሁ ተሻገር በማእከላዊ ጎንደር ዞን በላይ አርማጭሆ ወረዳ እየተከናወኑ ያሉ የችግኝ ዝግጅትና የተፋሰስ ልማትን እየጎበኙ ነው።
የታገቱ የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን አጠቃላይ ዝርዝር ሁኔታ የሚያሳይ መረጃ በቅረቡ ለህዝቡ ይፋ እንደሚደረግ የጠቅላይ ሚኒስቴር ፅህፈት ቤት አስታውቋል።በደንቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ግጭት መከሰቱን ተከትሎ ወደ ቤተሰቦቻቸው በመሄድ ላይ የነበሩ ተማሪዎች መታገታቸው ይታወሳል። እነዚህን ተማሪዎች ያሉበትን ሁኔታ የሚገመግም በፌዴራል ደረጃ በጠቅላይ ሚኒስትር የሚመራ ግብረ ሀይል ተቋቁሞ እየሰራ እንደሚገኝ የጠቅላይ ሚኒስቴር ፅህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ሀላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ከአሀዱ ቲቬ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል። አብመድም መረጃው ትክክለኛ መሆኑን አረጋግጧል።ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተልነው ነው ያሉት ሀላፊው ጉዳዩን አስመልክቶ ለሀብረተሰቡ መረጃውን ደረጃ በደረጃ መስጠት በሚገባ መልኩ ለመስጠት ቃል ብንገባም ሁኔታው ውስብስብ በመሆኑ ጊዜ ሊወስድ ችሏል ብለዋል።ጉዳዩ ውስብስብ ከመሆኑም በላይ በጉዳዩ ዘንድ ቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በርካታ ሰዎች የተሳተፉበት በመሆኑ ጊዜ ሊወስድ ችሏል ብለዋል አቶ ንጉሱ። ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያላቸው ሀያ ስምንት ሰዎች መያዛቸውንም በመግለፅ።ለዚህም በማሀበራዊ ድረ ገፅ የተሳሳተና ያልሆነ መረጃ ለህብረተሰቡ እየደረሰው ነው ያሉት አቶ ንጉሱ ታግቼ ነበር ተማሪ ነበርኩ ብለው በተለያየ መልኩ የቀረቡ ወደ አራት ያህል ተማሪዎች እንደተያዙ ጠቁመዋል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ ጉዳዩን ለማድበስበስ የሞከሩም ተይዘዋል ብለዋል።በፌዴራል ደረጃ እንዲሁም በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች የተቋቋመው ግብረ ሀይል ስራውን ሌት ተቀን እየተከታተለ እንደሚገኝ ገልፀውም ዝርዝርና የተሟላ መረጃውን በቅርቡ ለህዝቡ ይፋ እናደርጋለን ብለዋል።አቶ ንጉሱ እገታው እንዲከሰት ያቀዱ፣ ያቀነባበሩ መረጃ የሰጡና ያሰማሩ የተለያዩ ወገኖች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገላቸው ነው ብለዋል።
መንግስት በደምቢ ዶሎ በታገቱ ተማሪዎች ዙሪያ የደረሰበትን መረጃ በቅርቡ ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ ገለፀ።
አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና በማረጋገጥ ረገድ ትልቅ ተስፋ የተጣለበት መሆኑን የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ ገለፁ። የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ይፋዊ የማብሰሪያና ክልሉን የማስተዋወቂያ መርሀ ግብር በሆሳእና ከተማ ተካሂዷል። የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ ባስተላለፉት መልእክት፥ የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና በማረጋገጥ ረገድ ትልቅ ተስፋ የተጣለበት መሆኑን ገልፀዋል። ክልሉ የመልማት እና የማደግ ተስፋውን እውን ለማድረግ ስትራቴጂክ እቅድ በማዘጋጀት ወደ ተግባር መግባቱን ያነሱት አቶ አደም፥ የክልሉን ርእሰ መስተዳድር ጨምሮ በየደረጃው ያሉ የስራ ሀላፊዎች ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል። የአደረጃጀት ጉዳይን እንደ ግብ በመያዝ አግባብነት የሌላቸው እንቅስቃሴዎች መስተዋላቸውን የጠቆሙት ምክትል ፕሬዚዳንቱ፥ በዚህም አፍራሽ ተልእኮ ያላቸው አካላት በሚያደርጉት ጥረት አላስፈላጊ ዋጋ መከፈሉን አብራርተዋል። ከአደረጃጀት ጋር ተያይዞ የሚስተዋለውን ህገወጥ እንቅስቃሴ ሊታረም እና ሊገራ የሚገባው ጉዳይ እንደሆነ መናገራቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል። አደረጃጀት በራሱ ግብ አይደለም ያሉት ምክትል ፕሬዚዳንቱ ከሀገር እና ህዝብ ዘላቂ ጥቅም አኳያ በጥንቃቄ መምራት እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል። ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ ድረ ገፅ፦ ፌስቡክ፡ ዩትዩብ፦ ቴሌግራም፦ ትዊተር፦ በመወዳጀት ይከታተሉን። ኢንስታግራም፦ ቲክቶክ፦ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና በማረጋገጥ ረገድ ትልቅ ተስፋ የተጣለበት ነው አቶ አደም ፋራህ
ሯንዳ እና ህንድ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን የበለጠ ማጠናከር የሚያስችላቸውን ሰባት ማእቀፎች ላይ ተስማሙ።ስምምነቶቹ የመከላከያ፤ የንግድ እና የባህል ልውውጦችን እንደሚያካትቱ ለማወቅ ተችሏል።ሯንዳ እና ህንድ ከዚህ ቀደም የነበራቸውን ትብብር የበለጠ ለማተናከር ያስችላል የተባሉ ሰባት ጉዳዮች ላይ ከስምምነት መድረሳቸው ተነግሯል።የሯንዳው ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ እና የህንዱ ጠቅላይ ሚንስትር ናሬንድራ ሞዲ በሯንዳ ኡርግዊሮ መንደር ነው ስምምነቱን የተፈራረሙት።ጠቅላይ ሚንስትር ሞዲ ለሁለት ቀናት የስራ ጉብኝት ሯንዳ ሲገቡ በፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።ሁለቱ መሪዎች ያደረጉት ስምምነት በሀገራቱ ዘንድ ያለውን የረጅም ጊዜ ወዳጅነት እና ትብብር ወደ ላቀ ደረጅ ከፍ ለማድረግ እንደሚጠቅምም ነው የተመላከተው።ሀገራቱ የተፈራረሟቸው ስምምነቶች እንደ አውሮፓውያኑ ዘመን አቆጣጠር ከሁለት ሺህ እስከ ሁለት ሺህ ሀያ ሁለት የሚዘልቁ ሲሆን የመከላከያ፤ የንግድ እና የባህል ልውውጥ ትኩረታቸው ማድረጋቸው ታውቋል።ከዚህ በተጨማሪ የሁለቱ ሀገራት ባለስልጣናት በግብርና፤በእንስሳት ሀብት ልማት፤በቆዳና ሌጦ ኢንዱስትሪዎች ላይም በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል።ፕሬዝዳንት ካጋሜ ከስምምነቱ በኋላ በመሰብሰቢያ አዳራሽውስጥ ለነበሩ ጋዜጠኞች እንዳስታወቁት ማእቀፎቹ ላይ የተደረሰው መግባባት ሀገራቱ ቅድሚያ ለሚሰጧቸው የልማት አቅጣጫዎች መሳካት ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው አንስተዋል።የሁለቱን ሀጋራ ግንኙነት የበለጠ ለማጠናክር በማሰብ ህንድ በሯንዳ ኢምባሲዋን ለመክፈት ወስናለች። ሁለቱ አገራት እየሄዱበት ያለችውን ዲፕሎማሲያዊ መንገድ የሯንዳው ፕሬዝዳንት ፖልካጋሜ አድናቆት ችረውታል።የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር እና የሯንዳው ፕሬዝዳንት ፖልካጋሜ የአፍሪካ ሀገራት በነፃ የንግድ ቀጠና ለማስተሳሰር የሚደረገው ጥረትን ህንድ ማዋእለ ንዋይ በአፍሪካ እንድታፈስ የሚያበረታታ መሆኑን ለጠቅላይ ሚንስትር ሞዲ ተናግረዋል።ሞዲ በበኩላቸው ሀገራቸው ልምድ ባካበተችባቸው የቴክኖሎጂ፣ የመሰረተ ልማት ግንባታ እና የፋይናንስ አስተዳደር ዘርፎች ልምዷን ለሯንዳ ለማካፈል ዝግጁ መሆኗን ገልፀዋል።ጠቅላይ ሚንስትሩ አክለውም ሯንዳ ጥሩ ውጤት እያስመዘገበችባቸው ነው ባሉት የግብርናና ገጠር ልማት ስራዎች ሯንዳ ከህንድ ልምድ መቅሰም እንዳላትም ጠቁመዋል።ይህ በሯንዳ የመጀመሪያ ነው የተባለለት የህንድ ጠቅላይ ሚንስትር ጉብኝት የመጣው የሯንዳው ፕሬዝዳንት ካጋሜ በቅርቡ ወደ ህንድ ማቅናታቸውን ተከትሎ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።የሁለቱ ሀገራት የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከተጀመረተበት እኤአ ከአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ዘጠኝ ጀምሮ የሁለቱ ሀገራ ትብብር በየአመቱ እድገት እያሳየ መምጣቱ ኦል አፍሪካን ዶት ኮም ይዞት የወጣው ዘገባ ያስረዳል።
ሯንዳና ህንድ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ተስማሙ
ቤልጂየማዊው ኢንተርናሽናል አድናን ያንዩዣይ የዘንድሮ ሲዝን የጀመረው ለማንቸስተር ዩናይትድ ጎል በማስቆጠር የታጀበ ጥሩ እንቅስቃሴን በማሳየት ቢሆንም በሆላንዳዊው አሰልጣኝ ሉዊ ቫንሀል ግን ከፒ ኤስ ቪ አይንደንሆቨን የገዙት ሜምፌስ ዴፓይን ውጤታማ ፉትቦልን ለማጉላት በመጓጓት ያንዩዣይን በውሰት ውል ወደ ቦሪሽያ ዶርትሙንዱ የመልቀቅ ውሳኔ ላይ ደርሰዋል። ያንን ውሳኔያቸውን በማስመልከት ቫንሀል በተደጋጋሚ በሰጡት መግለጫዎች ከጀርመን ቡንደስሊጋ ውድድር በመሳተፍ በቂ ልምድን አግኝቶ እንደሚመለስልኝ በመጓጓት ነው ቢሉም በተግባር ከታየው ለመረዳት ያስቻለው ግን የያንዣይ በውሰት ውል ማምረት ሶቱን አካሎች ማለትም ቦሪሽያ ዶትሙንድ ማንቸስተር ዩናይትድና ራሱ ተጫዋቹን ያልጠቀመ ሆኗል። ምክንያቱም ያንዩዣይ ለቦሪሽያ ዶርትሙድ የተሰለፈው በአራት ግጥሚያዎች ብቻ ነው። ከእነዚህ ውስጥ አንዱ ብቻ የቡንደስሊጋ ግጥሚያው ነው ሌሎቹ ሶስት ጨዋታዎችን ያደረገው በዩሮፓ ሊግ ውድድር ነው። የዶርትሙንዱ አሰልጣኝ ለያንዣይ በበቂ ግጥሚያዎች የመሰለፍ እድልን ያልሰጡበት ምክንያት የሚገልኑት ግጥሚያዎችን ለማድረግ የስነ ልቦና ጥንካሬአልታየበትም በማለት ነው። ይህ አባባላቸው በ አመቱ ቤልጅየማዊው ኢንተርናሽናል በቫንሀል ችሎታው ሙሉ እምነትን ባለማሳደሩ መጠነኛ የሆነ የመረበሽ መንፈስ እንደተፈጠረበት ነው ባሳለፍነው ሳምንት ውስጥ ግን ዶርትሙንድ የያንዩዣይን ለአንድ አመት የሚዘልቅ የውሰት ውልን ለማቋረጥ በመስማማት ሉዊ ቫንሀል ወደሚወደው ክለቡ ማንቸስተር ዩናይትድ መልሰውታል። ይህንን ተከትሎም የያንዩዣይ ወደ ኦልድትራፎርድ መመለስ ከጉዳቱ ይልቅ ጠቀሜታው የሰፋ እንደሚሆን በማመን አስተያየታቸውን የሚሰጡ ባለሙያዎች ተበራክተዋል። በተለይም የዛሬ ሁለት አመት ከማንቸስተር ዩናይትድ ፉትቦል አካዳሚ ወደ ዋናው ቡድን ለመሸጋገር የቻለው ቤልጅየማዊው ወጣት ወደ ኦልድትራፎርድ መመለሱ በአሁኑና በሲዝኑ መጨረሻ መካከል ለሉዊ ቫንሀል ቡድን የሚኖረውን ጠቀሜታዎችን የዴይሊ ሚረር የፉትቦል ተንታኞች ከዚህ በታች ባለው መልኩ ዘርዝረዋቸዋል። ጎል የማስቆጠር ተሰጥኦው ማንቸስተር ዩናይትድ የዘንድሮን ሲዝንን ያጋመሰው ከዚህ በፊት በነበረው በተለይ ሁኔታ በበቂ ጎሎችን የማስቆጠር ረሀብ ተፈጥሮበት ነው። ለዚህ አንዱ ችግሩ የቡድኑ የአጥቂና አማካይ ክፍል ተጨዋቾች የጎል ማስቆጠር ሙከራዎችን የማድረግ ድርጊትን እያጡ ሲመጡ መታየታቸው ነው። ይህ ዥ ችግራቸው ማንቸስተር ዩናይትድ በእስካሁኑ ሲዝን ባደረጋቸው የፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያዎች ጎሎቹ ብቻ እንዲኖሩት መንስኤ ሆኖታል። ያንዩዣይ ግን በሚፈጠሩለት ጎል የማስቆጠር እድሎችን ካለምንም ማመንታት ለመጠቀም ከርቀት ሳይቀር ጠንካራ ሹትን በመምታት ከፍተኛ ድፍረትን የተላበሰ ተጨዋች ነው። የሚያስገኘው ከፍተኛ ፍጥነት በሉዊ ቫንሀል ስር በማንቸስተር ዩናይትድ የማጥቃት እንቅስቃሴ በመታየት ላይ ያለው ችግሮች ውስጥ ከፍተኛ ፍጥነቱ በጣት አንዱ ነው። ይህንን ችግሩን ለመቅፈረፍ ሲሉም ቫንሀል በዘንድሮው ሲዝን ዝውውር መስኮት ፔድሮ ባርሴሎና ለመግዛት ተቃርበው ነበር። ሆኖም ግን ፔድሮ በመጨረሻው ሰአት ወደ ቼልሲ ማምራትን ምርጫው በማድረጉ ጥረታቸው ሳይሰምርላቸው ቀርቷል። ከዚህ አንፃር ሌላው ከፍተኛ ፍጥነትን የተላበሰ የማጥቃት እንቅስቃሴ ያለው ያንዩዠይን የውሰት ውሉን አቋርጦ እንዲመለስ ባደረጉበት ውሳኔያቸው ፔድሮን ሲያስፈርሙበት የቀሩበት ስህተታቸውን መጠነኛ የሆነ እርምትን የሚያስገኙለት እንደሚሆን ይታመናል። በተጋጣሚ ላይ የሚፈጠረው ጫና ያንዩዣይ በተፈጥሮው በተጋጣሚ ቡድን የተከላካይ መስመር ተሰላፊዎች ላይ የኳስ ቁጥጥርን ይዞ በመሮጥ ከፍተኛ ጫና እንዲፈጠርባቸው የማድረግ ተሰጥኦው ከፍተኛ ነው። ይህ ተሰጥኦው የክለቡ ደጋፊዎች በመነቃቃት ለቡድናቸው ለሙሉሀይሉ የማጥቃት ተነሳሽነት እንዲኖው የማያቋርጥ ድጋፍን እንዲሰጡት የሚያስገድዳቸው ይሆናል። ምክንያቱም ያንዩዣይ በከፍተኛ ፍጥነት የታጀበ ድሪብሊንጎችን በሚያደርግበት ወቅት በኦልድትራፎርድ ተደናቂ ድባብ እንዲፈጠር ምክንያት ሲሆን መታየቱ የተለመደ ነው። ለማንዩናይትድ ስኬት ያለው ተቆረቋሪነት ሉዊ ቫንሀል ከተተቹበት ጉዳዮች ውስጥ አንዱ ማንቸስተር ዩናይትድ በፉትቦል አካዳሚ ያፈራቸው ዳኒ ዌልቤክና ቶም ክሌቨርሌይን የመሳሰሉት የራሱ የሆኑ ተጨዋቾችን ወደ ሌሎች ከክለቦች እንዳይመሩ ያደረጉበት ተግባራቸው ነው። በአሁኑ ወቅት ግን ያንዩዣይን የመሰሉበት ተግባራቸው ከዚህ ወቀሳ ራሳቸውን ማዳን እንዲጀምሩ የሚረዳቸው እንደሚሆን ይታመናል። ደግሞም ቤልጅየማዊው ኢንተርናሽናል በማንቸስተር ዩናይትድ ደጋፊዎች በከፍተኛ ደረጃ የሚፈቀር ለክለቡ ስኬታማነት ከፍተኛ የሆነ የተቆርቋሪነት መንፈስን በመላበስ በእያንዳንዱ ግጥሚያዎችን ከፍተኛ በሆነ በማሸነፍ ወኔ የማድረግ ባህል ያለው በመሆኑ ነው። የቤልጅየማዊው ከፍተኛ የማሸነፍ ወኔ በዙሪያው ላሉት የቡድኑ ጓደኞች በድል የመነሳሳትን መንፈስን የሚፈጥርላቸው እንደሚሆን ይታመናል። ለማታ የሚሰጠው ጠቀሜታ ሉዊ ቫንሀል በስፔናዊው ኢንተርናሽናል ኋን ማታ ተደናቂ ኳሊቲዎችን በግራ ክንፍ በኩል እንዲሰለፍ በማስገደድ እያባከኑት ይገኛሉ። ምክንያቱም ለማታ ይበልጥ ተስማሚ የሚሆንለት ጨዋታ ሚና ከፊት አጥቂ ጀርባ ባለው ቦታ ወደመሀል ገብቶ የሚጫወትበት ነፃነትን የሚያገኝበት ነው። በአንፃሩ ያንዩዩይ የበለጠ ውጤታማ ግልጋሎትን የሚሰጠው በግራ ክንፍ በኩል ግጥሚያዎችን በመጀመር ወደ መሀል ሰንጥቆ በመግባት በጠንካራ ቀኝ እግሩ የጎል ማስቆጠር ሙከራዎችን የሚያደርግበት ነው። ከዚህ አንፃር የያንዩዣይ መመለስ የማንቸስተር ዩናይትድ ግራ ክንፍን በመረከብ ወደ ማታ በሚመርጠው የጨዋታ ሚና በመሰለፍ እድልን ፈጠሮለት ነፃ እንዲወጣ የሚረዳው እንደሚሆን ይታመናል።
የአድናን ያንዩዣይ መመለስ ለማንቸስተር ዩናይትድ የሚያስገኙለት ቁልፍ ጠቀሜታዎች
በአንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች አሸንፈናል ተቃዋሚዎች ባለፈው ሳምንት በተካሄደው የከተማ ምክር ቤቶች ምርጫ ኢህአዴግ ጊዜያዊ ውጤት በመጥቀስ በሁሉም ቦታዎች እንዳሸነፈ የገለፀ ሲሆን በምርጫው የተሳተፉ ተቃዋሚዎች በውጤቱ እርግጠኛ ባይሆኑም በጥቂት የአዲስ አበባ ምክር ቤት ቦታዎች የምናሸንፍ ይመስለናል ብለዋል። የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ፕሬዚዳንት አቶ አየለ ጫሚሶ ህዝቡ ጥሩ ድምፅ እንደሰጠን እናውቃለን። ውጤቱን በተመለከተ ግን የምርጫ ቦርድ ይፋ ካደረገ በኋላ የምናየው ይሆናል ብለዋል። አቶ አየለ አክለውም በአንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች እጩዎቻቸው አሸናፊ እንደሆኑ ነገር ግን የመጨረሻውን ውጤት በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች የሚወሰን ስለሚሆን የምርጫ ቦርድ መግለጫ መጠበቅ የግድ እንደሆነ ተናግረዋል።አቶ አየለ በሂደቱ ላይ የታዩ ብዙ ችግሮች እንደነበሩ ገልፀው ከነዚህ መካከል የንብ ምልክት ብቻ በየጣቢያው መቀመጡ እንዲሁም በድምፅ ቆጠራ ወቅት የእነሱ ታዛቢዎች እንዳይገኙ መደረጋቸው ተገቢ አይደለም ቅሬታችንን በወቅቱ ለምርጫ ቦርድ አቅርበናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ራእይ ፓርቲ ኢራፓ ፕሬዚዳንት አቶ ተሻለ ሰብሮ በበኩላቸው በምርጫው ውጤት እንዳልቀናቸው ማረጋገጣቸውን ጠቅሰው ፓርቲያቸው በምርጫው መሳተፉን ይበልጥ ከህብረተሰቡ ጋር እንዲተዋወቅ እንዳደረገው ገልፀዋል። የምርጫው አጠቃላይ ሂደትና ውጤት በተመለከተ ያላቸውን አቋምም በምርጫ ቦርድ ውጤቱ ይፋ ከተደረገ በኋላ እንደሚያሳውቁ አቶ ተሻለ ገልፀዋል። የመላው ኢትዮጵያ ብሄራዊ ንቅናቄ መኢብን ሊቀመንበር አቶ መሳፍንት ሽፈራው በአዲስ አበባ በሶስት የምርጫ ጣቢያዎች ቢያሸንፉም አጠቃላይ ውጤቱን ለማወቅ የምርጫ ቦርድን መግለጫ እንጠብቃለን ብለዋል።ኢህአዴግ በበኩሉ በአዲስ አበባ ሙሉ ለሙሉ የአሸናፊነት ድምፅ አግኝቻለሁ ብሏል። በኢህአዴግ ፅህፈት ቤት የአደረጃጀትና የአጋር ድርጅቶች ዘርፍ ሀላፊ አቶ ተመስገን ጥላሁን በሰጡት ማብራሪያ የምርጫው አጠቃላይ ውጤት የሚታወቀው በቦርዱ ይፋ ሲደረግ ቢሆንም አሁን ባለው ጊዜያዊ ውጤት ግን በሁሉም የምርጫ ወረዳዎች አሸንፈናል ብለዋል። ምርጫው ኢህአዴግ ባሰበው መንገድ ዲሞክራሲያዊ ሰላማዊና ፍትሀዊ ሆኖ ተጠናቋል ያሉት አቶ ተመስገን ነገ እሁድ የሚካሄደው የወረዳ ምርጫ ሲጠናቀቅና ምርጫ ቦርድ ውጤቱን ይፋ ሲያደርግ ምርጫውን በተመለከተ አጠቃላይ መግለጫ እንሰጣለን ብለዋል። በኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የአዲስ አበባ ቅፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ጌታሁን ገመድህን በበኩላቸው በምርጫው የተገኘው አጠቃላይ ውጤት ግንቦት ቀን አመተ ምህረት ይፋ ሲደረግ በአዲስ አበባ በየክልሉ የተገኘው ደግሞ ሚያዚያ ቀን አመተ ምህረት ይፋ እንደሚደረግ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል። ባለፈው ምርጫ ጠንካራ ተፎካካሪ የነበሩ ተቃዋሚዎች ራሳቸውን ከምርጫው ማግለላቸው ይታወቃል።
ኢህአዴግ በሁሉም የምርጫ ቦታ አሸንፌያለሁ ይላል
ለወትሮው ሁለቱ ቡድኖች በሚገናኙበት ጨዋታ ከፍተኛ ተመልካች ፣ ውጥረት እና የማሸነፍ ፍላጎት የሚኖር ሲሆን ዛሬ በይርጋለም ሁለገብ ስታድየም የታየውም ይኸው ነበር።የሲዳማ ቡና ደጋፊዎች ቡድናቸውን ለመደገፍ ወደ ስቴዲዮሙ መትመም የጀመሩት ገና ከማለዳ ጀምሮ ነበር ። ቁጥራቸው ጥቂት የማይባል የወላይታ ድቻ ደጋፊዎችም ክለባቸውን ለመደገፍ በስቴዲዮም ታድመው ነበር።የእለቱ አልቢትር ፌደራል ዳኛ ዳዊት አሳምነው የጨዋታውን መጀመር የፊሽካቸው ድምፅ ካሰሙበት ሰአት አንስቶ በመጀመርያዎቹ ደቂቃዎች ሲዳማ ቡና ከፍተኛ ጫና በመፍጠር በአዲስ ግደይና በትርታዬ ደመቀ አማካኝነት በተደጋጋሚ የወላይታ ድቻን የኋላ መስመር የፈተሹ ሲሆን ከሀያኛው ደቂቃ በኋላ ወላይታ ድቻዎች ጨዋታውን ለማቀዝቀዝ በሚመስል መንገድ የተለያዩ ቴክኒኮችን ተጠቅመው ጨዋታውን አረጋግተውታል። በዚህም በዛብህ መለዮ በስላሳ ዘጠኝኛው ደቂቃ ካደረገው የጎል ሙከራ ውጪ እምብዛም የተለየ ነገር ሳይታይ የመጀመርያው አጋማሽ ያለጎል ተጠናቋል።በሁለተኛው አጋማሽ ኬንያዊው አንጋፋ ኤሪክ ሙራንዳ ተቀይሮ ከገባ በኋላ የጨዋታው ልዩነት ፈጣሪ መሆን ችሏል። ሲዳማ ቡናም ሙሉ በሙሉ ጨዋታውን ተቆጣጥሮ የተጫወተ ሲሆን በተለይ ስልሳ ሶስት እና ሰባ አንድኛው ደቂቃ ላይ አዲስ ግደይና ኤሪክ ሙራንዳ የሞከሯቸውና የግቡ አግዳሚ የመለሰባቸው ኳስ ለብልጫቸው ማሳያ ነበሩ።ጫናቸውን አጠናክረው የቀጠሉት ሲዳማዎች ጥረታቸው በሰባ ዘጠኝኛው ደቂቃ ፍሬ አፍርቶ ኤሪክ ሙራንዳ በቀኝ መስመር ያሻገረውን ኳስ አዲስ ግደይ በግሩም ሁኔታ በግንባሩ በመግጨት የሲዳማን ወሳኝ የድል ግብ ከመረብ አሳርፏል። በዝምታ ተውጦ የነበረው ስታድየምም በደጋፊዎች ጭፈራ ተንጧል።ከግቧ መቆጠር በኋላ ወላይታ ድቻ የአቻነች ግብ ለማግኘት በዛብህ መለዮ እና ዳግም በቀለ አማካኝነት ሙከራዎች ቢያደርጉም ሳይሳካላቸው ቀርቷል። ጨዋታውም በሲዳማ ቡና አሸናፊነት ተጠናቋል። የአሰልጣኞች አስተያየትአለማየሁ አባይነህ የቡድኔ እንቅስቃሴ ጥሩ ነበር። ብልጫ እንደመውሰዳችን ከአንድ በላይ ጎል አስቆጥረን ማሸነፍ ይገባን ነበር። በመጀመርያው አጋማሽ ላይ የነበሩብንን ክፍተቶች አርመን የአጥቂ አማራጫችንን አስፍተን ኤሪክ ሙራዳን በማስገባት ያደረግነው ቅያሪ ተሳክቶልን ጨዋታውን በሚገባ ተቆጣጥረን አሸንፈን ወጥተናል። በሜዳችን ያለመሸነፍ ጉዟችንን ከአሁን በኋላም አስጠብቀን እንቀጥላለን ። በጨዋታው ላይ ድንቅ አቋሙን ላሳየኝ አዲስ ግደይ አከብሮቴ የላቀ ነው መሳይ ተፈሪ ማንንም መውቀስ አልፈልግም። ተጫዋቾቼ የሚችሉትን ሁሉ አድርገዋል። ለአሸናፊው ቡድን እንኳን ደስ አላቹ ማለት እፈልጋለው። ለቀጣይ ጨዋታም የዛሬው ሽንፈት ምንም አይነት ተፅእኖ ያደርግብናል ብዬ አላስብም። በቀጣዩ ጨዋታ ወደ አሸናፊነት እንመለሳለን።
የጨዋታ ሪፖርት የደቡብ ደርቢ በሲዳማ ቡና አሸናፊነት ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ ስምንት፣ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ ኢትዮ ቴሌኮም የአድቫንስድ አራትጂ ኤል ቲ ኤል አገልግሎት በደቡብ ምእራብ ሪጅን አስጀምሯል። ኢትዮ ቴሌኮም በአገልግሎቱ ጅማ፣ አጋሮ፣ በደሌ፣ ቦንጋ፣ ኮይሻ፣ መቱ፣ ማሻ ፣ ሚዛንና ቴፒ ከተሞች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ገልጿል። ኢትዮ ቴሌኮም በደቡብ ምእራብ ሪጅን የሚሰጠዉን የኤል ቲ ኢ ዘመናዊ አገልግሎት በጅማ ከተማ የምረቃ መርሀ ግብር አስጀምሯል። በምረቃ መርሀ ግብሩ የኢትዮ ቴሌኮም ስራ አስፈፃሚ ቴሌብርን በተመለከተ ለተሳታፊዎች ገለፃ ያደረጉ ሲሆን፥ ህብረተሰቡ ቴሌብርን በመጠቀም የእለት ከእለት እንቅስቃሴውን እንዲያቀል ጥሪ አስተላልፈዋል። የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሪት ፍሬህይወት ታምሩ በጅማ ከተማ በተካሄደው የአገልግሎቱ ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ላይ እንደተናገሩት በጅማ ከተማ እና በአካባቢው በተደረገው የኔትዎርክ ማስፋፊያ በአሁኑ ወቅት ከሶስት መቶ ሀምሳ ሺህ በላይ ደንበኞችን የኤል ቲ ኢ አድቫንስድ አገልግሎት ተጠቃሚ ይሆናሉ። በተጨማሪም ኩባንያው በተያዘው በጀት አመት አንድ መቶ ሶስት ከተሞችን የአራተኛ ትውልድ አራት ጂ ኤል ቲ ኢ አድቫንስድ አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ አቅዶ እስካሁን በመላው ኢትዮጵያ ሀምሳ ሁለት ከተሞችን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ማድረጉን አስታውቋል። በቀጣይም ኩባንያው በተመሳሳይ ሁኔታ የዳታ ትራፊክ እድገትና ፍላጎትን መሰረት ባደረገ መልኩ በእቅድ ይዞ እያከናወናቸው ያሉ የአራተኛ ትውልድ አራትጂ ኤል ቲ ኢ አገልግሎት የማስፋፊያ ስራዎችን በማጠናቀቅ በተለያዩ የክልል ከተሞች አገልግሎቱን በቅርቡ ለማስጀመር የሚያስችሉ ቅድመ ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል ብለዋል። በማህሌት ተክለብርሀን እና ሙክታር ጠሀ ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ ድረ ገፅ፦ ፌስቡክ፡ ዩትዩብ፦ ቴሌግራም፦ ትዊተር፦ በመወዳጀት ይከታተሉን። ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
ኢትዮ ቴሌኮም የአድቫንስድ አራትጂ ኤል ቲ ኢ አገልግሎት በደቡብ ምእራብ ሪጅን አስጀመረ
የኦሮሚያና አማራ ክልሎችን መጎብኘት አልቻለም በኢትዮጵያ ጉብኝነት ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ዘይድ ራኢድ፤ በሀገሪቱ የሰብአዊ መብት ይዞታ ላይ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር የተወያዩ ሲሆን በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የታሰሩ የተቀዋሚ ፓርቲ አመራሮችንም ማነጋገራቸው ተጠቁሟል።ኤዴፓ፣ ሰማያዊና መኢአድን ጨምሮ የኢህአዴግ ተወካይ ባሉበት ከ ፓርቲዎች ጋር የተወያዩት ኮሚሽነሩ፤ በሀገሪቱ የሰብአዊ መብት አጠባበቅ፣ በሙስና እና በሚዲያ ነፃነት ጉዳይ ላይ የቀረበላቸውን አቤቱታ ካዳመጡ በኋላ ችግሮቹን ከጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለ ማርያም ደሳለኝ ጋር እንደሚያዩባቸው አስታውቀዋል። ሰማያዊ ፓርቲን ወክለው የተሳተፉት አቶ አበበ አከሉ ለአዲስ አድማስ ስለ ውይይቱ በሰጡት መረጃ በተለይ በቅርቡ በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን የቀረበውን ሪፖርት ተቀዋሚዎች እንደማይቀበሉት፣ በአመፅና ተቃውሞው መነሻ ከሰባ ሺህ በላይ ሰዎች በጅምላ መታሰራቸውንና ለአራት ወራት የተራዘመው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅም ሀገሪቱን እየጎዳ መሆኑን ማስረዳታቸውን አስታውቀዋል። በሀገሪቱ ሙስና የከፋ ደረጃ ላይ መድረሱንና ሀገሪቱን ወደማትወጣው አዘቅት እየከተታት መሆኑን መግለፃቸውን ጠቁመው በውይይቱ የተገኙት የኢህአዴግ ተወካይም ችግሩ ቢኖርም መንግስታቸው ለማሻሻል እየሰራ መሆኑን ማሰረዳታቸውን አቶ አበበ ጠቁመዋል።በሀገሪቱ ነፃ ፕሬስና የጋዜጠኝነት ሙያ አደጋ ላይ መውደቁን፣ ጋዜጠኞች እንደሚታሰሩና የፕሬስ ነፃነት እንደማይከበር ለኮሚሽነሩ እንደተብራራላቸው ተጠቁሟል። የተቀዋሚዎችን ሀሳብ ያዳመጡት ኮሚሽነሩ፤ እኛ እናንተን እንረዳችኋለን እንጂ በሀገራችሁ ጉዳይ ጣልቃ አንገባም፤ የሀገራችሁ መፍትሄ በእናንተው እጅ ነው። የሚል ሀሳብ ማቅረባቸውንና በተነሱት ችግሮች ላይም ከሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር እንደሚመክሩበት ቃል መግባታቸውን አስረድተዋል። ፓርቲዎቹ ከኮሚሽነሩ ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ መድረክ ጥሪው በአግባቡ ስላልደረሰኝ አልተገኘሁም ብሏል። በሌላ በኩል ኮሚሽነሩ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤትን የጎበኙ ሲሆን አንድ ከፍተኛ የተቀዋሚ ፓርቲ አመራር ማነጋገራቸውን የጠቆሙት ምንጮች፤ ያነጋገሩት የፓርቲ አመራር የኢፌኮ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ በቀለ ገርባ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።ኮሚሽነሩ ለጋዜጠኞች ስለ ጉብኝታቸው በሰጡት መግለጫ፤ በቅርቡ በተቃውሞና ግጭት ውስጥ የነበሩትን በአማራና በኦሮሚያ የሚገኙ አካባቢዎችን ለመጎብኘት እድል አለማግኘታቸውን አስታውቀዋል።
የተመድ የሰብአዊ መብት ኮሚሽነር በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የታሰሩ የፓርቲ አመራሮችን አነጋግረዋል
አዲስ አበባ፣ ጥር ስላሳ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ አምስትኛው የብስክሌተኞችና የእግረኞች ቀን በመላዉ የሀገሪቱ ከተሞች ተከበረ። የትራንስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር የኋላሸት ጀመረ በአዲስ አበባ ከቤቴል ሚካኤል አንፎ ስላሴ በተካሄደዉ መርሀ ግብር ተገኝተው እንዳሉት የትራፊክ አደጋን አሳሳቢነት ከግምት ውስጥ በማስገባት የእግር ጉዞና የብስክሌት ትራንስፖርትን ለማበረታታት ከጳጕሜን እስከ ጳጉሜን እንደርሳለን በሚል መሪ ሀሳብ የተጀመረውን ንቅናቄ በማስቀጠል ዛሬ ለአምስትተኛ ጊዜ በአገር አቀፍ ደረጃ በመከበር ላይ ነው። ሚኒስቴሩ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሞተር አልባ የትራንስፖርት ስትራቴጅን በመተግበርም የትራንስፖርት አማራጮችን በማስፋት ተግባራዊ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ገልፀው ብዙሀኑን የማህበረሰብ ክፍል ተደራሽ እና አሳታፊ የሚያደርግ ጤናማ የትራንስፖርት አማራጭችን የእግር ጉዞ፣ የብስክሌት እና በካይ ያልሆኑ ትራንስፖርቶችን መጠቀም ሊበረታታ ይገባል ብለዋል። ሚኒስትር ዴኤታዉ የሀገሪቱ ከተሞች ለእግረኞችና ሳይክል ተጠቃሚዎች ምቹና ንፁህ መንገዶችን ማዘጋጀት እንዳለባቸው ተናግረዋል። ህብረተሰቡ ደግሞ መንገዶች የሰዎች ሰላማዊ መገናኛ መድረኮች መሆናቸውን በመገንዘብ ለመንገዶች ምቾት፣ደህንነትና ንፅህና በመረባረብ የሞተር አልባ ትራንስፖርት ስርአት በአገራችን ይበልጥ ተጠናክሮ እንዲስፋፋ የበኩላችንን እንወጣ ሲሉ መልእክት ማስተላለፋቸውን ከትራንስፖርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ የፋና ድረ ገፅ ይጎብኙ፤ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገፃችን ይወዳጁን ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
አምስትኛው የብስክሌተኞችና የእግረኞች ቀን ተከበረ
እንዴት ሰነበታችሁሳ ሀሳብ አለን ነገሮች መለዋወጣቸው ካልቀረ ለ አራድነት ደረጃ ይውጣልን። ተቸገርን እኮ እኔ የምለው አለ አይደል የ አራድነት የሶስት ወር ስልጠና ምናምን ተጀመረ እንዴ እንደዛ ከሆነ እውቅና የሌላቸው አሰልጣኞች በዝተዋል ማለት ነው ቂ ቂ ቂ እኔ የምለው እነ እንትና የዘንድሮው አራድነት እናንተን አይመለከትም። አሀ እንዴት ብሎ ደረጃ ይውጣ በምን መለኪያ አስር ብር በሚመስሉ የሎተሪ ትኬቶች ዶሮ ማነቂያን ያመሳችሁት እኮ ዘንድሮ አራድነት ሳይሆን ህገ ወጥ የምናምን ዝውውር አይነት ነው። እናማ ለእናንተ አራድነትማ እንዴት ብለን ደረጃ እናውጣ አሁን ለምሳሌ አለ አይደል ፀጉሩን መሀል ለመሀል ከፍሎ ኤልቪስ ካላላችሁኝ ወዮላችሁ የሚለውን ደረጃ ስንት ልንለው ነው ባይሆን የዛኛው ዘመን አራድነት በአለም ታሪካዊ ቅርስነት እንዲመዘገብ ለዩኔስኮ ደብዳቤ የማናቀርብሳ ስሙኝማ እንግዲህ ጨዋታም አይደል የዘንድሮውም አራድነት መአት የሚያስቸግር ነገር አለው። ጠዋት አንድ ሰአት ላይ ያደረገውን የፀሀይ መከላከያ መነፅር፤ ማታ ሶስት ሰአት ላይ አጥልቆ ዲምላይት ቡና ቤት የሚገባውን ሸላይ ምን ልንለው ነው የአንተ እንኳን በልዩ ሁኔታ የሚታይ ነው ልንል ነው የምር ግን ምን ይመስለኛል መሰላችሁ በዚህ የ ስልጣኔ ዘመን በ ፈጣን አራድነት ከአፍሪካ አንደኛ ከአለም ሁለተኛ ያልተባልነው በተሸረበብን አለም አቀፍ ሴራ ነው። መቼም የሴራ ንድፈ ሀሳብ ን እንደኛ በደንብ የሚጠቀምባት የለም ብለን ነው። ስሚ፣ እስካሁን ድረስ የት ነው ያመሸሽው ጓደኛዬ አሟት እሷ ቤት ሄጄ መሸብኝ ሄድኩባት ያለቻትን ጓደኛዋን ከአርባ አምስት ደቂቃ በፊት አውቶብስ ስትጋፋ ስላየናት የሰጠችው ምክንያት ውሸት ይሆናል። ላይፍ አለ አይደል ኢንተረስቲንግ ሆነ ማለት አይደለም ሰስፔንሱ ን አስቡትማ ለቅሶ ቤት ነበርኩ ምናምን አይነት ሰበብ መስጠትም ይቻል ነበር። የምር ግን በቃለ ጉባኤ ምናምን ነገር አይስፈር እንጂ ሰልስት አድራለሁ እየተባለ፣ ታሪካዊውን ቀዶ ጥገና ሳይንስ ሳይደርስበት በፊት ስንት ነገር ላይመለስ ተበላሽቶ ቀርቷል አሁን፣ መጀመሪያ ነገር የት ነው ያመሸሽው ምናምን የሚል አራድነቱን አለ አይደል አፕግሬድ ያላደረገ ነው። እንደዛ ቢልም አንተ ማነህና ነው የት ነበርሽ፣ የት አመሸሽ የምትለኝ ቢባል ነው። ከወፈሩ ሰው አይፈሩ የሚል ነገር ነበር አይደል ዘንድሮ በ ተነፈሰ ሆድ ም የምንወፍር አለን። ስሙኝማ የውፍረት ነገር ካነሳን አይቀር ብዙ ቀዳዳ ያለው ቀበቶ ያስፈልገናል። ፍሌክሲብል እንደሚሉት አይነት ማለት ነው። ምናልባት እኮ ክብደት ልጨምር እችላለሁ የሚል ስጋት ቀርቷላ ወይም ከቀረብን ቀበቶው እንደ ጎል መረብ በርከት ያሉ ቀዳዳዎች ይኑሩት በየሁለት ወሩ ምስማር ከመፈለግ ያድነናላ በነገራችን ላይ አንተ፤ ሙክት አክለህ የለም እንዴ ማለት አድናቆት ሊሆንም፣ ላይሆንም ይችላል። በአንድ በኩል አለ አይደል ተመችቶሀል፣ ደልበሀል፣ ምን ተገኝቶ ነው በሌላ በኩል ወደ ላይ ጠጋ ብለህ ዝግ ዘጋህ ወይ ማለት ሊሆን ይችላል። እናላችሁ ስለ አራድነት ስናወራ ቀደም ሲል መገን የአራዳ ልጅ እነ ድንጋይ ኳሱምን ጊዜ ተጩሆ ምን ጊዜ ደረሱየሚሏት ነገር ነበረች። መጯጯህ እንደ ልብ ነበራ እሪ በከንቱ አካባቢ ወዳጆቻችን ሜሞሪው እንዴት ነው የምር እኮ ይባል የነበረው እንግዲህ መሸላቸው መጯጯሀቸውን ጀመሩ ሳይሆን አለ አይደል ዛሬ ምነው ፀጥ እረጭ አለ ባሻ ወልዴ ችሎት ሰላም አይደለም እንዴ አይነት ነገር ነው። እነ ድንጋይ ኳሱ ብሎ ቸስ ማለት ምን የሚሉት አራድነት ነው ለሚሉ መልስ ያላችሁ በቴልገራም ምናምን ላኩልንማ የምር እኮ እንግዲህ ጨዋታም አይደል ያኔ ቦዲ ቢልደርነት ከዱባይ ከምናምን የሚመጣ ኪኒን ባልነበረበት ዘመን፣ ዝም ብሎ ጡንቻ ቢፈረጥም ምን ዋጋ አለው ወሬው እኮ በቃ ይህ ልጅ ያለመደባደብ ሌላ ስራ የለውም አይነት ሳይሆን እናቶች እንኳን ብቻ እንዲህ ሽቅብ ብድግ አደረገውና መሬት ላይ ጧ ነው ያደረገው አይ ጀግና አይነት ነበር የሚሉት። ተደብድቦ የመጣ ልጅ እኮ ከሰው በመጣላቱ ሳይሆን ተደብድቦ በመምጣቱ ከአባቱ ተጨማሪ ጥፊና ኩርኩም ይገጥመው ነበር እናማ እነ ድንጋይ ኳሱ መባል እንደ ዘንድሮው ቪአይፒ ነገር ማለት ነው። እኔ የምለው እነ ድንጋይ ኳሱ አራዶች፣ ያ የካውቦይ ፊልም ትዝ አይላችሁም ቴክሱ አንድ ሀምሳ ምናምን ሬድ ኢንዲያን ሲፈጅ ያጨበጨብነው ማጨብጨብ ያኔ ደግነቱ ጄኖሳይድ ምናምን የሚባል ነገር አልነበረማ ኮሚኩ ነገር እኮ አለ አይደል ሽጉጥዬው የሚጎርሰው ስድስት ጥይት ብቻ ነው እናላችሁ ቴክሱ አንድም ጊዜ መልሶ ሳያጎርስ አስራ ሰባቱን ይረፈርፋል። አሀ ቻርለስ ብሮንሰን ወይም ጃክ ፓላንስ ይቺን ካልቻሉማ፣ ወደ ሰማይ ተኩሰው ነገርዬዋ በፊት ለፊት ሳይሆን በጀርባ ዞራ ሬድ ኢንዲያኑን አለ አይደል ጠብ ካላደረገችማ ቂ ቂ ቂ ምኑን ቴክስ ሆኑ ስሙኛማ እኛ የጎረቤቷ ሴትዮ ትዝ አይሏችሁም እሳቸው ሴትዮ ግን በሆነ ባልሆነው ጭናችሁ ስር ገብተው የሚመለዝጓችሁ ለምን ነበር አሀ ካልጠፋ የአካል ክፍል እጃቸውን ለምን ጭናችሁ ውስጥ እንደሚወሽቁ እስከ ዛሬ ገብቷችኋል የምር ግን ያን ጊዜ እንኳንም ተደብቀን አንተን የምናይበት ዩቲዩብ ምናምን አልነበር። ጉድ ይፈላ ነበራ ድምዳሜ ላይ ይደረሳላ እትዬ እንትና ጭኔ ስር የመዘለጉኝ ሊቀጡኝ አስበው ሳይሆን ምልክት ሊሰጡኝ ነው አይነት ውሳኔ ላይ ይደረሳላ ኸረ እንኳንም ዩቲዩብ አልኖረ ይሄኔ ሁለት መቶ ሚሊዮኗን ተጠግተን ለኪሎ ቲማቲም ብር በማዳበሪያ እየሞላን እንሄድ ነበር።ሚኒባስ ታክሲ ውስጥ ነው። አንዷ ልጅ ከረዳቱ ጋር ትጋጫለች። ጭቅጭቃቸው መልስ አልሰጠኸኝም፣ ሰጥቼሻለሁ ነበር። ልጅቱ የምትፈልግበት ስፍራ ደርሳ ስትወርድ ምን ብትል ጥሩ ነው በአንተ ቤት አራዳ መሆንህ ነው በየቦታው ቀሽም አራድነት ይገጥማችኋል። በቀደም የሆነ ቀን ረፋድ ላይ ነው አራት ኪሎ አካባቢ አንድ ትልቅ የአደጋ ጊዜ መኪና እየከነፈ ነበር። ታዲያ ከሹፌሩ ጀርባ የነበሩት ሰዎች ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ዘፈን አይሉት ምን ብቻ ይጮሁ ነበር የሆነ ቀሽም አራድነት እነዛ ሰዎች በዛን ሰአት ስራ ላይ ነበሩ እኮ ልክ ቢሮ ውስጥ እንዳሉ ሰዎች ነበሩ እኮ ይህ አራድነት ምናምን ሳይሆን ስርአት አለማክበር ነው።ስሙኝማ እኔ ኪስ ያለው ሱሪ አድርጌም አላውቅ፣ አልወድም ሲል የነበረው ሰው ዋሌቴን ሱሪ ኪሴ ውስጥ ረስቼው ስለመጣሁ መቶ ብር ታበድረኛለህ አይነት ቅሽምና ጥግ የደረሰ የ ቶክ ሾው አይነት አራድነት ቂ ቂ ቂ ስታዩ የድሮ አራድነት ቅሪተ አካል ይፈለግልን ለማለት ምንም አይቀራችሁ።ከዚህ በፊት ያወራናት ነገር ሲኒማ ቤት ነው። ውጪ ተመልካቾች ሲኒማ ቤት ሲገቡ ካፖርታቸውን ተቀብለው የሚያስቀመጡ አስተጋጆች አሉ። እናም ካፖርቱን ቀበል ሲያደርግ ፍራንክ ጣል ይደረግለታል። አንድ ጊዜ ልብ አንጠልጣይ የሚባል የወንጀል ነክ ፊልም ለማየት ባልና ሚስት ይገባሉ። ሚስት ካፖርቷን ለአስተናጋጁ ትሰጥና መንገዷን ትቀጥላለች። የተለመደው ቲፕ ጉርሻ አልነበረም። አስተናጋጁም ተበሳጨ፤ ወደ ሴትየዋ ጠጋ አለና በጆሮዋ ሴትየዋን የሚገድላት የቤቱ አገልጋይ ነው አላትና አረፈው። ከዛ በኋላ ፊልሙን ማየት አያስፈልግም። አራዳ አስተናጋጅ እንዲህም ያደርጋል ማለት ነው ከአራዳ ልጅ ጋራ በአንድ አብረው ሲሄዱቢያገኝም ያበላል ቢያጣም ያዝናል ሆዱይቺኛዋ አራድነት እንደገና ሪሳይክል ሳይደረግ ብትመለስልን አሪፍ ነው ግራ የተጋባነው መተዛዘን የሚሉት ነገር እየጠፋ ነውና ደህና ሰንብቱልኝማ
ቢያገኝም ያበላል ቢያጣም ያዝናል ሆዱ
በአሰፋ አደፍርስ አገሬ ኢትዮጵያ ማን ይሆን ወገንሽ የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ ሲበላሽ፣ ታዛቢ ያጣሽ ወገን የራቀሽ፣ መከራና ችጋር ተታውሮሽ ደረስኩልሽ የሚል ወገን ያጣሽ፣ የሰው ልጅ በገንዘብ ተውተብትቦ ግርማሽን ቀንሶ እንዳልሆነ ሆኖ ሊያዋርድሽ ደፋ ቀና ሲል ማየቱ አልገረመሽ ዋ አንቺ አገር ስንቱን አየሽ ስንቱንስ አሳለፍሽ አገሬ ኢትዮጵያ ሁልጊዜ ተስፈኛ፣ ወደቀች ጠፋች ሲሏት በተአምር የምትነሳ፣ ለጠላት የማትመች በእግዜር ጥበብ ነዋሪ፣ ሁሌም በአምላክ ፍቅር የተመላች ንፅህት ውድ አገሬ አይዞሽ በሀብት በገንዘብ የማንደለል ልጆችሽ አለንልሽ፣ በአለም አደባባይ ስምሽን ለማንሳት ወደኋላ የማንል ቆራጥ ልጆችሽ አለንልሽ፣ ወገን ከወገኑ አክርሮ ሲጣላ፣ ወንድም ከወንድሙ እንደ አውሬ ሲባላ እሰየው ይላል ያ የጠላት ተኩላ። ይህች ማስታወሻዬ ግራ ለተጋቡ ወገን ዘመዶቼ ማመላከቻ ስትሆን፣ የጥንቷ አገሬ በወገን አልጠግብ ባይ ልጆቿ የመጨረሻ እድሏ ሆነና ለውርደት መዳረጓ እጅግ ስላበሳጨኝ መልእክቴን ለእኔ መሰል ተቆርቋሪዎች ለማድረስ ተነሳሳሁ። የቀደምቷ አገሬ የታሪክ መሰረት እናቴ አገሬ ጌታ ክርስቶስ የወደዳት በቅዱስ መፅሀፍ የተወደሰች፣ የቀለም ልዩነትን የማታስተናግድና የሁሉ እኩል አገር የነበረችና አሁንም ያለች፣ ወደፊትም የምትኖር አገሬ ኩራቴና መከበሪያዬ ናት። ዋ አንቺ ኢትዮጵያ ታሪክሽን አይተው ማገናዘብ አቅቷቸው በአዳዲስ አለማዊ አመለካከት ያሸበረቁ መስሏቸው፣ ያለማወቅ ክፉ በብልጭልጭ ነገር ተታልለው አንቺን እንደ ትንሽ ሲያዩሽ እንዴት ታዝበሻቸው ይሆን አይዞሽ እናቴ ኢትዮጵያ፣ የማስተማሪያ ሰነዱ በግምጃ ቤትሽ መኖሩን ሳይረዱ በከንቱ ደከሙ። ልናስተምራቸው ብንል ራሳቸውን በማታለል አዋቂ መስለው ሲዘባነኑ አየናቸው። ዋ ያለማወቅ ብለን ታዝበን ተውናቸው። ይህንን ካልኩ በኋላ ወደ ተነሳሁበት ወደ አዲሱ ትውልድ የታሪክ እንዝህላልነት ገብቼ፣ አዲሱን የታሪክ መሰረት ላስተምር ተነሳሁኝ። አይ ይቅርታ ማስተማር ሳይሆን ለማስገንዘብ ማለቴ ነው። ኢትዮጵያ ጥንታዊት የታሪክ አገር መሆኗን የአለም ታሪክ የመሰከረላት፣ በመፅሀፍ ቅዱስም በቀደምትነቷ የታወቀች ለመሆኗ ብዙ ማስረጃዎች እንዳሉ የአለም ሊቃውንት የሚመሰክሩት ነው። አዎን የማያውቁ እንዝህላሎች የሉም ለማለት አይደለም። የታሪክ ምሁር ነኝ ባይ አንዱ እንዲህ ብሎ የለ አፄ ምኒልክ ሲባል በወሬ ሰማሁ እንጂ ታሪኩን አላውቅም፤ እንዳለው፣ ራሱን ሳያውቅ የ ኛውን ክፍለ ዘመን ያልተገነዘበ ነውና ምን ይባላል ወገኖቼ የተነሳሁበት ዋናው አላማ ነባሯ አገሬ ባልሆኑ ሰዎች እጅ ወድቃ ታሪኳን ሲሸረሽሩ በማየቴ፣ ያልነበረ ታሪክ ሲፈጠር በመመልከቴና ይህንን ታሪክ ርቆ ሳይሄድና መስመሩን ሳይለቅቅ መስመር ለማስያዝ ያለብን ጊዜ አሁን ነው። መቼም አውቆ የተኛን ቢቀሰቅሱት አይሰማ እንዲሉ፣ ተስፋ ሳንቆርጥ እንቀስቅሳቸው። ማን የበላይ፣ ማን የበታች ሆነና ይሆን ይህ ሁሉ እሽቅድምድም ሁሉ ቃልቻ ማን ይሸከም ስልቻ ሆነና ነገሩ፣ የሚይዙትንና የሚጨብጡትን ያጡ ወገኖቼ ሲራኮቱ፣ ሲፋጁና ከእኔ በላይ ላሳር ሲሉ ማየቱ አልገረመን ይሆን ወንዙ ሞልቶ ተትረፍርፎ፣ መሬቱ የገበሬ ያለህ አገላብጠኝ፣ ጎልጉለኝ፣ ዝራብኝ፣ ተጠቀምብኝ እያለ አፉን ከፍቶ ተንሰራፍቶ፣ ወጣቱ ወገኔ አስተምሮ የሚመራው አጥቶ በየመንገዱ ሲንገላወድ፣ ወጣቷ ህፃን አዝላ ለልጄ የዳቦ መግዣ እያለች ስትለምን፣ እኔ በተንቀባረረ ቤት እየኖርኩ በቀን ሶስቴ እየበላሁ በተንቀባረረ አውቶሞቢል ስንሸራሸር ይህ ይሆን ከወገኔ የለየኝ ታዲያ ያለኝን ተካፍዬና የስራውንም መንገድ አሳይቼ ባልፍ፣ ሁሉም ወገኔ ለቁምነገር እንዲበቃ መንገድ ብከፍት፣ ዋሾነት፣ ሰብቅና ማታለል እርም መሆኑን ባስተምር፣ የምትለምነዋ የህፃኑ እናት ለልጇ የዳቦ መግዣ ገንዘብ የማግኛ መንገዱን ባስተምራት አይገባት ይሆን ለምን አይገባትም በፀሀይ መንከራተቱን ትመርጥ ይሆን የለም አትመርጥም። የእኔ የግል ጥቅምን በማስቀደም የአዙሮ ማየት አንገቴ ተጣምሞ እንጂ፣ እሷስ ወዲያውኑ ሰልጥና ስራ ላይ ውላ ልጇን እንደ ሌሎቹ ለመንከባከብ ጠልታ አይደለም። ወጣቱ ጎረምሳ የሚሰራው አጥቶ በየበረሀው ባክኖ መቅረቱ ሰው ነውና የሰው ፍላጎቱን ለማሟላት በመጓጓቱ፣ ወንድ ነውና ሁሉንም መሞከር አለብኝ በማለት በየጥሻውና በየበረሀው ሲንከራተት፣ ሴቷም ልጃችን በተመሳሳይ ስትውተረተር የባህር አሳ ነባሪ ቀለብ ሆነው እየቀሩ ነው። ዋ የእኔ ነገር ሰው መስዬ ቀና ብዬ ስራመድ አይገርማችሁም ግማሽ ጎኔ ራቁቱን፣ ግማሽ ጎኔ ለብሶና ተኮፍሶ ዋ ሰው መሆን። ለአምስት መቶ ሚሊዮን ህዝብ የምትበቃ ሀብታም አገር ተሸክሜ በየጊዜው ስለመን የአለም ምሁራን ምን ይሉኝ ይሆን ይደሰቱ ይሆን ወይስ ይታዘቡን ይሆን እርስ በርስ ስንጠፋፋ፣ ወንድሜን ያለ ርሀራኄ ስገድለውና ሲገድለኝ፣ ስልጡን ነን ባይ አፋጂዎቻችን እንዴት ይታዘቡን ይሆን ዋ አንቺ ያልታደልሽ አገር ምን ጎድሎሽ ይሆን ለዚህ የበቃሽው የአርሲው፣ የባሌው፣ የሶዶው፣ የአቢቹ ግምቢቹው፣ የወላይታው፣ የከምባታው፣ የካፋው፣ ወዘተ የዚህ ሁሉ ሽማግሌ ምነው ድምፁ ጠፋ ፈርቶ ይሆን ወይስ ተፀይፎ እነዚህን ሁሉ ማስታረቅ ነበር ስራቸው። ታሪክን አውግተው፣ ምሳሌን ደርድረው፣ እርቅ ካልወረደ የሞተ ሰው አስከሬን የመቃብር ጉድጓድ አይገባም ብለው፣ ከዳር ዳር መሬት ወድቀው፣ ለምነውና ተለማምነው ያስታርቁ የነበሩ የአማራውና የሲዳማው ጉምቱ ምን በላቸው ዘንድሮ ጥንትማ ሽማግሌ ጦር አይፈራ፣ ለንዋይ አይጓጓ፣ ለእውነት ይሞት ነበር። ዛሬስ፣ ዛሬማ አዛውንትም ሆኑ የእምነት ተጠሪዎች ስልክ በኪሳቸው ይዘው ባልነበሩበት ቦታ አለሁ ማለት ከጀመሩ ሰነባበተ እኮ። አይገርምም ግን አትዋሽ፣ አትስረቅና አትጣላ የሚለውን የሚሰብኩ መጥፋታቸው የአየር ንብረት ለውጥ ይሆን እንዲህ ያዳከማቸው መምሩም ሆኑ ሽማግሌው ወደ ጥንቱ ይመለሱ፣ ስልኩንም ይጣሉት ከኪስዎ። እኛንም ይገዝቱን በነበረው ስርአታችን፣ እባካችሁ እንመለስ ወደ ልቦናችን። በሰው ታሪክና ወግ አንኩራራ ይብቃን እባካችሁ። ነባር ቋንቋዎቻችንን ንቀን ምነው በሰው ቋንቋ መንተባተብን መረጥን ዋ ያለማወቅ የዘጠኝ መቶ አመታት ቋንቋ ተከብሮ የሶስት ሺህ ሲናቅ ራሴን በጣም ጠልቼ ሌላውን ወደድኩኝ ብዬ ስመፃደቅ። ወገኖቼ ተው በራሳችን እንመካ፣ እንኩራራ፣ የሰው ወርቅ አያደምቅምና። የቤቱን አይናማ እንጀራ ጥሎ የጎረቤቱን አይን የለሹን ጥፍጥፍ እንጀራ እንደሚያደንቅ ወስላታ አንሁን። በራሳችን እንኩራራ፣ እንኮፈስ። ነገር ግን ሰርተን እንጂ ባልሰራነው በባዶ ሜዳ ማለቴ እንዳልሆነም ተገንዘቡልኝ። አገሬ ኢትዮጵያ ሁሉ ያላት ሁሉ የሞላት ሆና ተቸግራ፣ አፈር የሌላቸው አፈር ከውጭ አምጥተው በጥሩ ውጤት አገራቸውን አጥግበው እኛን ለመርዳት ሲችሉ፣ ሁሉ ያለን ለማኝ ሆነን መገኘት ካላሳፈረን ምን ያሳፍረን ይሆን የፍጅት ጦርነቱ ራስን ካለማወቅ ሌላ የሚባልለት ይኖር ይሆን እስቲ መልሱልኝ እባካችሁ። ወገኖቼ ይህችን የብሶት መልእክቴን ተነጋገሩባት፣ እንወያይባትም። ከአዘጋጁ፡ ፀሀፊው ግለ ህይወታቸውንና የጉዞ ታሪካቸውን የከተቡበት ከባቹማ እስከ ቨርጂኒያ በሚል ርእስ ለአንባቢያን ያቀረቡት መፅሀፍ ደራሲ ሲሆኑ፣ ፅሁፉ የእሳቸውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እየገለፅን በኢሜይል አድራሻቸው ማግኘት ይቻላል።
ፍቅርና ጥላቻ ሁሌም ቢፎካከሩ ማነው አሸናፊው
አፕል በአይፎን ዋጋ ላይ ቅናሽ ሊያደርግ እንደሚችል ተነግሯል ላለፉት ተከታታይ አመታት በአለማቀፉ የስማርት ፎን ገበያ ከፍተኛውን ድርሻ ይዞ የዘለቀው የደቡብ ኮርያው ሳምሰንግ፤ ያለፈውን የፈረንጆች አመት ሁለት ሺህ በቀዳሚነት ማጠናቀቁን ካናሊስ የተባለው የስማርት ፎን ገበያ የጥናት ተቋም አስታውቋል።ካናሊስ ከሰሞኑ ይፋ ባደረገው ሪፖርት እንዳለው፤ በሁለት ሺህ የፈረንጆች አመት አለማቀፍ የስማርት ፎን ገበያ ውስጥ የሀያ አንድ ነጥብ ሁለት በመቶ ድርሻ የያዘው ሳምሰንግ በአመቱ ሁለት መቶ ዘጠና ሶስት ነጥብ ሰባት ሚሊዮን የተለያዩ ሞዴል ያላቸው የሞባይል ስልኮቹን ለመሸጥ ችሏል።ተፎካካሪው አፕል ኩባንያ በበኩሉ፤ በአመቱ ሁለት መቶ ነጥብ አንድ ሚሊዮን የአይፎን ስልክ ምርቶቹን በመሸጥና በአለማቀፉ የስማርት ፎን ገበያ ውስጥ የ ነጥብ ሶስት በመቶ ድርሻን በመያዝ በሁለተኛ ደረጃ ላይ መቀመጡን ያስታወቀው ተቋሙ፤ በአመቱ ሁለት መቶ ስድስት ሚሊዮን የሞባይል ምርቶቹን ለመሸጥ የቻለው የቻይናው ኋዌለ፤ በ ነጥብ ስምንት በመቶ የገበያ ድርሻ በሶስተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝም አመልክቷል።ሳምሰንግ በገበያ ድርሻና በሽያጭ ከአፕል ቢበልጥም የሁለቱም ኩባንያዎች ሽያጭና አመታዊ እድገት ግን ከአምናው መቀነሱን የጠቆመው ሪፖርቱ፣ ኋዌ በበኩሉ በሽያጭና በአመታዊ እድገት ከአምናው ከፍተኛ ጭማሪ ማሳየቱን ገልጧል። በተያያዘ ዜናም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ገቢው በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰበት የመጣው አፕል ኩባንያ፤ በአንዳንድ አገራት ለገበያ ባቀረባቸው የአይፎን የስማርት ፎን ምርቶቹ ዋጋ ላይ ቅናሽ ሊያደርግ እንደሚችል ፍንጭ መስጠቱን ቢቢሲ ዘግቧል።አፕል ከአይፎን ሽያጭ የሚያገኘው ገቢ ባለፉት ሶስት ወራት በ በመቶ ያህል እንደቀነሰበት ያስታወሰው ዘገባው፣ የኩባንያው ዋና ስራ አስፈፃሚ ቲም ኩክ ከሰሞኑ ባደረጉት ንግግር፣ በአንዳንድ አገራት የአይፎን መሸጫ ዋጋ ላይ ቅናሽ ሊደረግ እንደሚችል መረጃ መስጠታቸውን ገልጧል።የአፕል አጠቃላይ ገቢ ባለፈው አመት ከነበረበት የአምስት በመቶ ቅናሽ በማሳየት፣ ሰማኒያ አራት ነጥብ ሶስት ቢሊዮን ዶላር መድረሱን የጠቆመው ዘገባው፣ ኩባንያው ለገቢው መቀነስ በምክንያትነት ከጠቀሳቸው ጉዳዮች መካከል በቻይና የኢኮኖሚ መቀዛቀዝ መፈጠሩ ይገኝበታል ብሏል።
ሳምሰንግ በአለማቀፉ የስማርት ፎን ገበያ ክብሩን አስጠብቋል
አዲስ አበባ፣ መጋቢት ሀያ ስድስት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ ህዝቡ ያነሳቸውን ጥያቄዎች ለመመለስ የተደራጀ እቅድ በማዘጋጀት ወደ ስራ መገባቱን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርእሰ መስተዳደር አሻድሊ ሀሰን ገለፁ። ርእሰ መስተዳድሩ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በነበራቸው ቆይታ ፥ ህዝብ ምላሽ ሊሰጥባቸው ይገባል በሚል የሚያነሳቸው ጥያቄዎች ተለይተዋል። በዚህም የሰላም፣ የኑሮ ውድነት፣ የአገልግሎት አሰጣጥ እንዲሁም ህገወጥ የማእድን ንግድን የመሳሰሉት ጉዳዮች ምላሽ እንዲሰጥባቸው ህዝቡ የሚያነሳቸው ጥያቄዎች መሆናቸውን አቶ አሻድሊ አመልክተዋል። በመሆኑም ጥያቄዎቹን በመለየትና በማደራጀት ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል የአጭር፣ የመካከለኛና የረጅም ጊዜ እቅድ ተዘጋጅቶ ወደተግባር መገባቱን ገልፀው ፥ ህዝቡን ያሳተፉ ዘላቂ የሰላም ግንባታ ስራዎች ትኩረት ያገኛሉ ብለዋል። በተለይም የሰላም ጥሪውን ተቀብለው ወደህብረተሰቡ የተቀላቀሉትን መልሶ የማደራጀት ተግባር በትኩረት እንደሚከናወን ተናግረዋል። በአፈወርቅ እያዩ
ህዝቡ ያነሳቸውን ጥያቄዎች ለመመለስ እቅድ በማዘጋጀት ወደ ስራ ተገብቷል አቶ አሻድሊ ሀሰን
ጥር አስራ ስምንት ቀን አመተ ምህረትኢሳት ዜናኢሳት ያነጋገራቸው ደጋፊዎች እንዳሉትምንም እንኳ ብሄራዊ ቡድኑ ከቡርኪና ፋሶ ጋር በተጫወተበት እለት ያገኘው ውጤት አሳዛኝ ቢሆንም በቀጣዩ ጨዋታ የናይጀሪያን ቡድን በማሸነፍ ለቀጣዩ ዙር ለማለፍ ድጋፋቸውን አጠንከረው እንደሚሰጡ ገልፀዋል።በደቡብ አፍሪካ የሚኖረው ደጀኑ በቀለ ድሉ የኢትዮጵያ ህዝብ እንደሚሆን ሙሉ እምነት እንዳለው ገልጿልከቡርኪና ፋሶ ከነበረው ጨዋታ በፊት ኢትዮጵያውያን ኮከብ ካለው ሰንደቃላማዎች ውጭ ሌሎችን ሰንደቃላማዎችን ይዘው ወደ ሜደ እንዳይገቡ ተከልክለው እንደነበር ታውቋል።አንዳንድ ኢትዮጵያውያን መንግስት እግርኳስ ጨዋታውን ለፖለቲካ አላማ ለማዋል ሞክረዋል በማለት ቅሬታቸውን አቅርበዋል።በሌላ በኩል በዚህን ያህል የጎል ልዩነት እንሸነፋለን ብለን አልጠበቅንም ያሉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ለዚህ የዳረገን ዋነኛው ችግር ሁለት ወሳኝ ተጫዋቾችን በጉዳት ሳቢያ ማጣታችን ነው ብለዋል።በብሄራዊ ቡድናችን ውጤት እጅግ ብናዝንም ነገም ሌላ ቀን ነውና እንደሚክሱን እናምናለን ተስፋ አንቆርጥም።
በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከዋሊያዎች ጎን እስከመጨረሻው እንደሚቆሙ ገለፁ
ባህር ዳር፡ ግንቦት ሁለት ሁለት ሺህ አመተ ምህረት አብመድ በጆን ሆፒኪንስ ዩኒቨርሰቲ መረጃ መሰረት በአለማቀፍ ደረጃ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከአራት ሚሊዮን አንድ መቶ አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ አልፏል። የሟቾች ቁጥርም ከሁለት መቶ ሰማኒያ ሺህ በላይ ደርሷል። ከዚህ ውስጥ አሜሪካ በቫይረሱ ከተያዙት ከሩብ በላዩን፣ ከሞቱት ደግሞ ሲሶውን ድርሻ ትወስዳች።ባለሙያዎች ታዲያ የሀገራት የመመርመር አቅም ውስን መሆን እንጅ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከምንሰማው በጣም ከፍ ያለ ነው እያሉ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል።በየእለቱ በቫይረሱ የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ከዚህ ቀደም ከፍተኛ በነበረባቸው እንደ ስፔን ያሉ ሀገራት እየቀነሰ ቢመስልም የገደቦች መነሳት ግን ግርሻ አስከትሎ የበለጠ እልቂት እንዳያመጣ ተሰግቷል። ስፔን ሁለት መቶ ስልሳ ሁለት ሺህ ሰባት መቶ ሰማኒያ ሶስት ሰዎች በቫይረሱ ተይዘውባት ሀያ ስድስት ሺህ አራት መቶ ሰባ ስምንት ሰዎችን በሞት ተነጥቃለች።የመንግስታት ትኩረትም ወረርሽኑን ከመከላከል ይልቅ ምጣኔ ሀብቱን ወደመታደግ ያዘነበለ እየመሰለ መሆኑም ተመላክቷል። በእርግጥ ወረርሽኙን ገበያውንና የአቅርቦት ሰንሰለቱን በጣጥሶታል፤ መንግስታት ይህንን ለመታደግ ቢተጉ ላይገርምም ይችላል።አንድ የቻይና ባለስልጣን የኮሮና ወረርሽኝ በጤና ስርአታችን ውስጥ የነበረውን ድክመት ያጋለጠ ነበር ማለታቸውን ተከትሎ ቢቢሲ በቫይረሱ ዙሪያ በቂ መረጃ አልሰጠችም እየተባለች ስትተች የነበረችው ቻይና ድክመቷን ያመነችበት ፍንጭ ነው የሚል ብያኔ ያለው ዘገባ ሰርቷል።
በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከአራት ሚሊዮን መብለጡ ቢገለፅም ከዚያም በላይ እንደሆነ ተመላከተ።
የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዘርአይ አስገዶምን ዘረኛና ጎጠኛ ሲሉ የፓርላማ አባላት አወገዙ። አባላቱ ኢህአዴግን ተጠልሎ ዘረኝነትን በኦፊሴላዊ ደረጃ ማራመድ፣ስልጣንን ማሳነስና የስም ማጥፋት ዘመቻ መክፈት ተጠያቂ ያደርጋል ብለዋል። የኮሚኒኬሽን ፅህፈት ቤትም ሆነ ሚኒስትሩ የሚወክሉት መንግስትን የሚያንፀባርቁትም የመንግስትን አቋም ነው ብለዋል አባላቱ። የመንግስት ኮሚኒኬሽኝ ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ሀላፊ ህዳር ሁለት ሺህ አስር ለፓርላማው የባህል፣ ቱሪዝምና መገናኛ ብዙሀን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሩብ አመት አፈፃፀማቸውን አቅርበዋል። በኮሚኒኬሽን ፅህፈት ቤትና በቃል አቀባዩ ስልጣንና ሀላፊነት እንዲሁም በተቋሙና በቃል አቀባዩ ላይ እየተካሄደ ያለው የስም ማጥፋት ዘመቻ ጠንከር ያለ አስተያየት የቀረበበት እንደነበርም ታውቋል። የቋሚ ኮሚቴው አባላት የኮሚኒኬሽን ፅህፈት ቤትም ሆነ ቃል አቀባዩ ዶክተር ነገሬ ሌንጮ የሚወክሉት መንግስትን፣የሚያንፀባርቁትም የመንግስትን አቋም ስለመሆኑ ሁሉም ሊገነዘብ ይገባል ብለዋል የቋሚ ኮሚቴው አባላት። ሁሉም አካላት የኮሚኒኬሽን ፅህፈት ቤቱንም ሆነ ሚኒስትሩን የሾመው ፓርላማው እንደሆነ ለማስታወስ እንወዳለን ሲሉ በትኩረት ተናግረዋል። በኦሮሚያ እየተካሄደ ባለው ህዝባዊ ተቃውሞና ግጭት የብሄር ግጭት አስመስለው የዘገቡትን የማህበራዊ ድረ ገፆችና የመገናኛ ብዙሀንን ቃል አቀባዩ ዶክተር ነገሬ ሌንጮ ማውገዛቸውና ህጋዊ ርምጃ እንወስዳለን የሚል መግለጫ ማውጣታቸው የሚታወቅ ነው። ይህንን መግለጫ ተከትሎ በማግስቱ የፕረስ ኮንፈረንስ የጠሩት የብሮድካስት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዘርአይ አስገዶም የቃል አቀባዩ አስተያየት የግላቸው ነው፣ርምጃ የመውሰድ ስልጣን የላቸውም ማለታቸው የሚታወስ ነው። የህወሀት ነባር አባል የሆኑት አቶ ዘርአይ አስገዶም በኮንፈረንሱ የሰጡት አስተያየት በመገናኛ ብዙሀን ተቋማት በሰፊው በመሰራጨቱና በኦህዴድ ባላስልጣናት ውስጥ ቁጣን በመቀስቀሱ ቃል አቀባዩ የአፀፋ ምላሽ በቢቢሲ የአማርኛው ክፍል እስከመስጠት ሄደው ነበር። ለቢቢሲ በሰጡት የአፀፋ ምላሻቸውም ቃል አቀባዩ የተናገሩት የግላቸውን ሳይሆን የመንግስትን አቋም መሆኑን አፅኖት ሰጥተውበታል። በሰኞው የፓርላማው የቋሚ ኮሚቴ ስብሰባ የፓርላማው አባላት የአቶ ዘርአይን አስተያየት በማውገዝ እንደ ሀገር እናስብ ካልን የሚጠቅመን ኢትዮጵያዊነታችን እንጂ ዘረኝነትና ጎጠኝነት አይደለም ብለዋል። ኢህአዴግን ተጠልሎ ዘረኝነትን በኦፊሴላዊ ደረጃ ማራመድ ተገቢ አይደለም ብለዋል። የቋሚ ኮሚቴው ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት ማንሳቱና እንዲሁም ለኮሚኒኬሽን ፅህፈት ቤትና ለሚኒስትሩ ላሳየው ተቆርቋሪነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የሚመለከተው አካልም በዝርዝር ተመልክቶ ርምጃ ይወስዳል ብለው እንደሚጠብቁ ተናግረዋል። በተከታታይ የፓርላማው ቋሚ ኮሚቴዎች የተለያዩ ተቋማትን ሲገመግሙ የሚያነሷቸው ነጥቦች በየተቋማቱ የሚታዩ ትላልቅ ችግሮች ናቸው። የተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሜቴክን በገመገመበት ወቅት ውጫዊ ምክንያቶች በዝተዋል እኔም የሜቴክ ጉዳይ ሰልችቶኛል ሲል መናገሩን በትላንት የዜና እወጃችን መዘገባችን ይታወሳል።
ዘርአይ አስገዶምን ዘረኛና ጎጠኛ ሲሉ የፓርላማ አባላት አወገዙ
አርባ ሰባት ፒተር ኗዲኬተጠናቀቀ ጨዋታው በኤሌክትሪክ አሸናፊነት ተጠናቀቀ። ኤሌክትሪክም ከመውረድ ተርፏል።የተጫዋች ለውጥ ኤሌክትሪክ ዘጠና ሁለት ፍፁም ገብረማርያም ወጥቶ ተስፋዬ መላኩ ገብቷል።ተጠማሪ ደቂቃ መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ተጠናቆ አራት ደቂቃ ተጨምሯል። ኤሌክትሪክ በሊጉ መቆየቱን ለማረጋገጥ እጅግ ተቃርቧል። አወት ከርቀት የሞከረው ኳስ ለጥቂት ወደ ውጪ ወጥቷል። ዳኛቸው በቀለ ወጥቶ ሰለሞን ገብረመድህን ገብቷል። ብሩክ አየለ ወጥቶ ማናዬ ፋንቱ ገብቷል። ኤፍሬም አሻሞ ወጥቶ አምሀ በለጠ ገብቷል። ማንኮ ክዌሳ ወጥቶ በሀይሉ ተሻገር ገብቷል። ፍቅረየሱስ ተ ብርሀን ወጥቶ ዳንኤል ለታ ገብቷል። ፍፁም ገብረማርያም ከግብ ጠባቂው ጋር አንድ ለአንድ ተገናኝቶ ቺፕ ያደረገው ኳስ ለጥቂት ወጥቷል። መደበኛው የመጀመርያ ግማሽ ክፍለ ጊዜ ተጠናቆ አንድ ደቂቃ ተጨምሯል። አማረ በቀለ ከርቀት አክርሮ የመታው ኳስ በግቡ አናት ለጥቂት ወጥቷል። ጨዋታው የተቀዛቀዘ እንቅስቃሴ እየታየበት ይገኛል። የግብ ሙከራዎችም መስተናገድ አልቻሉም። ኤሌክትሪክ የእንቅስቃሴ የበላይነቱን ወስዷል። ፒተር ኗድኬ ከርቀት በግራ እግሩ የመታውን ኳስ ፌቮ አድኖታል።ሀያ ሁለት አሰግድ አክሊሉሁለት አወት ገብረ ሚካኤል ሀያ አንድ በረከት ተሰማ ሀያ ስድስት ሲሴይ ሀሰን አማረ በቀለአራት ማንኮ ክዌሳ ዘጠኝ አዲስ ነጋሽ ሀያ ሶስት አሸናፊ ሽብሯስር ብሩክ አየለ ፍፁም ገብረማርያም ሀያ ስምንት ፒተር ኗድኬ አንድ ገመቹ በቀለ ተስፋዬ መላኩ ስድስት ዋለልኝ ገብሬ ስምንት በሀይሉ ተሻገር ትእዛዙ መንግስቱ አምስት አህመድ ሰኢድ ሀያ ሶስት ማናዬ ፋንቷንድ ኢማኑኤል ፌቮ አዲሱ ሰይፉ ቢንያም ሲራጅ አምስት ቶክ ጀምስ ሀያ ሰባት አንተነህ ገብረክርስቶስ ታዲዮስ ወልዴሀያ አንድ ኤፍሬም አሻሞ ሰማኒያ ቢንያም በላይ አብዱልከሪም ሀሰን ሁለት ፍቅረየሱስ ተክለብርሀንአስር ዳኛቸው በቀለ ስልሳ አራት ዳዊት አሰፋ ዘጠና ስምንት ዳንኤል አድሀኖም ዘጠና ዘጠኝ ዳንኤል ለታ ሀያ ሰባት ስንታለም ተሻገር አቤል አበበ ስድስት አምሀ በለጠ ስምንት ሰለሞን ገብረመድህን
ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቀጥታ የፅሁፍ ስርጭት
የቀድሞ የዩናይትድ ስቴትስ ሪፖብሊካን ፕሬዚዳንት ጆርጅ ደብሊው ቡሽ ባለፈው ሳምንት በተከናወነው ምርጫ ማሸነፋቸው ለተነገረላቸው ለዲሞክራቱ ጆ ባይደን የእንኳን ደስ ያለዎ መልእክት አስተላልፈዋል። ተመራጩ ፕሬዚዳንት ሀገራችንን የመምራት እና አንድ የማድረግ እድል አሸናፊ ሆነዋል ብለዋል ጆርጅ ቡሽ።እአአ ከሁለት ሺህ አንድ እስከ ሁለት ሺህ ዘጠኝ ሀገሪቱን የመሩት ቡሽ ከባይደን ጋር የፖለቲካ ልዩነቶች አሉን፤ የሆነ ሆኖ በስራቸው ስኬት እንዲያገኙ እፀልይላቸዋለሁ። በምችለው ሁሉ ልረዳቸው ቃል እገባለሁ ብለዋል። ተመራጯን ምክትል ፕሬዚዳንት ካምላ ሀሪስንም የቀድሞው ፕሬዚዳንት ቡሽ እንኳን ደስ ያለዎ ብለዋል።
ጆርጅ ደብሊው ቡሽ ለጆ ባይደን የእንኳን ደስ ያለዎ መልእክት አስተላለፉ
ቤተመፃህፍት ለመክፈት አቅዷል በዱከም ከተማ ተወልዶ ያደገውና የቴኳንዶ መምህር ወጣት ኤርሚያስ አሻግሬ ግለሰቦችና ተቋማት ማንኛውንም አይነት መፅሀፍት እንዲለግሱት ጠየቀ። በከተማዋ ለወጣቶች የተመቻቸ የመዝናኛም ሆነ የማንበቢያ ቦታ ባለመኖሩ ወጣቶች ለአጉል ባህርያትና ለሱስ መጋለጣቸውን የጠቆመው ወጣት ኤርምያስ ለመታደግ ቤተ መፅሀፍት ለመክፈት ከራሱና በቅርብ ከሚያውቃቸው ወዳጅ ጓደኞቹ መፃህፍቱ ማሰባሰብ መጀመሩን ገልፆ እስካሁን ወደ ያህል የተለያየ ይዘት ያላቸው መፅሀፍት ማግኘቱን አስታውቋል። ጉዳዩን ለአጎቴ ልጅ አማክሬው የቤተ መፅሀፍቱን ዲዛይን ሊሰራልኝ ተስማምተናል ያለው ወጣት ኤርያስም ቦታውን ደግሞ ለዱከም ከተማ ከንቲባ ለማመልከት እንዳሰበና ለጥያቄው ምላሽ እንደማይነፍጉት እምነቱን ገልጿል። ለነዚህ ወጣቶች ህይወት መቃናት በጎ የሚያደርግ በስሙ በተከፈተው የፌስ ቡክ አካውንቱ በኩል በመገናኘት እንዲለግሱት ተማፅኗል። ወጣቱ በአሁኑ ወቅት በዱከም ከተማ ጊቦር ማርሻል አርትና ጂም የተሰኘ ማሰልጠኛ ከፍቶ ከ በላይ ወጣቶችን በማሰልጠን ላይ የሚገኝ ሲሆን ከስፖርት አምልጠውኝ ወደሱስ የተዘፈቁትን ወደ ንባብ እንዲመለሱ ቤተ መፃህፍቱን ለማቋቋም ወሳኝ ነው ይላል።
የዱከሙ ወጣት የመፃህፍት ልገሳ እየጠየቀ ነው
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ ሰባት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በቀጣይ የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ እና የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በትኩረት እንደሚሰራ የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ገለፁ። የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት የሁለት ሺህ በጀት አመት የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ በሆሳእና ከተማ እየተካሄደ ነው። አቶ እንዳሻው በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር ያለፉት ዘጠኝ ወራት ለአጠቃላይ ተግባራት መሳካት መደላድል የተፈጠረበት እና አመራሩን በአስተሳሰብ ብሎም በተግባር ለማዋሀድ የተሻለ ስራ የተሰራበት መሆኑን አንስተዋል። መደበኛ የመንግስት እቅዶችን ለማሳካትም አበረታች ስራ መከናወኑን ጠቅሰው አቅሞችንና የህዝብ ፍላጎቶችን መለየት የተቻለበት ነው ማለታቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ አመላክቷል። በቀጣይም የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ፣ የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ፣ የኢንቨስትመንት፣ የግብርና እና በሌሎች መስኮችም መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት በትኩረት እንደሚሰራ ጠቁመዋል። መድረኩ በሴክተሮቹ ሪፖርቶች ላይ ተመስርቶ ዝርዝር ውይይት በማድረግ ጥንካሬዎችንና ውስንነቶችን ያገናዘበ አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተጠቁሟል።
አቶ እንዳሻው ጣሰው የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሰራ ገለፁ
አዲስ አበባ፣ የካቲት ስምንት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በሱዳን የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ይበልጣል አእምሮ በሱዳን ከሩሲያ አምባሳደር ቭላድሚር ዜልቶቭ እና ከስዊዘርላንድ አምባሳደር ክርስቲያን ዊንተር ጋር ተወያዩ። አምባሳደሩ በትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ፣ በኢትዮ ሱዳን የድንበር ጉዳይ ላይ ገለፃ አድርገዋል። እንዲሁም በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ዙሪያ ተወያይተዋል። በውይይቱም አምባሳደር ይበልጣል በተጠቀሱት ጉዳዮች ዙሪያ መንግስት ያለውን አቋም አስረድተዋል። የሩሲያው አምባሳደር በበኩላቸው ስለተደረገላቸው ገለፃ አመስግነው፥ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ መፈታት እንዳለባቸውና የሀገራት ሏላዊነት መከበር እንዳለበት ተናግረዋል። ሩሲያ ጉዳዮች ፖለቲካዊ መደረግ የለባቸውም የሚል የፀና አቋም እንዳላትም ገልፀዋል። የስዊዘርላንድ አምባሳደርም በተመሳሳይ በአምባሳደሩ ስለተደረገላቸው ገለፃ አመስግነው፥ በገለፃው ስለተጠቀሱት ጉዳዮች ሰፊ ግንዛቤ እንዳገኙ መናገራቸውን በሱዳን ከኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ የፋና ድረ ገፅ ይጎብኙ፤ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገፃችን ይወዳጁን የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት መተግበሪያን በስልክዎ በመጫን ቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት፣ ኤፍኤም ዘጠና ስምንት ነጥብ አንድ እና ብሄራዊ ሬዲዮን ይከታተሉ። ቪዲዮዎችንም ይመልከቱ። ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
አምባሳደር ይበልጣል አእምሮ በሱዳን ከሩሲያ እና ስዊዘርላንድ አምባሳደሮች ጋር ተወያዩ
ጠቅላይ አቃቤ ህግ በማካይድራ የሰዎች ግድያ ላይ የተሳተፉ ሁለት መቶ ሰባ ዘጠኝ ተጠርጣሪዎች መኖራቸውን ከተሰበሰቡ መረጃዎች መረዳት እንደቻለ ገለፀ። አቃቤ ህግ በትናንትናው እለት ከፌደራል ፖሊስ ጋር በመሆን መግለጫ የሰጠ ሲሆን ከተጠርጣሪዎች መካከልም ስላሳ ስድስትቱ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቋል። በጠቅላይ አቃቤ ህግ የሙስና እና የተደራጁ ወንጀል ጉዳዮች ምክትል ጠቅላይ አቃቤ ህግ አቶ ፍቃዱ ፀጋ እና የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ጄኔራል እና የወንጀል ምርመራ ቢሮ ሀላፊ ዘላለም መንግስቴ በጋራ በሰጡት መግለጫ ላይ አብዛኞቹ ተጠርጣሪዎች ወደ ሱዳን ማምለጣቸውን ተናግረዋል። በማይካድራ ጥቃት የተፈፀመው በፌደራል መንግስትና በህወሀት ሀይሎች መካከል ጥቅምት ሀያ አራት፣ ሁለት ሺህ አመተ ምህረት ግጭት ከተቀሰቀሰ ጥቂት ቀናት በኋላ፤ ጥቅምት ስላሳ፣ ሁለት ሺህ አመተ ምህረት ሰኞ እለት ሲሆን የሰብአዊ መብት ቡድኖች በጥቃቱ ከስድስት መቶ በላይ ሰዎች ተገድለዋል ሲሉ ተናግረዋል። ጥቃቱ የተፈፀመው ጥቅምት ስላሳ፣ ሁለት ሺህ አ ም ከሰአት በኋላ ዘጠኝ፡ ሰአት ላይ የነበረ ሲሆን አስከሚቀጥለው ቀን ጠዋት ድረስ መቀጠሉን ነዋሪዎቹ በወቅቱ ለቢቢሲ ተናግረው ነበር። ከዚህ ጥቃት ጋር በተያያዘ የሟቾችን ቁጥር ለማወቅ ከጤና ሚኒስቴር የሀኪሞች ቡድን ተልኮ፤ አንድ መቶ ጉድጓዶች የተገኙ ሲሆን አስክሬኖችን መርምሮ የሟቾቹን ብዛት እና የሞት ምክንያት ለማወቅ እየተሰራ መሆኑን አቶ ፍቃዱ ገልፀዋል። አቶ ፍቃዱ አክለውም፤ ይህ የህክምና ባለሙያዎች ቡድን ሪፖርት እስኪደርስ ድረስ ትክክለኛው በጥቃቱ የሞቱ ሰዎችን ብዛት መግለፅ እንደማይቻል አስታውቀው መሬት ባለው እውነት እና በየሚዲያው የተገለፀው መካከል ልዩነት መኖሩን በማብራሪያቸው አስረድተዋል። የማይካድራ ከተማ በትግራይ ክልል ደቡብ ምእራብ ዞን የምትገኝ ስትሆን ጥቅምት ሀያ አራት፣ ሁለት ሺህ አ ም ህወሀት ከፌደራል መንግስቱ ጋር ግጭት ውስጥ ከገባ በኋላ በርካታ ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸው ይፋ ተደርጎ ነበር። በወቅቱ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብት ሀላፊ ሚሼል ባችሌት በማይካድራ ከተማ ውስጥ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ በስለት ተገድለዋል የሚለው ሪፖርት እንዲጣራ ጠይቀው ነበር። አምነስቲ ኢንተርናሽናል በወቅቱ ባወጣው ሪፖርት ጥቃቱን ማን እንደፈፀመው ለማረጋገጥ አለመቻሉን አመልክቷል። ነገር ግን ያነጋገራቸው የአይን እማኞች ከፌደራል መንግስቱ ሰራዊት ጋር የሚዋጉትን የህወሀት ታማኝ ሀይሎች ይከስሳሉ። አምነስቲ ኢንትርናሽናል በማይካድራ ስለተፈፀመው ነገር ለማረጋገጥ ከጥቃቱ በኋላ ወደ ስፍራው የሄዱ እማኞችን ያነጋገረ ሲሆን፤ በከተማዋ ውስጥ በየቦታው የወደቁ አስከሬኖችንና ከጥቃቱ ቆስለው የተረፉ ሰዎችን እንደተመለከቱ ተናግረው ነበር። አብዛኞቹ አስከሬኖች የተገኙት በከተማዋ ማእከላዊ ክፍል ውስጥ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሚገኝበት አካባቢና በአቅራቢያው ወደምትገኝ የሁመራ ከተማ የሚያመራውን መንገድ ተከትሎ መሆኑን የአይን እማኞችና የተገኙት ምስሎች ጠቁመዋል። ሪፖርቱ በወጣበት ወቅት የትግራይን ክልል እያስተዳደሩ የነበሩት ደብረፅዮን ገብረ ሚካኤል ዶክተር ውንጀላዎቹን መሰረት የሌላቸው ናቸው ማለታቸውን አጃንሰ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቦ ነበር። የሰብአዊ መብቶች ተቆርቋሪው ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል እንዳለው በሰሜን ምእራብ ኢትዮጵያ በምትገኘው ማይካድራ ከተማ ውስጥ በተፈፀመው በዚህ ጥቃት ቁጥራቸው በመቶዎች ሊቆጠሩ የሚችሉ ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ በስለት ተገድለዋል። ድርጅቱ ከማይካድራ ከተማ የወጡና በየቦታው ወድቀው የሚታዩ አስከሬኖችን የሚያሳዩ አሰቃቂ ፎቶግራፎችንና ቪዲዮዎችን በመመርመር ምስሎቹ የቅርብ ጊዜና ስፍራውም ማይካድራ መሆኑን ለማረጋገጥ መቻሉን ገልፆ ነበር። በአገር መከላከያ ሰራዊት ሰሜን እዝ ላይ ተፈፀመ የተባለውን ጥቃት ተከትሎ ለወራት በውዝግብ ውስጥ ቆይተው የነበሩት የፌደራል መንግስት እና የትግራይ ክልል አስተዳደር ጥቅምት ሀያ አራት፣ ሁለት ሺህ አ ም ወደ ግልፅ ጦርነት መግባታቸው ይታወሳል። የፌደራል መንግስቱ መቀሌን ከተቆጣጠረ በኋላ ጦርነቱ መጠናቀቁን የገለፀ ቢሆንም አሁንም ግን በተለያዩ አካባቢዎች ውጊያ እንደሚካሄድ የተለያዩ አለም አቀፍ ሰብአዊ ድርጅቶች በሪፖርታቸው እየገለፁ ነው። ከዚህ ግጭት ጋር በተያያዘ ስልሳ ሺህ የሚጠጉ ሰዎች ወደ ሱዳን ሲሸሹ በሚሊዮኖች ሚቆጠሩ ደግሞ በአገር ውስጥ ተፈናቅለው የሰብአዊ እርዳታ እየጠበቁ ይገኛሉ። በትግራይ አሁንም የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ያልተመለሰ ሲሆን የሰብአዊ ርዳታ ድርጅቶችም እርዳታ ለሚፈልጉ ለማድረስ እንደልብ መንቀሳቀስ አለመቻላቸውን በመግለፅ ተደጋጋሚ መግለጫ አውጥተዋል።
ትግራይ፡ በማይካድራ ግድያ ከተጠረጠሩት መካከል ስላሳ ስድስትቱ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለፀ
አዲስ አበባ፣ የካቲት አምስት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የሶማሌ ማይክሮ ፋይናንስ ወደ ሸበሌ ባንክነት ተሸጋግሯል። ማይክሮ ፋይናንስ ተቋሙን ወደ ባንክ የማሳደጊያ መርሀግብሩ በጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ነው። በመርሀ ግብሩ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼህ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋን ጨምሮ ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። በሁለት ሺህ ሶስት የተመሰረተው ብድር እና ቁጠባ ተቋሙ፣ ሄሎ ካሽ በተሰኘ የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት በስፋት ይታወቃል። የሸበሌ ባንክ አሁን ላይ ከግማሽ ቢሊየን ብር ላይ በሆነ ካፒታል ሙሉ የባንክ አገልግሎት ለመስጠት ወደሚያስችለው ደረጃ ከፍ ማለቱ ተገልጿል። ተቋሙ ከአማራ ብድርና ቁጠባ፣ ከኦሮሚያ ብድርና ቁጠባ ተቋም በመቀጠል በአገሪቱ ራሱን ወደ ባንክ ያሳደገ ሶስተኛው ተቋም ሆኗል። በነስሪ ዩሱፍ
የሶማሌ ማይክሮ ፋይናንስ ወደ ባንክነት ተሸጋገረ
በመካከለኛው ምስራቅ በፐርሺያን ገልፍ ሰሜን ምእራብ ጫፍ የምትገኝ በረሀማ ነገርግን ስትራቴጂካዊ እና በነዳጅ ሀብት የበለፀገች አገር ናት። ለዜጎቿም ሆነ ለሌሎች አገሮች ዜጎች በነፃ ህክምና ትሰጣለች። የአገሪቱ ዜጎች ከመንግስታቸው ሌሎች የተለያዩ ጥቅማጥቅሞችን ያገኛሉ። የኩዌት ዲናር አቅም ካላቸው ገንዘቦች በቀዳሚነት የሚመደብ ሲሆን አንዱ ዲናር ሶስት ብር ከሀምሳ የአሜሪካን ዶላር ይመነዘራል። ኩዌት በህገመንግስታዊ የንጉስ ስርአት የምትመራ አገር ናት።ባለፈው ሳምንት ባዘጋጀችው ሶስተኛው የአፍሪካ አረብ ጉባኤ ስላሳ አራት የአገር መሪዎችን፤ ሰባት ምክትል ፕሬዚደንቶች፣ ሰባ አንድ አገሮች እና ድርጅቶች ተሳትፈዋል። የጉባኤው ዋና አጀንዳ በአፍሪካ እና በአረብ መካካል ያለውን ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት ማጠናከር ነበር። ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የኩዌት አሚር ሼክ ሰባህ አሀመድ አል ሰባህ የሁለቱ አካባቢ ህዝቦች ቆየት ያለ ታሪካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት እንዳላቸው በመግለፅ በዝቅተኛ የወለድ መጠን የሚከፈል በአፍሪካ አህጉር ለተለያዩ ኢንቨስትመንት የሚውል አንድ ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር በቀጣዩ አምስት አመት እንደሚሰጥና ለተለያዩ የምርምር ስራዎች የሚውል አንድ ሚሊዮን ዶላር ከኩዌት ለአፍሪካ እንደሚለግስ ቃል ገብተዋል። በሁለቱም አካባቢ ህዝቦች የምግብ ዋስትና እና የፀጥታ እና የደህንነት ጉዳዮች ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫዎች ሊሆነ እንደሚገባ በአፅንኦት የተናገሩት አሚሩ፣ ነገር ግን አንዱ ወገን እርዳታ እየሰጠ ሌላው ወገን ምንም አስተዋፅኦ የማያደርግበት አካሄድ መስተካከል እንዳለበት በንግግራቸው አስምረውበታል። የጉባኤው ትኩረት ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ቢሆንም አሚሩ የሶሪያን ጉዳይ በተመለከተ የመንግስታቱ ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ሀላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበው እስራኤል የምትወስዳቸው እርምጃዎች እንደሚያሳስቧቸው ተናግረዋል።ሁለተኛው አፍሮ አረብ ጉባኤ በሊቢያዋ ስርት ከሶስት አመት በፊት ሲካሄድ ከሁለት ሺህ አንድ እስከ ሁለት ሺህ ይተገበራሉ የተባሉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተቀርፀው የነበረ ቢሆንም ቱኒዚያን፣ ሊቢያን፣ ግብፅን እና የመንን ያናወጠው ህዝባዊ አመፅ እና የመሪዎች ከስልጣን መውረድ እንዲሁም እስከ አሁን የቀጠለው የሶሪያ ቀውስ ፕሮጀክቶቹ ብዙም እንዳይራመዱ ቀስፈው የያዙ ምክንያች ናቸው።ጉባኤውን በሊቀመንበርነት የመሩት የኢትዮጲያ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ለቀመንበር አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ በበኩላቸው፣ የስደተሶች ጉዳይ የጉባኤው አጀንዳ መሆኑ ተገቢ እና ወቅታዊ እንደሆነ በመግለፅ ጉዳዩ አሳሳቢ በመሆኑ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ መፍትሄ መፍትሄ እንደሚያስፈልገው አስቀምጠዋል። የፖለቲካ ቁርጠኝነት ካለ ችግሩን መፍታት ይቻላል ያሉት አቶ ሀይለማርያም ጉዳዩ እንደ ከዚህ ቀደም ዝም ብሎ የሚታይ አይደለም ብለዋል። የጉባኤውን ዋና አጀንዳ አስመልክቶም በአረብ በኩል ያለው አቅም እና በአፍሪካ በኩል ያሉ የተለያዩ እምቅ ሀብቶች ሁለቱን አካባቢዎች እንደሚያስተሳስሯቸው ተናግረዋል። ከመሪዎቹ ስብሰባ ቀደም ብሎ በተካሄደው የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ የስደተኞችን በሚመለከት ይቋቋማል የተባለው የአፍሮ አረብ የተቀናጀ ኮሚቴ ጥሩ ውጤት ያመጣል በለው እንደሚጠብቁ ተናግረዋል።ከጉባኤው ጎን ለጎንም ከሰላሳ በላይ ውይይቶች የተካሄዱ ሲሆን ከግጭቶች እና ከኢንቨስትመንት ጋር የተያያዙ አጀንዳዎች አብላጫውን ቁጥር ይይዛሉ። የኢትዮጲያ እና የግብፅ መሪዎች መሀመድ ሙርሲ ከስልጣን ከተወገዱ በኋላ ለመጀመሪያ ግዜ ተገናኝተው ኢትዮጲያ እየገነባች ስላለው የታላቁ የህዳሴ ግድብ ተወያይተዋል። የግድቡን ግንባታ አስመልክቶ በግብፅ በኩል የቀረበው ግንባታው ላይ የመሳተፍ ጥያቄ በኢትዮጲያ በኩል ተቀባይነት ያላገኘ ሲሆን ግድቡን አስመልክቶ በያዝነው ወር ግብፅ፣ ኢትዮጵያ እና ሱዳን ካርቱም ላይ ተገናኝተው ውይይት ያደረጉ ሲሆን ቀጣዩ ስብሰባም በታህሳስ ወር ካርቱም ይደረጋል።ጉባኤው ባወጣው የአቋም መግለጫ በአፍሪካ እና በአረብ አገሮች መንግስታት እና ህዝቦች መሀል የቀረበ ትስስር መፍጠር፣ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶችን ማጠናከር፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የአረ ሊግ የአፍሮ አረብ የድርጊት መርሀ ግብሮች እና ፕሮጀክቶች ተግባራዊ እንዲሆኑ የሚያግዝ ግብረ ሀይል እንዲያቋቁሙ፣ የአፍሪካ እና የአረብ አገሮ የገንዘብ ተቋሞች የግሉን ዘርፍ እና የሲቪል ማህበራትን በማጠናከር የሁለቱን አካባቢዎች የንግድ ትስስር እንዲያፋጥኑ ማስቻል፣ የአፍሪካ እና የአረብ የንግድ ምክር ቤቶች እና የኢንዱስትሪው ዘርፍ እነዲሁም ሌሎች የግል ተቋሞች ተከታታይ የሆነ የምክክር መድረኮችን በመፍጠር የሁለቱን አካባቢዎች ትስስር ለማፋጠን እገዘ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል።በሁለቱም አካባቢዎች ያሉ መንግስታት፣ የግሉ ዘርፍ እና የሲቪል ማህበራት የግብርናውን ዘርፍ እንዲያሳድጉ ማበረታታት፣ የገጠርልማት፣ የግብርና እና የምግብ ዋስትና ላይ የሚሰሩ ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠል፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የአረብ ሊግ ይህ የአቋም መግለጫውም ሆነ የአፍሮ አረብ የአጋርነት ስትራቴጂ ተግባራዊ እንዲሆኑ በገንዘብም ሆነ በቴክኒክ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል። ፍልሰትን በተመለከተም የተቋቋመው የአፍሮ አረብ የቴክኒክ እና የቅንጅት ኮሚቴንም ሆነ ከጉዳዩ ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ስትራቴጂዎች ሁለቱ አካባቢዎች በቅንጅት እንዲሰሩ፣ ለፈለሱ ሰዎች የደህንነትና ማህበራዊ ጥበቃ ማድረግ፣ ስደተኞችን፣ ተፈናቃዮቸችን እንዲሁም የፈለሱ ሰዎችን ለሚቀበሉ አገሮች በተለይም ለቡርኪናፋሶ እና የመን እገዛ ማድረግ እንደሚገባና ህገወጥ ፈላሾችን ለመለየት የአፍሮ አረብ የመረጃ ልውውጥ ማእከል እንዲቋቋም ስምምነት ላይ መደረሱን መግለጫው ያሳያል።የባህር ላይ ውንብድና እና የካሳ ጥያቄ፣ ህገወጥ የሰዎች ዝውውር፣ የአደንዛዝ እፅ ዝውውር እና የህገወጥ የመሳሪያ ዝውውር ላይ በጋራ ለመስራትም ስምምነት ላይ ተደርሷል። አንድ የኩዌት ከፍተኛ ባለስልጣን የፍልሰት ጉዳይ አሳሳቢ ችግር ነው ያሉ ሲሆን በጉባኤው ላይ ያነጋገርኳቸው ተንታኝም፣ የፍልሰት ጉዳይ ትኩረት ተሰጥቶት ካልተሰራበት እና መፍትሄ ካልተሰጠው የአፍሪካን እና የአረቡን አለም ግንኙነት እስከማቋረጥ ሊደርስ እንደሚችል አስቀምጠዋል። መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በአሁኑ ወቅት ከአምስትመቶ ሺህ በላይ አፍሪካውያን ወደ አረብ አገሮች ፈልሰዋል። ሁለቱ አካባቢዎች በፀጥታ እና አሸባሪነትን በጋራ ለመከላከል ለዚህመም መረጃ ለመለዋወጥ የተስማሙ ሲሆን በሁለቱ አካባቢዎች ለሚገኙ ግጭቶች እና አለመረጋጋቶች ለዜጎች አመቺ ሁኔታን በሚፈጥሩና ለደህንነታቸው ትኩረት በሰጠ መልኩ እልባት እንዲያገኝ መግባባት ላይ ተደርሷል። የኩዌቱ አሚር ሼክ ሰባህ በጉባኤው መዝጊያ ላይ ባደረጉት ንግግር ከፊታችን ረጅም እና አስቸጋሪ መንገድ ይጠብቀናል። ለዚህ ደግሞ ዋናው ምክንያት በሁለቱም አካባቢዎች ያለው ያለመረጋጋት ነው። ስለዚህ ያቀድናቸውን ለማሳካት ብዙ ጥረት ይጠበቅብናል ብለዋል። በአፍሪካ ርካሽ የሰው ጉልበት፣ ለእርሻ የሚውል ሰፊ የሚታረስ መሬት፣ አፋጣኝ የመሰረተ ልማት ፍላጎት ይገኛል። ይህን እድል ሁለቱም አካባቢዎች ሚዛኑን በጠበቀ የዜጎቻቸውን ፍላጎት በተከተለ መንገድ እንዴት ሊወጡት ይችላሉ የሚለው ጥያቄ ምላሽ ለግንኙነቱ ምላሽ ይሰጣል ያሉት የጉባኤው ተሳታፊ፣ በተለይ በአፍሪካ በኩል ጥንቃቄ የተሞላበት እርምጃ ግድ ይላል ይላሉ። ቀጣዩ የአፍሮ አረብ ጉባኤ በአፍሪካ እንዲዘጋጅ የተወሰነ ሲሆን ሰባተኛውን የአፍሮ አረብ ንግድ ትርኢትም ሞሮኮ በቀጣዩ አመት እንድታስተናግድ ተወስኗል።
የፍልሰት ጉዳይ መፍትሄ ካልተሰጠው የአፍሪካንና የአረቡን አለም ግንኙነት እስከማቋረጥ ሊደርስ ይችላል የኩዌት ፖለቲካ ተንታኝ
አዲስ አበባ፣ ህዳር ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ለኢትዮጵያ ህዝብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላለፉ። ከፍተኛ መስዋእትነት ከፍሎ የመከላከያ ሀይላችን ላጎናፀፈን ክብር መላው ኢትዮጵያውያንን እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ደስ አለን ብለዋል። ህግ የማስከበሩ ምእራፍ በድል ተጠናቋል፤ በመጭው ጊዜ ደግሞ ትልቅ ስራ እንደሚጠብቀን ለአፍታም አንዘናጋ ነው ያሉት። እጅ ለእጅ ተያይዘን የሀገራችንን ልማትና እድገት ለማረጋገጥ ጠንክረን እንስራ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል። የአሁኑ የመከላከያ ሀይል ድል ለዚህ ትልቅ መሰረት የሚጥል ነው። አኩርታችሁናልም ብለዋል ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ።
ህግ የማስከበሩ ምእራፍ በድል ተጠናቋል በመጭው ጊዜ ትልቅ ስራ እንደሚጠብቀን አንዘናጋ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ
መረጃው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ነው የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ከሀያ ስምንትኛ፣ ሀያ ዘጠኝኛ እና ስላሳኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ኘሪሚየር ሊግ ውድድር መርሀ ግብር ጋር በተያያዘ በፌዴሬሽኑ ከህግ ውጪ ተወስኖብኛል ስላላቸው ቅጣቶች ልዩ ልዩ ሰነዶችን በአባሪነት በማያያዝ የይግባኝ አቤቱታ በይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜ ውስጥ አስፈላጊው ክፍያ ከተፈፀመበት ደረሰኝ ጋር አቅርቧል። የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴውም የቀረበለትን ጥያቄ በዝርዝር ተመልክቷል።የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ፣ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ተወሰነብኝ በማለት በአስረጂነት ካቀረባቸው ሰነዶች ለመመልከት እንደተቻለው ክለቡ በጨዋታ ላይ ባለመገኘቱ የተወሰነበት የፎርፌ ውጤት ቅጣት ፣ የገንዘብ ቅጣት እና የቡድን መሪው ላይ የተወሰነበት የእገዳ ቅጣት መሆኑ ተገልፃል። የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ይኸ ቅጣት ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዲስኘሊን መመሪያ አንፃር በአግባቡ ታይቶ የተወሰነበት ውሳኔ እንዳልሆነ ያስረዱልኛል ያላቸውን ማስረጃዎች በማያያዝ አቤቱታውን አቅርቧል።በሁለት ሺህ አመተ ምህረት ጥቅምት ወር ተሻሻሎ በወጣው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዲስኘሊን መመሪያ፡ ክፍል ሁለት ፣ ምእራፍ አራት ፣ ከአንቀፅ ሀያ ሰባት ሀያ ዘጠኝ፡ በተፈጥሮ እና በህግ ሰው በሆኑ አካላት ላይ የሚጣሉ የዲስኘሊን እርምጃዎችና ቅጣቶች ምን ምን እንደሆኑ በዝርዝር ተቀምጠዋል። በቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ በኩል ተወስነውብኛል ተብለው የተዘረዘሩት የፎርፌ ውጤት የገንዘብ እና በቡድን መሪው የእገዳ ቅጣቶችም ከላይ በተጠቀሰው የዲስኘሊን መመሪያ ክፍል ውስጥ ከተዘረዘሩት የዲስኘሊን እርምጃዎችና ቅጣቶች መካከል ይገኙበታል።የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴው በቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ በቀረቡት ሰነዶች ላይ ብቻ በመመርኮዝ የጉዳዩን አቅጣጫ ከመመርመር ይልቅ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፅህፈት ቤትት በኩል የዲስኘሊን ኮሚቴውን ውሳኔ ዝርዝር ሁኔታ የሚያሳዩ ቃለጉባኤዎች ፣ ይኸንን ጉዳይ የሚመለከቱ ማናቸውም ከቅዱስ ጊየርጊስ ስፖርት ክለብ ጋር የተደረጉ የደብዳቤ ልውውጦች እንዲሁም የጨዋታዎቹ የዳኞችና የኮሚሽነሮች ሪፖርቶች፣ እንዳቀርቡለት በደብዳቤ ጠይቆ በቃልም በተደጋጋሚ ቢያሳስብም ምላሽ ሳይሰጥ ቆይቶ ከረዥም ሳምንታት በኋላ የተወሰኑ ሰነዶት ከዲስኘሊን ኮሚቴ የፅሁፍ ምላሽ ጋር ቀርበዋል። የቀረቡት ሰነዶች ከመመልከቱ በፊት ይግባግ ሰሚ ኮሚቴው በዋናነት የመረመረው የዲስኘሊን ኮሚቴ በፅሁፍ የተሰጠውን የደብዳቤ ምላስ ነበር።የዲኘሊን ኮሚቴው ምላሽ ዋና ሀሳብ በአጭሩ ሲገለፅ፣ ይኸንን ጉዳይ ለማለት ከቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ጋር በተያያዘ በተጠቀሱት ከሀያ ስምንት ስላሳኛው ሳምንት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ኘሪሚየር ሊግ ውድድሮችን በሚመለከት የቀረበለትም ሆነ ውሳኔ የሰጠበት ምንም አይነት ጉዳይ እንደሌለ ያሳወቀበት ምላሽ ነበር ።ከላይ በተጠቀሰው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዲስኘሊን መመሪያ ፣ በክፍል ሁለት ምእራፍ አንድ፣ አንቀፅ ፣ ተ ቁ ሁለት፣ በግልፅ በተደነገገው መሰረት በእግር ኳስ ዳኛው ከሚፈፅመው የቅጣት ውሳኔ ውጭ አንድ ድርጊት ማስቀጣት የሚችለው የፍትህ አካሉ ህገወጥ ድርጊት መፈፀሙን ከሚመለከታቸው አካላት ሪፖርት ቀርቦለት ሲያረጋግጥና ቅጣት የሚጣልበት ሆና ሲያገኘው ሲሆን በመርህ ደረጃ በመመሪያው መሰረት ጥፋተኛነቱ ካልተረጋገጠ በቀር ሊቀጣ አይችልም። ይላል።አንድ የይግባኝ አቤቱታ የሚያቀርብ ወገን ቀደም ሲል በሚመለከተው የፍትህ አካል ውሳኔ በተሰጠበት እና በዚህ ውሳኔ አልረካሁም ፍትህም አልተከበረልኝም ብሎ ሲያስብ እንደሆነ ግልፅ ነው። በመሆኑም የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴው የቀረበለትን የይግባኝ አቤቱታ በሚመለከት ወደ ዝርዝር ሁኔታ ከመግባቱ በፊት በቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ላይ በዚህ የዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት ቅጣት ተላልፎበታል ማለት ይቻላል ወይስ አይደለም ጉዳዩስ በይግባኝ መታየት ይኖርበታል ወይስ አይደለም በሚሉ ዋና ዋና ነጥቦች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ በመጨረሻ እንደሚከተለው ከድምዳሜ ደርሷል።በቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ የቀረበው የይግባኝ አቤቱታ ጥያቄ ቀደም ሲል በተጠቀሰው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት ጉዳዩ ላይ ቅጣት ውሳኔ የመስጠት ስልጣን በተሰጠው የፍትህ አካል በዲሲፕሊን ኮሚቴው የተወሰነ ባለመሆኑ የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴው የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ተሰጠብኝ ባለው ውሳኔ ዝርዝር ሁኔታ ላይ ውይይት ማድረግ የማይጠበቅበት መሆኑን እንዲሁም በዲሲፕሊን መመሪያው መሰረት በቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ እና በክለቡ የቡድን መሪ ላይ የተወሰነው ምንም አይነት ህጋዊ የዲሲፕሊን ቅጣት የፍትህ ውሳኔ የሌለ በመሆኑ፤ በህግ ስልጣን ከተሰጠው አካል ውጭ የተሰጠን የቅጣት ውሳኔ ውድቅ እንዲደረግ፤ እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ለይግባኝ ያስያዘው ብር አንድ ሺህ አምስት መቶ ብር አንድ ሺህ አምስት መቶ ተመላሽ አንዲደረግለት በማለት ውሳኔ ሰጥቷል።በተጨማሪ ይህንን ጉዳይ በተመለከተ የተደረሰበትን የውሳኔ ግልባጭ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ እና ለሚመለከታቸው አካላት በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፅህፈት ቤትት በኩል በፅሁፍ እንዲደርሳቸው በሚል ውሳኔ አስተላልፏል።
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ውሳኔ በቅዱስ ጊዮርጊስ ይግባኝ ዙርያ
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ሰባትኛ ሳምንት ጨዋታዎች ነገ እና እሁድ በሚደረጉ ጨዋታዎች ይቀጥላል። በተቀራራቢ ደረጃ ላይ የሚገኙ ክለቦች የሚያደርጉት ፍልሚያም ይጠበቃል።የምድብ ሀ ሁሉም ጨዋታዎች እሁድ የሚደረጉ ሲሆን በአንድ ነጥብ ልዩነት በደረጃ ሰንጠረዡ ሁለትኛ እና ሶስትኛ ደረጃ ላይ የተቀመጡት ፋሲል ከተማ እና መቀለ ከተማ ጎንደር ላይ የሚያደርጉት ጨዋታ ከፍተኛ ግምት የሚሰጠው ነው። በባህርዳር ደርቢ ባህርዳር ከተማ ከ አማራ ውሀ ስራ ማክሰኞ ሲጫወቱ መሪው አአ ፖሊስ ሱሉልታ ከተማን እሁድ ያስተናግዳል።በርካታ የአማራ ውሀ ስራ ተጫዋቾች በኢንፍሎዌንዛ በመጠቃታቸው እሁድ ሊያደርጉት የነበረው ጨዋታ ወደ ማክሰኞ ተዘዋውሮላቸዋል። የምድብ ሀ የደረጃ ሰንጠረዥየምድብ ለ ሰባትኛ ሳምንት ጨዋታዎች የሚከተሉት ናቸው።የምድብ ለ የደረጃ ሰንጠረዥ
የከፍተኛ ሊግ ሰባትኛ ሳምንት ጨዋታዎች ነገ እና እሁድ ይደረጋሉ
ኢትዮጵያን ከአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሀያ ስምንት እስከ አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ስላሳ ሶስት አመተ ምህረት ድረስ ወርሮ የነበረው የኢጣሊያ ፋሺስት ሰራዊት፣ ድል የተመታበትን ሰባ አምስትኛ አመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ የድል በአል ምክንያት በማድረግ ሶስት የውጭ አገር ዜጎችን ጨምሮ ለሀያ አምስት ታላላቅ አርበኞች የመታሰቢያ ቴምብር ታተመላቸው። የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት የኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ሰባ አምስትኛ አመት መታሰቢያ የድል በአል በሚል ርእስ ያሳተመው ስድስት አይነት ቴምብሮችን ሀዳር አንድ ቀን ሁለት ሺህ ዘጠኝ አመተ ምህረት በመላ አገሪቱ አሰራጭቷል። አምና በሚያዝያ ሁለት ሺህ ስምንት አመተ ምህረት የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማሀበር የድሉን አልማዛዊ ኢዮቤልዩ በብሄራዊ ደረጃ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ሲያከብር አንዱ እቅዱ የአርበኞች መታሰቢያ ቴምብር ማሳተም ነበር። እንደ ማሀበሩ መግለጫ፣ በቴምብሮቹ ላይ እነማን ይካተቱ በሚለው ጉዳይ ዙሪያ የማሀበሩ የስራ አመራር ምክር ቤት መክሮና ዘክሮበት በስማቸው ቴምብር እንዲታተምላቸው ከብዙዎቹ መካከል የመረጣቸው ሀያ አምስት ናቸው። በአንድ ቴምብር ላይ ከአራት እስከ ስድስት አርበኞችን የሚወክሉ ምስሎችን ወጥተዋል። በመስፈርቶቹ መሰረት ከተመረጡት አርበኞች መካከል ከሀይማኖታዊ ታላቅ ተልእኮአቸው በተጨማሪ የአርበኝነት ግዳጅን በመወጣት በጀግንነት የህይወት መስዋእትነት የከፈሉት የምእራብ ኢትዮጵያ ጎሬ ጳጳስ ብፁእ አቡነ ሚካኤልና የምስራቅ ኢትዮጵያ ጳጳስ ብፁእ አቡነ ጴጥሮስ በመታሰቢያው ቴምብር ተካትተዋል። እንዲሁም ጠላትን ፊት ለፊት ተጋፍጠው የህይወትና የአካል መስዋእትነት እየከፈሉ ካርበደበዱት መካከል ራስ ደስታ ዳምጠው፣ ደጃዝማች ሀይሉ ከበደ፣ ልእልት ከበደች ስዩም መንገሻ እመቤት ሆይ ፣ ደጃዝማች በላይ ዘለቀ፣ ደጃዝማች ሀይለማርያም ማሞ፣ ደጃዝማች ገረሱ ዱኪ፣ ደጃዝማች ባልቻ አባ ነፍሶ፣ ደጃዝማች አፈወርቅ ወልደሰማያት፣ ፊታውራሪ አለማየሁ ጎሹ፣ ሼህ ሆጄሌ አልሀሰን፣ ደጃዝማች ፍቅረማርያም አባተጫንና ኮሎኔል በላይ ሀይለአብ ይገኙበታል። በጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማሀበር ፕሬዚዳንትነት ካገለገሉት መካከል፣ ሁለቱ ቀዳሚዎች ራስ አበበ አረጋይና ራስ መስፍን ስለሺ፤ በፋሺስቱ ሩዶልፍ ግራዚያኒ ላይ የካቲት ቀን አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሀያ ዘጠኝ አመተ ምህረት አደጋ የጣሉት አብርሀ ደቦጭ፣ ሞገስ አስገዶምና ስምኦን አደፍርስ፣ የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ በፋሺስቶች ሲዋረድ፣ መቀበል አቅቷቸው በሮም አደባባይና በኢጣሊያ በረሀዎች ታላቅ ገድል የፈፀሙት ደጃዝማች ዘርአይ ድረስና ኮሎኔል አብዲሳ አጋ በየቴምብሮቹ ምስላቸው ታትሟል። የፋሺስቶች ወረራ አስቆጥቷቸው በአርበኝነት ተጋድሎ ከኢትዮጵያ ጐን ለቆሙ የውጭ ዜጐች እንግሊዛውያኑ ሲልቪያ ፓንክረስት፣ ሜጀር ጀነራል አርዲ ቻርለስ ዊንጌትና አሜሪካዊው ኮሎኔል ሲ ሮቢንሰንም የመታሰቢያ ቴምብሮቹ አካሎች ናቸው። በወቅቱ በነበረው የመንግስታቱ ማሀበር ሊግ ኦፍ ኔሽንስ መቀመጫ ጄኔቭ በመገኘት፣ ለአለም መንግስታት አቤቱታቸውን ያሰሙት ንጉሰ ነገስት ቀዳማዊ ሀይለ ስላሴ አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሀያ ሶስት አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ስልሳ ሰባት ዲስኩር ሲያሰሙ የተነሱት ፎቶም የሀትመቱ አካል ነው። ከሰማኒያ አመታት በፊት፣ ሰኔ ሀያ ሶስት ቀን አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሀያ ስምንት አመተ ምህረት ቀዳማዊ ሀይለ ስላሴ በሸንጎው ላይ ካደረጉት ዲስኩር የሚከተለው ሀይለ ቃል ይገኝበታል። ከእግዚአብሄር መንግስት በቀር የፍጡር መንግስት ሁሉ አንዱ ከአንዱ የማይበልጥ ስራ የለውም። ነገር ግን በምድር ላይ ሀይለኛ የሆነው መንግስት ምንም በደል የሌለበትን የሌላውን መንግስት ህዝብ ለማጥፋት የሚገባው መስሎት በተነሳበት ጊዜ ተጠቂው ወገን ለመንግስታት ማሀበር የተበደለውን የሚያቀርብበት ሰአት ነው። እግዚአብሄር ታሪክ ለምትሰጡት ፍርድ ለመንግስት ማሀበርም ምስክር ሆነው ይመለከታሉ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማሀበር እኔ ለሀገሬ በሚል ርእስ ባዘጋጀው፣ የሰባ አምስትኛ አመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ የድል በአል መታሰቢያ ቴምብሮች መግለጫው ላይ እንደተወሳው፣ በመታሰቢያ ቴምብሩ ላይ ምስሎቻቸው እንዲወጣ የተደረጉት አርበኞች አመራረጥ፣ በተቻለ መጠን ሚዛናዊ የሆነ ሀብረ ብሄራዊና የፆታ ስብጥርን ከግንዛቤ ውስጥ ያስገባ ነው። ይሁን እንጂ ከሀያ አምስትቱ አርበኞች መካከል ሴት አርበኛ አንድ ብቻ መሆናቸው ለምን ያሉ አልታጡም። በአምስቱ ዘመን በተለያዩ ግንባሮች በውጊያው አውድማ ውስጥ ከዘመቱት በሺዎች ከሚቆጠሩት ሴቶች መካከል አንዲት አርበኛ ልእልት ከበደች ስዩም ብቻ ለቴምብሩ በቅተዋል። ሌላው ቢቀር ማሀበሩ ለአልማዝ ኢዮቤልዩ መታሰቢያ ባሳተመው እኔ ለሀገሬ መፅሄት ጀግንንታቸው የተዘረዘረላቸው ፊታውራሪ በላይነሽ ገብረ አምላክ ሁለተኛዋ ለመሆን ለምን አልታደሉም በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሀያ ስምንት አመተ ምህረት በምስራቅ ግንባር ሰርጎ የገባው የፋሺስት ወራሪን ፊታውራሪ በላይነሽ ገብረ አምላክ ሱሪ ታጥቀው፣ ዝናር ታጥቀው ብረት አንግተው ተፋልመዋል። ከፊታውራሪ በላይነሽ ጋር ከ አመታት በፊት ቃለምልልስ ባደረገው እኔ ለሀገሬ መፅሄት አገላለፅ፣ ከወረራው አስር አመት በፊት ያረፉትን የአባታቸውን ፊታውራሪ ገብረአምላክ ውብነህ ማእረግን የያዙት ፊታውራሪ በላይነሽ፣ ከድል በኋላ ቀዳማዊ ሀይለ ስላሴ ዘንድ በቀረቡበት ጊዜ፣ ጃንሆይ ጄኔቭ በነበርንበት ጊዜ፣ በላይነሽ የምትባለው ሴት ትዋጋለች እየተባለ የምንሰማው እሷን ነው ብለው ጠየቁ። ደጃዝማች ይገዙም አዎ ብለው አቀረቡኝ። ጃንሆይም በፈገግታ ተቀበሉኝ። አለሽ እንዴ ማን ትባያለሽ አሉኝ። እኔም፣ ፊታውራሪ በላይነሽ ነኝ አልኳቸው። በስምሽ ተጠሪበት ብለው ሹመቱን አፀደቁልኝ። ፋሺስት ኢጣሊያ ኢትዮጵያን ሲወር ባለቤታቸው በጅጅጋ በኩል ወደ ጂቡቲ ለስደት እንዲሄዱ ቢገፋፏቸው አገራቸውን ትተው እንደማይሄዱና ተጋድሏቸውን እንደሚቀጥሉ ነግረዋቸው የተለዩዋቸውን እኚህን እርመኛ አርበኛ የቴምብሩ ገበታ ሊረሳቸው ባልተገባ ነበር። አደራ ተረካቢ ወካይ የሆኑ ወጣቶችን ጨምሮ በስድስት አይነት የታተሙት ስድስት መቶ ሺህ ቴምብሮች ሲሆኑ፣ የያንዳንዱ ዋጋም ከአንድ ብር እስከ አንድ ነጥብ አምስት ብር መሆኑ ታውቋል። በዳግማዊ ምኒልክ ዘመን አንድ ሺህ ስምንት መቶ ሰማኒያ ስምንት አመተ ምህረት አድዋ ላይ ድል የተመታው የኢጣሊያ ወራሪ ሰራዊት፣ ከአርባ አመት ቆይታ በኋላ በፋሺስቱ ቤኔቶ ሙሶሎኒ አማካይነት ኢትዮጵያን መውረሩና በተለይ በአለም የተከለከለው የመርዝ ጋዝ በመጠቀም የኢትዮጵያን ሰራዊት በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሀያ ስምንት አመተ ምህረት መፈታቱ ይታወሳል። እርመኛ አርበኞች የአገሪቱን ነፃነት ለማስከበር የህዝቡን ልእልና ለማስጠበቅ መራር ተጋድሎ ማድረጋቸውም ባይዘነጋም የፋሺስት ወንጀለኞች በታሀሳስ አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሀያ ስምንት አመተ ምህረት የኢትዮጵያን ሰራዊት የፈቱበት፣ በተምቤንና በሀሸንጌ በመርዝ ጋዝ ያደረሱት እልቂት ይጠቀሳል። ከሰባ አምስት አመታት በፊት የድሉን ብስራት አስመልክተው ባለቅኔው የእንጦጦ ራጉኤሉ ብርሀኑ ድንቄ ከስድስት አሰርታት በፊት በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር የነበሩ ግእዝ ከአማርኛ አጣቅሰው እንዲህ ተቀኝተው ነበር፡ ኢትዮጵያ ከማር ለሚጣፍጥ ለስምሽ አጠራር ሰላም ይገባል። ባምላክ እጅ ለተሰራ ለራስ ፀጉርሽም ሰላምታ ይገባል። ምሳሌ የሌለሽ መቅደስ ኢትዮጵያ፤ ጠላት ኢጣሊያ ስላረከሰሽና መሰዊያሽን ስላጠፋ ፈንታ፣ ከእንግዲህ ወዲህ ተቀደሽ፣ ሀይልንም ገንዘብ አድርጊ። እኚሁ ሊቀ ሊቃውንት ብርሀኑ ድንቄ እንዲህ እያሉም ዘመሩላት። እናታችን ኢትዮጵያ ሆይ ለታረዙ ልብስ ነሽና በባንዲራሽ ጥላ ሰብስቢ ልጆችሽን
ለሀያ አምስት ታላላቅ አርበኞች የመታሰቢያ ቴምብሮች ታተሙ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ ሀያ ስምንት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ አሜሪካ ለታይዋን የጦር መሳሪያዎችን ልትሸጥ አይገባም ስትል ቻይና በፅኑ ተቃውማለች። ባሳለፍነው መጋቢት ወር አሜሪካ የስድስት መቶ ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር የጦር መሳሪያዎችን ለታይዋን ለመሸጥ ማፅደቋ ይታወሳል። የቻይና የመከላከያ ሚስቴር ቃል አቀባይ ታን ኬፌይ ዛሬ በሰጡት መግለጫ አሜሪካ ከታይዋን ጋር ያላትን ወታደራዊ ግንኙነት በአስቸኳይ እንድታቋርጥ አሳስበዋል። የቻይና እና የታይዋን ጉዳይ የውስጥ ጉዳይ በመሆኑ አሜሪካ ጣልቃ ገብታ ውጥረቱን ከማባባስ እንድትታቀብ ጠይቀዋል። የአሜሪካ ጣልቃ ገብነት የአንድ ቻይናን መርሀ የሚጥስና ሶስቱን የቻይና አሜሪካ የጋራ የግንኙነት ድንጋጌዎች ያላገናዘበ ስለመሆኑም አስገንዝበዋል። የቻይና ጦር ማንኛውንም ትንኮሳ ለመመከት ዝግጁ ስለመሆኑ ማረጋገጣቸውን ጠቅሶ ሲጂቲ ኤን ዘግቧል።
ቻይና አሜሪካ ለታይዋን የጦር መሳሪያ እንዳትሸጥ ተቃወመች
ክርስቲያን ኤይድ የተሰኘው በጎ አድራጎት ድርጅት ባወጣው ሪፖርት መሰረት አለማችን እየተጠናቀቀ ባለው የፈረንጆቹ አመት በከፋ የአየር ንብረት ለውጥ መመታቷን አስታወቀ። ድርጅቱ በሁለት ሺህ ሀያ የተከሰቱ እና በአለማችን ላይ ከፍተኛ የሰብአዊ ቀውስ ያስከተሉ አስር ጉልህ ክስተቶችን መርጧል። ከእነዚህ መካከል ስድስቱ በእስያ የተከሰቱ ሲሆኑ በቻይናና በህንድ የተከሰተው የጎርፍ አደጋ ከአርባ ቢሊዮን ዶላር በላይ ውድመት አስከትሏል ሲል ያትታል። በአሜሪካ የተከሰተው ከባድ አውሎ ንፋስ እና ሰደድ እሳት ደግሞ ወደ ስልሳ ቢሊዮን ዶላር ኪሳራ አድርሷል። አለም በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ እግር ተወርች ተይዞ መላወሻ ባጣበት ወቅት የአየር ንብረት ለውጥ ደግሞ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ሆኖበት ነበር ይላል ሪፖርቱ። ክርስቲያን ኤይድ አስር ከባድ አውሎ ነፋሶችን፣ ሰደድ እሳቶችንና ጎርፎችን በመጥቀስ በአጠቃላይ አንድ ነጥብ አምስት ቢሊዮን ዶላር ውድመት አስከትለዋል ብሏል። አክሎም ከእነዚህ መካከል ዘጠኙ አምስት ቢሊዮን ዶላር ውድመት አድርሰዋል ሲል ያክላል። በህንድ ለወራት በዘለቀው እና ከባድ ዝናብ ባስከተለው ከባድ ጎርፍ ከሁለት ሺህ በላይ ሰዎች ህይወታቸውን ሲያጡ ሚሊዮኖች ደግሞ ቀያቸውን ጥለው ተሰድዷል። የመድን ዋስትና የተገባለት ንብረት ላይ የደረሰው ኪሳራ ብቻ ሲገመትም አስር ቢሊዮን ዶላር ይሆናል ተብሏል። ቻይና በጎርፍ አደጋ ብቻ ከፍተኛ የሆነ የምጣኔ ሀብት ቀውስ ገጥሟታል። በእርግጥ በሰው ህይወት ላይ የደረሰው አደጋ ከህንድ ጋር ሲነጣፀር አነስተኛ ቢሆንም፣ ከሰኔ እስከ ጥቅምት ወር ድረስ ስላሳ ሁለት ቢሊዮን ዶላር ኪሳራን ያስተናገደችው በጎርፍ የተነሳ ነው። እነዚህ አደጋዎች ቀስ በቀስ ተከስተው ውድመት ያደረሱ ሲሆን፣ ሌሎች ደግሞ በድንገት ተከስተው ከፍተኛ ጥፋት ያደረሱም ነበሩ። ለዚህ ተጠቃሹ በግንቦት ወር የቤንጋል የባህር ዳርቻን የመታው ሳይክሎን አምፋን ሲሆን፣ በጥቂት ቀናት ብቻ ቢሊየን ዶላር የተገመተ ንብረት አውድሟል። የአየር ንብረት ለውጥ በትሩን ካሳረፈባቸው አህጉራት መካከል አፍሪካ አንዷ ናት። በአህጉሪቷ የተከሰተው የበረሀ አንበጣ ወረርሽኝ ስምንት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ ሰብልን አውድሟል። የተባበሩት መንግስታት የበረሀ አንበጣ ወረርሽኙን ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ያያዘው ሲሆን፣ ከቅርብ አመታት ወዲህ በአፍሪካ ቀንድ እና በመካከለኛው ምስራቅ የተከሰቱ ከባድ ዝናቦች ለበረሀ አንበጣው መከሰትና መስፋፋት ምክንያት ሆነዋል ብሏል። አውሮፓም በሁለት ሺህ ሀያ ሲያራ የተሰኘ አውሎ ነፋስ ክፉኛ ጎድቷታል። ይህ አውሎነፋስ አየርላንድ፣ ዩናይትድ ኪንግደም እንዲሁም በርካታ አገራትን ባለፈው አመት የካቲት ወር ላይ አጥቅቷል። ይህ ከባድ አውሎ ነፋስ የ ሰዎችን ህይወት ሲቀጥፍ ሁለት ነጥብ ሰባት ቢሊዮን ዶላር የተገመተ ንብረት አውድሟል። ክርስቲያን ኤይድ በሪፖርቱ ላይ በገንዘብ ተገምተው የተቀመጡት ቁጥሮች የመድን ዋስትና በተገባላቸው ንብረቶች ላይ የደረሱ ኪሳራዎች ብቻ ዝቅ ተደርጎ ተሰልተው ነው ብሏል። ስለዚህ የጉዳቱ መጠን ከዚህ ከፍ ሊል የሚችልበት እድል ሰፊ ነው። በሀብት የደረጁ አገራት ከፍተኛ ዋጋ የሚያወጣ ንብረት ስላላቸው በተፈጥሮ አደጋዎቹም የሚደርስባቸው ጉዳት በዚያው ልክ ከፍ ያለ ይሆናል ሲል አስቀምጦታል። በእንደዚህ አይነት የተፈጥሮ አደጋዎች ወቅት የገንዘብ ኪሳራ ብቻ የጉዳቱን መጠን አያሳይም። ለምሳሌ በደቡብ ሱዳን የደረሰው የጎርፍ አደጋ የአንድ መቶ ስላሳ ስምንት ሰዎችን ህይወት የቀጠፈ ሲሆን፣ የዚህ አመት የምርት ዘመንን ሰብል ሙሉ በሙሉ አውድሞታል። ስለዚህ ኪሳራው በገንዘብ ተሰልቶ የሚቀመጥ አለመሆኑን ሪፖርቱ ያሳያል። ተመራማሪዎች እንደሚሉት የአየር ንብረት ለውጥ ተፅእኖ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየበረታ የመጣ እና ቀጣይነት ያለውም ነው ብለዋል። ከቀናት በኋላ በሚጀምረው የፈረንጆቹ አዲስ አመትም የአየር ንብረት ተፅእኖው ይቀጥላል ተብሎ የተገመተ ሲሆን፤ ነገር ግን ከሁለት ሺህ ሀያ በተለየ የፖለቲካ መሪዎች የከባቢ አየር ሙቀት መጨመርን ለመዋጋት የተሻለ እርምጃ ይወስዳሉ ተብሎ ተስፋ ተደርጓል። የጆ ባይደን የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሆኖ መመረጥ፣ የኮቪድ ወረርሽኝ መከሰት እና አረንጓዴ እፀዋት እንዲያገግሙ ያሳረፈው በጎ ተፅእኖ እንዲሁም የመብት ተሟጋቾች ውትወታ አገራት የአለማችንን ሙቀት ለመቀነስ እና ወደ ተሻለ ነገ ለሚደረገው ጉዞ የሚጠቅመውን ይወስናሉ ለሚለው ተስፋን ፈንጥቋል።
በፈረንጆቹ ሁለት ሺህ ሀያ ከባድ የአየር ሁኔታ አለምን ለኪሳራ ዳርጓታል ተባለ
ሪፖርተር መጋቢት አራት ቀን ሁለት ሺህ አምስት አመተ ምህረት የተቃውሞ ደብዳቤ ለፓትርያርክ ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ያቀረቡት የቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች፣ ላለፉት አስር ቀናት ትምህርታቸውን ከማቆማቸውም በተጨማሪ፣ ከመጋቢት ቀን ሁለት ሺህ አምስት አመተ ምህረት ምሽት ጀምሮ የረሀብ አድማ ማድረጋቸው ዛሬ አዲስ አበባ ላይ ታትሞ የወጣው ሪፖርተር ጋዜጣ ዘገበ። እንደሪፖርተር ጋዜጣ ዘገባ ተማሪዎቹ ያቀረቡት የተቃውሞ ደብዳቤ ለአንድ ሳምንት ምላሽ ስለተነፈገው፣ መጋቢት ቀን ሁለት ሺህ አምስት አመተ ምህረት ፓትርያርኩ በሚያስቀድሱበት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ቤተ ክርስቲያን፣ ልብስ ተክህኖ ለብሰው በመሄድ ቢጠብቋቸውም፣ ፓትርያርኩ ያለወትሮአቸው ሳይገኙ መቅረታቸውን ደቀ መዛሙርቱ ተናግረዋል። ከመልካቸው በስተቀር መጠሪያቸውና ማንነታቸው የማይታወቁ ግለሰቦች፣ አመልካች ጣታቸውን እየቀሰሩ ሊያስፈራሯቸው መሞከራቸውን የገለፁት ተማሪዎቹ ጥያቄያቸው ተገቢና አስፈላጊ በመሆኑ ምላሽ እስከሚሰጣቸው ድረስ የረሀብ አድማውንና ትምህርት ማቆማቸውን እንደሚገፉበት ተናግረዋል ያለው የጋዜጣው ዘገባ ፓትርያርኩን በፅህፈት ቤታቸው ተገኝተው ለማነጋገር ለመጋቢት ስድስት ቀን ሁለት ሺህ አምስት አመተ ምህረት በንቡረእድ ኤልያስ አብርሀ በኩል ቀጠሮ ተይዞላቸው እንደነበር የገለፁት ተማሪዎቹ፣ በእለቱ ለመግባት ሲሞክሩ የሲኖዶስ አባላት ስብሰባ ላይ ናቸው በማለት በጥበቃ ሰራተኞች መከልከላቸውን ተናግረዋል ብሏል። ከኮሌጁ ሀላፊዎች ጋር ሊያወያዩአቸው ወደ ኮሌጁ የመጡ የጠቅላይ ቤተ ክህነትና የመንግስት ባለስልጣናት፣ ተማሪዎቹ ያነሷቸውን ጥያቄዎች በማቅረብ ከማወያየት ይልቅ፣ ለመሸምገል መሞከራቸው እንዳሳዘናቸው የገለፁት ተማሪዎቹ እነሱንና የኮሌጁን ሀላፊዎች ሊያስማሟቸው የሚችሉት ያነሷቸውን ጥያቄዎች በመመልከት መፍትሄ እንዲያገኙ ሲያደርጉ ብቻ መሆኑን አሳውቀዋል። ተማሪዎቹ ምግብ የማይበሉና ትምህርታቸውን የማይማሩ ከሆኑ የተሰጣቸውን ብርድ ልብስ፣ አንሶላና መታወቂያ አስረክበው የኮሌጁን ግቢ እንዲለቁ የኮሌጁ አስተዳደር ማስታወቂያ ማውጣቱ ግርምት እንደፈጠረባቸውም ገልፀዋል። ተማሪዎቹ ላቀረቧቸው ጥያቄዎችና በረሀብ አድማ ላይ ስለመሆናቸው ኮሌጁም ሆነ ቤተክህነት ምን እያደረጉ እንደሚገኙ ማብራሪያ እንዲሰጡን የኮሌጁ የበላይ ጠባቂ አቡነ ጢሞቲዎስን፣ የስልጠናና ትምህርት ዋና ክፍል ሀላፊውን አባ ሰረቀንና የጠቅላይ ቤተ ክህነት ስራ አስኪያጅ አቡነ ፊሊጶስን አግኝተን ለማነጋገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካልንም ሲል ሪፖርተር ዘገባውን ቋጭቷል።
የቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች ከትምህርት ማቆም አድማው በተጨማሪ የረሀብ አድማ ጀመሩ
አዲስ አበባ፣ መስከረም ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በጋይንት እና አካባቢው የህውሀት የሽብር ቡድን በግፍ ለተረሸኑ እና ሀገራችን አናስደፍርም ብለው አንገት ለአንገት ተናንቀው ህይወታቸው ላጡ ቤተሰቦች በውጭ ሀገር በሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ድጋፍ ተደርጓል። ድጋፉ ለተሰው፣ ለቆሰሉ እና ለተደፈሩ ሴት እህቶች እና እናቶቻችን መከታ ለወገን ከተሰኝ በውጭ ሀገር እና በሀገር ውስጥ ከሚገኙ ወገኖች የተሰበሰበ ገንዘብ ድጋፍ ተደርጓል። የደቡብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቀለምወርቅ ምህረቴ፥ የተሰው ወገኖች ለሀገር ክብር ሲሉ በመዋደቃቸው ሁሌም ሲታወሱ ይኖራሉ እኛም ከተጎዱ ወገኖች ጎን ነን ብለዋል። የደቡብ ጎንደር ዞን የብልፅግና ፖርቲ ሀላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ፥ ትግሉ አለበቃም አሁንም ከህዝቡ ጋር በመሆን ትግላችን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። በስነስርአቱ ላይ የተገኙት የስላሳ አራትኛ ክፋለጦር አመራር ኮሎኔል ሽጉጤ አቡሀይ ፥የህውሀት የሽብር ቡድን ሰርጎ በገባባቸው አካባቢዎች በርካታ ጥፍቶችን አድርሷል። በዚህም በርካታ የጋይንት እና አካባቢው ነዋሪዎች በጀግንነት ተሰውተዋል ነው ያሉት። የህዝቡ ደጀንነት ለሰራዊቱ ትልቅ ነበር ያሉት ኮሎኔል ሽጉጤ፥ ትግሉ አሁንም አላበቃም ድጋፋችሁን አጠናክራችሁ ቀጥሉ የመከላከያ ሰራዊት በጥሩ ቁመና ላይ ይገኛል ብለዋል። በስነስርአቱ በውጭ የሚኖሩ የአካባቢው ተወላጆች ነዋሪዎች የሀይማኖት አባቶች ጨምሮ የተጎጂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል። በምንይችል አዘዘው ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ ድረ ገፅ፦ ፌስቡክ፡ ዩትዩብ፦ ቴሌግራም፦ ትዊተር፦ በመወዳጀት ይከታተሉን። ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
በህወሀት የሽብር ቡድን በግፍ ለተረሸኑ መታሰቢያ እና ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ ተደረገ
በአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ እየተመሩ በርካታ ዝውውሮችን ከፈፀሙ በኋላ ከነባሮቹ ጋር በማቀናጀት ያለፉትን ሳምንታት በሆሳእና ከተማ ቅድመ ዝግጅታቸውን እየሰሩ የሚገኙት ሀድያ ሆሳእናዎች ሁለት የውጪ ዜግነት ያላቸውን ተጫዋቾች ወደ ክለቡ አምጥተዋል።የመጀመሪያው ፈራሚ ከአራት አመታት በሀላ ዳግም ወደ ኢትዮጵያ የተመለሰው አይዛክ ኢሴንዴ ነው። የሀገሩን ክለብ ቪክቶርን ለቆ ከስድስት አመት በፊት ወደ ኢትዮጵያ ከመጣ በሀላ ቅዱስ ጊዮርጊስን በመቀላቀል በክለቡ አምስት አመታት አስደናቂ ብቃቱን ሲያሳይ እንደነበር ይታወሳል። በዩጋንዳ ብሄራዊ ቡድን ውስጥ በተደጋጋሚ ተጠርቶ መጫወት የቻለው አይዛክ ፈረሰኞቹን ከለቀቀ በሀላ ወደ ዛምቢያ አምርቶ በቢውልድኮን፣ በሀገሩ ክለብ ቡሶጋ ዩናይትድ እንዲሁም ያለፈውን አመት በህንዱ ትራሁ ክለብ ተጫውቶ ካሳለፈ በሀላ ሀድያ ሆሳእናን ተቀላቅሏል።ሌላኛው ፈራሚ ጋናዊው ተከላካይ ሊ አዲ ነው። በእግርኳስ ህይወቱ በአስራ አንድ ክለቦች ውስጥ መጫወት የቻለው ይህ የስላሳ አመት ተጫዋች ለሀገሩ ብሄራዊ ቡድን ተጫውቶ ያሳለፈ ሲሆን በክለብ ደረጃ ያለፉትን አራት አመታት በዛምቢያው ሉሳካ ዳይናሞስ እና በደቡብ አፍሪካው ፍሪ ስቴትስ ቆይታ ካደረገ በሀላ ሀድያ ሆሳእናን ተቀላቅሏል። ሶከር ኢትዮጵያ
ሀድያ ሆሳእና ሁለት የውጪ ዜጋ ተከላካዮችን አስፈረመ
በሀዳር ወር ሁለት ሺህ አመተ ምህረት ይካሄዳል ተብሎ ከታቀደው የደቡብ ክልል የሲዳማ ዞን ህዝበ ውሳኔ አስቀድሞ አስተዳደራዊና ህጋዊ ማእቀፎች በማዘጋጀት፣ እንዲሁም ተአማኒ በሆነ የጊዜ ሰሌዳ ላይ አስቀድሞ መግባባት ላይ በመድረስ ህዝበ ውሳኔውን ለማካሄድ የሚያስችል ምቹ የፖለቲካ ሁኔታ ለመፍጠር አፋጣኝ እርምጃ መውሰድ እንደሚያስፈልግ፣ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ ዶክተር አሳሰቡ። ዋና ኮሚሽነሩ ይህን ማሳሰቢያ የሰጡት ከመስከረም ሰባት እስከ ዘጠኝ ቀን ሁለት ሺህ አመተ ምህረት በሀዋሳ ከተማ ያደረጉትን የስራ ጉብኝት አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ ወቅት ነው። በሀምሌ ወር ሁለት ሺህ አመተ ምህረት ከሲዳማ ዞን የክልልነት ጥያቄ ጋር ተያይዞ በተነሳው ግጭት ምክንያት በፖሊስ ቁጥጥር ስር የሚገኙ ዜጎችን የጎበኙት ዋና ኮሚሽነሩ ከጉብኝቱ በኋላ፣ ለችግሩ መነሻ የሆነው ዋነኛ ምክንያት በሲዳማ ዞን ምክር ቤት ለቀረበው የክልልነት ጥያቄ በሚመለከታቸው አካላት ሲሰጥ የነበረው ምላሽ ወቅታዊና ስልታዊ አለመሆን፣ በሌላ በኩል ጥያቄውን በተናጠል ውሳኔና በሀይል ጭምር ለማስፈፀም የፈለጉ ቡድኖች ባራመዱት አስተሳሰብ የተነሳ የተፈጠረ የፖለቲካ ውጥረትና ቀውስ በመሆኑ ነው፤ በማለት፣ አሁንም ከመጪው ሀዳር ህዝበ ውሳኔ አስቀድሞ ምቹ የፖለቲካ ሁኔታ መፍጠሩ አስፈላጊ መሆኑን አበክረው አሳስበዋል። ዋና ኮሚሽነሩ በሀዋሳ ከተማ የተገኙት በአገሪቱ ውስጥ እየተካሄደ የሚገኘውን አዲስ የፖለቲካ ምእራፍና ራእይ ምክንያት፣ በኮሚሽኑ ውስጥም ስለሚደረገው የለውጥ መርሀ ግብር ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር ለማድረግ መሆኑን ኮሚሽኑ ለሪፖርተር በላከው መግለጫ አስታውቋል። በቆይታቸውም በሀዋሳ ከተማ ፖሊስ ፅህፈት ቤት ድንገተኛ ጉብኝት ማድረጋቸው የተገለፀ ሲሆን፣ በዚሁ ጉብኝታቸው ወቅትም በሀምሌ ወር ተከስቶ በነበረው ግጭት ምክንያት በቁጥጥር ስር የሚገኙ እስረኞችንና የአያያዛቸውን ሁኔታ ከመጎብኘታቸው ባለፈ ከክልሉ ርእሰ መስተዳደር፣ ከክልሉ ምክር ቤቶች አፈ ጉባኤዎች፣ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና ከመገናኛ ብዙሀንም ጋር ተገናኝተው በሰብአዊ መብቶች ላይ ውይይት ማድረጋቸው ተገልጿል። በሀምሌው ግጭት ተጎጂ ከነበሩ ቤተሰቦች ጋርም ውይይት ያደረጉት ዋና ኮሚሽነሩ፣ በግጭቱ የተጎዱ ሰዎችንና ቤተሰቦችን በተገቢ መጠን ከመርዳትና መልሶ ከማቋቋም በተጨማሪ፣ የምርመራው በፍጥነት መጠናቀቅ አፋጣኝ ትኩረት ይሻል፤ በማለት፣ ምርመራው በፍጥነት መጠናቀቅ እንደሚኖርበት አሳስበዋል። ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽንና ከሌሎች ምንጮች በተገኘው መረጃ መሰረት እስካሁን በተደረገው የፖሊስ ምርመራ በሶስት ማእከላት በእስር ይገኙ ከነበሩ ወደ አንድ አምስት መቶ ገደማ እስረኞች ውስጥ ከግማሽ በላይ መለቀቃቸውን ተረድተናል፤ በማለት ኮሚሽኑ በመግለጫው አስታውቋል። ፖሊስና አቃቤ ህግ በጋራ እያካሄዱ ባሉት የምርመራ ስራ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከእስር እንዲለቀቁ ማስቻሉ ጥሩ እርምጃ ነው፤ በማለት ኮሚሽኑ አስታውቆ፣ ነገር ግን ለችግሩ መነሻ ለሆኑ ጉዳዮች በቅጡ መፍትሄ መስጠት አስፈላጊ መሆኑንም ጠቁሟል። ዋና ኮሚሽነሩ ኮሚሽኑን በአዲስ መልክ በማደራጀትና በማጠናከር ነፃ የሰብአዊ መብት ተቋም አድርጎ ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት፣ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በየደረጃውና በየክልሉ የሚደረገው ምክክር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ከሲዳማ ዞን ህዝበ ውሳኔ በፊት ምቹ የፖለቲካ ሁኔታ እንዲፈጠር አሳሰበ
ከኢሳያስ ከበደ ላለፉት አመታት የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት በመሆን ከአበባ መቁረጥና መትከል ከእንግዳ መቀበልና መሸኘት በስተቀር አንዳችም ስልጣን ያልነበራቸውን ፕሬዚዳንት ግርማ ወጊዮርጊስን በመሸኘት አዲስ አበባ ቆራጭ ፕሬዚዳንት እንደሚመረጥ የኢህአዴግ ፓርላማ አፈጉባኤ አቶ አባዱላ ገመዳ አስታውቀዋል። እንደ አስተያየት ሰጪዎች ገለፃ ለፕሬዚዳንትነት የሚመረጠው ሰው ከፓርላማው ውጭ ያለም ሰው ሊሆን እንደሚችል የተገለፀ ሲሆን ፕሬዚዳንት የሚለው ስያሜ ከአበባ መቁረጥ ያለፈ ስልጣን ስለሌለው በርከት ያሉ ኢትዮጵያውያን ጉዳይም አይሰጣቸውም። ፕሬዚዳንቱ ተፅእኖ ፈጣሪ ቢሆንና ከአበባ መቁረጥ ያለፈ ስልጣን ቢኖረው የሰዎች መነጋገሪያ ሊሆን የሚችል ቢሆንም ሟቹ አቶ መለስ ዜናዊን የስልጣን ዘመን ለማራዘም ተብሎ የተቀረፀ ህገመንግስት ነው ሀገሪቱ ያላት። የአበባ ቆራጭነቱን ስልጣን እንደተቆናጠጡ መቶ አለቃ የሚለውን ስም አትጠቀሙ ፕሬዚዳንት ግርማ በሉኝ ያሉት መቶ አለቃ ግርማ ወጊዮርጊስ በመንግስታዊው ሚዲያዎች ለቀጣዩ አበባ ቆራጭ ስልጣናቸውን ሲያስረክቡ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ተደረገ ተብሎ ሊዘግብላቸው ሰአታት የቀሯቸው ሲሆን በዚህ ዋዜማ ከመንግስታዊው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ለቀረበላቸው ጥያቄ የሰጡት ምላሽ ብዙዎችን በሹፈት እንዲመለከቱት እያደረገ ነው። የአዲስ ዘመኑ ጋዜጠኛ ዳንኤል ንጉሴ መቶ አለቃ ግርማን በህይወቴ ያዘንኩባት ቀን አቶ መለስ ዜናዊ የሞቱበት ቀን የተደሰትኩበት ቀን ደግሞ ግንቦት ነው እንዲሉት ፈልጎ በህይወትዎ ያዘኑበትና የተደሰቱበት ቀን የቱ ነው በሚል ላቀረበላቸው ጥያቄ መቶ አለቃ ግርማ የሰጡት መልስ የሚከተለው ነውአዲስ ዘመን በጣም ያዘኑበትና የተደሰቱበት ቀንፕሬዚዳንት ግርማ በራሴ ጉዳይ ያዘንኩበት ቀን የለም። አድርጌው ቢሳካልኝ ለአገር ይጠቅም ነበር ብዬ የተበላሸብኝ ጉዳይ ግን አለ። ይሀውም የሲቪል አቪዬሽን ዋና ዳይሬክተር በነበርኩበት ጊዜ ሞንቲሪያ ካናዳ እመላለስ ነበር። ያኔ የአዲሱ ቦሌ አየር ማረፊያ ግንባታ ተጠናቆ ነበር። በዚህም አሮጌው አውሮፕላን ማረፊያ ባዶ ይሆን ነበር። አለም አቀፍ አቪዬሽን ድርጅት አፍሪካኖችን ለማሰልጠን አንድ የማሰልጠኛ ቦታ በኮትዲቯር በምስራቅ አፍሪካ አሩሻ ላይ ነበራቸው። ለኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽንም አንድ አስተማሪ ልከውልን ያሰለጥኑ ነበር።እኔ አዲስ አበባ የበረራ ኮሌጅ እንዲኖራት ፍላጎት ነበረኝ። የቋንቋ ችግር አለመኖሩንም አስረዳኋቸው። አሮጌ አውሮፕላን ማረፊያውን በሙሉ በነፃ ለመስጠትም ተስማማን። ግብዣውንም ተቀበሉ። ሁኔታውን ለመንግስት ካስረዳሁና መንግስት ካፀደቀው በኋላ ነው እንግዲህ ግብዣው ስራ ላይ የሚውለው። አዲስ አበባ ስመጣ ግን ወንበሬ ተሰብሮ ነው የጠበቀኝ። ከሲቪል አቪዬሽንም እንድወጣ ተደረግሁ።አዲስ ዘመን ለምንፕሬዚዳንት ግርማ ከአሜሪካኖች ጋርም እጣላ ነበር። በመሆኑም ከሙያው ውጪ አደረጉኝ። በዚህም አልተናደድኩም። አልተቃጠልኩም አልታመምኩም። ያቀድኩት ነገር ተግባራዊ ባለመሆኑ ግን አዝኛለሁ። በእኔ ቦታ ሰው ለመተካት ስድስት ወር ፈጅቶባቸዋል። እኔን ለመተካት ግን ቀላል ነበር እነ አላምረው ወልደማርያም ዋጋዬ ሀጎስ የመሳሰሉ የአቪዬሽን ሰዎች ነበሩ ግን የተፈለገው አሜሪካንን የሚወድ ሰው ነው።ከስድስት ወር በኋላ በእኔ ቦታ የተተካው ሰው እኔ የጀመርኩትን እንቅስቃሴ ጥቅሙንና አላማውን በደንብ አልተገነዘበውምአልተረዳውም። የእኔን ግብዣአንድ እብድ መቶ አለቃ ያመጣብን ጣጣ ነውና ይሻሩልን ብሎ ለንጉሱ አቅርቦ አሻረው። ይሄ በጣም ያሳዝነኛል። ከእዚያ ውጪ ሁልጊዜ ደስተኛ ነኝ። ሲያወጡኝም ሲያወርዱኝም ደስ ብሎኝ እቀበላለሁ። የፊታችን ሰኞ የሚሾመውና ለሚቀጥሉት አመታት አበባ ሲቆርጥ የሚከርመው ሰው ማን ይሆን
የፊታችን ሰኞ የኢህአዴግ ፓርላማ አበባ ቆራጭ ይሾማል
የካቲት ዘጠኝ ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅና ተግባራዊ መሆን የሚገባቸውን ድንጋጌዎች ተላልፈዋል ተብለው በኮማንድ ፖስቱ ታስረው የከረሙት፣ የኦሮሚያ ክልል ልዩ አድማ በታኝ ፖሊስ ምክትል አዛዥ፣ የፍትህ ቢሮ ኮሙዩኒኬሽን ሀላፊና የአምቦ ዩኒቨርሲቲ መምህር ከእስር ተፈቱ። በኮማንድ ፖስቱ ተጠርጥረው ላለፉት ስላሳ ዘጠኝ ቀናት በእስር ላይ የከረሙት ምክትል አዛዡ ኮማንደር ኢሳያስ አንጋሱ፣ የፍትህ ቢሮ ኮሙዩኒኬሽን ሀላፊ አቶ ታዬ ደንዷ፣ በአምቦ ዩኒቨርሲቲ ወሊሶ ካምፓስ መምህርና ጦማሪ ስዩም ተሾመ ናቸው። የኦሮሚያ ክልል ልዩ አድማ በታኝ ፖሊስ ምክትል አዛዥ ኮማንደር ኢሳያስ ለእስር የተዳረጉት፣ ከሶማሌ ልዩ ፖሊስ ጋር ያጋጠመውን ግጭት መልካም በሆነ መንገድ ለመፍታት ጥረት ባለማድረግና ከፌዴራል ፖሊሶችም ጋር በስምምነት ለመስራት ፈቃደኝነታቸውን አላሳዩም ተብለው መሆኑን፣ ሪፖርተር ካገኘው መረጃ ለማወቅ ተችሏል። ኮማንደሩ በቁጥጥር ስር የዋሉት የካቲት ሀያ ስምንት ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ሲሆን፣ በእለቱ በሀረር የነበሩ ተፈናቃዮችን ወደ ተዘጋጀላቸው መጠለያ ለመውሰድ በሄዱበት ወቅት መሆኑም ተጠቁሟል። በቁጥጥር ስር ከዋሉ በሀላ ወደ አዲስ አበባ ፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ማእከል ማእከላዊ ተወስደው ከቆዩ በኋላ፣ ማእከላዊ ሲዘጋ በትውስት ለጊዜው በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እስረኛ ማቆያ ውስጥ እንዳሉ፣ ሰኞ ሚያዝያ ስምንት ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ከእስር መፈታታቸው ተረጋግጧል። የኦሮሚያ ክልል ፍትህ ቢሮ ኮሙዩኒኬሽን ሀላፊ አቶ ታዬ ደንዷ የታሰሩት፣ በሞያሌ ከተማ በመከላከያ ሰራዊት አባላት መጋቢት አንድ ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ስለተገደሉ ወገኖች በሰጡት መግለጫ ምክንያት መሆኑ ይታወሳል። አቶ ታዬ በወቅቱ በሰጡት መግለጫ፣ በሞያሌ ነዋሪዎች ላይ የተፈፀመው ግድያ ሆን ተብሎና በፌዴራል መንግስት የተፈፀመ መሆኑን በመናገራቸው መሆኑም ተጠቁሟል። አቶ ታዬ ህዝብንና መንግስትን ሆን ብለው ለማጋጨት ያልተጣራ መረጃ በማሰራጨትና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ድንጋጌ ተላልፈዋል ተብለው ታስረው ከርመዋል። እሳቸውም ሚያዝያ ስምንት ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ከእስር ተለቀው ከቤተሰቦቻቸው ጋር ተቀላቅለዋል። በአምቦ ዩኒቨርሲቲ የወሊሶ ካምፓስ መምህርና ጦማሪ ስዩም ተሾመ፣ የካቲት ሀያ ዘጠኝ ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ከመኖሪያ ቤታቸው ተይዘው በእስር ላይ ቆይተዋል። የጦር መሳሪያ ቤትህ ውስጥ ሸሽገሀል፤ ተብለው ቤታቸው በመከላከያ ሰራዊት ተከቦ መያዛቸውን የገለፁት መምህር ስዩም፣ ቤታቸው ከተፈተሸና ምንም አይነት መሳሪያ እንደሌለ ሲረጋገጥ የተጠረጠሩበት ጉዳይ ወደ ሌላ መቀየሩን ለሪፖርተር ተናግረዋል። የጦር መሳሪያው ሲጠፋ መንግስትንና ህዝብን የሚጋጭ መጣጥፍ በማዘጋጀት ሁከት እየፈጠርክ ነው፤ ተብለው መጀመርያ ሰበታ ወደሚገኘው የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ካምፕ መወሰዳቸውን አስረድተዋል። በመቀጠልም ወደ ፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ማእከል ማእከላዊ ተወስደው መታሰራቸውን የገለፁት መምህር ስዩም፣ የካቲት ስላሳ ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት በፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ወንጀል ችሎት እንደቀረቡ ጠቁመዋል። በወንጀል መጠርጠራቸውንና ቀሪ ምርመራ እንዳለባቸው መርማሪ ቡድኑ ለፍርድ ቤቱ ገልፆ፣ ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ሲጠይቅ እንደተፈቀደለትም አክለዋል። በቀጣይ ቀጠሮ ግን እሳቸው ሳይቀርቡ መርማሪው ፍርድ ቤት ቀርቦ ተጠርጣሪው የታሰሩት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ድንጋጌ ተላልፈው በመሆኑ፣ ጉዳዩ የሚታየው በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መሰረት በሚቋቋመው ፍርድ ቤት እንደሆነ አስረድቶ መዝገቡን ማዘጋቱን መምህር ስዩም ገልፀዋል። ከመጋቢት ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት በኋላ በማእከላዊ ታስረው መክረማቸውንና አልፎ አልፎ ዘለፋና ማስፈራራቶች ቢደርስባቸውም አካላዊ ጉዳት እንዳልደረሰባቸው ተናግረዋል። በመጨረሻ ሰኞ ሚያዝያ ስምንት ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ከኮማንድ ፖስቱ የተላከ ደብዳቤ መጥቷል ተብሎ በአደራ ከታሰሩበት አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እስረኛ ማቆያ ቦታ ተጠርተው ማእከላዊ በመዘጋቱ ፣ በምርመራ ወቅት የሰጡትን ቃል ፈፅመሀል አልፈፀምክም የሚል ጥያቄ ቀርቦላቸው አልፈፀምኩም፤ በማለት መለቀቃቸውን አስረድተዋል። መርማሪው ጥያቄ ያቀረበው እኛ ጋ ነበር ለማለትና ለፎርማሊቲ እንጂ የተፈቱት በፖለቲካ ውሳኔ መሰረት መሆኑን አክለዋል።
በኮማንድ ፖስቱ ታስረው የነበሩ የኦሮሚያ ልዩ ፖሊስ ምክትል አዛዥና የፍትህ ቢሮ ቃል አቀባይ ተፈቱ
አዲስ አበባ፡ በአገር አቀፍ ደረጃ ሁለት ጠንካራ ፓርቲ ብቻ እንዲኖር ፍላጎቱ አለኝ ሲሉ የቀድሞ የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ኦኬሎ አኳይ አስታወቁ።ኢህአዴግ ከእህት ድርጅቶቹና ከአጋር ድርጅቶች ጋር ውህደት ለማድረግ ማሰቡንም በአድናቆት ተመልክተውታል።አቶ ኦኬሎ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደተናገሩት፣ ኢህአዴግ ባለው ተመሳሳይ አቋም በውስጡ ያሉ እህት ድርጅቶቹን እንዲሁም አጋር ድርጅቶችን ይዞ ውህደት ቢፈጥር ፣ተፎካካሪ ፓርቲዎችም እንዲሁ ባላቸው ተመሳሳይ አቋም አንድ በመሆን በአገሪቱ ሁለት ጠንካራ ፓርቲዎች ብቻ እንዲኖሩ ይመኛሉ።ኢህአዴግም ሆነ ተፎካካሪ ፓርቲዎች በየጎራቸው ውህደትን ሲፈጥሩ ግን ባላቸው እሴት፣ ራእይ፣አላማና አቋም ላይ መመስረት አለባቸው። ኢህአዴግ እህት ድርጅቶቹን ይዞ አጋር ፓርቲዎችን በማካተት ውህደት ለመፍጠር መንቀሳቀሱ መልካም ነው ያሉት አቶ ኦኬሎ፣ ይህ ግን ሊያመሳስሏቸው የሚያስችሏቸውን ነጥቦች ከግምት ውስጥ በማስገባት መሆን እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል።ካልሆነ ግን ውህደቱ በስም ብቻ ይሆንና ወደ ተግባር ሲመጣ ሊጣረስ እንደሚችል ጠቁመው፣በተመሳሳይ ተፎካካሪ ፓርቲዎችም እንዲሁ የሚያመሳስሏቸውን ነጥቦች መሰረት በማድረግ አንድ ጠንካራ ፓርቲ ሆነው መቆም እንደሚኖርባቸውም አስታውቀዋል። በአገር አቀፍ ደረጃ የሚያስፈልገው ሁለት ጠንካራ ፓርቲ ብቻ ነው። ያሉት አቶ ኦኬሎ፣ ለዚህ ምክንያታቸው በዋናነት የጠቀሱትም የአገር ሰላም መሆኑን ተናግረዋል። ጠንካራ ፓርቲ ሲኖር በሚረባውና በማይረባውም ነገር ብጥብጥ ሊነሳ አይችልም። ከዚህም በተጨማሪ የፓርቲዎች መብዛት የህዝብ ድምፅ እንዲባክን ከማድረግ ውጭ እምብዛም ፋይዳ የለውም።ስለዚህ በፓርቲ ቁጥር መብዛት ህዝብ እንዳይደናገርም ያግዛል። ሲሉም አብራርተዋል። እንደ አቶ ኦኬሎ ገለፃ፣ሁለት ጠንካራ ፓርቲዎች ብቻ የሚኖሩ ከሆነ የህዝቡ ድምፅ ሁለት ቦታ ብቻ ይሆናል።በስልጣን ላይ ያለው ፓርቲም የቱንም ያህል ጥሩ ቢሰራ ከሁለት ዙር እንዳይዘል ማድረግ ያስችላል። አቶ ኦኬሎ እንዳሉት፣የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት በነበሩበት ወቅት የጋምቤላ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ኮንግረንስ አባል የነበሩ ሲሆን፣ ኢህአዴግ የተፎካካሪ ፓርቲ መሆናቸውን እያወቀ ነበር በስልጣን ላይ እንዲቀመጡ የተደረገው።በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ ኢዜማ አባል መሆናቸውንም ተናግረዋል።አዲስ ዘመን ህዳር ሁለት ሁለት ሺህ አስቴር ኤልያስ
በአገር አቀፍ ደረጃ እንዲኖር የምፈልገውሁለት ጠንካራ ፓርቲ ብቻ ነው አቶ ኦኬሎ አኳይ የቀድሞ የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት
አዲስ አበባ፣ ህዳር አንድ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በትግራይ ክልል ህግ በማስከበር ዘመቻ ላይ የሚገኙ የመከላከያ ሰራዊትን እና ለሌሎች ፀጥታ አካላትን ለመደገፍ የገቢዎች ሚኒስቴር አመራሮች እና ሰራተኞች የደም ልገሳ እያደረጉ ይገኛል።ከሁለት መቶ በላይ የተቋሙ ሰራተኞች በበጎ ፍቃድ ደም የለገሱት በግዳጅ ላይ ለሚገኙ የፀጥታ አካላት ከጎናቸው መሆናቸውን ለማሳየት በማለም መሆኑን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በሰጡት አስተያየት ገልፀዋል።የገቢዎች ሚኒስትር አቶ ላቀ አያሌው እንደተናገሩት የሀገርን ሏላዊነት እና ክብር በማስጠበቅ ህግ በማስከበር ላይ ለሚገኘው የመከላከያ ሰራዊት በዚህ ወቅት ደም በመለገስ አጋርነትን በተግባር ለማሳየት የልገሳ መርሀ ግብር መከናወኑን ተናግረዋል።ደም መለገስ የህይወት ስጦታ በመሆኑ ህይወቱን ሳይሳሳ ለሀገሩ ለመክፈል ከተሰለፈው ጀግና ሰራዊት ጎን በዚህ ተግባር አጋርነትን በማሳየት አብሮ መቆም ይገባልም ብለዋል ሚኒስትሩ።ደም እየለገሱ የሚገኙት ሰራተኞችም መንግስት በአጥፊው የህወሀት ቡድን ላይ እየወሰደ ያለውን እርምጃ እንደሚደግፉ ገልፀዋል።መላው የኢትዮጵያ ህዝብም በሚችለው ሁሉ ከፀጥታ ሀይሉ ጎን እንዲሰለፍም ጥሪ አቅርበዋል።በመለሰ ምትኩ
የገቢዎች ሚኒስቴር አመራሮች እና ሰራተኞች የደም ልገሳ አደረጉ
ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ተመራማሪ ትምኒት ገብሩ፣ በአለማችን የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የምርምር መስክ እጅግ የላቀ አስተዋፅኦ በማበርከት ላይ ከሚገኙና በዘርፉ አስደናቂ ስኬት ካስመዘገቡ ድንቅ የአለማችን ሀያ አንድ ሴት ተመራማሪዎች አንዷ መሆኗን ታዋቂው ፎርብስ መፅሄት ዘግቧል።በልጅነቷ ወደ አሜሪካ ያመራቺው ትምኒት ገብሩ፣ የግልም ሆነ የሙያ ተግዳሮቶቻቸውን አሸንፈው በአለማችን የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የምርምር መስክና በኢንዱስትሪው ውስጥ አስደናቂ ተፅእኖ መፍጠር ከቻሉና በግምባር ቀደምትነት ከሚጠቀሱ ተፅእኖ ፈጣሪ ሴቶች አንዷ ናት ያለው ፎርብስ፣ በታዋቂው አፕል ኩባንያ በሙያዋ ተቀጥራ ለማገልገል የቻለች ብቁ ባለሙያ መሆኗንም ገልጧል።በስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲ በኤሌክትሪካል ምህንድስና የትምህርት መስክ የመጀመሪያና የሁለተኛ ዲግሪዋን የተቀበለቺው ትምኒት፤ በዩኒቨርሲቲው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ላቦራቶሪ፣ በኮምፒውተር ቪዥን መስክ የፒኤችዲ ትምህርቷን በመከታተል ላይ እንደምትገኝም አስረድቷል።የጎግል ምስሎችን በመጠቀም የህዝብ ቆጠራ መረጃዎችን መተንተን የሚያስችለውና በቅርቡ ይፋ ያደረገቺው የምርምር ስራ፣ በታዋቂው ዘ ኢኮኖሚስት መፅሄት ሰፊ ሽፋንና ከፍተኛ አድናቆት እንደተሰጠው የጠቆመው ዘገባው፣ ተመራማሪዋ በርካታ የጥናት ውጤቶችንና የምርምር ፅሁፎችን ለንባብ ማብቃቷንም ፎርብስ ባለፈው ሳምንት ባወጣው ዘገባ ጠቁሟል።በቅርቡ በተካሄደ አለማቀፍ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መስክ አውደጥናት ላይ የተሳተፈች ብቸኛዋ ጥቁር ተመራማሪ እንደነበረች ያስታወሰው ዘገባው፣ ይህን አጋጣሚ ተከትሎም ጥቁሮች ወደ ዘርፉ ምርምር እንዲገቡ መንገድ የሚከፍት ተቋም በመመስረት እየሰራች ትገኛለች።በአሜሪካ በሙያዋ የላቀ ደረጃ ላይ መድረሷን ተከትሎ፣ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሳ የአገሯን ወጣቶች በማስተማርና በቀጣይ በዩኒቨርሲቲዎች የትምህርት እድል የሚያገኙበትን መንገድ በማመቻቸት የላቀ አስተዋፅኦ ማበርከቷንም ፎርብስ በዘገባው አስነብቧል።
ትምኒት ገብሩ ከአለማችን ድንቅ ሀያ አንድ ሴት ተመራማሪዎች አንዷ ሆናለች
አለም አቀፉ የሰራተኞች ድርጅት አይ ኤል ኦ ኢትዮጵያን የማህበራትን የመደራጀት ነፃነት ከገደቡ ቀንደኛ አምስት ሀገራት አንዶ መሆኖን አስታወቀ። ጄኔቫ የሚገኘው አለም አቀፉ የሰራተኞች ማህበር ዛሬ ይፋ ባደረገው ሪፖርት እንዳስታወቀው የመሰባሰብና የመደራጀት ነፃነት ካፈኑና አደገኛና ፍፁም የሆነ ገደብ የጣሉ ሲል ካወጣቸው ስላሳ ሁለት ሀገራት ውስጥ ኢትዮጵያ፣ ካምቦዲያ፣ ፊጂ፣ አርጀንቲናና ፔሩ በዋነኝነት አስቅቀምጦቸዋል። የአይ ኤል ኦ ሪፖርት እንዳመለከተው እነዚህ ሀገሮች ከአንድ እስከ ሰላሳ ሁለት በሚደርስ የመሰባሰብና የመደራጀት ነፃነት አፋኝነት ያስቀመጠው የድርጅቱ የመደራጀት ነፃነት ኮሚቴ የየሀገሮቹ የአሰሪዎችና የንግድ ማህበር መብት ተሞጋች ድርጅቶችን የተመረጡ ጉዳዮችን በመመርመርና ማህበራዊ ውይይት በማካሄድ መሆኑን አስታውቆል። በዚህ መሰረት የሰራተኛ ማህበሩ በኢትዮጵያ በማህበርነት ለመደራጀት ከአራት አመት በፊት ማመልከቻ ያቀረበው ብሄራዊ የመምህራን ህብረት እስካሁን በማህበርነት እንዳልተመዘገበ አመልክቶል። የአለም አቀፉ የሰራተኞች ድርጅት በዚህ ሪፖርቱ ላይ የኤትዮጵያ መንግስት የሰራተኞችን የማህበራት አደረጃጀት መብትና ነፃነት የመምህራኑን ጨምሮ እንዲጠበቅ የብሄራዊ መምህራን ህብረትን ማመልከቻ ተቀብሎ ህጋዊ እንዲያደርገው መንግስትን በፅኑ አስተንቅቆል። አይ ኤል ኦ በዚህ ጥነቱ በአርጀቲና ስለተገደሉ አራት ሰራተኞችና ስለቆሰሉ ሁለት ሰዎች ጉዳይ ምርመራ አድርጎ ዝርዝሩን ያቀረበ ሲሆን የአርጀንቲና መንግስት ከቤታቸው ያፈናቀአልቸው አምስት መቶ ሰራተኞች የመኖሪያ ቤት ጥያቄ በማቅረባቸው ግድያውን መፈፀሙን በመጥቀስ አርጀንቲናን ከኢትዮጵያ ጋራ መደራጀትን በፅኑ በሚገድቡ ሀገራት ተርታ መድቦታል።
አይ ኤል ኦ ኢትዮጵያ የመደራጀት መብትን አግዳለች አለ
ከሙሉቀን ገበየሁበአገራችን ኢትዮጵያ የአገር ሽማግሌዎች የተከበሩና ብሂል ምክራቸውም የተደመጠ ነው። ባህላችንም ታሪካችንም ይሆንኑ ነው የሚነግረን። በመሀበራዊ ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም በተወሰነ መልኩ ፖለቲካዊና የወንጀል ጉዳዮች ላይ የሚሰጡት ብይንና ምክር ሁሌም የተከበረና ህብረተሰቡም ሲያከብርው የኖረ ባህላዊ እሴት ነበር። የአገር ሽማግሌዎች ያካበቱት እውቀት ልምድና ብሂል ባሉበት ሀገር ታላቁ የእውቀት መፅህፍ ኢንስይክሎፒድያ ያህል ያደርጋቸዋል። ይህ ለምእተአመታትና ለሺ አምታት ህብረተሰቡን አሁን ከምናየው የዘመናዊው የፍርድ ስርአት በተመጣጣኝ ወይም በተሻለ መንግድ ሲያገላግል የኖረ አሰራር ነው።ጥበባችውና ብሂላቸው የተመሰረተው ከህይወት ልምዳቸው በቀጥታና በተዘዋዋሪ ከሚያግኙት ትምህርት ከመሀባራዊ ግንኙንታቸው ና ከራሳቸው ህይውት ምልክታ የመንጨ ነው። የተባርኩ ጎብዞች የነሱን ጥበብና ምክር እያደመጡ የህይወትን ሚስጥርና መንገድ ባጭር መንግድ ያገኙታል። የሚያድምጥ ህብረተሰብ ደግሞ ምንኛ የታደለ ነው። አርጋውያውኑና የማያክበርና ብሂላቸውን የሚያናንቅ ቡድን ግን አደጋ ሊያመጣ የሚችል ሀይል ሊሆን ይችላል።ሳንታደል ቀርተን ላለፉት ከአርባ ለበለጡ አምታት ኢትዮጲያን ሲገዙንና እየገዙን ያሉ ገዚዎቻችን ይህን ያግር ብሂሎችን ሳየደሙጡና ኢያናናቁ በመኖራቸው አስፍሪና አደግኛ ሰከን የማይሉ ሁነውብናል። የስልጣን ዘመናቸውን በሙሉ በራስ መወደድ በስግብግብነት ከኔ በላይ ማን አልበኝነት በእብሪትና ጥርጣሬ የስልጣን እብድት ላይ ሁነው የኢትዮጲያን ህዝብ ሲያሰቃዩት ኑረዋል።እይኖሩም ነው።የተማሩ የተመራመሩ አርጋውያን ባንድ አገር በዝተው ሲኖሩ ላንድ ሀገረ እንደ ልዩ ስጦታ እንደ ማለት ነው። በህይወት ልምዳቸው ካገኙት ልምድ በተጨማሪ በትምህርት ስለአለም የቀሰሙት እውቀትና ልምድን ለ አዲሱ ትውልድ ማስተላለፍ ስለሚቻላቸው ነው። የሚያደርጉት አስተዋፆ ምክርና ብሂል እጅግ ጠቃሚ ነው።ሰሞኑን ባገራችን የተከብሩና የተመሰገኑ ሁለት የተማሩ የአገር ሽማግሌዎችን ፅሁፍና የድምፅ ምስል መልክት አነበብኩ አደምጥኩ። እኒህ የተከብሩ ሙሁራን ሽማግሌዎች ራሳቸውን ለሚጠቅም ስልጣን ሀብት ወይም ብቀላ ብለው አይደለም። ከእድሜና ከትምህርት ልምድ ያካበቱትን ብሂል ሀላፊነት ተስምቶቸው ለወገኖቻቸው ሲያቀርቡ ለአገር ይበጃል አገር ከመፍርስ ያድናል ብለው ነው።የፕሮፌሰር መስፍን ወማርያምን የፅሁፍ መልክትና የ ፕሮፌሰር አዱኛ ወርቁን በ አመት የልደት ባአላቸው ላይ ያስተላልፉትን የድምፅና ምስል መልክት አንብቢያልሁ ተመለክቻለሁ። መልክቱም ለኛ ለሁላችን በስልጣን ላይ ላሉ ለተቃዋሚዎች እንዲሁም ለህዝቡም ነው።ሁላችንም ከዚ መልእክትና ምክር እንጠቀማለን። ገዢዎች ተቃዋሚዎች እንዲሁም ህዝቡ እጅጉን ይጠቀምበታል። ላስበነው መልካም የአገርና የህዝብ ምኞት ቦታ ላይ ለመድረስ የሚያስችል የአቋራች መንገድ ነው። ሁላችንም ልንመለከተውና ልናደምጠው የሚገባ ወርቃማ መልክት ብሂልና አባባልን ያካተተ ነውና ተመልከቱት አንብቡት።ከሚተናነቀን ግላዊ የራስ ጥቅም ስሜትና የፖለቲካ ወይም ጎሳ ወገነተኛነት እስኪ ላንድ አፍታ ወጣ ብለን እንደ አንድ ሰበአዊ ፍጡር በኢትዮጲያ ምድር በእግዚሄቤር ፈቃድ የተወለድን ሁሉ መቼም ፈቃዱ ባይሆን እዚያ አንወለድም ነበር እናስብ። ለተወሰኑ ሰአታት አእምሮችንን ንፁህ አደርገን የሁለቱን አዛውንት ልሂቃን መልክትና ምከር እናንብ እንስማው። ላለንበት ድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ብርሀን የሚፈነጥቅ ነው። ካለንበት ጨለማ ዋሻ መውጫ በር ላይ የሚያደርሰን የብርሀን ብልጭታ ነው። ከተዘፈቅንበት የጥላቻ የፍርሀት አንዲሁም የርስበርስ ጠላትነት ስሜት ያፀዳናል።ለኢትዮጲያ ልጆች ሁሉ ይህን የአዘውንቶችን ምክርና መልክት ትንሽ ሰአት መሰአውት አድርጋችሁ እንድታነቡና እንድታደምጡ ከዚያም ለሀገራችን መፍቴ የሚሆነውን ራሳቸንን እንድንጠይቅ በአክብሮት እማፀናልሁ። ለተጠላለፉ ችግሮቻችን ሁሉ መፍቴ የሚሆነን መልስ እኛው ራስችን ውስጥ አለ። እግዚሀቤር ይርዳን።
እስኪ የተማሩ የአገር ሽማግሌዎቻችንን እናድምጥ ከሙሉቀን ገበየሁ
የበላይ ባለስልጣናት በፈፀሙት ወንጀል እኛ ዋጋ እየከፈልን ነው ባለፈው ሀምሌ ወር በተካሄደው የፀረ ሙስና ዘመቻና በተለያዩ ጊዜያት በልዩ ልዩ የሙስና ወንጀሎች ተከሰው ጉዳያቸው በፍቤት እየታየ የሚገኘው ተከሳሾች ፍትህ ይሰጠን የሚል አቤቱታቸውን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አቀረቡ። ጉዳያቸው በፍቤት ቀጠሮ ላይ የሚገኘው እነዚህ የሙስና ወንጀል ተከሳሾች ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ እንዲቀርብላቸው የላኩት የ እስረኞችን ፊርማ ያካተተ የአቤቱታ ደብዳቤ ሲሆን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲደርስ በፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ለፍትህ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ተመርቶላቸዋል። ተከሳሾቹ በዚህ አቤቱታቸው ላይ እንደገለፁት የሙስና ወንጀል ሳንፈፅም ለፖለቲካ ፍጆታ ሲባል የታሰርን ሰዎች በመሆናችን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሌሎች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ፍትህ እንድናገኝ ሊያደርጉን ይገባል ብለዋል። ትልልቆቹና ዋንኞቹ አሳዎች በሰሩት ሙስና እኛ ዋጋ ከፋይ ልንሆን አይገባም ያሉት እነዚሁ ተከሳሾች አብዛኛዎችን የራሳችን የሆነ ምንም ነገር የሌለን በኪራይ ቤት የምንኖርና በወንጀል ስራ ውስጥ ተሳትፎ ያላደረግን ሰዎች ነን ብለዋል። አቤቱታ አቅራቢዎቹ ዘመቻው የፖለቲካ መሆኑን ጠቁመው ያለበቂ ማስረጃ ክስ ቀርቦባቸው ያለአግባብ እየተሰቃዩ መሆኑን በአቤቱታቸው ላይ ገልፀዋል። ፍርድ ቤቶች ያለ ተፅእኖ በነፃነት ፍትህ እየሰጡን አይደለም ያሉት አቤቱታ አቅራቢዎቹ ያለ ስራችን እጅግ አሳፋሪና ሞራላችንን የሚነካ ሙሰኞች የሚል ስም ተሰጥቶን በእስር እየተሰቃየን እንገኛለን። ስለዚህም ፍቤቱ ነፃ ሆኖ የሚገባንን ፍትህ ይሰጠን ዘንድ እንጠይቃለን ብለዋል። እነዚሁ አቤቱታ አቅራቢዎች በአቤቱታቸው ላይ እንደገለፁት አቃቤ ህግ ያለፍርድ ቤት ትእዛዝ አወጣሁ በሚላቸውና ትክክለኛውን የፍትህ ሂደት ባልጠበቁ የተለያዩ ማስረጃዎች ማቅረብ ሰበብ የማይገባንን ዋጋ እየከፈልን በመሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆኑን ለአቤቱታችን አፋጣኝ ምላሽ ይሰጡን ዘንድ እንጠይቃለን ሲሉ ተማፅነዋል።
በሙስና ወንጀል ተከሰው በቀጠሮ ላይ የሚገኙ ከ በላይ ተከሳሾች ለጠቅላይ ሚኒስተር አቤቱታ አቀረቡ
አዲስ አበባ ፣ የካቲት ስምንት ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሀ ግብር ዋና አካል የሆነው የመንግስት የልማት ድርጅቶችን ውጤታማነት ለማሻሻል ፣ ተወዳዳሪነታቸውን ለማጎልበት እና የአገልግሎቶት አሰጣጣቸውን ቀልጣፋ እንዲሆኑ ለመደገፍ ያተኮረ ለአምስት ቀናት የሚቆይ ውይይት ተጀመረ። በመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ ስር በትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ፣ በግብርና እና ግብርና መቀነበባር፣ በአምራች ኢንዱስትሪ እና ኢንጅነሪንግ፣ የንግድ እና የአገልግሎት ዘርፍ፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የተግባቦትና ግንባታ ስር ተመድበው የሚገኙ የመንግስት የልማት ድርጅቶች በሁለት ሺህ በጀት አመት በመጀመሪያው አጋማሽ የነበራቸውን የስራ አፈፃፀም ግምገማ እየተካሄደ ይገኛል። ለሁሉም የልማት ድርጅቶች የኦዲት ሪፖርት ላይ የተሰጡ የማሻሻያ ሀሳቦችን ተግባራዊንት እንዲያረጋግጡ የግምገማው ትከረት ሰጥቷል። የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴመንግሰት የልማት ድርጅቶቹን ለመደገፍ የቴክኒክ ኮሚቴዎቸን አዋቅሮ ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰው በተለይም ሁሉም የልማት ድርጅቶች አለም አቀፍ የፋይናንስ አስተዳደር እና ሂሳብ አያያዝ ስርአት ተከትለው እንዲተገብሩ በመደረጉ የአሰራር መሻሻሎች እየተገኙ እንደሆነ ጠቅሰዋል። ሚኒስትሩ የመንግስት የልማት ድርጅቶችን የእዳ መጠን ዘርዝሮ በማጥናትና የመክፈል አቅማቸውን ከግምት ውስጥ በማስገባት የመንግስት የልማት ድርጅቶችን የእዳ ጫና በማቃለል እና ውጤታማ ሆነው እንዲዘልቁ ለማስቻል የሚያግዝ የእዳና ሀብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን እንዲቋቋም በሚኒስትሮች ምክር ቤት ተወስኖ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም አስገንዝበዋል። የመንግስት የልማት ድርጅቶች ለሀገር ልማትና እድገት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ መንግስት የተለያዩ የፖሊሲ ማሻሻያዎች በመቅረፅ እና የአሰራር ስርአቶችን በመንደፍ ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝ አብራርተዋል። ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ የፋና ድረ ገፅ ይጎብኙ፤ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገፃችን ይወዳጁን የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት መተግበሪያን በስልክዎ በመጫን ቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት፣ ኤፍኤም ዘጠና ስምንት ነጥብ አንድ እና ብሄራዊ ሬዲዮን ይከታተሉ። ቪዲዮዎችንም ይመልከቱ። ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
የመንግስት የልማት ድርጅቶች የግማሽ አመት ስራ አፈፃፀም እየተገመገመ ነው
ከአራት አመታት ቆይታ በኋላ ከመቐለ ሰባ እንደርታ ጋር የተለያየው አሌክስ ተሰማ ቀጣይ ማረፍያው በቅርቡ ይታወቃል።ባለፉት ሶስት አመታት በዋናው ሊግ ደረጃ በወጥነት ጥሩ ብቃት ካሳዩት የመሀል ተከላካዮች አንዱ የሆነው አሌክስ ተሰማ የዳሽን ቢራ መፍረስ ተከትሎ በወቅቱ የከፍተኛ ሊግ ተወዳዳሪ ለነበረው መቐለ በሁለት ሺህ ዘጠኝ ፈርሞ በዛው አመት ቡድኑ ወደ ፕሪምየር ሊግ እንድያድግ ሚና የነበረው ሲሆን በሁለት ሺህ ቡድኑ የፕሪምየር ሊጉን ዋንጫ ሲያነሳም ትልቅ ሚና ከነበራቸው ተጫዋቾች አንዱ ነው።ተጫዋቹ ከአራት አመታት የመቐለ ቆይታ በሀላ ከክለቡ ጋር ተለያይቶ በቅርቡ ወደ ሌላ ክለብ ለመቀላቀል ተቃርቧል። በቀጣይ ማረፍያው ዙርያ ከሶከር ኢትዮጵያ ቆይታ የነበረው አሌክስ ከአንድ የሊጉ ክለብ ጋር ከስምምነት ለመድረስ ከጫፍ እንደደረሰ ገልፆ ከመቐለ ጋር ባሳለፋቸው አመታት የክለቡ ደጋፊዎች ላሳዩት ድጋፍ እና አክብሮት አመስግኗል። ባልጠበቅኩት መንገድ ከምወደው ክለብ ጋር ለመለያየት ችያለው። ሆኖም በክለቡ ቆይታዬ ደጋፊዎች ላደረጉልኝ የማያቋርጥ ድጋፍ እና አክብሮት ከልብ አመሰግናለሁ። በቀጣይ ቀናትም ወደ ሌላ ክለብ ለመዘዋወር ከጫፍ ደርሻለው።
መቐለ ሰባ እንደርታ ከተከላካዩ ጋር ተለያይቷል
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የአመራሩን የተግባር አንድነት ለማጠናከር ሰፊ ጥረት መደረጉን የኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ ተናገሩ። የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት እና የፓርቲ የሁለት ሺህ የመጀመሪያው ሩብ አመት አፈፈፃፀም ግምገማ በአዳማ ገልማ አባገዳ እየተካሄደ ነው። የፅህፈት ቤት ሀላፊው አቶ ፍቃዱ ተሰማ በአንዳንድ አመራሮች መካከል ወጥ የሆነ የአመለካከት ውስንነት መኖሩ ክልሉን ዋጋ እንዳስከፈለው ገልፀው፥ ይህንንም ለማስተካከል ሰፊ ጥረት ተደርጓል ብለዋል። በክልሉ አንዳድን አካባቢዎች የገጠሙ የሰላም እጦት ችግሮችን በመቅረፍ አካባቢዎቹን ወደ ነበሩበት ሰላም ለመመለስ የክልሉ የፀጥታ ሀይል ከፌደራል የፀጥታ መዋቅር ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን አንስተዋል። የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎች በክልሉ መከናወናቸውን ያነሱት ሀላፊው፥ ካለው ፍላጎት አንፃር በቂ ባለመሆኑ ትኩረት ተሰጥቶት መሰራት እንዳለበት አሳስበዋል። በግምገማ መርሀ ግብሩ የተለያዩ የክልል የስራ ሀላፊዎች እና የዞን አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ። በወንድሙ አዱኛ ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ ድረ ገፅ፦ ፌስቡክ፡ ዩትዩብ፦ ቴሌግራም፦ ትዊተር፦ በመወዳጀት ይከታተሉን። ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
የአመራሩን የተግባር አንድነት ለማጠናከር ሰፊ ጥረት ማድረጉን የኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ገለፀ
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተመድ የምእተ አመቱን የልማት ግብ አጠናቆ፣ በሁለት ሺህ ስምንት አመተ ምህረት ተግባራዊ ማድረግ በጀመረው የ አመቱ የዘላቂ ልማት ግብ ተሳታፊ የሆነው የኢትዮጵያ መንግስት ፈቃደኛ በመሆን የአንድ አመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርቱን ሊያስገመግም ነው። ኢትዮጵያን ጨምሮ አርባ አራት አገሮች የእቅድ አፈፃፀማቸውን ለማስገምገም ፈቃደኛ ሆነዋል።ብሄራዊ ፕላን ኮሚሽን ለተመድ በሚቀርበው የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ከፌዴራልና ከክልል ባለሙያዎች ጋር እየመከረ ነው። እ ኤ አ በሁለት ሺህ ዝርዝር ግምገማ የሚካሄድባቸው የዘላቂ ልማት ግቦች ስድስት ናቸው።እነሱም ድህነትን ማጥፋት፣ ረሀብን ማጥፋት፣ ጤናማ ህይወትና ደሀንነት፣ የስርአተ ፆታ እኩልነት፣ የመሰረተ ልማት ግንባታና ኢንዱስትሪ ፈጠራ፣ እንዲሁም የውሀ ስነ ምሀዳርን ዘላቂ ልማት መጠበቅ የሚሉት ናቸው።ማክሰኞ ግንቦት አንድ ቀን ሁለት ሺህ ዘጠኝ አመተ ምህረት በተካሄደው የዘላቂ ልማት ግቦች የፈቃደኝነት ብሄራዊ ግምገማ መድረክ ላይ የብሄራዊ ፕላን ኮሚሽን የክትትልና ግምገማ ቢሮ ሀላፊ አቶ ተመስገን ዋለልኝ ባቀረቡት ፅሁፍ፣ ኢትዮጵያ ባለፉት አመታት ከአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ስድስት እስከ ሁለት ሺህ ስምንት በየአመቱ በአማካይ አስር ነጥብ ስድስት በመቶ ኢኮኖሚያዊ እድገት ማስመዝገቧን ገልፀዋል። መሰረተ ልማትና ማሀበራዊ ልማት በከፍተኛ ደረጃ ተስፋፍቷል። ይህም በአገሪቱ ከጫፍ እስከ ጫፍ ለሚገኙ ዜጎች መሰረታዊ አገልግሎቶች ተደራሽ እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል፤ ሲል አቶ ተመስገን ያቀረቡት ፅሁፍ ይተነትናል።በሁለት ሺህ ስምንት የበጀት አመት የተመዘገበው የስምንት ነጥብ በመቶ አማካይ የኢኮኖሚ እድገት ከእቅድ አንፃር ሲታይ የሶስት ነጥብ ሁለት መቶኛ ነጥብ ቅናሽ ያለው ቢሆንም፣ በአለም ባንክ እ ኤ አ የሁለት ሺህ ትንበያ ከተቀመጠው የሁለት ነጥብ አምስት በመቶ አማካይ የኢኮኖሚ እድገት ግብ ጋር ሲነፃፀር፣ በሶስት እጥፍ የላቀ መሆኑን አቶ ተመስገን በፅሁፋቸው አብራርተዋል። የነፍስ ወከፍ ገቢ በሁለት ሺህ ሁለት አመተ ምህረት ከነበረበት ሶስት መቶ ሰባ ሰባት ዶላር፣ በሁለት ሺህ ሰባት አመተ ምህረት ወደ ስድስት መቶ ዘጠና አንድ ዶላር አድጓል። በሁለት ሺህ ስምንት አመተ ምህረት ወደ ሰባት መቶ ዘጠና አራት ዶላር ያደገ ሲሆን፣ በሁለት ሺህ አመተ ምህረት ደግሞ ወደ አንድ አንድ መቶ ሰባ ሰባት ዶላር ለማድረስ ታቅዷል፤ ሲል የቀረበው ፅሁፍ ያስረዳል።ላለፉት አስር አመታት ተግባራዊ በተደረገው የምእተ አመቱ የልማት ግብ ከተቀመጡት ሰባት ነጥቦች ውስጥ ኢትዮጵያ አብዛኛዎቹን ማሳካቷ ተገልጿል።አገሪቱ በየአመቱ ከምትይዘው አጠቃላይ በጀት ውስጥ ቢሊዮን ብር ለልማት ግቦች ተለይቶ ሲያዝ ቆይቷል። የብሄራዊ ፕላን ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ጌታቸው አደም፣ የልማት በጀቱ ማነስና መብዛቱ አይደለም ቁምነገሩ። ዋናው ነገር የኢትዮጵያ መንግስት ድህነትን ለማጥፋት ያለውን ቁርጠኝነት ምን ያህል እንደሆነ ማሳያ ነው፤ ሲሉ ለሪፖርተር ገልፀዋል። ሪፖርቱ በሚመለከታቸው አካላት ከዳበረ በኋላ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቦ ለተመድ እንደሚላክ አቶ ጌታቸው አስረድተዋል።
ኢትዮጵያ ለተመድ በፈቃደኝነት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ልታቀርብ ነው
በቶፊቅ ተማምምንም የማይሰማ የማያይ እንዲሁም የማይናገር ሰው መቶ አመታትን በሰላም መኖር ይችላል። ይህ አባባል ኦሜርታ ተብሎ የሚጠራውን የዝምታ ህግ አስፈላጊነት ለመግለፅ በተለይ በጣሊያን ሲሲሊዎች ዘንድ የሚነገር የዘወትር ቃል ነው።ዛሬም ድረስ ታዲያ በአንዲት አገርና ህዝብ ላይ የፍርሀት ድባብ ሲነግስና የፍርሀቱም ምክንያት ከቡድን ወይም ከመንግስት አስተዳደር ጋር ሲገናኝ በውጤቱም ህዝብ እንዲሁም ምሁራን አላየሁም አልሰማሁም አልናገርም የሚል ዝምታ ሲፈጠር ክስተቱ ኦሜርታ ይባላል።በእርግጥ በዚህ ፅሁፍ ከምሁራን ባላውቅም በዋነኛነት በአጭሩም ቢሆን ለመዳሰስ የምሞክረው ጉዳይ ቢኖር በአገሪቱ ምሁራን ዘንድ እየተስተዋለ የሚገኘውን ኦሜርታ ይሆናል። በአንድ አገር የፖለቲካ የኢኮኖሚና የማህበራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ የምሁራን ሚና ከፍተኛ ነው። ምሁራን ለልማት እንዲሁም ለዘላቂ ልማትና ሰላም የሚጠቅሙ ሀሳቦችን በማመንጨት የሚጫወቱት ሚና የላቀ ቢሆንም በኢትዮጵያ ግን በአጥጋቢ ሁኔታ እየተተገበረ አይደለም። ለዚህም አንዱና መነሻ ምክንያት የሚሆነው የመንግስት አስተዳደር ስርአትን ለመተቸትና ያልተገቡ አካሄዶችን ነቅሶ ለማውጣት አመቺ በሆነ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ ባለመኖራቸው ምክንያት የአገሪቱ ምሁራን ከትችትና ከአስተያየት ተቆጥበው ዝምታን መርጠው እየኖሩ ነው።በማንኛውም አገር ምሁራን ትውልድን በእውቀት መቅረፅ ብቻ ሳይሆን በአገር ጉዳይ ላይ የተሻለ አመራር እንዲመጣ የእውቀታቸውን ያህል ማበርከት ድርሻቸው ነው። ከላይ ለመግለፅ እንደ ተሞከረው ምሁራንን አሳታፊ የፖለቲካ ምህዳር ባለመኖሩ በአገር ጉዳይ ተሳትፎ ለማድረግ ምን ቸገረኝ የሚል እሳቤ እያመጣ ነው። በዚህም ሳቢያ ምሁራን ራሳቸውን ለመደበቅና ለዝምታ የተዳረጉ ሲሆን ከሰጎን ፖለቲካ ሊያልፉ አልቻሉም። በዚህ የሰጎን ፖለቲካ የምሁራን ዝምታ ለአገርና ለወገን የማይበጅ በመሆኑ ሊቆም የሚገባበት ወቅት ላይ እንገኛለን። በአንድ አገር የፖለቲካ ማህበራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ የምሁራን ሚና ከፍተኛ መሆኑ እሙን ነው። ምሁራን ለልማት የሚጠቁሙ ሀሳቦችን በማመንጨት ረገድ የላቀ ሚና የሚኖራቸው ሲሆን በተለይ ከሌላው ህብረተሰብ በላቀ ደረጃ እውነት በመናገር ሀሰትን ሊያጋልጡ እውቀትን አክብረው ሊያስከብሩና ለምሁርነታቸው ታማኝ ሊሆኑ ራሳቸውን ለውይይትና ጥያቄ ክፍት ሊያደርጉ ይገባቸዋል።በኢትዮጵያ በርከት ያሉ ፖለቲካው የፈጠራቸው ችግሮች እንዳሉ የሚታወቅ ነው። የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታና ትግበራው ችግር ያለበት ከመሆኑም በላይ የመልካም አስተዳደር ጉድለትና የመንግስት ባለስልጣናት ግልፅነትና ተጠያቂነት ገና ተገቢ መፍትሄ ያላገኙ ተግዳሮቶች ናቸው። ከዚህ አንፃር የኢትዮጵያ ምሁራን ፖለቲካዊ ሚና ሊሆን የሚችለው ችግሮችን በጥልቀት መርምሮ በመረዳት እውነትና እውቀትን መሰረት በማድረግ የመፍትሄ ሀሳብ ማመንጨትና ሀሳቦች ወደ ህብረተሰቡ እንዲደርሱ ለማድረግ የሚረዳ ስልት መቅረፅ ከአገሪቱ ምሁራን የሚጠበቅ ተግባር ነው።አገሪቱ ያሉባት ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ምሁሩ ሊያቀርባቸው በሚችሉ የእድገት ሀሳቦች ሊታገዙ ይገባል። አገሪቱ በርካታ የኢኮኖሚና ሌሎች ተዛማጅ መስኮች ባለሙያዎችን ያፈራች ሲሆን አገሪቱ አማራጭ የእድገትና የልማት ሀሳቦችን ታገኝ ዘንድ ምሁራንም ሀላፊነታቸውን ለመውጣት የተለየ ጥረት ሊያደርጉ ይገባል።ከኢኮኖሚያዊ ችግሮች ባልተናነሰ የአገሪቱ ማህበራዊ ችግሮች በርካታ መሆናቸው እሙን ሲሆን እጅግ የባሱት ለአብነት ያህል የትምህርት ጥራት ጉድለት ስራ አጥነትና ሌሎችንም ችግሮች መጥቀስ ይቻላል። ምሁራን ማህበራዊ ችግሮችን በማጥናት የመፍትሄ ሀሳቦችን ማመንጨት እንዲሁም ማሰራጨት ይጠበቅባቸዋል።ከላይ የጠቀስናቸውን ተግባራት ምሁራን በአግባቡ መፈፀም ያስችላቸው ዘንድ መደማመጥና በልዩነታቸው ተከባብረው ለመስራት ቅን መንፈስ ሊኖራቸው ይገባል። ዛሬ የኢትዮጵያ ምሁራን በአገር ቤት ብቻ ሳይሆን በመላው አለም ተሰራጭተው የሚገኙ በመሆናቸው በቦታ በርቀት ሳይገደቡ በብዙ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ስምምነት ሊፈጥሩ ይገባል። በአገሪቱ ያሉትን ችግሮች ከመፍታት አንፃር አገሪቱ የሚታዩ ችግሮች ነቅሰው የሚያወጡ ለዚህም መፍትሄ አቅጣጫ የሚጠቁሙ ብዙ የአደባባይ ምሁራን በአገሪቱ ሊፈሩ ግድ የሚል ወቅት ላይ እንገኛለን። ከዚሁ ጎን ለጎን በሚኖሩበት አገር ውስጥ ካለ ፍርሀት እንዲሁም መሸማቀቅ ስለሚኖሩበት ህብረተሰብ ካላቸው ጥልቅና የበለፀገ እውቀት በመነሳት የሚታዩ ክፍተቶችን የሚሄሱ እንዲሁም አገር በቀጥተኛ ጎዳና ትሄድ ዘንድ ህፀፆችን የሚጠቁሙ ሀያሲ ምሁራን ቁጥር የበለጠ ሊያሻቅብ ይገባል።በእርግጥ ስለምሁራን ሲወራ ብዙ ምሁራን በአገር ቤት እንዳሉት ሁሉ በውጭ አገር ያሉ ቀላል የማይባል ቁጥር ያላቸው ዳያስፖራ ምሁራን አሉ። ከፊሎቹ በሙያና በገንዘባቸው ለአገራቸው የሚችሉትን እያደረጉ ሲሆን ቀላል የማይባል ቁጥር ያላቸው ዳያስፖራ ምሁራን አሁን ያለውን ነባራዊ ሁኔታ መነሻ በማድረግ ለአገሪቱ መስጠት ያለባቸውን ያህል እየሰጡ አለመሆኑ ዳያስፖራውም በአገሪቱ ጉዳይ ዙሪያ ኦሜርታን የመረጡ እንደሆነ መገንዘብ ይቻላል። ከዚህ ጎን ለጎን በአገሪቱ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያደርገው ተሳትፎ አሉታዊም ይሁን አዎንታዊ በማህበራዊ ድረ ገፆች ላይ ያዘነበለ መሆኑ የሚከተሉት የፖለቲካ ስልት ከሰጎን ፖለቲካ የወጣ ነው ለማለት አያስደፍርም። ከላይ በጥቂቱም ቢሆን የአገሪቱ ምሁራን በአገሪቱ ልማት ዙሪያ ሊጫወቱ የሚገባቸውን ሚና በተመለከተ የተገለፀ ሲሆን የምሁራን እንቅስቃሴ ብቻውን በአንድ እጅ እንደ ማጨብጨብ የሚቆጠር ነው። ምሁራን በአገራቸው ኢኮኖሚያዊ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች በንቃት ይሳተፉ ዘንድ የመንግስት ድርሻ ወሳኝ ነው።በምሁራን የሚቀርቡ ሀሳቦች በነፃነት በህብረተሰቡ ውስጥ እንዲንሸራሸሩ የሚረዳ ፖለቲካዊ ሁኔታ ማመቻቸት የወቅቱ መንግስት ሀላፊነት ሲሆን ይህ ደግሞ ለህብረተሰቡ ከሚጠበቁ አገልግሎቶች ዋነኛው ነው። የፖለቲካ ምህዳሩ ልዩ ልዩ ሀሳቦች የሚንሸራሸሩበት እንዲሆን አለማድረግ አማራጭ ማስቀረት መሆኑ ሊታወቅ ይገባል።መንግስት ምሁራንን የበለጠ አሳታፊ የሚያደርግ የፖለቲካ ስርአት በመዘርጋት ምሁራን በራሳቸው አማራጭ የፖለቲካ ሀይል ሆነው እንዲወጡ በማድረግና መልካም ፈቃድን በማሳየት ምሁራን ለአገራቸው ልማት የበኩላቸውን ይወጡ ዘንድ ሁኔታዎች ሊያመቻች ይገባል።ከቅርብ አመታት ወዲህ ህብረተሰቡ በአንድም ይሁን በሌላ ምክንያት የተለያዩ አግባብ ያልሆኑ ጉዳዮች ሲያጋጥሙት ቆሞ በምን ቸገረኝነት ችግሮችን እንዳላየና እንዳልሰማ ባለማለፍ ከኦሜርታ ሲያፈገፍግ የህብረተሰቡን ጥያቄዎች በአግባቡ መንግስት ዘንድ በማድረስ እንዲሁም ይህን ተከትሎ የሚከሰቱ ቀውሶችን በመከላከል ረገድ የምሁራን ሚና ለአፍታም ቸል የማይባል መሆኑ ሊታወቅ ይገባል።ይህ ፅሁፍ በሚዘጋጅበት ወቅት የኦህዴድ ማእከላዊ ኮሚቴ ባወጣው መግለጫ የኦሮሞ ምሁራን በሁሉም የታሪክ ምእራፍ ላይ የኦሮሞ ህዝብ ባለፈበት የትግል ሂደት ውስጥ መስዋእትነት መክፈላቸውን እንዲሁም አሁንም ከኦህዴድ ጋር በመሆን ዋነኛ ስራቸው የሆነውን ሀሳብ የማፍለቅ ጥናትና ምርምርን እንዲቀጥሉ በማሳሰብና ከምሁራን ጋር አብሮ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን የገለፀ ሲሆን ይህም በአዎንታዊ መልኩ የሚታይና በአፋጣኝ ወደ ተግባር ሊገባበት የሚገባ ጉዳይ ነው።ከቅርብ አመታት ወዲህ አልፎ አልፎ ለሚከሰቱ ችግሮች አንዱ ምክንያት የሚሆነው በመንግስት በኩል ለምሁራን ተገቢው የፖለቲካ ምህዳር አለመመቻቸቱ ሲሆን መንግስት በኦሜርታ ጥላ ስር የሚገኙ ምሁራንን ካሉበት ጥላ በማውጣት ከምሁራን ጋር ተባብሮ የመስራት ባህልን ሊያዳብር የሚገባበት ወቅት መሆኑን መገንዘብ ያሻል።በመንግስት በኩል እስካሁን ያልተሰሩና መሰራት ያለባቸው ጉዳዮች እንደተጠበቁ ሆነው በምሁራን በኩል በስሜት የማይነዱ በአገሪቱ ለሚታዩ አዎንታዊና አሉታዊ ጉዳዮች ሚዛናዊ የሆነ እይታ ያላቸው እንዲሁም በውይይት የሚያምኑ ሆነው ሊገኙ የሚገባቸው ሲሆን እነኚህን ምሁራን አገሪቱ አጥብቃ የምትፈልግበት ጊዜ ላይ እንገኛለን። በመጨረሻም አገሪቷ ያሏትን ምሁራን በአግባቡ መጠቀም ባለመቻል የወላድ መሀን ከመሆን ትድን ዘንድ ምሁራንን በየተዋረዱ የሚያሳትፍ የፖለቲካ ስርአት መዘርጋት ያስፈልጋል። በአሁኑ ጊዜ ተሰብሮ ያለውን በመንግስትና በምሁራን መካከል ያለውን ድልድይ በአግባቡ በመስራት ምሁራን በአሁኑ ወቅት ከሚገኙበት ጥልቅ ዝምታና አሁን ካሉበት የሰጎን ፖለቲካ ይወጡ ዘንድ በመንግስት በኩል አሳታፊና አካታች ስርአት በየተዋረዱ መዘርጋትና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ለአፍታም ቢሆን ቸል ሊባል አይገባውም።ከአዘጋጁ ፅሁፉ የፀሀፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን ፀሀፊውን በኢሜይል አድራሻቸው ማግኘት ይቻላል።
የአገሪቱ ምሁራን በኦሜርታና በሰጎን ፖለቲካ ጥላ ስር
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት ስድስት፣ ቀ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በምርቶችና ሸቀጦች ላይ አለአግባብ የዋጋ ጭማሪ እንዳይኖር ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ እንደሚያስፈልግ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ገለፁ።ሚኒስትሩ ይህንን የገለፁት ከክልልና ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ሀላፊዎች ጋር መደበኛ የቪዲዮ ኮንፈረንስ ውይይት ባካሄዱበት ውቅት ነው ተብሏል።ብዙ ጊዜ ለወቅታዊ የዋጋ ንረት ምክንያት የሚሆነው የንግድ ዘርፉ የመንግስት ተቋማት ቁጥጥር መለላት ነው ም ነው የተባለው።ስለሆነም ህብረተሰቡንና የንግድ ማህበረሰቡን ያሳተፈ ዘላቂነትና ተከታታይነት ያለው የቁጥጥር ስርአት መዘርጋትና የባለሙያዎችን የስራ እንቅስቃሴ መከታተልና መደገፍ ያስፈልጋል።ከዚያም ባለፈ የህገ ወጥ ንግድ ኮንትሮ ባንድ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራት የተወሰዱ እርምጃዎች በመገምገም የተገኘውን ውጤት እየለኩ መሄድ እንደ አንድ ቁልፍ ተግባር አደርጎ መውሰድ እንደሚገባ ም ሚኒስትሩ አሳስበዋል። ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የወጪ ንግድ ምርቶች ላይ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንዳለባቸው የጠቆሙት ሚኒስትሩ በኮሮና ቫይረስ መከሰት ምክንያት በምርቶችና ሸቀጦች ላይ ያለአግባብ የዋጋ ጭማሪ እንዳይኖር ጥብቅ ቁጥጥር ከማድረግ ጎን ለጎን አቅርቦት ማሻሻልና ትስስር መፍጠር ላይ ትኩረት ተደርጎ መስራት ይገባልም ነው ያሉት።በመጨረሻም የኮቪድ ስርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠር እና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀንስ የወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እና አዋጁን ለማስፈፀም የወጣውን ደንብ ለማስፈፀም በሚኒስትሮች ኮሚቴ የወጣ የግብይት ዘርፍ መመሪያ ላይ ውይይት ማድረጋቸውንየንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። የዜና ሰአት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልእክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ ስምንት ሺህ አንድ መቶ ብለው ይላኩ።
በምርቶችና ሸቀጦች ላይ ያለአግባብ የዋጋ ጭማሪ እንዳይኖር ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ ያስፈልጋል ተባለ
በመላው አለም ከሁለት መቶ አገራት በላይ የተዛመተው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የአለምን የስፖርት እንቅስ ቃሴ በከፍተኛ ቀውስ ውስጥ ከቶታል። በወረርሽኙ ሳቢያ ትልልቅ የስፖርት ውድድሮች በመራዘማቸው፣ በመሰረዛቸው እና በመስተጓጐላቸው ኢንዱስትሪውን ከፍተኛ ገቢ እንደሚያሳጣው የተለያዩ ትንበያዎች አመልክተዋል። የስፖርት ኢንዱስትሪውን በስፖንሰ ርሺፕ የሚደግፉ ትልልቅ አለም አቀፍ ኩባንያዎች የበጀት ቀውስ ውስጥ መግባታቸው፣ ከትኬት ሽያጭ ከማርኬቲንግና ከተለያዩ ንግዶች የሚገኙ ገቢዎች መቆማቸው ሁሉንም ስፖርት ጎድቷቸዋል።በተለይ የእግር ኳስ ስፖርት ከፍተኛ ድርሻ የሚይዝ መሆኑ እየተነገረ ይገኛል።በዚህ አመት የእግር ኳሱ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራል ተብሎ ሲጠበቅ ከተላላፊው ቫይረስ ጋር በተያያዘ ገቢው በእጅጉ እያሽቆለቆለ ይገኛል።የአብዛኛዎቹ የእግር ኳስ ክለቦች ዋነኛ ገቢያቸውን የሚያገኙት ከሶስት ምንጮች ሲሆን፤ ይኸውም ከመገናኛ ብዙሀን የስርጭት መብት፣ ከስፖንሰርና ማስታወቂያዎች እንዲሁም በጨዋታ ወቅት ከስታዲየም የትኬት ሽያጭ እንደሆነ የወርልድ ኢኮኖሚ ፎረም መረጃ ያመላክታሉ።አስር በሚደርሱ ሊጎች ያለው ቁጥራዊ መረጃ እንደሚያሳየው ከሆነም ክለቦቹ ከሚዲያ መብት ብቻ ከሀምሳ ቢሊዮን ዶላር በላይ ያገኛሉ።ይህም ከአጠቃላይ ገቢያቸው ስልሳ ከመቶ ይሸፍናል።በወረርሽኙ ምክንያት የውድድሮች መቋረጥን ተከትሎ ክለቦች ከእነዚህ ምንጮች የሚያስገቡት ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ማሽቆልቆሉን ያመላክታል።ዴይሊሜይል በዚሁ ዙሪያ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን እንደ ማሳያ በመጥቀስ ያወጣው ይሄንኑ ያጠናክራል።የአለማችን እጅግ ተወዳጅ ከሆኑ ሊጎች በግንባር ቀደምነት የሚጠቀሰው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በወረርሽኙ ምክንያት በከፍተኛ ሁኔታ መጎዳቱን በዘገባው ጠቅሷል። ፕሪምየር ሊጉ ባለፈው አመት አዲስ በገባው ለሶስት አመታት ኮንትራት ቢሊየን ዶላር ከሚዲያ መብት ብቻ ለመሰብሰብ አቅዶ ነበር።እግር ኳሱ አሁን ካለው ቁመና አኳያ እቅዱን ማሳካት የሚቻል አይሆንም ሲል ዘገባው አትቷል።ውድድሩሁለት ወራትን እንኳን ሳያስቆጥር ክለቦቹ ከስልሳ እስከ አንድ መቶ ሀምሳ ሚሊየን ዶላር ኪሳራ ማስተናገዳቸውን እያስታወቁ ይገኛሉ።በመሆኑም ከቴሌቪዥን መብት ከሚገኝ ገቢ ብቻ እያንዳንዱ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ክለብ ሰባት መቶ ሀምሳ ሚሊዮን ፓውንድ ያጣል። ስለዚህም ነው ክለቦቹ ከተጫዋችና አሰልጣኞች ቡድን ባሻገር የሚገኙ ሰራተኞቻቸውን በጊዜያዊነት እያሰናበቱ ይገኛሉ ።የተጫዋቾቻቸውን ደመወዝ ለመክፈል በመቸገራቸውም አንዳንዶች ግማሽ ክፍያ ሌሎች ደግሞ የተወሰነ ቅናሽ በማድረግ እንደሚከፍሉ እያሳወቁ ይገኛሉ።ፕሪሚየር ሊጉ በዚህ ምስቅል ቅል ውስጥ ሆኖ ለማግኘት ያቀደውን ገቢ ማሳካት እንደማይችል ዴይሊ ሜል በዘገባው ተመልክቷል። በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ስፖርታዊ ክንውኖች መቆማቸው እንደ እንግሊዝና የመሳሰሉት ሊጎች ሁሉ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ሰለባ መሆኑ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።ከብሄራዊ ፌዴሬሽኑ መግለጫ በመነሳት በአለማችን ታላላቅ ክለቦች ላይ የተከሰተው የፋይናንስ ቀውስ መንገዱና የኪሳራው መጠን ቢለይም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከችግሩ አለመዳኑን የዘርፍ ሙያተኞች እየተናገሩ ይገኛሉ።በፕሪሚየር ሊጉ የሚገኙ አብዛኛዎቹ ክለቦች ከኮሮና ቀደም ብሎ በፋይናንስ ቀውስ የሚዋልሉ እንደሆኑ እሙን ነው። የተጫዋቾች ደመወዝ ለመክፈል የነበሩትን ውዝግቦች ወደ ኋላ መለስ ብለን ስናስታውስ ይሄንኑ እውነታ በሚገባ እንረዳለን።በክለቦቹ ላይ ከአስተዳደር፣ ከእቅድ፣ ገቢና ወጪን ያለማመጣጠን ችግሮች በስፋት የሚታዩ እንደሆነ የሚካድ አይደለም።ክለቦቹ ወጪን እንጂ ገቢን መሰረት ያደረገ የፋይናንስ ስርአት የማይከተሉ በመሆኑ በቀውስ እንዲቆዩ ሆነዋል።የኮሮና ወረርሽኝ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚፈጥረው ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ሲታከልበት በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ይሆናል።የወረርሽኙ ተፅእኖ ከክለቦች አልፎ የፌዴሬሽኖችን አቅም እየፈተነ ስለመሆኑ ከሰሞኑ የወጡ መረጃዎች ያመላክታሉ። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በኮቪድ ወረርሽኝ ምክንያት የገንዘብ ችግር ውስጥ በመግባቱ መንግስት የገንዘብ ድጎማ እንዲያደርግለት ጥያቄውን በደብዳቤ ማስገባቱን አስታውቋል።የብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ እንዳብራሩት፣ ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ መንግስት የገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርግለት ጥያቄ አቅርቧል መልስ እየጠበቀ ነው። ምክንያትም ሁሉም እንደሚያውቀው በኮቪድ ወረርሽኝ ሁሉም ነገር ቆሟል፣ የሁሉም አካላት ትኩረት ቅድሚያ ለሰው ልጆች ህይወት በሚል ስፖርቱን በሚመለከት ምንም አይነት እንቅስቃሴ እያደረጉ እንዳልሆነ ይታወቃል። ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ችግሩን መቋቋም በሚችልበት ቁመና ላይ አይደለም፣ ለዚህም ነው መንግስት የገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርግ በደብዳቤ የጠየቅነው ብለዋል።ሀገሪቱ ከገባችበት ፈተና አንፃር ብሄራዊ ፌዴሬሽኑን የመንግስትን ደጅ መጥናቱ ውጤትያመጣል የሚገመት አይሆንም ተብሏል።በተመሳሳይ የክለቦች እጣ ፈንታ ከዚህ የተለየ እንደማይሆን ከተለያዩ ወገኖች ግምቶች እየቀረቡ ይገኛሉ።ለዚህ እንደ መከራከሪያ በፕሪሚየር ሊጉ የሚሳተፍ አብዛኛዎቹ ክለቦች በመንግስት የሚደጎሙ መሆናቸውን ያነሳሉ። ሀገሪቱ እየገጠማት ካለው የኢኮኖሚ ቀውስ አንፃር መንግስት እንደቀደመው ለክለቦች ከፍተኛ ገንዘብ ስለማውጣቱ አጠራጣሪ ይሆናል ይላሉ።ከዚህ በመነሳት ክለቦችም ሆኑ ፌዴሬሽኑ ከነበረባቸው መጪውን ጊዜ ፈታኝ እንደሚሆንባቸው ሀሳባቸው እየሰነዘሩ ይገኛሉ። የአለም አቀፍ እግር ኳስ ማሀበር ፊፋ ከሰሞኑ ይፋ ያደረገው መረጃ ግን በኢትዮጵያን እግር ኳስ መፃኢ ጉዞ ላይ የተስፋ ጭላንጭል የፈጠረ ሆኗል። የፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ፤ የኮሮና ቫይረስ ለመከላከል የፊፋ አባል አገራት ለሆኑት ሁለት መቶ ብሄራዊ ፌዴሬሽኖች የ አንድ መቶ ሀምሳ ሚሊዮን ዶላር አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚደረግ አስታውቀዋል።በዚህ መሰረት እያንዳንዱ አባል ሀገራት ከሶስት ወራት በፊት የአምስት መቶ ሺህ ዶላር ከፊፋ ድጋፍ ይደረግላቸዋል ሲሉ አስታውቀዋል።ፊፋ የሚያደርገው ድጋፍ የአለም እግር ኳስ ከገባበት ቀውስ ያወጣው ይሆን የሚል ጥያቄ አጭሯል።በኢትዮጵያ ብቻም ሳይሆን በበርካታ ሀገራት በጉጉት የሚጠበቀው ገንዘብ ለማግኘት ፊፋ ቅድመ ሁኔታዎች ማስቀመጡም ተነግሯል።ሀገራት በወረርሽኙ ያደረሰባቸውን ተፅእኖ በተመለከተ በሚያቀርቡት ትንተና ላይ መሰረት ያደረገ ሊሆን ይችላልም ተብሏል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ይሄንኑ መሰረት ባደረገ መልኩ ተንትኖ ማቅረብ እንደሚጠበቅበት የዘርፍ ሙያተኞች እያሳሰቡ ይገኛሉ።ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ከክለቦቹ ጋር በሚገባ ተነጋግሮ የደረሰውን የጉዳትና የኪሳራ መጠን አስረጅና ገላጭ በሆነ መልኩ የሚያስረዳ ሰነድ መላክ ይኖርበታል።ብሄራዊ ፌዴሬሽኑም ሆነ ክለቦቹ ከወዲሁ ተቀራርበው መወያየትና ከድጎማው ተቋዳሽ መሆን ይገባቸዋል።ፕሪሚየር ሊጉ፣ብሄራዊ ሊጉ እና እታች የሚገኙት ክለቡች ምን ያህል ቀውስ እንደደረሰባቸው በሚገባ ተንትኖ ማቅረብ ይገባል።ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ በአፋጣኝ ወደ እንቅስቃሴ ካልተገባ ሰርገኛ መጣ አይነት እንዳይሆን ከወዲሁ ነቅቶ መረጃዎችን መከታተልን ይጠይቃል። አዲስ ዘመን ሚያዝያ ሀያ ሶስት ሁለት ሺህ ዳንኤል ዘነበ
የፊፋ ድጎማ እግር ኳሱን ይታደገው ይሆን
አለመግባባቱ ወጪና ገቢ እቃዎችን ለአጭር ጊዜም ቢሆን ሊያዘገይ ይችላል ተብሏል በጂቡቲ መንግስትና በዱባዩ የወደብ አስተዳዳሪ ኩባንያ ዲፒ ወርልድ መካከል በተፈጠረው አለመግባባት ሳቢያ፣ የጂቡቲ መንግስት ከኩባንያው ጋር የነበረውንና ለ አመታት የቆየ የወደብ አስተዳደር ስምምነት የጂቡቲ መንግስት ማቋረጡ የተሰማው ሀሙስ የካቲት ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ነበር። በሁለቱ ወገኖች አለመግባባት ሳቢያ በኢትዮጵያ ገቢና ወጪ እቃዎች ላይ ስጋት ሊፈጠር ይችል እንደሆነ ለኢትዮጵያ ማሪታይም ጉዳዮች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መኮንን አበራ ሪፖርተር ጥያቄ አቅርቧል። አቶ መኮንን በሰጡት ምላሽ፣ በጂቡቲ መንግስትና በዱባዩ ኩባንያ መካከል የተፈጠረው አለመግባባት የሁለቱ ወገኖች ጉዳይ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያ በዋናነት በምትገለገልበት የዶራሌህ ኮንቴይነር ማስተናገጃ ተርሚናል አገልግሎት ላይ ስጋት እንዳላቸው አቶ መኮንን ሳይጠቅሱ አላለፉም። ምንም እንኳ ዲፒ ወርልድ ግዙፍና በወደብ አስተዳደር ስራው ትልቅ ስም ያካበተ ኩባንያም ቢሆን፣ ከጂቡቲ መንግስት ጋር በተፈጠረው አለመግባባት ሳቢያ፣ ነገሮች ወደ ቀድሞ ቦታቸው ተመልሰው እስኪገቡ በሚኖረው የሽግግር ወቅት የኢትዮጵያን የወጪና ገቢ ንግድ በመጠኑም ቢሆን ሊያስተጓጉል የሚችል አጋጣሚ ሊፈጠር እንደሚችል ተገልጿል። ሆኖም በአጭር ጊዜ ውስጥ ነገሮች ተረጋግተው የወደብ አገልግሎቱም እንደነበረው ሊቀጥል እንደሚችል ያላቸውን ተስፋ የገለፁት አቶ መኮንን፣ የወደቡ የሰው ሀይልና የሎጂስቲክስ ፋሲሊቲዎችም ወደፊት በደንብ እንደሚታዩ አብራርተዋል። የጂቡቲ መንግስት ከዲፒ ወርልድ ጋር የነበረውን ግንኙነት ማቋረጡን ማስታወቁ ተከትሎ አብዛኛውን የኢትዮጵያን ገቢና ወጪ እቃዎች የሚያስተናግደውን የዶላራሌህ ኮንቴይነር ተርሚናል መንግስት በራሱ ለማስተዳደር ፍላጎት ይኑረው አሊያም ሌላ ኩባንያ ሊቀጥር ስለማሰቡ የሚታወቅ ነገር እንደሌለም ከአቶ መኮንን ለመረዳት ተችሏል። የጂቡቲ መንግስት ከዲፒ ወርልድ ኩባንያ ጋር የነበረውን የስራ ውል ለማቋረጥ የተገደደው በተደጋጋሚ ያደረገው ድርድር ከውጤት ሊደርስ ባለመቻሉ እንደሆነ አስታውቋል። የዱባይ ኩባንያ ሲያስተዳድረው የቆየውን ወደብ፣ በጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኦማር ጊሌህ ውሳኔ መሰረት መንግስት እንደተረከበው ተገልጿል። የጂቡቲ መንግስት ከኩባንያው ጋር የነበረው የስራ ስምምነት መሻሻል እንዳለበት፣ ለአገሪቱ ጥቅም ለማስጠበቅ ሲባልም ከዚህ ቀደም የነበረው የወደብ አስተዳደር ስምምነት የጂቡቲን ሏላዊ ጥቅም የሚፃረሩ አንቀፆች ያሉበት በመሆኑ የስምምነት ለውጥ እንዲደረግ መጠየቁ ተሰምቷል። የጂቡቲ መንግስት የአገሪቱን ሏላዊነት የሚፃረርና የህዝብ ጥቅም የሚነካ ነው ያለው ጥሰት ምን እንደሆነ ከመግለፅ ተቆጥቧል። ባለፈው ሀምሌ ወር ስትራቴጂካዊ የተባሉ የመሰረተ ልማት ስምምነቶችን በሚመለከት አዲስ ህግ ማውጣቷን ዘገባዎች ይጠቁማሉ። በአዲሱ ህግ መሰረት የጂቡቲ መንግስት ስትራቴጂካዊ የሆኑ የመሰረተ ልማት አውታሮችን ለማስተዳደርና የኦፕሬሽን ስራዎችን ለመምራት የተገቡ ስምምነቶች ላይ ዳግም ድርድር እንዲካሄድ ከማድረግ ባሻገር እስከማቋረጥ የሚደርሱ እርምጃዎችን መውሰድ እንደሚችል ተደንግጓል። ይህንን ተከትሎም ከዲፒ ወርልድ ጋር የነበረውን ስምምነት ለማደስ የጂቡቲ መንግስት በቅንነት መንፈስ ያደረገውን ሙከራና በድርድር መፍትሄ ለማፈላለግ ሲያደርግ የነበረውን ጥረት የዲፒ ወርልድ አስተዳደር ውድቅ ያደረገው ያለምንም ምክንያት ነው፤ በማለት በመግለጫው አስፍሯል። የአስተዳደር ስራውንና የወደብ ኦፕሬሽን ተግባሩን ከኩባንያው መንጠቁን ይፋ ከማድረጉ በፊት የጂቡቲ መንግስት ለመጨረሻ ጊዜ የእንደራደር ጥያቄ ያቀረበው ጥር ሀያ አራት ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ወይም ፌብሯሪ አንድ እንደነበር አስታውሶ፣ ከዲፒ ወርልድ ያገኘው ምላሽ ግን ኩባንያው ጉዳዩን በግልግል ዳኝነት ለማየት መፈለጉን የሚገልፅ ምላሽ ብቻ እንደነበር አስታውቋል። ይህ በመሆኑም መንግስት ስምምነቱን በማፍረሱ የሚጠበቅበትን ካሳ ለመክፈል ዝግጁ እንደሆነ ይፋ አድርጓል። የጂቡቲን መንግስት ውሳኔ የተቃወመው ዲፒ ወርልድ በበኩሉ፣ ድርጊቱ ፍትሀዊነትና ተገቢነት የጎደለው ሲል ከማጣጣሉም በላይ፣ መንግስት ላለፉት አመታት የነበረውን ስምምነት በማፍረስ አዲስ ስምምነት በጫና ለማስፈረም የተደረገ ነው ሲል ኮንኖታል። በመሆኑም ኩባንያው በለንደን የጀመረው የግልግል ዳኝነት ሂደት፣ በዶራሌህ ኮንቴይነር ተርሚናል ያለውን ንብረቱ በጂቡቲ መንግስት ሲወረስበት ለደረሰው ጉዳት ጥበቃ እንዲሰጥለት በማሰብ የወሰደው እርምጃ እንደሆነ አስታውቋል። ዲፒ ወርልድ በዶራሌህ የኮንቴይነር ተርሚናል የስላሳ ሶስት በመቶ የባለቤትነት ድርሻ እንዳለው ከማስታወቁም ባሻገር፣ የለንደኑ የግልግል ዳኝነት አካል በሁለቱ ወገኖች መካከል ከዚህ ቀደም የነበረው ስምምነት ፍትሀዊና ምክንያታዊ፤ ነው በማለት ውሳኔ መስጠቱንም ኩባንያው ያወጣው መግለጫ አስፍሯል። በሁለቱ መካከል የተፈጠረው አለመግባባት በዚህ አኳኋን ከቀጠለ አብዛኛውን የኢትዮጵያ እቃዎች በሚስተናዱበት ወደብ መጉላላት ሊከሰት እንደሚችል ከወዲሁ በርካታ አስመጪና ላኪዎችን ስጋት ውስጥ እንደከተተ እየተገለፀ ነው። ወደቡ ለተወሰነ ጊዜ እንኳ አገልግሎት ቢያቋርጥ በተለይ ወደ ውጭ በሚላኩ እቃዎች ላይ የሚፈጠረው መጉላላት፣ በላኪዎችና በአገሪቱ የወጪ ንግድ እንቅስቃሴ ላይ ሊያስከትል የሚችለው ኪሳራ ያሳሰባቸው ነጋዴዎች ብቻም ሳይሆኑ በዘርፉ የሚመለከታቸው የመንግስት ሀላፊዎችም ጉዳዩን በንቃት እንደሚከታተሉት ለማወቅ ተችሏል።
ጂቡቲ የዱባዩን የወደብ አስተዳዳሪ ኩባንያ ማሰናበቷ በኢትዮጵያ ላይ ስጋት ደቅኗል
ሙዚቃን ለትግል በመጠቀም እና ለትግል በማነሳሳት ረገድ ሀጫሉ ሁንዴሳንና አሊ ቢራን የሚያመሳስላቸው ነገር አለ። በኦሮምኛ ሙዚቃ አዋቂዎችም ዘንድ ድምፃዊ ሀጫሉ የዚህ ዘመን አሊ ቢራ ነው፤ ለሚቀጥሉት አስርት አመታት ከአሊ ቢራ ተቀብሎ ወደሚቀጥለው ትውልድ የሚያስተላልፍ ነው ሲሉ ይገልፁታል። እነዚህ ሁለቱ ድምፃውያን ይተዋወቁ ነበር አሊ ቢራስ አርቲስት ሀጫሉን እንዴት ይገልፀዋል ለኔ ሀጫሉ የጀግኖች ጀግና ነው፤ የምንኮራበት ነው። በማለት አሊ ይናገራል። መጀመሪያ እነዚህ ሁለት ሰዎች፣ አሊ ቢራና ሀጫሉ፣ የተዋወቁት በአካል አልነበረም። ኢትዮጵያ ከመምጣቴ በፊት የዛሬ አመት አካባቢ የሙዚቃ ቪዲዮ ላይ ነው ያየሁት ይላል አሊ ቢራ። የሙዚቃ ቪዲዮውም ላይ አሊ እንዳው ያኔ ሀጫሉ ገና አፍላ ወጣት ነበር ። ነገር ግን ይላል አሊ፣ ሙዚቃዎቹና የሙዚቃ ቪዲዮዎቹ ስለባህል፣ ሰለ ማንነት፣ ስለ ቋንቋ ቀልብ በሚገዛ መልኩ ይሰራ ስለነበር አድናቆትም እንዳደረበት ለቢቢሲ ገልጿል። በጣም የሚያድግ ትልቅ የኪነጥበብ ባለሙያ የታየኝ ገና ያኔ ነበር ይላል አሊ ቢራ። በወቅቱም አሊ ወደ ኢትዮጵያ የሚመላለስበት ጊዜ ሲሆን ጠቅልሎም ወደ ኢትዮጵያ ከተመለሰ በኋላ፣ ድምፃዊ ሀጫሉ በሙዚቃ ስሙ ገንኖ፣ ከኦሮምኛ ተናጋሪ ውጪ ያሉ ሌሎች ኢትዮጵያውያን የሙዚቃ አድናቂዎች ዘንድ ተወዳጅነት አትርፎ ነበር። ከዚያም አሊና ሀጫሉ በአካልም ተዋወቀው በደንብ መቀራረብ መጀመራቸውን ይናገራል። እርሱም የምገልፀው እንደ ሙዚቀኛ ሳይሆን እንደ ጀግና ነው። የሚለው አሊ የሀጫሉ ሁንዴሳን ጥንካሬ፣ አቋም፣ በዘፈኖቹ የሚያስተላልፋቸው መልእክቶች፣ ከኦሮሞ ህዝብ ተሻግሮ፣ የተጨቆኑ ሰዎች ባሉበት ሁሉ ሊደመጥ የሚችል መልእክት እንዳለውም ይናገራል። የሚዘፍንበት ቋንቋ ነው እንጂ ኦሮምኛ የዘፈኑ መልእክቶች አለም ላይ ላለ ለተጨቆነ ህዝብ ሁሉ የሚሆን ነው። ይላል አሊ ለዚህ ነው የእኛ ጀግና ብቻ ሳይሆን የአለም ህዝብ ጀግና ነው ብዬ ነው የማየው ሲል ሀሳቡን አፅንኦት ይሰጠዋል። ነፍሳችን አንድ ናት እኔ አቋሜ እንደ ሀጫሉ ነው የሚለው ድምፃዊ አሊ ቢራ፣ ለህዝቤ ያለኝ ተቆርቋርነት እንደ ሀጫሉ ነው በማለት ሁለቱ በሀሳብ አንድ መሆናቸውን ያስረዳል። እርሱንም እዚያ መስመር ላይ አየሁት፤ እኛ የኔና የእርሱ ነፍስ አንድ ናት፤ ሀሳባችንም አንድ ነው። እርሱም በዘፈኖቹ ውስጥ ስሜን አንስቷል፤ ይኼ ማለት የአሊ ቢራ መስመር ላይ ነው ያለሁት፤ እርሱ ያለውን ነው እኔም የምለው እንዳለ አድርጌ ነው የምረዳው። በዚህም ምክንያት ሞቱ እጅግ በጣም እንደጎዳው ገልፆ እርሱ ብቻ ሳይሆን፣ አሜሪካውያን፣ ጃፓናውያን፣ ኡጋንዳውያን፣ የድምፃዊ ሀጫሉ ስራዎችን ተተርጉመው ቢሰሙ ሀዘኑም የእነርሱ ጭምር ይሆን እንደነበር ይገልፃል። ከእጃችን ላይ ነጠቁን፤ በአካል እንጂ የነጠቁን ነፍሱ ከእኛ ነጋር አለች በማለት ሁሌም በህዝቡ ልብና መንፈስ እንዲሁም ታሪክ ውስጥ አብሮ እንደሚኖር ይገልፃል። የሀጫሉን ሞት እንዴት ነው የሰማው ድማፃዊ አሊ የሀጫሉን ሞት ሌሊት ተደውሎ እንደተነገረው ያስታውሳል። መናገር ነበር ያቃተኝ፤ ደነገጥሁ፤ ህልም ነው እንጂ ይህ እውነት አይሆንም እያልኩ ነበር፤ ሲቆይ ግን እውነት ሆነ። ቀናት በተቆጠሩ ቁጥር ሀዘኑ እየበረታ እንደመጣ በመግለፅም በወቅቱ መናገር እንዳልቻለ፣ እጅግ በጣም እንደተጎዳ ለቢቢሲ ገልጿል። ያበረታታንኝ ነገር የሀጫሉ አይነቶች ብዙ ሚሊየኖች ይመጣሉ። በዚህም በሚቀጥለውም ትውልድ ይነሳሉ ብለን እናስባለን። ይህ ያበረታታኛል። ብሎ ከስራዎቹ ውስጥ የትኛዎቹን ነው የምትወደው ተብሎ በቢሲ የተጠየቀው አሊ፣ ለመመለስ ተቸግሮ ነበር። ይህኛው ከዚህኛው ይልጣል ብዬ መመምረጥ ይቸግረኛል። ሀጫሉ አስሬ ዘፈን ቢዘፍን፣ ሶስተኛው ጥሩ ነው፤ አስረኛው እንዲህ ነው ማለት ይቸግረኛል፤ ሁሉም እኩል ዋጋ ነው ያላቸው ለእኔ የድምፋዊ ሀጫሉን የሙዚቃ ክህሎትም በማንሳት፣ ግጥሞቹን ራሱ እንደሚፅፍ፣ ዜማ እንደሚሰራ፣ ሰው እንኳ ሰርቶ የሰጠው ቢሆን የህዝቡንና የአድማጩን ስሜት በሚኮረኩር መንገድ የማቅረብ ችሎታ ያለው ትልቅ ተሰጥኦ የነበረው ድምፃዊ እንደነበር ይመሰክራል። ሀጫሉን በቃላት ለመግለፅ የተቸገረው አሊ በህይወቴ ያየሁት ይህ ልጅ የፈጣሪ መልእክተኛ እንደሆነ ነው። ብሏል። ፈጣሪ ለእያንዳንዱ ህዝብ አንድ አንድ ሰው ያስነሳል የሚለው አርቲስት አሊ ቢራ፣ ሀጫሉም በእነ ማርቲን ሉተር ኪንግ፣ ማህተመ ጋንዲ፣ ኔልሰን ማንዴላ፣ ማልኮም ኤክስ ደረጃ እንደሚያየውም ለቢቢሲ አስረድቷል። የህዝቡን ብሶት፣ ያለምንም ፍርሀት፣ አፈሙዝ ፊት ለፊት ሆኖ፣ ሲናገር የነበረ እንደሆነ ያብራራል። አስከትሎም እንዴት መታወስ እንዳለበት ለቢቢሲ ሲገልፅ፣ እርሱ ስራዎቹን ሲሰራ ልታወስ ብሎ አለመስራቱን በመጥቀስ ነው። ነገር ግን በማለት መታወስ ደግሞ አለበት። ሀውልቶች ማቆም፣ መንገዶች፣ ትምህርት ቤቶች በእርሱ ስም፣ ማን እንደነበር ስለእርሱ ማስተማር አስፈላጊ ነው ይላል። በመጨረሻም ፈጣሪ ጀግናችንን ነፍሱን በገነት እንዲያኖርልን፤ ለወደፊት ደግሞ እርሱን የሚተካ፣ የህዝባችንንም ፍላጎት ከዳር የሚያደርስ ጀግና እንዲሰጠን እንለምናለን ብሏል።
ድምፃዊ አሊ ቢራ ስለ ሀጫሉ ሁንዴሳ ምን ይላል
ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ አምስት ዘነብ ወርቅ ታቦት ማደሪያ አካባቢ፣ ጤፍን ከጀሶ ጋር በመቀላቀል እንጀራ ጋግረው ለጠቃሚዎች ያሰራጩ ግለሰቦች በአስር አመት ፅኑ እስራትና በገንዘብ ተቀጡ። ድርጊቱን የፈፀሙት ተከሳሾቹ አንደኛ አልማዝ ሺፈሬና ሁለተኛ ጥሩሴት ወዲያ በቁጥጥር ስር የዋሉት ሀምሌ ቀን ሁለት ሺህ ስምንት አመተ ምህረት ጤፍን ከጀሶ ጋር ቀላቅለው በመጋገር ላይ እያሉ ነበር። ተከሳሾቹ በቁጥጥር ስር በዋሉበት ወቅት ሊጋገር የተዘጋጀ በተለያዩ እቃዎች ተቦክቶ የተቀመጠ የጤፍና የጀሶ ድብልቅ ተይዟል። ተከሳሾቹ ከጤፍና ከጀሶ ድብልቅ ቡኮ በማዘጋጀት በቀን እስከ አንድ ሺህ እንጀራ በመጋገር በደንበኝነት ለያዟቸው ሆቴሎችና ተጠቃሚዎች እንደሚያቀርቡ በክሱ ተጠቅሷል። ከዚህ ቡኮና ከተጋገረው እንጀራ የተወሰደ ናሙና በላቦራቶሪ ተመርምሮ፣ የሰው ልጅ ቢመገባቸው ከፍተኛ የሰውነት ክብደት መቀነስና እስከሞት የሚያደርስ አደጋ እንደሚያስከትል ተረጋግጧል። ተከሳሾቹ የማይገባቸውን ጥቅም ለማግኘት በማሰብ የተበላሹ እቃዎች በመስራትና በመሸጥ እንዲሁም ጥራታቸውን በማርከስ ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸዋል። የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራኒዮ ምድብ ችሎት ክሱን ለተከሳሾች በንባብ ያስደመጠ ሲሆን፣ ተከሳሾቹ የወንጀል ድርጊቱን አልፈፀምንም ብለው ክደው ተከራክረዋል። ይሁን እንጂ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ያቀረበባቸውን የሰውና የሰነድ ማስረጃ ማስተባበል ሳይችሉ ቀርተዋል። የግራና ቀኙን ክርክር ያደመጠው ፍርድ ቤቱም ተከሳሾቹን ጥፋተኛ ብሏቸዋል። የቀደመ የወንጀል ሪከርድ የሌለባቸው መሆኑን እንደ ቅጣት ማቅለያ በመያዝም አንደኛ ተከሳሽ በአስር አመት ፅኑ እስራትና በአምስት ሺህ ብር፣ እንዲሁም ሁለተኛ ተከሳሽን በአስር አመት ፅኑ እስራትና በአንድ ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል። ከአዲስ አበባ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ በተገኘ መረጃ መሰረት በከተማዋ ሁለት ሰባት መቶ ሀያ አንድ በዳቦ፣ ኬክ ብስኩትና እንጀራ ምርት የተሰማሩ፣ አንድ መቶ ሰባ ስምንት የምግብ ዘይት የሚያመርቱ፣ አንድ መቶ ሀያ አምስት በእንስሳት እርባታና ተዋፅኦ ማምረት ላይ የተሰማሩ አሉ። ወደ አምስት መቶ የሚሆኑ በባልትና ውጤቶችና በመሳሰሉት የተሰማሩ ነጋዴዎችና ድርጅቶችም ይገኛሉ። በህገወጥ ንግድ የተሰማሩም ጥቂት አይደሉም። ከእነዚህ መካከል አንዳንዶቹ በአቋራጭ ለመክበር ሲሉ በሚያዘጋጁት ምግብ ላይ ባእድ ነገር እየቀየጡ ለገበያ ሲያቀርቡ ይታያል። የምግብነት ይዘት የሌለውን ባእድ ነገር ከምግብ ጋር መቀላቀል በኩላሊት፣ በጉበት፣ በጨጓራ፣ በምግብ ቱቦ ላይ ከፍተኛ የጤና ችግር ከማድረሱም ባለፈ በውስጡ የሚኖረው የኬሚካል ይዘት ለካንሰር በሽታ አስተዋፅኦ የሚደረግበት ሁኔታ መኖሩን የሚናገሩት በፉድ ኤንድ ኒውትሪሽን ሶሳይቲ ኦፍ ኢትዮጵያ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያው ዶክተር አብነት ተክሌ ናቸው። ምግብነት የሌለው ነገር ከምግብ ጋር ተቀላቅሎ ወደ ሰውነት በሚገባበት ጊዜ በሶስት አይነት መንገዶች ጉዳቶችን ያደርሳል። የመጀመሪያው አላስፈላጊ ኬሚካል ወደ ውስጥ በሚገባበት ጊዜ የሚፈጠረው የጤና ቀውስ ነው። ሁለተኛው በአይን የማይታይ ተህዋሲያን በውስጡ ሲኖር አልያም ከተህዋሲያኑ በሚመነጭ መርዛማ ንጥረ ነገር የሚፈጠረው ነው። ሌላው ተደባልቀው ወደ ሰውነት በሚገቡበት ጊዜ የሚደርሰው አካላዊ አደጋ ነው። ማንኛውም ኬሚካል ወደ ሰውነታችን ሲገባ በጉበት መጣራት ይኖርበታል። ጉበት በሰውነታችን ያልተለመዱ ኬሚካሎችን ለማጣራት በሚያደርገው ሂደትም ይጐዳል። ጨጓራም እንደዚሁ፤ የሚሉት ዶክተር አብነት፣ ባእድ ነገር ወደ ሰውነት ውስጥ በሚገባበት ወቅት በማንኛውም አይነት መንገድ የጤና ችግር ሊፈጥር እንደሚችል ያስረዳሉ። በአጭር ጊዜ ከሚታዩት ችግሮች ባሻገር ከጊዜ በኋላ የሚከሰቱ መኖራቸውን፤ ባእድ ነገርን ከምግብ ጋር ቀላቅሎ ለገበያ የማቅረቡን ድርጊት የሚፈፅሙ ግለሰቦችም ይህንን ተገን በማድረግ በድፍረት እየሰሩበት እንደሚገኙ ይጠቁማሉ። የሸማቹን ጤና አደጋ ላይ የሚጥል ተግባር መፈፀም ወንጀል ነው። በዚህ ወንጀል ተከሰው ጥፋተኛ የተባሉ በአንድ አመት ነግደው ካገኙት ገቢ ላይ አስር በመቶውን እንዲከፍሉ ይደረጋል። እንደ ጥፋታቸው ክብደትና ቅለትም ከሶስት አመት እስከ ሰባት አመት የሚደርስ የእስራት ቅጣት ይፈረድባቸዋል። በቅቤ፣ በወተት፣ በማር፣ በእንጀራና በሌሎችም ለምግብነት በሚውሉ ነገሮች ላይ ባእድ ነገር በመቀየጥ ተግባር ወደኛ የሚመጡ ኬዞች ብዙ ናቸው፤ ያሉት በንግድ ውድድርና ሸማቾች ጥበቃ ባለስልጣን የህዝብ ግንኙነት ማስተባበሪያ ሀላፊ አቶ እንዳልካቸው ፀጋዬ ናቸው። በኢትዮጵያ የምግብ የመድሀኒትና ጤና ክብካቤ አስተዳደር ቁጥጥር ባለስልጣን አዋጅና ደንብ መሰረት የምግብ መልክን ለማሳመርና ክብደትን ለመጨመር ሲባል ምግብን ከባእድ ነገር ጋር መደባለቅ በህግ የተከለከለ ነው። ባለፈው አመት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ጤፍን ከሰጋቱራ ጋር ቀላቅሎ ለገበያ የማቅረቡ ሁኔታ በስፋት ታይቶ ነበር። በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማም እንደዚሁ ከሸክላ ጋር የተቀየጠ ሀያ ኩንታል በርበሬ እንዲወገድ፣ ድርጊቱን የፈፀሙም ለህግ እንዲቀርቡ መደረጉን ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የተገኘ መረጃ ያሳያል። በተግባሩ የተሰማሩት ህጋዊ ፈቃድ የሌላቸው በቤታቸው ውስጥ ተደብቀው የሚሰሩ ናቸው። ከፈቃድ ጋር በተያያዘም ውስብስብ ነገሮች ታይተዋል። በተለይ በየካ ክፍለ ከተማ ምንም አይነት ፈቃድ ሳይኖራቸውና ጉዳዩ ከሚመለከተው መንግስታዊ አካል የብቃት ማረጋገጫ ሳያገኙ ለ ምጣዶች የሚያገለግል የኤሌክትሪክ ሀይል ተገጥሞላቸው ሲሰሩ የቆዩ፣ በተመሳሳይ የወንጀል ተግባር የተሰማሩን በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል።
ጤፍን ከጀሶ ጋር በመቀላቀል እንጀራ ጋግረው ያሰራጩ ግለሰቦች ተቀጡ
ዋዜማ ራዲዮ የታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሀይሌ ገብረስላሴ ንብረት የሆነ ሪዞርት በአስቸኳያ ጊዜ አዋጁ ስበብ በኮማንድ ፖስቱ እንዲዘጋ መደረጉን የዋዜማ ሪፖርተሮች አረጋግጠዋል።በኦሮምያ ክልል ሱሉልታ ከተማ የሚገኘውያያ ሪዞርት ባለፈው ሳምንት የተጠራውን የሶስት ቀናት የስራ ማቆም አድማ ተከትሎ አገልግሎት በማቋረጡ ሳቢያ የኮማንድ ፖስቱ ተቆጣጣሪዎች እንዳሸጉትና እስከ ቅዳሜ ምሽት ድረስ ተዘግቶ እንደነበር ተመልክተናል።ድርጅቱን ለማስከፈት አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት እያደረገ እንደነበርም የደረሰን መረጃ ያመለክታል።ይህ ጉዳይ በእንጥልጥል ባለበት ወቅት ሀይሌና ሌሎች ለመንግስት ቅርብ የሆኑ የሀገር ሽማግሌዎች የኢትዮጵያ ቀውስ በሽምግልና እንዲፈታ ሙከራ እያደረጉ የነበረበት ወቅት ነው።ሀይሌ በመንግስት መገናኛ ብዙሀን ቀርቦ የስራ ማቆም አድማ በሰለጠነው አለም ታይቶ የማይታወቅ የተቃውሞ ስልት ነው ሲል በማጣጣሉ ከፍተኛ የህዝብ ተቃውሞ እየቀረበበት ስንብቷል።የተቃውሞው ምክንያት ስራ አጥነት ነው ያለው ሀይሌ ችግሩን በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ መክሯል።ሀይሌ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ትላልቅ የንግድ ተቋማትን ገንብቶ የሚንቀሳቀስ ሲሆን በፖለቲካ ጉዳዮች ላይ የሚሰጣቸው ብስለት የሚጎድላቸው አስተያየቶቹ አትሌቱ ለአመታት የተጎናፀፈውን ክብር የማይመጥኑ በመሆናቸው ይተቻል።
የሀይሌ ገብረስላሴ የንግድ ተቋም በኮማንድ ፖስቱ ትእዛዝ ተዘጋ
በደርግ ዘመነ መንግስት የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና የትምህርት ሚኒስትር የነበሩት ኮል ጎሹ ወልዴ ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል።የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሂሩት ዘመንና እና በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአሜሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ነብያት ጌታቸውን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች አቀባበል አድርግውላቸዋል።የቀድሞው ሚኒስትር በቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የደርግን አገዛዝ በመቃወም ሀላፊነታቸውን በፈቃዳቸው ከለቀቁና ኑሯቸውን በአሜሪካ ካደረጉ ጀምሮ ላለፉት አመታት የአገራቸውን መሬት ሲረግጡ የመጀመሪያቸው መሆኑን ገልፀዋል።ኮል ጎሹ ወልዴ አመጣጣቸው የአገሪቱን አጠቃላይ የለውጥ ሂደት ለማየት ለረጅም ጊዜ የናፈቋቸውን ዘመድ ወዳጆች ለማግኘትና የተጀመረውን የሰላም የፍቅርና የመደመር ሂደት በሚችሉት መጠን ለመደገፍ መሆኑን ገልፀዋል።ምንም አይነት ፖለቲካዊ ውድድር የማድረግም ሆነ ስልጣን የማግኘት ፍላጎት የለኝም ያሉት ኮል ጎሹ በአሁኑ ወቅት በአገራችን የተጀመረው የሰላም የእርቅና የመደመር እንቅሴቃሴ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ በመሆኑ እርሳቸውን ጨምሮ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊደግፈው እንደሚገባ በማመን መምጣታቸውን ጠቁመው ለዚህም ለጠቅላይ ሚኒስተር ዶክተር አቢይ አህመድ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።ወጣቱ የሰላምን አስፈላጊነት በሚገባ ተገንዝቦ ለግጭት ከሚዳርጉ እንቅስቃሴዎች እንዲቆጠብ ጥሪ አቅርበዋል። ማንኛውንም ጥያቄዎች በሰላማዊ መንገድ በማቅረብ መፍትሄ ማግኘት የሚያስችል ሁኔታ ተፈጥሯል የሚል እምነት እንዳላቸውም ተናግረዋል።ለዚህም ያላቸውን ልምድና ተሞክሮ ለማጋራትና ለሰላማዊ ሂደቱ መጎልበት የተቻላቸውን አስተዋፅኦ ለማበርከት ቃል ገብተዋል።ምንጭ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
ኮል ጎሹ ወልዴ አዲስ አበባ ገቡ
አዲስ አበባ፣ ነሀሴ ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በክረምት የበጎ አድራጎት ስራ የማህበረሰቡን ችግር ለመቅረፍ እኔ ለወገኔ ጥላ እሆናለሁ በሚል መሪ ቃል እንደ ክልል በአንድ ቀን የአንድሺህ አንድ መቶ የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ ስራ እየተከናወነ መሆኑ ተገለፀ። የኦሮሚያ የእቅድና የኢኮኖሚ ልማት ኮሚሽነር ዶክተር ተሾመ አዱኛ በዛሬው እለት በጅማ ዞን ዴዶ ወረዳ ተገኝተዉ የክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት አስጀምረዋል። በዚሁ ወቅት በተለያዩ ምክንያቶች አቅም አንሷቸው መኖሪያ ቤታቸው ዘሞ ያስቸገራቸውን የአቅመ ደካሞችን ቤት በህብረተሰቡ ተሳትፎ መስራት መቻሉ ፍትሀዊ የሀብት ክፍፍል እንዲኖርና ሁሉም እኩል ተጠቃሚ ለማድረግ የበጎ አድራጎት ስራ ከፍተኛ ድርሻ ስላለዉ ለወደፊትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የጅማ ዞን ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ፅህፈት ቤት ሀላፊ ወይዘሮ ፈዲላ ቃዲ እንደ ጅማ ዞን በአንድ ቀን በዞኑ ሁሉም ቀበሌዎች አምስት መቶ ስልሳ ዘጠኝ የአቅመ ደካማ ቤቶችን ከስላሳ አራት ሚሊየን ብር በላይ በሚገመት ወጭ መሰራታቸውም ነው የተገለፀው። የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዱልሀኪም ሙሉ በዞኑ እስካሁን ድረስ በተሰሩ የበጎ አድራጎት ስራዎች የህብረተሰቡን ማህበራዊና ምጣኔ ሀብታዊ ችግሮች መፍታት መቻሉን ነው የተናገሩት። ይህ መልካም ስራ የህብረተሰቡን የአብሮነትና የመረዳዳት ባህል እንዲዳብር ስላደረገ ስራዉ ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት። ተስፋሁን ከበደ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ ድረ ገፅ፦ ፌስቡክ፡ ዩትዩብ፦ ቴሌግራም፦ ትዊተር፦ በመወዳጀት ይከታተሉን። ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
ፍትሀዊ የሀብት ክፍፍል እንዲኖር የበጎ አድራጎት ስራ ከፍተኛ ድርሻ አለዉ የኦሮሚያ የእቅድና የኢኮኖሚ ልማት ኮሚሽን
አዲስ አበባ፣ መስከረም ዘጠኝ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ስር ያሉ ዘጠኝ የልማት ድርጅቶች ከታክስ በፊት የስምንት ነጥብ ሁለት ቢሊየን ብር ትርፍ ማግኘታቸው ተገለፀ። በተጠናቀቀው የሁለት ሺህ በጀት አመት በአስተዳደሩ ስር ካሉት የልማት ድርጅቶች በአጠቃላይ አርባ አምስት ነጥብ ሶስት ቢሊየን ብር ጠቅላላ ገቢ መገኘቱንም ኢዜአ ዘግቧል። ገቢው ከባለፈው አመት ጋር ሲነፃፀር የሀያ ሰባት በመቶ ብልጫ እንዳለው ተጠቁሟል። ድርጅቶቹ ለተለያዩ የሀብረተሰብ ክፍሎች ስድስት መቶ አራት ነጥብ ሰባ ዘጠኝ ሚሊየን ብር የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ማሀበራዊ ሀላፊነታቸውን መወጣታቸውም ነው የተገለፀው። በበጀት አመቱ በቋሚ፣ በኮንትራትና በጊዜያዊ ቅጥር ለስልሳ አምስት ሺህ ሶስት መቶ ሰባ አንድ ዜጎች የስራ እድል መፍጠራቸውም በዘገባው ተመላክቷል። ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ ድረ ገፅ፦ ፌስቡክ፡ ዩትዩብ፦ ቴሌግራም፦ ትዊተር፦ በመወዳጀት ይከታተሉን። ኢንስታግራም፦ ቲክቶክ፦ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
ዘጠኝ የልማት ድርጅቶች ስምንት ነጥብ ሁለት ቢሊየን ብር ትርፍ ማግኘታቸው ተነገረ
ከኡመልኸይር ቡሎ ካዪላ ዊህለር የተወለደችው ሁለት እግርና አንድ እጅ ሳይኖራት ነው። ሀኪሟም ዋናን እንደ አንድ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እንድትጠቀም ይመክራት ነበር። በእዚህ መሰረት ባደረገችው ጥረት ዊህለር ግን በ አመቷ በዋና የአለምን ሪከርድ ለመስበር ችላለች። ሲ ኤን ኤን እንደዘገበው ታዳጊዋ በብራዚል ሜክሲኮና ኔዘርላንድ ውድድሯን ያደረገች ሲሆን፤ በሁለት ሺህ ፓራኦሎምፒክ ለመወዳደር እቅድ ይዛለች። በሁለት ሺህ በተካሄደውሀምሳ ሜትር የሴቶች ሻምፒዮን ተወዳድራ አዲስ ሪኮርድ አስመዝግባለች። ነገሩን ሁሉ ለመግለፅ አስቸጋሪ ነው። ስሟ ሲጠራና ዩናይትድ ስቴትን መወከሏን ሳውቅ በጣም ተገረምኩ፣ ማመን አቃተኝ፣ ከደስታ ብዛት የምይዝ የምጨብጠውን አጣሁ። ይች እኮ የእኔ ድንቅ ልጅናት አልኩኝ ይላሉ እናቷጆሲ ዊህለር። ሁሌም ምንም ማድረግ የማትችይው ነገር የለም እያልን እንነግራታለን። ነገር ግን ነገሮችን ላንቺ ማድረግ እንዲመቹ ማመቻቸት ይጠበቅብናል ስለምንላት እርሷም በጥረቷ ቀጠለች ሲሉ አክለዋል። ዊህለር በማትዋኝባቸው ጊዜያት ቤዝቦል እና ቦውሊንግ በመጫወት ጊዜዋን ታሳልፋለች በትምህርቷም ከፍተኛ ውጤት የምታስመዘግብ የደረጃ ተማሪ ስትሆን፤ በኮምዩኒቲ ኮሌጆች አድቫንስድ ኮርሶችን ትወስዳለች። ንቁ ተሳተፎም ታደደርጋለች። በእዚህ አመት ባስመዘገበችው ከፍተኛ የአትሌቲክስና የአካዳሚክ ውጤት ስኩላ ስቲክ የተባለ የክብር ስያሜ አግኝታለች። በርግጥ ዊህለር በሁለት ሺህ ም ፓራኦ ሎምፒክ ለመወዳደር ተመርጣ ነበር። ነገር ግን እንዳጋጣሚ ሆኖ አብሯት የሚወዳደር ሰው ባለመኖሩ ሳትወዳደር ቀርታለች። ምክንያቱ ደግሞ በፓራኦሎምፒክ የሚሳተፉ ተወዳዳሪዎች የሚመደቡት እንደ አካል ጉዳታቸው ደረጃ በመሆኑ በእርሷ የጉዳት ደረጃ የሚወዳደር ሰው ባለመኖሩ ነው። አምና በፓራኦሎምፒክ አልተወ ዳደርኩም ነበር። ምክንያቱም በእኔ ምድብ የምትወዳደር ሌላ ሴት ተወዳዳሪ አልነ በረችም። የእኔ ምድብ ኤስ ዋን ሲሆን፤ በእዚህ ምድብ የሚካተቱ ሰዎች ከፍተኛ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ናቸው ትላለች ዊህለር። ሀገሬን በመወከል መወዳደር እፈል ጋለሁ። አዲስ ሪኮርድ ማስመዝገብና ሜዳሊያ ማግኘት በጣም የሚያስደስትና የሚያስገርም ነገር ቢሆንም እኔ ግን ከውድድሩ ባሻገር አርአያ በመሆን እዚያ ቦታ መገኘት እፈልጋለሁ ብላለች።
ሁለት እግርና አንድ እጅ አልባዋ የዋና ሻምፒዮን
የአዲስ አበባና የአዲስ አበባ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ የጋራ ማስተር ፕላን በገጠመው ተቃውሞ ከተሰረዘ በኋላ፣ የፌዴራል መንግስት በመላ አገሪቱ የተቀናጀ የከተማ ፕላን ለመፍጠር ያረቀቀው አዋጅ ለፓርላማ ቀረበ። ረቂቁ በስራ ላይ የሚገኘውን የከተማ ፕላን አዋጅ ቁጥር አምስት መቶ ሰባ አራት ሁለት ሺህ ሙሉ በሙሉ የሚተካ ሲሆን፣ አላማውም በስራ ላይ ያለው አዋጅ ላይ የታዩ የአፈፃፀም ችግሮችን መቅረፍ ስለመሆኑ የረቂቁ ማብራሪያ ይገልፃል። አጠቃላይ አላማውም ከአገሪቱ ፖሊሲና የእድገት አቅጣጫ ጋር የተጣጣመና የተቀናጀ የልማት ፕላን እንዲኖር ማድረግ፣ በአገሪቱ ውስጥ የሚገኙ ከተሞች የከተማ ገጠርና የከተማ ከተማ ትስስርን ማጠናከር፣ እንዲሁም ተመጋጋቢና የተመጣጠነ የአከታተም ስርአት በመፍጠር ከተሞችን የልማትና የእድገት ማእከል ማድረግ መሆኑ በረቂቁ ላይ ተገልጿል። በዚሁ መሰረት በረቂቁ አንቀፅ ሰባት ላይ የፕላን አይነትና ተዋረዶች ተዘርዝረዋል። እነዚሁም አገራዊ የከተማ ፕላን፣ ክልላዊ የከተማ ልማት ፕላን፣ የከተማ አቀፍ ልማት ፕላንና ስኬቶች ፕላን ናቸው። አገራዊ የከተማ ፕላን በአገር ደረጃ የከተማ ልማትና የአከታተም ስርአትን የሚያሳይ የፕላን አይነት እንደሆነ፣ በይዘቱም የአገሪቱን ፖሊሲዎች፣ ስትራቴጂዎችና እቅዶች መሰረት በማድረግ ዋና ዋና የልማት ቀጣናዎችን፣ የአገሪቱን ስርአተ ከተማና የመሬት አጠቃቀም ስርአት ያካትታል። እንዲሁም ከተሞች ከገጠርና ከተሞች ከከተሞች ጋር ያላቸውን ትስስር፣ አሀጉራዊና አለም አቀፍ ትስስርን የሚያመለክት ማብራሪያ ይዟል። ክልላዊ የከተማ ፕላን ደግሞ በክልል ደረጃ የከተማ ልማትና የአከታተም ስርአትን የሚያሳይ የፕላን አይነት ሆኖ አገራዊና ክልላዊ ፖሊሲዎችን፣ ዋና ዋና የልማት ቀጣናዎችን፣ የክልሉን ስርአተ ከተማ እንዲሁም የመሬት አጠቃቀም ስርአትን የሚያብራራ መሆን እንደሚጠበቅበት በረቂቁ ተገልጿል። ከተሞች ከከተሞች ጋር ያላቸውን ትስስርና በክልሎች መካከል ያለውን ትስስር የሚያመለክት ማብራሪያ ማካተት ይጠበቅበታል። ረቂቁ የህግ ሰነዱ ክልል ለሚለው የሚሰጠው ትርጓሜ፣ በህገ መንግስቱ አንቀፅ አርባ ሰባት አንድ የተመለከተው ማንኛውም ክልል ሲሆን፣ የአዲስ አበባና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮችንም ይጨምራል፤ ይላል። ከተማ አቀፍ ፕላን ደግሞ በከተማ አቀፍ ደረጃ የሚዘጋጅ ሆኖ መዋቅራዊ ፕላን፣ ስትራቴጂካዊ ፕላን፣ መሰረታዊ ፕላንና ስኬች ፕላን አይነቶችን እንደሚያካትት በረቂቁ ተመልክቷል። መዋቅራዊ ፕላን የህዝብ ቁጥራቸው ከአንድ መቶ በላይ ለሆኑ ከተሞች የሚዘጋጅ ሆኖ፣ ከተማው በአቅራቢያው ከሚገኙ የገጠር አካባቢዎችና ከሌሎች ከተሞች ጋር የሚኖረውን ትስስር፣ ከተማው የሚያድግበትን መጠንና አቅጣጫ ማካተት ይኖርበታል። ስትራቴጂካዊ ፕላን ደግሞ የህዝብ ቁጥራቸው ከሀያ ሺህ እስከ አንድ መቶ ሺህ ለሆኑ ከተሞች የሚዘጋጅ እንደሆነ ያመለክታል። የከተማ ነዋሪዎች፣ ባለድርሻ አካላት፣ ወይም ማንኛውም ጉዳዩ የሚመለከተው አካል ፕላን እንዲዘጋጅ ሀሳብ ካመነጩ ፕላን እንደሚዘጋጅ በረቂቁ ተካቷል። የከተማ ልማትና ቤቶች ሚኒስቴር ይህንን አዋጅና አዋጁን ተከትለው የሚወጡ ደንቦችና መመርያዎች በሁሉም ክልሎች መፈፀማቸውን እንደሚከታተል፣ ጉድለቶች ካሉም ተገቢውን ማስተካከያ የማድረግ ሀላፊነት በረቂቁ ተሰጥቶታል። ረቂቁ ሀሙስ ጥቅምት ሁለት ቀን ሁለት ሺህ ዘጠኝ አመተ ምህረት ለፓርላማ በቀረበበት ወቅት የቀረበው ጥያቄ አንድ ብቻ ሲሆን ይኸውም፣ ፓርላማው ይህንን አዋጅ የማፅደቅ ስልጣን አለው ወይ ህገ መንግስታዊስ ነው ወይ የሚለውን የሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ እንዲያጤነው፤ የሚል ነበር። በዚሁ መሰረት አዋጁ ለሚመለከተው ለከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለዝርዝር እይታ ተመርቷል።
ክልሎችን ከአጎራባች ክልሎችና ከከተማ አስተዳደሮች የሚያቀናጅ አገር አቀፍ የከተማ ፕላን ሊዘጋጅ ነው
ከአንድ መቶ ስልሳ ሁለት መንገደኞች እስካሁን የሰባትቱ አስከሬን ተገኝቷልባለፈው እሁድ አንድ መቶ ስልሳ ሁለት ሰዎችን ይዞ በበረራ ቁጥር ስምንት ሺህ አምስት መቶ አንድ ከኢንዶኔዥያዋ ሱራያባ ከተማ ወደ ሲንጋፖር በመጓዝ ላይ እያለ ድንገት የተሰወረው ንብረትነቱ የኤርኤዥያ አየርመንገድ የሆነው ኤርባስ ኤሶስት መቶ ሀያ ሁለት መቶ አውሮፕላን እጣ ፋንታ አለምን አሳዝኗል። ኢንዶኔዢያውያንም አዲሱን የፈረንጆች አመት በጥልቅ ሀዘንና በአስከሬን ፍለጋ ተቀብለውታል።አውሮፕላኑን መሰወሩን ተከትሎ ኢንዶኔዢያና ሌሎች አገራት በመርከብና በአውሮፕላን ታግዘው ለፍለጋ በተሰማሩ በሶስተኛው ቀን የተሰማው ነገር፣ አዲስ አመትን በደስታ ለማክበር ለተዘጋጁ ኢንዶኔዢያውያን ትልቅ መርዶ ሆኗል።አንድ መቶ ስላሳ ሰባት አዋቂዎች፣ ህፃናት አንድ ጨቅላ፣ ሁለት አብራሪዎችና አምስት የበረራ ሰራተኞች፣ ሁሉም የጃቫ ባህር ውስጥ ሰምጠው ለህልፈተ ህይወት ተዳርገዋል። በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩት መንገደኞች አንድ መቶ ሀምሳ አምስት ኢንዶኔዢያውያን፣ ሶስት ደቡብ ኮርያውያን፣ አንድ እንግሊዛዊ፣ አንድ ፈረንሳዊ፣ አንድ ማሌዢያዊና አንድ ሲንጋፖራዊ ነበሩ ተብሏል።ለአውሮፕላኑ መከስከስ በሰበብነት የተጠቀሰው አስቸጋሪ የአየር ንብረት ሁኔታ ሲሆን፣ ሌሎች ምክንያቶች እንዳሉ የማጣራቱ ሂደትና የመንገደኞችን አስከሬን የማውጣቱ ሂደት እንደቀጠለ ነው። እስካለፈው ረቡእ ድረስም የአራት ወንድ እና የሶስት ሴት መንገደኞች አስከሬን ከባህር መውጣቱንና በአካባቢው ያለው የአየር ንብረት ሁኔታ ፍለጋውን አስቸጋሪ እንዳደረገው ቢቢሲ ዘግቧል።የኢንዶኔዢያው ፕሬዚደንት ጆኮ ዊዶዶ ግን ምንም እንኳን አስቸጋሪ የአየር ንብረት ሁኔታው ፍለጋውን እጅግ አዳጋች ቢያደርገውም፣ አስከሬንና የአውሮፕላኑን ስብርባሪዎችን የማውጣቱ ስራ በመርከቦችና በሄሊኮፕተሮች በመታገዝ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ባለፈው ማክሰኞ አስታውቀዋል።በራዳር መረጃዎች ላይ በተደረገ ማጣራት፣ አውሮፕላኑ ከሚገባው የበረራ ከፍታ በላይ ወጥቶ እንደነበርና ይህም ለመከስከሱ ምክንያት እንደሆነው የሚያመላክቱ መረጃዎች ተገኝተዋል።ከዚህ ቀደም ጥሩ የሚባል የደህንነት ታሪክ እንደነበረው ያስታወሰው ዘገባው፣ በአውሮፕላኖቹ ላይም ይህ ነው የሚባል አስከፊ አደጋ ደርሶ እንደማያውቅ አክሎ ገልጧል።
ኢንዶኔዢያውያን አዲሱን አመት በሀዘን ተቀብለውታል