text
stringlengths
140
24k
summary
stringlengths
13
164
ለሁለተኛ ጊዜ የሚካሄደው ኢትዮትሬል የተራራ ላይ ሩጫ በሚቀጥለው እሁድ ነሀሴ ሶስት ቀን ሁለት ሺህ ሰባት አመተ ምህረት እንደሚካሄድ የውድድሩ አዘጋጆች ባለፈው ሀሙስ በጉለሌ የእፅዋት ማእከል በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል። ለሁለተኛ ጊዜ በሚካሄደው ሩጫ ለመካፈል ከሁለት መቶ ስድስት በላይ የአገር ውስጥና የውጭ አገር ዜጎች ለመሳተፍ የተመዘገቡ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ አርባ በመቶ የሚሆኑ ከውጭ አገር ዜጎች መሆናቸውን ገልፀዋል። በዋነኛነት ከስፔን፣ ጣልያን፣ እንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ ፈረንሳይ፣ ጃፓን፣ ብራዚልና ቬኑዝዌላ ተወጣጥተው ከሚሳተፉት የውጭ አገር ዜጎች ስላሳ ሰባት በመቶ ሴቶች መሆናቸውም ተገልጿል። የዘንድሮ ሩጫ በአለም አቀፍ ለማስተዋወቅና ኢትዮጵያ በተራራ ሯጮች እይታ ውስጥ እንድትገባ ለማድረግ የሁለት ሺህ አምስት የአውሮፓና የስፔን አልትራ ትሬል ከፍተኛ የትሬል ውድድር አሸናፊ የሆነችው ቼሪ አድሪያን ካሮ በክብር እንግድነትና ተሳታፊነት እንደምትገኝ ተገልጿል። የአብጃታ ሻላ የተራራ ላይ ሩጫ በዋናነት የአካባቢን ደሀንነት በመጠበቅና ለአካባቢው ነዋሪዎች የገቢ ምንጭ ለማስገኘት ታስቦ በአብጃታና ሻላ ሀይቆች ብሄራዊ ፓርክ የሚካሄድ ሲሆን፣ ሩጫው ሶስት የተለያዩ ርቀቶችን ማለትም አርባ ሁለት ኪሎ ሜትር፣ ሀያ አንድ ኪሎ ሜትርና ኪሎ ሜትር የሚያካልል ነው። ማንኛውም ሰው በመሮጥ ወይም በእግር በመጓዝ በግራር የተከበቡትን የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች የሚያደንቅበትና ደስታን የሚሽምትበት እንደሚሆን አዘጋጆቹ አትሌት ገብረ እግዚአብሄር ገብረ ማርያምና አቶ ቃለ አብ ጌታነህ በጋራ በሰጡት መግለጫ ገልፀዋል። የሁለተኛው ውድድር ለየት ከሚያደርጉት ምክንያቶች አንዱ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣንና የኦሮሚያ ክልል የባህልና ቱሪዝም ቢሮ በውድድሩ ዝግጅት የራሳቸውን ሚና መጫወታቸው ሲሆን፣ ይህም በአደጋ ውስጥ የሚገኙትን የስምጥ ሸለቆ ሀይቆችንና የዱር እንስሶችን ለመታደግ የህዝብ ንቅናቄን እንደሚፈጥር የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዳውድ ሙሜ ገልፀዋል። በዚህ ውድድር ለአንድ መቶ ሀምሳ የአገር ውስጥ ተሳታፊዎች ቦታ የተያዘ ሲሆን፣ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በአካል በመቅረብ የውድድሩ አዘጋጅ በሆነው ሪያ ኢትዮጵያ ቢሮ መመዝገብ እንደሚችልም ተገልጿል።
ሁለተኛው ኢትዮትሬል የተራራ ላይ ሩጫ ሳምንት ይካሄዳል
ሰኔ ፲፯ አስራ ሰባት ቀን ፳፻፭ አመተ ምህረት ኢሳት ዜና ፎሬን ፖሊሲ መፅሄት በእያመቱ በሚያወጣው የወደቁ አገራት ሪፖርት ወይም በእንግሊዝኛው አጠራር ፌልድ ስቴትስ ኢንዴክስ ኢትዮጵያ እንደ አለፉት አመታት ሁሉ ዘንድሮው የወደቁ ወይም በመውደቅ ላይ ካሉ ሀያ አገራት መካከል አንዷ ሆና ተመድባለች። የህዝብ ቁጥር ፣ የስደተኛ ቁጥር፣ የህዝብ ብሶት፣ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት፣ ያልተመጣጠነ እድገት፣ የመንግስት ህጋዊነት፣ ማህበራዊ አገልግሎት፣ የደህንነት ጥበቃ፣ የሊህቃን መከፋፈልና የውጭ ጣልቃ ገብነት የሚሉት መስፈርቶች ተገምግዋል። በዚህም መሰረት ከአንድ እስከ ሀያ ያሉት አገራት ህልውናቸው አስተማማኝ ያልሆነ ከፍተኛ ችግር ያለባቸው ተብለው ተመድበዋል። ሶማሊያ ቀዳሚ የወደቀች አገር ስትባል፣ ዲሞክራቲክ ኮንጎ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ቻድ፣ የመን፣ አፍጋኒስታን፣ ሀይቲ ፣ ሴንትራል አፍሪካ ፣ ዝምባብዌ፣ ኢራቅ ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ፓኪስታን፣ ጊኒ፣ ጊኒ ቢሳው፣ ኬንያ፣ ኒጀር፣ ኢትዮጵያና ቡሩንዲ ተከታታዮችን ደረጃዎች ይዘዋል። ከሀያዎቹ አገራት የተሻሉ ተብለው በሁለተኛው ምድብ ውስጥ ከሚገኙት መካከል ደግሞ ሶሪያ፣ ዩጋንዳ፣ ላይቤሪያ፣ ሰሜን ኮሪያ፣ ኤርትራ፣ ማይናማር፣ ካሜሩን፣ ስሪ ላንካ፣ ባንግሊያዲሽ፣ ኔፓል፣ ሞሪታኒያ፣ ኢስት ቲሞር፣ ሴራ ሊዮን፣ ግብፅ ፣ ቡርኪና ፋሶ፣ ኮንጎ፣ ኢራን፣ ማሊ፣ ርዋንዳ እና ማላዊ ተመድበዋል። የኢህአዴግ መንግስት ኢትዮጵያ በተሻለ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የደህንነት ጥንካሬ ላይ እንደምትገኝ በተደጋጋሚ ሲናገር ይሰማል። ይሁን እንጅ የፎሬን ፖሊስ መረጃ እንደሚያሳየው ኢትዮጵያ ባለፉት ተከታታይ አመታት ይህ ነው የሚባል የደረጃ መሻሻል አልታየባትም። በዚህ አመትም ኤርትራ በአንፃራዊ መልኩ ከኢትዮጵያ በተሻለ ደህንነት ላይ እንደምትገኝ ሪፖርቱ ሲያሳይ፣ ኬንያ፣ ናይጀሪያና ሱዳን ደግሞ ከኢትዮጵያ አንሰው ተገኝተዋል።
በሁለት ሺህ አምስት አም ኢትዮጵያ ከወደቁ አገራት ምድብ ተመደበች
ኢሳት ጥር ሀያ ሁለት ፥ ሁለት ሺህ ዘጠኝ ባለፈው ስድስት ወራቶች ብቻ በአዲስ አበባ ከተማ ሺ የንግድ ተቋማት የንግድ ፈቃዳቸውን በተለያዩ ችግሮች እንደመለሱ ተገለፀ። እነዚሁ በተለያዩ የንግድ ስራዎች ላይ ተሰማርተ የነበሩ ድርጅቶች ህገወጥ ንግድ መበራከት፣ በከተማዋ እየተካሄደ ያለው የልማት እንቅስቃሴ ደካማ የንግድ ስርአት አንዲሁም የቤት ዋጋ ንረት ከገበያ እንዲወጡ ጫና እንዳደረሰባቸው ማስታወቃቸውን ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል። በከተማዋ እየተስተዋሉ ያሉ እነዚህን ችግሮች ተከትሎ በየእለቱ ሰባ የሚሆኑ የንግድ ተቋማት የንግድ ስራ ፈቃዳቸውን ለአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ እየመለሱ መሆናቸው ተመልክቷል። የንግድ ድርጅቶቹ ፈቃዳቸውን ለመመለስ በመንግስት የግብር ገቢና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ አሉታዊ ተፅእኖ ሊያሳድር እንደሚችል ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው አካላት አስረድተዋል። በተለያዩ አካላት ወደ ሀገሪቱ የሚገቡ ያልተቀረጡ ሸቀጣሸቀጦች በንግድ ስራቸው ላይ ከፍተኛ ጫና መፍጠሩን አቶ ኤርሚያስ ሀይሌ የተባሉ በኮሞፒውተር ንግድ ላይ የተሰማሩ ነጋዴ ለጋዜጣው ገልፀዋል። የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ተወካይ የሆኑት ምትኬ እንግዳ በበኩላቸው ቢሮው ህገወጥ ንግዱን ለመቆጣጠር የተለያዩ ጥረቶችን ሲያደርግ ቢቆይም ችግሩ ሊቀንስ እንዳልቻለ ተናገረዋል። ባለፈው አመት በተመሳሳይ ችግሮች ሀያ ስድስትሺ ስምንት መቶ ስልሳ የንግድ ተቋማት ፈቃዳቸውን መልሰው የነበረ ሲሆን፣ አሁን ባለው ሂደት ቁጥሩ ሊጨምር እንደሚችል ተመልክቷል። የንግድ ፈቃዳቸውን እየመለሱ ያሉ የንግድ ድርጅቶች መንግስት ለችግሮቹ መፍትሄን እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። በአዲስ አበባ ከተማ ሁለት መቶ ስልሳ አንድሺ አራት መቶ አንድ የንግድ ድርጅቶች በተለያዩ ስራዎች ላይ ተሰማርተው እንደሚገኙ ታውቋል።
በአዲስ አበባ ሺ የንግድ ተቋማት የንግድ ፈቃዳቸውን በተለያዩ ችግሮች መለሱ
ከዚሁ ጋር ተያይዞም እቃ አቅራቢው ገቢው ከአምስት መቶ ሺ ብር በላይ ቢሆንም እንኳን ታክሱን የመክፈል ግዴታ የሌለበት ሲሆን የካፊቴሪያ ወይም የምግብ ቤት አገልግሎት የሚሰጠው ሰው ግን ገቢው ከአምስት መቶ ሺ ብር በላይ ከሆነ ለታክሱ የመመዝገብ ግዴታ እና ታክሱን የመክፈል ሀላፊነት ይኖርበታል። ከላይ የቀረበው ድንጋጌ የተወሰደው ተጨማሪ እሴት ታክስ በኢትዮጵያ በሚል ርእስ በሳሙኤል ታደሰ ተዘጋጅቶ በግንቦት ወር ሁለት ሺህ አራት አመተ ምህረት ለአንባቢያን ከቀረበው መፅሀፍ ነው። የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ በወጣ አስረኛ አመት ዋዜማ ታትሞ የቀረበው መፅሀፍ፤ ባለፉት አመታት ህብረተሰቡ ግር ለተሰኘባቸው ብዥታዎች ማጥሪያ ሊሆኑ የሚችሉ ሰፋ ያሉ መረጃዎችን ይዟል። ከቫት ነፃ የሆኑት ዳቦ፣ እንጀራና ወተት የቫት ሰለባ የሚሆኑበት ምክንያት ምን እንደሆነ የቀረበው አንዱ ማሳያ ነው።በሁለት መቶ ሰማኒያ ስምንት ገፆች የቀረበው መፅሀፍ፤ ግብርና ታክስ በአለም ላይ ምን ታሪክ እንዳላቸው በማመልከት ነው ወደ ተነሳበት ርእሰ ጉዳይ የሚዘልቀው። ግብርና ታክስን ክፈል፤ አልከፍልም ሙግትና ትግል ከክርስቶስ ልደት በፊት በእስራኤላዊያን ዘንድ ይታይ እንደነበርና ንጉስ ሰለሞን ግብርን ከህዝቡ አስገድዶ ይቀበል እንደነበር ተገልጿል።ግብርና ታክስ አንዱ ሌላውን መወንጀያ፣ ማሳደጃ፣ መውቀሸያ የመሆኑ ታሪክም እጅግ ጥንታዊ እንደነበር፤ ከሳሾቹ ከቄሳር ጋር ሊያጣሉት ሲሞክሩ የቄሳርን ለቄሳር፣ የእግዜአብሄርን ለእግዚአብሄር ስጡ ብሎ በብልሀት ያሸነፈው የኢየሱስ ክርስቶስ ታሪክም ተጠቅሷል።በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ሀብት ያለው ለሌለው የሚያካፍልበት ዘካ በመባል የሚታወቀው ሀይማኖታዊ ግዴታ፣ በተለይም እስልምናን እንደ መንግስት ሀይማኖት ተቀብለው የሚከተሉ አገራት ህግ አውጥተው ዘካን እንደ ግብር በግዴታ እንደሚሰበስቡ ፓኪስታንን በምሳሌነት አቅርቧል መፅሀፉ።በጥንታዊ ግብፅ፣ ግሪክ፣ ሮም ግብርና ታክስ የመሰብሰብ ሂደት ምን ይመስል እንደነበር የሚያስቃኘው የሳሙኤል ታደሰ መፅሀፍ፤ እንግሊዝና ፈረንሳይን ጦር ያማዘዘው የግብርና ታክስ ታሪካቸው ምን ይመስል እንደነበርም ያስቃኛል።በግብፅ፣ በግሪክ፣ በሮም እንደታየው ሁሉ በጥንታዊው የኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥም በነበረው የንግድ እንቅስቃሴ ቀረጥ ይሰበሰብ ነበር። በ ኛው ክፍለ ዘመን በእንግሊዝ የታክስና ግብር ስርአት እድገት እንዳሳየው ሁሉ በኢትዮጵያም ከአንድ ሺህ አራት መቶ እስከ አንድ ሺህ አራት መቶ ሀያ ዘጠኝ አመተ ምህረት በአፄ ይስሀቅ ዘመነ መንግስት ሰላሳ ዘጠኝ ግዛቶች ለማእከላዊ መንግስት ግብር ይከፈሉ እንደነበር ምንጭ ጠቅሶ ገልጿል።ግብርና ታክስን በተመለከተ ከጥንታዊያኑ ግብፅ፣ ግሪክና ከሮም ጋር ትመደብ የነበረችውና በመካከለኛውም ዘመን ከእንግሊዝና ፈረንሳይ እኩል ትታይ የነበረው አገራችን በብዙ ዘርፎች እንደሚታየው ተከታታይና ቀጣይነት ያለው እድገት ሳታስመዘግብ ቀረች። ሆኖም በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና አምስት አመተ ምህረት የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅን በማውጣት ጥለዋት የሄዱት አገራት ላይ ለመድረስ የሚያፈጥናትን አቋራጭ መንገድ የተከተለች ይመስላል።ስለ ተጨማሪ እሴት ታክስ የጥናት ፅሁፎች መቅረብ የጀመሩት እ ኤ አ በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሀምሳዎቹ ነው የሚለው የሳሙኤል ታደሰ መፅሀፍ፤ ታክሱን የግብር ስርአቷ አድርጋ በመንቀሳቀስ ጀማሪዋ ፈረንሳይ ነበረች አ ኤ አ በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ አርባ ስምንት።በመቀጠል ኮትዲቭዋር፣ ሴኔጋል ተግባራዊ አደረጉት። እ ኤ አ በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ስልሳ እና በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰባዎቹ ብዙ የአለም አገራት እንደ ተቀበሉት የሚጠቁመው መፅሀፍ፤ በሀያኛው ክፍለ ዘመን የመጨረሻ አመታት በአለማችን የታክስ ስርአቶች ውስጥ ከታዩ እድገቶች መካከል የተጨማሪ እሴት ታክስ እድገት ዋነኛው ነው ይላል።መንግስታት የተጨማሪ እሴት ታክስ ስርአትን እንዲከተሉ ያተጋቸው የተለያዩ ምክንያቶች አሉ። የምእራብ አውሮፓ አገሮችና የደቡብ አሜሪካ አገሮች የተጨማሪ እሴት ታክስ ስርአትን የሚጠቁሙበት ምክንያትን የሚጠቁመው መፅሀፉ፤ ታዳጊ አገሮች የግብር ስርአቱን እንዲከተሉ ያስገደዳቸው ዋነኛው ምክንያት ከቀጥታ ታክስ የሚያገኙት ገቢ የሚያወላዳ ባለመሆኑ እንደሆነ ገልፃ፤ በአገራችንም በዚህ ዋነኛ አላማ አዋጁ እንደወጣ ተጠቅሷል። ከአርባ አመት በፊት በአለማችን በጥቂት አካባቢዎች ብቻ ይታወቅ የነበረው የተጨማሪ እሴት ታክስ፤ በአሁኑ ወቅት አራት ቢሊዮን የሚያህል ህዝብ ወይም ከአለማችን ህዝብ ሰባ በመቶ ያህሉ በሚገኝባቸው አገሮች ተግባራዊ ሆኖ ይገኛል የሚሉት የመፅሀፉ ደራሲ፤ በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ስድስት አመተ ምህረት በፌደራል አገር ውስጥ ገቢ ባለስልጣን በነገረ ፈጅነት ተቀጥረው ሲገቡ ጀምሮ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ጋር በተያያዘ ብዙ ችግሮች መኖራቸው እንደተረዱ ይገልፃሉ። የታክስ ህግ በአንፃራዊነት ሲታይ ከሌሎች የህግ አይነቶች ሁሉ በውስብስብነቱ የታወቀ ነው። የዚህም ዋና ምክንያት ሆኖ የሚነሳው ደግሞ ህጉ የሌሎች በርካታ የማህበራዊ ሳይንስ የትምህርት ዘርፎች ማለትም የህግ፣ የኢኮኖሚክስ፣ የፖለቲካ ሳይንስ እና የአካውንቲንግ ድምር ውጤት ሲሆን ህጉን በቀላሉ ለመረዳት በርካታ ባለሞያዎች ብዙ መስራት ወይም መፃፍ እንዳለባቸው ይታመናል። በዚህ ምክንያትና አላማ ተጨማሪ እሴት ታክስን ርእሰ ጉዳይ ያደረገ መፅሀፍ ያዘጋጁት ደራሲው፤ ስለ ታክስ ምንነት፣ አተገባበሩ በተለያዩ አገራት ምን እንደሚመስልና በአገራችን በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና አምስት አመተ ምህረት የወጣው የተጨማሪ እሴት ታክስ ህግ ዋና ዋና ድንጋጌዎች ምን እንደሚመስሉ ምሳሌና ማሳያ እያቀረቡ ለማስረዳት ታትረዋል።የተጨማሪ እሴት ታክስ ተግባራዊ መሆን ከጀመረ አስር አመት ገደማ ቢሆነውም አሁንም ድረስ በምንበላውና በምንጠጣው ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ መጣሉ አግባብ አይደለም የሚል ቅሬታ በስፋት ይደመጣል። ምግብ የቫት ሰለባ ሊሆን የቻለበት ምክንያት ምን እንደሆነ ህጋዊ ትርጉሙን በሙያዊ ትንታኔ አቅርበዋል ደራሲው።ለረጅም አመታት ልማዳዊ በሆነ መልኩ ሲሰራበት የቆየውን የግብርና ታክስ ስርአትን ለማሻሻል ከአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ ሶስት አመተ ምህረት በኋላ አገሪቱ የተከተለችውን የኢኮኖሚ ስርአት መሰረት አድርጐ የወጣው የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ በስራ ላይ ሲውል የታዩት ክፍተቶች በዘርፉ ላይ ብዙ ስራ መሰራት እንዳለበት ያመላከተ ነበር የሚሉት ፀሀፊው፤ ደራሲ በተለያዩ ጊዜያት በወጡ ህጐች ውስጥ የተፈጠረ ልዩነት፣ የታክስ ሰብሳቢ መስሪያ ቤቶች ድክመትና የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ተጠያቂነት አናሳ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ የተፈጠሩ ችግሮችን ለማሳየት ሞክረዋል።የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ለአገራችን አዲስ እንደመሆኑ ከፍተኛ የሆነ መደናገርና ብዥታ በአስፈፃሚውና በፈፃሚው ወገን ላይ ይታያል ያሉት ደራሲው፤ የታክስ ስርአቱ አሁንም ብዙ ስራ የሚጠይቅ መሆኑን የሚያመለክቱ ምሳሌና ትንታኔዎችን አቅርበዋል በመፅሀፉ ማጠቃለያ።ህዳር አንድ ቀን አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ስድስት አመተ ምህረት በፌዴራል አገር ውስጥ ገቢ ባለስልጣን በህግ ባለሙያነት ሲቀጠሩ መስሪያ ቤቱ ስልሳኛ አመቱን ያከበረ ቢሆንም በህግ ባለሙያነት ስራዬ ተግባራዊ ስለማደርጋቸው ህጐች የተፃፈ አንድ መፅሀፍ እንኳን አለመኖሩ ስልሳ አመት ስንት ነው የሚለውን ጥያቄ እንዳነሳ አስገድዶኛል የሚሉት የመፅሀፉ ደራሲ ሳሙኤል ታደሰ፤ በፌደራል አገር ውስጥ ገቢ ባለስልጣንና በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ለስምንት አመት ካገለገሉ በኋላ በተጨማሪ እሴት ታክስ ዙሪያ መፅሀፍ አዘጋጅተው ማሳተማቸው ተቋማትን ብቻ ሳይሆን ግለሰቦችንም ለተመሳሳይ ስራ የሚያነሳሳ አርአያነት ያለው ታላቅ ተግባር ነው። መፅሀፉ ሀምሌ ቀን ሁለት ሺህ አራት አመተ ምህረት በአዲስ ቪው ሆቴል በተመረቀበት ምሽት በክብር እንግድነት የተገኙት አቶ ተፈራ ዋልዋ ጡረታ የወጣሁት እረፍት ፈልጌ የነበረ ቢሆንም ወጣቶች በየመድረኩ እየጋበዙኝ ንግግር ማድረጌን ቀጥያለሁ። በመፅሀፍ ምረቃ ላይ ስገኝ ሁለተኛ ጊዜዬ ነው። ዛሬ ወደዚህ መድረክ እንድመጣ ምክንያት ከሆነኝ አንዱ ሳሙኤል ታደሰ መፅሀፍ ባዘጋጀበት ርእሰ ጉዳይ ላይ ተመሳሳይ ስራዎች እንዲሰሩ አልሞ መፅሀፉን ማሳተሙን በመስማቴ ነው ብለዋል።ሌሎች ባለሙያዎችም ለደራሲውና ለመፅሀፉ ያላቸውን አድናቆት በምረቃ ስነ ስርአቱ ላይ ተናግረዋል።
ታክስ፤ የህግ፣ የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካና የአካውንቲንግ እውቀትን ይጠይቃል
ነሀሴ አስራ ሰባት ቀን አመተ ምህረትኢሳት ዜናበኢትዮጵያ የፕትርክና ታሪክ አወዛጋቢ የሆኑት ብፁወ ቅዱስ አቡነ ጳውሎስ የመንግስት ባለስልጣናት እና ሌሎች ዲፐሎማቶች በተገኙበት ዛሬ በቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን የቀብራቸው ስነስርአት ተፈፅሟል።ከሀምሌ ቀን አመተ ምህረት ጀምሮ ኛ አመት በአለ ሲመታቸውን ሲያከብሩ የነበሩት አቡነ ጳውሎስ በድንገት ማረፋቸው የብዙዎች መነጋገሪያ አጀንዳ እንደሆነ ነው። በተለይም የእርሳቸውን ሞት ተከትሎ የአቶ መለስ ዜናዊ ዜና እረፍት ይፋ መሆን ኢትዮጵያውያን ነገሩን ከሀይማኖት ጋር እንዲያያዙት ግድ ብሎአቸዋል።አቡነ ጳውሎስ በልማቱ ዙሪያና ኤች አይ ቪ ኤድስን በመከላከል ረገድ አወንታዊ ተግባራትን መፈፀማቸው ቢነገርም ጥንታዊቷን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን ከሁለት በመክፈልና በማዳከም የገዢው ፓርቲ መሳሪያ በመሆን እና ከህዝብ ጎን ባለመቆም እንዲሁም ለአለማዊ ቅንጦት ከፍተኛ ቦታ በመስጠታቸው ይወቀሳሉ። በተለይም በቅርቡ የብጿን አባቶች መደብደብ እና ሀውልታቸውን በቁማቸው ማሰራታቸው ለከፍተኛ ትችት ዳርጓቸው እንደነበር ይታወሳል።
የብፁእ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ የቀብር ስነ ስርአት በቅድስት ስላሴ ካቴድራል ተፈፀመ
ብዙውን ጊዜ በቴሌቪዥን መስኮትም ሆነ በጋዜጦችና መፅሄቶች የሚተላለፉና የሚወጡ ትዝብቶች ወይም አስተያየቶች በአብዛኛው በታዋቂ ግለሰቦች በምሁራን አለያም በፖለቲከኞች ይጣበባሉ። እንደ እኔ ያለው ጭቁን የገጠር መምህር ግን እንዲህ ያለው እድል ብዙም አይገጥመውና እንዲሁ እድሌን ልሞክር ብዬ ነው ይህን ፅሁፍ መላኬ። ለሚዲያ ቢሆን ብዬ ስፅፍም የመጀመሪያ ጊዜዬ ነው። እድሜ ለአበበ ቢቂላ ይሁንና ከእሱ ጊዜ ጀምሮ አትሌቶቻችን በመላው አለም ታውቀው አሳውቀውናል። አበበ ቢቂላ በአለም የውድድር መድረክ አሸንፎ ከመጣ በኋላ ስታዲየሙን እየዞረ የኢትዮጵያን ባንዲራ እያውለበለበ ሲዞር፣ በወቅቱ በስፍራው የነበረ አፍሪካዊ ስደተኛ ራሱን ደፍቶ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ። ደስ አለው። ጀግኖች አትሌቶቻችን የታመመንም ያድናሉ። ለዚህ ሁሉ መንደርደሪያዬ ሙያዊ ብቃታቸው የትየለሌ መሆኑ ነው። አንድ ፌደሬሽንን ቀርቶ አለም አቀፍ ተቋምን መምራት እንደሚችሉ የሚያሳየን አትሌት ሀይሌ ገብረ ስላሴ ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንትነት እንደተመረጠ ወዲያውኑ ድጋፋቸውን በተለያዩ ድረ ገፆች፣ አለም አቀፍ መፅሄቶችና ጋዜጦች ሲገልፁ ማየታችን ነው። በአለም ጋዜጦችና ታዋቂ ድረ ገፆች መነጋገሪያ መሆንና መሞካሸት ከሙያ ብቃት የመጣ ነው። አትሌት ሀይሌ አለም አቀፍ ድጋፍ ማግኘቱ ዛሬ ብቻ ሳይሆን ዱሮ ታዳጊ ልጆች እያለን ነፍሳቸውን ይማርና ጋሽ ይድነቃቸው ተሰማም በተለያዩ የአለም መድረኮች አገራችንን ከፍ ከፍ አድርገውን እንደነበር ይታወሰኛል። የሀይሌን መመረጥ የደገፍኩት በተለይ ህዝቡን የማገልገል ውስጣዊ ፍላጎትና ብቃቱን ሳስብ ነው። በጀግንነት ባሸነፋቸው መድረኮች የራሱን ደስታ ብቻ አይደለም ያየነው፤ አገር ወዳድነቱን ጭምር እንጂ። ከፊቱ ከሚነበበው ስሜት፣ በቄንጠኛ ሁኔታ ባንዲራውን እያውለበለበ በርከክ ማለቱ ብቻም ሳይሆን፣ የአገሪቱ ብሄራዊ መዝሙር ሲዘመርና ባንዲራዋ ሲሰቀል እንባውን ማፍሰሱ ተቆርቋሪነቱንና ወገንተኝነቱን የሚያሳይ ነው። ወደፊት ፌዴሬሽኑን ሲመራም በሀቀኝነት ሁሉንም እያሳተፈ ውጤታማ መሪ እንደሚሆን ጥርጥር የለኝም። ያለአግባብ ለመጠቀም ብሎ እንደማይሰራ አምናለሁ። የዋህ ባህርይ የተባበሰ ሰው ነውና ቢሳሳትም ከአቅም ወይም ከአመራር ልምድ ማነስ እንደሚሆን ይሰማኛል። ህዝብንና አብረውት የሚሰሩ ባልደረቦቹን አክባሪ፣ ምክር ጠያቂም እንደሆነም አውቃለሁ። የስፖርት ጋዜጠኞች ሙያዊ አስተያየትም ትምህርት ሰጭ እንደሆነ የሚቀበል ሰብእና ያለው ስለመሆኑ እንዴት አወቅህ ብትሉኝ፣ በቴሌቪዥን የሚደረጉ ውይይቶችን ስለምከታተል ነው። የገጠር አካባቢ መምህር ብሆንም እንዷቅሚቲ በማገኛቸው መረጃዎች አማካይነት ነገሮችን ለመመዘን ስለሞክር፣ ወደ መፃህፍት ጎራም ስለማዘወትር ለማገናዘብ የምችልበት እድል ሰጥተውኛል። ወደ ርእሰ ጉዳዬ ልመለስና ላለፉት ስድስት ወራት የስፖርት ዜና አንባቢዎች የህዝብን ድምፅ እየተከታተሉና ከራሳቸውም ስፖርታዊና ሙያ መርሀ በመነሳት ለሚመለከታቸው የአትሌቲክስ ዘርፍ ሀላፊዎች ለምን ወደ ኋላ እየተጓዝን እንደሆነ፣ ውጤታችን ለምን ከዱሮው እንደቀነሰ ወዘተ እየጠቃቀሱ ሲያነጋግሩ፣ ሹሞቹ ሲሰጡ የነበሩትን ምላሽ ለህዝብ ድምፅ ጆሮ አለመስጠት ይታይባቸው እንደነበር አስታውሳለሁ። ስፖርት እንደሆነ ወዳጅን ብቻ ሳይሆን የሚያገናኘውና የሚያፈቅረው በክፉ የሚፈላለገውንም ጭምር ነው። የእስራኤልና የፍልስጤም ሁለት ወጣቶችን የዛሬ አምስት አመት አፋቅሮ ለጋብቻ ያበቃቸው ስፖርታዊ ትእይት ነበር። የፖለቲካ ታማኝነት ብቻውን የትም እንደማያደርስና እንደማያዋጣ መገንዘብ ይገባል። ጋዜጠኞች በአለም ኦሊምፒክ መድረክ አንድ ወርቅ ብቻ ማግኘታችን ውድቀትን አያሳይም ወይ ብለው ሲጠይቋቸው፣ በተቃራኒው ውጤታማ ነን በማለት ድርቅ ማለታቸው የሚያስተዛዝብ ነው። ይህ እንግዲህ ሙያዊ ብቃት አስፈላጊነቱ ምን ያህል እንደሆነ ያሳያል። ባለስልጣኖቹም ጥፋታቸውን ማመን ይገባቸዋል። የህዝቡን ውጤት አጣን ጥያቄ ማስተናገድ ይገባቸዋል። ጋዜጠኞች ውጤት ያጣንበትን ምክንያት በማውሳት እርምት እንዲደረግ ብዙ ታግለዋል። ሆኖም ሹሞቹ ግን ድንግጥም የሚሉ አይነት ሆነው አልተገኙም ነበር። እነሱ አይሰሙም እንጂ መንግስት የምሁራንን ሚና ተረድቶ በፕሮፌሰሮችና በዶክተሮች የተሞላ ካቢኔ አቋቁሟል። ሻለቃ ሀይሌ ገብረ ስላሴና አዲሱ የአትሌቲክስ ፌደሬሽን ስራ አስፈፃሚ የወደፊቱን አትሌቲክስ ስፖርት በድል ጎዳና እያራመዱ፣ የጠፋውን ውጤት እንደሚያስመልሱ በማመን መልካም የስራ ዘመን እላለሁ። አደፍርስ፣ ከወሎ ሀይቅ የህንፃዎችን የፓርኪንግ ክፍያ ተመን የሚቆጣጠር አካል አለን ለተለያዩ ጉዳዮች መኪኖች በህንፃዎች ማቆሚያ ቦታዎች ወይም የፓርኪንግ አገልግሎት በሚሰጥባቸው ስፍራዎች ማቆም ሊያስፈልገን ይችል ይሆናል። ያስፈልጋልም። ምንም እንኳ አዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ ህንፃዎች ተገቢውን የመኪና ማቆሚያ ቦታ በመገንባት ረገድ የሚወቀሱ ቢሆኑም፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ብቅ እያሉ ያሉት ህንፃዎች እንዲህ ያለውን አገልግሎት የሚሰጡ የፓርኪንግ ቦታዎችን ማዘጋጀት ጀምረዋል። እሰየው ያስብላል። ይሁንና ግን ችግር ያለባቸውም አሉ። አገልግሎቱን ቢሰጡም ለሚሰጡት አገልግሎት የሚጠይቁት ክፍያና የሚከተሉት የክፍያ አጠያየቅ ስርአት አስገራሚም፣ አሳፋሪም ሆኖ ያገኘናቸው ህንፃዎች አሉ። ከሰሞኑ የገጠመኝም ከዚሁ ከፓርኪንግ ክፍያ ጋር የሚገናኝ ነው። ቦሌ፣ ሚሊኒየም አዳራሽ አካባቢ የሚገኝ ዘመናዊና አዲስ ህንፃ ነው። የተሟላ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ቢኖረውም፣ ህንፃው የሚከተለው የክፍያ ስርአት ግን አግባብነት የጎደለው ይመስለኛል። ለአንድ ሰአት ቆይታ የሚያስከፍለው ገንዘብ ስምንት ብር መሆኑ ግራ አጋብቶኛል። በየመንገዱ ለምናቆምበት የምንጠየቀው ሀምሳ ሳንቲም ሆኖ ሳለ በዚህ ህንፃ ውስጥ ለአንድ ሰአይ ቆይታ ስምንት ብር መጠየቅ ከምን መነሻ እንደሆነ ግልፅ አይደለም። የሂሳቡ መጋነን ሳያንስ ወደ ማቆሚያ ቦታ ለሚገባው አሽከርካሪ ሂሳቡ አይነገረውም። ይህ ደግሞ ፈፅሞ ስነ ምግባር የሌለው ድርጊት ነው። በጥቅሉ ግን እንዲህ ያሉ ቅጥ ያጡ አሰራሮች እየተለመዱ ከሄዱ የኋላ ኋላ ነገሮችን ለማስተካከል አስቸጋሪ ያደርጋቸዋልና የሚመለከተው አካል ካለ እርምት ያድርግበት። ቢሻው ቢልልኝ፣ ከአዲስ አበባ
ለአትሌቲክስ ውጤታማነት አዲሱን አመራር ተስፋ እናደርጋለን
በእንግሊዝ መንግስት የገንዘብ ድጋፍ በጋምቤላ ክልል በተከናወነ አስገዳጅ የሰፈራ ፕሮግራም፣ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ደርሶብኝ፣ ለስደት ተዳርጊያለሁ ያሉ አንድ ኢትዮጵያዊ ገበሬ፤ በአገሪቱ ላይ የመሰረቱትን ክስ ያዳመጠው የለንደን ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ እንግሊዝ ለኢትዮጵያ የምትሰጠው እርዳታ የዜጎችን ሰብአዊ መብቶች ለሚጥሱ ፕሮግራሞች መዋል አለመዋላቸው እንዲጣራ መወሰኑን የኢትዮጵያ መንግስት ተቃወመ። ብሉምበርግ ኒውስ ከትናንት በስቲያ እንደዘገበው፣ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉዳዩን በተመለከተ ለንደን በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል በላከው መግለጫ፤ ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ማስተላለፉ አግባብነት እንደሌለው ገልፆ፣ ክሱ የተመሰረተው ያለምንም ተጨባጭ መረጃና የራሳቸውን ፖለቲካዊ ጥቅም ለማስከበር በሚፈልጉ ሀይሎች አነሳሽነት እንደሆነ ገልጿል። በክልሉ የተከናወኑ የሰፈራ ፕሮግራሞች በነዋሪዎች ፈቃደኝነት ላይ የተመሰረቱና ማህበራዊ አገልግሎቶችን በማሻሻል የተበታተነ አሰፋፈር ባለባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ ማህበረሰቦችን ተጠቃሚ የማድረግ ግባቸውን በማሳካት ረገድም ውጤታማ እንደነበሩ መግለጫው አስታውሷል። መንግስት ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ በሚያከናውነው በዚህ የሰፈራ ፕሮግራሞች ላይ መሰል ውንጀላዎችና የተዛቡ አመለካከቶች እንዲፈጠሩ ከሚያደርጉ ምክንያቶች አንዱ የሰፈራ ፕሮግራሙን አላማ በአግባቡ አለመረዳት ነው ብሏል። ሂዩማን ራይትስ ዎች የተባለው አለማቀፍ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅት በጋምቤላ ክልል የተከናወነው የሰፈራ ፕሮግራም፣ አስገዳጅና በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን ለከፋ ስቃይና የሰብአዊ መብቶች ጥሰት የዳረገ ነው ማለቱን የዘገበው ብሉምበርግ ኒውስ፤ ፍርድ ቤቱ ይህን ውሳኔ ማስተላለፉ ይበል የሚያሰኝ ነው ሲል እንዳሞካሸውም ጠቁሟል። የእንግሊዝ አለምአቀፍ የልማት ተቋም በበኩሉ፣ በጋምቤላ ክልል ብዙ ዜጎችን ያለፍላጎታቸው ከቀያቸው አፈናቅሏል፣ ለእስራት፣ ለድብደባና ለስቃይ ዳርጓል ለተባለው የሰፈራ ፕሮግራም የገንዘብ እርዳታ እንዳልሰጠ መናገሩን ገልጿል። ከጋምቤላ ክልል ተፈናቅለው በኬኒያ በስደት የሚገኙ ስማቸው ያልተገለፀ ገበሬ፤ በእንግሊዝ መንግስት ላይ የመሰረቱትን ክስ የተቀበለው የለንደን ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ የእንግሊዝ የእርዳታ ድርጅት ለኢትዮጵያ የሚያደርገው ድጋፍ የአገሪቱን ዜጎች የሰብአዊ መብቶች በማይጥስ ሁኔታ ጥቅም ላይ ስለመዋሉ ይጣራ ሲል ከሁለት ሳምንታት በፊት መወሰኑን መዘገባችን ይታወሳል። ምንጭ፥ አዲስ አድማስ
መንግስት የእንግሊዝ እርዳታ በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶችን ለመጣስ ስለመዋሉ መጣራቱን ተቃወመ
በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት በጊዜያዊነት ወደ ጃንሜዳ ተዛውሮ የቆየው አትክልት ተራ በቋሚነት አገልግሎት እሚሰጥበት ወደ ሀይሌ ጋርመንት አካባቢ መዛወሩንና በዛሬው እለት ታሀሳስ ሰባት ቀን ሁለት ሺህ አመተ ምህረት የማፅዳት ስራ እንደሚከናወን የአዲስ አበበ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ። ጃንሜዳ ለመጪው ለጥምቀት በአል እንዲደርስ፣ ስፖርታዊና ሌሎች ማሀበራዊ አገልግሎቶችን መስጠት እንዲችል በዛሬው እለት ከጠዋቱ ፡ ሰአት ጀምሮ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች፣ የስፖርት ቤተሰቦችና ወጣቶች፣ የፅዳት ባለሙያዎች ጨምሮ የማፅዳትና የማሳመር ስራ እንደሚሰሩ አስተዳደሩ ገልጿል። ሀይሌ ጋርመንት አካባቢ እየተገነባ ያለው የገበያ ማእከል በቅርቡ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆን የመንገድ፣ የመብራት፣ የመፀዳጃ ቤትና አስፈላጊ መሰረተ ልማቶች ዝርጋታ እየተጠናቀቀ መሆኑንም ተነግሯል። በመጠናቀቅ ላይ ያለው የገበያ ማእከሉ ከአንድ መቶ ሀያ በላይ ተሽከርካሪዎችን የሚይዝ ሶስት ስድስት መቶ ካሬ ሜትር የመኪና ማቆሚያና ሶስት መቶ ሜትር በአርባ ሜትር ስፋት ያለው ከዋና መንገድ ጋር የሚያገናኝ መንገድ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል። በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን አማካይነት በአንድ ቢሊዮን ብር ወጪ እየተገነባ ያለው የአትክልት ገበያ ማእከል፣ ሰማኒያ ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያርፋል። በመጀመርያው ምእራፍ የሚገነቡት ሼጆች ናቸው። እያንዳንዱ ሼዶች ሰባ ሜትር በስድስት ነጥብ ስድስት ሜትር ስፋት አላቸው። አምስት መቶ ሰማኒያ ስምንት የሚሆኑ የመገበያያ ሱቆችም ይኖሩታል ተብሏል።
የጃንሜዳ ጊዜያዊ አትክልት ተራ ወደ ሀይሌ ጋርመንት የማዘዋወሩ ስራ ተጠናቀቀ
ቻይና በሀገሪቱ ዋና ዋና ቦታዎች ላይ ብሄራዊ የሆኑ የሳይንስ መሰረተ ልማቶችን ለመገንባት እንቅሰቃሴ መጀመሯን አሰታውቃለች።በተለይም በመሰረተ ልማት ግንባታው ዘርፍ ከሀገሯ አልፋ በማደግ ላይ ካሉ ሀገራት ጋር በትብብር በመሰራትም ላይ ትገኛለች ።በሳይንሰ እና ቴክኖሎጂው ዘርፍም ቢሆን የምታደርገው እንቅስቃሴ ከፍተኛ እንደሆነ ይነገራል። አሁን ደግሞ ሀገሪቱ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ቀመሰ የሆኑ መሰረተ ልማቶችን ለመገንባት ቆርጣ መነሳቷን የሀገሪቷ መገናኛ ብዙሀን እየዘገቡይገኛሉ።የተራቀቁ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ወደ ሙከራ መግባቷም የተገለፀ ሲሆን ይህ ተጠናቆ ወደ ሰራ ሲገባ ሀገሪቷን በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዘርፍ በአለም ላይ ተወዳዳሪ እድተሆን ያደርጋታል ተብሎ ይታመናል።ይህ ማለት ደግሞ ሀገሪቷ በተለያዩ ዘርፎች እያደረገችው ላለው ኢኮኖሚያው፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ እንቅሰቃሴም ሆነ ከሊሎች ሀገራት ጋር ላላት ግንኙነት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ታምኗል። ሀገሪቷ በአለም ላይ በዘርፉ ያላትን ተቀባነት እንደሚያሳድገው ተስፋ ተጥሏል።በሀገሪቷ የሚገባው የመጀመሪያው የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት የሚገነባው በሰሜናዊ ቤጅንግ የምትገኝው ኋሩ ከተማ ውሰጥ እደሆነ ታውቋል። ይቺ ከተማ ሁለት ነጥብ ስድስት ሰኩየር ኪሎሜትር የሚሰፍን ስፋት እንዳላት ይነገራል።በከተማዋ የሚገነባው ይህ የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ተቋም የተለያዩ ቤተሙከራዎች እንደሚኖሩት እና ለአዳዲስ የፈጠራ ውጤቶችም ምቹ የሆነ ቦታ እንደሚሆን ተገልጿል።ከዚህ ውስጥ እንደ እቅድ የተያዘው እና በሙከራ ደረጃ ያለው የአለምን ሙቀት መቆጣጠር የሚያሰችል መሳሪያ ነው። የአለም የሙቀት መጨመር አሁን ላይ የያንዳንዱ ሀገር እራስ ምታት ከሆነ ሰነባብቷል።ለዚህም ሲባል የአለም ሀገራት የአለምን የሙቀት መጠን እንዳይጨምር ለመቆጣጠር እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር በሁለት ሺህ በፈረንሳይዋ ዋና ከተማ ፓሪስ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም።ቻይና ለዚህ ሰምምነት ታማኝነቷን እያሳየች ያለች ሀገር ሰትሆን የአለምን የሙቀት መጠንም ለመቆጣጠር ቆርጣ መነሳቷን ያሳያል ሲሉ የኋሩ ከተማ የሳይንስ ቤተ ሙከራ ዋና ዳይሬክተር ፋንግ ቹንንግ ተናግረዋል።ከዚህም በተጨማሪ በርካታ አዳዲስ ፈጠራዎችን በመሰራት ላይ እንደሆኑ ሲያስታውቁ በቅርቡ በሰፋት መንቀሳቀሰ እንደሚጀምሩ እና የፈጠራ ውጤታቸውን ይፋ እንደሚያደርጉ አሰታውቀዋል ሲል የቻይናው አለም አቀፍ ቴሌቪዥን ጣቢያ ሲጅ ቲኤን ዘግቧል።
ቻይና ሳይንሳዊ መሰረተ ልማቶችን ለመገንባት እንቅስቃሴ መጀመሯ ተገለፀ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ ሰባት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂዮ ሜሎኒ በኢትዮጵያ የነበራቸውን የስራ ጉብኝት አጠናቅቀው ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በመገኘት ለጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂዮ ሜሎኒ አሸኛኘት አድርገውላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂዮ ሜሎኒ በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ በጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ በታላቁ ቤተ መንግስት የክብር የእራት ተጋብዘዋል። በተጨማሪም ሚኒስትሯ ከጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ እና ከሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ጋር የሶስትዮሽ ውይይት አድርገዋል። በውይይታቸውም ሀገራቱ ያላቸውን የሶስትዮሽና ባለብዙ ወገን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር መስማማታቸው ነው የተገለፀው።
የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር በኢትዮጵያ የነበራቸውን የስራ ጉብኝት አጠናቅቀው ወደ ሀገራቸው ተመለሱ
አዲስ አበባ፣ መስከረም ሁለት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ ፍርድ ቤቱ የውጭ ሀገር ገንዘቦችን በማተምና ጥቁር ገበያን በማስፋፋት ወንጀል በተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ ተጨማሪ ምርመራ ማድረግ እንዲችል ለፖሊስ ቀናት ፈቀደ። የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ተረኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮውን ለፖሊስ የፈቀደው የተሰሩና ቀሪ የምርመራ ስራዎችን እንዲሁም የተጠርጣሪዎችን የመከራከሪያ ነጥብ መርምሮ ነው። ተጠርጣሪዎቹ የፀሀይ ሪል ስቴት ጀነራል ማናጀር ኪያ ዦንግን ጨምሮ ዘጠኝ የውጭ ሀገር ዜጎች እና ሶስት ኢትዮጵያውያን ናቸው። የፌዴራል ፖሊስ መርማሪ ተጠርጣሪዎቹ የውጭ ሀገር ገንዘቦችን በማተምና ጥቁር ገበያን በማስፋፋት ወንጀል መጠርጠራቸውን፣ በቁጥጥር ስር በዋሉበት ወቅት የተለያዩ የውጭ ሀገር ገንዘብ የሚታተምባቸው ማተሚያ ማሽኖች እና ለግብአት የሚያገለግሉ ኬሚካሎች እንዲሁም በርካታ ዩሮ፣ የአሜሪካን ዶላርና የሌሎች ሀገራት ገንዘቦች መያዙን ተከትሎ የምርመራ ስራ መጀመሩን መግለፁ ይታወሳል። በዛሬው ቀጠሮ ደግሞ መርማሪ ፖሊስ ከዚህ በፊት በተሰጡት የ ቀናት የምርመራ ጊዜ ውስጥ የተለያዩ ስራዎችን ማከናወኑን ለተረኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ አስታውቋል። ቀሪ የምርመራ ስራዎችን ለማከናወንም ተጨማሪ ቀናት እንዲሰጠውም ጠይቋል። የተጠርጣሪ ጠበቆች በበኩላቸው ፖሊስ ከዚህ በፊት በተሰጠው የምርመራ ጊዜ ውስጥ የተጠርጣሪዎችን ተሳትፎ ለይቶ መቅረብ ሲገባው ለይቶ ባልቀረበበት ሁኔታ ላይ ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ መጠየቁ ተገቢነት እንደሌለው በመግለፅ የደንበኞቻቸው የዋስትና መብት እንዲፈቀድ በመጠየቅ ተከራክረዋል። የፀሀይ ሪል ስቴት ጀነራል ማናጀር ኪያ ዦንግን የተባሉት ተጠርጣሪ ባጋጠማቸው የጤና እክል በቂ ህክምና እንዲያገኙ እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል። መርማሪ ፖሊስ በበኩሉ ተሳትፏቸውን በሚመለከት ከወንጀል ድርጊት ጋር ተያያዥነት ያላቸው ብርበራዎች መቀጠላቸውን በመጥቀስ ቀሪ ምርመራውን አከናውኖ ተሳትፎ ደረጃን ለይቶ እንደሚያቀርብ ገልጿል። የወንጀል ድርጊቱ ሀገርን በከፍተኛ ሁኔታ የሚጎዳ ተግባር መሆኑን የጠቀሰው መርማሪ ፖሊስ የተጠርጣሪዎቹን የዋስትና ጥያቄ በመቃወም ተከራክሯል። የግራ ቀኙን ክርክር የተከታተለው ተረኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ተጠርጣሪዎች ላይ ከቀሪ ስራ አንፃር ተጨማሪ የማጣሪያ ምርመራ መደረግ እንዳለበት በማመን የዋስትና ጥያቄያቸውን ለጊዜው ውድቅ በማድረግ ፖሊስ የምርመራ ስራውን አከናውኖ እንዲቀርብ ቀናት ተጨማሪ ጊዜ ፈቅዷል። በታሪክ አዱኛ ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ ድረ ገፅ፦ ፌስቡክ፡ ዩትዩብ፦ ቴሌግራም፦ ትዊተር፦ በመወዳጀት ይከታተሉን። ኢንስታግራም፦ ቲክቶክ፦ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
የውጭ ሀገር ገንዘቦችን በማተምና ጥቁር ገበያ በማስፋፋት በተጠረጠሩት ግለሰቦች ላይ ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ተፈቀደ
አዲስ አበባ፣ ታሀሳስ ሶስት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የቴክኒክና ሙያ አሰላሳይና ሀሳብ አመንጪዎች ቡድን ቲንክ ታንክ ግሩፕ በአዲስ አበባ በይፋ ተመስርቷል። የስራና ክሀሎት ሚኒስትር ሙፈሪሀት ካሚል በምስረታው ላይ እንዳሉት፥ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ለውጥ እንዲመጣ በእውቀት፣ በጥናትና ምርምር መደገፍ ያስፈልጋል። ለዚህም አዳዲስ አሰራሮች ቀጣይነት ባለው መልኩ የሚፈልቁበትን አሰራርና አደረጃጀት መፍጠር ይገባል ብለዋል። በዛሬው እለት የተመሰረተው የቴክኒክና ሙያ አሰላሳይና ሀሳብ አመንጪዎች ቡድንም ጥሩ ጅምር መሆኑን ጠቅሰው፥ ሀገራዊ የልማት ተልእኮን ለማሳካት የላቀ ሚና እንደሚኖረው አመላክተዋል። በተጨማሪም የሪፎርም እሳቤዎችን ውጤታማ ለማድረግና ተወዳዳሪ ሀገራዊ ኢኮኖሚ ለመገንባት የማይተካ ሚና አለው ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል። የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር ዶክተር በበከሉላቸው፥ በዘርፉ አሰላሳይና ሀሳብ አመንጪዎች ቡድን መመስረቱ የሀገሪቱን የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ጥራት ለማስጠበቅ ከፍተኛ እገዛ አለው ብለዋል። የቡድኑ መመስረት በፖሊሲ አተገባበር ሂደት ውስጥ የካበተ ሀሳብ በመስጠት፣ ልምዶችን በማካፈል፣ የውይይት ባህል እንዲዳብርና በዘርፉ ተዋንያን መካከል ተቀራርቦ ለመስራት ትልቅ አስተዋፅኦ ያለው መሆኑንም ገልፀዋል።
የቴክኒክና ሙያ አሰላሳይና ሀሳብ አመንጪዎች ቡድን ተመሰረተ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት ሀያ ዘጠኝ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ የጃራ አባገዳ ትምህርት ቤት ውስጥ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ ህንፃዎች የግንባታ ስራ ለማስጀመር የመሰረት ድንጋይ አስቀመጡ። ለተከታታይ ሶስት አመታት ሲጠየቅ የቆየውን በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ የጃራ አባገዳ ትምህርት ቤት ውስጥ የተማሪዎች መማሪያ፣ የአስተዳደር ህንፃ፣ የላይብረሪና የላብራቶሪ አገልግሎት የሚውሉ ህንፃዎች ናቸው የሚገነቡት። ከዚህ ቀደም ከፍተኛ የህዝብ ጥያቄ ከነበረባቸው አንዱ የሆነው ይህ ትምህርት ቤት፥ ግንባታው ሲጠናቀቅ የቅበላ አቅሙን ከአራት መቶ አምስት ወደ አንድ ሺህ አምስት መቶ በማሳደግ ትልቅ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተገልጿል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ የመሰረት ድንጋዩን ባስቀመጡበት ወቅት፥ የህዝብን አንገብጋቢ ችግሮች ቅድሚያ ሰጥተን በመፍታት ሂደት ላይ ነን ያሉ ሲሆን፤ ትምህርት ቤቱም የዚህ ማእቀፍ አንዱ አካል መሆኑን አስረድተዋል። ተማሪዎች በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው መማር አለም አቀፍ ተቀባይነት ያገኘና ህገ መንግስታዊም መብት ነው ያሉ ያሉት ከንቲባዋ ፥ በሌሎች የሀገራችን ክልሎችም በበርካታ ቋንቋዎች ትምህርት እየተሰጠ ነው ብለዋል። አዲስ አበባ ውስጥም ተማሪዎች በአማርኛ ብቻ ሳይሆን በተለያዩ አለም አቀፍ ቋንቋዎች ማለትም በግሪክ፣ በፈረንሳይኛ፥ በአረብኛ፣ በቱርክና በመሳሰሉት እንደሚማሩ ጠቁመው፥ የአገራቸውን ባንዲራ ይሰቅላሉ፤ የአገራቸውንም መዝሙር ይዘምራሉ ፤ ከአገራቸው ቋንቋ አንዱ በሆነው በኦሮምኛም መማር ከጀመሩም ዋል አደር ብለዋል ነው ያሉት። ሆኖም ግን አንዳንዶች ይህንን እንደ ስህተት በመቁጠር የፖለቲካ አጀንዳ ሊያድረጉት መሞከራቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልፀው፥ ህፃናት በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው መማርና መናገር ሙሉ መብት እንዳላቸው ገልፀው፥ ልጆች በመብታቸው እንዳይጠቀሙና እንዲሸማቀቁ የሚያደርጉ አካላት ከህገ ወጥ ድርጊታቸው እንዲታቀቡም አሳስበዋል። አዲስ አበባ ለኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካውያን እና ለአለም አቀፍ ተቋማት መልካም ቤት ሆናለች ያሉት ከንቲባ አዳነች ፥ የራስዋን ልጆች የምታሸማቅቅ እንድትሆን ለማድረግ የሚጥሩ አካላት መሰረታዊ ስህተት እየፈፀሙ ስለሆነ በፍጥነት መታረም አለባቸው ሲሉ በአፅንኦት ገልፀዋል። ዘላቂ ሰላምና ልማት የሚመጣው ህዝቡን አስተባብሮና አንድነቱን አጠናክሮ በመምራት እንጂ የጥላቻን አስተሳሰብ በመዝራት አይደለም ነው ያሉት ከንቲባዋ። የትምህርት ቤቱ ግንባታ በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ መግለፃቸውንም ከከንቲባ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ ድረ ገፅ፦ ፌስቡክ፡ ዩትዩብ፦ ቴሌግራም፦ ትዊተር፦ በመወዳጀት ይከታተሉን። ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የጃራ አባገዳ ትምህርት ቤት ውስጥ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ ህንፃዎች የግንባታ ስራ የመሰረት ድንጋይ አስቀመጡ
የፌስ ቡክ ተከታዮቹ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ሆነዋልቃና ቴሌቪዠን የተመልካቾቹን የመዝናኛ አማራጭ ለማጎልበት ሁለት አዳዲስ ዝግጅቶችን አንድ ወጥ እና አንድ በአማርኛ የተመለሰ ማቅረብ መጀመሩን ገለፀ። በአሁኑ ጊዜ ጣቢያው በየሳምንቱ የስላሳ ሰአት አዳዲስና ያልታዩ ዝግጅቶችን ለተመልካቹ እንደሚያቀርብ በላከው መግለጫ አስታውቋል።ሰሞኑን አምስትኛ ክፍሉ የተሰራጨው የ ምንድን ዝግጅት፣ የተለያዩ ወቅታዊ ማህበረሰብ ተኮር ርእሶችን እያነሳ ከተለያዩ ምልከታዎች አንፃር የሚያወያይ ሲሆን በዚህም የተመልካቾችን ተሳትፎና ጤናማ ውይይቶች ያበረታታል ተብሏል። አዲስ የተጀመረው ልጅቷ የተባለው የኮሎምቢያ ድራማ፤ በእውነተኛ ክስተቶች ላይ የተመረኮዘ ሲሆን የጦርነትን አስከፊ ገፅታ ያሳያል። ታሪኩ አንዲት ሴት በሽምቅ ተዋጊዎች ተመልምላ የጦርነትን አስከፊ ገፅታ በአፍላ እድሜዋ እንድትኖረው ስትገደድና ከብዙ አመት በኋላ አምልጣ አዲስ ኑሮ ለመጀመር ስትሞክር፣ ከህብረተሰብ ጋር ለመቀላቀል፣ ነፃነትዋን ለመልመድና ቤተሰብዋን ለመጋፈጥ የሚደርስባትን ውጣ ውረድ ያስቃኛል። ድራማው ከፍተኛ አድናቆትን ያገኘ ሲሆን በቅርቡ ኔትፍሊክስ በተባለው ታዋቂ የፊልም አቅራቢና አከፋፋይ ተገዝቶ፣ በብዙ አገሮች እየታየ ይገኛል ብሏል ቃና በመግለጫው።በተመልካቾች ዘንድ ተወዳጅነትን ያተረፈውን ጥቁር ፍቅር የተሰኘ ድራማ የሚተካ ቅጣት የተባለ ወደ አማርኛ የተመለሰ የቱርክ ድራማ በቅርቡ ማቅረብ እንደሚጀምር ጠቁሞ ቅጣት በይዘቱ ልክ እንደ ጥቁር ፍቅር በተለያዩ አገሮች ዝና እና ሽልማት ተቀዳጅቷል ተብሏል። ጣቢያው የተመልካቾቹን እይታ ለማበልፀግና ፍላጎታቸውን ለመገንዘብ፣ በየጊዜው የተለያዩ ጥናቶችና ዳሰሳዎች እንደሚያካሂድ ጠቁሞ ግኝቶችንም በሚያቀርባቸው ዝግጅቶች ላይ እንዲንፀባረቁ ይደረጋል ብሏል።በስርጭት ላይ በቆየበት የስድስት ወር ጊዜያት ውስጥ ጥሩ አቀባበል ማግኘቱን የጠቀሰው ቃና ፤ የፌስ ቡክ ተከታዮቹ ከአንድ ሚሊዮን በላይ መድረሳቸውን አስታውቋል። በቅርቡ በቤል ካሽ የተካሄደ በ አምስት ሺህ ሰዎች ላይ የተደረገ አገር አቀፍ የስልክ መጠይቅ፤ ከሶስት ተጠያቂዎች ውስጥ አንዱ የቃና ቴሌቪዥን ዝግጅቶችን ከሰኞ እስከ አርብ በየቀኑ እንደሚያዩ አመልክቷል። ቃና ቴሌቪዥን በህብረተሰቡ ዘንድ ያለው አቀባበል አበረታችና ከጠበቅነው በላይ ነው። ወደፊትም የመዝናኛ አማራጭ የሆኑ አዝናኝና አሳታፊ ዝግጅቶችን ለማቅረብ የተመልካቾቻችንን ፍላጎት ማጥናት እንቀጥላለን ብለዋል፤ የቃና ቴሌቪዥን የኮሙኒኬሽን እና ማርኬቲንግ ዳይሬክተር። ቃና ቴሌቪዥንና የዝግጅት አጋሩ ቢ ሚዲያ በቅርቡ ይፋ የሚሆኑ ተጨማሪ ወጥ ስራዎችን እያዘጋጁ እንደሚገኙም ለማወቅ ተችሏል።
ቃና ሁለት አዲስ ዝግጅቶችን ማስተላለፍ ጀመረ
ኢሳት ዲሲሚያዚያ የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ኮሚሽነር ዛይድ ራድ አል ሁሴን የኢትዮጵያ መንግስት የሰብአዊ መብትን በማክበር ለዜጎች ተስፋ እንዲሰጥ ጠየቁ።ኮሚሽነሩ በኢትዮጵያ ያካሄዱትን ጉብኝት ካጠናቀቁ በኋላ በሰጡት መግለጫ አዲሱ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አመራር ለህዝቡ የሰጠውን ተስፋ በመተግበር የሰብአዊ መብቶች ሊጠበቁ ይገባል ብለዋል።በጉብኝታቸውም የፖለቲካ እስረኞች የነበሩ ሰዎችን የሀይማኖት አባቶችንና ባህላዊ መሪዎችን አነጋግረው ህዝቡ በአዲሱ አስተዳደር የተገቡ ተስፋዎች መክነው እንዳይቀሩ ስጋት እንዳላቸው መረዳታቸውን ኮሚሽነሩ ገልፀዋል።የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ኮሚሽነር ዛይድ ራድ አልሁሴን የአገዛዙ ባለስልጣናትን ካነጋገሩ በኋላ በኦሮሚያና በአዲስ አበባ የፖለቲካ እስረኛ የነበሩትንና የሀይማኖት እንዲሁም ባህላዊ መሪዎችን አነጋግረዋል።በመጀመሪያው ጉብኝታቸው በኦሮሚያና አማራ ክልሎች ጉብኝት እንዲያደርጉ ተከልክለው የነበሩት ኮሚሽነሩ በአሁኑ ኛ የኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ገደቡ ተነስቶ ወደ ቢሾፍቱና መሰል አካባቢዎች ከነዋሪዎች ጋር መወያየታቸው አዎንታዊ ርምጃ መሆኑን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል።በዚሁ ውይይታቸውም ዜጎች በአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ንግግሮችና በሰጧቸው ቃል ኪዳኖች ተስፋ መሰነቃቸውን እንደተረዱ ነው የተናገሩት።ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር ባካሄዱት ውይይትም ለግጭት ምክንያት የነበሩ የፍትህ እጦቶችን ለማስተካከል መንግስታቸው ቁርጠኛ መሆኑን እንደተገነዘቡም ገልፀዋል።መንግስትን በመቃወማቸውና በመተቸታቸው ታስረው የነበሩ ጋዜጠኞችና ፖለቲከኞች ከእስር መፈታታቸው አዎንታዊ ርምጃ እንደሆነም ኮሚሽነር ዛይድ ራድ አልሁሴን በመግለጫቸው ተናግረዋል።እናም ከእስር የተለቀቁ ሰዎችንና ልዩ ልዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን ለማነጋገር መቻላቸውን ነው የገለፁት።በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ አባገዳዎችን ሲያናግሩም በሀገሪቱ ያለውን ችግር በግልፅ በማውራት በመንግስት የተፈፀሙ በደሎችን እንደዘረዘሩላቸው ተናግረዋል።ኮሚሽነሩ ከአባ ገዳዎች ጋር ሲወያዩ የክልል ባለስልጣናት የነበሩ ቢሆንም ሰዎቹ ግን ችግሩን ከመናገር አልተቆጠቡም።ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን አባ ገዳ በየነ ሰንበቶ በእሬቻው እልቂት ጉዳይ ላይ የፀጥታ ሀይሎች ሰው አልገደሉም የሚል ምስክርነት እንዲሰጡ ተገደው እምቢተኛ እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል።በተለይ ከሰብአዊ መብት ጠበቃ ከሆኑ ሁለት የአለም አቀፍ ተወካዮች ጋር በሮዝሜሪ የተካሄደው ውይይት በመንግስት ባለስልጣናት ትእዛዝ እንዲቋረጥ መደረጉ ተነግሯል።
የህወሀት አገዛዝ የሰብአዊ መብትን በማክበር ለዜጎች ተስፋ እንዲሰጥ ተጠየቀ
ዜጐች ወደተለያዩ አገሮች ሄደው እንዲሰሩ የሚፈቅደው አዲሱ የግል ሰራተኞችና አሰሪ አዋጅ በተወካዮች ምክር ቤት ቢፀድቅም አዋጁ ማሟላት ያለባቸው ብዙ ነገሮች ስላሉ ጉዞው አሁኑኑ አይጀምርም ተባለ። ጉዞው መቼ እንደሚጀመር የተጠየቁት የሰራተኛና ማሀበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ግርማ ሸለመ፣ አዋጁ ታኀሳስ ቀን ሁለት ሺህ ስምንት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቢፀድቅም በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ስላልወጣ፣ የአዋጅ ማስፈፀሚያ፣ አደረጃጀት መመሪያና ደንብ መውጣት ስላለበትና ተጓዦች ስልጠና መውሰድ ስላለባቸው ጉዞው በዚህ ጊዜ ይጀመራል ማለት አይቻልም ብለዋል። ወደተለያዩ የአረብ አገሮች የሚሄዱ ዜጐቻችን የተለያዩ የመብት ጥሰቶች፣ እንግልት፣ የአካል ጉድለትና የሞት አደጋ ሲደርስባቸው ቆይቷል፤ መብታቸው፣ ደህንነታቸውና ክብራቸው ሳይጠበቅ እየተዋረዱ ይመለሱ ነበር ያሉት አቶ ግርማ፤ መንግስት፣ ዜጐቻችን እንደሌሎች አገሮች ዜጎች ለምንድነው መብታቸውና ደህንነታቸው የማይከበረው ኮንትራታቸውን ሲጨርሱ ለምንድነው በደሀና ወደ አገራቸው የማይመለሱት ችግሩ ምንድነው የአዋጁ ወይስ ውጭ ያለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ችግር ወይስ የዜጐቻችን ሳይሰለጥኑ መሄድ የሚሉ ጥያቄዎችን በማንሳት ችግሩን ለማወቅ ከሁለት አመት በፊት የውጭ አገር የጉዞ ስምሪት እንዲቆም መደረጉን አስታውሰዋል። በተደረገውም ጥናት የቀድሞው አዋጅ ክፍተቶች እንደነበሩት፣ ዜጐች ከሚሄዱባቸው አገራት ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያለመኖር እንዲሁም ዜጐች ወደ ውጭ አገር ለስራ ሲሄዱ ያለምንም እውቀት እንደሚጓዙ ስለታወቀ አዲሱ አዋጅ በፊት የነበሩት ጉድለቶች ታርመው መዘጋጀቱን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። በአዲሱ አዋጅ ወደተለያዩ አገራት የሚሄዱ ዜጐች የትምህርት ደረጃ ስምንትኛ ክፍልና ከዚያ በላይ መሆን እንዳለበት የተካተተ ሲሆን ተጓዦች በቤት አያያዝና በእንክብካቤ አጠባበቅ ቢያንስ የሶስት ወር ስልጠና የተወሰዱና የብቃት ማረጋገጫ ሲኦሲ ፈተና ተሰጥቷቸው ያለፉ መሆን እንዳለባቸው ተገልጿል። ስልጠናው የሚሰጠው በውጭ አገር እንዲሰሩበት ብቻ ሳይሆን ከመንግስት ብድር ወስደው፣ የመሸጫ ቦታ ተመቻችቶላቸውና የገበያ ትስስር ተፈጥሮላቸው በአገር ውስጥ እንዲሰሩም ጭምር ነው ብለዋል፤ አቶ ግርማ። የሙያ ስልጠናው የሚሰጠው በአራቱ ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች፡ በአማራ፣ በትግራይ፣ በኦሮሚያና በደቡብ ብሄርና ብሄረሰቦች እንዲሁም በአዲስ አበባና በድሬዳዋ ከተሞች እንደሆነ የጠቀሱት ዳይሬክተሩ፣ ስልጠናው የሚሰጠው በክልሎቹና በከተሞቹ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት እንደሆነም ገልፀዋል። ከኩዌት፣ ከኳታርና ከጆርዳን ጋር የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ተፈጥሮ ስምምነት ተፈራርመናል ያሉት ዳይሬክተሩ፤ ከሳኡዲ አረቢያና ከሌሎች አገሮች ጋር እየተወያዩ መሆኑንም ተናግረዋል። ህዝቡ ህገ ወጥ የሰው አዘዋዋሪዎች፣ አሁን አዋጁ ፀድቋል በሚል ማታለያ ልጆቻቸውን እንዳያስኮበልሏቸውም ጥንቃቄ ያደርጉ ዘንድ አቶ ግርማ ሸለመ አሳስበዋል።
የውጭ አገር የስራ ስምሪት አዋጅ ቢፀድቅም አሁኑኑ ጉዞ አይጀመርም ተባለ
አቶ አንዱአለም ተፈራ ከገዢው መደብ የምንለይበት በሚል ርእስ ባስነበቡን ፅሁፍ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግስት የሚለውን አጠራር ለምን እንደመረጡ ያስረዳሉ። መጠሪያው ለወያኔ የማይገባው በመሆኑና አቶ አንዱአለም መጠሪያውን ለመጠቀም ያአስቻለኝ ብለው ያቀረቡት ምክንያት በቂና ተገቢ ሆኖ ስላልተሰማኝ ይህችን አስተያየት ፃፍሁ። ትግሬ ስንል የኢትዮጵያ አንድ ክፍል በሆነው ትግራይ የተወለዱና ትግረኛ ቋንቋ የሚናገሩ ወይንም የወላጆቻቸው ስር ከዛ ሆኖ የትም ይሁን የት የተወለዱና ቋንቋውን ሊናገሩም ላይናገሩም የሚችሉትን ሁሉ የሚያጠቃልል ነው። ስለሆነም የትግሬ ነፃ አውጪ ስንል ወያኔ ትናንትም የታገለው ዛሬም ስልጣን ላይ ሆኖ የሚሰራው እነዚህን ነፃ ለማውጣት ነው፣ እነርሱም ነፃ አውጪነቱን አውቀውና አምነው የተቀበሉት ነው ወደሚል አንደምታ ይወስዳል። ይህ ደግሞ ወያኔ የሚፈልገው ነው። እሱ የሚለውን ተቀብሎ ትግሬና ወያኔን አንድ አድርጎ የመመልከቱ አደገኛነት የታያቸው ኢትዮጵያውያን ገና ከጅምሩ ወያኔንና ትግረኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያንን ለይቶ ማየት እንደሚገባ፣ ሁለቱን መቀላቀል ትግሉን የሚጎዳና ወያኔን የሚጠቅም ብሎም በወደፊት የኢትዮጵያ አንድነት ላይ መጥፎ ደንቃራ የሚያስቀምጥ መሆኑን አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል፣ፅፈዋል። ይህም ሙሉ በሙሉ ባይሆንም በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ተቀባይነት በማግኘቱ ወያያኔ ባሰበውና በተመኘው መጠን ትግረኛ ተናጋሪውን ከቀሪው ኢትዮጵያዊ ወገኑ ነጥሎ የርሱ ብቸኛ መከታ ማድረግ አልቻለም። ወያኔዎች ትናንትም ሆነ ዛሬ አላማ ፍላጎታቸው ስልጣን ነው። ትግል ሲጀምሩ መላ ኢትዮጵያን መያዝ አንችልም ብለው ስላመኑ ትግራይን ይዘው የስልጣን ፍልጎታቸውን ለማርካት ስማቸውን ተሀህት፣ማገብት ህውሀት እያሉ ለትግረኛ ተናጋሪው ወገን የሚታገሉ መስለው ተጓዙ እንጂ ከራስ ጥቅም ያለፈ አላማም አጀንዳም ያላቸው አይደሉም። ይህን ደግሞ በሀያ አራት አመታት አገዛዛቸው በሚገባ የተገነዘብን ይመስለኛል። በአላማም በግብርም የማይመስሉትን የቀዳማይ ወያኔን ስም የያዙትም በእምነት ሳይሆን ድጋፍ ለማግኘት ካልሆነም ተቃውሞን ለመቀነስ እንደሆነ የትግራይ አባቶችን ጠጋ ብሎ ጠይቆ መረዳት ይቻላል። በኢትዮጵያዊ እምነትና ስሜታቸው ጥያቄ የማይነሳባቸው ዶክተር ሀይሉ አርአያ በአንድ ፅሁፋቸው እነዚህ ሰዎች ከቀዳማይ ወያኔ ጋር በአላማም በተግባርም ስለማይመሳሰሉ ወያኔ ተብለው መጠራት የለባቸውም አስመሳይ ወያኔዎች ናቸው ማለታቸውን አስታውሳለሁ። ስለሆነም የትግሬ ነፃ አውጪ ማለት ለግብራቸው የማይመጥን ስም ነው፤ ይበዛባቸዋል። እንደውም ለእነርሱ ፍላጎት መሳካት የሚበጃቸው ነው። አቶ አንዱአለም በፅሁፋቸው እኔ ራሳቸውን እንዲጠሩበት በመረጡት ስም ነው የጠራኋቸው ይላሉ። ሰይጣን ለተንኮሉ ከመፅሀፍ ቅዱስ ይጠቅሳል እንዲሉ ወያኔ ትክክለኛ ማንነቱን የሚከልልለትንና ትግረኛ ተናጋሪውን ኢትዮጵያዊ ወገን ጋሻ ማድረግ ያስችለኛል ብሎ የመረጠውን ግብሩን የማይገልፅ ስም ለራሱ ስለሰጠ እኛ ተቀብለን ማስተጋባት የለብንም። ይህን አደረግን ማለት በተዘዋዋሪ የወያኔን ፍልጎት ማሳካት ነው የሚሆነው። የወያኔ ስብከትና ማስፈራራያ ያልበገራቸው በርካታ ትግረኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን በተቃውሞው ጎራ ጥንቃቄ የጎደለው ተግባር ያለፍላጎታቸው ወያኔን ለመደገፍ መገደዳቸው የአደባባይ ምስጢር ይመስለኛል። የሚወዱትን ሲያጡ እንደሚባለው ሆኖባቸው። አቶ አንዱአለም ትግሬዎችን ነፃ አወጣለሁ ብሎ የተነሳ ግንባር፤ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ነኝ ሲል፤ ሌላ ምን ብዬ ልጠራው ይላሉ። ይህን አባባል ከላይ ለመግለፅ በሞከርኩት አስተሳሰብ ስናየው ሶስት ጉድለቶች አሉት የመጀመሪያው ትግሬዎችን ነፃ አወጣለሁ ብሎ የተነሳ የሚለው ሲሆን ይህን ከላይ ለማሳየት ሞክሬአለሁ፤ ሁለተኛው ግንባር የሚለው ነው፡ከመጠሪያው ጋር ሊቀራረብ የሚችለው ህወሀት ነው እሱ ደግሞ ግንባር አይደለም፤ ግንባሩ ኢህአዴግ ነው። እሱን በጥቅሉ የትግሬ ነፃ አውጪ ለማለት ተፈልጎ ከሆነ ደግሞ ወያኔ ሀገራዊውን የፖለቲካ ትግል የጎሳ ትግል ለማድረግ ሌት ከቀን የሚማስንበትን ስራ እያሳካንለት ነው ማለት ነውና አደጋ አለው። ሶስተኛው ነኝ ሲል እኔ ምን ብዬ ልጥራው የሚለው ነው። እኛ መጠራት ያለብን እሱ ነኝ በሚለው ማንነቱን በማይገልፀው ሳይሆን ለማንነቱ በሚመጥነው ለግብሩ መገለጫ በሚሆን መጠሪያ መሆን አለበት። አሁን ልማታዊ መንግስት እያለ ራሱን እየጠራ ነው ታዲያ እኛ በዚህ እንጠራዋለን ነገርን ነገር ያነሳዋል አንዲሉ በዚህ ረገድ ሌሎች ስህተቶችም ስንፈፅም ኖረናል አሁንም እየፈፀምን ነው፤ ብሶት የወለደኝ ሲል ተቀብለን ብሶት የወለደው ብለናል፣ በረሀ የወረድነው አንባገነኑን የደርግ መንግስት ለማስወገድ ነው ሲሉ ሰምተን አሰምተናል ተቀብለን ተናግረናል። እንደሚነግሩን ጫካ የገቡት የካቲት አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ስልሳ ሰባት ነው። በዚህ ወቅት ንጉሱን ከስልጣን
ወያኔን የትግሬ ነፃ አውጪ ማለት ያለ ግብሩ ስም መስጠት
የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ፤ ባለፈው ረቡእ ለሶስት ሰአታት በፖሊስ ጣቢያ ታስረው መፈታታቸው ተገለፀ። ዶክተር ነጋሶ፤ ፓርቲው ነገ ያካሂዳል ተብሎ ለሚጠበቀው ሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ እንዲያደርጉ ካሰማራቸው አባላት ጋር በተያያዘ ታስረው እንደነበር ታውቋል። ባለፈው ረቡእ የሰላማዊ ሰልፍ ቅስቅሳ ሲያደርጉ የነበሩ የፓርቲው አባላት የቅስቀሳ ፈቃድ የላችሁም ተብለው በፖሊስ መያዛቸውን የገለፀው ፓርቲው፤ የአንድነት ልሳን ጋዜጣ ፎቶግራፍ አንሺም በራሪ ወረቀት ሲቀበሉ የነበሩ ሰዎችን ያለፍላጐታቸው ፎቶግራፍ አንስቷል፤ ተሳድቧል በሚል ክስ እንደቀረበበት አስታውቋል። ዶክተር ነጋሶ የሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ እንዲደረግ ለአባላቱ የስምሪት ደብዳቤ በመፈረማቸው፣ ድርጊቱ የተፈፀመው እሳቸው በሰጡት አመራር እንደሆነ በፖሊስ ተገልፆላቸው ጉዳዩ እስኪጣራ መታሰራቸውን ነው ፓርቲው የገለፀው። ከሶስት ሰአት እስር በኋላም ፎቶግራፈሩ በዋስ ሲለቀቅ ዶክተር ነጋሶ በነፃ እንደተለቀቁ ታውቋል።
ዶክተር ነጋሶ ለሶስት ሰአት ታስረው ተፈቱ
ኢሳት ዜናጥቅምት በቅርቡ ስልጣን በለቀቁት በአቶ በረከት ስምኦን ንብረቶች ላይ የተጀመረው የሙስና ምርመራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የኢሳት ምንጮች ገለፁ።በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ ከተገነባው ደብል ትሪ ሆቴል ጋር በተያያዘ የተጀመረው ምርመራ ሙሉ በሙሉ የሆቴሉ ግንባታ የገንዘቡ ምንጭ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መሆኑን አረጋግጧል።ይህም የተፈፀመው በአቶ በረከት ስምኦን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቦርድ ሊቀመንበርነት ግዜ እንደሆነ መረጋገጡን ምንጮቹ ጨምረው ገልፀዋል።በአቶ በረከት ስምኦን ንብረቶች ላይ የተጀመረው የሙስና ምርመራ መቀጠሉን ነው የኢሳት ምንጮች የገለፁት። በምርመራውም በአዲስ አበባ ከተማ የተገነባው የደብል ትሪ ሆቴል የገንዘብ ምንጭም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መሆኑና አቶ በረከት የቦርድ ስብሳቢ በነበሩበት ጊዜ የተፈፀመ መሆኑንም አረጋግጧል።የደብል ትሪ ሆቴል ባለቤት ሆነው የተመዘገቡት አቶ ተካ አስፋውም የዳሽን ባንክ ቦርድ ሰብሳቢ ቢሆኑም ለዚህ ሆቴል ግንባታ በሚል ከዳሽን ባንክ ምንም አይነት ብድር እንዳልወሰዱም ታውቋል።የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብድር በዋናነት እንዲሰጥ የተቀመጠውን የመንግስት ፖሊሲ በመፃረር ብድሩ እንደተለቀቀም ለማወቅ ተችሏል።በዋናነት በአምራችነትና በወጭ ንግድ ላይ ለተሰማሩ ብድር እንዲሰጥ በፖሊሲ ደረጃ አቅጣጫ የተቀመጠለት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለሆቴሉ ግንባታ የሚውለውን ወጪ መቶ በመቶ ማበደሩንም ምርመራው አረጋግጧል።በቅድሚያ ሁለት መቶ ሚሊየንበቀጣይ ደግሞ ሚሊየን ብር በአጠቃላይ ሚሊየን ብር ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወጪ የሆነው በአቶ በረከት ስምኦን ትእዛዝና በባንኩ ፕሬዝዳንት በአቶ በቃሉ ዘለቀ አስፈፃሚነት እንደሆነም ለኢሳት የደረሰው ማስረጃ ያሳያል።ባንኩ ብድር ከመልቀቁ በፊት ተበዳሪው በመቶ መነሻ ማቅረብ እንዳለበት ተደንግጓል።በዚህ ሆቴል ግንባታ ግን ከተበዳሪው ወገን አንድም ሽራፊ ሳንቲም እንዳልቀረበና መቶ በመቶ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ገንዘብ ሆቴሉ መገንባቱን ምርመራው አረጋግጧል።የኢሳት ምንጮች የምርመራ ቡድን አሁንም ስራውን መቀጠሉን አስታውቀዋል።መቀሌ የተጀመረው የህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ስብሰባ ላይ እነ አቶ አባይ ወልዱ መልሰው የበላይነታቸውን ካላረጋገጡ በአቶ በረከት ላይ የተጀመረው ምርመራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና በመገናኛ ብዙሀን ይፋ እንደሚደረግም ምንጮቹ ጨምረው ገልፀዋል።አንዳንድ ወገኖች እንደሚሉት በአቶ በረከት ስምኦን ላይ ከደብል ትሪ ሆቴል ጋር በተያያዘ በዚህ ወቅት ምርመራ የተጀመረው የሆቴሉ ባለንብረት ሆነው የተመዘገቡት አቶ ተካ አስፋው ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንትነት ስለሚወዳደሩ የህወሀት ሰዎች የእርሳቸውን ተቀናቃኝ የህወሀቱን ተክለወይኒ አሰፋን ለማስመረጥ የሚደረግ ማሸማቀቅ ሊሆን ሲሉ ስጋታቸውን ይገልፃሉ።ንብረትነቱ የአቶ በረከት ስምኦን በሚል ምርመራ የተጀመረበት በአለም አቀፍ ደረጃ የተገነባውና በአዲስ አበባ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢ የሚገኘው ደብል ትሪ ሆቴል በመጪው ሰኔ ስራ ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል።ጠቅላላ ወጪው ሚሊየን ብር የፈጀው ደብል ትሪ ሆቴል ባለ ፎቅ ሲሆን መኝታ ክፍሎች እንዳሉትም ታውቋል።
በአቶ በረከት ስምኦን ንብረቶች ላይ የተጀመረው የሙስና ምርመራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ታወቀ
የአባዲ ሀዲስ እድሜ እያነጋገረ ነው በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ስላሳ አንድኛው ኦሊምፒያድ ከተጀመረ ስድስተኛ ቀን አስቆጥሯል። ከተለያዩ የአለም አገሮች የተሰባሰቡት ስፖርተኞች በተገኙበት የዘንድሮው የሪዮ ኦሊምፒክ ጨዋታ ሀምሌ ሀያ ዘጠኝ ቀን ሁለት ሺህ ስምንት አመተ ምህረት በድምቀት ሲከፈት፣ የኢትዮጵያ ልኡካን ቡድን በዋናተኛው አቤል ኪሮስ መሪነት ወደ ስታዲየም ሲገባ አቀባበል ተደርጎለታል። ኢትዮጵያ በወርቃማ ውጤቷ የምትታወቅበት የረዥም ርቀት ሩጫ ከነገ በስቲያ አርብ ነሀሴ ስድስት ቀን በሚካሄደው የሴቶች አስር ሜትር ፍፃሜ ውድድር የሚጀመር ሲሆን፣ አዲሷ ኮከብ አልማዝ አያና፣ ገለቴ ቡርቃ እና የሁለት ኦሊምፒኮች ባለድሏ ጥሩነሽ ዲባባ የአገሪቱን ድል እንደሚያስቀጥሉ ይጠበቃል። በመካከለኛ ርቀት በስምንት መቶ ሜትር መሀመድ አማን፣ በአንድ አምስት መቶ ሜትር ገንዘቤ ዲባባ፣ ዳዊት ስዩምና በሱ ሳዶ የመጀመርያ ማጣሪያ ውድድራቸውንም ያከናውናሉ። ቅዳሜ በሚካሄደው የአስር ሜትር ወንዶች ፍፃሜም ይገረም ደመላሽ፣ ታምራት ቶላ እና አባዲ ሀዲስ ሲፎካከሩ፣ በእሁዱ የሴቶች ማራቶን ፍፃሜ ትእግስት ቱፋ፣ ማሬ ዲባባና ትርፊ ፀጋዬ ይወዳደራሉ። የአርብ ተወዳዳሪ አትሌቶች ነሀሴ ሶስት ቀን ሪዮ የገቡ ሲሆን፣ የቅዳሜና እሁድ ተፎካካሪዎች ነሀሴ አራት ቀን ወደ ስፍራው እንደሚያቀኑ ብሄራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴው አስታውቋል። አነጋጋሪው እድሜ የሪዮ ኦሊምፒክ ከመጀመሩ በፊት ኢትዮጵያን በሚወክሉ አትሌቶች መረጣ ብዙ ማከራከሩ አይዘነጋም። በተለይ ኢትዮጵያ በረጅሙ ርቀት ካላት ታሪክ ጋር በተያያዘ ትክክለኛውን አትሌት ወደ ስፍራው ለመላክ ሽኩቻ መፍጠሩ ይታወሳል። ዛሬ ወደ ሪዮ ከሚጓዙት የአስር ሺህ ሜትር ርቀት ተወዳዳሪ አትሌቶች ውስጥ በግንቦት ወር ቻይና ሻንጋይ ላይ በተደረገ የዳይመንድ ሊግ አለም አቀፍ ውድድር የተሳተፈው ወጣቱ አባዲ ሀዲስ ተጠቃሽ ነው። አትሌቱ በዳይመንድ ሊግ ሲሳተፍ በ አመት እድሜ መወዳደሩ ይታወሳል። ባለፈው ግንቦት በሻንጋይ በተደረገው የአምስት ሺህ ሜትር ውድድር ላይ ደቂቃ ከሁለት ነጥብ አራትዘጠኝ ሰከንድ በመግባት አራተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቋል። በውድድሩ ላይ ያመጣው ሰአት ከቀድሞ አትሌቶች ቀነኒሳ በቀለና ኢብራሂም ጄላን የተሻለ ስለነበር ለሪዮ መመረጥ ችሏል። በእለተ ቅዳሜ ነሀሴ ሰባት ቀን ሁለት ሺህ ስምንት አመተ ምህረት በሚደረገው የአስር ሜትር ፍፃሜ ውድድር ላይ ይግረም ደመላሽ፣ ታምራት ቶላና አባዲ ሀዲስ ቀዳሚ ተሰላፊዎች ተደርገው ተይዘዋል። በሻንጋይ አምስት ሜትር ውድድር አመት የሚታወቀው አባዲ አሁን የ አመት ወጣት ተደርጎ ኢትዮጵያን እንደሚወክላት እየተገለፀ ይገኛል። ግንቦት ወር ላይ በ አመት የተወዳደረው አባዲ እንዴት አሁን በ አመት ተደርጎ ተወስዶ ሊወዳደር ይችላል የሚለው የብዙዎቹ ጥያቄ ሆኖ ቆይቷል። አለም አቀፉ የአትሌቲክስ ማሀበር አይኤኤኤፍ እንደሚያስቀምጠው፣ የአስር ሜትር ደንብ ከሆነ በኦሊምፒክ አንድ አትሌት ከ አመት በታች ከሆነ ውድድር ላይ መሳተፍ እንደማይችል የተለያዩ ባለሙያዎች ይናገራሉ። ለዚህም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተጠባባቂ ባልያዘበት የአስር ሜትር ውድድር የእድሜ ማጣራት ተደርጎ አትሌትውን ከውድድሩ ውጪ ሊሆን ይችላል የሚለው ሀሳብ በብዙዎቹ ዘንድ ስጋት ፈጥሯል። ፌዴሬሽኑ በበኩሉ በአትሌቱ ላይ የተነሳው የእድሜ ችግር ከአለም አቀፍ አትሌቲክስ ማሀበር ጋር በመነጋገር ተስተካክሏል ሲል በቅደም የሪዮ ዝግጅት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ አብራርቷል። የብሄራዊ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ስለሺ ብስራት ለሪፖርተር ከሪዮ በማሀበራዊ ድረ ገፅ እንደተናገሩት ከሆነ፣ አባዲ በ አመት እንደተመዘገበና መቶ በመቶ ውድድር ላይ እንደሚሳተፍ ከስፍራው አረጋግጠዋል። የረዥም ርቀት አሰልጣኝ ቶሌራ ዲንቃ አትሌቶቹ ለውድድሩ በቂ ዝግጅት እንዳደረጉ ተናግረው ስለ አባዲ የተነገረው የእድሜ ጉዳይ ፌዴሬሽኑ ከአይኤኤኤፍ ጋር ተነጋግሮ መፍትሄ ላይ እንደደረሰ አስረድተዋል። ኢትዮጵያ ካላት የረዥም ርቀት ውጤት አንፃር በዚህ ወቅት አንደዚህ ያልተጣሩና መፍትሄ የሚሹ ጉዳዮች በመነሳታቸው ብዙዎችን ቅር አሰኝቷል። በተለይ በአስር ሺህ ሜትር ኢትዮጵያ በእንግሊዛዊው ሞፋራህ የተወሰደባትን ብልጫ ስፖርት ቤተሰቡን እንዲሁም የቀድሞ አትሌቶችን ያስቆጨ ክስተት ነበር። በእንደዚህ አይነት ወቅት ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ የሚከተለው መንገድ በተደጋጋሚ ችግር ሲስተዋልበት ይታያል። በተለያዩ አለም አቀፍ ውድድሮች ላይ በቡድን ውስጥ ልምድ ያላቸውን አትሌቶች እንዲሁም ተተኪ አትሌቶችን አጣጥሞ ለውድድር መዘጋጀት ዋነኛ ስራ እንደሆነ ባለሙያዎች በተለያየ አጋጣሚ ሲናገሩ ይደመጣል። ኢትዮጵያ በምታደርጋቸው አለም አቀፍ የአትሌቲክስ ውድድሮች ከእድሜ ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ችግርና መስተጓጎል ሲደርስ ይስተዋላል። በዚህም መሰረት ዘንድሮ ደቡብ አፍሪካ ደርባን ከተማ ላይ በተደረገው የወጣቶች ሻምፒዮና ላይ ትክክለኛ እድሜ ያላቸውን አትሌቶች በቴክኒካል ባለሙያዎች ባለመስተካከሉ አትሌቶች ከኤምባሲ ሳይፈቀድላቸው ቀርቶ አራት አትሌቶች ብቻ ተስተካክሎላቸው ወደ ውድድሩ ማምራታቸው የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። ቀሪዎቹ ተወዳዳሪዎች ግን በሌሎች ተተክተው ወደ ስፍራው ቢያመሩም፣ ዘጠኙ አትሌቶች ደርባን ላይ ባልተለመደ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ታሪክ በዚያው መቅረታቸው ይታወሳል። ለዚህም ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ በአግባቡ አትሌቶችን ለውድድር ያለመ ቅርብ ችግር እንደሆነ ይነገራል። በመጨረሻም ምንም እንኳ ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ የአባዲን ጉዳይ ከአለም አቀፍ የአትሌቲክስ ማሀበር ጋር ተነጋግሬያለሁ ቢልም ልምድ ያላቸው አትሌቶችን በተጠባባቂነት እንኳን ይዞ ባለመጓዝ ቅሬታ ያስነሳ ጉዳይ ሆኗል።
የሴቶችና የወንዶች አስር ሜትር አርብና ቅዳሜ ይካሄዳል
አዲስ አበባ፣ ሰኔ ሁለት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሀድያ ሆሳእና እና አዳማ ከተማ ሶስትለ ሶስት በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል። ጥሩ ፉክክር በታየበት በዚህ ጨዋታ አዳማ ከተማ ሶስት ለ እየመራ ቢቆይም ሀድያ ሆሳእና ነጥብ መጋራት ችሏል። በጨዋታው የአዳማ ከተማን ሁለት ግቦች ዳዋ ሆቴሳ ሲያስቆጥር ቀሪዋን አንድ ግብ አዲስ ተስፋዬ አስቆጥሯል። የሀድያ ሆሳእናን ሁለት ግቦች ደግሞ ባዬ ገዛኸኝ ያስቆጠረ ሲሆን ፥ አንዷን ግብ ሰመረ ሀፍተይ ማስቆጠር ችሏል።
የሀድያ ሆሳእና እና የአዳማ ከተማ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ጥር ሀያ ሰባት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ዳንኤል አራፕ ሞይ ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገለፁ።ፕሬዚዳንቷ ለኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ባስተላለፉት መልእክት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልፀዋል።ዳንኤል አራፕ ሞይ ለኬንያ ነፃነት ያደረጉትን ተጋድሎ ያስታወሱት ፕሬዚዳንቷ፥ በኢጋድ ምስረታ ላይ ጉልህ ስፍራ እንደነበራቸውም አንስተዋል።ፕሬዚዳንት ዳንኤል አራፕ ሞይ ቢያልፉም ለህዝባቸው እና ለአፍሪካ ደህንነት ባደረጉት በጎ ተግባር ሁሌም ይታወሳሉ ብለዋል በመልእክታቸው።ለመላው ኬንያውያን፣ ለኬንያ መንግስት እና ለሟች ቤተሰቦችም መፅናናትን ተመኝተዋል።ዳንኤል አራፕ ሞይ በዘጠና አምስት ከዚህ አለም በሞት የተለዩ ሲሆን፥ ኬንያም ቀብራቸው እስከሚፈፀምበት እለት ድረስ ብሄራዊ የሀዘን ቀን አውጃለች።መረጃው በኬንያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ነው፤ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ለኬንያውያን የሀዘን መግለጫ አስተላለፉ
በአዲስ አበባ የዳቦ እጥረት ተከሰተ ዘሀበሻ በአዲስ አበባ ከተማ ዳቦ በበቂ ሁኔታ እየቀረበ እንዳልሆነ ተገለፀ። የከተማው ነዋሪዎች በየዳቦ ቤቱ ዳቦለመግዛት ሲሄዱ ዳቦ አለመኖሩ እየተነገራቸው በተደጋጋሚ እየተመለሱ መሆኑንና ችግሩም እስካሁን እንዳልተቀረፈሰንደቅ ጋዜጣ በጥቅምት ቀን አመተ ምህረት እትሙ ዘግቧል። እንደጋዜጣው ዘገባ ከሆነ አንዳንድ ዳቦ መሸጫሱቅ የስራ ሀላፊዎችና ባለቤቶች በተገኘው መረጃ መሰረት በዳቦ መሸጫ መንግስት ከተመነው ዋጋ አንፃር ሲታይ አንድን ዳቦ ለገበያ በማቅረብ የሚገኘው የትርፍ መጠን አነስተኛ በመሆኑ ዘርፉ አበረታች አለመሆኑ ተገልፁአል።እጥረቱን በተመለከተ ጋዜጣው ያነጋገራቸው በንግድ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ምክትል ሀላፊአቶ አብዱራህማን ሰይድ የዳቦ ዋጋ ትርፍን በተመለከተ መንግስት ተመኑን ሲያስቀምጥ ያሉትን ወጪዎች ታሳቢአድርጎ መሆኑን ገልፀዋል። የተፈጠረውንም የዳቦ እጥረት በተመለከተ ስንዴ በእህል ንግድ በኩል ተገዝቶሀገር ውስጥ ሲገባ መንገድ ላይበተፈጠረው መዘግየት የተፈጠረ መሆኑን ሀላፊው አመለክተዋል። ያም ሆኖ እህል ንግድ ከመጠባበቂያ ክምችቱበማውጣት ለአዲስ አበባም ሆነ ለክልል የዱቄት ፋብሪካዎች እንደተቀመጠላቸው ኮታ እንዲያከፋፍል መሆኑንም ጨምረውገልፀዋል። መንግስት በሀገሪቱ የተከሰተውን የዋጋ ንረት ለመቆጣጠር በሚል በ አመተ ምህረት በበርካታ የፍጆታሸቀጦች ላይ የዋጋ ተመን ከጣለ በኋላ በስተመጨረሻ የሌሎች ተመን ሲነሳ የስኳር የዘይትና የስንዴ ምርቶችንየማከፋፈል ስራ ሙሉ ለሙሉ በመንግስት ቁጥጥር ስር ውሎ እስከ ዛሬም እንደቀጠለ ነው።ይሁን እስካሁን በስርጭቱረገድ በስኳር ላይ ተደጋጋሚ ችግር እየታየ ሲሆን አሁን ደግሞ በዳቦ ስንዴ ላይ ችግሩ እየተንፀባረቀ መሆኑንሰንደቅ ጋዜጣ ዘግቧል። የመጅሊስ እና የኡለማዎች ምክር ቤት የይፍረሱ ክስ ለሰበር ሰሚ ችሎት እንደሚቀርብ ተገለፀ ዘሀበሻ የኢትዮጵያ እስልምና እና የኡለማዎች ምክር ቤት ይፍረሱ በሚል የቀረበው አቤቱታ ውድቅ ከተደረገ በኋላ በድጋሚለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት እንደሚቀርብ ኢትዮ ምህዳር ጋዜጣ ጥቅምት ቀን አመተ ምህረትባወጣው እትሙ አስነብቧል። የታሰሩት የኢትዮጵያ ሙስሊም ችግሮች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ጠበቃ ተማም አባ ቡልጉ እንደተናገሩት የተጀመረውክስ ለመስከረም ቀን አመተ ምህረት ድጋሚ ያስቀርባል አያስቀርብም የሚለውን ለማየት እንደነበር ተናግረው ጉዳዩ ተብራርቶ በመቅረቡ ለማክሰኞ ጥቅምት ቀን አመተ ምህረት ሰበር ሰሚ ችሎት እንደሚሰየም ጋዜጣውቢዘግብም የማክሰኞ ችሎት ውሎውን በመለከተ ግን ያለው ነገር የለም። እንደጋዜጣው ዘገባ ከሆነ ኡለማዎችምክር ቤት በራሱ በእስልምና ጠቅላይ ጉባኤዎች ስር ያለ በመሆኑ እና የነዚህ የበላይ ደግሞ መጅሊሱ በመሆኑኡለማዎች ምክር ቤት የማስመረጥ መብት የለውም የሚለው የክሱ አንዱ ጭብጥ መሆኑን ጠበቃ ተማም መናገራቸውተዘግቧል። እንደጠበቃ ተማም ገለፃ ኡለማዎች ምክር ቤት ምርጫ ያካሄደው የራሱ የሆነ ህጋዊ ሰውነት ሳይኖረው ነው።ምርጫውን የማካሄድ ስልጣን የኡለማዎች ምክር ቤት ሊሆን አይችልም። ምርጫው አስመራጭ በሌለበት ሁኔታ ሊደረግአይችልም። ለዚህም አዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ የወጣውን ሁሉ በማስረጃነት አቅርበናል በማለት የክሳቸውን ዝርዝርጠቁመዋል። ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከቀረቡ የክስ ፋይሎች መካከል ጅሀዳዊ ሀረካትን በተመለከተ በኢቴቪ የቀረበው ዘጋቢ ፊልምፌደራል ፖሊስ ደህንነት ከፍተኛ ፍርድ ቤትን እና የከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዘዳንት ተከሰው የነበረ ቢሆንምፍርድ ቤቱ የዘጋቸው ፋይሎች በሰበር ችሎቱ በድጋሚ እንደሚቀርቡ ይጠበቃል ሲል ጋዜጣው ዘግቧል። ፖሊስ በቦምብ ፍንዳታ ህይወታቸው ያለፈው ሶማሊያውያን አሸባሪዎች ናቸው ሲል መናገሩ ተጠቆመ ዘሀበሻ ጥቅምት ቀን አመተ ምህረትበአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ሯንዳ ማዞሪያና ቦሌ ሚካኤል መግቢያ አካባቢበቦንብ ፍንዳታ ህይወታቸው ያለፈው ሁለት ሶማሊያውያን ሽብርተኞች መሆናቸውን ማረጋገጡን የፌደራል ፖሊስ የፀረሽብር ግብረ ሀይል ማስታወቁን ሪፖርተር በጥቅምት ቀን አም እትሙ ዘግቧል። የአንድ ግለሰብ ሰርቪስ ቤት ተከራይተው ከነበሩት ሶማሊያውያን መካከል አንደኛው ከ ቀናት በላይ የቆየ ሲሆንሌላኛው ፍንዳታው ከመድረሱ በፊት ከሁለት ሰአታት በፊት የደረሰ መሆኑን ግብረሀይሉ ማረጋገጡን አስረድቷል።ሽርተኛ የተባሉት ሶማሊያውያን ካፈነዱት ቦምብ በተጨማሪ መጠናቸው ያልተገለፀ ቦምቦችና አንድ ሽጉጥ ከሁለት ካርታጥይት ጋር መገኘቱን የፈንጅ ማቀጣጠያና የአደጋ መከላከያ ጃኬቶች የኢትዮጵያ ብሄራዊ እግር ኳስ ቡድንማሊያና ቀበቶዎች መገኘታቸውም ተጠቁሟል። እንደሪፖርተር ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ ከሶማሊያውያኑ ጋር ቀጥታ ግንኙነት አላቸው የተባሉ ተጠርጣሪዎችና የቤቷከራይ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑንም ግብረ ሀይሉ አስታውቋል። የአደጋውን መንስኤናአጠቃላይ ስለነበረው ሁኔታ ፖሊስ መረጃ እያሰባሰበ በመሆኑ ዝርዝ መረጃ ለመስጠት እንደማይችሉ የአዲስ አበባፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ይህደጎ ስዩም ለሪፖርተር የገለፁ ቢሆንም የፌደራል ፖሊስ የፀረ ሽብር ግብረ ሀይልግለሰቦቹ ሽብርተኛ መሆናቸውን ማረጋገጡን አስታውቋል። ከዚህ ጋር በተያያዘ የውስጥ አዋቂ ምንጮች እንደጠቆሙት ከሆነ የፍንዳታው ቅንብር ኢህአዴግ ቀደም ሲል ልክጨዋታው ሲያልቅ በተለይ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሄራዊ ቡድን ካሸነፈ ስታዲየም አካባቢ በማፈንዳት የድርጊቱፈፃሚዎች የትጥቅ ትግል እያደረጉ ያሉ ተቃዋሚዎች እና የሀይማኖት አክራሪዎች ናቸው ለማለት አቅዶት የነበረውንሆን ብሎ ግቡ ሳይሳካ ሲቀር በበሌላ ቦታ ማፈንዳቱን የከዚህ ቀደም የኢህአዴግን ድርጊት እያመሳከሩ ያስታወሷልታጡም ። በተለይም በፍንዳታው አለም አቀፉ ማሀበረሰብ የታሰሩ የህሊና እና የፖለቲካ እስረኞች ላይ መንግስትየወሰደውን እርምጃ እንዲደግፉና እንዲፈጡ የሚጠይቀውን ጫና በመግታት እውቅና ለማግኘት ታቅዶ እንደነበርከኢህአዴግ ውስጥ እየወጡ ያሉ መረጃዎች ጠቁመዋል።
ዛሬ ከወጡ ጋዜጦች የተመረጡ ዜናዎች እነሆ።
ኢትዮጵያና ሱዳን የአረብ ሊግን ውሳኔ ተቃውመዋል በህዳሴው ግድብ ጉዳይ ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብፅ በአምስት ወሳኝ ጉዳዮች ላይ ተደራድረው መግባባት እንደሚጠበቅባቸው የተገለፀ ሲሆን ችግሩን ለመፍታት ከድርድር ውጪ ሌላ አማራጭ እንደሌለ የኢትዮጵያ መንግስት አስታውቋል። እ ኤ አ በሁለት ሺህ በተፈረመው የመርሆ መግለጫ ስምምነት መሰረት፤ ከሰሞኑ አሜሪካና የአለም ባንክ ጣልቃ የገቡበት የድርድር ሂደት መጀመሩን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የህግ አማካሪ አምባሳደር ረታ አለሙ አስረድተዋል። በመርሆ ስምምነቱ አንቀፅ አምስት መሰረት፤ የግድቡ የውሀ ሙሌትን፣ የግድቡን አሰራር ሂደት ወይም የውሀ አለቃቀቅ በሚመለከት ከሁለቱ ሀገራት ጋር ስምምነት ላይ እንደምትደርስ ተደንግጓል ያሉት አምባሳደር ረታ፤ በዚህ መሰረት ወደ ድርድር መገባቱን አውስተዋል። የተጀመረው ድርድርም የህዳሴውን ግድብ አሞላልና አለቃቀቅ የሚመለከት መሆኑን፣ በዚህም አምስት ስምምነት ላይ ሊደረስባቸው የሚገቡ ጉዳዮች ተለይተው ወደ ድርድር መገባቱን አስረድተዋል አምባሳደሩ። እልባት ያላገኙትና በድርድር ሂደት ላይ የሚገኙት አምስቱ ጉዳዮችም የስምምነቱ የተፈፃሚነት ወሰን፣ የአፈፃፀምና የክትትል ስርአቱ እንዲሁም የአሞላልና የውሀ አለቃቀቅ ስርአትን የሚመለከቱ ድንጋጌዎች፣ የመረጃ ልውውጥ ስርአት፣ ክርክር ቢነሳ መፍትሄ የሚሰጥበት አሰራር እንዲሁም አምስተኛው የማጠቃለያ ድንጋጌዎች ናቸው ተብሏል። የተፈፃሚነት ወሰንን በተመለከተ በኢትዮጵያ በኩል የቀረበው የድርድር ሀሳብም፡ አንደኛ ድርድሩ በህዳሴው ግድብ ላይ ብቻ የታጠረ እንዲሆን፣ ሰነዱ የውሀ ክፍፍልን ወይም ድርሻን የማይመለከት መሆኑን እንዲሁም የቀድሞ የቅኝ ግዛት ስምምነቶችን የማይመለከት መሆኑ በግልፅ እንዲቀመጥ በድርድር ሀሳብነት መቅረቡን አምባሳደሩ አስረድተዋል። በውሀ አለቃቀቅና ሙሌት ጉዳይ እንደ ሁኔታው ተለዋዋጭ ሊሆን ስለሚችል በሰነዱ ላይ መጠንን የሚገልፁ ቁጥሮች እንዳይቀመጡ በመጠየቅ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅሟን ሊያስጠብቅ የሚችል ሀሳብ ማቅረቧንና ጉዳዩም ገና በድርድር ሂደት ላይ መሆኑም ተጠቁሟል። የመረጃ ልውውጥን በተመለከተም ኢትዮጵያ የሰጥቶ መቀበል መርህን የመጠቀም ፍለጐት እንዳላት አቋሟን ማሳወቋን፣ ይህም ጉዳይ ገና በሶስቱ ሀገራት መግባባት ያልተደረሰበት መሆኑ ተመልክቷል። በሶስቱ ሀገሮች መካከል ክርክር ቢነሳ የሚፈታበትን መንገድ በተመለከተ ኢትዮጵያ የዲፕሎማሲና ድርድር መንገድን መከተል የሚል ማቅረቧን በግብፅ በኩል ደግሞ የሽምግልና ስርአትና የግድ ውሳኔ የሚሰጥበት አሰራር እንዲኖር ሀሳብ መቅረቡንና ገና በድርድር ሂደት ላይ ያለ ጉዳይ መሆኑም ተገልጿል። በድርድር ላይ ያለው መመሪያዎችንና ደንቦችን የተመለከተው የስምምነት ሰነድ ከአስር አመት በላይ ሊያገለግል የማይችል መሆኑና በሂደት የሚከለስበት አማራጭ እንዲኖር ኢትዮጵያ ተጨማሪ ሀሳብ ማቅረቧንም አምባሳደሩ አስረድተዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ገዱ አንዳርጋቸው በበኩላቸው፤ በቀጣይም በግድቡ ጉዳይ መግባባት ላይ ለመድረስ ብቸኛው አማራጭ ድርድር ብቻ መሆኑን ነገር ግን የሚካሄደው ድርድር የኢትዮጵያን ጥቅም እስካስከበረ ድረስ ብቻ ኢትዮጵያ ተሳትፎዋን እንደምትቀጥል አስታውቀዋል። በዚሁ ጉዳይ የተለያዩ ምሁራን የራሳቸውን ምልከታና ምክረ ሀሳብ እያቀረቡ ሲሆን የኢንሼቲቭ አፍሪካ መስራቹ አቶ ክቡር ገና በፌስ ቡክ ገፃቸው ባቀረቡት ምክረ ሀሳብ፤ ኢትዮጵያ በድርድሩ ውስጥ ለመቆየት የተቻላትን ጥረት ማድረግ እንዳለባትና ጉዳዩ የሶስቱንም ሀገር ጥቅም ባስከበረ መልኩ በመግባባት መቋጨት የሚችልበትን መንገድ መፈለግ እንደሚገባ ጠቁመዋል። በድርድሩ መቆየት የመጀመሪያው አማራጭ ሊሆን ይገባል የሚሉት ሌላው የአባይ ጉዳይ ተንታኙ አቶ ፈቄ አህመድ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ሌሎች ተጨማሪ አሸማጋዮችን ወደ ድርድር ማእቀፉ በመሳብ የአሜሪካንና የአለም ባንክን ጫና መገደብ ይኖርባታል ሲሉ ምክረ ሀሳብ ያቀርባሉ። በተጨማሪም ኢትዮጵያውያንን በሙሉ ከግድቡ ጐን በማሳለፍም፣ ለዲፕሎማሲያዊ ጥረቱ እንደ አጋዥ መሳሪያ መጠቀም ያስፈልጋል፣ መንግስት በዚህ በኩል ጠንካራ የህዝብ ንቅናቄ መፈጠር አለበት ይላሉ አቶ ፈቄ። የፖለቲካ ተንታኙ አቶ ሙሼ ሰሙም ህዝብን ለአንድ አላማ በማሰለፍ ጉዳይ ይስማማሉ። ለሰላምና ለጋራ ጥቅም የሚደራደር ማንነት እንጂ ድፍረት የተሞላበትና ሏላዊነታችንን የሚፃረር ትእዛዝ ለመቀበል ዝግጁ የሆነ ኢትዮጵያዊነት እንደሌለብን በጋራ በመቆም ማስመስከር አለብን የሚሉት አቶ ሙሼ፤ኢትዮጵያም ግድቡን አጠናቃ ውሀ ከመሙላት የሚያግዳት ሀይል እንደሌለ ማሳየት ያስፈልጋል ብለዋል። አንዳንድ የአሜሪካ ባለስልጣናትም ከወዲሁ የአሜሪካ ግምጃ ቤት ጣልቃ ገብነትንና ተፅእኖን መቃወም ጀምረዋል። የአሜሪካ ኮንግረስ አባሉ ስቴቪን ሆርስፎርድ እንዲሁም በኢትዮጵያና በቡርኪናፋሶ የአሜሪካ አምባሳደር የነበሩት ዴቪድ ሺን፤ የአሜሪካ መንግስት በድርድሩ ለግብፅ እያደላ ነው ሲሉ በግልፅ ወቅሰዋል። አሜሪካ ሶስቱን አገራት ለማደራደር ከፈለገች የገለልተኝነት መርህን እንድትከተል፤ ይህን ካደረገች ኢትዮጵያ ወደ ድርድሩ ለመመለስ እንደማትቸገር ኮንግረስማን ሆርስፎርድ ገልፀዋል። በተመሳሳይ አምባሳደር ሼንም አገራቸው በኢትዮጵያ ላይ የምታሳርፈው ጫና ሊታረም ይገባል ብለዋል። ግብፅ በበኩሏ በአባይ ወንዝ ላይ ያላትን ጥቅም ለማስከበር ማንኛውንም አማራጭ እንደምትጠቀም፣ ለዚህም ከጎኗ በርካታ ደጋፊ አገራት እንዳሉ በመግለፅ፣ ኢትዮጵያ በአሜሪካ የቀረበውን የስምምነት ሰነድ እንድትፈርም አስጠንቅቃለች። አያይዞም የአገሪቱ መንግስት የአረብ ሊግ በአባይ ጉዳይ ከግብፅ አቋም ጎን እንዲሰለፍ ከትናንት በስቲያ ጥሪ ያቀረበች ሲሆን የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሚ ሹክሮ ኢትዮጵያ ስምምነቱን እንድትፈርም የአረብ ሊግ ተፅእኖ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።ኢትዮጵያ በሁለት ሺህ የተፈረመውን የመርሆዎች መግለጫ ስምምነትን በመጣስ የግድቡን ስራ በማከናወን ላይ ትገኛለች ስትልም ግብፅ ለአረብ ሊግ ባቀረበችው የድጋፍ ጥያቄ አመልክታለች። የአረብ ሊግም ግብፅ በአባይ ውሀ ላይ ያላትን መብት ኢትዮጵያ እያሳጣቻት ነው በማለት ኢትዮጵያን የሚኮንን ውሳኔ ማሳለፉ የተገለፀ ሲሆን የአረብ ሊግ አባል የሆነችው ሌላኛው አገር ሱዳን በበኩሏ፤ የውሳኔ ሀሳቡ ኢትዮጵያን የሚያስቀይም ከመሆኑም በላይ የአገሯን ብሄራዊ ጥቅም የሚጋፋ መሆኑን በማመልከት ሀሳቡን እንደማትቀበለው አስታውቃለች። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ፤ የአረብ ሊግ በግድቡ ዙሪያ እየተደረገ ያለውን ድርድር ቁልፍ እውነታዎች ሳያገናዝብ በውሳኔ ሀሳቡ የሰጠው ጭፍን ድጋፍ እንዳሳዘነው አመልክቶ ሱዳን ያሳየችውን አቋም አድንቋል። የሊጉ ውሳኔም ተቀባይነት የሌለው ነው ሲል መንግስት ውድቅ አድርጎታል። ይህ ሁሉ የግብፅ ማስጠንቀቂያ፣ ማሳሰቢያና አቤቱታ እያለ ግን የህዳሴው ግድብን አሁንም በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ ግንባታው እየተፋጠነ መሆኑን መንግስት ያስታወቀ ሲሆን ሰባ አንድ በመቶ የግንባታ አፈፃፀም ላይ መድረሱንም ለማወቅ ተችሏል። በቀጣይ ክረምትም አራት ነጥብ ዘጠኝ ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሀ እንደሚገደብ እንዲሁም በመጋቢት ሁለት ሺህ የመጀመሪያ የሙከራ ሀይል ማመንጨት እንደሚጀመርም የውሀ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያና ግብፅ አምስት ጉዳዮች ላይ ተደራድረው መግባባት ይጠበቅባቸዋል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት ሀያ ሶስት፣ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ ባለፉት ሀያ አራት ሰአት ውስጥ ሶስት ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ህይወታቸው ማለፉን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። በሀያ አራት ሰአት ውስጥ በተደረገው ሁለት ሺህ ስምንት መቶ ስላሳ ስድስት የላብራቶሪ ምርመራ አንድ መቶ ዘጠኝ ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል። በዚህም በአጠቃላይ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች አንድሺህ አንድ መቶ ሰባ ሁለት ደርሷል። ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎችም ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ሲሆኑ ዘጠና ዘጠኝኙ ከአዲስ አበባ ፣ ሁለት ሰዎች ከትግራይ ክልል ፣ አምስት ሰዎች ከኦሮሚያ ክልል እና ሶስት ሰዎች ከሀረሪ ክልል ናቸው። ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር ደግሞ ሁለት መቶ ዘጠኝ ደርሷል። ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተገናኘ የሶስት ኢትዮጵያውያን ህይወት አልፏል ፤ አንደኛዋ የሀያ ዘጠኝ አመት በትግራይ ክልል የሰቲት ሁመራ ነዋሪ፣ ሁለተኛ የሰባ አምስት አመት ሴት የአዲስ አበባ ነዋሪ እና ሶስተኛ የሀምሳ አምስት አመት በደቡብ ክልል የከፋ ዞን ነዋሪ በቅርቡ ወደ አዲስ አበባ የመጣ ናቸው። በመሆኑም በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ የተገኘባቸው እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር ደርሷል። የመጀመሪያ ሁለቱ ግለሰቦች በሆስፒታል ውስጥ ህክምና ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን ሶስተኛው ህይወቱ ያለፈና ለአስክሬን ምርመራ ወደ ሆስፒታል የመጣና በተደረገልት ምርምራ የኮሮና ቫይረስ የተገኘበት ነው። የዜና ሰአት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዘናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልእክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ ስምንት ሺህ አንድ መቶ ብለው ይላኩ።
በኢትዮጵያ ባለፉት ሀያ አራት ሰአታት በኮሮና ቫይረስ የሶስት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ አንድ መቶ ዘጠኝ ሰዎች ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል
የኢህአዴግ መስራች አባል የሆኑት ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ህወሀት እና የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ኦህዴድ የተናጠል ግምገማቸውን ከዚህ ሳምንት ጀምሮ እስከቀጣዩ ሳምንት እንደሚያከናውኑ ተጠቆመ። በዚህ ሳምንት ግምገማውን የሚጀምረው የህወሀት ማእከላዊ ኮሚቴ ሲሆን፣ በሚቀጥለው ሳምንት መጀመሪያ ላይ ደግሞ ኦህዴድ ግምገማውን እንደሚጀምር ለማወቅ ተችሏል። ኢህአዴግን ከመሰረቱት ፓርቲዎች መካከል በቀዳሚነት የማእከላዊ ኮሚቴ ስብሰባውን በማካሄድ በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል እንዲሁም በፓርቲው ውስጥ ያሉ ችግሮችን የገመገመው የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝብች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ደኢህዴን መሆኑ ይታወሳል። ከዚህ በመቀጠል የብሄረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ብአዴን ማእከላዊ ኮሚቴ ባለፈው ሳምንት ግምገማውን በማካሄድ በሳምንቱ መጨረሻ ላይ መግለጫ ማውጣቱ አይዘነጋም። በአማራ ክልል በስፋት ለተነሳው ተቃውሞ መንስኤ ናቸው በማለት የክልሉ ገዥ ፓርቲ ካስቀመጣቸው ምክንያቶች መካከል የመንግስትን ስልጣን የህዝብ ጥቅም ማስከበሪያ መሳሪያ በማድረግ ከመንቀሳቀስ ይልቅ፣ የመንግስት ስልጣን የኑሮና የጥቅም መሰረት ሆኗል የሚለው ይገኝበታል። ሌላው ዋነኛ ምክንያት ለህዝብ ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ ያለመስጠት መሆኑ በብአዴን መግለጫ ተጠቅሷል። በእነዚህ ችግሮች የተነሳ ተዳክሞ የነበረው የጠባብነትና የትምክህተኝነት አስተሳሰብና ተግባር ቀስ በቀስ እየሰፋ ሄዶ፣ የአመራሩንና የአባላትን አስተሳሰብ ማዛባቱን መግለጫው ይጠቁማል። ይህ አይነቱ አስተሳሰብ ቀላል ባልሆነ ደረጃ በመስፋፋቱም ህዝባዊና አገራዊ አንድነትን የሚያዳክሙ የተሳሳቱ ተግባራት መከሰታቸውን መረጃዎች አመልክተዋል። ህወሀት በዚህ ሳምንት በሚጀምረው የማእከላዊ ኮሚቴው ግምገማ በትግራይ ክልል የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችን የሚቃኝ ቢሆንም፣ በአንዳንድ የአገሪቱ አካባቢዎች ፀረ ትግራይ አመለካከቶች የመታየታቸው መንስኤና መፍትሄውን በጥልቀት እንደሚወያይ መረጃዎች አመልክተዋል። የአማራ ክልል ተቃውሞ የተቀሰቀሰው ከወልቃይት የማንነት ጥያቄ ጋር ተገናኝቶ በተነሳው የወሰን ለውጥ ጥያቄ ቢሆንም፣ ይህ ጥያቄ በፍጥነት ባለመመለሱ በአጠቃላይ የገዢው ፓርቲን አስተዳደር ሙሉ በሙሉ ወደ መቃወም ተለውጧል። በዚህ ተቃውሞም በአማራ ክልል ውስጥ ቦታዎች የትግራይ ተወላጆች ላይ ትኩረት ያደረገ ጥቃት መሰንዘሩ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለ ማርያም ደሳለኝ እነዚህን ተቃውሞዎች አስመልክቶ የአማራና የትግራይ ክልል ርእሰ መስተዳደሮችና በየደረጃው ያሉ አመራሮች ተጠያቂ እንደሚሆኑ መግለፃቸው ይታወሳል። በቀጣዩ ሳምንት መጀመሪያ ላይ የኦህዴድ ማእከላዊ ኮሚቴ በሚጀምረው ግምገማ ማጠናቀቂያ ላይ፣ ከፍተኛ የሆነ የአመራር ለውጥ እንደሚጠበቅ ምንጮች ለሪፖርተር ገልፀዋል። የፓርቲዎቹ የተናጠል ግምገማ ገዢው ፓርቲ ኢህኢዴግ ለሚያዋቅረው አዲስ ማእከላዊ ኮሚቴና ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የመጀመሪያው እርምጃ እንደሚሆንም ተጠቁሟል። ኢህአዴግ አዲሱን አመት በማስመልከት ባወጣው መግለጫ፣ ኢህአዴግ የህዝብ ሏላዊነትን ጠንቅቆ የሚረዳና ለዚህም የታገለና እየታገለ ያለ ህዝባዊ ድርጅት መሆኑን ገልፆ፣ በመሆኑም ለህዝብ ጥያቄዎች ሁነኛ ምላሽ መስጠት የሚያስችለውን ጥልቅ ተሀድሶ ለማድርግ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን አስታውቋል። ለህዝቡ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ተገቢ የሆነ ምላሽ በመስጠት እርካታውን ለማረጋገጥ በከፍተኛ የሀላፊነት መንፈስና ቁርጠኝነት እንደሚሰራ በአዲሱ አመት ቃሉን በማደስ መሆኑን ገልጿል። ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግና ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ህገ መንግስታዊ ዋስትና ባገኙባት አዲሲቷ ኢትዮጵያ ሰላማዊ ኑሮን በሚያውክ መልኩ ሁከትና ብጥብጥ ማስነሳት ሳያስፈልግ፣ ማንኛውንም ጥያቄ በህጋዊ መንገድ ብቻ በማቅረብና ከዚህ ውጪ ለሚደረጉ ማናቸውም እንቅስቃሴዎች በፅናት በመታገል የአገራችንን ህዳሴ ለማረጋገጥ እጅ ለእጅ ተያይዘን እንድንረባረብ ኢህአዴግ ጥሪውን ያቀርባል፤ ሲል በመግለጫው አስታውቋል።
የህወሀትና የኦህዴድ ማእከላዊ ኮሚቴዎች የተናጠል ግምገማቸውን ሊጀምሩ ነው
አዲስ አበባ፣ ሀምሌ ሀያ ሰባት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በአፍሪካ ህብረት የሚመራውና ለጊዜው ተቋርጦ የነበረው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ዛሬ እንደሚቀጥል የውሀ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ እንደገለፀውም በአፍሪካ ህብረት መሪነት ለ ቀናት ሲካሄድ ቆይቶ ከሁለት ሳምንታት በፊት የተቋረጠው የታላቁ ህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ከሳምንት በፊት ሊቀጥል የነበረ ቢሆንም በሱዳን በኩል በቀረበው ለአንድ ሳምንት የይዘግይልኝ ጥያቄ መሰረት ለአንድ ሳምንት ዘግይቷል። በመሆኑም ተቋርጦ የነበረው ድርድር ዛሬ ከሰአት ጀምሮ ለቀጣይ አንድ ሳምንት እንደሚቀጥል ተገልጿል። የዚህ ሳምንት ድርድር ቀደም ሲል ከተካሄደው የ ቀናቱ ድርድር በኋላ ለመሪዎች በቀረበው ሰነድ መሰረት መሪዎቹ ባስቀመጠጡት አቅጣጫ የሚቀጥል እንደሆነም ታውቋል። ሚኒስቴሩ ኢትዮጵያ እንደ ከዚህ ቀደሙ ፍትሀዊና ምክንያታዊ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረገ ሁኔታ ሁሉንም ወገን ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ ድርድሩን ለመቋጨት ትሰራለች ብሏል። የዜና ሰአት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዘናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልእክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ ስምንት ሺህ አንድ መቶ ብለው ይላኩ።
ተቋርጦ የነበረው የታላቁ ህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ዛሬ ይቀጥላል
አስናቀ ፀጋዬ አዲስ አበባ፡ በሲሚንቶ አቅርቦት ሰንሰለቱ ላይ አሁንም ችግሮች እንደሚታዩ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ። በሀገሪቱ የሚታየውን የሲሚንቶ እጥረት በዘላቂነት ለመቅረፍ የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝም አመለከተ። በንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የብረታ ብረትና ኬሚካል ሚኒስትር ዴኤታ አማካሪ አቶ ዱጋሳ ዶንሳ ለአዲስ ዘመን እንደገለፁት ፣ሚኒስቴሩ ከስድስት ወር በፊት በምርትና በአቅርቦት በኩል የተፈጠረውን የሲሚንቶ እጥረት መንስኤ ለማጥናት በሀገር አቀፍ ደረጃ ኮሚቴ አቋቁሞ ሲሰራ ቆይቷል። በዚህም በሀገሪቱ ያሉ ፋብሪካዎች ለረጅም ጊዜ የሚቆሙ፣ ገሚሶቹም ያረጁና መለዋወጫ የሚፈልጉ፣ የገበያ ፍላጎታቸውም በሶስት ኢንዱስትሪዎች ላይ መሰረት ያደረጉ መሆናቸውንና አብዛኛዎቹ ግንባታዎችም በተመሳሳይ ወቅት መከናወናቸው ችግሩ እንዲጎላ ማድረጉን ለማረጋገጥ መቻሉን ገልፀዋል። የሲሚንቶ ምርት ፍላጎትና አቅርቦት ልዩነት እንደነበር መረጋገጡን አመልክተዋል። የሲሚንቶ ምርት አቅርቦትና ፍላጎት በኩል ያለውን ልዩነት ለማጥበብ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተወሰነ ሲሚንቶ ከውጭ ሀገር እንዲገባ መፍቀዱን ጠቁመው ፣ ከዚህ በፊት ተይዞ የነበረው የሲሚንቶ ኢንቨስትመንትም እንዲለቀቅ መደረጉንም አስታውቀዋል። በአማራ ብሄራዊ ክልል ደጀን አካባቢ የሚገኘው አባይ የሲሚንቶ ፋብሪካ ግንባታ እንዲፋጠንም የሀያ ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ተፈቅዶለት ግንባታው እየተከናወነ እንደሚገኝም ገልፀዋል። ቀደም ሲል የነበረውን የሲሚንቶ የማምረት አቅም ለመጨመርም የመለዋወጫ እቃዎች ከውጭ ሀገር እንዲገቡ ሰማኒያ አምስት ሚሊዮን ብር መመደቡንም ጠቁመዋል። የክረምቱን ወቅት ተከትሎ በሲሚንቶ ፋብሪካዎች ላይ ያጋጠሙ የተፈጥሮ አደጋዎችና በዘርፉ የሰለጠኑ ባለሙያዎች እጥረቶች እንዳሉ ሆነው እነዚህን ስራዎች በመስራት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከሲሚንቶ አምራቾች ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሞ በበጀት አመቱ የሀገሪቱን አጠቃላይ ሲሚንቶ የማምረት አቅም ለማሳደግ ከያዘው ሰማኒያ አምስት በመቶ እቅድ ውስጥ ሰባ ዘጠኝ ያህሉን ማሳካት እንደቻለም ገልፀዋል። በነሀሴ ወር መጨረሻ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሲሚንቶ የመሸጫ መቁረጫ ዋጋ መመሪያ አውጥቶ እንደነበርም አማካሪው አስታውሰው፤ ዋጋው እንደገበያው መሆን እንዳለበት ታምኖ መመሪያው እንዲነሳ መደረጉንም ጠቁመዋል። የዋጋ መመሪያው ከተነሳ በኋላም የሲሚንቶ ዋጋው እንዳልወረደ ነገር ግን መመሪያው እንዳያሻቅብ ማድረጉን የተደረጉ ጥናቶች እንደሚያሳዩ አመልክተዋል። አምና የተመረተውን ስምንት ነጥብ አምስት ሜትሪክ ቶን ሲሚንቶ ወደ ሜትሪክ ቶን በማሳደግ በአቅርቦቱና በፍላጎቱ መካከል ያለውን ክፍተት ለመማጥብ እየተሰራ እንደሚገኝም አማካሪው አስታውቀው፣ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ባስቀመጠው እቅድ መሰረት ባደረገው ጥረት ከዚህ ቀደም በሀይል መቆራረጥ ምክንያት ሲቆም የነበረውን የሲሚንቶ የማምርት አቅም ችግር ሙሉ በሙሉ መፍታቱን አመልክተዋል። ፋብሪካዎች ከውጭ የሚያስገቧቸውን የድንጋይ ከሰል የመሰሉ የኢነርጂ ምንጮችን በሀገር ውስጥ እንዲጠቀሙ ከመአድን ነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስቴር ጋር በመሆን ጥረት መደረጉንም አማካሪው ጠቁመዋል። በዚህም የመሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካን ሳይጨምር በቀን በአማካይ ሁለት መቶ አርባ ሺ ኩንታል ማምረት እንደተቻለም ጠቁመዋል። ሆኖም ምርቱ ከወጣ በኋላ የአቅርቦት ሰንሰለቱ ላይ አሁንም ችግሮች እንደሚታዩ አስታውቀዋል
በሲሚንቶ አቅርቦት ሰንሰለቱ ላይ አሁንም ችግሮች እንደሚታዩ ሚኒስቴሩ አስታወቀ
ኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኘው የሶማሌ ክልል ውስጥ በርካታ አሰቃቂ ድርጊቶች ሲፈፀምበት እንደቆየ የሚነገርለት የጄል ኦጋዴን እስር ቤት ሀላፊ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ። ሀሰን ኢስማኤል ኢብራሂም ሀሰን ዴሬ አብዲ ሞሀመድ ኡመር በቁጥጥር ስር ዋሉ የቀድሞው የእስር ቤቱ ሀላፊ ሀሰን ኢስማኤል ኢብራሂም በቅፅል ስሙ ሀሰን ዴሬ ሶማሊያ ውስጥ በቁጥጥር ስር ውሎ ለኢትዮጵያ ተላልፎ በመሰጠቱ ወደ ጅግጅጋ ተወስዷል። ግለሰቡ ክስ ወደ ተመሰረተበት አዲስ አበባ ሊወሰድ እንደሚችልም ተነግሯል። ምንጮች ለቢቢሲ እንደተናገሩት ግለሰቡ የተያዘው ሶማሊያን ከኢትዮጵያ ጋር በምታዋስነው ጎልደጎብ ተብላ በምትጠራው የድንበር ከተማ ውስጥ ነዋሪዎች ለፀጥታ ሀይሎች በሰጡት ጥቆማ አማካይነት ነው። ግለሰቡ በሶማሌ ክልል ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ እስር ቤቶች ውስጥ በተለይ ደግሞ ጄል ኦጋዴን ተብሎ በሚታወቀው እስር ቤት ውስጥ ተፈፅመዋል በሚባሉ ሰቆቃዎችና የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ውስጥ ዋነኛ ሚና አለው ተብሎ ሲፈለግ ቆይቷል። አቶ ገዱም ሆነ ደመቀ እኛም ብንፈተሽ ግድፈት አለብን ማለታቸውን አስታውሳለሁ የአቶ ታደሰ ጥንቅሹ ባለቤት ሀሰን ኢስማኤል ሀሰን ዴሬ የቀድሞውን የክልሉን ፕሬዝዳንት አብዲ መሀመድ ኦማርን ጨምሮ በሶማሌ ክልል ውስጥ በተፈፀሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ምክንያት ክስ ከተመሰረተባቸው አርባ ያህል ተጠርጣሪዎች መካከል አንዱ እንደሆነም ተነግሯል። ግለሰቡ በቀድሞው የሶማሌ ክልል መስተዳደር ውስጥ በከፍተኛ የደሀነትና የፀጥታ ሀላፊነቶች ላይ በተለያዩ ጊዜያት የሰራ ሲሆን ከእነዚህም መካከል የሶማሌ ክልል የፀጥታ ዘርፍ ሀላፊ፣ የማረሚያ ቤቶች ሀላፊ፣ የጄል ኦጋዴን ሀላፊ እና በክልሉ ልዩ ፖሊስ ውስጥም በኮሎኔልነት አገልግሏል። በሶማሌ ክልል የሚገኙ እስር ቤቶች በተለይ ደግሞ ጄል ኦጋዴን ውስጥ ተይዘው የነበሩ እስረኞች ላይ አሰቃቂ ድርጊቶች ይፈፀሙባቸው እንደነበር የፌደራል መንግስቱና የክልሉ መንግስት ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለ በረከት አናግረውናል የአቶ በረከት ስምኦን ባለቤት በእስር ቤቱ ይገኙ በነበሩ በመቶች በሚቆጠሩ እስረኞች ላይ ይፈፀሙ ከነበሩት ድርጊቶች መካከል ከመሬት በታች ባሉ ጨለማ ጉድጓድ ውስጥ ማስቀመጥ፣ የተለያዩ አይነት ሰቆቃዎች፣ ከአደገኛ የዱር እንስሳት ጋር እስረኞችን ማስቀመጥ፣ አስገድዶ መድፈርና የመሳሰሉ ድርጊቶች እንደነበሩ ተገልጿል።
በሶማሌ ክልል የጄል ኦጋዴን እስር ቤት ሀላፊ ተይዞ ለኢትዮጵያ ተሰጠ
የጣሊያን የፋይናንስ ተቋም የብድር ዋስትና ሰጠ የጣሊያን ግዙፉ ኩባንያ ሳሊኒ ኮንስትራክሽን፣ ጊቤ አራት ሀይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክት እንዲሰጠው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ጋር ሲያካሄድ የቆየው ድርድር ተጠናቀቀ። ሳሊኒ በቅርብ ቀናት ውስጥ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ጋር ስምምነት ይፈራረማል ተብሎ ይጠበቃል። ሳሊኒ ኮንስትራክሽን ኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ የሀይድሮ ኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ያካሄደ በመሆኑ የቴክኒክ ጉዳይ አሳሳቢ እንዳልነበረ ያስታወሱት የሪፖርተር ምንጮች፣ የድርድሩ ማጠንጠኛ ሆኖ የቆየው የፋይናንስ ግኝት ጉዳይ እንደነበር አመልክተዋል። ሳሊኒ ኮንስትራክሽን ለዚህ ፕሮጀክት የሚያስፈልገውን በጀት አንድ ነጥብ አምስት ቢሊዮን ዩሮ የጣሊያን ብድር ዋስትና አገልግሎት ሰጪ ተቋም ዋስትና እንደሚሰጥ መተማመኛ በማቅረቡ፣ በጥር ወር ሁለት ሺህ ስምንት አመተ ምህረት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አዜብ አስናቀና የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር የህግ ክፍል ዳይሬክተር አቶ ዋሲሁን አባተ የተገኙበት ልኡካን ቡድን ጣሊያን ሮም በመጓዝ ውይይት አድርጎ ተመልሷል። ምንጮች እንደገለፁት፣ የልኡካን ቡድኑ ከጣሊያን ብድር ዋስትና አገልግሎት ሰጪ ተቋም ጋር ባደረገው ውይይት ለፕሮጀክቱ ፋይናንስ አቅራቢ ተቋም ዋስትና ለመስጠት ፈቃደኛ መሆኑን አረጋግጧል። በዚሁ ምክንያት የፋይናንስ ጉዳይ መቋጫ አግኝቷል ተብሏል። በዚህ ሳቢያ የፋይናንስና ኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ሚኒስትሩ ዶክተር ደብረ ፅዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው የኤሌክትሪክ ቦርድ በዚህ ሳምንት መጀመርያ ፕሮጀክቱን ያፀድቀዋል ተብሎ ይጠበቃል። እስካሁን ማረጋገጫ ባይገኝም በዚህ ሳምንት ኢትዮጵያን የሚጎበኙት የጣሊያኑ ፕሬዚዳንት ሰርጂዮ ማታሬላ በተገኙበት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይልና በሳሊኒ ኮንስትራክሽን መካከል የግንባታ ውል እንደሚፈረም ተገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለ ማርያም ደሳለኝ ሰሞኑን የመንግስታቸውን የግማሽ አመት ሪፖርት ለህዝብ ተወዮች ምክር ቤት ባቀረቡበት ሰነድ፣ ሁለት ሁለት መቶ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሀይል የማመንጨት አቅም ያለው ፕሮጀክት ግንባታ ለማካሄድ ቅድመ ዝግጅት እንደተጠናቀቀ ገልፀዋል። ፕሮጀክቱ በጥቂት ወራት ውስጥ በይፋ እንደሚጀምር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢገልፁም ፕሮጀክቱ የቱ እንደሆነ ግን ምንም ሳይሉ አልፈዋል። የሪፖርተር ምንጮች እንደገለፁት፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተናገሩት ጊቤ አራት ሀይድሮ ኤሌክትሪክ ሀይል ፕሮጀክትን በሚመለከት ነው። ከማምረት አቅሙ ሲሶ ያህል አምስት መቶ አርባ ሜጋ ዋት ማምረት የጀመረው ጊቤ ሶስት ሀይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ጣቢያ ቀጣይ ክፍል የሆነው ጊቤ አራት፣ በደቡብ ክልል በቱርካና ሀይቅ አቅራቢያ የሚገኝ ፕሮጀክት ነው። ቀድሞ በተካሄደ ጥናት ይህ ፕሮጀክት አንድ አራት መቶ ሀምሳ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሀይል የማመንጨት አቅም ይኖረዋል ቢባልም፣ በተደረገው የዲዛይን ክለሳ የማምረት አቅሙ ወደ ሁለት ሁለት መቶ ሜጋ ዋት ከፍ ማለቱ ታውቋል። ሳሊኒ ኮንስትራክሽን ኩባንያ በሀምሌ ወር ሁለት ሺህ ሰባት አመተ ምህረት ይኼንን ፕሮጀክት ለማጥናት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ጋር የመግቢያ ስምምነት ተፈራርሟል። ነገር ግን በዚሁ ስምምነት ብቻ የግንባታ ውል ሳይፈፀም የአፈር ቆረጣ ስራዎችን በማካሄድ ላይ እንደሚገኝ መዘገባችን ይታወሳል።
የጊቤ አራት ሀይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ግንባታ ድርድር ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ የካቲት ሀያ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በጋምቤላ ክልል የእንቦጭ አረም በውሀ አካላት ላይ እያደረሰ ያለውን ጉዳት ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩን የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ። የዩኒቨርሲቲው ማሀበረሰብ አባላት በጋምቤላ ክልል ጎግ ወረዳ በሚገኘው የታታ ሀይቅ ላይ የእንቦጭ አረም የማስወገድ ዘመቻ አካሂዷል። የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ጋልዋክ ጋርኮት እንዳሉት በክልሉ በሚገኙ የውሀ አካላት ላይ የእንቦጭ አረም እያደረሰ ያለውን ጉዳት ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት በጉልበትና በምርምር ለማገዝ ዩኒቨርሲቲው እየሰራ ነው። በሀይቆች፣ ወንዞች እና ኩሬዎች ላይ አረሙ የሚያደርሰውን ጉዳት በጥናት በመለየት ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት እንደሚሰራም ነው ገልፀዋል። የዩኒቨርሲቲው የጥናትና ምርምር ዳይሬክተር ዶክተር ቾል ኬት በበኩላቸው አረሙን ለማስወገድ የሚያግዙ ቴክኖሎጂዎችን በምርምር ለማፍለቅ እንደሚሰራ ጠቁመው ከተያዘው በጀት አመት ጀምሮ የእንቦጭ አረም ላይ ምርምር ለማካሄድ ተግባራዊ ስራ ተጀምሯል ብለዋል። መምህራንን በማሳተፍ ጭምር እንቦጭ አረም ላይ በሚካሄደው ምርምር ተመራቂ ተማሪዎችም ጥናታቸውን በእንቦጭ ላይ እንዲሰሩ እየተደረ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። የጎግ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኡጁሉ ጎራ እንቦጭ አረም በታታ ሀይቅ ላይ ባደረሰው ጉዳት ምክንያት የሀይቁ መጠነ ስፋት ከአራት መቶ ሀምሳ ሰባት ሄክታር ወደ ሁለት መቶ ሀምሳ አንድ ሄክታር ዝቅ ማለቱን አብራርተዋል። ሀይቁን ከመጥፋት ለመታደግ የመከላከል ስራው ውጤታማ እንዲሆን የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ትብብር ይጠይቃል ማለታቸውን ማለታቸውን ከጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ ድረ ገፅ፦ ፌስቡክ፡ ዩትዩብ፦ ቴሌግራም፦ ትዊተር፦ በመወዳጀት ይከታተሉን። ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
ዩኒቨርሲቲው የእንቦጭ አረም እያደረሰ ያለውን ጉዳት ለመከላከል እየሰራ ነው
ፀጋዬ አራርሳፀጋዬ አራርሳ በኢሊባቡር በተፈፀመው ዘግናኝ ዘር ተኮር ግድያ ጀርባ ያለውን እውነት እንድንመረምር ፍንጭ ሰጥቶናል።እንዲህም ብሏልኦነግ እኛ ከኦህዴድ ጋር ያደረግነውን የስልጣን ክፍፍል ስምምነት ኦነግ በቅናት አይን እየተመለከተው ነው። የተቃውሞ ሰልፉንም የጠራው የኦነግ ክንፍ የሆነው ነው ሲል ይፈርጃል።ጥቅምት በ ላይ እኦህዴድ ኦነግን ለመደምሰስ ከህወሀት ጋር ሰርቷል።በ ኦነግ ኦህዴድን ለማጥፋት ከህወሀት ጋር ወግኗል።ወዳጅ ጠላት ጠላትም ወዳጅ እየሆነ ነውይለናል።ጥቅምት ኦነግ የህወሀት አጋር ኦህዴድም የኦሮሞ አክቲቪስቶች ስልጣን ተጋሪና ተባባሪ ነው ከተባልን ጉዳዩ ወደ ኤሊባቡር ንፁሀን አማሮች ጭፍጨፋ ላይ የማን እጅ እንዳለበት ሁለት ምክንያታዊ ግምቶችን እንድናጤን ግድ ይለናል። ሰልፉን የጠራውና ያደራጀው ኦነግ ነው። ግድያው የተፈፀመው በዚህ ሰልፍ ባለበት አካባቢ ነው። ኦነግ ከህወሀት ጋር ወግኗልከተባልን ግድያውን ሊያቀነባብሩት የሚችሉት ኦነግና ህወሀት በጋራ ነው ማለት ነው። እነ ፀጋዬ አርአርሳና አክቲቪስቶች በኦነግ የተጠራውን ሰልፍ እንደማይደግፉት በመግለፅ ከኦህዴድ ጋር ያደረጉት የስልጣን ክፍፍል ስምምነት ካለ ኦነግና ህወሀት በአንድ ጎራ ኦህዴድና አክቲቪስቶቹ በሌላ ጎራ ሆነው የኦሮሞ ወገኖችን ድጋፍ ለማግኘት እየተናጩ ነው ማለት ነው።ስለዚህ የኤሊባቡር ንፁሀን አማሮች ጭፍጨፋ የተከናወነው በዚህ የስልጣን ሽኩቻ መሀል በመሆኑሀ አንድም ኦነግና ህወሀት ከእጃቸው የወጣውን ተቀባይነት ለመመለስ ሲሉ በጋራ ማለትም ከዚህ በፊት በአርባጉጉ አማሮች ላይ በጋራ እንዳደረጉት ጭፍጨፋወይምለ ኦህዴድና አክቲቪስቶቹ የኦነግና የህወሀትን ጥምረት ሚዛን ለማሳጣትና እቅዳቸውን ለማክሸፍ በሚስጥር እጃቸውን ከተዋል እርምጃውን ወስዷል ማለት ነው።ሁሉም ግምቶች ወደዚህ ያመራሉ። ለማንኛውም ሁሉም ክስተት እነዚህ አራት ተዋናይ ሀይሎች ያራግቡ የነበረውና እያራገቡም ያለው የጎሳ ፖለቲካና ጥላቻ መራር ውጤት ነው። በበደኖ ጉራፈርዳ ወዘተ የታየም ነው። ለዚህ ነው እነዚህ ሀይሎች አንድም አራትም ናቸው ማለት የምንደፍረው።
ከኤሊባቡር ንፁሀን አማሮች ጭፍጨፋ በስተጀርባ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ከምታከብራቸው ታላላቅ ሀይማኖታዊ በአላት መካከል አንዱ የሆነው የደመራ በአል በዛሬው እለት በመላ አገሪቱ ተከብሮአል። የደመራ በአል ንግስት ኢሌኒ እየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበትን መስቀል ለመፈለግ የተጠቀመችበትን ደመራ እና የእጣን ጭስ ለመዘከር የሚደረግ ሀይማኖታዊ በአል ነው። የቤተክርስቲያኗ መፅሀፍት እንደሚያመለክቱት ግማደ መስቀሉ በአፄ ዳዊትና በልጃቸው ባአፄ ዘርአያቆብ በአስራ አምስተኛም ምእተ አመት መግቢያ ላይ ወደ ኢትዮጵያ ገብቷል። በአዲስ አበባ ዛሬ በተከበረው የደመራ በአል ላይ በርካታ ጎብኝዎች ስርአቱን ተከታትለውታል። የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንም በቀጥታ ስርጭቱ አንድ ጊዜ የአቶ መለስ ዜናዊን ፎቶ ግራፍ ሌላ ጊዜ የበአሉን ስነስርአት እያፈራረቀ ለህዝብ አቅርቧል።
የደመራ በአል በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ዘንድ ተከበረ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን በማረሚያ ቤቶች ለመከላከል ይቻል ዘንድ አራት ሺህ የህግ ታራሚዎች በይቅርታ እንደሚለቀቁ አስታወቀ። የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በጉዳዩ ላይ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እነዚህ ታራሚዎች በይቅርታ እንዲለቀቁ የይቅርታ ቦርድ ለሪፐብሊኩ ፕሬዚዳንት አቅርቦ ማስፀደቁን አስታውቀዋል። የሚለቀቁት የህግ ታራሚዎች በቀላል ወንጀል እስከ ሶስት አመት ድረስ ተፈርዶባቸው በማረሚያ ቤት ውስጥ የሚገኙ፣ በማረሚያ ቤት ቆይተው የአመክሮ ጊዜያቸው እስከ አንድ አመት የሚቀረው፣ በግድያ ወንጀል ያልተሳተፉ የሚያጠቡ እናቶች፣ ነብሰ ጡሮች እና የውጭ ሀገር ዜጎች መካተታቸውን ነው ያመለከቱት። በይቅርታ የሚለቀቁ የውጭ ሀገራት ዜጎችም ወደየሀገራቸው እንደሚላኩ ገልፀዋል። በተጨማሪም የሚያጠቡ እናቶች ሆነው በእስር ላይ የሚገኙ ሰባት ሴቶች እና በሙስና ወንጀል በተባባሪነት የተሳተፉ ሴቶችም አሁን ካለው ችግር አንፃር ክሳቸው እንዲቋረጥ መደረጉን ጠቁመዋል። እነዚህ ዜጎች ከማረሚያ ቤት ሲወጡ ተገቢው ምርመራ እንደሚደረግላቸው፣ በቫይረሱ ተጠርጣሪዎች ካሉ ወደ ለይቶ ማቆያ እንደሚሄዱ፣ ከህብረተሰቡ ጋር ሲቀላቀሉም ከወንጀል እንዲጠበቁ ዝርዝራቸው በየአካባቢው ለፖሊስ እንደሚሰጥ እና ህግ ተላልፈው ከተገኙ ይቅርታቸው ተሰርዞ በህግ እንደሚጠየቁ ወይዘሮ አዳነች ተናግረዋል። በሀይለየሱስ መኮንን ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን በማረሚያ ቤቶች ለመከላከል አራት ሺህ የህግ ታራሚዎች በይቅርታ እንደሚለቀቁ አስታወቀ
ግንቦት ፲፬ አስራ አራት ቀን ፳፻፮ አመተ ምህረት ኢሳት ዜና ከትናንት በስቲያ ከመደበኛ የስራ ሰአት ውጭ ከጧቱ አንድ ሰአት ተኩል ላይ ወደ ቢሮአቸው በመግባት ራሳቸውን ከሁለትኛ ፎቅ ወርውረው የገደሉት የስልሳ ሁለት አመቱ ዲፕሎማት አቶ ፍሰሀ ተስፉ ስለ አሟሟታቸው መንስኤ መንግስት እስካሁን ይፋዊ መግለጫ አልሰጠም። ክሮናካ ዲ ሮማ የተባለው የጣሊያን ጋዜጣ ዛሬ ይዞት በወጣው ሰፊ ዘገባ ዲፕሎማቱ ከመሞታቸው ከሁለት ቀናት በፊት ከስራ ተነስተው ወደ አገራቸው እንደሚመለሱ ተነግሮዋቸው እንደነበር አንዳንድ ጓደኞቻቸውን ጠቅሶ ዘግቧል። ሌሎች የስራ ባልደረቦቻቸው ግን ዲፕሎማቱ ወደ አዲስ አበባ እንዲመለስ ስለመታዘዙ እንደማያውቁ ተናግረዋል። ጋዜጣው እንደዘገበው ዲፐሎማቱ ራሱን ያጥፋ ወይም ሌላ ሰው ይግደለው እንደማይታወቅ ገልፆ፣ ራሱን ካጠፋ ግን አንድ መልእክት ለማስተላለፍ አስቦ ያደረገው ሊሆን እንደሚችል የፖሊስ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል። በዲፕሎማቱ ቢሮ ውስጥ ምንም አይነት ማስታወሻ አለመገኘቱን፣ የተዘበራረቀ ነገር አለመኖሩንም የገለፀው ጋዜጣው፣ የረጅም ጊዜ ዝግጅት የተደረገበት ነበር ብሎ ለመናገር እንደማይቻልም አትቷል። ፖሊስ ኢምባሲውን በመዝጋት ካለፉት ሁለት ቀናት ጀምሮ ምርመራ በሰራተኞች ላይ እያደረገ ይገኛል። ዲፕሎማቱን ያገኙት የኢምባሲው ሰራተኞች ሲሆኑ ከሞተ ከአንድ ሰአት በኋላ አምቡላንስ በቦታው ቢደርስም የዲፕሎማቱን ህይወት ለማትረፍ እንዳልተቻለ ታውቋል። አንዳንድ ጣሊያን ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ግለሰቡ ራሱን አጥፍቷል ብለው እንደማያምኑ እየተናገሩ ነው። አቶ ፍስሀ ወደ ኢጣሊያ ከመዛወራቸው በፊት በአውሮፓ ህብረት ዴስክ ኦፊሰር ሆነው ከሰሩ በኋላ፣ የአለማቀፍ ተቋማት ጊዜያዊ ዳይሬክተር እንዲሁም የዲያስፖራ ክፍል ዳይሬክተር ጄኔራል ሆነው ሰርተዋል። አቶ ፍስሀ የህወሀት አባል መሆናቸውን አንዳንድ ወገኖች ይገልፃሉ።
በጣሊያን ራሳቸውን እንዳጠፉ የተነገረላቸው ኢትዮጵያዊው ዲፕሎማት አሟሟት መንስኤ በውል አልታወቀም
አማርኛ ተናጋሪዎችን የማመናመን የማደህየት የማራቆትና ክልላቸውን እያሳነሱ የማጥፋት እቅድ በህወሀት መርሀግብር ውስጥ የተካተተ ዋና ተግባር እንደሆነ ተገለፀ። አማርኛ ቋንቋንም ማሽመድመድ የዚሁ እቅድ አካል መሆኑ ተዘግቧል።አቶ ገመድህን አርአያ ከኢሳት ሬዲዮ ጋር ባካሄዱት ቃለ ምልልስ በህወሀት ፕሮግራም ገፅ አካባቢ አማራ የትግራይና የኤርትራ ህዝብ ጠላት እንደሆነ ተመልክቷል ብለዋል። አያይዘውም አማራ ማጥፋት የቅስቀሳው ዋና መሳሪያ ቢሆንም የትግራይ ህዝብ አልተቀበለም ብለዋል። ቅስቀሳውን አንቀበልም ያሉ የትግራይ ሸዋ ተብለው መገደላቸውን ይፋ አድርገዋል።በተለይ የድርጊቱ ዋና አስተባባሪ በማለት የጠቀሷቸው አቶ መለስ ዜናዊ አቶ ስብሀት አቶ ስዩም መስፍን አቶ አባይ ፀሀዬን የጠቀሱት አቶ ገመድህን በ በሰሜን ጎንደር የዘር ማጥፋት ወንጀል መፈፀሙን አጋልጠዋል። በወቅቱ የተካሄደው ጭፍጨፋ ከፍተኛ የዘር ማጥፋት ወንጀል እንደሆነም አመልክተዋል። በሰላም እጃቸውን የሚሰጡ ወታደሮች እንኳ አማርኛ የሚናገሩ ከሆነ ይረሸኑ ነበር ሲሉ እነ መለስ ያለቸውን በዘር ላይ የተመሰረተ ቆሻሻ አመለካከት አጋልጠዋል።ኢትዮጵያ የምትበተነው አማራ ሲጠፋ ነው በሚለው የነመለስ ሀሳብ መተግበር የጀመረው ህወሀት አዲስ አበባ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ መሆኑንን ያወሱት አቶ ገመድህን ህወሀት ያሰማራቸው ከሺህ በላይ ካድሬዎች ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ አማራዎች በተለያዩ ምክንያቶች እንዲጨፈጨፉ ማድረጋቸውን አመልክተዋል።ብአዴንን አማራን ለማጥፋት የተፈጠረ ፀረ አማራ ድርጀት ሲሉ የሰየሙት አቶ ገመድህን አመራሮቹ የኤርትራና የትግራይ ተወላጆች መሆናቸውን በርግጠኛነት ተናግረዋል። የትግራይ ህዝብ የተወከለው በባንዳ ልጆችና የኤርትራ ተወላጆች ነው ሲሉም ህዝቡ አደጋ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ አባይ ወልዱን የባሻ ወልዱ ልጅ ነው በማለት የትግራይ ህዝብ በባንዳ ኤርትራዊ ልጅ እንደሚመራ ያመለከቱት አቶ ገመድህን ብርሀነ ገብረክርስቶስ ቴድሮስ ሀጎስ ቴድሮስ አድሀኖም በማለት በመዘርዘር የባንዳ ልጆች መሆናቸውን ይፋ አድርገዋል።አማራው የሚኖርበትን መሬት በመውሰድ መሬቱን ያጠቡበታል ከሌላው ክልል በማባረር የሚኖርበትን ክልል ያጠቡታል ያሉት አቶ ገመድህን ይህ የሚደረገው ከመጀመሪያው እንዲጠፋ የተወሰነበትን ህዝብ አጥብቦ በማፈን በችግር ለመግረፍና ለመቆጣጠር ተብሎ እንደሆነ ገልፀዋል።ዘር የማጥራት የህወሀት የቀደመ ድርጅታዊ መዋቅር እንደሆነ በማመልከት መለስን የጠቀሱት አቶ ገመድህን አማራውን ዝም ካልነው አያስቀምጠንም የሚለው የመለስ መፈክር አካል የሆነው የቤኒሻንጉል ክልል ርምጃ የህወሀት ቤት ስራ እንደሆነ አረጋግጠዋል። አማራውን ፋታ ማሳጣት ማንገላታት ስነልቦናውን መግፈፍ ህወሀት በፕሮግራም ደረጃ የያዘው እቅድ ስለሆነ ወደፊትም እንደሚቀጥል አቶ ገመድህን ተናግረዋል።ሞት መፍራት አያስፈልግም። የተቀደሰ ሞት መሞት ክብር ነው ሲሉ በቃለ ምልልሳቸው መጨረሻ የተናገሩት የቀድሞው የህወሀት የፋይናንስ ሀላፊ ህዝቡ ተባብሮ ህወሀትን ማስወገድ ካልቻለ ማፈናቀሉና መሰደዱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስጠንቅቀዋል።ማሳሰቢያ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገፅ ጋዜጣ ላይ የሚወጡት ፅሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገፅ ጋዜጣንብረት ናቸው። ይህንን ፅሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ፅሁፍ አስፈንጣሪ ወይም የድረገፃችንን አድራሻ አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሰራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።
አማራንና አማርኛን ማጥፋት የህወሀት ፕሮግራም ነው
የአገሪቱ ባለሙያዎችና ድርጅቶች እስከ ሀምሌ ይመዝገቡ ተባለበፌደራል ዋና ኦዲተር ጄነራል በብሄራዊ ባንክና በሌሎችም ተቋማት ለሂሳብ ባለሙያዎችና ለኦዲተሮች የሙያ ፈቃድ የብቃት ማረጋገጫና መሰል የእውቅና አሰጣጥ ስርአት በመሻር ለአዲሱ የኢትዮጵያ የሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ የሰጠው አዋጅና እሱን ተከትሎ የወጣው ደንብ መተግበር ጀመረ። ለአዲሱ ቦርድ የቦርድ አባላትና የስራ ሀላፊዎች ተሹመውለታል።የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ አለማየሁ ጉጆ ለሪፖርተር እንዳስታወቁት ቦርዱ ለብቻው ተለይቶ በሂሳብ ሙያና በኦዲት አሰራር ላይ የበላይ አካል ሆኖ እንዲሰራ የተቋቋመው የህዝብ ጥቅም ባለባቸው በመንግስት የልማትና በግል ድርጅቶች ላይ ተፈፃሚነት ያለው አንድ ወጥ የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ እንዲኖር ለማስቻል ነው። በመሆኑም በመላ አገሪቱ አንድ ወጥ የፋይናንስ ሪፖርት ስርአት የሚዘረጋ ሲሆን የፋይናንስ ስርአቱም አለም አቀፍ የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ ደረጃዎችን እንዲከተል ለማድረግ ቦርዱ መመስረቱን አቶ አለማየሁ ገልፀዋል።መንግስታዊ የልማት ድርጅቶችና የግል እንዲሁም የውጭ ድርጅቶች ከዚህ ቀደም በተለያየ መለኪያ የሚለኩበት የሂሳብ አያያዝና ሪፖርት አቀራረብ ስርአት ከእንግዲህ አይኖርም ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው በሌሎች አገሮችም እንደሚደረገው የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብን የሚመራ ራሱን የቻለ ተቋም መመስረት ወደፊት ሊያጋጥሙ የሚችሉ የኢኮኖሚ ቀውሶችን ለመቀነስ እንዲቻልም የሚረዳ ነው ብለዋል።አዲሱ ቦርድ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ያሉት ሲሆን አባላቱ ከመንግስት መስሪያ ቤቶች ከግሉ ዘርፍ ከሂሳብና ኦዲት ባለሙያዎችና ለሙያው ቅርበት ካላቸው አካላት የተወጣጡ አባላት መሆናቸው ሲታወቅ የኢትዮጵያ ሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድን በዋና ስራ አስፈፃሚነት የሚመራ ግለሰብ በዳይሬክተርነት ከመቅጠሩም ባሻገር ባለሙያዎችን እያካተተ እንደሚገኝ አቶ አለማየሁ ጠቅሰዋል።ከዚህ ቀደም በፌደራል ዋናው ኦዲተር ጄነራል ማቋቋሚያ አዋጅ መሰረት ለሂሳብ ባለሙያዎችና ኦዲተሮች ፈቃድ የመስጠትና የማደስ ስልጣን ተሰጥቶት የነበረ ሲሆን ቦርዱን ለማቋቋም በወጣው የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ አዋጅ ቁጥር መሰረት መሻሩን አቶ አለማየሁ አብራርተዋል። ከዚህ ባሻገር በኢትዮጵያ ንግድ ህግ በመንግስት ልማት ድርጅቶች በምርት ገበያ ባለስልጣን ማቋቋሚያ አዋጅ በኤክሳይስ ታክስ አዋጅ በገቢ ግብር አዋጅ በባንክ ስራዎች አዋጅ በመንድን ስራ አዋጅ እንዲሁም በክፍያ ስርአት አዋጅ ውስጥ ስለ ሂሳብ አያያዝና ኦዲት የተደነገጉ አንቀፆች መሻራቸው ታውቋል።የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ አዋጅን የኢትዮጵያ ሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድን አሰራርና አላማዎች ለማስረዳት መጋቢት ቀን አመተ ምህረት በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የተጠራ የውይይት መድረክ ተካሂዷል። የሚመለከታቸው የፌደራልና የክልል መስሪያ ቤቶች ተሳትፈዋል። ጥያቄዎችንም ለሚኒስትር ዴኤታውና ለባልደረቦቻቸው አቅርበዋል። ከተነሱት ጥያቄዎች መካከልም በአዋጁ የመንግስት መስሪያ ቤቶችን ጥቃቅንና አነስተኛ ድርጅቶችን አይመለከትም መባሉ በምን አግባብ እንደሆነ ተሳታፊዎች ጠይቀዋል። ከዋናው ኦዲተር ጄነራል በመውሰድ የክልል ኦዲተር ጄነራሎች ለባለሙያዎች ፈቃድና እድሳት እየሰጡ እንደሚገኙ በመጥቀስ እጣ ፈንታቸው ምን እንደሚሆን ጠይቀዋል።አቶ አለማየሁ በምላሻቸው እንደገለፁት ቦርዱ በተማከለ አሰራር እየተንቀሳቀሰ በክልሎች ቅርንጫፎችን እንደሚከፍትና በመላው አገሪቱ ከአሁኑ በኋላ ከቦርዱ በስተቀር የሙያ ፈቃድ የመስጠትና የማደስ ስልጣን ሌሎች የክልል መስሪያ ቤቶች እንደማይኖራቸው አረጋግጠዋል። ቀደም ሲል ክልሎች በነበሯቸው ህጎች መሰረት ለኦዲተሮችና ለፋይናንስ ሪፖርት አቅራቢዎች ፈቃድ መስጠታቸውን ያቆማሉ። ህጎቻቸውንም ማሻሻል ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።የመንግስት መስሪያ ቤቶች ከዚህ ቀደም በነበራቸው የኦዲትና የሂሳብ አዘገጃጀትና አቀራረብ ስርአት መሰረት ይቀጥላሉ ስለመባሉ ምክንያትአዊነት ያስረዱት ሚኒስትር ዴኤታው ይህ የተደረገው ከሌሎች አገሮች ልምድ ተወስዶ ነው በማለት ምላሽ ሰጥተዋል።በመሆኑም የሚኒስትሮች ምክር ቤት አዲሱን ቦርድ ለማቋቋም ጥር ቀን አመተ ምህረት ባወጣው ደንብ ቁጥር መሰረት በስራ ላይ ያሉ የኦዲት ድርጅቶችና ኦዲተሮች የሂሳብ ባለሙያዎችና የፋይናንስ ሪፖርት አቅራቢዎች እስከ መጪው ሀምሌ ቀን አመተ ምህረት ማመልከቻቸውን ለቦርዱ በማቅረብ መመዝገብና ፈቃድ የማግኘት ግዴታ ተጥሎባቸዋል። በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ማመልከቻ ያላቀረቡ ፈቃድ አያገኙም ተብሏል። ከዚህ ባሻገር አዲስ ፈቃድ መስጠት እንደቆመና ለነባር ባለሙያዎችና ድርጅቶች በትምህርትና ስልጠና ላይ ለሚገኙትም ጭምር በቦርዱ የሚቀመጡ መስፈርቶችን ማሟላት የማይችሉ ከሆነ ግን እስከ አምስት አመት የሚቆይ የእፎይታ ጊዜ መሰጠቱንና በዚያ ጊዜ ውስጥ የአገሪቱ የሂሳብ ባለሙያዎችና ድርጅቶች መስፈርቶችን አሟልተው መገኘት እንደሚገባቸው ተመልክቷል።
የሂሳብ ባለሙያዎችና ኦዲተሮችን የሚቆጣጠር አዲስ ቦርድ ተቋቋመ
ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ በስግብግቡ ጁንታ የህወሀት ሀይል ላይ የተደረገው የመጀመሪያው ዙር ዘመቻ በስኬት መጠናቀቁን አስታወቁ።ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት መግለጫ፤ የአየር ሀይል በወሰደው እርምጃ በተለያዩ ስፍራዎች ላይ የነበሩ ሮኬቶችን ጨምሮ ሌሎች የተለያዩ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን ሙሉ በሙሉ ማውደም መቻሉን ገልፀዋል።ሮኬቶቹ እስከ ሶስት መቶ ኪሎ ሜትር መወንጨፍ የሚችሉ በመሆናቸውና በወንጀለኛው ቡድን ሮኬቶቹን የመጠቀም ፍላጎት በመኖሩ በመቐለና አካባቢዋ በነበረው የከባድ መሳሪያ ማስቀመጫ ላይ የአየር ሀይሉ እርምጃ እንዲወስድ መደረጉ ተገልጿል።ከህወሀት ጋር ከእንግዲህ ድርድር እንደማይኖርና ጉዳዩ ፌደራል መንግስት በሚወስደው ህግን የማስከበር እርምጃ ብቻ ይፈታል የተባለ ሲሆን መከላከያ ሰራዊት ሰላማዊ ዜጐች በማይጐዱበት ሁኔታ ተልእኮውን በጥንቃቄ ይወጣል ተብሏል። በመከላከያ ሰራዊት እየተወሰደ ያለው እርምጃ ግልፅ፣ የተወሰነና ሊደረስበት የሚችል አላማ ያለው መሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትርኒስትሩ ትናንት በትዊተር ገፃቸው ያመለከቱ ሲሆን እርምጃውም በሀገሪቱ ህግና ስርአትን ለማስፈን ያለመ ነው ብለዋል። መንግስት ወደ ሀይል እርምጃ ከመግባቱ በፊት ከህወሀት ጋር ያለውን ልዩነት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ለወራት ታግሶ ድርድርና ሽምግልና ሲያካሂድ መቆየቱን የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትርኒስትሩ፤ ይሁን እንጂ መንግስት ያደረገው ጥረት በሙሉ በህወሀት እምቢተኝነት መክሸፉንም ገልፀዋል። የመንግስት ወቅታዊ አቋም ይፋ ያደረገው የመንግስት መግለጫ በበኩሉ ህወሀት ድብቅ ሴራ ሲያራምድ ቆይቷል፤ አሁንም እያደረገው ነው፤ ከአንድነት ይልቅ የብተና ፖለቲካ በማራመድ ህዝብን እርስ በእርስ በማጋጨት ለሞትና መፈናቀል ዳርጓል ይላል። ከለውጡ ማግስት ጀምሮም ይህን እኩይ አላማ ይዞ መንግስትን በተለያዩ ጉዳዮች ውጥረት ውስጥ በመክተት ወደ ኋላ ለመጐተት ያለማቋረጥ ትንኮሳ ሲፈፀም መቆየቱንም መግለጫው ያትታል። የፌደራል መንግስት በእነዚህ ጊዜያት ሁሉ በሆደ ሰፊነት ነገሮችን ለማለፍ መሞከሩን፣ ለእርቅና ለሰላም ጥሪ ሲያቀርብ መቆየቱን፣ በተለያዩ አካላትም የሰላም ጥሪ በተደጋጋሚ መቅረቡን፤ ነገር ግን እነዚህን ሁሉ ህወሀት ሳይቀበላቸው መቅረቱም ተመልክቷል። ይባስ ብሎ በህገ ወጥ መንገድ ምርጫ ማካሄዱን፣ ከዚህም አልፎ የሀገሪቱ ኩራት የሆነው መከላከያ ሰራዊት ላይ ተኩስ በመክፈት፣ የሀገር ሏላዊነትና ክብርን መዳፈሩን የጠቆመው መግለጫው፤ የህወሀት ቡድን በተለያዩ እኩይ ድርጊቶቹ ሀገሪቱን በግልፅ ለማፈራረስ መንቀሳቀሱን ያመለክታል። ከእንግዲህ በኋላ ግን ይህ ሀገርን የማፍረስ እንቅስቃሴ አይፈቀድለትም ያለው መንግስት፤ አስፈላጊው ሁሉ እርምጃ እስከመጨረሻው ተወስዶ የህግ የበላይነት እንደሚከበር ነው በአቋም መግለጫሙ ያስገነዘበው።በህወሀት ቡድን ላይ የሚደረገው የህግ የበላይነትን የማስከበር ተልእኮ ያለ ምንም ድርድር እንደሚከናወን የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትርኒስትሩ በበኩላቸው፤ ሀሙስ እለት የተለያዩ የዲፕሎማቲክ አካላት ለድርድር እንዲቀመጡ ያቀረቡትን ጥያቄ ውድቅ ማድረጋቸውንም ሲኤንኤን ዘግቧል።የህወሀት ቡድን በሰሜን እዝ ላይ የፈፀመው ክህደትና ወረራ በብቃት መመከቱን የገለፁት የመከላከያ ሰራዊት ምክትልኢታማዦር ሹም ጀነራል ብርሀኑ ጁላ በበኩላቸው፤ ሀገራችን ያላሰበችው ጦርነት ውስጥ ገብታለች፣ ጦርነቱ አሳፋሪና አላማ የሌለው ነው ብለዋል። መከላከያ ሰራዊቱ ተልእኮውን ሰላማዊ ዜጐች በማይጐዱበት ሁኔታ በጥንቃቄ ያከናውናል ያሉት ጀነራል ብርሀኑ ጁላ፤ የትግራይ ወጣቶች በዚህ ጦርነት እንዳይሳተፉ ለሀገራቸው ኢትዮጵያ ዘብ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። የህወሀት ቡድን በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ባደራጃቸው ቡድኖች ያልታሰቡ ጥቃቶችን ሊያደርስ ስለሚችልም ሁሉም ህብረተሰብ አካባቢውን በንቃት እንዲጠብቅ ጀነራል ብርሀኑ ጁላ አሳስበዋል። የፌደራል ፖሊስ ትናንት በሰጠው መግለጫም፤ የህወሀት ፅንፈኛ ቡድን በትላልቅ ከተሞች የሽብር ጥቃት ለመፈፀም ሀይል ማሰማራቱ መረጋገጡን አስታውቋል። የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር እንዳሻው ጣሰውና የኮማንድ ፖስቱ ፕሬስ ሴክሬቴሪያት ትናንት በጋራ በሰጡት መግለጫ፤ ቡድኑ የሽብር ሀይል ወደተለያዩ ትላልቅ ከተሞች ማሰማራቱንና ከእነዚህ ሀይሎችም የተወሰኑት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቀዋል። ህወሀትና ኦነግ ሸኔ ከሀገር ውስጥም ከውጭ በሚደረግላቸው የፋይናንስ ድጋፍ በበርካታ የሀገሪቱ አካባቢዎች ባለፉት ሁለት አመታት ጥፋት ሲፈፀም ቆይተዋል ብለዋል የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል። ጥቅምት ሀያ አራት ቀን ሁለት ሺህ በትግራይ ክልል ከሀያ ሁለት በላይ ተቋማት በሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ሀይል ጥቃት ከመፈፀሙ በተጫማሪ ከፍተኛ የንብረት ዝርፊያ መፈፀሙ ነው ኮሚሽሩ በግለጫው ያመለከቱት።በአሁኑ ወቅት በህወሀት የተከፈተው ጦርነት ለመመከት የመከላከያ ሰራዊት ፌደራል ፖሊስ እና የክልል የፀጥታ ሀይሎች በተቀናጀ መልኩ እየወሰዱ ባለው እርምጃ አብዛኞቹ በቁጥጥር ስር መዋሉንና የተቀረውንም በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ኮሚሽነር ጀነራሉ አስገንዝበዋል። ውጥኑንም ሙሉ ለሙሉ ለማክሸፍ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው ህብረተሰቡም ከፀጥታ ሀይሉ ጐን በመቆም ድጋፉን እንዲያሳይ ኮሚሽነሩ አሳስበዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ መከላከያ ሰራዊት በተለያዩ አቅጣጫዎች ተልእኮ ተቀብሎ መሰማራቱንና ትናንትም ጠንካራ እርምጃዎች ሲወስድ መዋሉን ነው መንግስት ያስታወቀው። የመቀሌ አየር ማረፊያን ጨምሮ በትግራይ አየር ክልል ውስጥ ማንኛውም አውሮፕላን እንዳይበር የፌደራል ሲቪል አቪየሽን ትእዛዙንም አስተላልፏል። የሱዳን መንግስትም በከሰላ በኩል ያለውን ድንበሩን ሙሉ በሙሉ መዝጋቱን ሱዳን ፖስት አታውቋል።
በህወሀት ሀይል ላይ የተወሰደው የመጀመሪያው ዙር ዘመቻ በስኬት ተጠናቀቀ ጠቅላይ ሚኒስትር
አዲስ አበባ፣ሚያዚያ አስር፣ሁለት ሺህ ኤፍ ቢሲ በመዲናዋ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በህገ ወጥ መንገድ የግለሰብን የኤሌክትሪክ ቆጣሪ ቆርጠው ሀይል አቋርጠዋል የተባሉ ሶስት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለሙያዎች ጉቦ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገለፀ። በክፍለ ከተማው ወረዳ ስድስት ልዩ ቦታው ጨው በረንዳ አካባቢ ተጠርጣሪዎቹ ወደ ግል ተበዳይ መኖሪያ ቤት በመምጣት ቆጣሪ ልናነብና ልንመረምር ነው ካሉ በኋላ የኤሌክትሪክ ቆጣሪውን አይተው ስላሳ ሶስት ሺህ ብር እንደቆጠረ ለግል ተበዳይ ነግረዋቸዋል ነው የተባለው። የግል ተበዳይም ያልተጠቀሙበትን ፍጆታ እንደቆጠረባቸውና ከአቅማቸው በላይ መሆኑን ሲያስረዷቸው ከተፈቀደልህ በላይ ሀይል ጨምረህ ተጠቅመሀል በማለት የሁለት ቆጣሪዎች ሀይል እንዲቋረጥ ማድረጋቸውን የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ወንጀል ምርመራ ማስተባበሪያ ሀላፊ ምክትል ኢንስፔክተር እሱባለው ጌትነት ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ባለሙያዎቹ ሺህ ብር እጅ መንሻ ጉቦ ከሰጧቸው እንደሚያስተካክሉላቸው ለግል ተበዳይ ነግረው ገንዘብ መጠየቃቸውን የጠቀሱት ምክትል ኢንስፔክተሩ የግል ተበዳይም ይህን ያህል ገንዘብ እንደሌላቸው እና አስር ሺህ ብር እንዲያደርጉላቸው ተደራድረው ከጠየቋቸውም ገንዘብ ውስጥ አምስት ሺህ ብር ሲቀበሉ ቀደም ብለው ጉዳዩን ለፖሊስ አሳውቀው ስለነበር ከነ ገንዘቡ እጅ ከፍንጅ ሊያዙ መቻላቸውን አብራርተዋል። ህዝብ እና መንግስት የጣሉባቸውን ሀላፊነት ወደጎን በመተው ህብረተሰቡን የሚያማርሩ ግለሰቦችን ለህግ አጋልጦ በመስጠት ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ ማድረግ የሁላችንም ሀላፊነት ነው ሲሉ የግል ተበዳይ መናገራቸውን ከአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ፅቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ሶስት የኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለሙያዎች ጉቦ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ መያዛቸውን ፖሊስ ገለፀ
አዲስ አበባ ፣ ሰኔ ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የምሁራን ሚና ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የበይነ መረብ ምክከር እየተካሄደ ነው። ውይይቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጋር በመተባበር አዘጋጅተውታል። በውይይቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶክተር ሳሙኤል ኡርቃቶ ፣የውሀ፣ መስኖ እና ኢነርጅ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሽ በቀለን ጨምሮ ከሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ የስራ ኀላፊዎች እየተሳተፉ ነው። በዚህም የህዳሴ ግድብን ተከትሎ እየደረሰ የሚገኘውን ጫና ለመመከት የሚያስችል እና የዲጅታል ዲፕሎማሲውን ለማጠናከር ያለመ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ማእከል ተቋቁሟል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ማእከል ሁሉም ዜጋ ዲፕሎማት ነው የሚለውን ሀሳብ እንደሚያጠናክር ተናግረዋል። ሁሉም ኢትዮጵያውያን ህልማቸውን እውን ለማድረግ እውቀታቸውን፣ ጉልበታቸውን እና ሀብታቸውን አስተባበረው ግድቡን እውን ሊያደረጉ እየተጉ መሆኑንም አውስተዋል። ኢትዮጵያውያን የዚህን ፍሬ ለማየት ወደተራራው እየዘለቁ ባሉበት ወቅት የኢትዮጵያን እድገት የማይፈልጉ አካላት ከዚህ ለመመለስ የሀሰት መረጃዎችን በማሰራጨት ላይ ይገኛሉም ነው ያሉት። ግብፅ ኢትዮጵያውያን ፍሬያቸውን እንዳያዩ ያለ የሌለ አቅሟን እየተጠቀመች ትገኛለች ያሉት አቶ ደመቀ ይህ ማእከልም የግብፅ እና መሰሎቿን ሴራ ለመቋቋም ምሁራኖችን ከተማሪዎች ጋር ለማቀናጀት ጠቀሜታው ላቅ ያለ ነው ብለዋል። ማእከሉ የበሰሉ ኢትዮጵያዊ ዲፕሊማቶችን ለማፍራትም ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው መጠቆማቸውን ከደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶክተር ሳሙኤል ኡርቃቶ በበኩላቸው ምሁራን ለሀገራቸው የሚያበረክቱት አስተዋፅኦ እያደገ መምጣቱን አንስተዋል። ምሁራኑ ይህንን ሚና በማሳደግ ኢትዮጵያ እና አፍሪካን የማንቃት ሚናቸውን በተገቢው መንገድ እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። የውሀ፣ መስኖ እና ኢነርጅ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጅነር ስለሽ በቀለም አሁን ላይ ዝናብ በአስተማማኝ እና ከመደበኛ በላይ እያገኘን በመሆኑ የግድቡ ሁለተኛ የውሀ ሙሌት ያለምንም ችግር እንደሚከናወን አረጋግጠዋል።
የዲጅታል ዲፕሎማሲውን ለማጠናከር ያለመ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ማእከል ተቋቋመ
ኢሳት ግንቦት ሀያ ሶስት ፥ ሁለት ሺህ ዘጠኝ በኢትዮጵያ ለአስቸኳይ የምግብ እርዳታ ተጋልጠው የሚገኙ ከሰባት ሚሊዮን በላይ ሰዎች ከቀጣዩ ሰኔ ወር ጀምሮ የሚቀርብላቸው የምግብ ድጋፍ አቅርቦት ሊያልቅ እንደሚችል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አሳሰበ። የተረጂዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣትና የአለም አቀፉ ማህበረሰብ ለእርዳታ ጥሪው የሰጠው ምላሽ አነስተኛ መሆን የእርዳታ አቅርቦቱ ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ ማሳደሩን ድርጅቱ የድርቁን ሁኔታ አስመልክቶ ባወጣው አዲስ ሪፖርት ገልጿል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና መንግስት ባለፈው ወር ባወጡት አዲስ የተረጂዎች ቁጥር አምስት ነጥብ ስድስት ሚሊዮን የነበረው የአስቸኳይ ጊዜ የምግብ እርዳታ ፈላጊዎች ቁጥር ሰባት ነጥብ ሰባት ሚሊዮን መድረሱ የሚታወስ ነው። ይሁንና ድርቁን ለመከላከል እና ለተረጂዎች ድጋፍ ለማቅረብ የሚደረገው ጥረት የተጠበቀውን ያህል ውጤት ባለማምጣቱ ችግሩ እየተባባሰ ሊሄድ መቻሉ ታውቋል። የምግብ አቅርቦቱ እየተጠናቀቀ መምጣት ሰባት ነጥብ ሰባት ሚሊዮን የሚሆኑ ተረጂዎች ከሰኔ ወር ጀምሮ የምግብ አቅርቦት ላይኖር እንደሚችል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታውቋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና መንግስት የድርቁን አደጋ ለመታደግ ወደ አንድ ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ ከወራት በፊት ቢገልፁም እየተገኘ ያለው ድጋፍ ግን እጅግ አነስተኛ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል። ችግሩን ለመቅረፍ የምግብ አቅርቦት ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት በትንሹ ሶስት ወራትን የሚፈጅ ሲሆን፣ በቀጣዩ ወር ሊያልቅ ይችላል የተባለው የምግብ ክምችት በእርዳታ ተቋማት ዘንድ ስጋትን አሳድሯል። የአለም ምግብ ፕሮግራም በበኩሉ ከእርዳታ ድርጅቶች ጋር በመመካከር ምግብን ከገበያ ማግኘት ለሚችሉ ተረጂዎች ጥሬ ገንዘብ ለመስጠት አማራጭ መያዙም ታውቋል። በሶማሌ ክልል ያለው የምግብ አጥረት እየተባባሰ ባለበት በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ያለው የምግብ እርዳታ ክምችት ወደ ማለቅ መሆኑ አሳሳቢ ሆኖ ይገኛል ሲል የተባበሩት መንግስታት የእርዳት ማስተባበሪያ ቢሮ በሪፖርቱ አክሎ ገልጿል። የኦሮሚያ፣ አፋር ደቡብና የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ስር የሚገኙ በርካታ ዞኖች የተከሰተው የድርቅ አደጋ ጉዳት እያደረሰባቸው መሆኑ ይገልፃል። ከአንድ አመት በፊት ለአስር ሚሊዮን ሰዎች የምግብ እጥረት ምክንያት የነበረው የድርቅ አደጋ ሙሉ ለሙሉ እልባት ሳያገኝ አዲስ የድርቅ አደጋ በአራቱ ክልሎች መከሰቱ በእርዳታ አቅርቦት ላይ ጫና ማሳደሩንም የእርዳታ ድርጅቶች አስታውቀዋል። በተለይ በኢትዮጵያ የሶማሌ ክልል ያለው የድርቅ አደጋ ለአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት በሽታ ምክንያት የሆነ ሲሆን፣ ከሰባት መቶ በላይ ሰዎች መሞታቸውን የአለም ጤና ድርጅት በቅርቡ ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ነው። ይሁንና፣ መንግስት በጉዳዩ ዙሪያ የሰጠው ማስተባበያም ሆነ ማረጋገጫ የለም።
ለተረጂዎች ሲሰጥ የነበረ የአስቸኳይ ጊዜ የምግብ እርዳታ ከሰኔ ወር ጀምሮ ሊያልቅ እንደሚችል ተመድ አሳሰበ
መጋቢት አስራ ዘጠኝ ቀን አመተ ምህረት ኢሳት ዜና ላለፉት ሁለት አመታት ሲካሄድ የቆየው ከቅርብ ወራት ወዲህ ቀዝቀዝ ብሎ የነበረው የሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ ዛሬ ቁጥሩ እጅግ ብዙ የሆነ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን በተገኙበት በአንዋር መስጊድ ተካሂዷል።ሙስሊም ኢትዮጵያዊያኑ አላህ ሰላምን እንዲያመጣ ሲማፀኑ አርፍዷል። የሰላም ሰዎች መሆናቸውን ነጭ ወረቀቶችን በማውለብለብ ያሳዩ ሲሆን ተቃውሞውም ያለምንም የፀጥታ ችግር ተጠናቋል።መንግስት እንቅስቃሴውን በሀይል እንደተቆጣጠረው ሲያውጅ ቢከርምም ዛሬ በአንዋር የተገኘው ህዝብ ብዛት ሙስሊሙ ኢትዮጵያዊ ጥያቄዎቹ ካልተመለሱ ዝም የማይል መሆኑን አሳይቷል ሲል አንድ ስሙ እንዳይገለፅ የፈለገ ወጣት ለዚጋቢያችን ተናግሯል።የዛሬው ተቃውሞ በግፍ እስር ላይ ለሚገኙት ለመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት የስነልቦና ጥንካሬ ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ የገለፀው አስተያየት ሰጪ በኮሚቴ አባላቱ ላይ የሚሰጠው የሀሰት የፍርድ ውሳኔም ተቃውሞውን ይበልጥ ያጎላዋል እንጅ አያደበዝዘውም ብሎአል።የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት የፍርድ ሂደት ነፃና ገለልተኛ አይደለም በሚል በአለማቀፍ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ይተቻል።
ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ ተቃውሞ አሰሙ
በሱዳን መንግስት እና አማፂያን መካከል የመጨረሻ የሰላም ስምምነት መስከረም ሀያ ሁለት በደቡብ ሱዳን መዲና ጁባ እንደሚፈረም የሰላም ድርድሩ ሀላፊ ገለፁ። የድርድር ቡድኑ ሀላፊ እና የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት የፀጥታ ጉዳዮች አማካሪ የሆኑት ቱት ጋትሏክ ጥቅምት ሁለት በአውሮፓውያኑ በመንግስት እና በሰላም ድርድሩ ሂደት ውስጥ ባሉ ወገኖች መካከል የተደረገው የሰላም ስምምነት የመጨረሻ ፊርማ የሚደረግበት ቀን ነው ሲሉ በትዊተር ገፃቸው ገልፀዋል። የሱዳን ባለስልጣናት እና የአማፂ ቡድኖች ጥምረት የሆነው የሱዳን አብዮታዊ ግንባር ኤስ አር ኤፍ ፣ በመቶ ሺዎች ለሚቆጠሩ ሰዎች ሞት ምክንያት የሆነውን በተለይም በምእራብ ዳርፉር የተከሰተውን ግጭት ለማስቆም የታቀደ ታሪካዊ የሰላም ስምምነት በአውሮፓውያኑ ባለፈው ነሀሴ ስላሳ አንድ ጁባ ውስጥ ተፈራርመዋል። እ ኤ አ በ ሁለት ሺህ የተቋቋመው ኤስ አር ኤፍ በጦርነት ከተጎዳው የምእራብ ዳርፉር ክልል እና እንዲሁም ከደቡብ የሀገሪቱ ክፍል የብሉ ናይል እና የደቡብ ኮርዶፋን ግዛቶች አማፂያንን ያሰባሰበ ነው። የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላህ ሀምዶክ በጁባ በተደረገው ድርድር ለመስማማት ፈቃደኛ ካልሆነው የሱዳን ህዝባዊ ነፃነት ንቅናቄ ሰሜን ኤስ ፒ ኤል ኤም አማፂ ቡድን ጋር በኢትዮጵያ ውስጥ የተለየ ስምምነት መፈራረማቸውን የሁለቱ ወገኖች ባለስልጣናት አስታውቀዋል። የሱዳን የረጅም ጊዜ መሪ ኦማር አልበሽር ፣ ለወራት የዘለቀውን ከፍተኛ ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ ፣ እ አ ኤ ሚያዚያ ሁለት ሺህ ከስልጣን ሲወገዱ ወደ ሀላፊነት የመጣው የሱዳን የሽግግር መንግስት ከአማፂያን ቡድኖች ጋር የሰላም ስምምነት ላይ መድረስን ቀዳሚ ተግባሩ አድርጎ ሲሰራ ቆይቷል። ስምምነቱ በዋነኝነት በፀጥታ ፣ በመሬት ባለቤትነት ፣ በሽግግር ፍትህ ፣ በስልጣን ማጋራት እና በጦርነት ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው የተሰደዱ ሰዎችን መልሶ ማቋቋም ላይ ያተኮረ ነው። በተጨማሪም የአማፂ ሀይሎችን ማፍረስ እና ተዋጊዎቻቸውን ወደ ብሄራዊ ጦር ስለማቀላቀልም ይመለከታል። እ ኤ አ በ ሁለት ሺህ ሶስት አማፂያን መሳሪያ ካነሱ በኋላ በዳርፉር ብቻ በተካሄደው ውጊያ ሶስት መቶ ያህል ሰዎች ለህልፈት መዳረጋቸውን ሲጂቲኤን ዘግቧል። ከጥቅምት ሁለት ሺህ እ ኤ አ ጀምሮ ደቡብ ሱዳን በሱዳን መንግስት እና በዳርፉር ፣ ደቡብ ኮርዶፋን እና ብሉ ናይል ግዛቶች በሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ቡድኖች መካከል ሽምግልና ስታደርግ ቆይታለች።
የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላህ ሀምዶክ ከቀናት በፊት ከአንድ አማፂ ቡድን ጋር በአዲስ አበባ ተስማምተዋል
አዲስ አበባ፣ የካቲት ሀያ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ ወርሀ ፆሙ ለተፈናቀሉና በድርቁ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ የምናደርግበት ሊሆን ይባል ሲሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኩስም ወጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሀይማኖት ተናገሩ። ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የአቢይ ፆም መግባትን አስመልክተው ለመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሀዶ ቤተክርስቲያን ምእመናን የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል። በመልእክታቸውም በግጭቱና በድርቁ ለተጎዱ ወገኖች ካለን በማካፈል የችግሮቻቸው ተካፋይ መሆን ይገባል ብለዋል። ህዝበ ክርስቲያኑ ወርሀ ፆሙን ራሱን ሀይል ሰጪ ከሆኑ ምግቦች በመከልከል ብቻ ሳይሆን ከፀብና ከጥላቻ በመራቅ ሊያሳልፈው እንደሚገባ ገልፀዋል። የፆሙ ወቅት ምእመኑ ንስሀ የሚገባበት፣ ጥላቻን ከህሊናው የሚያስወግድበት ፍቅርን በመሻት ወደ እግዚአብሄር የሚቀርብበት ሊሆን እንደሚገባም ተናግረዋል። በዚህ ፆም ህዝበ ክርስቲያኑ ስለሀገር እና ስለቤተክርስቲያን መፀለይ እንደሚገባውም በመልእክታቸው አንስተዋል። በቅድስት ብርሀኑ ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ ድረ ገፅ፦ ፌስቡክ፡ ዩትዩብ፦ ቴሌግራም፦ ትዊተር፦ በመወዳጀት ይከታተሉን። ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
ወርሀ ፆሙ ለተፈናቀሉና በድርቁ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ የምናደርግበት ሊሆን ይገባል ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ
አዲስ አበባ፣ጥር ዘጠኝ፣ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የከተራና የጥምቀት በአል ተሳታፊዎች በአሉን ሲያከብሩ ርቀታቸውን በመጠበቅ ፣ ከንክኪ በመቆጠብ ፣ በተደጋጋሚ እጃቸውን በማፅዳት እንዲሁም የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ሳያወልቁ በመንቀሳቀስ ሊሆን እንደሚገባ የጤና ሚኒስቴር አሳሰበ። ሚኒስቴሩ ለክርስትና እምነት ተከታዮች፥ ለከተራና ለጥምቀት በአል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፏል። ሚኒስቴሩ በመልእክቱ የከተራና የጥምቀት በአል በምእመናን በብዛት የሚታጀብና አካላዊ ንክኪው እና ጥግግቱ የጠነከረ በመሆኑ ሰዎች ስሜቶቻቸውን ስገልፁ በጥንቃቄ ሊሆን እንደሚገባ ነው ያሳሰበው። ይህ ሁኔታ በተለይ የኮቪድ ወረርሽኝን ከሰው ወደ ሰው በማስተላለፍ ረገድ ምቹ ሁኔታ ሊፈጥር ስለሚችል፥ በአሉን ለማክበር የሚሰባሰቡ ሰዎች ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብሏል። የበአሉ ተሳታፊ ምእመናንም በተቻለ መጠን ርቀታቸውን በመጠበቅ ከንክኪ በመቆጠብና በተደጋጋሚ እጃቸውን በማፅዳት እንዲሁም የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ሳያወልቁ በመንቀሳቀስ በአሉን ማክበር እንዳለባቸው ሚኒስቴሩ አሳስቧል። ኢትዮጵያን፦ እናልማ፤ እንገንባ፤ እንዘጋጅ ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ ድረ ገፅ፦ ፌስቡክ፡ ዩትዩብ፦ ቴሌግራም፦ ትዊተር፦ በመወዳጀት ይከታተሉን። ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
የከተራና የጥምቀት በአል ተሳታፊዎች በአሉን ሲያከብሩ ርቀታቸውን በመጠበቅና ከንክኪ በመቆጠብ ሊሆን እንደሚገባ ማሳሰቢያ ተሰጠ
ሶስት መቶ ሰባ አምስት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የውሀና መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ያለበትን ወቅታዊ የግንባታ ደረጃ ዛሬ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይፋ አድርጓል። በዚህም መሰረት የግድቡ ሲቪል ስሰራዎች በአሁኑ ወቅት የዋናው ግድብ የሲቪል ስራዎች ሰማኒያ በመቶ ተጠናቋል፤ የሀይል ማመንጫዎች የሲቪል ስራ በአማካይ ስልሳ ስድስት በመቶ ተጠናቋል፤ የጎርፍ ማስተንፈሻ የሲቪል ስራዎች ዘጠና ዘጠኝ በመቶ ተጠናቋል፤ የኮርቻው ግድብ ስራዎች ዘጠና ሶስት በመቶ ተጠናቋል የስዊችያርድ የሲቪል ስራዎች ስላሳ ሶስት በመቶ ተጠናቋል፤ በአጠቃላይ የሲቪል ስራዎች ሰማኒያ ሁለት በመቶ ተጠናቋል። የአሌክትሮመካኒካል ስራዎች ተርባይን እና ጄኔሬተር ምርትና ተከላን ያለበትነ ደረጃ በተመለከተም ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጀነር ስለሺ በቀለ ለምክር ቤቱ አብራርተዋል። በዚህም መሰረት የዘጠኝ ተርባይን እና ጄኔሬተር በአብዛኛው የተከናወነ ሲሆን በፕሮጀክት የስራ ቦታ ጉባ እና አንዳነዶቹ በወደቦች ይገኛሉ። የተወሰኑት የተርባይንና ጄኔሬተር አካላት በሀገር ውስጥ ይመረታሉ ተብለው የታሰቡት አልተመረቱም፤ የመጀመሪያ ሁለት ዩኒቶች የተርባይን አካል የሆኑትውሀን ለተርባይኖች የሚያመራ ተከላ ሀያ ሶስት ነጥብ ሰባት በመቶ ተከናውኗል፤ የከፍተኛ ሀይል መቆጣጠሪያ እና ማስተላለፊያ ስዊችያርድ ተከላ የመጀመሪያ ሁለቱ ዩኒቶች ትርንስፎርመር ተመርተው ሳይት ደርሰዋል፤ የተከለ ስራ አልተጀመረም፤ የከፍተኛ ሀይል መቆጣጠሪያ እና የማስተላለፊያ ስዊችያርድ እቃዎች ተመርተው የደረሱ ሲሆን ተከላ በጅምር ላይ ነው። አጠቃላይ የኤሌክተሮ መካኒካል ስራዎች አፈፃፀም ሀያ አምስት በመቶ ሲሆን፤ የሀይድሮሊክስ ስቲል እስትራክቸር ስራዎች አፈፃፀም በመቶ ብቻ ነው። በብረታብረትና ኢንጅነሪንግ ብኢኮ የተሰራው ስራም ሀያ ሶስት በመቶ ብቻ ሲሆን ፕሮጀክቱ አሁን የደረሰበት የግንባታ ደረጃም ስልሳ አምስት በመቶ መሆኑን ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጅነር ስለሺ አብራርተዋል። ሶስት መቶ ሰባ አምስት
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አሁን ያለበት ደረጃ ይፋ ሆነ
ከግማሽ ቢሊዮን በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የጎንደር ከተማ ውሀ ፕሮጀክት በተመረቀ በጥቂት ወራት ውስጥ ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት መስጠት አቆመ።ኢሳት ዜና ሚያዝያ ቀን አመተ ምህረት ለዘመናት በከፍተኛ የውሀ እጥረት ችግር ተጠቂ ከሆኑት የኢትዮጵያ ከተሞች መካከል አንዷ የሆነችው የጎንደር ከተማን የውሀ ችግር ከ በመቶ ወደ መቶ በመቶ ከፍ ያደርገዋል በዘላቂነትም የከተማዋን የውሀ ችግር ይፈታል የተባለለት የውሀ ፕሮጀክት በተመረቀ በጥቂት ወራት ውስጥ ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት መስጠት በማቆሙም ህዝቡ ለከፍተኛ ችግር መዳረጉ እና ከ ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ ገንዘብ ባክኖ መቀረቱ ተዘግቧል።ፕሮጀክቱ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸውና የውሀና ኢነርጂ ሚንስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ በተገኙበት ህዳር ቀን አመተ ምህረት በይፋ ተመርቆ ስራ መጀመሩ ይታወሳል።ከአለም ባንክ በተገኘ ብድርና በመስተዳደሩ ወጪ ከ ሚሊዮን ብር በላይ የፈሰሰበት የውሀ ፕሮጀክት ለሚቀጥሉት ሀያ አመታት ዋስትና አለው ተብሎ ታስቦ የተሰራ ነው ተብሎ ነበር። አዲሱ ፕሮጀክት ስምንት ጥልቅ ጉድጓዶች ሲኖሩት በሰከንድ እስከ ሊትር በቀን ደግሞ እስከ ሽህ ሜትር ኩብ ውሀ እንደሚያመነጭና ከአንገርብ የውሀ ማመንጫ ጋር ተዳምሮ በቀን እስከ ሽህ ሜትር ኩብ ውሀ ያቀርባል ተብሎ ዲዛይን ተደርጎ መሰራቱ ይታወቃል። ይሁንና ጉድጓዶቹ በተባለላቸው መጠን የተጠበቀውን ያህል ውሀ ማመንጨት ሳይችሉ አገልግሎት መስጠት በማቆማቸው የከተማዋ ነዋሪዎች በውሀ ማጣት ከመቸገራቸው በተጨማሪ ተጨማሪ ወጭዎችን ለማውጣት ተገዷል።ኢሳት ከወራት በፊት የውሀ ጉድጓዶች መድረቃቸውን መረጃ ደርሶ ሲከታተለው ቆይቷል። በግንባታው ላይ ከፍተኛ ሙስና መፈፀሙንም የደረሰን መረጃ ያመለክታል።ችግሩን አስመልክቶ የጎንደር ከተማ ውሀ ፕሮጀክት ፅህፈት ቤት ሀላፊ ብዙ ገንዘብ ወጪ ወጥቶበት የተገነባው ፕሮጀክት የተጠበቀውን ያህል አገልግሎት መስጠት ባለመቻሉ በግንባታ ፕሮጀክቱ ላይ የተሳተፉ በሙሉ ተጠያቂዎች ናቸው ብለዋል።ታሪካዊቷን የጎንደር ከተማን ጨምሮ በመዲናዋ አዲስ አበባ አዳማ መቀሌ አሰላ በመሳሳሉት ታላላቅና አነስተኛ ከተሞች የንፁህ መጠጥ ውሀ አቅርቦት ችግር ከጊዜ ወደ ጊዜ በመባባሱ በነዋሪዎች ህይወት ላይ አሉታዊ ጫና እያሳደረ ነው።
ከግማሽ ቢሊዮን በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የጎንደር ከተማ ውሀ ፕሮጀክት በተመረቀ በጥቂት ወራት ውስጥ ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት መስጠት አቆመ።
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ አራት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ ያለምንም የውጭ ምንዛሬ ፈቃድ መሰረታዊ የምግብ ሸቀጦችን ለሚያስገቡ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ስርአት መዘርጋቱን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ። የገንዘብ ሚኒስቴር የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት ዘይት፣ ስንዴ፣ ስኳር ፣ የህፃናት ወተት እና ሩዝ ያለምንም የውጭ ምንዛሬ ፈቃድ በጉምሩክ ኮሚሽን በቀጥታ እንዲገቡ መወሰኑን ተከትሎ ኮሚሽኑ የዚህ እድል ተጠቃሚ ለሆኑ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል የአሰራር ስርአት መዘርጋቱንና አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረጉን የህግ ተገዥነት ምክትል ኮሚሽነር አቶ ሙሉጌታ በየነ ገልፀዋል። በዘርፉ የሚሰማሩ አካላት በጉምሩክ ኮሚሽን ዋናው መስሪያ ቤት ፈቃድ እንደሚሰጣቸው ጠቅሰው ፈቃዱን ካገኙ በኋላ በኮሚሽኑ ስር በሚገኙ እና በመረጡት ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች በኩል መስተናገድ እንደሚችሉ ተናግረዋል። ፈቃድ ለማግኘት በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸውም አቶ ሙሉጌታ አስረድተዋል። ሸቀጦቹ ከጉምሩክ ወደብ ከተነሱ በኋላ በአግባቡ ለተጠቃሚው እንዲደርሱ የሚመለከታቸው መንግስታዊ ተቋማት ተቀናጅተው እንደሚሰሩ ገልፀው በተለይም ህብረተሰቡ ከመንግስት የፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት ህገወጦችን ማጋለጥ ይገባዋል ብለዋል። መሰረታዊ የምግብ ሽቀጦች ያለምንም የውጭ ምንዛሬ ፍቃድ ከሚያስገቡት አካላት በተጨማሪ በሀገር ውስጥ የምንዛሬ ፈቃድ አግኝተው በዘርፉ ለተሰማሩ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል መናገራቸውን ከኮሚሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
የጉምሩክ ኮሚሽን የምግብ ሸቀጦችን ከውጭ ለሚያስገቡ ፈጣን አገልግሎት እሰጣለሁ አለ
በጋራ የተመረቱ የጦር መሳሪያዎችን ለሶስተኛ አገር መሸጥ ያስችላቸዋል ኢትዮጵያና ቱርክ በመከላከያ ኢንዱስትሪ ዘርፍ መተባበር የሚያስችላቸውን ስምምነት ሊያፀድቁ ነው። ስምምነቱ የኢትዮጵያ የመከላከያ አቅምን በአለም አቀፍ ደረጃ ከመገንባት ባሻገር፣ ሁለቱ አገሮች በጋራ ያመረቷቸውን የጦር መሳሪያዎች ለሌላ ሶስተኛ አገርም ለመሸጥ የሚያስችላቸው ነው ተብሏል።ሁለቱ አገሮች በመከላከያ ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለመተባበር ስምምነት የተፈራረሙበት በሚያዝያ ወር አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ስምንት አመተ ምህረት ቢሆንም፣ ስምምነቱ ወደ ተግባር መቀየር ባለመቻሉ ይህንኑ ስምምነት ለማጠናከርና ወደ ስራ ለመግባት በግንቦት ሁለት ሺህ አምስት አመተ ምህረት ተጨማሪ ስምምነት አድርገዋል።ሁለቱ አገሮች በውስጥ አሰራራቸው መሰረት ስምምነቱን በአዋጅ ማፅደቅ የሚጠበቅባቸው በመሆኑ፣ ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ በኩል ስምምነቱ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቧል። የስምምነቱ አንቀፅ አራት የትብብር መስኮችን የሚዘረዝር ነው። በዚህም መሰረት የመከላከያ ሰራዊት የሚፈልጋቸውን የመከላከያ እቃዎች የመለዋወጫዎች ዲዛይን ለማውጣት፣ ለማምረት፣ ለመጠገን፣ ለመለወጥና ለማዘመን የሚያስችሉ የምርምር ስራዎች ላይ መተባበርን ይመለከታል።የመከላከያ ኢንዱስትሪ ዘርፍ ቁሳቁሶችንና አገልግሎቶችን ለማምረትና ለመግዛት ወይም ለመሸጥ፣ የጦር መሳሪያዎችን ለማዘመን የጋራ ትብብር ማድረግ፣ የመከላከያ የጦር መሳሪያዎችን ለመፈብረክ የጋራ ፕሮጀክቶችን በመቅረፅ ለሁለቱም አገሮች ወይም ለአንዱ አገር የሚጠቅሙ ሳይንሳዊ ምርምሮችን ማድረግ የትብብሩ አካል ነው።በየአገሮቹ ህግ መሰረት ከበቂ በላይ የሆኑ የመከላከያ ኢንዱስትሪ እቃዎችንና አገልግሎቶችን አንዱ አገር ለሌላው አገር የጋራ ሽያጭ እንዲኖር ማድረግ፣ የሚስጥራዊ መረጃዎች ደሀንነት ስምምነት በማድረግ በዚሁ መሰረት ሳይንሳዊና ቴክኒካዊ መረጃዎችን መለዋወጥም የትብብሩ አንድ አካል ሆኖ በስምምነቱ ውስጥ ተጠቅሷል። በጋራ ትብብር ፕሮጀክቶች የተመረቱ የጦር መሳሪያዎችን በሁለቱ አገሮች ስምምነት ለሌላ ሶስተኛ አገር መሸጥ ሌላው የትብብሩ አካል ነው። የተዋዋይ ወገኖች መብትና ጥቅም በሰጥቶ መቀበል መርህ መሰረት አንዱ ሌላውን በማክበር ላይ የተመሰረተ መሆን እንዳለበት፣ በዚህ የትብብር ማእቀፍ መሰረት የተሰጠ፣ የተሸጠ ወይም በልውውጥ መልክ የተገኘን ቁሳቁስ፣ ቴክኒካዊ መረጃና ሰነዶች የአንደኛውን ወገን የፅሁፍ ስምምነት ሳያገኙ ለሌላ ሶስተኛ አገር አሳልፎ መስጠት እንደማይቻል ስምምነቱ ይገልፃል።ስምምነቱን ወደ ተግባር ለመለወጥ ከሚረዱ ተግባሮች መካከል አንዱ የጋራ ኮሚቴ ማቋቋም መሆኑን የሚያመለክተው የስምምነቱ ሰነድ፣ ከሁለቱም አገሮች የመከላከያ ሚኒስቴሮች በእኩል በተውጣጡ አባላት ኮሚቴው አንደሚዋቀር ይገልፃል።ለሚቋቋመው ኮሚቴ የኢትዮጵያ ልኡክ የሚመራው በኢትዮጵያ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ዳይሬክተር ጄነራል መሆኑን፣ በቱርክ በኩል ደግሞ በአገሪቱ መከላከያ ሚኒስቴር የቴክኖሎጂና ትብብር ምክትል ሚኒስትር መሆኑን ስምምነቱ ይገልፃል።በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤትና በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማሀተም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው ሰነድ፣ የስምምነቱ መፅደቅ ብቃት ያለው የመከላከያ አቅምን ለመገንባት ከተያዘው ጥረት ጋር አብሮ የሚሄድ በአገር ውስጥ ከሚደረገው ጥረት ባሻገር፣ ስትራቴጂካዊ አጋር ከሆኑ አገሮች ጋር በሚፈጠር ትብብር የበለጠ የመከላከያን አቅም የማጎልበትና የማዘመን ፋይዳ እንደሚኖረው ይገልፃል።ፓርላማው ስምምነቱን በዝርዝር ተመልክቶ የውሳኔ ሀሳብ እንዲያቀርብለት ለመከላከያና የውጭ ደሀንነት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርቶታል።
ኢትዮጵያና ቱርክ በመከላከያ ኢንዱስትሪ ዘርፍ ሊተባበሩ ነው
የቀድሞው ኦነግ እና በአሁኑ ወቅት የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግምባር የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የሆኑት አቶ ሌንጮ ለታ ከአመታት በፊት የኦነግ አመራር በነበሩበት ወቅት ከጋዜጠኛ ሙሉጌታ ሉሌ ጋር በዋሽንግተን ዲሲ ቃለምልልስ አድርገው ነበር። ቃለምልልሱም በወቅቱ በጦቢያ መፅሄት ላይ ወጥቶ ነበር። ይህ ታሪካዊ ቃለምልልስ በፒዴፍ ከረጅም አመታት በኋላ እየተሰራጨ ነው። ይህ ቃለምልልስ ከኦነግ ምስረታ እስከ አሁን ስላለው ትግል ብዙ ጠቃሚ መረጃዎችን ያስቃኛችኋል ብለን ተስፋ እናደርጋለን። እኛም ለዘሀበሻ አንባቢዎች ግንዛቤ ይረዳል ብለን ስላሰብን እነሆ ይዘንላችኋል። እዚህ ይጫኑ
አቶ ሌንጮ ባቲ ከጦቢያ መፅሄት ጋር አድርገውት የነበረው ቃለምልልስ ሊነበብ የሚገባው
ከይርጋ አበበ በአገራችን እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ በግብ ጠባቂነት ስመ ጥር የሆኑ እንደነ ተካበ ዘውዴ ያሉ በርካታ ስፖርተኞች አሉ። በዘመናቸው ለክለባቸውም ሆነ ለአገራቸው የሚችሉትን አበርክተዋል። ለእዚህ ዝግጅት የኢትዮጵያ ቡና፣ የመብራት ሀይልና ቅዱስ ጊዮርጊስ ክለቦችንና የብሄራዊ ቡድናችንን በር ከጠበቁት ተጫዋቾች መካከል ሶስቱ ያሉበትን ሁኔታ በአጭሩ እነሆ አሊ ረዲ አሊ ረዲ የኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ ደጋፊዎች ከለላችን እያሉ የሚጠሩት ቁመተ መሎሎ ግበ ጠባቂ ነው። በአንድ ወቅት በደረሰበት ከባድ ጉዳት ሼህ ሙሀመድ ሁሴን አሊ አላ ሙዲ ለህክምና ሙሉ ወጪውን ሸፍነው ካሳከሙት በኋላ የክለቡ ደጋፊዎች አላሙዲ አላህ ይስጣቸው ብለው ምስጋናቸውን በአደባባይ ያስነገራቸው የተጫዋቹ ከፍተኛ ባለውለታቸው መሆን ነበር። አሊ ረዲና እግር ኳስ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዋወቁት የሀገራችን ስፖርት ባለውለታ በሆነው የኦሜድላ ክለብ ሲሆን፤ ዘመኑም በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ ሰባትአመተ ምህረት ነበር። ኢትዮጵያ ቡና ደግሞ የኦሜድላውን ፍሬ ገና ከእሸትነቱ ጀምሮ እስኪጎመራ ድረስ ተጠቀመበት ከአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ ዘጠኝ እስከ አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና አምስትአመተ ምህረት ድረስ። ክለቡ ኢትዮጵያ ቡና ጠንካራዎቹን የግብፅ ክለቦች አልሀሊና ዛማሌክ በማሸነፍ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ክለብ በሆነበት ዘመን የክለቡን በር በንቃትና በታማኝነት ጠብቋል። እንዲሁም የጥሎ ማለፍ ዋንጫዎችን ደጋግሞ ማንሳት የቻለውን ክለብ በር የጠበቀውም ይኼው ቁመተ ሎጋ ግብ ጠባቂ ነበር። ከተካበ ዘውዴ በኋላ ብሄራዊ ቡድናችንን በር በንቃት የጠበቀ ታታሪ ግብ ጠባቂ ነው እየተባለ የሚጠራው አሊ ረዲ ለሀገሩ በተሰለፈባቸው ጨዋታዎችም ቢሆን ሀገራዊ አደራውን ተቀብሎ በኩራት የተወጣ ባለአደራ ተጫዋች ነው። አሊ ረዲ ከኢትዮጵያ ቡና የተለየው አሊን ካጋጠመው ከባድ የደም ካንሰር በኋላ ከእግር ኳስ ለረጅም አመታት በመገለሉ ሲሆን፣ የቀድሞው ቡናማ በአሁኑ ወቅት የውሀ ስራዎች እግር ኳስ ክለብ ግብ ጠባቂ ነው። ደያስ አዱኛ ዲያጎ ጋርዚያቶ በአሰልጣኝነት እየመሩ ወደ አርጄንቲና የተጓዘውን የወጣት ብሄራዊ ቡድናችንን ግብ የጠበቀው ወጣት ተጫዋች ነው። በተለይ ሀገራችን ያደረገቻቸውን ሶስቱንም ጨዋታዎች በቴሌቪዥን ሲያስተላልፉ የነበሩ ጋዜጠኞች የግብ ጠባቂያችን ስም ሲጠሩ ደያስ አዱግና እያሉ ሲጠሩት በርካታ ኢትዮጵያውያንን ፈገግ ያሰኙ ነበር። ደያስ አዱኛ የቅዱስ ጊዮርጊስና መብራት ሀይልን ክለቦች ግብ ጠባቂነት ያገለገለ ታታሪ ግብ ጠባቂ ነበር። ወደ አዲስ አበባ መጥቶ የሁለቱን ክለቦች በር ከመጠበቁ በፊት የሙገር ሲሚንቶ ክለብ ተጫዋች ነበር። በርካታ ታዳጊዎችን ከየመንደሩ እያሰሰ ወደ አደባባይ በማውጣት የሚታወቀው ሙገር ሲሚንቶ ደያስንም ለብሄራዊ ቡድናችንና ለሁለቱ ታላላቅ የአዲስ አበባ ክለቦች ማብቃት ችሏል። ደያስ አዱኛ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር የነበረውን ቆይታ ካጠናቀቀ በኋላ ኑሮውን ያደረገው አሜሪካ ነው። አሁንም የሚገኘው እዛው አሜሪካ እንደሆነ ለተጫዋቹ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለዝግጅት ክፍላችን ገልፀውልናል። ታዲዮስ ጌታቸው ታዳጊዎችን በማእከሉ እያሳደገ ለዋናው ክለብ በማሰለፍ የሚታወቀው ቅዱስ ጊዮርጊስ ይህንን መለሎ ግብ ጠባቂም በአካዳሚው አሳድጎ ለቁም ነገር ማብቃቱ ይነገርለታል። ከአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ ዘጠኝአመተ ምህረት ጀምሮ እስከ አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ስድስትአመተ ምህረት ድረስ የፈረሰኞቹን በር መጠበቅ የቻለው ታዲዮስ ጌታቸው ከክለቡ ጋር የተለያዩ ዋንጫዎችን ማንሳት የቻለ ሲሆን፣ የምስራቅ አፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮና ላይም ቢጫና ቀዩን ማሊያ ለብሶ በመጫወት የነሀስ ሜዳሊያ መሸለም የቻለ ግብ ጠባቂ ነበር። ከፈረሰኞቹ ጋር የነበረውን ቆይታ አጠናቅቆ ወደ ታሪካዊ ተቀናቃኛቸው ኢትዮጵያ ቡና በማምራት የቢጫ ለባሾቹን የግብ ክልል ከአሊ ረዲ ተረክቦ መጠበቅ ችሏል። ከቡና ጋር የነበረው ቆይታ እንደ አሳዳጊ ክለቡ ያልሰመረለት ታዲዮስ ከክለቡ ጋር ያለውን ውል ሳይጨርስ በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ዘጠኝአመተ ምህረት ወደ አገረ አሜሪካ ተጉዟል። ልክ እንደ ደያስ አዱኛ ሁሉ ታዲዮስ ጌታቸውም አሁን በአሜሪካን አገር በሎሳንጀለስ ከተማ ይኖራል። ለሀገር ውለታ ለዋሉ ክብር እንስጥ
ሶስትቱ የቀድሞ ብሄራዊ ቡድናችን በረኞች አሊ ረዲ፣ ደያስ አዱኛና ታድዮስ ጌታቸው የት ይገኛሉ
በሰሜን ኢትዮጵያ በተለያዩ ማሀበረሰቦች ዘንድ በነሀሴ ወር አጋማሽ በልጃገረዶችና በሴቶች የሚከበረው በአል ከፍልሰታ ለማርያም ክብር ጋር የተያያዘ እንደሆነ ይወሳል። ይህ በትግራይ አሸንዳ፣ አይን ዋሪ፣ ማርያ፤ በሰቆጣ ሻደይ፣ በላስታ ላሊበላ፣ በደቡብ ጎንደር አሸንድዬ፣ በቆቦ ሶለል በሚባል የሚጠራው ክብረ በአል ሴቶች በባህላዊ አልባሳትና ጌጣ ጌጦች ተውበውና አደባባይ ወጥተው የሚያከብሩት በአል ነው። ነሀሴ ቀን ከሚከበረው የፍልሰታ ማርያም በአል ጋር ተያይዞ ከዋዜማው እስከ ማግስቱ በገጠርና በከተማ እየተከበረ ይገኛል። ከህፃን እስከ አዋቂ የአሸንዳ ቅጠልን አሸርጠው አደባባይ በመውጣትና በየቤቱ በመዞር እየጨፈሩና እያዜሙ ያከብሩታል። የፀጉር አሰራራቸው በትግራይ ከአልባሶ እስከ ግልብጭ፣ ከጋመ እስከ ድርብ፤ በሰቆጣና በላሊበላ ጋሜ፣ ቁንጮ፣ ግልብጭ፣ ሳዱላና ቅርድድ ተሰርተው ይታዩበታል። ጌጣ ጌጣቸውም ልዩ ልዩ አይነት ህንቆ፣ አልቦ፣ ድሪ፣ ድኮት፣ ጉትቻ፣ ማርዳ መስቀል ሲሆን፣ አለባበሳቸውም በመልጉም ባለጥልፍ ቀሚስ ፣ ሹፎን፣ ጀርሲና በመሳሰሉት ይሆናል። ዘንድሮ እንደወትሮው ሁሉ ክብረ በአሉ በመቐለ፣ በሰቆጣ፣ በላሊበላ፣ በአክሱም፣ በደብረ ታቦርና በባህር ዳር ከተሞች እንዲሁም በአዲስ አበባም በየማሀበረሰቡ በልዩ ልዩ ዝግጅት እንደሚከበር አዘጋጆቹ አስታውቀዋል። በተለይ በመቐለ እና በሰቆጣ ክብረ በአሉን አስመልክቶ አውደ ጥናት እንደሚካሄድ ታውቋል። የዩኔስኮ ምዝገባ ባህልን የሚመለከተው የመንግስታቱ ድርጅት ዩኔስኮ በየአገሩ ከሚገኙ የማይዳሰሱ ባህላዊ ቅርሶች መካከል በየአመቱ የሰው ልጅ ወካይ በሚል በአለም ቅርስነት ይመዘግባል። ኢትዮጵያ እስካሁን ሶስት የማይዳሰሱ ባህላዊ ቅርሶችን የመስቀል፣ የፊቼ ጫምባላላ በአላትና የገዳ ስርአት በዩኔስኮ ተመዝግቦላታል። ከአመታት በፊት ሰነዱ የተላከው የጥምቀት ክብረ በአል በመጪው ሀዳር ሁለት ሺህ አመተ ምህረት በሚካሄደው ኛ ስብሰባ ውሳኔ ይሰጥበታል ተብሎ ይጠበቃል። ዩኔስኮ የማይዳሰሱ ባህላዊ ቅርሶችን ለአንድ አገር የሚመዘግበው ቢያንስ በየሁለት አመት ልዩነት ውስጥ ነው። በአለም አቀፉ ተቋም ድረ ገፅ እንደተመለከተው የሁለት ሺህ ፋይሎች ውስጥ ለውሳኔ ከቀረቡት ሀምሳ አራት ፋይሎች አንዱ ጥምቀት ሲሆን፣ በሁለት ሺህ ሀያ ፋይሎች ውስጥ ለሀዳር ሁለት ሺህ አመተ ምህረት ለውሳኔ ከሚታዩት አርባ ሁለት ፋይሎች ውስጥ ኢትዮጵያ የለችበትም። በይደር ፋይል ሁለት ሺህ ሀያ ውስጥ ያለተጨማሪ ሰነዶች ርእሳቸው ከተዘረዘሩት ውስጥ ግን እነ አሸንዳ አሉበት።
ዩኔስኮ ባለ ስድስት መጠሪያውን የነሀሴ በአል የሚመለከተው ከሁለት አመት በኋላ ነው
ተቃዋሚ ፓርቲዎች በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሚያደርጓቸው የተቃውሞ ሰልፎች ተደጋጋሚና መንግስት አቋም የያዘባቸውን ጉዳዮች የሚያነሱ እንደሆኑ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስተርኒስትር ሀማርያም ደሳለኝ መንግስት ለእያንዳንዱ ሰልፍ ጥበቃ ማድረግ ስለማይችል ሰልፎቹ በተለመደው መልኩ ላይቀጥሉ እንደሚችሉ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስተር ሀይለማርያም ደሳለኝ ትናንት በፅቤታቸው ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ተቃዋሚ ፓርቲዎቹ የሚያነሷቸው ጥያቄዎች የራሳቸው የፓርቲዎቹ ሳይሆኑ የሌሎች ሀይሎች እንደሆኑ ገልፀዋል።ፓርቲዎቹ ሰልፍ ማካሄድ ህገመንግስታዊ መብታቸው መሆኑን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስተርኒስትሩ መንግስት በተደጋጋሚ ጥበቃ ሲያደርግ ቢቆይም በሰልፎቹ የሚነሱት ጥያቄዎች ፋይዳ ቢስ ከመሆናቸውና ከፓርቲዎቹ ብዛት አንፃር መንግስት በቀጣይ ለሰልፎች ጥበቃ ለማድረግ የሚቸገርበት ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚችል አስረድተዋል።ተቃዋሚ ፓርቲዎች መንግስት በተደጋጋሚ ምላሽ የሰጠባቸውን ጥያቄዎች መላልሰው የሚያቀርቡት በመንግስት ላይ ጫና በመፍጠር አቋሙን ለማስቀየር በማሰብ ሊሆን ይችላል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስተርኒስትሩ ይሄ ግን በፍፁም የማይሳካ ሀሳብ ነው ብለዋል። ግንቦት ሰባት በቅርቡ መንግስትን ለመጣል ወታደራዊ እርምጃ እንደሚወስድ በይፋ መግለፁን በተመለከተ ተጠይቀው ሲመልሱም የፓርቲው አመራሮችና ደጋፊዎች ተጨባጭ ያልሆነ ህልም ውስጥ ሆነው የተናገሩት ነገር እንደሆነና ከህልማቸው ሲነቁ እውነታውን እንደሚገነዘቡት ጠቅላይ ሚኒስተርኒስትሩ ተናግረዋል። ኢህአዴግ ውስጥ መከፋፈልና የሀይል መጠባበቅ አለ የሚለውን መረጃ በተመለከተም ይህ የአንዳንድ አፍራሽ ሀይሎች ከንቱ ምኞትና ተጨባጭ ያልሆነ አሉባልታ ነው ሲሉ አጣጥለውታል።
ጠቅላይ ሚኒስተርኒስትር ሀይለማርያም የተቃዋሚ ፓርቲዎች ሰልፍ ላይቀጥል ይችላል አሉ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ አንድ ሺህ አራት መቶ አርባ አራትኛው የኢድ አልፈጥር ረመዳን በአል በሰላም እንዲጠናቀቅ የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ሀይል አስፈላጊውን ዝግጅት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን አስታውቋል። የበአሉ የኢድ ሶላት ተጀምሮ እሰከሚጠናቀቅ የሚዘጉ መንገዶች እንደሚኖሩም የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል። በየአመቱ ከሚከበሩ ሀይማኖታዊ በአላት አንዱ የሆነው የኢድ አልፈጥር ረመዳን በአል በመላው የእምነቱ ተከታዮች ዘንድ በጉጉት የሚጠበቅ በአል መሆኑን የጋራ ግብረ ሀይሉ ገልጿል። በአዲስ አበባ ስታዲዮምና በዙሪያው የሚከናወነው የኢድ ሶላት ላይ በርካታ የእምነቱ ተከታዮች የሚታደሙበት እንደመሆኑ የሶላት ስነ ስርአቱ በሰላም እንዲጠናቀቅ እና የበአሉ ድባብ ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ እንዲከበር ወቅታዊውን የፀጥታ ሁኔታ ያገናዘበ እቅድ አውጥቶ ወደ ስራ መግባቱን የጋራ ግብረ ሀይሉ አስታውቋል። የእምነቱ ተከታዮችና በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች በተለይም ለኢድ ሶላት የሚመጣውን ህዝበ ሙስሊም በማስተባበር እና የበአሉን ድባብ ሊያደፈርስ የሚችል ችግር እንዳያጋጥም ከፀጥታ አካላት ጋር ተቀናጅተው በመስራት የሚያደርጉት ተሳትፎ የጎላ መሆኑንም የጋራ ግብሩ ሀይሉ ጠቅሷል። በዘንድሮው በአልም ይህንኑ አጠናክሮ ለማስቀጠል ከእምነቱ አባቶች እና ከወጣቶች ጋር ተገቢው ውይይት መደረጉ ነው የተመላከተው።፡ የእምነቱ ተከታዮች በየአካባቢያቸው በአሉን ሲያከብሩም ሆነ ወደ ኢድ ሶላቱ ሲመጡ እንደወትሮው ሁሉ የፖሊስን መስተንግዶና ትእዛዝ በማክበር ተባባሪ እንዲሆኑ እና የበአሉ ስነ ስርአት በሰላም እንዲጠናቀቅ መላው የከተማችን ነዋሪዎች የተለመደ ትብብራቸውን እንዲያደርጉ የጋራ ግብረ ሀይሉ ጥሪ አቅርቧል። በዚህ ህብረተሰቡ ለሰላም እንቅፋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮችን ሲመለከት በ አንድ ሀያ ስድስት አርባ ሶስት ሀምሳ ዘጠኝ ፣ አምስት ሀምሳ ሁለት ስልሳ ሶስት ሁለት ሶስት፣ አምስት ሀምሳ ሁለት አርባ ሰባ ሰባት፣ አምስት ሀምሳ አራት ስላሳ ስድስት ሰባ ስምንት እና አምስት ሀምሳ አራት ስላሳ ስድስት ሰማኒያ አንድ እንዲሁም በዘጠኝ መቶ ሰማኒያ ሰባት፣ ዘጠኝ መቶ ዘጠና አንድ እና ስምንት መቶ ነፃ የስልክ መስመሮች ጥቆማ በመስጠትና አስፈላጊውን ትብብር በማድረግ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ የጋራ ግብረ ሀይሉ መልእክት አስተላልፏል። በተጨማሪም የኢድ አልፈጥር ረመዳን በአል የኢድ ሶላት ተጀምሮ እሰከሚጠናቀቅ ለተሸከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች እንደሚኖሩ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል። የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር አሽከርካሪዎች ከዚህ በታች የተገለፁት መንገዶች ዝግ መሆናቸውን ተገንዝበው ሌሎች አማራጮችን እንዲጠቀሙም አሳስቧል። በዚህም መሰረት ከቦሌ አየር መንገድ በሚሊኒየም አዳራሽ ወደ ስታዲዮም የሚወስደው መንገድ ደንበል ሲቲ ሴንተር ኦሎምፒያ አደባባይ አከባቢ ከመገናኛ ፣ በሀያ ሁለት ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከቦሌ መድሀኒያለም፣ በአትላስ ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኡራኤል ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ባሻ ወልዴ ችሎት ወይም ፓርላማ መብራት ከፒያሳ አካባቢ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቸርችል ጎዳና ቴዎድሮስ አደባባይ ከተክለ ሀይማኖት በሜትሮሎጂ ወደ ስታዲዮም የሚወስደው መንገድ ሜትሮሎጂ መስሪያ ቤት አካባቢ ከተክለ ሀይማኖት ፣ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የሚወስደው መንገድ ጥቁር አንበሳ የኋላ በር አካባቢ ከሲኒማ ራስ በጎላ ሚካኤል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ጎላ ሚካኤል መስቀኛ ከጌጃ ሰፈር ፣ ጤና ጥበቃ፣ ብሄራዊ ቲያትር የሚወስደው መንገድ ጎማ ቁጠባ ከባሻ ወልዴ ችሎት በኦርማ ጋራዥ ወደ ፍል ውሀ መስኪድ የሚወስደው መንገድ ንግድ ማተሚያ ቤት ከጎፋ በቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ወደ ለገሀር አዲሱ መንገድ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን መስቀለኛው ላይ ከጦር ሀይሎች ፣ ልደታ ፣ ፖሊስ ሆስፒታል ሜክሲኮ አደባባይ ከሳሪስ በጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለቀላል መኪና የቀድሞ አራተኛ ክፍለ ጦር አካባቢ እንዲሁም ለከባድ መኪና አጎና ሲኒማ አካባቢ ይለፍ ለሌላቸው ተሽከርካሪዎች ከሌሊቱ አስር ሰአት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ዝግ በመሆኑም ህብረተሰቡ ከፖሊስ የተሰጠውን መረጃ ተገንዝቦ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀም እና ለትራፊክ ፖሊስ አባላት ትእዛዝ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል። ለእምነቱ ተከታዮች በአሉ በሙሉ በአሉ የፍቅርና የሰላም እንዲሆን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ሀይል መልካም ምኞቱን ገልጿል።
በመዲናዋ የኢድ ሶላት ተጀምሮ እሰከሚጠናቀቅ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ሆኑ
የአፍሪካ የሆቴል ኢንዱስትሪ መሪዎች በየአመቱ በሚያደርጉት ቋሚ አፍሪካ ሆቴል ኢንቨስትመንት ፎረም ኤኤችአይአፍ ተገናኝተውበአፍሪካ ሆቴሎችን ማሳደግና ማስፋፋት በሚቻልባቸው ነጥቦች ላይ ተመካክረዋል። በአለም አቀፍ ደረጃ ትስስር ያላቸውበርካታ እውቀትና ልምድ ያካበቱ ከፍተኛ የሆቴል ስራ አስፈፃሚዎች ዋና ዋና የአለማችን የሆቴል ኢንቨስተሮችና በዘርፉ የላቀ እውቀትያላቸው በርካታ አማካሪ ባለሙያዎች በጉባኤው ተሳትፈው በአፍሪካ ሆቴሎችን ለማስፋፋት አስፈላጊ ናቸው ያሏቸውን ነጥቦችተናግረዋል። የፎረሙ አዘጋጅ ቤንች ኢቨንት የጉባኤው ተሳታፊዎች ቅድሚያ ሊሰጧቸው ይገባል ብለው የወሰኗቸውን ነ ጥቦች የረዥም ጊ ዜ እ ቅድ ፋ ይናንስ እ ድገት ልማት ህዝብ እ ና ልማት በ ማለት በ አምስት ክ ፍሎች አ ጠቃሎ አ ቅርቧቸዋል።ሀ የረዥም ጊዜ እቅድየአፍሪካ መንግስታት የአገራቸውን ሰፊ የቆዳ ሽፋን ያካለለ የረዥም ጊዜ እድገት ልማት ስትራቴጂ መንደፍ አለባቸው። ይህን ሲያደርጉ በአገሪቷ ውስጥ አዲስ የተሰራ ወይም ማስፋፊያ የተደረገለት ሆቴል ያለበትን ደረጃ በከፍተኛ እርግጠኝነት ማወቅ ያስችላቸዋል። ይህም በተወሰነ አካባቢ ብቻ የሚደረገውን የኢንቨስትመንት ክምችት ስጋት በማስቀረት በመላ አገሪቱ የተመጣጠነ ልማትና እድገት እንዲኖር ያስችላል።በመሰረተ ልማት ላይ ኢንቨስት ማድረግ የአፍሪካ መንግስታት በራሳቸው ተነሳሽነት መዳረሻ እሆናለሁ ብለው ሩቅ በማለም በመሰረተ ልማት በመንገድ ስልክ ኢንተርኔት ውሀ መብራት ላይ ኢንቨስት ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። መሰረተ ልማት ሲያሟሉ በራእያቸው የተገረሙና የተደነቁ ቱሪስቶችን የቢዝነስ ሰዎችንና ኢንቨስተሮችን መሳብ ይችላሉ። በጣም ጠቃሚ ከሆነው የትራንስፖርት መሰረተ ልማት አንዱ የአውሮፕላን ማረፊያ ኤርፖርት ነው። በዚህ ረገድ በአንጐላ በኬንያ በናይጄሪያ በሯንዳና ሴኔጋል ኮትዲቯር አዳዲስ አውሮፕላን ማረፊያዎች እየተሰሩ ነው።ለ ፋይናንስለፋይናንስ ችግር እጥረት ወደ ውጪ ተመልከቱ የአፍሪካ መንግስታትና ኢንተርፕርነሮች ለሚያስፈልጋቸው የገንዘብ እጥረት መፍትሄ እንዲሆናቸው ወደ ውጭ አገር መመልከት ወይም በአገር ውስጥ በፕሮጀክታቸው አካባቢ ያሉ ኢንቨስተሮችን መቃኘት ይኖርባቸዋል። ምክንያቱ ደግሞ ብዙ አለም አቀፍ ኢንቨስተሮች ከሌሎች አገሮች ጋር በንፅፅር ሲመለከቱ ብዙ የአፍሪካ አገሮች እያሳዩ ባሉት ከፍተኛ እድገት እየተሳቡ ናቸው።በአፍሪካ ኢንቨስት ያደርጋሉ ተብለው የሚጠበቁት ጥሩ የአየር ትራንስፖርት ትስስር ካላቸው መካከለኛ ምስራቅ አገሮችና በአህጉሩ የተስፋፋ ቢዝነስ ካላት ቻይና ነው።ሆቴሎችን በንብረትነት ማየት በተለምዶ ሆቴሎች በራሳቸው እንደ ንብረት አይታዩም ነበር። አሁን ግን ሁኔታዎች እየተቀየሩ ነው። የሆቴል ባለቤት መሆን በረዥም ጊዜ አገር የቱሪስት ወይም የቢዝነስ መዳረሻ ስትሆን እኔም ውጤታማ እሆናለሁ ብሎ በረዥሙ ማሰብ ነው። ይህ ብቻ አይደለም። ኢኮኖሚው ደካማ ቀዝቃዛ በሆነበት አመት ከተገኘው ትርፍ ላይ እንደገና ኢንቨስት ማድረግ ለታክስ የሚከፈለውን ገንዘብ በከፍተኛ ደረጃ መቀነስ ማዳን ነው።ሀ እድገት ልማትየእድገት ሂደትን ማፋጠን ኢንቨስተሩ አንድን ንብረት ለመግዛት ውል ከተፈራረመ በኋላ ወዲያውኑ ቢዝነሱን ከጀመረ በንግዱ ወይም በስራው የበለጠ ስኬታማ የመሆን እድሉ ከፍተኛ ነው። በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ በ አመት ቢዝነሴን ሆቴሌን እዚህ ደረጃ አደርሳለሁ ማለት አይታወቅም። በአንፃሩ ግን በሰንሰለት የተሳሰሩ ሆቴሎች ከምንም ተነስተው በወራት ፍጥነት ከፍተኛ ደረጃ የሚደርሱበትን የኮንስትራክሽን ሞጁል ውጤት ለማግኘት እየተመራመሩ ነው።የአየር መስመር መክፈት አንዲት አገር የበለፀገች የቱሪስት ወይም የቢዝነስ መዳረሻ ለመሆን የአየር መስመር በጣም አስፈላጊ ነው። በኢኮኖሚ የበለጠ ለመበልፀግ የአየር ትራንስፖርት ዋነኛው አንቀሳቃሽ ሀይል መሆኑን በርካታ ጥናቶች አመልክተዋል። ስለዚህ የበለጠ የአየር ትስስር መፍጠር ያስፈልጋል።መ ህዝብከአገር ውስጥ ኢንቨስተሮች ጋር ማስተሳሰር ብዙ የውጭ ኢንቨስተሮች ጠንካራ ወይም ሁነኛ ሸሪክ ካላገኙ በአፍሪካ አዲስ ኢንቨስትመንት መጀመር አይፈልጉም። ስለዚህ እነዚህን ሁለት ወገኖች ማስተሳሰር ቅድሚያ የሚሰጠው ስትራቴጂ መሆን አለበት።ኢንዱስትሪዎችን ማቀራረብ አዲስ ሆቴል ለማቋቋም የሚያነሳሱ ውይይትን መፍጠር የሚችሉ ዝግጅቶችን መደገፍ ያስፈልጋል። እንዲሁም ጠቃሚ የሆኑ አዳዲስ ሰዎችን በማስተዋወቅ አነስ ያለ እውቀትና ልምድ ያላቸው ኢንቨስተሮች ስለሁሉም የስራ ሂደቶች እንዲያውቁ ማድረግ ያስፈልጋል።ረ ባህልፖለቲካው የተረጋጋ መሆኑን ማስተዋወቅ ለአንድ አገር እንግዳ ተቀባይነትና ለኢንቨስትመንት ምቹነትና ለኢንዱስትሪው ሰላምየተረጋጋ ፖለቲካ እጅግ ወሳኝ ናቸው። በሰሜን አፍሪካ አገሮች የተከሰተው አይነት የፖለቲካ ብጥብጥ ያለመረጋጋት በአገሮቹ ሊካሄዱ የነበሩ የሆቴል ኢንቨስትመንቶች እንዲዘገዩ አድርጓል። እውነተኛ አለም አቀፍ ኢንቨስተሮች ገንዘባቸውን ማፍሰስ የሚፈልጉት የተረጋጋ ሰላምና ፖለቲካ ባለበት አገር ነው። ስለዚህ የአፍሪካ መንግስታት በአገራቸው የተረጋጋ ፖለቲካ እንዲኖር ከልብ መጣር አለባቸው። የሚታመንባችሁ ሆኑ እምነት ፍጠሩያለመታደል ሆኖ በአንዳንድ የአፍሪካ ክፍሎች እቃዎች እንደሚጠፉና የተገባ ቃል እንደማይከበር በጣም ብዙ ታሪኮች ይነገራሉ።ይህ ነገር ሁሉንም የቢዝነስ ሰዎች እንዲሰጉ ያደርጋቸዋል። መታመንን ለመፍጠርና ለመገንባት የሚደረገው ሂደት እንደ ፈታኝ የባህል ለውጥ ስለሚቆጠር እጅግ የላቀ ጥንካሬና ትግል ይጠይቃል።ስለዚህ በቆራጥነት መስራት አማራጭ የሌለው ነገር ነው። እነዚህ ሁሉ ከውይይቱ የተገኙ አስተያየቶችና ሌሎች ተመሳሳይ ጉዳዮች ከሴፕቴምበር እስከ ኦክቶበር ቀን አመተ ምህረት በአዲስ አበባ በሚደረገው አለም አቀፍ የኤኤችአይኤፍ ጉባኤ ቀርበው በሚኒስትሮች በከፍተኛ የስራ ሀላፊዎችና ከደህንነት ከሆስፒታሊቲ ኢንዱስትሪ በመጡ ተሳታፊዎች ጠንካራ ውይይት እንደሚደረግባቸው ይጠበቃል።
በአፍሪካ የሆቴል ኢንዱስትሪውን ለማሳደግ ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡ ነጥቦች
የእስራኤሉ ትድሀር ኤክስካቬሽን ኤንድ ኧርዝ ሙቪንግ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ባለቤት፣ ጉቦ በመስጠትና ታክስ ስወራ ወንጀል ተጠርጥረው ሀምሌ ቀን ሁለት ሺህ ሰባት አመተ ምህረት ክስ ተመሰረተባቸው።የፌዴራል የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን አቃቤ ህግ፣ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት ክስ የመሰረተባቸው፣ የኩባንያው ባለቤትና ስራ አስኪያጅ ሚስተር ሚናሼ ሌቪና ኩባንያቸው ትድሀር ኤክስካቬሽን ኤንድ ኧርዝ ሙቪግ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ናቸው።ሚስተር ሌቪ ክስ የተመሰረተባቸው፣ ለኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ሶስት ኦዲተሮች ለእያንዳንዳቸው አምስት መቶ ሺህ ብር በድምሩ አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር በመስጠትና ለባለስልጣኑ ሊከፍሉ ይገባ ከነበረው ታክስ ሀምሳ ሁለት ሰባት መቶ ዘጠና ሰባት ሰባት መቶ ሰባ ዘጠኝ ብር ውስጥ አርባ ስድስት ስምንት መቶ ሰማኒያ ሶስት ዘጠኝ ብር ለግል ጥቅማቸው በማዋል ተጠርጥረው መሆኑን የኮሚሽኑ አቃቤ ህግ ክስ ያስረዳል።የባለስልጣኑ ኦዲተሮች ከግለሰቡ ጋር በመመሳጠር፣ ለመንግስት ገቢ መደረግ የሚገባውን ገንዘብ ቀንሰው ስድስት አንድ መቶ ሰባት መቶ ሰባ ብር ብቻ እንዲከፍሉ በማድረግ በመንግስት፣ በህዝብ ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸውንም ክሱ ይገልፃል።ተጠርጣሪዎቹ የዋስትና መብታቸው ታልፎ በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ፍርድ ቤቱ ትእዛዝ ሰጥቷል። የድርጅቱ ባለቤት በአጠቃላይ ከአንድ መቶ አርባ ሚሊዮን ብር በላይ የታክስ ገቢ አጭበርብረዋል ተብለው የተጠረጠሩ ሲሆን፣ የወንጀሉን ዝርዝር ድርጊት የሚያስረዱ ክሶች ቀርበውባቸዋል።ትድሀር ኤክስካቬሽን ኤንድ ኧርዝ ሙቪንግ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማሀበር፣ በአዲስ አበባ በመገንባት ላይ ከሚገኙት መንገዶች ውስጥ ከዊንጌት እስከ አቡነ ጴጥሮስ ማዘጋጃ ቤት ድረስ ከስድስት ኪሎ አንበሳ ግቢ እስከ ፈረንሳይ ጉራራና ከመገናኛ የውሀ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ድረስ ያሉትን መንገዶች በመገንባት ላይ ያለ ኩባንያ ነው።የክስ መቃወሚያ ካለ ለማሰማትና ክሱን ለማንበብ ለሀምሌ ሀያ ሶስት ቀን ሁለት ሺህ ሰባት አመተ ምህረት ተቀጥሯል።
የእስራኤሉ ትድሀር ኮንስትራክሽን ኩባንያ ባለቤት በጉቦና ታክስ ስወራ ተጠርጥረው ተከሰሱ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ አንድ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በህንድ የሚማሩ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል ከሁለት መቶ ሀምሳ ሺህ ብር በላይ ለገሱ። በሀገሪቱ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ ከአንድ ሺህ የሚበልጡ ተማሪዎች ናቸው በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የሚውል የገንዘብ ድጋፍ ያደረጉት። በህንድ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ዶክተር ትዝታ ሙሉጌታ እንደገለፁት፥ ኤምባሲው በኢሜል፣ በፌስቡክ፣ በተማሪ አደረጃጀት እንዲሁም በምስል የተቀነባበረ ዘዴ በመጠቀም ለተማሪዎቹ ስለወረርሽኙ አስከፊነትና ጥንቃቄ እያስገነዘበ ነው። የቫይረሱ ስርጭት በቁጥጥር ስር እስከሚውል ድረስም ይህ ስራ እንደሚቀጥል አምባሳደር ትዝታ ተናግረዋል። ተማሪዎቹ ላደረጉት የገንዘብ ድጋፍ በኤምባሲው ስም አምባሳደሯ ምስጋና አቅርበዋል።
በህንድ የሚማሩ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል ከሁለት መቶ ሀምሳ ሺህ ብር በላይ ለገሱ
ሁለት መቶ ሰባ አንድ የትግሬ ወያኔ መንግስት እስከምናውቀው ድረስ የኢትዮጵያን ብር የሚሳትመው ሱዳን ውስጥ ነው። ትግሬ ወያኔ ይኽን ያደረገበት ምክኒያት ግልፅ ነበር። አሁን መጠነኛ ለውጥ ከመጣ በሀላ አብይ ብሩን እንዲቀይር ብዙ ግፊት ቢደረግም የሚሰማ አእምሮ አልተገኘም።በተለይ አሁን የወያኔው የነገር አባት በሽር ስልጣን ወርዶ ሱዳን ቀውስ ውስጥ መሆኗ እየታወቀ እነ አብይ የብሩን ህትመት በተመለከተ ፀጥ ማለታቸው ያሳዝናል። የበሽር ደጋፊ የፀጥታ አባላት የሱዳን አዲስ ኖቶችን አትመው ካርቱም ውስጥ እየረጩ ነው። የኢትዮጵያንም ብር እንዲሁ አትመው ቢረጩ ምን ዋስትና አለ ዛሬ የሱዳን ጦር ሀይሎች ካርቱም ላይ ከድሮ የፀጥታ መስሪያ ቤት ጠቅላይ መምርያ ውስጥ የያዘውን አዲስ የሱዳን ኖቶች ቪዲዎ ተመልከቱ። ሁለት መቶ ሰባ አንድ
ሱዳን ውስጥ የሚታተመው የኢትዮጵያ ብር ህትመት ጉዳይ አሳሳቢ ነው
መንግስት በተያዘው በጀት አመት የመጀመርያው ስድስት ወራት ከእርዳታና ከብድር ሰማኒያ ዘጠኝ ነጥብ ሶስትአራትስድስት ቢሊዮን ብር ማግኘቱን፣ ከዚህ ውስጥ ሀምሳ ነጥብ አራትአራትሶስት ቢሊዮን ብር እንደተለቀቀለት አስታወቀ። በመጀመርያው ስድስት ወራት ከአለም አቀፍ የልማት ተቋማት መልቲ ላተራል በብድር ሀያ ነጥብ ዘጠኝሰባትአንድ ቢሊዮን ብር፣ ከእርዳታ ስላሳ አራት ነጥብ አምስትስምንት ቢሊዮን ብር በድምሩ ሀምሳ አምስት ነጥብ አምስትአምስት ቢሊዮን ብር አዲስ እርዳታና ብድር መገኘቱን፣ የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ሀጂ ኢብሳ አርብ የካቲት ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። በተመሳሳይ ከመንግስታት ትብብር ባይላተራል ምንጮች ነጥብ ዘጠኝሰባት ቢሊዮን ብር በብድር፣ ነጥብ ስምንትሁለትስምንት ቢሊዮን ብር በእርዳታ፣ በድምሩ ስላሳ ሶስት ነጥብ ሰባትዘጠኝስምንት ቢሊዮን ብር አዲስ ብድርና እርዳታ ተገኝቷል ብለዋል። ከሁለቱም የፋይናንስ ምንጮች ባለፉት ስድስት ወራት ሰማኒያ ዘጠኝ ነጥብ ሶስትአራትስድስት ቢሊዮን ብር መገኘቱን፣ ከዚህ ግኝት ውስጥ ብድር ስላሳ ሰባት ነጥብ ዘጠኝአራትአንድ ቢሊዮን ብር፣ እርዳታ ሀምሳ አንድ ነጥብ አራትአምስት ቢሊዮን ብር ድርሻ መያዛቸው ተገልጿል። ከዚህ ገንዘብ ውስጥ ፈሰስ ወይም የተለቀቀው ሀምሳ ነጥብ አራትአራትሶስት ቢሊዮን ብር መሆኑን አቶ ሀጂ ገልፀዋል። ከመልቲላተራል ምንጮች ብድርና እርዳታ ሀያ ነጥብ ዘጠኝስድስትሰባት ቢሊዮን ብር፣ ከባይላተራል ምንጮች ደግሞ በብድርና እርዳታ ሀያ ዘጠኝ ነጥብ አራትሰባትስድስት ቢሊዮን ብር መለቀቁን አቶ ሀጂ ጨምረው ገልፀዋል። በግማሽ አመቱ የተለቀቀው ገንዘብ ካለፈው በጀት አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በሀያ አንድ ነጥብ ስምንትሰባትሶስት ቢሊዮን ብር አርባ ሶስት ነጥብ ሶስትስድስት በመቶ ብልጫ አለው፤ ሲሉ አስረድተዋል። በግኝትም ሆነ በፍሰት የሚመጣው ገንዘብ በአሜሪካ ዶላር የተሰላ ሲሆን፣ በበጀት አመቱ መጀመርያዎቹ ሶስት ወራት የተገኘውና የተለቀቀው ገንዘብ በወቅቱ በነበረው አንድ ዶላር ሀያ ሶስት ነጥብ ሁለትአምስትሁለት ብር ተመን መሆኑን፣ በቀጣዮቹ ሶስት ወራት የተሰላው ደግሞ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ከጥቅምት አንድ ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ጀምሮ ብር ከዶላር ጋር ያለው ምጣኔ በ በመቶ እንዲቀንስ ተደርጎ በወጣው ሀያ ስድስት ነጥብ ስድስትዘጠኝዘጠኝአምስት ብር ሂሳብ መሆኑ ተገልጿል። መንግስት በቅርቡ ካፀደቀው ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት ጋር በድምሩ ለሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ሶስት መቶ ስላሳ አራት ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ብር አመታዊ በጀት ማፅደቁ ይታወሳል። በተለይ ከውጭ እርዳታ አንድ መቶ ስላሳ ሰባት ስምንት መቶ ሰባ ስምንት መቶ ሀያ ስድስት ብር፣ ከውጭ ብድር ደግሞ ሀያ ስምንት ስድስት መቶ ስድስት መቶ ሀያ ሁለት ሰባት መቶ ብር እንደሚገኝ ታሳቢ ተደርጎ የበጀት አዋጅ መዘጋጀቱ አይዘነጋም። ከውጭ በብድርም ሆነ በእርዳታ ይገኛል ተብሎ ታቅዶ የነበረው አርባ አምስት ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ብር ነበር።
መንግስት በግማሽ አመቱ ሰማኒያ ዘጠኝ ነጥብ ሶስትአምስት ቢሊዮን ብር በብድር እርዳታ ማግኘቱን አስታወቀ
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቤተ መዛግብት እና ቤተ መፃህፍት ኤጀንሲ የስነ ፅሁፍ ውጤቶች አውደ ርእይ እና የምክክር መድረክ እንደሚያዘጋጅ ለዋልታ ቴሌቪዥን ገልጿል።ኤጀንሲው አውደ ርእዩን የሚያዘጋጀው ከደቡብ ክልል ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ፣ ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር እና ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ሲሁን ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል በሚል መሪ ቃልይከበራል።ኤጀንሲው እንዳለው ዝግጅቱ ከመጋቢት ጀምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት የሚቆይ ሲሆን የባህልና ቱሪዝም ቢሮዎችን ጨምሮ በንባብ ዙሪያ የሚሰሩ የግልና የመንግስት ተቋማት፣ ደራሲያን እና የመገናኛ ብዙሀን ይሳተፋሉ።በዝግጅቱ የስነ ፅሁፍ ውጤቶች ለእይታና ለሽያጭ የሚቀርቡ ሲሆን ከንባብ እና ከፅሁፍ ሀብቶች ጋር የተያያዙ ጥናታዊ ፅሁፎችም ይቀርባሉ ነው የተባለው። ዝግጅቱ ሲካሄድ በደቡብ ክልል ለሶስተኛ ጊዜ በሀዋሳ ከተማ ደግሞ ለሁለተኛ ጊዜ እንደሆነ ኤጀንሲው ለዋልታ በላከው መግለጫ አስታውሷል።
ብሄራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ መፃህፍት ኤጀንሲ የስነ ፅሁፍ ውጤቶች አውደ ርእይ ሊያዘጋጅ ነው
ሀሙስ ጅዳ ላይ ያልቀናው ቦንድ ሽያጭ ትናንት ሪያድ ከተማም ከሽፏል።የሁለቱም ከተሞች እቅድ መክሸፍ ምክንያት የህወሀት ሰዎች ጉልበት የመጠቀም ስህተት መሆኑ ያመሳስለዋል።ጅዳ ኮሚዩኒቲ አዳራሽ አቶ ከድር የሚባል የህወሀት ሰው አንዲትን ስብሰባ የምትሳተፍ እህት በጥፊ መትቶ ሞባይሏን ለመንጠቅ ባደረገው ትንቅንቅ ስብሰባው ወደሁከት ተቀይሮ መበተኑ ይታወሳል።ሪያድ ስለሆነው ደግሞ እንከታተል ።የትናንቱ የሪያድ ስብሰባ ለኤምባሲው ሩቅ ያልሆኑ ከየብሄሩ ሀያ ሰዎች በድምሩ አንድ መቶ ሀምሳ ሰዎች ብቻ በሚስጥር የተጠሩበት ነበር።መረጃው ለህዝብ ይፋ ከተደረገ በኋላ በርካታ ሰው ወደኮሚዩኒቲው አዳራሽ በማምራት ለመግባት ይጠይቃል።ከመግቢያ በር የጥሪ ካርድ አምጡ ይባላል ።የለንም ይላል ህዝብ።ከየትኛው ብሄር ናችሁብለው በረኞች ሲጠይቁ ኢትዮጵያውያን ነን።ጉዳዩ እንደዜጋ ይመለከተናል።ይላሉ።በዚህ ምልልስ መሀል አንድ ሰው ሞባይል ሲቀርፅ የህወሀት አባል የሆነ ግለሰብ ይመታውና ሞባይሉን ሊነጥቀው ይሞክራል ።በር ላይ የተሰበሰበው ኢትዮጵያዊ የዚህ ህወሀት እብሪት አበሳጭቶት ግብግብ ሲጀመር ከአዳራሹ ውስጥ የነበሩ ሌሎች ህወሀቶች መቀመጫ ወንበር በማንሳት የአዳራሹ መስተዋት በመሰባበር ህዝቡን ለመደብደብ ወደውጭ ይወጣሉ።የኮሚዩኒቲው ፀጥታ አስከባሪ የሳኡዲ ፖሊሶች በመሀል ገብተው ነገሮች በቁጥጥር ስር ዋለ።የችግሩን መከሰት የሰሙት አምባሳደር መሀመድ ሀሰን መጀመርያ ላይ ፀብ ያጫረውን ሰው አምጡልኝ።የኤምባሲው ሰራተኛ ቢሆን እንኳ በህግ ይከሰሳል።አሉ።ሰውየውን ህወሀቶች አስቀድመው ቢያሸሹትም በህዝብ ጥቆማ ያሸሸው ሰው ይያዛል።አምባሳደሩ ሰውየው ህወሀት መሆኑን ሲያውቁ አፈገፈጉ።በቃ ጉዳዩን ፀውስጥ እንጨርሰዋለን።አሁን ወደጉዳያችን እንግባ።ብለው በግርግሩ ያለጥሪ ከገቡት ሰዎች ጭምር ስብሰባው ተጀመረ።ገና እንደተጀመረ አንድ ሰው ብድግ ብሎ ሀገራችን ውስጥ በሀይማኖታችን ምክንያት ቁምስቅል የምታሳዩን አንሶ በሰው ሀገር እንዴት ትደበድቡናላችሁብሎ እምባ እየተናነቀው ተናገረከበር ላይ የህወሀት እብሪተኞች የፈፀሙት የንቀት ድርጊት ከዚህ ሰው ንግግር ታክሎ የመንግስት ደጋፊ የሚባሉ ሰዎችን ሳይቀር አስከፍቶ እያንዳንዱ ሰው ከወንበሩ ብድግ አዳራሹን ለቆ ወጣኢትዮጵያ የግል መኝታ ቤታቸው የምትመስላቸውና በሌላው ዜጋ የሀገር ባለቤትነት የማያምኑ ጭፍን የህወሀት ግልፍተኞች የሪያድና ጅዳን የህዳሴ ግድብ የልማት ውይይትየቦንድ ሽያጭ በዚህ መልኩ አኮላሽተውታል
የሪያዱ ሚስጥራዊ ቦንድ ሽያጭ ከሸፈ
አዲስ አበባ ፣ ጥር ሀያ ሁለት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢሲ ነጥብ አንድ ኪሎ ግራም የብር ጌጣጌጥ ቀረጥ ሳይከፈልበት ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ሲሞከር ተያዘ። ጌጣጌጡ ሊያዝ የቻለው ቀረጥ ሳይከፈልበት ከዱባይ ወደ ሀገር ውስጥ ሊገባ ሲል በቦሌ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት በጉምሩክ ሰራተኞች በተደረገ ፍተሻ ነው። የብር ጌጣጌጡ ከዱባይ በተነሱ ሶስት መንገደኞች ኪሎ ግራም በጃኬት መልክ በተሰራ ልብስ፣ አንድ ነጥብ አንድ ኪሎ ግራም በልብስ በመደብቅና፣ ቀሪው ሁለት ኪሎ ግራም ጥፍጥፍ ብር ደግሞ በድብቅ ለማስገባት ሲሞከር የተያዘ ነው። ዋጋቸውም ሺህ ሰባት መቶ ሀያ አራት የአሜሪካ ዶላር ሲሆን፥ በመደበኛ ታክስ ደግሞ ግምቱ አምስት መቶ ስልሳ ስድስት ሺህ ስምንት መቶ ብር ነው ተብሏል። በዚህም የተጠረጠሩ አንድ የውጭ ሀገር ዜጋ እና ሁለት ኢትዮጵያውያን በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሚገኝ ከገቢዎች ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ነጥብ አንድ ኪሎ ግራም የብር ጌጣጌጥ ቀረጥ ሳይከፈልበት ወደ ሀገር ውስጥ ሊገባ ሲል ተያዘ
የፌዴራሉ ዋና ኦዲተር ማክሰኞ ግንቦት ሀያ ሁለት ቀን ሁለት ሺህ ዘጠኝ አመተ ምህረት ባቀረበው ሪፖርት፣ የጥፋተኝነት ስሜት የተሰማቸው የፓርላማ አባላት ራሳቸውንና ምክር ቤቱን ጭምር ወቀሱ።ዋና ኦዲተሩ አቶ ገመቹ ዱቢሶ በሁለት ሺህ ስምንት በጀት አመት በመስሪያ ቤታቸው የተካሄዱትን የፋይናንስ ህጋዊነት የክዋኔ ኦዲቶች አስመልክቶ ሪፖርት አቅርበዋል። በሁለት ሺህ ሰባት አመተ ምህረት ከቀረበው ሪፖርት ጋር ሲነፃፀር የባሱ የህግ ጥሰቶች በመስተዋላቸው፣ እንዲሁም ከአመት አመት የአስፈፃሚው የህግ ጥሰትን ፓርላማው ማስቆም ባለመቻሉ ያዘኑና የጥፋተኝነት ስሜት የተሰማቸው የምክር ቤት አባላት ወቀሳቸውን ሰንዝረዋል።የህወሀት ተወካይ የሆኑት ወይዘሮ ሙሉ ገበረ እግዚአብሄር ዋና ኦዲተር ገመቹና ተቋማቸው ያቀረቡትን ሪፖርት አድንቀው፣ የተሰጠውን ተልእኮ የሚፈፅም የፓርላማው ቀኝ እጅ እንደሆነ መስክረዋል።ይሁን እንጂ ኦዲተሩ የሚያቀርቡትን ሪፖርት እንደ መረጃ ወስዶ በአስፈፃሚው አካል ላይ እርምጃ በመውሰድ፣ የህዝብ ሀብትና ንብረትን ከብክነት ማዳን አለመቻሉን በቁጭት ተናግረዋል። ክቡር አፈ ጉባኤ ይህ ጨዋታ ማብቃት አለበት፤ ሲሉ በአፅንኦት ተናግረዋል። ዋና ኦዲተር ስራውን በድፍረትና በልዩ ሁኔታ ሲሰራ እኛ ስራችንን እየሰራን አይደለንም። የሚመለከተውን አካል ተጠያቂ ማድረግ አለብን። የተከበሩ አፈ ጉባኤ ህዝብ ይጠይቀናል፤ ሲሉ አሳስበዋል።በየአመቱ በኦዲተሩ የሚቀርበው የኦዲት ሪፖርት ትልቅ ጥናታዊ ፅሁፍ ይወጣዋል ያሉት ወይዘሮ ሙሉ፣ ለዚህ እኛ ተጠያቂ ነን፤ ብለዋል። የብአዴን ተወካይ አቶ ታደሰ መሰሉ በበኩላቸው፣ ኦዲተር መስሪያ ቤቱ ነፃነቱን ጠብቆ እንዲሰራ ማረጋገጥ የሚችለው ሪፖርቱ በድፍረት ባስቀመጣቸው ግኝቶች መሆኑን ተናግረዋል።በየአመቱ ደንብና መመርያ የማያከብር፣ የግዥ ስርአት የማይከተል የስራ አስፈፃሚው ባለስልጣን ማነው የሚቀጣኝ እያለ ነው ብለዋል። በየአመቱ ተመሳሳይ ነገር እየደገምን መሄድ የለብንም። እርምጃ መውሰድ መጀመር አለብን፤ ሲሉም አክለዋል። የኦህዴድ ተወካይ አቶ ተስፋዬ ዳባ በተመሳሳይ ባነሱት ሀሳብ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እርምጃ ለመውሰድ ቃል የገቡ በመሆኑ በሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት እርምጃ ተወስዶ ፓርላማው ሪፖርት ሊቀርብለት ይገባል ብለዋል። ዋና አቃቤ ህጉ የፓርላማ አባል በመሆናቸውና አሁንም በመሀላችን የሚገኙ ስለሆነ፣ ለጉዳዩ አፅንኦት እንደሚሰጡት እምነቴ ነው፤ ብለዋል።ዋና ኦዲተሩ ባቀረቡት ሪፖርት የፋይናንስ ህጋዊነትንና የክዋኔ ኦዲትን የተመለከቱ ግኝቶችን አቅርበዋል። የጥሬ ገንዘብ አያያዝና አጠባበቅ ትክክለኝነት ለማረጋገጥ ኦዲት ሲደረግ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ብቻ አንድ መቶ አርባ አራት ሰባት መቶ ብር ጥሬ ገንዘብ ጎድሎ ተገኝቷል ብለዋል። በሂሳብ መግለጫ ሪፖርት በተደረገውና በቆጠራ የተገኘው ጥሬ ገንዘብ መካከል በአምስት መስሪያ ቤቶች ቆጠራ ከመዝገብ ጋር ሲነፃፀር ሶስት መቶ ሰባ ዘጠኝ ነጥብ አራት ሚሊዮን ብር ጉድለት መገኘቱን በሪፖርታቸው ገልፀዋል።ባለፈው አመት ሪፖርት የስድስት መስሪያ ቤቶች ሂሳብ መግለጫ ሪፖርት የተደረገውና በቆጠራ የተገኘው ሁለት መቶ ሰማኒያ አራት ዘጠኝ መቶ ሰባ አንድ ብር ብቻ ነበረ።በሚኒስትሮች ምክር ቤት የፋይናንስ አስተዳደር ደንብ አንድ መቶ ዘጠና ሁለት ሺህ ሁለት በተደነገገው መሰረት የሰነድ ሂሳብ በወቅቱ መወራረዱ ሲጣራ፣ በአንድ መቶ መስሪያ ቤቶች በድምሩ አምስት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር በደንቡ መሰረት ያልተወራረደ ሂሳብ መገኘቱን በሪፖርታቸው አስረድተዋል።ገቢ ሰብሳቢ መስሪያ ቤቶችና አገልግሎት ሰጪዎች በገቢ ግብር፣ በቀረጥና ታክስ፣ እንዲሁም በሌሎች ገቢ መሰብሰብን በሚፈቅዱ ህጎች ገቢ የሰበሰቡ መሆኑን ለማረጋገጥ ኦዲት ሲደረግ፣ በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ብቻ አንድ ነጥብ አንድሶስት ቢሊዮን ብር ገቢ ሳይሰበሰብ መቅረቱን ሪፖርት አድርገዋል።ያልተሰበሰበ ውዝፍ ገቢን በተመለከተ በቀረቡት ሪፖርት ደግሞ አራት ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር ውዝፍ ገቢ መኖሩን አረጋግጠዋል። ደንብና መመርያ ያልተከተሉ ዘጠና አንድ መስሪያ ቤቶች ዘጠና ስምንት ነጥብ ሰባት ሚሊዮን ብር ከፍለው መገኘታቸውን፣ የግዥ አዋጅ ደንብና መመርያ ሳይከተሉ የተፈፀሙ ግዥዎችን በተመለከተ ደግሞ፣ በሰባ ዘጠኝ መስሪያ ቤቶች ሶስት መቶ ሀያ አራት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን ብር የመንግስት ግዥ አዋጅ፣ ደንብና መመርያ ሳይከተሉ ግዥ መፈፀማቸውን በሪፖርታቸው ገልፀዋል።ማስረጃ ሳይኖር በወጪ የተመዘገበ ስላሳ ስድስት ሚሊዮን ብር፣ የማማከር ፈቃድ ሳይኖር ያላግባብ ተረጋግጦ የተፈፀመ ሁለት መቶ ስልሳ ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን ብር የግንባታ ክፍያ መኖሩን ገልፀዋል።ሪፖርቱን ያዳመጠው ፓርላማው ለመጨረሻ ጊዜ ወደ እንቅስቃሴ እንደሚገባ፣ የወንጀል ይዘት የታየባቸው የኦዲት ግኝቶችም ላይ ዋና አቃቤ ህግ እንዲላክ ወስኗል።
የፓርላማ አባላት በዋና ኦዲተር ሪፖርት ሳቢያ ራሳቸውን ወቀሱ
መንግስት በግማሽ ቢሊዮን ብር ከተገዙ በኋላ የጥራት ችግር የተገኘባቸው ማዳበሪያዎች ላይ ማጣራት እያደረገ እንደሆነ የሪፖርተር ምንጮች ገለፁ። መጠናቸው ከሰባ እስከ ሰባ አምስት ቶን ይጠጋሉ ተብለው የተገመቱት ማዳበሪያዎች ካለፉት ሶስት አመታት ጀምሮ ተገዝተው እንደገቡ ተገልጿል። እነዚህ ማዳበሪያዎች አገር ውስጥ ከገቡና በየክልሉ ለሚገኙ የማዳበሪያ ማቀነበበሪያ ፋብሪካዎች ከተሰራጩ በኋላ የጥራት ችግር እንዳለባቸው እንደታወቀ፣ ሪፖርተር ያነጋገራቸው ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገልፀዋል። የጥራት ችግር ያለባቸው ማዳበሪያዎች ወደ ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች ሲገቡ ችግር እንደነበረባቸው በዚህም ሳቢያ ፋብሪካዎቹ ጉዳት ላይ እንደወደቁ ተገልጿል። ከዚህም ጋር በተያያዘ ትግራይ ክልል ውስጥ በሚገኘው የእንደርታ የገበሬዎች ሀብረት ስራ ማሀበር ስር ያለው ፋብሪካ፣ ስላሳ ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ጉዳት እንደደረሰበት የፋብሪካው ሀላፊዎች ተናግረዋል። በወቅቱ አምስት ሺህ ኩንታል የሚሆን የቦሮንና ስላሳ ሰባት ሺህ ኩንታል የፖታሽ ማዳበሪያ ከመንግስት መቀበላቸውን፣ የእንደርታ ሀብረት ስራ ማሀበር ሀላፊ አቶ ጎይቶም ከሰተ ለሪፖርተር ተናግረዋል። ነገር ግን በወቅቱ የተላኩት ማዳበሪያዎች በውስጣቸው ያለው ንጥረ ነገር ከሚፈለገው የመጠን አይነት በታች ሆኖ እንደተገኘና ገልፀዋል ማቀነባበሪያ ውስጥ ሲገቡም በመሳሪያዎች ላይ ጉዳት መድረሱን ሀላፊው ገልፀዋል። ማዳበሪያዎቹን የያዘው ከረጢት ላይ የተገኘው ዝርዝር መረጃና ውስጡ የተገኘው የተለያየ ሆኖ አግኝተነዋል፤ ሲሉ አቶ ጎይቶም አክለዋል። እንደ አቶ ጎይቶም ገለፃ፣ በአሁኑ ወቅት እነዚህ ችግር ያለባቸው ማዳበሪያዎች መጋዘን ውስጥ ተቀምጠዋል። ከእንደርታ በተጨማሪ በአማራ ክልል ያለው መርከብ የገበሬዎች ሀብረት ስራ ማሀበር፣ እንዲሁም ደቡብ ክልል የሚገኘው ወሊሶ የሀብረት ስራ ማሀበር የዚሁ ችግር ተጠቂዎች ናቸው። ከዚህም ጋር በተያያዙ መርከብ በወቅቱ ስምንት ኩንታል ቦሮን ማዳበሪያ ከመንግስት ወስዷል። ቦሮን ማዳበሪያ በታዋቂው የኖርዌይ የማዳበሪያ አቅራቢ ያራ ኩባንያ የቀረበ እንደሆነ ሪፖርተር ያነጋገራቸው ሀላፊዎች ገልፀዋል። ይህ ኩባንያ በኢትዮጵያ ረዥም ታሪክ ያለው ሲሆን፣ በተለያዩ ጊዜያት ማዳበሪያ ማቅረቡ ይታወቃል። ያቀረብነው ማዳበሪያ በተባለው የጥራት ደረጃና መጠን የቀረበ ነው፤ ሲሉ የያራ ማርኬቲንግ ዳይሬክተር ሯን ቦዛርት ለሪፖርተር በላኩት የኢሜይል መልእክት ገልፀዋል። በተወዳደርንባቸው ጨረታዎች ያቀረብናቸው ቦሮን ማዳበሪያዎች የተቀመጠላቸውን ጥራት የሚያሟሉ ናቸው፤ ሲሉም ተከራክረዋል። ማዳበሪያዎቹ በቀድሞው የግብርና ግብአት አቅራቢ ኢንተርፕራይዝ የተገዙ ሲሆን፣ ይህ ኢንተርፕራይዝ ከአመት በፊት ወደ ኮርፖሬሽንነት አድጓል። ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የኮርፖሬሽኑ ሀላፊዎች ከችግሩ ጋር በተያያዘ ግንኙነት የነበራቸው ሀላፊዎች ከቦታቸው መነሳታቸውን አስረድተዋል። ለአብነትም ከዚህ ጋር በተያያዘ የኢንተርፕራይዙ ግብርና ግብአት ገበያ ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ሽብሩ ደምሴ መነሳታቸው ታውቋል። ጉዳዩ በአሁኑ ጊዜ በእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ሚኒስቴር እየታየ ነው፤ ሲሉ የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ከፍያለው ብርሀኑ ለሪፖርተር ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት ዝርዝር ጉዳዮችን ለመናገር እንቸገራለን። ጉዳዩን በሁለት ሳምንት ውስጥ እንገልፃለን፤ ሲሉ የእርሻና የተፈጥሮ ሀብት ሚኒስትሩ እያሱ አብርሀ ዶክተር ለሪፖርተር ገልፀዋል። ሌሎች ከጉዳዩ ጋር ቅርበት ያላቸው የሪፖርተር ምንጮች እንደገለፁት ከሆነ ደግሞ፣ ችግሩ አሁን ከተነሱት ሀላፊዎች ባለፈ ሌሎችንም ይነካል። በወቅቱ ውሳኔ የሰጡ የኢንተርፕራይዙ ሀላፊዎች ተጠያቂ ሊሆኑ እንደሚችሉም ግምታቸውን ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅት ጉዳዩን በህግ ለማየት የሚመለከታቸው የመንግስት መስሪያ ቤት እየተንቀሳቀሱ እንደሆነ ተረጋግጧል። ከዚህም በተጨማሪ ከስምንት አመት ጀምሮ ከሚፈለገው መጠን በላይ ያላግባብ ወደ አገር ውስጥ ከገቡ በኋላ ክፍያ የተፈፀመባቸው ማዳበሪያዎች ጉዳይም ማጣራቱ እንደሚያካትተው ለማወቅ ተችሏል። ለአሁኑ የምርት ዘመን ብቻ ኮርፖሬሽኑ ወደ ዘጠኝ መቶ ስላሳ ስድስት ሺህ ቶን የሚጠጋ ማዳበሪያ በሁለት መቶ ዘጠና ሚሊዮን ዶላር መገዛቱ ይታወሳል።
በግማሽ ቢሊዮን ብር የተገዙ ማዳበሪያዎች ያጋጠማቸው የጥራት ችግር እየተመረመረ ነው
መኳንንት ጌጡ በከብት ንግድ ላይ ከተሰማራ ከአስር አመት በላይ አልፎታል። በጎችና ፍየሎችን ከገበሬዎች እየገዛ ለአዲስ አበባ ነጋዴዎች የሚያከፋፍለው መኳንንት በስራው ላይ ብዙ ጊዜያትን ቢያሳልፍም፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ገበያው ተገማች ባለመሆኑ ኪሳራ ውስጥ እየወደቀ መሆኑን ይናገራል። ለአብነትም ባለፈው የአዲስ አመት በአል ገበያ ይኖራል በሚል እሳቤ በከፍተኛ ዋጋ በጎችና ፍየሎችን ከገበሬዎች ገዝቶ የነበረ ቢሆንም፣ ሸማቾች ዋጋ በመወደዱ እንዳልገዙት ያስታውሳል። ገበሬዎች ዋጋ በመጨመራቸው የተነሳ እኔም ይህንን ማካካስ ነበረብኝ፤ የሚለው መኳንንት፣ ዋጋ በመጨመሩ ምክንያት ሸማቾች ፍላጎት የነበራቸው ቢሆንም፣ ሊገዙት እንዳልቻሉ፣ ምንም እንኳን በጎቹን ከበአል በኋላ በአነስተኛ ዋጋ ቢሸጣቸውም፣ ከፍተኛ ኪሳራ ደርሶበት እንደነበር ያወሳል። ታዲያ ለዘንድሮ ገና በአል ከአዲስ አመት ገጠመኙ ትምህርት በመውሰድ ረከስ ባለ ዋጋ ከገበሬዎች ቢገዛም፣ የሸማቾች ፍላጎት በጣም ወርዷል ይላል። ከጊዜ ወደ ጊዜ ገበያውን መገመት አዳጋች እየሆነ ነው፤ የሚለው መኳንንት፣ በተለይ በአገሪቱ የሚስተዋለው አለመረጋጋት ሸማቾች በተረጋጋ መንፈስ እንዳይሸምቱ እንዳደረጋቸው ምልከታውን ያጋራል። የገና ገበያ ምን ይመስላል በዘንድሮ የገና በአል ገበያ ከአዲስ አመት አኳያ የምግብ ምርቶች ዋጋና የአቅርቦት መረጋጋት ቢያሳዩም፣ የሸማቾች ቁጥር ብዙም ጭማሪ አለማሳየቱን ነጋዴዎች ይናገራሉ። የሪፖርተር ዘጋቢዎች በቦሌ፣ ሾላ፣ መርካቶና ቄራ በሚገኙ ገበያዎች ባለፉት ሁለት ቀናት ያደረጉት ዳሰሳ እንደሚያሳየው፣ በተለይም የዶሮ፣ የበግና የፍየል አቅርቦት ካለፈው በአል አንፃር ጭማሪ አሳይቷል። በአዲስ አመት ወቅት እስከ አምስት መቶ ሀምሳ ብር ሲሸጥ የነበረው የዶሮ ዋጋ በገና ወደ አራት መቶ ብር የወረደ ሲሆን ከወላይታ፣ ከአርባ ምንጭ እንዲሁም በአዲስ አበባና ዙሪያ ከተሞች የዶሮዎች ቁጥር መጨመሩ እንደ ምክንያት ተነስቷል። ከበግና በፍየል ገበያ መረጋጋት ታይቷል። ባለፈው በአል አዲስ አመት ከኦሮሚያ አንዳንድ ከተሞች ይመጡ የነበሩ በግና ፍየሎች በነበረው አለመረጋጋት የተነሳ ቁጥራቸው ቀንሶ የነበረ ሲሆን፣ በገና በአል ይህ ችግር ተቀርፏል፤ የሚለው በቄራ አካባቢ የሚሰራው ሰኢድ መሀመድ የተባለ ነጋዴ ነው። ይህም ዋጋ እንዲረጋጋ ትልቅ ሚና እንደተጫወተ አስረድቷል። የሸማቾችም አስተያየት ከዚህ ብዙ የተለይ አይደለም። በአዲስ አመት ሁሉ ነገር ተወዶ ነበር፤ የሚሉት ተመስገን ቢተው የሚባሉ ሪፖርተር በቦሌ አካባቢ ያገኛቸው ሸማች፣ የበግና የፍየል ዋጋ ከፍተኛ ቅናሽ ማሳየቱንና የተሻሉ አማራጮቹም በዘንድሮ በአል መታየታቸውን ተናግረዋል።በአዲስ አመት ወቅት እስከ ስድስት ብር ሲሸጥ የነበረው መካከለኛ መጠን ያለው በግ በዘንድሮ ገበያ ወደ አራት ሺህ ብር ዝቅ ያለ ሲሆን፣ ሙክት የሚባል የሰባ በግ ከዘጠኝ ብር ወደ ስድስት ሺህ ዝቅ እንዳለ ነጋዴዎች ተናግረዋል። በተመሳሳይ ከፍተኛው የፍየል ዋጋ ከ ብር ወደ ስምንት ብር ዝቅ ማለቱን፣ አነስተኛ ክብደት ያለው የፍየል ዋጋ ከአንድ ሺህ ብር በላይ ቅናሽ በማሳየት በሶስት ብር ሲሸጥ ተስተውሏል። እንደ ገበያው ቅርበት ቢለያይም በአዲስ አበባ ሲሸጡ የነበሩ ፍየሎችና በጎች በብዛት ከደብረ ብርሀን፣ ከዱበር፣ ከጊንጪ፣ ከደሴና ከጅማ የመጡ ናቸው። ሰንጋዎች በአብዛኛው ከምስራቅ ኦሮሚያ በተለይም ሀረርጌ ዞን ውስጥ ከሚገኙ አነስተኛ ከተሞች የመጡ እንደሆኑ ሪፖርተር በከተማው ያደረገው ዳሰሳ አመላክቷል። በተጨማሪ ቅልብ ሰንጋዎች በአብዛኛው ከአዳማ፣ ከባሌና ከአርሲ የገቡ ሲሆን ከጎንደርና ከወለጋ የመጡ ሰንጋዎች ቁጥር ላይ ቅናሽ መታየቱን ለማወቅ ተችሏል። በግና ፍየል ላይ የታየው የዋጋ መቀነስ ሰንጋዎች ላይ የታየ ሲሆን፣ እስከ አምስት ብር የሚደርስ ቅናሽ ተስተውሏል። የሀረር ሰንጋዎች ከስላሳ አራት ብር አንስቶ እየተሸጡ የነበረ ሲሆን፣ ዝቅተኛ ዋጋ ያላቸው ሰንጋዎች ደግሞ ከአስር ብር እስከ ብር ድረስ ሲሸጡ ተስተውሏል። ያላቸው ክብደት መካከለኛ የሚባሉት ሰንጋዎች ደግሞ ከ ብር እስከ ብር ሲሸጡ ተስተውሏል። ይሁን እንጂ በአዲስ አበባ በቅርጫ ሰንጋ የመግዛት ልማድ እየቀነሰ በመምጣቱ፣ በብዛት ሰንጋዎችን የሚገዙት ልኳንዳዎች መሆናቸውን ማወቅ ተችሏል። በሌላ በኩል ከአቅርቦት አኳያ ከአዲስ አመት መሻሻል ቢታይም፣ የገዥዎች ቁጥር ላይ እምብዛም ለውጥ እንዳልታየ አሸናፊ ሽፈራው የተባሉ የከብት ነጋዴ ለሪፖርተር ተናግረዋል። ለዚህም እንደ ምክንያት ያነሱት፣ በአሉ በሀሙስ ቀን መዋሉን ሲሆን፣ በማግስቱ የፆም ቀን በመሆኑ የገዥዎች ፍላጎት ቀንሷል ብለዋል። የሰንጋ ዋጋ መረጋጋት ቢያሳይም ልኳንዳ ቤቶች በስጋ ዋጋ ላይ ቅናሽ ማድረጋቸው አልታየም። በአንዳንድ አካባቢዎች ከወዲሁ ጭማሪዎች እየታዩ ሲሆን፣ በአሁኑ ጊዜ የአንድ ኪሎ ስጋ ዋጋ ከሁለት መቶ ብር እስከ ስድስት መቶ ብር እየተሸጠ መሆኑን ሪፖርተር ያደረገው ዳሰሳ ያሳያል። በሌላ በኩል በአልን ተከትሎ በስፋት በጥቅም ላይ ከሚውሉ ምርቶች መካከል የሆነው ቅቤ ዋጋ ላይ እስከ ሀያ ብር ጭማሪ የታየ ሲሆን፣ በመርካቶና በሾላ ገበያዎች በኪሎ እስከ ሁለት መቶ ዘጠና ብር ሲሸጥ ተስተውሏል። ከአቅርቦት አኳያ ካለፈው በአል አንፃር የተሻለ ሁኔታ እንደነበር ነጋዴዎች ተናግረዋል። በተመሳሳይ በኮረሪማ አቅርቦት ላይ መሻሻል መታየቱን ተከትሎ ከአዲስ አመት አኳያ እስከ ሰማኒያ ብር የሚደርስ ቅናሽ ታይቷል። በሾላና በመርካቶ ሪፖርተር ባደረገው ዳሰሳ በኪሎ እስከ አንድ መቶ ሰባ ብር ሲሸጥ ተስተውሏል። በአዲስ አመት ወቅት እስከ ስላሳ ስምንት ብር ሲሸጥ የነበረው የሽንኩርት ዋጋ ወደ ብር የቀነሰ ሲሆን፣ የነጭ ሽንኩርት ዋጋም ከአንድ መቶ ስልሳ ብር ወደ አንድ መቶ ብር ወርዷል።በምግብ ምርቶች ላይ የታየው መረጋጋት ምግብ ነክ ያልሆኑ ምርቶች ላይ ሊታይ አልቻለም። ለአብነት አልባሳቶችን ማንሳት ይቻላል።በመርካቶ፣ በፒያሳና በሀያ ሁለት አካባቢዎች የሪፖርተር ዘጋቢ ባደረገው ዳሰሳ መሰረት፣ ከውጭ የሚገቡ ሱሪዎች ላይ ከአንድ መቶ ብር እስከ ሁለት መቶ ብር የሚደርስ ጭማሪ የታየ ሲሆን፣ የወንድና የሴት ጫማዎች ላይ ከሀምሳ ብር እስከ አንድ መቶ ሀምሳ ብር ጭማሪ ታይቷል። ከቻይና የሚገቡ ምርቶች በውጭ ምንዛሪ እጥረት የተነሳ አቅርቦታቸው መቀነሱ እንደ ምክንያት ተወስቷል። በኢትዮጵያ በየአመቱ ከውጭ ከሚገቡ አልባሳት ውስጥ ዘጠና በመቶ ከቻይና በመሆናቸው፣ ያለው የአቅርቦት ችግር ካልተፈታ የታየው የዋጋ ጭማሪ ከፍተኛ ሽያጭ ይኖራል ተብሎ በሚገመትበት የጥምቀት በአል ላይ የበለጠ ሊጨምር እንደሚችል፣ አብሽሮ አወል የተባሉ በልብስ ንግድ ላይ የተሰማሩ ነጋዴ ተናግረዋል። ባለፉት ሶስት ወራት የታየው የምርት እጥረት በአይነቱ የከፋ መሆኑን ሪፖርተር ያነጋገራቸው ነጋዴዎች የተናገሩ ሲሆን ከዱባይ የሚገቡ ምርቶች ላይ የሚጣለው ቀረጥ ከፍ ማለቱም ለታየው የዋጋ ጭማሪ ምክንያት እንደሆን አስረድተዋል።የታየው የዋጋ ግሽበት በዚህ አያበቃምበአገር ውስጥ የሚመረቱ ጫማዎች የችርቻሮ ዋጋ ላይ እስከ አንድ መቶ ብር የሚደርስ ጭማሪ ታይቷል። በተለይም ጫማ ለማምረት የሚውሉ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች አቅርቦት በመቀነሱና የፋብሪካዎች የማምርት አቅም በመውረዱ የጫማ ዋጋ ሊጨምር እንደቻለ፣ አማኑኤል መንግስቱ የተባሉ በአመዴ አካባቢ የጫማ ንግድ ላይ የተሰማሩ ነጋዴ ተናግረዋል። የሸማቾች ልበ ሙሉነትበኢትዮጵያ በተደጋጋሚ የሚታየው አለመረጋጋት፣ የሸማቾች ልበ ሙሉነት ላይ አሉታዊ ተፅእኖ እንደሚያሳድር ግልፅ ነው። በተለይም አለመረጋጋቶች በሚከሰቱ ጊዜ ሸማቾች የምግብ ምርቶች ይጠፋሉ በሚል ፍራቻ በብዛት ሲገዙ ማየት የተለመደ ሲሆን፣ በእንዲህ አይነት ወቅቶች እንደ አልባሳት ላሉ ምግብ ነክ ላልሆኑ ምርቶች ያለው ፍላጎት ሲቀንስ ይስተዋላል። በገና በአል የዋዜማ ገበያ ላይ የታየው ከዚህ የተለየ እንዳልሆነ ነጋዴዎች ያስረዳሉ። በአገሪቱ ያለው አለመረጋጋት በከፋ ቁጥር ሸማቾች ልበ መሉነታቸው ስለሚቀንስ የሚያወጡት ገንዘብ ይቀንሳል የሚሉት የጫማ ነጋዴው አማኑኤል፣ አለመረጋጋቶች በተከሰቱ ቁጥር የሽያጭ ገቢያቸው ወዲያውኑ እንደሚቀንስ ይናገራሉ። የኮሮና ወረርሽኝ የተከሰተ ሰሞን ሸማቾች በመደናገጣቸው ምግብ ነክ ያልሆኑ ምርቶችን መግዛት አቁመው እንደነበር ያወሱት አማኑኤል፣ ከዚያም የሀጫሉን ሞት ተከትሎ በተከሰተው የፖለቲካ አለመረጋጋትና በትግራይ በነበረው ግጭት የተነሳ ተመሳሳይ ችግር ገጥሟቸው እንደነበር ተናግረዋል። ይሁን እንጂ አሁን በአገሪቱ አንፃራዊ ሰላም እየታየ በመሆኑ የሸማቾች ልበ ሙሉነት ስለጨመረ የንግድ እንቅስቃሴው የተሻለ መሆኑን የሚናገሩት አማኑኤል፣ በገና በአል ገበያ ከአዲስ አመት የተሻለ ሽያጭ ማስመዝገባቸውን አውስተዋል። በሌላ በኩል በአገሪቱ አንፃራዊ ሰላም ቢታይም ሸማቾች ከፍተኛ ገንዘብ ለማውጣት ያላቸው ፍላጎት ብዙም አላደገም የሚሉት በከብት ንግድ ላይ የተሰማሩት መኳንንት፣ አሁንም መንግስት ይህንን ለመቅረፍ መስራት እንደሚገባው አውስተዋል። በተመሳሳይ የሸማቾች ልበ ሙሉነት ወሳኝነት እንዳለው የሚናገሩት የምጣኔ ሀብት ባለሙያው አቶ አየለ ገላን ሲሆኑ፣ ለኢኮኖሚ እድገት ሞተር በመሆን እንደሚያገልግል ያስረዳሉ። ሸማቾችና ነጋዴዎች በምጣኔ ሀብት ላይ ያላቸው መተማመን የተሻለ ሲሆን፣ የኢኮኖሚው እድገትም የተሻለ ይሆናል። ይህንን ማድረግ ካልተቻለ ደግሞ አገሪቱ የምታሳየው እድገት ይቀንሳል፤ በማለት፣ የሸማቾች ልበ ሙሉነት ለኢኮኖሚ እድገትና መረጋጋት ያለውን የማይተካ ሚና የመንግስት የፖሊሲ አውጪዎች ሊረዱት ይገባል ሲሉ አቶ አየለ ሀሳባቸውን ለሪፖርተር አጋርተዋል። በሳምሶን ብርሀኔ
የዋጋ መረጋጋት የታየበት የገና ገበያ
አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ በሚዛን አማን ከተማ ሀያ አራትኛ ቅርንጫፉን ከፈተ። ቅርንጫፉን በምክትል ርእሰ መስተዳድር ማእረግ የደቡብ ብሄር፥ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል የግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ መርቀው ከፍተዋል። የዞኑ አስተዳደር በደቡብ ብሄር፥ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል፣ በቤንች ሸኮ ዞን፣ ሚዛን አማን ቅርንጫፍ መገልገያ የሚሆን አርባ ሺህ ኩንታል የሚይዝ መጋዘንና የተሟላ አገልግሎት መስጠት የሚቻልበትን ቢሮ ለስራ አመቺ እንዲሆን በማድረግ አዘጋጅቷል። ቅርንጫፉ የምርት ጥራት መመርመሪያ ላቦራቶሪና የተሟላ የቢሮ አደረጃጀት አለው ተብሏል። በዚህ ቅርንጫፍ በቤንች ሸኮ ዞን ለሚገኙ ስምንት ወረዳዎችና በምእራብ ኦሞ ዞን ለሚገኙ ሰባት ወረዳዎች አገልግሎት ለመስጠት ተዘጋጅቷል ነው የተባለው። በሁለቱ ዞኖች የሚገኙ አርሶአደሮችና አቅራቢዎች ያመርቱትን ቡና በአቅራቢያ ወደሚገኝ ቅርንጫፍ ለመውሰድ የሚያደርጉትን ተጨማሪ ጉዞ በአማካይ በአንድ መቶ ሀያ ኪሎሜትር ይቀንሳል ተብሏል። አከባቢው ከቡና በተጨማሪ ምርት ገበያው የሚያገበያያቸውና ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ሰሊጥ፣ አረንጓዴ ማሾ፣ ቅመማ ቅመምና ሌሎችም የግብርና ምርቶች የሚመረቱበት በመሆኑ ቅርንጫፉ እነዚህንም ተቀብሎ ለማስተናገድ ይችላል መባሉ ከኢትዮጵያ ምርት ገበያ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ ድረ ገፅ፦ ፌስቡክ፡ ዩትዩብ፦ ቴሌግራም፦ ትዊተር፦ በመወዳጀት ይከታተሉን። ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
የኢትዮጵያ ምርት ገበያ በሚዛን አማን ሀያ አራትኛ ቅርንጫፉን ከፈተ
በአቶ ጉርሜሳ አያኖ የክስ መዝገብ የተካተቱት እነ አቶ በቀለ ገርባ አራት ተከሳሾች በመከላከያ ምስክርነት የቆጠሯቸው ከፍተኛ ባለስልጣናት ለፍርድ ቤት በሰጡት ምላሽ ላይ ትእዛዝ ለመስጠት፣ ለታሀሳስ ሀያ ሰባት ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ቀጠሮ ተሰጠ። ፍርድ ቤቱ ከታሀሳስ እስከ ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ድረስ እነ አቶ በቀለ በመከላከያ ምስክርነት የቆጠሯቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለ ማርያም ደሳለኝ፣ አቶ አባዱላ ገመዳ፣ አቶ ለማ መገርሳ፣ አብይ አህመድ ዶክተር ፣ የለገዳዲ ከንቲባ ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒና የእድሜ ልክ ፍርደኛ አቶ አንዱአለም አራጌን ለመስማት ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረ ቢሆንም ሳይቀርቡ ቀርተዋል። የመከላከያ ምስክሮቹ የበኩላቸውን ምላሽ ሰጥተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ለፍርድ ቤቱ በሰጠው ምላሽ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለ ማርያም በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ በከፍተኛ ስራ ላይ በመሆናቸው ሊቀርቡ እንደማይችሉ መግለፁን ለችሎቱ አስታውቋል። የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ ባለስልጣናትን በሚመለከት የኦህዴድ ፅህፈት ቤት ለፍርድ ቤቱ በፃፈው ደብዳቤ፣ በአስቸኳይ አገራዊ ስብሰባ ምክንያት ቀርበው ለመመስከር ስለማይችሉ ፍርድ ቤቱ ችግሩን ተረድቶ ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲመቻችላቸው በአክብሮት እንጠይቃለን ብሏል። የእድሜ ልክ ፍርደኛ የሆኑት የቀድሞው የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ አንድነት ፓርቲ አመራር አቶ አንዱአለም አራጌን በሚመለከት፣ የማረሚያ ቤቱ ጉዳይ አስፈፃሚ ለምን እንዳልቀረቡ ተጠይቀው ምላሽ ሰጥተዋል። አቶ አንዱአለም ከባድ ፍርደኛ በመሆናቸው ለማቅረብ እንደሚቸገር ማረሚያ ቤቱ መግለፁን አስረድተው ነበር። ፍርድ ቤቱ ግን በፍርድ ቤት የተሰጠው ትእዛዝ መጥሪያውን የማረሚያ ቤቱ ፖስተኛ እንዲያደርስ የሚል እንጂ፣ በቀጥታ ለአቶ አንዱአለም እንዲደርሳቸው ትእዛዝ አለመስጠቱን ጠቁሟል። በመሆኑም በሶስቱም የመከላከያ ምስክሮች ላይ ተገቢውን ትእዛዝ ለመስጠት ለታሀሳስ ሀያ ሰባት ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ቀጠሮ ሰጥቷል። ታሀሳስ ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት የግል መከላከያ ምስክራቸውን አሰምተው ያጠናቀቁት አንደኛ ተከሳሽ የኦፌኮ ወጣቶች ሊግ ምክትል ሊቀመንበር አቶ አያና ጉርሜሳ ናቸው። አቶ አያና በመከላከያ ምስክርነት የቆጠሯቸው የኦፌኮ ወጣቶች ሊግ ሊቀመንበርና የህግ ባለሙያ መሆናቸውን የገለፁት አቶ ደስታ ዲንቃ ናቸው። አቶ ደስታ ከአቶ አያና ጋር በእስር ላይ የሚገኙ ሲሆኑ፣ ስለአቶ አያና ለፍርድ ቤቱ የሚያስረዱት በኦፌኮ የወጣቶች ሊግ አብረው ሲሰሩ አቶ አያና የነበራቸው ባህሪ ምን ይመስል እንደነበር መሆኑን፣ ጠበቃቸው አቶ አመሀ መኮንን ጭብጥ አስይዘዋል። አቶ ደስታ ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዱት፣ ከአቶ አያና ጋር በኦፌኮ ውስጥ የሰሩት ከየካቲት ቀን ሁለት ሺህ ስድስት አመተ ምህረት እስከ ታሀሳስ አምስት ቀን ሁለት ሺህ ስምንት አመተ ምህረት ነው። ከስራ ውጪ አይተዋወቁም። በድርጅቱ ውስጥ እሳቸው የሊጉ ሊቀመንበር ሲሆኑ አቶ አያና ምክትል ሊቀመንበር ናቸው። በየሳምንቱ ቅዳሜ በድርጅቱ ፅህፈት ቤት እየተገናኙ ስለፖለቲካ ፕሮግራምና ወቅታዊ ጉዳዮች ውይይት ያደርጋሉ። ስራቸው ጥብቅና ስለሆነ፣ ስራ በሌላቸው ጊዜ እየተገናኙ በፅህፈት ቤቱ ወጣቱን በሚመለከት ይመካከራሉ። አቶ አያና የኦሮሞ ህዝብ በሰላማዊ መንገድ መብቱ እንዴት መከበር እንዳለበትና የኢትዮጵያን አንድነት ማጠናከር ስለሚቻልበት ሁኔታ ውይይት እንደሚያደርጉ አስረድተዋል። ውይይት በሚያደርጉበት ጊዜ የተለያዩ የፖለቲካ ጥያቄዎችንና ሌሎች አጀንዳዎችን በመያዝ ውይይት ከማድረጋቸው ውጪ፣ ስለሽብርና ሽብርተኝነት አንስተውም ሆነ ተወያይተው እንደማያውቁ ምስክሩ ተናግረዋል። ኦፌኮም ሆነ አቶ አያና የሚያንፀባርቁት ሰላምንና አንድነትን እንጂ ስለሽብር እንዳልሆነ አክለዋል። አቃቤ ህግም ለምስክሩ ባቀረበው መስቀለኛ ጥያቄ ከኦነግ ጋር በተገናኘ ስለመከሰሳቸው ምስክሩ ፣ ስለአቶ ጉርሜሳ የእለት ከእለት ስራ ስለማወቃቸው፣ በኦፌኮ ውስጥ ወጣቶች ከሽብር ተግባር ጋር በተገናኘ ስለመገምገማቸውና ሌሎች ጥያቄዎችን አቅርቦላቸው ምላሽ ሰጥተዋል። ከኦነግ ጋር አለ ስለተባለው ግንኙነት ሲጠየቁ ጠበቃቸው ምስክሩ የመጡት ስለአቶ አያና የግል ባህሪ ለመመስከር ነው ብለው በመቃወማቸውና ፍርድ ቤቱም በመቀበሉ ምላሽ ሳይሰጡ አልፈዋል። የአቶ አያናን የእለት ተእለት ስራ የሚያውቁት ባገኟቸው መጠን ብቻ መሆኑንና ሽብርን በተመለከተ ግምገማ አጋጥሟቸው እንደማያውቅ ገልፀዋል። ፍርድ ቤቱ በሌሎችና ታሀሳስ ሀያ ሰባት ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት የሚሰጠውን ትእዛዝ ጨምሮ ቀሪ የመከላከያ ምስክሮችን ለመስማት፣ ከየካቲት አምስት እስከ ዘጠኝ ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ድረስ ቀጠሮ ሰጥቷል።
በእነ አቶ በቀለ ገርባ የመከላከያ ምስክሮች ላይ ትእዛዝ ለመስጠት ቀጠሮ ተሰጠ
ሁለት መቶ አርባ ስምንት ዶክተር አብይ እንዳለው የኢህአዴግ አባል ድርጅቶችና አጋሮች ተዋህደው አንድ አገር አቀፍ ፓርቲ የመሆን ሀሳብ አላቸው። ያ ከሆነ ብዙ የሚለወጡ መልካም ነገሮች ይኖራሉ ብዬ አስባለሁ። በዘረኝነትና በጎሰኝነት የተመታው አንዱ ክልል ቢኖር የኦሮሞ ክልል ነው። በኦሮሞ ክልል ላለፉት ሀያ ሰባት አመትታ አፓርታይድ ነው የነበረው። አሁንም እንደዚያው ነው። እንደ ሸዋ ባሉ አካባቢዎች ብዙ የሌላው ማህበረሰብ አባላት አሉ። በኦሮሞ ክልል የተካለሉ፣ በቀድሞ ሸዋ ግዛቶች ከግማሽ በላይ የሚሆኑ ኦሮሞዎች አይደሉም ተብሎ ነው የሚገመተው። እስከ አሁን ባለው አሰራር የኦህዴድ አባል መሆን የሚችለው ኦሮሞ የሆነ ብቻ ስለሆነና ኦህዴድም ገዢ ፓርቲ ስለበረ፣ በሁሉም የስልጣን እርከን የሚቀመጡት ኦሮሞዎች ብቻ ነበሩ። አሁንም በክልል፣ በዞኖ፣ በወረዳ፣ በከተሞች፣ በቀበሌ ሀላፊነት ቦታ ላይ ያሉት ሁሉም ኦሮሞዎች ናቸው። ለምሳሌ በአዳማ ፣ በጂማና ቡራዮ ልዮ ዞኖች፣ በአሰላ፣ በሰበታ፣ በቦሾፍቱ ከተሞች፣ አብዛኛው ነዋሪ ህብረብሄራዊ ቢሆንም፣ የነዚህ አካባቢዎች መስተዳደሮች፣ የቀበሌ ፅህፈት ቤትቶች የሚሰሩት ኦሮሞዎች ብቻ ናቸው። አሁን ኢህአዴግ ሁሉን አቃፊ አንድ አገር አቀፍ ፓርቲ ከሆነ ግን ማንም ዜጋ ይሄን ፓርቲ መቀላቀል ይችላል። የግድ ኦሮሞ ብቻ በኦሮሞ ክልል በሀላፊነት ላይ አይቀመጥም። ያኔ ሀላፊነት በብቃት ይሆናል። ለቦታው የሚመጥን፣ ህዝብ የመረጠው ሀላፊነት ላይ ይቀመጣል ማለት ነው። ኦሮሞ ይሁን ኦሮሞ አይሁን። ከዚህም የተነሳ፣ በኦሮሞ ክልል ህብረ ብሄራዊ የሆነ ማህበረሰብ በብዛት በሚኖሩባቸው አካባቢዎች ፣ አሁን ኦሮሞ ስለሆኑ ብቻ በሀላፊነት ላይ የተቀመጡ የኦህዴድ ሰዎች በብዛት ከሀላፊነታቸው መነሳታቸው የግድ ነው የሚሆነው። ብቃት ያለው ኦሮሞ ብቻ ይሆናል የሚቆየው። ኦህዴድንም ተጠቅመው እኩልና ዘረኛ ተግባራት የሚፈፀሙ አካላትም እነ ጃዋር ቀዳዳዎች ይደፈንባቸዋል። ትልቁ ጥያቄ እንግዲህ የኢህአዴግ አባል ድርጅቶችና አጋሮቻቸው ዶክተር አብይ እንዳለው ይዋሀዳሉ ወይ የሚለው ነው። ብአዴን አዴፓ፣ ደሀዴን፣ የአፋር፣ የጋምቤላ፣ የሀረሬና የቢኔሻንጉል አጋር ደርጅቶች የዉህደቱ አካል ይሆናሉ ብዬ አስባለሁ። ኦህዴድ ኦዴፓ፣ ሶዴፓ የሶማሌ ዴሞክራቲክ ፓርቲ እና ህወሀት ጋር እርግጠኛ አይደለሁም። ዉህደቱን ከመለስ ዜናዊ ጊዜ ጀምሮ ህወሀቶች ደጋፊ ነበሩ። ዉህደቱ ከማንም በላይ የትግራይን ህዝብ የሚጠቅም ነው። ከእልህ ፖለቲካ ከወጡና የትግራይን ህዝብ ጥቅም ካስቀደሙ ፣ ህወሀትም የዉህደቱ አካል ሊሆን ይችላል። አንድ የትግራይ ተወላጅ የአዲሱ ፓርቲ አባል ሆኖ ብቃት ካለው የባህር ዳር ፣ የነቀምቴ ከንቲባ መሆን የሚያስችል ሁኔታ ይፈጠርለታል ማለት ነው። ኦህዴድ ኦዴፓ ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ ዉህደቱን ይቃወም የነበረ ደርጅት ነው።በመሆኑም አብዛኛው የኦህዴድ አባልና አመራር ለህዝቡ ጠቃሚ ቢሆንም የነርሱን ስልጣን የሚያሰጋ ነው። ኦሮሞ ስለሆኑ ብቻ ብቃት ሳይኖራቸው ማማ ላይ እንዳይቀመጡ ያስገድዳቸዋል። ከሌላው እኩል መታየት ይጀምራሉ። በመሆኑም እነዚህ የኦህዴድ አባላትና አመራሮች በዉች ካሉ ፅንፈኛ የኦሮሞ ብሄረተኞች ጋር በመሆን ኦህዴድ ከስሞ በአገር አቀፍ ድርጅት ውስጥ እንዳይገባ ከፍተኛ ዘመቻ ያደርጋሉ ተብሎ ነው የሚጠበቀው። እነዚህ ቡድኖች በውስጠ ኦህዴድ ትግል አሸናፊ ሆነ ከወጡ ኦህዴድ ኦዴፓ ለሁለት ይልከፈላል። በነ ዶክተር አብይ የሚመራው ቡድን ዉህደት ሲመሰርት፣ ሌሎች እንደ ኦሮሞ ድርጅት ምን አልባትም ኦነግንና ኦፌኮን ተቀላቅለዉ ይቀጥላሉ። በነሙስጠፋ የሚመራው ሶዴፓ የዉህደቱ አካል ፣ በነ አቶ ሙስጠፋ ደርጅታዊ ጥንካሬ የሚለካ ነው የሚሆነው። አቶ ሙስጠፋ የዉህደቱ አካል የመሆን ፍላጎት ያለው ይመስለኛል። ግን ሌላዉን ይዞ አብሮ መሄድ ስላለበት እንዳሰበው ማድረግ ለጊዜው ሊያስቸግረው ይችላል። ሁለት መቶ አርባ ስምንት
የኢህአደግ ድርጅቶች ዉህደት ያለው አዋንታዊ እድምታ ግርማ ካሳ
ጥቅምት ፲፮ አስራ ስድስት ቀን ፳፻፯ አመተ ምህረት ኢሳት ዜና በጋምቤላና በደቡብ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች በሚኖሩ በመዠንገርና በመንግስት ታጣቂ ሀይሎች መካከል የተፈጠረውን ግጭት ተከትሎ፣ ቁጥራቸው ሀምሳ የሚጠጋ የፌደራል ፖሊስ፣ የመከላከያና የአካባቢው ሚሊሺያዎች ከተገደሉ በኋላ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የመከላከያ ሰራዊት አሁንም በአካባቢው እንቅስቃሴ እያደረገ ነው። ወኪላችን እንደሚለው ጦርነት ይነሳል በሚል ካለፈው ሳምንት አጋማሽ ጀምሮ ከፍተኛ ስጋት የነበረ ሲሆን፣ ትምህርት ቤቶች ለአንድ ቀን ተዘግተው መዋላቸውንም ገልጿል። የጦርነት ወሬዎች መናፈሳቸው በአካባቢው ነዋሪ ላይ አለመረጋጋት ቢፈጥርም እስካሁን ይህ ነው የሚባል ነገር አለመከሰቱንና የወሬው ምንጭም በአካባቢው የሚታየው የሰራዊት እንቅስቃሴ ሊሆን ይችላል ብሎአል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በቅርቡ በአበቦና በጋምቤላ ከተማ የተነሳውን ግጭት ተከትሎ የተገመገሙ በርካታ ቁጥር ያላቸው የልዩ ሀይል አባላት እስከነመሳሪያቸው መጥፋታቸውን ምንጮች ገልፀዋል። በርካታ ቁጥር እንዳላቸው የተነገረው እነዚህ አባላት፣ የአኝዋክ፣ ኑዌርና መዠንገር ተወላጆች ናቸው። ኢሳት የጠፉትን ወታደሮች ለማነጋገር ካለፉት ሶስት ቀናት ጀምሮ ሲያደርገው የነበረው ሙከራ በስልክ ኔትወርክ ችግር ምክንያት ሊሳካለት አልቻለም። ከዚሁ አካባቢ ሳንወጣ ካለፉት አራት ቀናት ጀምሮ በአራት ዞኖች የታየው የመብራት መጥፋት የአካባቢውን ነዋሪዎች ለችግር ዳርጎአቸዋል። በጅማ፣ ከፋ፣ ማሻ ና ቤንች ማጂ ዞኖች የታየው የመብራት መጥፋት መንስኤ ምን እንደሆነ ለማወቅ አልተቻለም። ከዚሁ ጋር ተያይዞ ከፍተኛ የውሀ እጥረትም ተከስቷል። በጉዳዩ ዙሪያ የአካባቢውን ባለስልጣናት ለማነጋገር ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።
በጋምቤላ የሚታየው ወታደራዊ እንቅስቃሴ ጨምሯል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት ሀያ ስድስት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ ማሻሻያ ተደርጎበት የፀደቀዉ አለም አቀፉ የጤና ህግ ለድንገተኛ የህብረተሰብ ጤና አደጋ ወረርሽኝ ቁጥጥር፣ ዝግጁነትና ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ያግዛል ሲሉ የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለፁ። በጄኔቫ ስዊዘርላንድ ሲካሄድ የነበረው ሰባ ሰባት ኛው የአለም ጤና ጉባኤ በሁለት ሺህ አምስት አለም አቀፍ የጤና ህግ ላይ የተደረገዉን ማሻሻያ በማፅደቅ ተጠናቋል። አለምአቀፉ የጤና ህግ በዋናነት በህብረተሰብ ድንገተኛ የጤና አደጋዎች ወቅት የሀገራት ዝግጁነትና ምላሽ አሰጣጥ አቅምን ለማሻሻል እንዲሁም አለም አቀፍ ወረርሽኞችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ታሳቢ ያደረገ ነዉ ተብሏል። ይህም ድንገተኛ የህብረተሰብ ጤና አደጋና ወረርኝ ሲከሰት ፍትሀዊ የሆነ አቅርቦት እንዲኖርና ሀብት በማሰባሰብ ታዳጊ ሀገራትን ለመደገፍ ታሳቢ ያደረገ መሆኑ ተገልጿል። የቀረበዉ ማሻሻያ በጉባኤዉ ተቀባይነት አግኝቶ መፅደቁ ግብአት ፍትሀዊ በሆነ መልኩ ተደራሽ እንዲደረግ እና ቀጣይ የጤና ወረርሽኝ ስጋቶችን አለም በጋራ በመቆም መከላከል እንዲችል የሚያደርግ መሆኑም ተመላክቷል። በጉባኤዉ የአፍሪካ አባል ሀገራትን በመወከል ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ዳባ አለም አቀፍ የጤና ህግ አገራት ከተባበሩና በጋራ ከሰሩ ለጋራ አላማ በጋራ መቆም እንደሚቻል አይነተኛ ማሳያ ነው ብለዋል። ህጉ ለድንገተኛ የህብረተሰብ ጤና አደጋ ወረርሽኝ ቅኝትና ቁጥጥር፣ ዝግጁነት እንዲሁም ፈጣን ምላሽ ለመስጠት እጅጉን እንደሚያግዝ መናገራቸውን ከጤና ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
አለም አቀፉ የጤና ህግ ለድንገተኛ የህብረተሰብ ጤና አደጋ ወረርሽኝ ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ያግዛል ዶክተር መቅደስ
አዲስ አበባ፣ ሀምሌ ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወሩ የነበሩ ከሁለት መቶ ሀምሳ ሰባት ሺህ በላይ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች ተያዙ። እንዲሁም ሀያ አራት ሚሊየን ሶስት መቶ ስላሳ ዘጠኝ ሺህ ሁለት መቶ ሰማኒያ ብር የሚያወጣ ከስድስት ኪሎ በላይ ወርቅ ተይዟል። ህገ ወጥ ገንዘቦቹ እና ወርቆቹ የተያዙት በትናንትናው እለት መነሻዉን አዲስ አበባ መድረሻዉን ደግሞ ምስራቅ ሀረርጌ ሀረር ከተማ ለማድረግ አስቦ በመኪና ሲዟዟር ቀረሳ ኬላ ላይ ነው ። በዚህም ሁለት አዘዋዋሪዎች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጓል። በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተያዘው ገንዘብም አንድ መቶ ሰማኒያ ሁለት ሺህ ስድስት መቶ ሰባ አምስት የአሜሪካ ዶላር ፣ አምስት ሺህ አምስት መቶ ስላሳ የካናዳ ዶላር ፣ አንድ ሺህ ስምንት መቶ ፓዉንድ እና ስልሳ ሰባት ሺህ አንድ መቶ አርባ አምስት የሳኡዲ ሪያል መሆኑ ታውቋል። በሌላ በኩል በደቡብ ወሎ ዞን ኩታበር ወረዳ ሁለት መቶ ሀምሳ የከባድ መሳሪያ ተተኳሾች መገኘታቸውን የወረዳው ሚሊሻ ፅህፈት ቤትት ገልጿል። የወረዳው ሚሊሻ ፅህፈት ቤትት እንደገለፀው፥ በወረዳው ሶስት ቀበሌ ልዩ ስሙ አላንሻ ከተባለ ቦታ የተለያዩ የዙ ሀያ ሶስት፣ የዲሽቃና የሞርታር ተተኳሾች ተገኝተዋል። የፅህፈት ቤትቱ ሀላፊ አስር አለቃ ፀጋየ አባተ እንደገለፁት፥ የተገኙት የጦር መሳሪያ አይነቶች አንድ መቶ ስላሳ የዲሽቃ ተተኳሽ ጥይት ዘጠና ሰባት የዙ ሀያ ሶስት ተተኳሽ ጥይትና የሞርታር ተተኳሽ ጥይት በአጠቃላይ ሁለት መቶ ሀምሳ ተተኳሽ ጥይቶችና ሶስት የሞርታር ፊውዝ ናቸው። መሳሪያዎቹ የትህነግ ወራሪ ቡድን ሲሸሽ ጥሏቸው የሄዱ እንደሆኑና በአካባቢው ማህበረሰብ ጥቆማ በፖሊስና የሚሊሻ ሀይሎች ክትትል ተደብቀው የተያዙና አንዳንዶቹም በግለሰብ ቤት የተገኙ መሆናቸውንም የኩታበር ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል። የጦር መሳሪያዎቹ በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት ስለሚያስከትሉ ማህበረሰቡ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት ገልፀው፥ በፅህፈት ቤቱ በኩል ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ክትትል እንደሚያደርግና ህብረተሰቡም ጥቆማ በመስጠት የተለመደ ትብብሩን እንዲቀጥል መልእክት አስተላልፈዋል።
በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወሩ የነበሩ ከሁለት መቶ ሀምሳ ሰባት ሺህ በላይ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦችና ስድስት ኪሎ ወርቅ ተያዙ
በጅግጅጋ ባለፈው ቅዳሜ በደረሰው የጎርፍ አደጋ እስካሁን ከሰባት ያላነሰ አስከሬን መገኘቱ ታወቀ የአካባቢው ነዋሪዎ እንደገለፁት ባለፈው ቅዳሜ በጅግጅጋ ቀበሌ አስር፣ እና የተፈጠረውን ጎርፍ ተከትሎ በርካታ ዜጎች በጎርፍ ተወስደው ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን፣ ኢሳት ዘገባውን ባቀረበ ማግስት የክልሉ ፖሊስ እና መከላከያ ፍለጋ ጀምረው እስካሁን የሰባት ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል። የበርካታ ዜጎች አስከሬን አሁንም ድረስ አለመገኘቱን፣ በጎርፍ ከተወሰዱት መካከል የንግድ ባንክ ስራ አስኪያጅ የሆነ ግለሰብም እንደሚገኝበት የክልሉ ዘጋቢያችን ገልጿል። በጎርፉ አንድ የመብራት ሀይል መኪን ጨምሮ አራት አይሱዙ መኪኖች በጎርፍ ተወስዷል። አንድ ኮካ ኮላ የጫነ መኪና እስከሙሉ ጭነቱ የተገለበጠ ሲሆን፣ የጫነው ኮካ ኮላም በጎርፍ ተወስዷል። በመኪኖች ላይ የነበሩ ሰዎችም በጎርፍ ተወስዷል። ጎርፉ በምስራቅ ሀረርጌ ዞን ጭናክሰን ከተማ በዘነበው ዝናብ ምክንያት የተፈጠረ ነው።
በጅግጅጋ ባለፈው ቅዳሜ በደረሰው የጎርፍ አደጋ እስካሁን ከሰባት ያላነሰ አስከሬን መገኘቱ ታወቀ
ነሀሴ አስራ ስድስትቀን አመተ ምህረት ኢሳት ዜና ከሀምሌ ወር ጀምሮ ለመንግስት ሰራተኛው ደመወዝ ጭማሪ መደረጉ ከተነገረ በሀላ ይበልጥ የተባባሰውንየዋጋንረትለማስታገስመንግስትእየወሰዳቸውያሉትየሀይልእርምጃዎችውጤትባለማምጣታቸውከፍተኛአመራሩውጥረትውስጥከመወደቁጋርተያይዞአምራችአስመጪናአከፋፋይነጋዴዎችዋጋአለመጨመራቸውንለህዝብእንዲናገሩ እየተገደዱ ነው።በሰኔ ወር አጋማሽ የሲቪል ሰርቪስ ቀን ሲከበር ከአንድ አመት በላይ ተጠንቶ የዋጋ ንረት በማያስከትል መልኩ የደመወዝ ጭማሪ መደረጉ በጠቅላይ ሚኒስተርኒስትርሀማርያምደሳለኝከተነገረበሀላበዋናነትበሸቀጦችበምግብናበቤትኪራይዋጋላይከፍተኛንረትመከሰቱየመንግስትን ጭማሪ ዋጋቢስነት ያሳየ ከመሆኑም በላይተ አማኒነቱንምጎድቶአል።በተለይየጭማሪውመጠንእጅግዘግይቶሲነገርገዥውፓርቲበራሷባሎችናደጋፊዎችጭምርእየተተቸመምጣቱከፍተኛአመራሩንአደናግጦአል።በዚህም መደናገጥበየመንደሩየሚገኙተራሱቆችንከማሸግናነጋዴዎችንከማሰርጀምሮበራዲዮናበቴሌቪዥንነጋዴውንየማጥላላትናየማስፈራራትስራዎችንሲያከናውንየቆየቢሆንምየዋጋንረቷሁንምቢሆንሊረጋጋአልቻለም። የንግድ ሚኒስቴር ከደመወዝ ጭማሪው በፊት ዋጋ ጨምረው የነበሩ የቢራ ፋብሪካ አመራሮችን በመጥራት ምክንያታቸውን በጠየቃቸውወቅትየግብአትዋጋመናርእንዳጋጠማቸውበመጥቀስምክንያታዊጭማሪማድረጋቸውንቢያስረዱምይህምክንያትበሚኒስቴሩበኩልአልታመነበትምበማለትዋጋቸውቀድሞወደነበረበትእንዲመልሱበቅርቡባዘዘውመሰረትፋብሪካዎቹያደረጉትንጭማሪ ለማንሳትተገዷል።ባለፈውማክሰኞነሀሴ ቀን አመተ ምህረትየንግድሚኒስቴርበተመሳሳይሁኔታከአምራችአስመጪእናአከፋፋይድርጅቶችጋርበዋጋንረቱጉዳይከመከረበሀላአብዛኛውነጋዴዎችዋጋአልጨመርንምማለታቸውንተከትሎበተለይየመንግስት መገናኛ ብዙሀንን በመጥራት እያንዳንዱ ነጋዴ ዋጋ አለመጨመሩን በቴሌቪዥን እየተቀረፀለህዝብእንዲናገርናይህምንግግሩበመንግስትመገናኛብዙሀንእንዲተላለፍአደርጎአል።የአንድየግልአምራችፋብሪካተወካይለዘጋቢያችን እንደገለፁትበእለቱሰብሰባአለተብለውወደንግድሚኒስቴርማምራታቸውንአስታውሰውነገርግንእዚያሲሄዱዋጋጨምራችሀልበሚልከፍተኛማስፈራራትናዛቻየታከለበትስብሰባአጋጥሟቸዋል።በዚህስብሰባምዋጋየጨመሩነጋዴዎችካሏጋቸውንበአስቸኳይካለስተካከሉ ፈቃዳቸውንእስከመሰረዝናበወንጀልአስከመጠየቅየሚደርስ እርምጃ እንደሚወሰድባቸውበግልፅእንደተነገራቸው በኋላምእያንዳንዳችንእንደሌባበቴሌቪዥንእየተቀረፅንዋጋአልጨመርንምእያልንእንድንናዘዝአስገድደውናልብለዋል።ያለምንምምክንያትዋጋበመቆለልየራሱንገበያየሚያበላሽነጋዴአለብለው እንደማያምኑየጠቆሙትአስተያየትሰጪውነጋዴዎችምሆኗምራቾችዋጋለመጨመርየሚገደዱትአስመጪከሆኑበአለም ገበያላይዋጋከፍናዝቅማጋጠምንተከትሎበተዋረድዋጋሲጨምርናፋብሪካዎችደግሞየጥሬእቃዋጋማሻቀብሲያሳይነውብለዋል።ይህችግርደግሞአምራቹወይንምነጋዴውብቻተሸክመውይቆዩየሚለውየመንግስትጥያቄ የንግድስራውንይበልጥየሚጎዳእንጂመፍትሄአይደለምሲሏስረድተዋል።የመከላከያናየፖሊስአባላትንጨምሮከሁለትሚሊየንበላይየሚደርሰውየመንግስትሰራተኞችየተደረገውየደመወዝ ጭማሪየሀምሌወርንያልተከፈለሂሳብጨምሮበዚህወርመጨረሻለመክፈል ቃል መገባቱን ይሁን እንጅ እስካሁን የክፍያ ትእዛዝ አለመተላለፉን በትናንት ዘገባችን ገልፀን ነበር። ይሁን እንጅ በዛሬው እለት የሲቪል ሰርቪስባለስልጣናት ስለ አከፋፈሉ የፊታችን ሰኞ ገለፃ እንደሚያደርጉ ለማወቅ ተችሎአል።አብዛኛውሰራተኞችጭማሪውተጋንኖየተወራለትያህልአለመሆኑናካለውየኑሮውድነትጋርሊመጣጠንካለመቻሉጋር ተያይዞበግልፅቅሬታውንበመናገርላይመሆኑን ተከትሎመንግስትሌሎች አማራጮች እንዲታዩ መመሪያ ማስተላለፉን መዘገባችን ይታወቃል።
የዋጋ ንረቱ አለመረጋጋት ከፍተኛ አመራሩን ውጥረት ውስጥ ከቷል
ታህሳስ ሀያ ስምንት ቀን አመተ ምህረት ኢሳት ዜና የመንግስትና የተቃዋሚ ደጋፊዎች በአዲስ አበባ ለድርድር ቢገኙም ቦር እየተባለ በሚጠራው አካባቢ አሁንም ከፍተኛ ጦርነት እየተካሄደ መሆኑን የሚደረሱን መረጃዎች ያመለክታሉ። ሰሞኑን በተቀሰቀሰው ጦርነት ኢትዮጵያን እንደተገደሉ የሚደረሱን መረጃዎች ያመለክታሉ።ሁለቱን ተፋላሚ ሀይሎች ፊት ለፊት በማገናኘት ጦርነቱ እልባት ያገኛል የሚል ተስፋ ቢያዝም እስካሁን ድረስ በተጨባጭ የታየ ነገር የለም። በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በሚገኙበት በዋና ከተማው ጁባ ዳርቻዎች ከሁለት ቀናት በፊት የጦርነት ድምፅ የተሳማ ሲሆን በእነዚህ ግጭቶችና በቦር አካባቢ በሚካሄደው ከፍተኛ ጦርነት ኢትዮጵያውያን መገደላቸውን የደረሰን መረጃ አመልክቷል። አንዳንዶች የሞቱ ኢትዮጵያውያንን ቁጥር ከ በታች ሲያደርሱት ሌሎች ደግሞ እሰከ ያደርሱታል። ኢሳት በራሱ እና ከአለማቀፍ የመገናኛ ብዙሀንና የእርዳታ ድርጅቶች ተገደሉ የተባሉትን ኢትዮጵያውያንን በተመለከተ ለማጣራት ሙከራ ቢያደርግም አልተሳካለትም። የኢትዮጵያ መንግስትም ስለዚህ ጉዳይ ምንም ያለው ነገር የለም። አብዛኛው አገራት ዜጎቻቸውን ከደቡብ ሱዳን አስወጥተዋል የኢትዮጵያ መንግስት እስካሁን በይፋ ዜጎቹን ከአገሪቱ ማስወጣት አልጀመረም። ከዚህ ቀደም ወደ የሚደረሱ ኢትዮጵያውያን ከአገሪቱ ለቀው እንዲወጡ ቢደረግም እንቅስቃሴው አልቀጠለም። የመንግስት ወታደሮች ቦርን ለመያዝ በሚቀጥሉት ሰአት ውስጥ በሚያደርጉት ጦርነት ከፍተኛ እልቂት ሊፈጠር ይችላል ተብሎ ተስግቷል።ይህ በእንዲህ እንዳለ የአገሪቱ ነዳጅ ማውጫ በተቃዋሚዎች እጅ መውደቁን ተከትሎ በተፈጠረው ችግር የሱዳኑ መሪ ፕሬዚዳንት አልበሽር ወደ ጁባ በማቅናት የነዳጅ ማውጫው በሁለቱም አገራት ጥበቃ ስር እንዲውል ስማማታቸውን ተናግረዋል።አንድ የመንግስት ጄኔራል እሁድ እለት በተቃዋሚዎች ተገድለዋል።
በደቡብ ሱዳን የሚካሄደው ጦርነት እንደቀጠለ ነው
በቅርቡ በውጭ ምንዛሪ ላይ በተደረገው የ በመቶ ለውጥ ምክንያት፣ በየካቲት ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ለሚደረገው አራተኛው የህዝብና ቤቶች ቆጠራ እንዲያገለግሉ የተገዙ አንድ መቶ ሰማኒያ ሺህ ታብሌት ኮምፒዩተሮችና አንድ መቶ ሀያ ስምንት ሺህ ፓወር ባንኮች ዋጋ በአንድ መቶ አርባ አራት ሚሊዮን ብር አደገ።የግዥ ውላቸው በግንቦት ሁለት ሺህ ዘጠኝ አመተ ምህረት የተፈረመው የእነዚህ እቃዎች አቅርቦት መጀመርያ በነበረው ውል መሰረት መንግስት ለአቅራቢዎቹ ስድስት መቶ ስልሳ አምስት ሚሊዮን ብር መክፈል የነበረበት ቢሆንም፣ ከአምስት ወራት በሀላ በተደረገው የብር ምንዛሪ ለውጥ ምክንያት የተጠቀሰው ጭማሪ ተከስቷል። ውሉ ሲፈረም በውጭ ምንዛሪ ስለነበረ የብር ምንዛሪ ተመን ማስተከከያው የመግዣውን ወጪ ሊጨምር ችሏል፤ ሲሉ የእቃዎቹን ግዥ የፈፀመው የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ይገዙ ዳባ ለሪፖርተር ተናግረዋል።የእቃዎቹ ግዥ የተፈፀመው በአለም አቀፍ ደረጃ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቁሳቁሶች አቅራቢነታቸው ከሚታወቁት ሌኖቮና ኋዌ ከተባሉ ኩባንያዎች ነው። በአገልግሎቱ በኩል ግዥው ተፈፅሞ ለማእከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ የሚቀርበው የሁለቱ እቃዎች ግዥ ብዙ ውጣ ውረዶችን ማለፉ ይታወሳል። ስድስት ወራት የፈጀው የግዥው ሂደት በቅሬታዎችና በአቅራቢ ኩባንያዎች መካከል በተፈጠሩ አለመግባባቶች የተሞላ ነበር።ለወራት የዘለቀው ቅሬታ ጨረታው ተሰርዞ እንደገና እንዲደገም አድርጓል። በዚህም ምክንያት ግዥው ተፈፅሞ እቃዎቹ ግንቦት ሁለት ሺህ ዘጠኝ አመተ ምህረት ይቀርባሉ ተብሎ የታቀደ ቢሆንም ይህ ሳይሆን ቀርቷል።የእቃዎቹ አቅርቦት እስከ ጥቅምት ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ድረስ ተራዝሞ የጥቅምት ወር መጀመርያ ሳምንት በመንግስት ከተደረገው የብር ምንዛሪ ለውጥ ጋር ሊገጥም ችሏል። በዚህም ምክንያት መጀመርያ በነበረው የእቃዎቹ ዋጋ ላይ ጭማሪ አምጥቷል።የግዥው አካሄድ መጀመርያ ከታቀደለት ጊዜ መጓተቱ ካስከተለው የወጪ ጭማሪ በተጨማሪ፣ የቆጠራው ጊዜ ከሀዳር ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ወደ የካቲት ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት እንዲራዘም ሆኗል።በመንግስት ሶስት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር በጀት ተይዞለት እየተደረገ ላለው ዝግጅት፣ አብዛኛው ወጪ ለቆጠራው ለሚያስፈልጉ ግብአቶች ግዥ ላይ ይውላል። አንድ ሳምንት ይፈጃል ተብሎ ለሚጠበቀው ቆጠራ ከአንድ መቶ ዘጠና ሺህ በላይ ሰዎች ይሳተፋሉ። ከተገዙት አንድ መቶ ሰማኒያ ሺህ ታብሌቶችና አንድ መቶ ሀያ ስምንት ሺህ ፓወር ባንኮች ውስጥ አብዛኛዎቹ ወደ አገር ውስጥ የገቡ ሲሆን፣ ማእከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ መረከብ መጀመሩን ለማወቅ ተችሏል።በየካቲት ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ቆጠራው ከተጠናቀቀ በኋላ፣ የቆጠራው ውጤት በስድስት ወራት ውስጥ ይፋ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።
የውጭ ምንዛሪ ለውጡ የህዝብና ቤቶች ቆጠራ ወጪን አናረ
የአንበሶቹን ያህል ለሰራተኞቹ ጥንቃቄ አይደረግም ሰራተኞቹ ቸልተኝነቱ ከቀጠለ ሌላም ሰው ሊሞት ይችላል አስተያየት ሰጪዎች አደጋው የደረሰው አንበሶች በምግብ ስለተጐዱ አይደለም ዋና ዳሬክተር ለአንበሳ ስጋ በአመት ከአንድ ነጥብ አምስትሚ ብር በላይ ወጪ ይደረጋል ባሳለፍነው ሰኞ ማለዳ ስድስት ኪሎ በሚገኘው አዲስ ዙ ፓርክ አንበሳ ግቢ ውስጥ በአንድ የግቢው ሰራተኛ ላይ የተከሰተው አስደንጋጭ አደጋና አሰቃቂ ህልፈተ ህይወት የብዙዎች መነጋገሪያ ሆኖ ሰንብቷል። በእለቱ ተራቸውን ጠብቀው የአንበሳውን ማደርያ ለማፅዳት ወደ ውስጥ የዘለቁት አቶ አበራ ሲሳይ የተባሉ ሰራተኛ፤ በጥቂት መዘነጋት አንበሳውን ወደ መዋያው አስገብተው በር ባለመዝጋታቸው፣ በአንበሳው ማጅራታቸውን ተይዘው፣ ለሀያ ደቂቃ ያህል ሲሰቃዩ ቆይተው መሞታቸው እጅግ አሳዛኝ ክስተት መሆኑን የሟች ባልደረባ አቶ ምትኩ ጭብሳ ይናገራሉ። ምንም እንኳን አደጋው በጥቂት መዘነጋት እንደደረሰ ቢነገርም ይህ አይነት አደጋ የመጀመርያው እንዳልሆነና የመጨረሻውም ሊሆን እንደማይችል ነው የአንበሳ ግቢ ሰራተኞች የሚናገሩት። ከዚህ በፊት በአንበሳ ተበልተው የሞቱ አንድ ሰራተኛ እንደነበሩ የሚያስታውሱት ሰራተኞቹ፤ ተነክሰው ከሞት የተረፉም እንዳሉ ይገልፃሉ። አሁን ባለው ቸልተኝነት ከቀጠለም ሌላ ሰው መሞቱ አይቀርም ሲሉ ስጋታቸውን ተናግረዋል። በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ አርባ አመተ ምህረት ለቀዳማዊ ንጉሰ ነገስት ሀይለስላሴ፤ ከኢሊባቡር ጐሬና ከሲዳማ በመጡ አራት ትላልቅ እና ሶስት ደቦል አንበሶች የተመሰረተው አዲስ ዙ ፓርክ፤ ላለፉት ስልሳ አመታት አንበሶችንና ሌሎች እንስሳትን አካቶ ለጐብኚዎች አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል። ለንጉሱ የመጡት እነዚህ ሰባት አንበሶች በጊዜ ሂደት በመራባት በአሁኑ ሰአት በፓርኩ ውስጥ የሚኖሩት አንበሶች ቁጥር ደርሷል። ከነዚህ ውስጥ አምስቱ ሀይሌ፣ ቀነኒሳ፣ መሰረት፣ ጥሩነሽና እጅጋየሁ በሚሉ የታዋቂ ጀግኖች አትሌቶች ስም የተሰየሙ ሲሆን ሌሎቹም ላይሽ ተረፈ፣ ሰለሞን ጠንክር፣ መኮንን ተጋፋው፣ ወርቁ ገረመው፣ በሻዱ ጫላ፣ ቃኘው ወርቁ ወዘተ በሚል ስም ይጠራሉ። በተለይ ጠንክር የተባለው አንበሳ ከሁሉም አንጋፋው ሲሆን በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ አራት አመተ ምህረት ነው የተወለደው። ቀነኒሳ በቀለ ወርቁ፣ ሀይሌ ገብረ ስላሴ ወርቁና መሰረት ደፋር ወርቁ ወንድምና እህትና አንበሶች ናቸው። ወንድማማቾቹ ሀይሌና ቀነኒሳ በአንድ ማደሪያና መዋያ ቢያድጉም በጊዜ ሂደት ግን መስማማት አለመቻላቸው ብዙዎችን ያስጨንቅ እንደነበር የፓርኩ አስጐብኚ ይናገራሉ። በተለይ ቀነኒሳ ከወንድሙ ሀይሌ ጋር በየቀኑ መደባደብ ልማዱ ነበር። በዚህም የተነሳ ሀይሌና ቀነኒሳን በተለያየ ኬጅ ውስጥ ለማዋልና ለማሳደር ግድ ሆኗል ብለዋል አቶ ምትኩ ጭብሳ። በነገራችን ላይ መጀመሪያ ከሞላ ጋር የመጣው ሉሉ የተባለው አንበሳ፤ በጃንሆይ የውሻ ስም የተሰየመ ሲሆን ሞላ የተባለው የመጀመርያው አንበሳም ሚስቱን በመግደሉ የሞት ፍርድ ተፈርዶበት እንደተገደለ ይነገራል። የአንበሶቹ አያያዝ በአሁኑ ወቅት በግቢው ውስጥ የሚኖሩት አንበሶች የሚመገቡት ስጋ በቀጥታ ከቄራ ተመርምሮ የሚመጣ ሲሆን ለእያንዳንዱ አንበሳ በቀን ከአምስት ሰባት ኪሎ ንፁህ ስጋ ይቀርባል። ለአንድ ኪሎ ስጋ ሀምሳ አምስት ብር ከሀያ ሳንቲም እንደሚወጣና በቀን እስከ አንድ መቶ ሀያ ኪሎ የሚደርስ ንፁህና የተመረመረ ስጋ እንደሚቀርብ የፓርኩ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሙሴ ክፍሎም ተናግረዋል። አንበሶቹ በግቢው ውስጥ የራሳቸው ቋሚ ሀኪም ያላቸው ሲሆን ለውስጥ ጥገኛ ተውሳኮች ከምግብ ጋር መድሀኒት እንደሚሰጣቸውና ምርመራም እንደሚደረግላቸው ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀውልናል። የአቶ አበራን በአንበሳው ተነክሶ መገደል ከአንበሶች በቂ ምግብ አለማግኘትና መጎሳቆል ጋር የሚያገናኙ ወገኖች እንዳሉ የተገለፀላቸው ዳይሬክተሩ፤ጉዳዩ መሰረተ ቢስ አሉባልታ መሆኑን ተናግረዋል። በአጠቃላይ አንበሶቹ በአመጋገብና በጤና በኩል አንዳችም ጉድለት እንደሌለባቸው የገለፁት ዶክተር ሙሴ፤ አቶ አበራ ላይ የደረሰው አደጋ ከአንበሶቹ ምግብ ማጣትና ጉስቁልና ጋር እንደማይገናኝና አንበሶቹ በተፈጥሯቸው መላመድ የማይችሉ በመሆናቸው እንዲሁም በሩ ባለመዘጋቱና ከአንበሳው ጋር ፊት ለፊት ስለተገናኙ ለአሰቃቂው የህልፈት አደጋ መዳረጋቸውን አብራርተዋል። የአንበሶችን የምግብ አቅርቦት በተመለከተም፣ የዚህ ፓርክ ትልቁ ወጪ የአንበሶች ምግብ ነው፤ በአመት ከአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር በላይ ለስጋ ይወጣል። ችግሩ የተፈጠረው አንበሳው ከማደሪያው ወደ መዋያው ከገባ በኋላ ሁለቱን ቦታዎች የሚያገናኘው በር ባለመዘጋቱ ነው። አንበሶች ምግብ አያገኙም ተጐሳቁለዋል እየተባለ የሚወራው ስህተት ነው ብለዋል። ባለትዳርና የሶስት ልጆች አባት የነበሩት የሀምሳ ሁለት አመቱ አቶ አበራ ሲሳይ፤ ጠንካራና ታታሪ ሰራተኛ እንደነበሩ የጠቆሙት ዶክተር ሙሴ፤ ወደ መጋቢነት እና ፅዳት ሰራተኝነት ከገቡ አንድ አመት ቢሆናቸውም በግቢው ውስጥ በሌላ የስራ ዘርፍ ለረጅም አመታት መስራታቸውን ተናግረዋል። በዚህ ግቢ ውስጥ ሰው በአንበሶች ሲገደል የመጀመርያው አይደለም፤ ከዚህ ቀደም የተነከሰ ሰራተኛ አለ፤ ታዲያ ይህን ለመከላከል የዚህ ግቢ ሀላፊዎች ለምን ቅድመ ዝግጅት አያደርጉም ሲሉ ይጠይቃሉ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አስተያየት ሰጪ። በዚህ ቸልተኝነት ከቀጠለ ሌላም ሰው ሊሞት እንደሚችል ስጋታቸውን የገለፁት ሌላው የፓርኩ ሰራተኛ፤ ለግንባታ ሰራተኞች ሄልሜት እና ሌላ የአደጋ መከላከያ መሳሪያዎች የሚሰጡ ሲሆን ለአንበሳ መጋቢዎችና ፅዳት ሰራተኞች ግን ምንም አይነት መከላከያ እንደሌለ ተናግረዋል። ሌላው ቀርቶ የዋና ገንዳ ባለባቸው ቦታዎች ህይወት አድን ሰራተኛ ይዘጋጃል ያሉት እኚሁ ሰራተኛ፤ አንበሳን ከሚያክል እንስሳ ጋር ለሚሰሩ ግን ምንም አይነት አደጋ መከላከያ እንደሌለ ገልፀው፣ ህይወት አድን ሰራተኛ ቢኖር ኖሮ ባልደረባቸው ከሞት ሊተርፉ ይችሉ እንደነበር በቁጭት ተናግረዋል። ደሞዛችን እንኳን ከስድስት መቶ ብር አይበልጥም፤ እኔ እዚህ ግቢ መስራት ከጀመርኩ አስር አመት አልፎኛል፤ ስራው ከባድ ክፍያው ግን አነስተኛ ነው ያሉት ሌላው የግቢው ሰራተኛ፤ መንግስትና የፓርኩ ሀላፊዎች የሰራተኞችን ደህንነት ለመጠበቅ አስፈላጊውን ጥረት ማድረግና መሟላት ያለባቸውን ነገሮች በአስቸኳይ ማሟላት እንዳለባቸው ተናግረዋል። ያለበለዚያ እኔ በአንበሳ ተንገላትቼ ስሞት ያየ ሌላ ሰራተኛ፣ ወደዚህ ግቢ ገብቶ ለመስራት እግሩን አያነሳም ሲሉ ስጋታቸውን ገልፀዋል። የሰራተኞቹን የህይወት ዋስትና በተመለከተ የፓርኩ ዳይሬክተር ሲናገሩ፤ ስራው ከባድና ከአንበሳ ጋር የሚሰራ እንደመሆኑ ሁሉም ሰራተኞች ኢንሹራንስ መግባት አለባቸው ያሉ ሲሆን ይህንን ከግምት ውስጥ በማስገባት የኢንሹራንሱ ፕሮሰስ ተጀምሯል ብለዋል። አንበሳውን ገድሎም ቢሆን የስራ ባልደረባችንን ለማዳን ጥረት ተደርጐ ነበር ያሉት ዳይሬክተሩ፤ ከዚያ በኋላ ሊመጡ የሚችሉትን አለም አቀፍ የእንስሳት መብት ጥያቄዎችና ሌሎች ጉዳዮችን እንመልሳቸው ነበር ብለዋል። በፅዳትና በመጋቢነት ለሶስት አመታትን የሰሩት አቶ ምትኩ ጭብሳ፤ ከሌላ የስራ ዘርፍ ወደ መጋቢነት ሲዛወሩ የወሰዱት ስልጠና ስለመኖሩ ጠይቀናቸው፤ ስልጠና ሳይሆን በመ ቤቱ የሚሰጡ መመሪያዎችና ማስጠንቀቂያዎች እንዳሉ ጠቁመው፤ ስራው ከአንበሳ ጋር የሚሰራና ህይወትን እስከማጣት ለሚያደርስ አደጋ የተጋለጠ በመሆኑ መዘናጋት እንደማያስፈልግ ተናግረዋል። ሁሌም በአእምሯችን ስጋት መመላለስ አለበት፤ በንቃትና በጥንቃቄ የሚሰራ ስራ ነው፤ ከአንበሶች ጋር የሚውል ሰው ለሰከንድ እንኳን መዘናጋት የለበትም ሲሉም ምክራቸውን ይለግሳሉ፤ አቶ ምትኩ። በተለያዩ የአገር ውስጥ ሚዲያዎችና ድረገፆች የአቶ አበራ በአንበሳ መገደል ሲዘገብ የሰነበተ ሲሆን ቀነኒሳ መጋቢውን ገደለ የሚሉ እና መሰል አዘጋገቦችን በተመለከተ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጆርናሊዝም እና ኮሚዩኒኬሽን መምህር አዘጋገቡ ከሙያ ስነ ምግባር እጅግ ያፈነገጠ ነው፤ ታዋቂውን አትሌት ቀነኒሳንም የሚያስከፋና በመልካም ዝናው ላይ ጥቁር ነጥብ የሚጥል ነው ሲሉ ተችተዋል። በዚህ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን በሌሎች ፖለቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚዘገቡ በርካታ ዘገባዎች ሙያው ከሚፈቅዳቸው አካሄዶች ያፈነገጡ ናቸው ያሉት መምህሩ፤ ሙያው በባህሪው ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚሻ በመሆኑ ሙያተኞቹ ይህን ግምት ውስጥ በማስገባት መስራት እንዳለባቸው መክረዋል። ሌላው የግቢው ሰራተኛ የሆኑና ለ አመታት እንደሰሩ የገለፁ ግለሰብ የአንበሶቹን ያህል ለእኛ ለሰዎች ጥንቃቄ አይደረግልንም ያሉ ሲሆን የጓደኛቸው የአቶ አበራ አሟሟት ዘግናኝ እንደነበርና ነገ በራሳቸው ላይ ሊደርስ እንደሚችል ገልፀው፤ በጤና፣ በደሞዝና አደጋን በሚከላከሉ መሳሪያዎች ልንታገዝና መንግስት ከአቶ አበራ ሞት ትምህርት ወስዶ ሌሎች ሰራተኞችን ከአደጋ መታደግ አለበት ብለዋል። ያለበለዚያ ግን አንበሶቹ ይወገዱ ብለዋል እኚሁ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ሰራተኛ። የአንበሶቹ ዝርያ ለየት ያለ መሆኑ ከጀርመኑ ላይፕ ዚክ እህት ከተማ ጋር በመተባበር በተካሄደ የደም ምርመራ መረጋገጡን ዶክተር ሙሴ ይናገራሉ። በኬጅ ውስጥ የሚኖር አንበሳ ከሀያ ሀያ አምስት አመት የመኖር እድል እንዳለው የገለፁት ባለሙያዎች፤ በዱር የሚኖር አንበሳ ግን በአማካኝ አመት ብቻ በህይወት እንደሚቆይ ይናገራሉ። ምክንያቱን ሲያስረዱም በጫካ የሚኖር እንስሳ ምግብ ለማግኘት ብዙ ከመድከሙም በላይ ከሌሎች ጋር የሚያደርገው ተጋድሎ እድሜውን ያሳጥረዋል። በኬጅ የሚኖረው እድሜው የተሻለ የሚሆነው የተመረመረ ምግብ ከማግኘቱም በላይ ጤንነቱ በባለሙያ ክትትል ይደረግለታል፣ ከዚያም በላይ ከየትኛውም አቅጣጫ ትግልና ድካም አይኖርበትም ይላሉ ባለሙያዎቹ። በአሁኑ ሰአት በአዲስ ዙ ፓርክ ውስጥ ስምንት ወንድና ሴት አንበሶች፣ አምባራይሌ የተባለ እንስሳ፣ ጭላዳ ዝንጀሮ፣ ኤሊዎች፣ ንስር፣ ጦጣና የተለያዩ አእዋፋት እንደሚኖሩም ለማወቅ ተችሏል። ባለፈው ሰኞ በአንበሳ ተነክሰው ለህልፈት የተዳረጉት ሟች አቶ አበራ ሲሳይ፤ ባለፈው ማክሰኞ በገርጂ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ስርአተ ቀብራቸው ተፈፅሟል። ሰበተለያዩ የአገር ውስጥ ሚዲያዎችና ድረገፆች የአቶ አበራ በአንበሳ መገደል ሲዘገብ የሰነበተ ሲሆን ቀነኒሳ መጋቢውን ገደለ የሚሉ እና መሰል አዘጋገቦችን በተመለከተ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጆርናሊዝም እና ኮሚዩኒኬሽን መምህር አዘጋገቡ ከሙያ ስነ ምግባር እጅግ ያፈነገጠ ነው፤ ታዋቂውን አትሌት ቀነኒሳንም የሚያስከፋና በመልካም ዝናው ላይ ጥቁር ነጥብ የሚጥል ነው ሲሉ ተችተዋል። በዚህ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን በሌሎች ፖለቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚዘገቡ በርካታ ዘገባዎች ሙያው ከሚፈቅዳቸው አካሄዶች ያፈነገጡ ናቸው ያሉት መምህሩ፤ ሙያው በባህሪው ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚሻ በመሆኑ ሙያተኞቹ ይህን ግምት ውስጥ በማስገባት መስራት እንዳለባቸው መክረዋል።
አንበሳ ግቢና የሰራተኛው አሰቃቂ ሞት
ከሱሊማን አህመድከለንደን ወያኔ እንደወትሮው ሁሉ ለስልጣኑ ማቆያ ወዳጅ ለማፍራት የኢትዮጵያን ሏላዊ ግዛት በድብቅ እየተደራደረ የመሸጡን ተግባር ትልቁ ስራው አድርጎ ገፍቶበታል። ይህንን አደገኛ የወያኔ ፕሮግራም መላው ኢትዮጵያዊይም ሆነ አለን የሚሉ የፖለቲካ ድርጅቶች ትንሹም ትልቁም በቸልታ የሚያዩት አገራዊ ጉዳይ እንዳልሆነ በጣም ግልፅ እየሆነም ነው።ወያኔ በገፀበረከትነት ለሱዳን መንግስት የሰጠው ኪሎ ሜትር ርዝመትና ከ እስከ ኪሎ ሜትር የጎን ስፋት ያለው ለምና ማእድን ያረገዘ መሬት እባክህን ድሮ ለእኔ እንዳደረከው ዛሬ ደግሞ ለጠላቶቸ መከታ ከለላና መተላለፊያ እትሁንብኝ ብሎ የሰጠው ገፀበረከት ብቻ ሳይሆን ብዙዎቻችን እንደምንገምተው ዶላርም ተከፍሎት እንደሆነ አዳዲስ መረጃ እየተገኘ ነው።ዛሬ ስልጣን ላይ ያሉት ነፍሳት በግልም በቡድንም ሲገመገሙ በፍቅረነዋይ የሰከሩ ራስ ወዳድና ይሉኝታ ቢስ በመሆናቸው ደረቅ ጡቷን እያጠባች ያሳደገቻቸውን ኢትዮጵያን እስክታልቅ ድረስ በካሬ ሜትር እየሸነሸኑ ለመሸጥ ቆርጠው የተነሱ ለመሆናቸውም በየቀኑ እያየን ነው። ይህን አያደርጉም የሚል ካለ አንድም ሞኝ ነው አለበለዚያም የወያኔ ሽርካ መሆን አለበት።በጣም አሳዛኙ ነገር ግን ይህን በአለም ታሪክ ታይቶም ተሰምቶም የማይታወቅ ጭካኔ የተመላበት አገር ሽያጭ ሌላው ቢቀር እንደ አንድ አገሩን ክብሩንና ኩራቱን እንደሚወድ ማንኛውም የአለም ህዝብ ማስቆም አለመቻላችን ነው። በእኔ እምነት ይህን ማድረግ ያልቻልንበት ትልቁ ምክንያት በጥላው ስር ህዝብን ማሰባሰብ የሚችል አገራዊ ራእይ ያለውያላቸው ወይም የተሳካለት ገለሰብም ሆነ ድርጅት መውለድ ያለመቻላችን እንደሆነ ዛሬ ዛሬ ብዙ ኢትዮጵያውያን የምንስማማበት ገሀድ እውነታ ነው ብይ አምናለሁ።ሌላው የኛ ነገር ፈርዶብን ግራ የተጋባን ሆንና ወያኔ ትናንት ሳይሆን ዛሬ በአገራችንና በህዝቡ ላይ የፈፀመውንና እየፈፀመ ያለው አገር የመሸጥ ዘመቻ አእምሯችንን ክፉኛ አቁስሎት እህህ እያልን ቁስላችንን በማስታመም ላይ እያለንና ይኼው ከፍተኛ ቁስል ሳያገግም ሌላ አእምሯችንን ቀስፎ የሚይዝ የተንኮል መላ እየፈጠረ የህሊና እስረኞች ሆነን በየጓዳችን እየተብተከተክን እንድንደበቅ ማድረግ መቻሉ ነው።ከዚህ አንፃር የወያኔ ትልቁ መሳሪያው ከህዝብ በጉልበት ከአገር ሽያጭና ከፈረንጆች በድርጎ በሚያገኘው ገንዘብ ለሆዳቸው ያደሩና ለማጭበርበሪያ ያህል ትንሽ ፊደል የቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ምንደኞችን ቀጥሮ በሀቀኛና ቁርጠኛ የኢትዮጵያ ልጆች መሀከል የአላማና የተግባር አንድነት እንዳይፈጠር ሳይታክቱ የሚሰሩ ባንዳዎችን በማሰማራት ነው። ለመከፋፈሉ ዘመቻ ኢትዮጵያውያንን ብቻ ሳይሆን በገንዘብና በኢንቨስትመንት ሽፋን የአገሪቱን ጥቅም አሳልፎ በመስጠት በሚገዙ ተሰሚነት ያላቸውን ምእራባውያን ባለስልጣናትን ጋዜጠኞችን የፓርላማ አባላትን ልዩ ለዩ ባለሙያዎችና ሀብታም ነጋዴዎች አማካይነትም የሚከናወን ነው።ወያኔ በነዚህ አገር በቀልና ፀጉረ ልውጥ አጭበርባሪዎች አማካይነት እየፈፀመ ያለውን አገር የመሸጥ ዘመቻ አሳሶቦት በፅናት የሚቃወም በትግል አጀንዳው ውስጥ አካቶ ህዝብን የሚያስተባብርና የሚመራ የፖለቲካ ድርጅት እስከአሁን ያለመኖር ጉዳይ ወያኔን ያለስጋት የሚፈነጭበት አገርና ህዝብ ያገኘ እድለኛ ድረጅት አድርጎታል።ወያኔ የኢትዮጵያን ኪሎ ሜትር ርዝመትና ከ ኪሎ ሜትር የጎን ስፋት ያለው ለም መሬት ለሱዳን በርካሽ ሲሸጥ ህይዎታቸውን ድንበራቸው ላይ ለማሳለፍ ቆርጠው ከተነሱ ጥቂት ገበሬዎችና ደባውን ለህዝባችን በተከታታይ መግለጫው ለህዝብ ይፋ ካደረገው የኢትዮጵያ ድንበር ኮሚቴ በስተቀር ሌሎቻችን ምን መሰረታዊ ስራ ሰራን ስለመሬታችን መሸጥስ የተቆጨን ስንቶቻችን ነን ለትውልድ እያካበትን ያለውንስ አበሳ የምንገነዘብ ይቅርታ ይደረግልኝና በጣም ጥቂቶች ነንለሱዳን ተገምሶ ስለተሸጠው አገር መቃወም ቀርቶ ስለመሸጡም ገና ሳናውቅ ወያኔ ከቀረው የኢትዮጵያ ግዛት ኛውን ከነውሀው ለህንድ ለቻይና ለሳኡዲና ለሌሎች በብሳና ስር ውል ማንም ሳያውቅ በሚስጥር መሸጡን የሽያጩንም ገንዘብ በደቡብ መስራቅ እስያ ባንኮች በመለስ ዜናዊ ስም በተከፈተ የባንክ ሂሳብ ታጭቆ እያቃሰተ ስለመሆኑ እየሰማን እኛ ኢትዮጵያውያን ምን አልን የፖለቲካ ድርጅቶችስ መምራት የሚገባቸው ምሁራንስ ምንም ጉዳዩ በሁለተኛ ደረጃ እየታየ።ይሀን በዘዴና ባለማቋረጥ በሚደረግ ትግል ወያኔን ከወንጀል ድርጊቱ ትንሽ እንኳን ሰቅጠጥ የሚያደርግ እርምጃ መውሰድ ቀርቶ ገና አውርተን ሳንጨርስ የዛሬውም የነገውም ትውልድ ህይዎቱን አሳልፎ እንዲሰጥ የሚጠይቅበትን ትልቅ አገራዊና ትውልዳዊ ጉዳይ ማንም ሳያውቅ ማንም ሳይመክርበት ሌላ የቤት ስራ ይዞ ከተፍ አለ።የኢትዮጵያን ለም መሬት ታይቶ የማይጠገብ ውብ ሸለቆና ሸንተረር ማእድንና ውሀ ባለቤት እንደሌለው ለድርቡሽ አሳልፎ የሰጠ ወያኔ የሽሬን የሽራሮን የተከዜን የአዲያቦንና የባድመን የዋልድባንና የበረሀሌን ፖታሽ አሳልፎ የሰጠ ወያኔ የአሰብን ወደብ ለሸአቢያ ሸጦ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ለጂቡቲ የሚሰጥ ወያኔ ከወደቡ ገቢ ወያኔ ሼር አለው ዛሬ ማንንም ሳያማክር ከድሆች ኢትዮጵያውያን በጉልበት እየነጠቀ አገርንና ህዝብን እያስራበ ትልቅ ግድብ እገነባለሁ ብሎ ተነሳ። ትንሳኤ ግድብ። አሳፋሪው ጉዳይ ወያኔ ይህንን ሲያደርግ የጠየቀም ሆነ በፅኑ የተቃወመ ያለመኖሩ ሳይሆን ግማሻችን ደጋፊ ግማሻችን ተቃዋሚ ሆነን ቁጭ ማለታችን ነው።በዚህም ወያኔ በመበራታቱ የደገፈውን ብርዶላር አምጣ ለማለት የተቃወመውን ወይንም ትንሽ ያንገራገረውን በብሄራዊ ስሜት አልባነትና በሀሞተ ፈሳሳነት እየከሰሰና አግጣጫ እያሳተ እኛ ስንጨቃጨቅ የቀረውን አገር ለመሸጥ ሰፊ ጊዜ ገዛበት።የአገራችንን ጉዳይ በቸልታ የምንመለከት ዝንጉዎች የተካፋፈልንና በአንድነት መቆም የማንችል መሆናችንንም በደንብ ስለተረዳ ክፋትና ተንኮል የማያልቅበት ወያኔ ዛሬ ደግሞ አዲስ አገር የመሸጥ አጀንዳ ይዞ ከተፍ ብሏል።ሰሞኑን ስለአባይ ግድብ ስራ መፋፋምና ከጅረቱ አግጣጫ መለወጥ ጋር ተያይዞ ተፈጥሮ የነበረው ግርግር የግብፁ ሙርሲም ወንዜን በደሜ እጠብቃለሁ ድንፋታ የሁላችንንም ደም ያንተከተከ አገራዊ ጉዳይ ሆኖ እንደሰነበተ ይታወሳል። ይህ በወያኔና በግብፅ መሪዎች ተዋናይነት ይካሄድ የነበረው ቲያትር ዛሬ ከቶ ምንም እንዳልነበረ ምንም እንዳልልሆነ ጭራሽ ደብዛው መጥፋቱን እየታዘብን ነው። ለምን መሰላችሁ ወያኔ አገሪቷን ለሌላ ሽያጭ በመደራደር ላይ ስለሆነ ነው። ሌላ የቤትስራ ሌላ የምናወራው ዜና ሌላ እዳ እያዘጋጀልን ነው ማለት ነው። ወያኔይህ አባይን የመገደብ ጉዳይ በድንገት የወያኔ ግንባር ቀደሞ የኢትዮጵያዊ አርበኝነት መግለጫ ሆኖ የቀረበበት ዋና ምክንያት ወያኔ እንደሚያወራውና እንደሚያስወራው ለኢትዮጵያ ህዝብ እድገትና ብልፅግና ራእይ ኖሮት አስቦ ያደረገው ሳይሆን የግብፅን ህዝብ በተለይም የአክራሪ ሙስሊሙን እንቅስቃሴ አግጣጫ ለማስለወጥ ሆን ተብሎና ግዜ ተጠብቆ በአሜሪካና በኤል በእስራኤል አማካይነት ለወያኔ በተሰጠ ትእዛዝ የሚካሄድ ፕሮጀክት እንጅ የአስዋን ግድብ በሶቪየቶች መገደብ ጋር የተያያዘ የቆየ ታሪካዊ ምክንያትም አለው። የግድቡ ስራ ሲጀመር ምእራባውያን በተለይም አሜሪካውያን አይተው እንዳላዩ የመሰሉትም ለዚህ ነበር። ስራው ከተጀመረና አሜሪካና ኤልም ለግብፅ ማድረስ የፈለጉትን ፖለቲካዊ መልእክት ካስተላለፉና ግብፅን የመጉዳት አቅማቸውን ካሳዩ በኋላ ችግሩን በውይይት ፍቱጨርሱ ማለታቸው ወያኔ አደብ እንዲገዛና አርፈህ የሚሰጡህን ተቀበል ትእዛዝ ማስተላለፋቸው ፕሮጀክቱ የእነሱ እንጅ የወያኔ ያለመሆኑን ያራጋግጣል።ስለሆነም ተንበርካኪው ወያኔ ከአሜሪካ በተሰጠው ትእዛዝ በመልካም ጉርብትና ልማትና የኢኮኖሚ ጥቅም ስም የግድቡን ስራ አቀዝቅዞ ኢትዮጵያን እስከወዲያኛው የሚጎዳ ሌላ የሚያስር ስምምነት ከግብፅ ጋር ለማድረግ ላይ ታች ማለት መጀመሩን እያየን ነው። ስለሆነም ነው ዛሬ ያ ሁሉ ሩጫና ግርግር ቀዝቅዞ ዜናው ከአለም አቀፍ ሚዲያ ከኢትዮጵያና ከግብፅ ፕራዮሪቲ ርእሰ ዜና ውጪ እንዲሆን የተደረገውም። በአሁኑ ወቅት የግብፅና አለም አቀፍ ቱጃሮች ከወያኔ ጋር በሚደረግ ሽርክና ለህንድ ለቱርክ ለቻይናና ለሳኡዲ ወዘተ የኢትዮጵያ ለም መሬት ውሀና ማእድን እንደተሸጠ ሁሉ ዛሬም የኢትዮጵያን ለም መሬት ውሀ ደንና ማእድን ወደፊት ከግድቡ የሚመነጨውንም የኤሌክትሪክ ሀይል በሽርፍራፊ ሳንቲም ለመሸጥ የግድቡንም መጠን ለመቀነስ እየሰሩና እየተደራደሩ ያሉት።የግብፅ መሪዎችና ቱጃሮች በብዙ ምክንያት ውሀውን ድሮ ሲጠቀሙበት እንደነበረው ሁሉ በፍፁም ባለቤትነት ዝንተአለም ሊጠቀሙ እንደማይችሉ ይረዳሉ። ውሀም በትነት በተለይም ወደፊት በአለም ሙቀት መጨመርና በተፈጥሮ ፀጋ መመናመን አብዛኛውን ውሀ በምታመነጨው በኢትዮጵያ አስተማማኝ ዝናብ ያለመኖር የግብፅም እንደ አገር ሊኖራት የሚችለው አስተማማኝ ሰላምና መረጋጋት ወዘተ የሚያሳስባቸው ቢሊየነር ግብፃውያንና ሌሎች ሀብታቸውን ለማሸሽና ሌላ አገር ኢንቨስት ለማድረግ እየመከሩና እየሰሩ ሲሆን ከመረጧቸውም አገሮች አንዷ ኢትዮጵያ ነች። አዲስ አበባም በአሁኑ ወቅት በግብፅ ሀብታሞች ተጨናንቃለች።ይህ ማለት ምን ማለት ነው ይህ ማለት ኢትዮጵያ ከግብፆች ጋር በመልካም ጉርብትና በሰላምና በጋራ ልማት ስም ወያኔ የሚያደርገው ህዝብ የማያውቀው ያልመከረበትና ያልተስማማበት ልፍስፍስ ስምምነት አንዴ ከፀደቀና አለም አቀፍ እውቅና ካገኘ ለዛሬው ሳይሆን ለነገውም ለተነገ ውዲያውም ቀጥሎ ቀጥሎ ለሚመጣውም ወያኔም እኛም ትተነው የምንሄድ የተውልድ አበሳ ማለት እንደሆነ ግልፅ ነው። መፍትሄውም ዛሬ ነገ ሳንል በአንድ ሆነን ይህንን የአገር ሽያጭ ማስቆምና ህገወጥ ነጋዴውንም ማስወገድ መቻል ነው። ይህንን ማድረግ ካልቻልን የወደፊቷ ኢትዮጵያ ምን እንደሚጠብቃት ማሳሰብ ያንባቢዎቼን እውቀት መጠራጠር ይመስልብኛልና አላነሳውም።ወያኔ ጊዜ እየጠበቀ በሚቀይስልን ተለዋዋጭ ተንኮል እየተመራን አንዱን እያነሳን ሌላውን እየጣልን ያለፈውን እየረሳን አዲሱን እያዳነቅን እርስ በርሳችን ከመነታረክና የትውልድ አበሳ ከመሆን እራሳችንን ማዳን ካልቻልን የአገራችን ፖለቲካ መላው እየጠፋ እዳችንም እየከበደ መፍትሄውም ከሰማይ እየራቀ እንደሚሄድ ግን አያጠራጥርም።ስለሆነም አለን የሚሉ የፖለቲካ ድርጅቶች ትግላቸውን በያዝ ለቀቅ ሳይሆን በግልፅ አገራዊና ሁሉን አቀፍ እስትራቴጂካዊ ፕሮግራም መሪና አሰባሳቢ መፈከር ነድፈው ህዝቡን ማስተማር ማሳወቅና ኢንፎርም ማድረግ መምራት ተቀዳሚ አላማቸውና ትልቁ ስራቸው መሆን ይገባዋል። ፕሮግራማቸውንም መንደፍ ያለባቸው ይሄኛው እከሌን ያስደስታል ያኛው እክሌን ያስቀይማል ያስቆጣል ሳይሉ ለጊዜያዊ ታክቲክና ጥቅም ሳይታለሉ ለረጅሙ ግብ ህዝብን ማዘጋጀት የሚችል አግጣጫ ጠቋሚና አሰባሳቢ ትልም መሆን አለበት።በመርሀ ግብራቸው ውስጥም መካተት ካለባቸው ዋናና ቀዳሚ ጉዳዮች አንዱ የኢትዮጵያ ሏላዊ ግዛትና ዳር ድንበር ከየት እስከየት እንደሆነ የማስቀመጥና ለመጠበቅም ያለባቸውን አደራና ሀላፊነት በግልፅ መያዝ ይገበዋል።ነገ መምጣቱ ለማይቀር አገራዊ ጉዳይ ፖለቲካዊ ድርጅቶች በቅድሚያ ራሳቸውን ቀጥሎም ህዝቡን አሰባሳቢ በመሆን መርሀ ግብር አደራጀተው መጠበቁ ወሳኝና ለሚቀጥለው ስራቸውም ጠንካራ መሰረት ነው።ፖለቲካ ድርጅቶችና መሪ ኤሊቶች ይህን መሰረታዊ ጉዳይ ለጊዜያዊ ፖለቲካዊ ጥቅምና መሽኮርመም ወይም ፖለቲካዊ ይሉኝታ ወይም ታክቲክ ወይም በቸልታ የሚያልፉት ከሆነ እንደ ኢትዮጵያ ድንበር ኮሚቴ መግለጫ አዲሱ ብቻ ሳይሆን የነገውም ትውልድ ከማይሸከመው እዳ ውስጥ መነከሩ አይቀርምና ከአሁኑ አካሄድን ማሳመር ለነገ የሚተው ሀላፊነት አይደለም።
ምን አዲሱ ትውልድ ብቻ የነገውም እዳ ውስጥ ተነክሯል
ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ በተመራጩ የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ሙሀማዱ ቡሀሪ በአለ ሲመት ላይ ለመገኘት ትናንት ወደ አቡጃ አቀኑ።ጠቅላይ ሚኒስትሩ በናይጄሪያ ቆይታቸው በፕሬዝዳንቱ በአለ ሲመት ላይ ከመገኘት በተጨማሪ በአገራቱ ግንኙነት ላይም ውይይት ያደርጋሉ።ሙሀማዱ ቡሀሪ ባለፈው መጋቢት በተካሄደው ምርጫ ሀምሳ ሰባት ነጥብ ሁለት በመቶ በሆነ ድምፅ አሸንፈው ነበር ፕሬዝዳንት ለመሆን የበቁት።ናይጄሪያ ከወታደራዊ አገዛዝ ወጥታ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ስታካሂድ የዘንድሮው ለአምስተኛ ጊዜ ነው።የናይጄሪያ አጠቃላይ ምርጫ እንዲካሄድ ታቅዶ የነበረው ባለፈው የካቲት ወር ቢሆንም የአገሪቱ ምርጫ ኮሚሽን ጊዜውን በስድስት ሳምንታት በማራዘሙ ነበር መጋቢት ላይ እንዲካሄድ የተደረገው። ናይጄሪያ በአፍሪካ ከፍተኛ የህዝብ ብዛት ያላት አገር ከመሆኗ ባሻገር ድፍድፍ ነዳጅ በማምረት ከአህጉሪቱ ቀዳሚ ናት።ተመራጩ ፕሬዝዳንት የናይጄሪያውን ኦል ፕሮግረሲቭ ኮንግረስ ፓርቲ በመወከል ነበር የገዢው ፒፕልስ ዴሞክራቲክ ፓርቲ ሊቀመንበር ከሆኑት ጉድላክ ጆናታን ጋር የተወዳደሩት።ኢትዮጵያና ናይጄሪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ ኤ አ ከአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ስልሳ በፊት ነው።ኢትዮጵያ ኤምባሲዋን በናይጄሪያ እ ኤ አ በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ስልሳ አንድ በቀድሞ የአገሪቱ ርእሰ ከተማ ሌጎስ የከፈተች ሲሆን ናይጄሪያ ደግሞ እ ኤ አ በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ስልሳ ሶስት በአዲስ አበባ ከፍታለች። የቀድሞ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እ ኤ አ በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ስድስት ከናይጄሪያ በቀረበላቸው ግብዣ አገሪቱን መጎብኘታቸው የሚታወስ ነው።በተመሳሳይም የቀድሞ የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ኦሊሶጎን ኦባሳንጆ እ ኤ አ በሁለት ሺህ ስድስት ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል።እ ኤ አ አቆጣጠር ሰኔ ሁለት ሺህ ሁለቱ አገራት የናይጄሪያን ምሁራን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ማስተማር የሚያስችል የአቡጃ ስምምነት ተፈራርመዋል።እ ኤ አ በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ስልሳ የናይጄሪያ የመከላከያ ሀይል አባላት በሀረር የጦር አካዳሚ ወታደራዊ ስልጠና መውሰዳቸው የሚታወቅ ነው። ኢዜአ
ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ወደ አቡጃ አቀኑ
የኢትዮጵያ ተጋጣሚ የጋና የሴቶች ብሄራዊ ቡድን ዛሬ ምሽት ሸገር ይገባል። በፓፓ ኒው ጊኒ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የአለም ከሀያ አመት በታች የሴቶች እግር ኳስ የአለም ዋንጫ አፍሪካን ወክሎ ለመሳተፍ ከኢትዮጵያ አቻው ጋር ቅዳሜ ጥቅምት ቀን ሁለት ሺህ ስምንት አመተ ምህረት ከአስር፡ ጀምሮ በአዲስ አበባ ስታድየም የሚጫወተው የጋና ከ ሀያ አመት በታች የሴቶች እግር ኳስ ቡድን ዛሬ ምሽት ሁለት፡አርባ አምስት ላይ አዲስ አበባ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል። ተጨዋቾቹ በአለም ዋንጫ ላይ ተሳትፈው ታሪክ ለማስመዝገብ እንዳሰቡ ተናግረዋል። እንደ ኢትዮ ኪክ ዘገባ ለኢትዮጵያ እና ጋና ከሀያ አመት በታች የሴቶች እግር ኳስ ቡድን ጨዋታ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ሶስት የኡጋንዳ ዳኞች መመደቡን ይፋ አድርጓል። ተጠባባቂ አርቢትርዋ ከብሩንዲ ሲመደቡ የጨዋታው ኮሚሽነር ደግሞ ኬንያዊ ናቸው።
የኢትዮጵያ ከሀያ አመት በታች የሴቶች ብሄራዊ ቡድን ለአለም ዋንጫ ለማለፍ ከጋና ጋር ይጫወታሉ
አዲስ አበባ፣ ሀምሌ ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በኦሮሚያ ክልል በሁለት ሺህ ሁለት ሺህ የምርት ዘመን ከስምንት መቶ ስላሳ ስድስት ሺህ በላይ ሄክታር መሬት በክረምት ስንዴ መሸፈኑን የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ገለፁ። ክልሉ በሁለት ሺህ ሁለት ሺህ አመተ ምህረት ምርት ዘመን ሁለት ነጥብ ሁለት ሚሊየን ሄክታር መሬት በክረምት ስንዴ ለመሸፈን ማቀዱን ገልፀው፥ እስከ አሁን ስምንት መቶ ስላሳ ስድስት ሺህ አንድ መቶ ሰማኒያ ስድስት ሄክታር መሬት ላይ ስንዴ መዘራቱን ጠቁመዋል። በምርት ዘመኑ በስንዴ የሚሸፈነው ማሳ ከሁለት ሺህ የምርት ዘመን አንፃር የአምስት መቶ ሺህ ሄክታር ብልጫ እንዳለው ጠቅሰዋል። በተያዘው ክረምት በምእራብ አርሲ ዞን ዶዶላ ወረዳ በክላስተር እየለማ የሚገኘው የስንዴ ቡቃያ በጥሩ ሂደት ላይ እንደሚገኝም ነው ርእሰ መስተዳድሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ያሰፈሩት።
በኦሮሚያ ክልል ከስምንት መቶ ስላሳ ስድስት ሺህ በላይ ሄክታር መሬት በክረምት ስንዴ ተሸፍኗል ርእሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ
የገጣሚ ዮሀንስ ሞላ ሁለተኛ ስራ የሆነው የብርሀን ሰበዞች የግጥም ስብስብ መፅሀፍ ከነገበስቲያ በብሄራዊ ቴአትር አዳራሽ ከምሽቱ ፡ ሰአት ጀምሮ ይመረቃል።በማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ ውስጠ ወይራ የሆኑ ከሰባ በላይ ግጥሞችን ያካተተው መፅሀፉ፤ በአንድ መቶ አስር ገፆች የተቀነበበ ሲሆን ለአገር ውስጥ በአርባ ስድስት ብር፣ ለውጭ አገራት በ ዶላር ለገበያ ቀርቧል። በምረቃ ስነስርአቱ ላይ ከመፅሀፉ የተመረጡ ግጥሞች የሚነበቡ ሲሆን ወጣትና አንጋፋ ገጣሚያንም ግጥሞቻቸውን ለታዳሚው እንደሚያቀርቡ ተገልጿል። የግጥም መድበሉን ሊትማን መፅሀፍት መደብር ያከፋፍለዋል ተብሏል።ዮሀንስ ሞ ላ ከ ዚህ ቀ ደም በ ሁለት ሺህ አምስት አ ም የብርሀን ልክፍት የተሰኘ የግጥም መፅሀፍ ለአንባቢ ማድረሱ የሚታወስ ሲሆን ጠይም በረንዳ በተሰኘው የራሱ ጦማር ላይ የተለያዩ ርእሰ ጉዳዮችን በመፃፍ ይታወቃል። ገጣሚውበተጨማሪም የዘፈን ግጥሞችን የሚፅፍ ሲሆን ቀደም ሲ ል በ ግጥም የ ተሳተፈበት የ ፀደንያ ገ ማርቆስ ዘፈን፤ ሁለት የአገር ውስጥ፣ አንድ አህጉር አቀፍ ሽልማቶችን አሸንፏል።
የብርሀን ሰበዞች የግጥም መፅሀፍ ሰኞ ይመረቃል
የሱዳን ፕሬዚዳንት ኦማር ሀሰን አል በሽር የኢትዮጵያና ግብፅ የሚኒስትሮች ስብሰባ ዛሬ ይጀመራል የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድቡን በመገንባት ጫናውን ለብቻቸው እንደተሸከሙ፣ የሱዳን ፕሬዚዳንት ኦማር ሀሰን አል በሽር ተናገሩ። ፕሬዚዳንቱ ይህንን የተናገሩት በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ወርቅነህ ገበየሁ ዶክተር የተመራ የኢትዮጵያ ልኡካን ቡድን የጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለ ማርያም ደሳለኝን መልእክት ሲያደርስና በሁለትዮሽ ግንኙነት ላይ በተነጋገረበት ወቅት መሆኑን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ መለስ አለም ለሪፖርተር ገልፀዋል። ኢትዮጵያውያን የህዳሴ ግድቡን የመገንባት ጫና ለብቻቸው ተሸክመዋል፤ ያሉት ፕሬዚዳንት አል በሽር፣ ሱዳናውያን የዚህ እዳ አለብን፤ ብለዋል። የግድቡ መገንባት ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለሱዳንና ለሌሎች ህዝቦችም የበለጠ ጠቀሜታን እንደሚገኝበትም መናገራቸውን፣ ውይይቱን የተከታተሉት አቶ መለስ ገልፀዋል። የኢትዮጵያና የሱዳን እጣ ፈንታ አብሮ የተገመደ መሆኑንና በመንግስታት ለውጥ ወቅትም ሳይላላ እንደቀጠለ ፕሬዚዳንቱ መናገራቸውን አቶ መለስ ጠቁመዋል። የፕሬዚዳንት አል በሽር ንግግር ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ አቋም ጋር የሚመሳሰል ነው። አቶ መለስ የታላቁ ህዳሴ ግደብ የመሰረት ድንጋይን ከአምስት አመት በፊት ባስቀመጡበት ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ ፍትህ ካለ የዚህን ግድብ ግንባታ ወጪ ሱዳን ሀያ በመቶ፣ ግብፅ ስላሳ በመቶ ሊሸፍኑ ይገባል፤ ብለው ነበር። የጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለ ማርያምን መልእክት ይዘው እሁድ ጥር ስድስት ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ሱዳን ካርቱም ከተማ የተገኙት ወርቅነህ ገበየሁ ዶክተር ፣ ኢትዮጵያና ሱዳን የአንድ ወንዝ ልጆች ናቸው፤ ማለታቸውን አቶ መለስ አስታውሰው፣ ከሱዳኑ አቻቸው ጋርም በወቅታዊ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውን አስረድተዋል። በኢትጵያና በሱዳን መካከል ቀደም ብለው የተፈረሙ ስምምነቶች በፍጥነት ተግባራዊ እንዲሆኑና የሁለቱን አገሮች ግንኙነት የበለጠ መጠናከር እንደሚገባው የተግባቡ መሆኑን፣ እንዲሁም በየጊዜው የፖለቲካ ምክክር ማድረግ እንደሚገባ መስማማታቸው ተገልጿል። በተያያዘ ዜና በስድስተኛው የኢትዮጵያና የግብፅ የሁለትዮሽ የጋራ ኮሚሽን ስብሰባ ላይ ለመገኘት በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የሚመራ ልኡካን ወደ ግብፅ ማክሰኞ ጥር ስምንት ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ማምሻውን ማቅናቱን ለማወቅ ተችሏል። ከረቡእ ጥር ዘጠኝ ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ጀምሮ የሁለቱ አገሮች የሚኒስትሮች ስብሰባ የሚካሄድ ሲሆን፣ ሀሙስ በመሪዎች ደረጃ ውይይት እንደሚደረግ አቶ መለስ ለሪፖርተር ገልፀዋል። በዚህም መሰረት ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለ ማርያም ረቡእ ጥር ዘጠኝ ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ወደ ካይሮ ያመራሉ። ይህ የኢትዮጵያና የሱዳን የጋራ ኮሚሽን የተጀመረው እ ኤ አ በአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ ዘጠኝ ነው። የአሁኑ ለስድስተኛ ጊዜ የሚካሄድ ሲሆን፣ በመሪዎች ደረጃ ሲካሄድ ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለ የግብፅ ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ በኢትዮጵያና በሱዳን የውስጥ ጉዳይ ግብፅ ጣልቃ አትገባም ማለታቸው ተደምጧል። የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በመረቁበት ወቅት ፕሬዚዳንቱ ባደረጉት ንግግር፣ ከወንድሞቻችን ጋር ጦርነት ውስጥ አንገባም፣ በወንድሞቻችን ላይም አናሴርም፤ ማለታቸውን የተለያዩ ሚዲያዎች ዘግበዋል። ይህ የፕሬዚዳነቱ ንግግር የሱዳን መንግስት በኤርትራ በኩል ያለውን ድንበሩን በመዝጋቱ ሳቢያ እንደሆነ ተገምቷል። ሱዳን ይህንን ድንበር የዘጋችው የግብፅ ጦር በኤርትራ እንደሰፈረ ከተረዳች በኋላ ነው።
ኢትዮጵያውያን የህዳሴ ግድቡን ለመገንባት ጫናውን ለብቻቸው ስለተሸከሙ እዳ አለብን
አገራት ድንበሮቻቸውን በጥንቃቄ እየከፈቱ ባሉበት በአሁኑ ወቅት የአየር በረራ መጀመርን ተከትሎ በወጡ አዳዲስ ደንቦች ምክንያት ተጓዦች ከኮቪድ ተህዋሲ ነፃ መሆናቸውን በምርመራ እንዲያረጋግጡ ይገደዳሉ። በኢትዮጵያ ይህንን ምርመራ በማድረግ ውጤት ከሚሰጡ ተቋማት መካከል የሆነውና አብዛኞቹ የውጭ አገር ተጓዦችን የሚያስተናግደው ተቋም የምርመራ ፈላጊዎች ቁጥርና አገልግሎቱ ተመጣጣኝ እንዳልሆነ ተገልጋዮች እየተናገሩ ነው። የአየር በረራ አገልግሎት ለረጅም ጊዜ ተቋርጦ በመቆየቱ ለወራት ሲጠባበቁ የነበሩ ተጓዦች ይህንን ምርመራ ለማድረግ ከባድ ፈተና ሆኖብናል ይላሉ። ምክንያቱ ደግሞ ምርመራውን የሚያከናውነው ተቋም የወሰደውን ናሙና ውጤት ለማሳወቅ ቢያንስ አርባ ስምንት ሰአታትን ይፈልጋል። አገራት ደግሞ ተጓዦች ከመሳፈራቸው በፊት ምርመራ እንዲያደርጉ የሚፈልጉበት የሰአት ገደብ ከአርባ ስምንት ሰአት እስከ ዘጠና ስድስት ሰአት እንደየአገሩ ይለያያል። ምርመራውን ከብዙ ጥበቃ በኋላ ባለፈው አርብ እለት ማድረግ የቻሉ ተጓዦች ውጤት አልደረሰም በመባላቸው በረራቸውን ለመሰረዝ እንደተገደዱ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ክሊኒኩ ለተመርማሪዎች ውጤት የሚሰጠው የጉዞው እለት ወይም ከአንድ ቀን ቀደም ብሎ በአስር ሰአት ብቻ ነው። በዚህም ምክንያት የጉዞ ቀን፣ የሚጓዙበት አገር የምርመራ ደንብና የክሊኒኩ ውጤት መስጫ እለት ለማጣጣም ፈታኝ እንደሆነ ተጓዦቹ ጠቅሰዋል። ቢቢሲ ሰኞ ማለዳ ከንጋቱ ፡ ሰአት ጀምሮ ምርመራ በሚሰጠው ተቋም ደጃፍ ላይ ተሰልፈው ያገኛቸው ተጓዦች ተቋሙ ስለምርመራው በቂ መረጃ እንዳልሰጣቸው፣ በረራቸውን በተደጋጋሚ ለመሰረዝ እንደተገደዱና ላልተጠበቀ ወጪና መጉላላት እንደተዳረጉ ገልፀዋል። አገልግሎቱን ፈልገው ወደተቋሙ የሄዱ ሰዎች ለቢቢሲ እንደገለፁት ምርመራውን የሚያደርገው ላቦራቶሪ ስራውን የሚያስኬድበት ግልፅ አሰራር እንዳልዘረጋም ተናግረዋል። አገልግሎት ፈላጊዎች የሚስተናገዱት በቅድሚያ በኢሜይልና በስልክ ከተመዘገቡና የጉዞ ትኬታትና የፓስፖርታቸውን ቅጂ ከሰጡ በኋላ ነው የሚል ማስታወቂያ በክሊኒኩ ደጃፍ ላይ የተለጠፈ ቢሆንም፤ በክሊኒኩ የማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ የተጠቀሱት የስልክ መስመሮች ከአገልግሎት ወጪ ናቸው አልያም ተዘግተዋል። የኢሜይል ምላሽም ከክሊኒኩ ማግኘት አልተቻለም። የቢቢሲ ዘጋቢዎችም ይህንኑ ማረጋገጥ ችለዋል። የክሊኒኩ ሰራተኞች በበኩላቸው ሰዎች ከተመዘገቡ በኋላ በራሳቸው ምክንያት ሊቀሩ ስለሚችሉ ይህንን የቅድመ ምዝገባ አሰራር ትተን ሰዎች እንደ አመጣጣቸው ማስተናገድ ጀምረናል ይላሉ። ሰኞ ማለዳ በስፍራው ተሰልፈው ከነበሩ ተጓዦች ቢቢሲ እንደተረዳው አንዳንዶቹ ተገልጋዮች እሁድ ከቀትር ጀምሮ ለረዥም ሰአት አገልግሎቱን ለማግኘት በዝናብ ተሰልፈው የጠበቁ ቢሆንም አሁን ደክሞናል ከዚህ በላይ አናስተናግድም በሚል እንዲበተኑ ተደርገዋል። ሌሎች ደግሞ ነገ በአዲስ መልክ አንሰለፍም በሚል ቅሬታ በማንሳታቸውና የክሊኒኩን በር አናዘጋም በማለታቸው ስም ዝርዝራቸው ተፅፎ በቀጣይ ቀን ቅድሚያ ተሰጥቷቸው እንደሚስተናገዱ ቃል እንደተገባላቸው ተናግረዋል። ክሊኒኩ በዚህ መንገድ ተገልጋዮቹን ካሰናበተ በኋላ የተወሰኑ ሰዎችን አሾልኮ እንዳስገባና አገልግሎት እንደሰጣቸው በቦታው ነበርኩ ያሉ እማኝ ተናግረዋል። በአካባቢው የሚገኙ የመኪና አስተናባሪዎችና የጎዳና ተዳዳሪዎች የችግሩን ስፋት በመረዳት በጠዋት ወረፋ በመያዝ ሰልፋቸውን እስከ ሁለት መቶ ብር እየሸጡ እንደሚገኙ ተገልጋዮች ይናገራሉ። የምርመራ አገልግሎት ሰጪው ተቋም በርካታ ለምርመራ የሚመጡ ሰዎች በሚስተናገዱበት በአንደኛው ቅርንጫፉ በሁለት ነርሶችና በሁለት ናሙና ሰብሳቢዎች ብቻ አገልግሎቱን እየሰጠ እንደሆነና የሚሰጠው ምርመራው አገልግሎቱን ከሚፈልገው ሰው ጋር ተመጣጣኝ እንዳልሆነ ቢቢሲ ለመታዘብ ችሏል። የቢቢሲ ዘጋቢ ሰኞ ማለዳ በስፍራው እንደተመለከተ የአገልግሎት ደረሰኝ ወረቀት ማተሚያ ማሽን ብልሽት ገጥሟል በሚልም ክሊኒኩ ለግማሽ ሰአት ያህል ስራውን አቁሞ ነበር። ክሊኒኩ ምንሊክ ሆስፒታል አካባቢና ቡልጋሪያ ባሉት ቅርንጫፎቹ የምርመራ አገልግሎት ይሰጣል ቢባልም የሌሎች ቅርንጫፎቹ ተገልጋዮች ከሌሎች ቅርንጫፎች ይልቅ ወደ አንደኛው ክሊኒክ በብዛት ሄደው ምርመራ ለማግኘት እየጣሩ ነው። ወደ ሌላ ቅርንጫፍ ሄደን እድላችንን እንሞክር ስንላቸውም መልስ አይሰጡንም፣ መረጃ እንኳን ማግኘት ብርቅ ነው ይላሉ ስማቸውን መግለፅ ያልፈለጉ ተገልጋይ። ሰኞ በዚህ ቅርንጫፍ ረዣዥም ሰልፎች የነበሩ ሲሆን በምንሊክ ሆስፒታል አካባቢ በሚገኘው የክሊኒኩ ቅርንጫፍ ግን የተገልጋዩ ቁጥር አነስተኛ ሆኖ ታይቷል። ክሊኒኩ ተመርማሪዎችን አንድ ሺህ ሶስት መቶ ሀያ ብር ለአገልግሎቱ ካስከፈለ በኋላ ውጤቱን የሚሰጠው ከአርባ ስምንት ሰአታት በኋላ እንቁላል ፋብሪካ አካባቢ በሚገኘው ቅርንጫፉ ብቻ ነው። ጠዋት በረራ ያላቸው ሰዎች ውጤት ስለማይደርስላቸው በብዛት ለድጋሚ የትኬት ማስቀየሪያ ወጪ፣ እንዲሁም ለሌላ አዲስ ምርመራ ወጪ እየተዳረጉ መሆናቸውን ቢቢሲ ካናገራቸው ሰዎች ለመረዳት ችሏል። ቢቢሲ ምርመራውን ከሚሰጠው የኢንተርናሽናል ክሊኒካል ላቦራቶሪስ ምላሽ ለማግኘት በማስታወቂያ ሰሌዳቸው ላይ ባሰፈሩት የስልክ አድራሻ በተደጋጋሚ ቢደውልም ቁጥሩ ስለማይሰራ መልስ ማግኘት አልቻለም።
ኮሮናቫይረስ፡ የውጭ አገር ተጓዦች የኮቪድ ምርመራ ለማድረግ ፈተና ሆኖባቸዋል
የአፍሪካ ሶርሲንግና የፋሽን ሳምንት ኤክስፖ የፊታችን ማክሰኞ በሚሊኒየም አዳራሽ ይከፈታል። አዘጋጁ ትሬድ ኤንድ ፌይርስ አፍሪካ ሊሚትድ የተሰኘውና በምስራቅ አፍሪካ አካባቢ መሰል የንግድ ትርኢቶችን በማዘጋጀት የሚታወቀው አውሮፓዊ ድርጅት ከትላንት በስቲያ ረፋድ ላይ ቦሌ በሚገኘው ጎልደን ቱሊፕ ሆቴል ኤክስፖውን አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ በዚህ የንግድ ትርኢትና ኮንፍረንሰ ላይ በጅምላና በችርቻሮ የቡቲክ ስራ የተሰማሩ ነጋዴዎችን ጨምሮ በጨርቃጨርቅና አልባሳት በልዩ ልዩ የመስተንግዶ ስራ የተሰማሩ መዋቢያና መጫሚያ አምራችና አከፋፋዮች በፋሽንና በዲዛይን ስራ የተሰማሩና ከ በላይ የዘርፉ አምራችና ላኪዎች እንደሚሳተፉ ተናግረዋል። እነዚህ የዘፍ ተዋናዮች ኢትዮጵያውያን ጨምሮ ከ የአለም አገራት ምርቶቻቸውን ይዘው እንደሚቀርቡም ተገልጿል። እንደ ኤግዚቢሽኑ አዘጋጆች ገለፃ በአጠቃላይ በኤግዚቢሽኑ ላይ ከ ሺህ በላይ ከአለም ዙሪያ የሚመጡ ተሳታፊዎች ይጠበቃሉ። ከመስከረም ቀን አመተ ምህረት በሚቆየው ከዚህ የንግድ ትርኢት ጎን ለጎን የሶስት ቀናት ጉባኤ የሚካሄድ ሲሆን ጉባኤው በዋናነት በአሜሪካ የአፍሪካ ከቀረጥና ኮታ ነፃ የንግድ እድል አጎዋ ላይ በዘርፉ ኢንቨስትመንትና ቀጣይነት ዙሪያ በቢዝነስ አጋርነትና በሎጂስቲክና ፋሽን ዙሪያ በተያያዥ ጉዳዮች ላይ ከመንግስትና ከኢንዱስትሪው ተወክለው የሚገኙ የአለም ኤክስፐርቶች የመፍትሄ ሀሳቦቻቸውን በጉባኤው አቅርበው ውይይትና ውሳኔ እንደሚካሄድባቸው አዘጋጆቹ ገልፀዋል። ለአራት ቀናት የሚቆየውን ይህን የፋሽን ሳምንት ትርኢት ሰዎች እንዲጎበኙትም ጥሪ አቅርበዋል።
የአፍሪካ የፋሽን ሳምንት ኤክስፖ ማክሰኞ ይከፈታል
አዲስ አበባ፣ መስከረም ዘጠኝ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ ሀበሻቪው ከማልታ ኤምባሲ ጋር በመተባበር በማልታ ለመጀመሪያ ጊዜ፤ በካናዳ ደግሞ ለአምስትተኛ ጊዜ የኢትዮጵያ ፊልም ፌስቲቫል ሊያካሂድ ነው። በፌስቲቫሉ ላይ በማልታ አፊኒ፣ አባይ ወይስ ቬጋስ እና ዝምታዬ የተሰኙ ፊልሞችን በሴንት ጀምስ ካሻሊየር ሲኒማ ከጥቅምት አንድ እስከ ጥቅምት ሶስት፤ ሁለት ሺህ አመተ ምህረት ለእይታ እንደሚቀርብ ተነግሯል። በተመሳሳይ በለንደን ላምባዲናና አፊኒን በሪትዝ ሲኒማ ከጥቅምት ስምንት እስከ አስር እንደሚያሳይ ተጠቁሟል። ፊልሞቹ ለሀገራቱ ዜጎች፣ ለዘርፉ ባለሙያዎችና ለዳያስፖራው ማህበረሰብ አባላት እንዲሁም ጥሪ ለተደረገላቸው እንግዶች ለእይታ የሚቀርቡ መሆኑም ነው የተገለፀው። ስነ ስርአቱ በውጭ ሀገር ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከሀገራቸው ኪነ ጥበብ ጋር ለማገናኘት ከሚፈጥረው እድል እንዲሁም ለኢንዱስትሪው እድገት ከሚኖረው ፋይዳ ባለፈ በዲፕሎማሲው መስክም በሀገራቱ መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጎልበት ከፍ ያለ አስተዋፅኦ አለው ተብሏል። መሰል መርሀ ግብሮች ባለፉት አመታት በተለያዩ አለም ሀገራት ሲዘጋጁ የቆየ ሲሆን ፥ ዘንድሮ አራት የኢትዮጵያ ፊልሞችን በማልታና ካናዳ ለእይታ ይቀርባሉ ተብሏል። የፌስቲቫሉ አዘጋጅ ሀበሻ ቪው ድርጅት በቀጣይ የተለያዩ ሀገርኛ ፊልሞችን ወደተለያዩ አለም ሀገራት በመውሰድና በማስተዋወቅ ተወዳዳሪነታቸው ለማሳደግ የሚሰራ መሆኑን ስራ አስፈፃሚዋ ወይዘሮ ትእግስት ከበደ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል። በመራኦል ከድር
የኢትዮጵያ ፊልም ፌስቲቫል በማልታና ለንደን ሊካሄድ ነው
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር የኢትዮኤርትራ ድንበርን አቋርጠው ኤርትራ የሚገኘውን ግንቦት ሰባት የተባለ በተወካዮች ምክር ቤት ሽብርተኛ የተባለ ድርጅትን ሊቀላቀሉ ሲሄዱ ተይዘዋል በሚል የሽብር ክስ የተመሰረተባቸው እነ ብርሀኑ ተያሬድ ላይ የአቃቤ ህግ ምስክር ተሰማ። ዛሬ ነሀሴ አመተ ምህረት በፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡት አንደኛ ተከሳሽ ብርሀኑ ተያሬድ ሁለተኛ ተከሳሽ እየሩሳሌም ተስፋው ሶስተኛ ተከሳሽ ፍቅረማርያም አስማማው እንዲሁም አራተኛ ተከሳሽ ደሴ ካህሳይ አቃቤ ህግ በፃፈውና ለተከሳሽ በደረሰው የክስ ማመልከቻ ላይ አቃቤ ህግ የሰው ማስረጃ ምስክር አልጠቀሰም እኛም መቃወሚያ ስናስገባም ሆነ እምነት ክህደት ቃል ስንሰጥ ይህን ግምት ውስጥ በማስገባት ነው በመሆኑም የአቃቤ ህግ ምስክር ሊሰማብን አይገባም በሚል ተቃውሞ ቢያቀርቡም አቃቤ ህግ ለፍርድ ቤቱ ባስገባው ክስ ላይ ምስክሩን መጥቀሱን በማስረዳት ምስክሩ እንዲሰሙለት ጠይቋል። ፍርድ ቤቱ የደረሰው የክስ ማመልከቻ ላይ ምስክር እንደተመዘገበ በማረጋገጥም ብቸኛ ሆነው የቀረቡትን አንድ የአቃቤ ህግ ምስክር ሰምቷል። ምስክሩም ከኛ ኛ እና ኛ ተከሰሾች ጋር ሰማያዊ ፓርቲ በሰላማዊ ትግል ውስጥ ሆነው እንደሚተዋወቁ የካቲት አመተ ምህረት በኛ እና ኛ ተከሳሽ አማካኝነት ሰላማዊ ትግሉ እንዳላዋጣ በመጥቀስ ግንቦት ሰባትን ለመቀላቀል ወደ ኤርትራ መጓዝ ማሰባቸውን ገልፀውለት በዚያው ቀን ማታ ኛ ተከሳሽን ጨምሮ ወደ ባህር ዳር እንደተጓዙ ለችሎቱ አስረድቷል። ባህር ዳር ሲደርሱ ጠዋት ላይ ግን ምስክሩ ሀሳቡን በመቀየር ወደ አዲስ አበባ መመለስ እንደሚፈልግ እንደገለፀላቸው ኛ ተከሳሽ በበኩሉ ጎንደር ላይ የምናገኘው ሰው ስላለ ቢያንስ እሱን ካገኘሀው በኋላ መመለስ ትችላለህ እናዳለው ነገር ግን ምስክሩ በሀሳቡ ባለመስማማት ወደ አዲስ አበባ መመለሱንና ሌሎቹ ሶስቱ ግን ጉዟቸውን መቀጠላቸውን አስረድቷል። ባህር ዳር ላይ ለምን ለመመለስ ወሰንህ የሚል መስቀለኛ ጥያቄ ከኛ ተከሳሽ የቀረበለት ምስክሩ በወቅቱ ስሜታዊ የሚያደርጉ የግል ጉዳዮች ስለነበሩብኝ በስሜታዊነት የወሰንኩት ውሳኔ በመሆኑ ነው ሲል ተናግሯል። ምስክሩ ለምስክርነት ያስገደደህ አካል የለም ወይ ተብሎ ሲጠየቅ የለም የሚል መልስ ሰጥቷል። ግንቦት ሰባት ነፃ አውጭ ድርጅት ነው ወይስ አሸባሪ ተብሎ በተከሳሾች መስቀለኛ ጥያቄ ተነስቶ አቃቤ ህግ ተቃውሞውን በማሰማት ድርጅቱ በተወካዮች ምክር ቤት አሸባሪ ተብሏል። ይህ የህግ ጉዳይ ነው በማለት ጥያቄውን ምስክሩ የመመለስ ግዴታ እንደሌለባቸው አስረድቷል። ፍርድ ቤቱም ይህን ተቃውሞ ተቀብሎ ምስክሩ ጥያቄውን እንዲያልፉት ተደርጓል። ማእከላዊ ታስረህ ነበር ድብደባም እንደደረሰብህ በሚዲያ ሳይቀር ተዘግቧል። ልክ ነው ተብሎ በመስቀለኛ ጥያቄ ሲጠየቅ ምስክሩ ማእከላዊ ቃል እንድሰጥ ተደርጌያለሁ ግን አልታሰርኩም የሚል መልስ ሰጥቷል። ፍርድ ቤቱ የምስክሩን ቃል ከሰማ በኋላ የአቃቤ ህግን አስተያየት የጠየቀ ሲሆን አቃቤ ህግ የምስክሩ ቃልና የሰነድ ማስረጃውን መርምሮ ፍርድ ቤቱ ብይን እንዲሰጥለት ጠይቋል። ፍርድ ቤቱም ብይኑን ለማሰማት ለመስከረም አመተ ምህረት ቀጠሮ ሰጥቷል።
ኤርትራ ሄደው ግንቦት ን ሊቀላቀሉ ነበር ተብለው በተከሰሱት ላይ ምስክርነት ተሰማ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት ስድስት ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የተመራ ልኡክ በኦሮሚያ ክልል የግብርና ስራዎችን እየጎበኘ ነው። የፌዴራል እና የክልል መንግስታት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች እና አዲስ የተሾሙ ሚኒስትሮች በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን አዷ ወረዳ ተገኝተው በኩታ ገጠም የለሙ እህሎች፣ አትክልት እና ፍራፍሬዎችን እየጎበኙ ነው። የኩታ ገጠም የእርሻ ስራ አርሶ አደሮችን ይበልጥ እንዲተሳሰሩ አድርጓቸዋል ሲሉ የገለፁት የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ አርሶ አደሮች እንዲያለሙ ከማድረግ ጎን ለጎን በጋራ እንዲያቅዱ፣ ተመሳሳይ ቴክኖሎጂ እንዲጠቀሙ እና ምርት እንዲያመርቱ በመደረጉ ይበልጥ እንዲቀራረቡ እድል ፈጥሯል ነው ያሉት። ርእሰ መስተዳድሩ አክለውም ለአርሶ አደሮች የሚሰጠው ትኩረት ይበልጥ ይጠናከራል ብለዋል። ጉብኝቱ ዛሬና ነገ እንደሚቀጥል ይጠበቃል። ከሰሞኑ በጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ የተመራ ልኡክ በኦሮሚያና ሶማሌ ክልሎች የተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር የግብርና ስራዎችን መጎብኘቱ ይታወቃል። በደበላ ታደሰ ተጨማሪ ፎቶ ከኦቢኤን ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ ድረ ገፅ፦ ፌስቡክ፡ ዩትዩብ፦ ቴሌግራም፦ ትዊተር፦ በመወዳጀት ይከታተሉን። ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ ልኡክ በኦሮሚያ ክልል የግብርና ስራዎችን እየጎበኘ ነው
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ ሀያ አራት፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የኢትዮጵያን ጥሪ የተቀበሉ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጦርነቱ የተካሄደባቸውን አካባቢዎች ለመጎብኘት ሰመራ ገብተዋል። በኢትዮጵያ ዳያስፓራ ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሀመድ ኢድሪስ የሚመራው ቡድን ከዳያስፓራዎቹ ጋር በመሆን ነው አካባቢዎቹን ለመጎብኘት ሰመራ የገቡት። በቀጣይ ቀናት በአማራና አፋር ክልሎች በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችንና ነዋሪዎችን ይጎበኛሉ ተብሎም ይጠበቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አቢይ አንድ ሚሊየን ዳያስፓራዎች የውጭውን ጫና ለመቀልበስ ወደ ሀገር እንዲገቡ ባደረጉት ጥሪ መሰረት በርካቶች ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል። በሀብታሙ ተ ስላሴ ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ ድረ ገፅ፦ ፌስቡክ፡ ዩትዩብ፦ ቴሌግራም፦ ትዊተር፦ በመወዳጀት ይከታተሉን። ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
ዳያስፖራዎች ጦርነቱ የተካሄደባቸውን አካባቢዎች ለመጎብኘት ሰመራ ገቡ
ኢሳት መስከረም በአዲስ አበባ ከተማና በዙሪያዋ ባሉ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች ማክሰኞ የተቀሰቀሰውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ የኢትዮጵያ መንግስት የኢንተርኔት አገልግልቶ ማቋረጡን የብሪታኒያው አለም አቀፍ የማሰራጫ ጣቢያ ረቡእ ዘገበ። ተቃውሞውን ምክንያት በማድረግ በተወሰደው በዚሁ እርምጃ በመደበኛና በተንቀሳቃሽ የስልክ አገልግሎት የኢንተርኔት አገልግሎትን ሲያገኙ የነበሩ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች አገልግሎቱ እንደተቋረጠባቸው ታውቋል።በተንቀሳቃሽ የእጅ ስልክ የላቀ ነው የተባለን የኢንተርኔት አገልግሎት ለማግኘት ከኢትዮቴለኮም ጋር ውል የፈፅሙ ተጠቃሚዎች ሳይቀር የኢንተርኔት አገልግሎት እያገኙ አለመሆናቸውን ረቡእ በአበይት የአፍሪካ ጉዳዮች ዙሪያ ባቀረበው ዝግጅት አመልክቷል።ነዋሪነታቸው በመዲናይቱ አዲስ አበባ እና ሌሎች ከተሞች የሆነ ተጠቃሚዎች በበኩላቸው የኢንተርኔንት አገልግሎት ከሰኞ ጀምሮ መቋረጡን ገልፀዋል።በአንዳንድ አካባቢዎች የመደበኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ረቡእ ቢቀጥልም የተንቀሳቃሽ የእጅ ስልኮች ከአገልግሎቱ ውጭ መሆናቸውን ከተጠቃውሚዎችና ከ መረጃ ለመረዳት ተችሏል።በቅርቡ አጨቃጫቂ ነው የተባለ የኢንተርኔት አጠቃቀም አዋጅን ያፀደቀው የኢትዮጵያ መንግስት በኦሮሚያና አማራ ክልሎች በመካሄድ ላይ ያሉ ተቃውሞዎችን ተከትሎ በተደጋጋሚ የኢንተርኔት አገልግሎት ላይ እርምጃ ሲወስድ መቆየቱ ይታወሳል።በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ መንግስት በአገልግልቱ ላይ በሚወስደው እርምጃ በመደበኛ የስራ እንቅስቃሴው ላይ ተፅእኖ ፈጥሮ ማሳደሩን በቅርቡ መግለፁ የሚታወቅ ነው።
በኢትዮጵያ ኢንተርኔት መቋረጡን ቢቢሲ ዘገበ
የቀድሞ የግብፅ ፕሬዝደንት ሆስኒ ሙባረክ በዘጠና አንድ አመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለዩ። ሆስኒ ሙባረክ ህይወታቸው ያላፈው ግብፅ ካይሮ በሚገኝ ሆስፒታል ውስጥ ህክምና እየተደረገላቸው ሳለ ነው። ሆስኒ ሙባረክ እ አ አ ሁለት ሺህ ላይ በግብፅ የአረብ አብዮት ከተቀሰቀሰ በኋላ በአገሪቱ ጦር ከሰልጣናቸው እንዲነሱ ተደርገዋል። የቀድሞ ፕሬዝደንት ግብፅን ለሶስት አስርት አመታት መርተዋል። የአረብ አብዮት በተቀሰቀሰ ወቅት ለተቃውሞ በወጡ ሰልፈኞች ላይ በተወሰደው እርምጃ በተባባሪነት ተጠያቂ ተደርገው የጥፋተኝነት ውሳኔ ተላልፎባቸው ነበር። ይሁን እንጂ ከሶስት አመት በፊት የተመሰረቱባቸው ክሶች ውድቅ ተደርገው ነፃ ወጥተው ነበር። የቀድሞ ፕሬዝደንት ህልፈተ ህይወትን ይፋ ያደረገው የግብፅ ብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ ነው። ሙባረክ ከአንድ ወር በፊት የቀዶ ህክምና ማድረጋቸውን እና በፅኑ ህሙማን ማቆያ ውስጥ መቆየታቸውን የቤተብ አባሎቻቸው ለግብፅ መገናኛ ብዙሀን ተናግረዋል። ሙባረክ ከልጅ ልጃቸው ጋር በሆስፒታል ሳሉ የተነሱት ፎቶግራፍ በርካቶች ተጋርተውት ነበር። ባሳለፍነው ቅዳሜ የሙባረክ የልጅ ልጅ የሆነው አላ፤ አያቱ በፅኑ ህሙማን ማቆያ ውስጥ እንደሚገኙ አረጋግጦ ነበር። እአአ አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሀያ ስምንት የተወለዱት ሙባረክ፤ በወጣትነት እድሜያቸው የግብፅ አየር ሀይልን የተቀላቀሉ ሲሆን፤ የአረብ አስራኤል ጦርነት ወቅት ጉልህ ሚና ተጫውተዋል። ፕሬዝደንት አንዋር ሳዳት መገደላቸውን ተከትሎ ሙባረክ የግብፅ ፕሬዝደንት በመሆን መንበረ ስልጣኑን ይዘዋል።
የቀድሞ የግብፅ ፕሬዝደንት ሆስኒ ሙባረክ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ
በሰሜን ጎንደር ዞን ጭልጋ ወረዳ አዲስ ውጥረት መቀስቀሱ ተሰማ። ባለፈው እሁድ የተሰጠውን ህዝበውሳኔ ተከትሎ የተቀሰቀሰው ውጥረት እስከአሁን የአራት ሰዎችን ህይወት ማጥፋቱ ተሰምቷል። ከፍተኛ ቁጥር ያለው የመንግስት ሰራዊትም ወደ አካባቢው መግባቱ ታውቋል። ያለህዝብ ይሁንታ ቀደም ብለው የተካለሉት አርባ ሁለትቱ ቀበሌዎች ላይ ህዝበ ውሳኔ እንዲካሄድ ከህዝብ ግፊት እየተደረገ ባለበት በዚህ ወቅት ግጭት መፈጠሩ ጉዳዩን አሳሳቢ አድርጎታል። በህዝብ ተቃውሞ ውድቅ በተደረጉት አራት ቀበሌዎች ህዝበ ውሳኔ እንዲደረግባቸው በህወሀት መንግስት በኩል እንቅስቃሴ መጀመሩ ለግጭቱ መንስኤ እንደሆነ የአካባቢው የኢሳት ምንጮች ገልፀዋል። በሰሜን ጎንደር የቅማንትና የአማራን ማህበረሰብ ለመለየት በሚል የተካሄደውን ህዝበ ውሳኔ ተከትሎ ግጭት እያገረሸ ይገኛል። ምክንያቱ ደግሞ የቅማንት ኮሚቴ አባላት የሚባሉና በህወሀት የሚመሩ ታጣቂዎች የምርጫው ውጤት ለምን አቅጣጫውን ቀየረ በሚል ህዝቡን በማስጨነቃቸው ነው ተብሏል። የኢሳት ምንጮች እንደሚሉት ህወሀት በአካባቢው ከተካሄደው ህዝበ ውሳኔ ሊማር አልቻለም። እንዲያውም በአካባቢው ግጭት በመፍጠር ህዝበ ውሳኔ ባልተካሄደባቸው አራትቱ የቅማንትና የአማራ ህዝብ የጋራ መኖሪያዎች ድምፅ መሰጠት አለበት በሚል ህዝቡን ለምርጫ ማስገደድ ጀምሯል ነው የተባለው። በ ቱ ቀበሌዎች ህዝበ ውሳኔው ይካሄዳል ከተባለ በኋላ በአራትቱ ቀበሌዎች የአካባቢው ህብረተሰብ አንመረጥም በሚል ለምዝገባ ፍቃደኛ አልሆነም ነበር። እነዚሁም ቀበሌዎች ለዛ፣አወራረዶ፣አደዘና ገለድባ ናቸው። እናም ከፌደራል ፣ከክልልና ከዞን የተላኩ ካድሬዎች የአካባቢውን ህዝብ ሰብስበው ለዘመናት ሲጠየቅ የነበረው የቅማንት ማንነት ጥያቄ በዚህ መልኩ ሊደፈን አይገባም በማለት በዛቻ ቅስቀሳ ጀምረዋል። ይህንኑ ተከትሎም በነዚሁ ቀበሌዎች ግጭት መቀስቀሱንና አራት ሰዎች ሌሊቱን መገደላቸውን ምንጮቻችን ገልፀዋል። የቅማንት ማህበረሰብ አሸንፏል የተባለበት ኳርበር ኮዛ ቀበሌም ምርጫው ተጭበርብሯል በሚል ህዝቡ ተቃውሞ አሰምቷል። በዚህችው ቀበሌ አንድ ሺህ አንድ መቶ አርባ ስምንት ቅማንት ነን በሚል ሁለት ሺህ አራት መቶ ሀያ ስድስት ደግሞ አማራ ነን ብለው ድምፅ ለመስጠት የተመዘገቡ ቢሆንም ውጤቱ የተገላቢጦች መሆኑ ብዙዎችን አስገርሟል። ብዙዎቹ አማራ ነን የሚሉት ድምፃችን የት ገባ እያሉ እየጠየቁ መሆናቸውም ተነግሯል። ይህ ብቻ አይደለም በህወሀት ብአዴን ውሳኔ አርባ ሁለት ቀበሌዎች በቅማንት ስር ይተዳደራሉ ተብሎ ቀደሞ መወሰኑም ጥያቄ እያስነሳ ይገኛል። በእነዚህም አካባቢዎች መወሰን ያለበት ህዝቡ እንጂ አገዛዙ አይደለም ባይ ናቸው።ቅማንትና አማራ አንለይም የሚሉት የጎንደር ነዋሪዎች።
በሰሜን ጎንደር ዞን ጭልጋ ወረዳ አዲስ ውጥረት ተቀሰቀሰ
የአለም አቀፍ እግር ኳስ ማሀበር ፊፋ የሁለት ሺህ ሀያ ሁለት የአለም እግር ኳስ ዋንጫ እንድታዘጋጅ ሲመርጣት ያልተባለ ነገር የለም። በርሀማነቷ አለም እንደ አይኑ ብሌን ለሚሳሳለት እግር ኳስ ምቾት አይሰጥም በሚል ፊፋ ውሳኔውን እንዲያጤን ግፊት ሲደረግበት ቆይቷል። የእስያ አሀጉር አካል የሆነችው ኳታር በርሀማነቷ ጎን ለጎን ተፈጥሮ ያጎናፀፋት ፀጋ ግን ከሰሞኑ አንቱታን ያተረፈላትን ታሪክ አስመዝግቦላታል። ኛውን የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በስኬት ማጠናቀቋ የፊፋን ውሳኔ ትክክለኛነት ማሳያ ሆኗል። የአለም አቀፍ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር አይኤኤኤፍ በባለቤትነት በየሁለት አመቱ የሚያሰናዳው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናን ያዘጋጀችው ኳታር ባለፉት አስር ተከታታይ ቀናት ያልተጠበቁ አስደናቂ አሸናፊዎችን ብቻ ሳይሆን በተለይ ከኢትዮጵያውያን ውጪ ሆኖ ለሁለት አስርታት ያህል ርቆ ለቆየው የማራቶን ውጤት ወደ ቤቱ እንዲመለስ ምክንያት ሆኖ ባለፈው እሁድ መስከረም ሀያ ስድስት ቀን ሁለት ሺህ አመተ ምህረት ፍፃሜውን አግኝቷል። በሁለት ወርቅ፣ በአምስት ብርና በአንድ የነሀስ ሜዳሊያ ከአለም አምስተኛ ከአፍሪካ በኬንያ ተበልጣ ሁለተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀችው ኢትዮጵያ፣ በኳታሩ የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ያስመዘገበችው የማራቶን ውጤት እ ኤ አ በሁለት ሺህ አንድ ኤድመንተን ላይ ገዛኸኝ አበራ ካስመዘገበው የወርቅ ሜዳሊያ በኋላ የተገኘ መሆኑ ውጤቱን ልዩ እንደሚያደርገው እየተነገረ ይገኛል። በኳታሩ የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ማጠናቀቂያ ላይ በወንዶች መካከል በተደረገው የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያኑ የርቀቱ አሸናፊዎች ሌሊሳ ዲሳሳና ሙስነት ገረመው የወርቅና የብር ሜዳሊያ ባለቤቶች የሆኑበትን ውጤት አስመዝግበዋል። ይህ ውጤቱ ልዩ እንዲሆን በዋናነት ምክንያት የሆነው፣ አትዮጵያውያን አትሌቶች በግል በሚደረጉ የጎዳና ላይ ውድድሮች በውጤታማነታቸው የሚታወቁ ቢሆንም፣ በአለም አትሌክስ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ግን እንዲህ እንደ አሁኑ የወርቅና የብር ሜዳሊያ ባለቤት ለመሆን አመታትን መጠበቅ ግድ ብሏቸው መቆየቱ ነው። ከዚህ ውጪ ኢትዮጵያ በሴቶች አስር ሜትር በለተሰንበት ግደይ የብር፣ በአምስት ሜትር ወንዶች በሙክታር እንድሪስና ሰለሞን ባረጋ አማካይነት የወርቅና የብር፣ በሶስት ሜትር መሰናክል በለሜቻ ግርማ የብር፣ በአንድ አምስት መቶ ሜትር ጉዳፋይአፍ ፀይዬ የነሀስና በአስር ሜትር ወንዶች ኦሪገን በናይኪ አካዴሚ እየሰለጠነ በሚገኘው ዮሚፍ ቀጀልቻ የብር ሜዳሊያዎች መመዝገባቸው፣ ኢትዮጵያ በደረጃ ሰንጠረዡ ከተካተቱት አገሮች ተርታ እንድትጠቀስ ያስቻሉ ሆነዋል። በዘይት ሀብቷ የበለፀገችው ኳታር ከተፈጥሮ ጋር ታግላ ባሳናዳችው በዚህ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በርካታ አስገራሚና አስደናቂ ገጠመኞች ሲስተናገዱ ታይቷል። ከገጠመኞቹ መካከል በመክፈቻ በሴቶች መካከል በተደረገው የማራቶን ውድድር ላይ ኢትዮጵያውያኑን ጨምሮ ለአሸናፊነት ትልቅ ግምት የተሰጣቸው ብዙዎቹ እንስቶች ሩጫው ተጀምሮ ጥቂት ኪሎ ሜትሮችን ብቻ ሮጠው ማቋረጣቸው የውድድሩ ባለቤት አይኤኤኤፍን ጨምሮ በርካቶችን ያስደነገጠ መሆኑ ከብዙ በጥቂቱ ይጠቀሳል። ኢትዮጵያን የወከሉት ሶስቱም ማቋረጣቸውን ተከትሎ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አትሌቶቹ ለሶስት ወራትና ማናቸውንም ውድድር እንዳያደርጉ ክልከላ ማድረጉ ይታወሳል። ከአለም ሻምፒዮናው ከፍ ብሎ ከሁለት መቶ በላይ አገሮች በተለያዩ የውድድር አይነቶች የሚሳተፉበት ኦሊምፒክ ደግሞ ከዘጠኝ ወር በኋላ በጃፓን ቶኪዮ በሚመጣው ክረምት እንደሚካሄድ ይጠበቃል። የሁለት ሺህ ሀያ ኦሊምፒክ አስተናጋጇ ቶኪዮ ከኳታር ያልተናነሰ ሞቃታማ የአየር ፀባይ እንደሚኖራት ከወዲሁ እየተነገረ ይገኛል። ኢትዮጵያ እንደ አለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናው ሁሉ በኦሊምፒክም የሚኖራት ተሳትፎ ከአትሌቲክሱ የዘለለ እንደማይሆን የሚናገሩ የዘርፉ ሙያተኞች፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፈዴሬሽንም ሆነ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ይመክራሉ።
በአለም ሻምፒዮና ዳግም ያንሰራራው ማራቶን
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የአሸባሪው ህወሀት ወታደሮች በዘረፉት እና በአወደሙት ሆስፒታል ቁስለኛ ሆነው ታክመውበታል። በጋሸና ግንባር የአፄ ውሀ ምሽግ በጀግናው መከላከያ ሰራዊት በአማራ ልዩ ሀይል፣ ፋኖ እና ሚሊሻ ሲደመሰስ የሽብር ቡድኑ ለውጊያ ያዘጋጃቸው ታጣቂዎቹ ሙት እና ቁስለኛ ሆነዋል። በነበረው ውጊያ አርቢት በሚባለው አካባቢ የቆሰሉ የጁንታው ወታደሮች በየመንገዱ ወድቀው የተመለከቱ አርሶ አደሮች ቁስለኞችን በማንሳት ለመከላከያ ሰራዊቱ አስረክበዋል። የመከላከያ ሰራዊቱም ቁስለኞችን በመንከባከብ በነፋስ መውጫ ሆስፒታል አስፈላጊውን ህክምና ሲያደርግላቸው ቆይቷል። ቀድሞውንም የሽብር ቡድኑ የነፋስ መውጫ ሆስፒታልን ዘርፎና አውድሞት ስለነበር እነዚህ ወታደሮች ባወደሙት ሆስፒታል እንደገና ሊታከሙበት ችለዋል። ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ያነጋገራቸው የጁንታው ቁስለኞች በአርሶ አደሮቹ እና በነፋስ መውጫ ሆስፒታል የጤና ባለሙያዎች ለተደረገላቸው ክብካቤ አመስግነዋል። የሽብር ቡድኑ በየአውደ ውጊያው ያሰለፋቸው የትግራይ ወጣቶች እንደ ቅጠል ረግፈው ቀርተዋል የሚሉት ቁስለኞቹ፥ እኛ በአማራ ህዝብ ችርነት ለዚህ መብቃታችን አስደስቶናል ብለዋል። በህዝቡ ላይ የደረሰው ሰብአዊ እና ቁሳዊ ውድመት በእጅጉ እንዳሳዘናቸውም ነው የተናገሩት። በምንይችል አዘዘው አካባቢዎን ይጠብቁ ወደ ግንባር ይዝመቱ መከላከያን ይደግፉ ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡ ድረ ገፅ፦ ፌስቡክ፡ ዩትዩብ፦ ቴሌግራም፦ ትዊተር፦ በመወዳጀት ይከታተሉን። ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
ራሳቸው ባወደሙት ሆስፒታል የታከሙ ቁስለኛ የአሸባሪው ህወሀት ወታደሮች
ጥያቄው ያለው በመደመርና ባለመደመር ውስጥ አይደለም። የተደመረው ቂል ያልተደመረውብልህ መሆኑ ላይ አይደለም። ፓለቲካ ንግድ እንደመሆኑ ህብረት የሚመሰረተው ትርፍና ኪሳራን በማስላት ነው።ጥያቄው ያለው ከጠቅላይ ሚኒስተር አቢይና ቡድናቸው ዴሞክራሲያዊ ሀገር ሰርተው ሊሰጡን ይችላሉ ወይ የሚለው ላይ አይደለም። በታየው የለውጥ ጭላንጭል ውስጥ ገብቶ ዴሞክራስያዊ ፉክክር በማድረግ ዴሞክራሲያዊ ሀገርን መገንባት ይቻላል ወይ የሚለው ነው። ውሻ በቀደደው ጅብ ማለፉን ማስተዋል ላይ ነው።ጥያቄው ያለው ቁጥር መቁጠር እስኪያቅተው ድረስ ጠቅላይ ሚኒስተር አቢይ በሚሾሟቸው ግለሰቦች ዙሪያ እይደለም። ችግሩ በስልጣን ላይ ያለው ኢህአዴግ መሆኑን መዘንጋቱ ላይና ከ አመት በኋላ ኢህአዴግ እሯሯጭ ሳይሆን ተፎካካሪ ፓርቲ መሆኑን መርሳት ላይ ነው። መፍትሄው ያለው ጠቅላይ ሚኒስተር አቢይ ላይ የሰላ ግን መፍትሄ አልባ ትችት ማቅረቡ ላይ አይደለም። እየተቦካ ያለው የጎሳ ፓለቲካ ሊጥ ነው። ገበቴውም የጎሳ ፌደራሊዝም ነው። ሁኔታውን እንዲያመቻቹ ነው የጠየቅነው። ይህን የተፈጠረውን ጠባብ እድል ተጠቅሞ ዴሞክራሲያዊ ሽግግር የሚከሰትበትን መንገድ ማሳየትና መላ ማዘጋጀት ላይ ነው።መፍትሄው ያለው የጎሳ ፌደራሊዝም በዴሞክራሲያዊ ስርአት ለመተካት ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ማድረጉና ይህም እንዳይኮላሽ መስራቱ ላይ ነው።መፍትሄው ያለው በየቀኑ የፌስቡክ የተከታዮችን ቀልብ ለመግዛት ከእውነትና ከምናምንበት ውጭ የባህሪ ጥቃት ማፋፋም አይሆንም። መሪዎቹን በማብጠልጠል ወደ አክራሪው ጎራ ጠቅለው እንዳይገቡ በዘዴና በብልሀት መያዙ ላይ ነው።መፍትሄው ያለው እያከምን ያለነውንና የሚያሰቃየንን የጎሳ ፓለቲካን ቁስል በጎሳ ፓለቲካ መድሀኒት ለማከም የምናደርገውን ቅዠት አቁመን ዴሞክራሲያዊ ሂደቱ እንዳይኮላሽ መስራት ነው። በሽታን በበሽታ ማከም በሽታን ማስረፅ መሆኑን መገንዘቡ ላይ ነው። በሽታን መድሀኒት እንጂ በሽታ እንደማያድነው ማስተዋሉ ልይ ነው። ሁላችንም የያዝነው ማማሰያ የጎሳ ፓለቲካ የምናቁላላብት ድስትም የጎሳ ፌደራሊዝም ነው። ይህ ግብዝነትም ነው።መፍትሄው ያለው በኢትዮጵያዊነት ፀንተን በመቆምና ሀግራዊ ህብረት በመፍጠር አደጋውን መቀልበሱ ላይ ነው።ኢትዮጵያ እራሷን አልመሰረተችም። እራሷንም አታጠፋም። መስራቾቿም ይሁኑ አጥፊውቿ ልጆቿ ናቸው።ደጋግመን ብለናል። አሁንም እንላለን። እንደ ሀገር ብቻ ሳይሆን እንደ ህዝብ እንጠፋለንነፃነትን ደብቀን ነፃነትን እየፈለግን ነውኢትዮጵያዊነት አይረታም
ፓለቲካዊው እንቆቅልሽ ጥያቄውና መፍትሄው የት ላይ ነው ሀይሉ አባይ ተገኝ
ከአክሲዮን ሽያጭ የገቢ ግብር ላይ የዋጋ ግሽበት ኪሳራ ተቀናሽ እንዲሆንም ተፈቅዷል የንግድ ተቋማት በውጭ ገንዘብ ከፈፀሙት ግብይት ወይም የንግድ እንቅስቃሴ ጋር በተገናኘ የሚገጥማቸው የምንዛሪ ኪሳራ እንዲካካስ፣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ወሰነ። የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባለፈው ሳምንት ባካሄደው ስብሰባው፣ በስራ ላይ የሚገኘው የገቢ ግብር ደንብ ላይ ተስተውለዋል ተብለው የተለዩ የህግ ክፍተቶች ላይ በመወያያት የማሻሻያ ውሳኔዎችን አሳልፏል። ከለተዩት ክፍተቶች መካከል አንዱም የንግድ ተቋማት በውጭ አገር ገንዘብ ግብይት ከፈፀሙ በኋላ በሚፈጠር የውጭ ምንዛሪ ምጣኔ ልዩነት፣ የሚደርስባቸውን የምንዛሪ ኪሳራ ማካካስ የሚችሉበት የህግ አግባብ አለመኖሩና በዚህ የተነሳ በንግድ ተቋማቱ ላይ እያደረሰ ያለው ጉዳት ነው። ከባንኮች ውጪ ያሉ ሌሎች የንግድ ስራ ድርጅቶች ለካፒታል ንብረት ማፍሪያ የወሰዱትን ብድር በሚከፍሉበት፣ ወይም በውጭ ምንዛሪ ሌሎች የንግድ ስራ እንቅስቃሴዎችን በሚያከናውኑበት ጊዜ የውጭ ምንዛሪ ኪሳራ ያጋጥማቸዋል፤ ሲሉ አንድ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው የሪፖርተር ምንጭ አስረድተዋል። ምንጩ እንዳስረዱት በስራ ላይ የሚገኘው የገቢ ግብር ደንብ በውጭ ምንዛሪ ግብይት የደረሰ ኪሳራ እንዲካካስ የሚፈቅደው፣ በውጭ ምንዛሪ ግብይት ለተገኘ ጥቅም ብቻ ነው። ነገር ግን የንግድ ተቋማት ለካፒታል ንብረት ማፍሪያ የወሰዱትን ብድር በሚከፍሉበት ወቅት ወይም ሌላ ግብይት በውጭ ምንዛሪ ሲፈፅሙ፣ በምንዛሪ ለውጥ የሚደርስባቸው ኪሳራ ታሳቢ የሚደረግበት አሰራር አልነበረም ይላሉ። እነዚህ ድርጅቶች የውጭ ምንዛሪ የማይዙ በመሆኑ ከግብይቱ የሚያገኙት ጥቅም ስለሌለ፣ ለከፍተኛ ችግር ሲዳረጉ መቆየታቸውንም ይገልፃሉ። በመሆኑም ይህንን የህግ ክፍተት ለማስተካከል በገቢ ግብር ደንብ ላይ ማሻሻያ እንዲደረግ ተጠይቆ፣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ጉዳዩን ገምግሞ ማሻሻያው እንዲደረግ መወሰኑን ምንጩ ገልፀዋል። በተፈቀደው ማሻሻያ መሰረትም በውጭ ምንዛሪ ግብይት ላይ ያጋጠመ ኪሳራ በሁለት ተከፍሎ ማካካሻ እንዲደረግበት መወሰኑን አስረድተዋል። በዚህም መሰረት የውጭ ምንዛሪ ግብይቱ የተፈፀመው ከካፒታል ንብረት ግዥ ጋር በተያያዘ ከሆነ፣ የውጭ ምንዛሪ ኪሳራው የካፒታል ንብረቱ የተገዛበት ዋጋ ላይ ተደምሮ ለእርጅና ቅናሽ መሰረት እንዲሆን የሚፈቅድ ማሻሻያ በደንቡ ላይ እንዲደረግ ተፈቅዷል። በሌላ በኩል የውጭ ምንዛሪ ግብይቱ የተፈፀመው ከካፒታል ንብረት ግዥ ጋር ባልተያያዘ ከሆነ፣ የውጭ ምንዛሪ ኪሳራው በግብር ዘመኑ እንደ ወጪ እንዲያዝ የሚፈቅድ ማሻሻያ እንዲደረግ መወሰኑን ምንጩ አስረድተዋል። ሌላኛው በገቢ ግብር ደንቡ ላይ የታየው የህግ ክፍተትና ማሻሻያ እንዲደረግበት የተጠየቀው ጉዳይ፣ ከካፒታል ዋጋ እድገት ጥቅም ላይ ከሚጣለው ግብር ጋር የተያያዘ ነው። ለንግድ ስራ የሚያገለግልን ህንፃ ወይም አክሲዮን በሽያጭ በማስተላለፍ በሚገኝ የዋጋ እድገት ጥቅም ላይ የሚከፈለው የካፒታል ዋጋ እድገት ግብር አጣጣልን በተመለከተ የሚደነግገው የገቢ ግብር ደንብ፣ ህንፃን በመሸጥ በሚገኝ የዋጋ የካፒታል እድገት ላይ የዋጋ ግሽበት ማስተካከያ ወይም ቅናሽ ተደርጎ በሚገኘው ዋጋ ላይ ግብር እንዲከፈል ሲፈቅድ፣ ከአክሲዮን ሽያጭ በሚገኝ የዋጋ እድገት ጥቅም ላይ የዋጋ ግሽበት ማስተካከያን አለመፍቀዱ ግብር ከፋዮች በእኩል እንዳይስተናገዱ ማድረጉን ምንጩ አስረድተዋል። በመሆኑም ይህንን ችግር ለማስተካከል ማሻሻያ ድንጋጌ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቦ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልፀዋል። አክሲዮን የሚሸጡ ግብር ከፋዮች የአክሲዮን ሰነዱ ሲወጣ በተቆረጠለት ዋጋ፣ ወይም አክሲዮን ሰነዱ ላይ በተፃፈው ዋጋ እና በተሸጠበት ዋጋ መካከል ያለው ልዩነት ጥቅም እንደሆነ ተቆጥሮ ግብር እንዲከፍሉ ሲጠየቁ መቆየታቸውን ገልፀዋል። ይህ የግብር አጣጣል በብር የመግዛት አቅም መዳከም በዋጋ ግሽበት ምክንያት ግብር ከፋዩ ወይም ባለ አክሲዮኑ ሊያጣ የሚችለውን ገቢ ያላገነዛበ እንደሆነ የሚያስረዱት ምንጩ፣ በግብር አዋጁ መሰረት ግብር የሚጣለው ግብር ከፋዩ በትክክል አግኝቷል በሚባለው ጥቅም ላይ በመሆኑ በዚሁ አግባብ እንዲስተካከል መደረጉን ገልፀዋል። ከአክሲዮን ሽያጭ የሚገኝ ጥቅም የዋጋ ግሽበት ማስተካከያ እንዲፈቀድ በሚያስችል አኳኋን በገቢ ግብር ደንቡ ላይ ያለው አንቀፅ እንዲሻሻል መወሰኑን የገለፁት ምንጩ፣ በዚህ ማሻሻያ መሰረትም ከአክሲዮን ሽያጭ በትክክል ተገኝቷል ሊባል የሚችለው ጥቅም በአክሲዮኑ የወቅቱ ዋጋና በተሸጠበት ገንዘብ መካከል ያለው ልዩነት እንደሚሆን አስረድተዋል።
የንግድ ተቋማት የሚገጥማቸው የውጭ ምንዛሪ ኪሳራ እንዲካካስ ተወሰነ
በቅርቡ ለምስረታ የበቃው ጎህ የቤቶች ባንክ ቦርድ አመራር የቀድሞውን የአቢሲኒያ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ ሙሉጌታ አስማረን በፕሬዚዳንትነት መረጠ። በባንክ ኢንዱስትሪው ከሀያ ሰባት አመታት በላይ ልምድ ያካበቱት አቶ ሙሉጌታ፣ የጎህ ባንክ ፕሬዚዳንት ሆነው እንዲሰሩ የቀረበላቸውን ጥያቄ በመቀበላቸው፣ የእጩ ፕሬዚዳንቱን ሹመት ያፀድቅለት ዘንድ የባንኩ ዳይሬክተሮች ቦርድ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ጥያቄ አቅርቧል። ባለፈው ወር በይፋ መመስረቱ ይፋ የተደረገው ጎህ ባንክ፣ በጥቂት ወራት ውስጥ ስራ እንደሚጀምር ያስታወቀ ሲሆን፣ ብሄራዊ ባንክ ሹመታቸውን ካፀደቀላቸው አቶ ሙሉጌታ የጎህ ባንክ መስራች ፕሬዚዳንት ይሆናሉ። አቶ ሙሉጌታ አስማረ ለሀያ ሰባት አመታት በባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ ያገለገሉ ሲሆን፣ በተለይም በአቢሲኒያ ባንክ ከመምርያ ሀላፊነት ጀምሮ እስከ ምክትል ፕሬዚዳንትነት ብሎም በፕሬዚዳንትነት ከዘጠኝ አመታት በላይ ሰርተዋል። አቢሲኒያ ባንክን ከመቀላቀላቸው ቀደም ብሎ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተለያዩ የሀላፊነት ቦታዎች ላይ ሰርተዋል። ኢንዱስትሪው ከ አመታት በላይ የሚሆነውን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቆዩት አቶ ሙሉጌታ በባንኩ ቆይታቸው እስከ መምርያ ሀላፊነት ደረጃ ማገልገላቸው ይጠቀሳል። አቢሲኒያ ባንክን ከለቀቁ በኋላ በተለይ ለአራት አመት ተኩል ለሚሆን ጊዜ የባንኩ ፕሬዚዳንት በመሆን የሰሩ ሲሆን፣ አቢሲኒያ ባንክን በፈቃዳቸው ሲለቁም እሳቸውን ተክተው እንዲሰሩ የቀድሞው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንትና ለተወሰኑ ወራቶች የብሄራዊ ባንክ ምክትል ገዥ የነበሩት አቶ በቃሉ ዘለቀ እንዲተኳቸው ማድረጋቸውም ይነገርላቸዋል። ጎህ ቤቶች ባንክ እስካሁን በኢንዱስትሪው ውስጥ ካሉና በምስረታ ላይ ከሚገኙት ወደ ሀያ ከሚጠጉ ባንኮች በተለየ በቤቶችና ተያያዥ የባንክ አገልግሎቶች ላይ በማተኮር የሚሰራ ባንክ እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን፣ መደበኛ የባንክ አገልግሎቶችንም አካቶ እንደሚሰራ መገለፁ አይዘነጋም። የአገሪቱን የመኖሪያ ቤት ችግር ከግምት ውስጥ በማስገባት በዘርፉ የባንክ አገልግሎት በመስጠት ያለውን ችግር ለማቃለል የበኩሉን ለማበርከት ጭምር የተቋቋመው ጎህ ቤቶች ባንክ ወደ ስራ ለመግባት የመጨረሻ ምእራፍ ላይ ደርሷል። ባንኩ ባለፈው ወር የምስረታ ጉባኤውን ባካሄደበት ወቅት እንዳስታወቀው በአምስት መቶ ስላሳ ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታልና በአንድ ነጥብ ሁለት ቢሊዮን የተፈረመ ካፒታል ምስረታ አካሂዶ ባንኩን በቦርድ ዳይሬክተርነት የሚመሩ አባላትንም መርጧል። በዚሁ መሰረት ከብሄራዊ ባንክ ስራ ለመጀመር የሚያስችለውን የመጨረሻ ፈቃድ ካገኘ በኋላ በጥቂት ወራት ውስጥ ወደ ስራ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል። ጎህ ቤቶች ባንክ የተመሰረተው ከስምንት ሺህ በላይ የሚሆኑ ባለአክሲዮን በመያዝ ነው።
የቀድሞው የአቢሲኒያ ባንክ ፕሬዚዳንት የጎህ ባንክ እጩ ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡ
ተከሳሹ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ በማእከላዊ አስደብድበውኛል ብሏል ከአርበኞች ግንቦት ሰባት ድርጅት ጋር ግንኙነት እንዳለውና ከድርጅቱ መሪ ብርሀኑ ነጋ ዶክተር ጋር በመገናኘት የተሰጠውን ተልእኮ ለመፈፀም ሲንቀሳቀስ ተደርሶበታል ተብሎ ክስ የተመሰረተበት ተጠርጣሪ፣ ሶስት የመከላከያ ምስክሮቹን አሰማ። ምስክሮቹ ከመሰማታቸው በፊት በሰጠው የተከሳሽነት ምስክርነት ቃሉ እንደተናገረው፣ በፌዴራል ወንጀል ምርመራ ማእከል ማእከላዊ ታስሮ በነበረበት ወቅት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ በቦታው ተገኝተው እንዳስደበደቡትና እንደደበደቡት ለፍርድ ቤት የተከሳሽነት ቃሉን ሰጥቷል። የወንጀል ህግ አንቀፅ ስላሳ ሁለት አንድ ሀ እና ለ ፣ ስላሳ ስምንት እና የፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር ስድስት መቶ ሀምሳ ሁለት ሁለት ሺህ አንድ አንቀፅ ሰባት ሁለት ን በመተላለፍ ማለትም፣ ማንኛውም ሰው በሽብርተኛ ድርጅት ውስጥ በአመራርነት ወይም በውሳኔ ሰጪነት መሳተፍ የሚለውን ተላልፏል ተብሎ ክስ የተመሰረተበት አቶ ሰይፉ አለሙ ነው። በእነ አቶ ጌታሁን በየነ የክስ መዝገብ ተካቶ ታሀሳስ ሀያ ስድስት ቀን ሁለት ሺህ ዘጠኝ አመተ ምህረት ተሻሽሎ በቀረበው ክስ ሶስተኛ ተከሳሽ አቶ ሰይፉ አለሙ ሲሆን፣ አቃቤ ህግ ያቀረበበትን ክስ በሰውና በሰነድ ስላስረዳበት እንዲከላከል የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ኛ ወንጀል ችሎት ብይን ከሰጠ በኋላ መከላከያ ምስክሮቹን አቅርቦ አሰምቷል። ተከሳሹ የመከላከያ ምስክሮቹን ከማሰማቱ በፊት በሰጠው የተከሳሽነት የምስክርነት ቃል እንዳስረዳው፣ በማእከላዊ በተለያዩ ሰዎች ከፍተኛ ድብደባ ደርሶበታል። ማንነቱ እየተጠቀሰ መደብደቡንና ከአስደብዳቢዎቹና ከደብዳቢዎቹ መካከል፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባዩ አንዱ እንደነበሩ ለፍርድ ቤቱ ተናግሯል። በወቅቱ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበት እንደነበርና ህክምና በመከልከሉም አብረውት ታስረው የነበሩ የረሀብ አድማ አድርገው እንደነበር ገልጿል። በሰውነቱ ላይ የደረሰበትን የድብደባ ጠባሳ ለማሳየት ልብሱን ለማውለቅ ሲሞክር ፍርድ ቤቱ ከልክሎታል። ተከሳሹ በማእከላዊ የደረሰበትን የምርመራ ሂደት አስረድቶ እንደጨረሰ፣ በመከላከያ ምስክርነት የቆጠራቸው ሶስት ምስክሮች በማእከላዊ በደረሰበት ድብደባ ሰውነቱ ቆስሎ እንደነበርና የህክምና እርዳታ እንዲያገኝ የረሀብ አድማ አድርገው እንደነበር መስክረዋል። ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር ከተገቢው ህግ ጋር መርምሮ ብይን ለመስጠት ለሚያዝያ ቀን ሁለት ሺህ አስር አመተ ምህረት ቀጠሮ ሰጥቷል። ከአቶ ሰይፉ ጋር በሽብር ተግባር ወንጀል ተጠርጥረው ክስ የተመሰረተባቸው ግለሰቦች ነበሩ። ዘጠኙ የመከላከያ ምስክር እንደሌላቸው በመግለፃቸው፣ ጥፋተኛ ተብለው የእስራት ቅጣት ተጥሎባቸዋል። አቶ ለገሰ ሀይለ መስቀል፣ አቶ ተክሌ ተሾመ፣ አቶ ሰይፉ አለሙ፣ አቶ ኪሩቤል ግርማና አቶ አስፋው አባተ የመከላከያ ምስክር እናሰማለን በማለታቸው ክርክራቸው ቀጥሏል። አቶ ኪሩቤል ግርማና አቶ አስፋው አባተ አቃቤ ህግ ክሱን በማቋረጡ ከእስር ተፈትተዋል። ፍርድ ካረፈባቸውም ሁለት ፍርደኞች መንግስት ባደረገው ይቅርታ ተፈተዋል። ተከሳሾቹ የአርበኞች ግንቦት ሰባት አባል በመሆን ኤርትራ ሄደው በመሰልጠን፣ አስመራ ብርሀኑ ነጋን ዶክተር በማግኘትና ተልእኮ በመቀበል ሲንቀሳቀሱ የነበሩ መሆኑን በክሱ ተገልጿል። አቶ ሰይፉ የሎጂስቲክስና የፋይናንስ ሀላፊ ሆኖ ሲንቀሳቀስ እንደነበርና ከሶስት አባላት ጋር በመሆን፣ በኡጋንዳና በኬንያ በማድረግ ሞያሌ ገብተው፣ በሀገረ ማርያምና በአርባ ምንጭ በተዘጋጀ ካምፕ መቀላቀላቸውን ክሱ ያብራራል።
ከአርበኞች ግንቦት ሰባት ጋር ግንኙነት አለው የተባለው ተከሳሽ የመከላከያ ምስክሮቹን አሰማ
ኢሳት ዲሲመጋቢት በሞያሌ የተፈፀመውን ግድያ ተከትሎ ወደ ኬንያ የሚሰደዱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር መጨመሩን አለም አቀፉ ቀይ መስቀል አስታወቀ።መንግስት ስደተኞቹ እየተመለሱ መሆናቸውን ቢገልፅም አለም አቀፉ ቀይ መስቀል ትላንት እንዳስታወቀው በየቀኑ ሰዎች እየተሰደዱ ኬንያ በመግባት ላይ ይገኛሉ።ችግሩ በተፈጠረ በመጀመሪያዎቹ ሶስት ቀናት ሺ ኢትዮጵያውያን መሰደዳቸውን ያስታወሰው አለም አቀፉ ቀይ መስቀል በመጪዎቹ ቀናት ቁጥሩ ወደ ሺ እንደሚያሻቅብም አስታውቋል።የቀንድና የጋማ ከብቶችም በተመሳሳይ መሰደዳቸው ተመልክቷል።የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን የኬንያ ቀይ መስቀልና የስደተኞች ጉዳይ ፅህፈት ቤት ባደረጉት ምዝገባ በመጋቢት ወር ብቻ ከሞያሌ ግድያ ጋር በተያያዘ ድንበር አቋርጠው ኬንያ የገቡ ኢትዮጵያውያን ቁጥር እስካለፈው ሳምንት ሺ ደርሷል።አሁንም በየቀኑ ቤተሰቦች ማለትም በትንሹ ያህል ሰዎች ድንበር አቋርጠው ኬንያ በመግባት ላይ መሆናቸውን በሰብአዊ ቀውስ ሪፖርቱ ላይ ተመልክቷል።በየቀኑ ያህል ሰዎች መሰደዳቸው በተገለፀበት በአሁኑ ወቅት በሚቀጥሉት ሶስት ቀናት የስደተኞቹ ቁጥር ወደ ሺ እንደሚያሻቅብም አለምአቀፉ ቀይ መስቀል አስታውቋል።አንዳንድ ስደተኞች የቤት እንስሳትን ጭምር ይዘው መሰደዳቸውም ይፋ ሆኗል።በዚህም ግመሎችሺ ላሞችና በሬዎች በግና ፍየሎች እንዲሁም አህዮችም በተመሳሳይ ድንበር ተሻግረው ኬንያ መግባታቸው ታውቋል።የአለምአቀፉን ቀይ መስቀል እንዳስታውቀው ባለፉት ቀናት ኬንያ ከገቡት ኢትዮጵያውያን ወስጥ ነፍሰጡሮች ሲሆኑ ዎቹ ደግሞ አራስ እናቶች መሆናቸው ተመልክቷል።እድሜያቸው ከ አመት በታች የሆኑት ህፃናት ቁጥር ደግሞ ሺ መሆኑ ታውቋል። ህፃናት ደግሞ ወላጅም ሆነ አሳዳጊ ሳይኖራቸው መሰደዳቸውን ከሪፖርቱ መረዳት ተችሏል። አዛውንቶችም ከተሰደዱት ውስጥ መሆናቸው ታውቋል።የሞያሌውን ግድያ ተከትሎ በተፈጠረው ቀውስ ለደህንነታቸው ሰግተው የተሰደዱ ኢትዮጵያውያንን ለመደገፍ አለምአቀፉ ቀይ መስቀል ለሶስት ወራት የማቋቋሚያ ድጋፍ ጥሪ አቅርቧል።እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር እስከ ሰኔ ድረስ የሚያስፈልጉትን ወጪ ዝርዝሮችም ይፋ አድርጓል።በየቀኑ ቤተሰቦች ማለትም ያህል ሰዎች የሚሰደዱበት የሞያሌው ቀውስ የ ሰዎች መገደልን ተከትሎ የመጣ መሆኑን አለምአቀፉ ቀይ መስቀል አስታውቋል።በመከላከያ ሰራዊት ከተገደሉት ሰዎች በተጨማሪ ሰዎች መቁሰላቸውን እንዲሁም ደግሞ መሰወራቸውን አስታውቋል።
ወደ ኬንያ የሚሰደዱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር መጨመሩ ተገለፀ
አዲስ አበባ፣ መስከረም ሀያ ዘጠኝ፣ ሁለት ሺህ ኤፍ ቢ ሲ የሁለት ሺህ ሀያ የኖቤል የሰላም ሽልማትን የአለም ምግብ ፕሮግራም አሸነፈ። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አንዱ አካል የሆነው የአለም የምግብ ፕሮግራም የዘንድሮውን የሰላም ሽልማት የወሰደው ረሀብን ለመዋጋት ባደረገው ጥረት መሆኑን ኮሚቴው አስታውቋል። በዚህም የአለም የምግብ ፕሮግራም ከኮሚቴው አንድ ነጥብ አንድ ሚሊየን ዶላር ተበርክቶለታል። ፕሮግራሙ ይህንን የኖቤል ሽልማት ሲያሸንፍ አንድ መቶ አንድኛ ነው ተብሏል። የፕሮግራሙ ቃል አቀባይ የሽልማቱን ይፋ መሆን ተከትሎ ደስታቸውን ገልፀዋል። የአለም ምግብ ፕሮግራም በሰማኒያ ስምንት ሀገራት ውስጥ የሚገኙ ዘጠና ሰባት ሚሊየን ሰዎችን እንደሚደግፍ ቢቢሲ ዘግቧል። የባለፈውን አመት የኖቤል የሰላም ሽልማት ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ ማሸነፋቸው የሚታወስ ነው።
የሁለት ሺህ ሀያ የኖቤል የሰላም ሽልማትን የአለም የምግብ ፕሮግራም አሸነፈ
ራሱን የቤኒሻንጉል ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ ቤህነን ብሎ የሚጠራው ቡድን አባላትና አመራሮች መመለሳቸው በክልሉ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ እየተደረገ ያለው ጥረት ውጤት መሆኑን የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን አስታወቁ።ርእሰ መስተዳድሩ እንደገለፁት ክልሉ ያለው የተረጋጋ ፖለቲካዊ ሁኔታ ፣ እየተመዘገበ የሚገኘው የልማትና የመልካም አስተዳደር ስኬት የቡድኑ አባላትና አመራሮች ወደ ክልሉ እንዲመለሱ ምክንያት ሆኗል።ሀገሪቱ ሰላምን መሰረት አድርጋ መስራቷ ተከታታይና ፈጣን እድገት በማስመዝገብ ድህነትን በአጭር ጊዜ ለማስወገድ የሚደረገውን ጥረት ውጤታማ ማድረጉን አስረድተዋል። የክልሉ ህዝቦችም የልማትና የዴሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታው ቀጣይነት ሊኖረው የሚችለው ሰላም ሲረጋገጥ እንደሆነ በመገንዘብ ፀረ ሰላም ሀይሎችን በመታገል ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ ነው ያሉት ።ህዝቡ ለሰላሙ መጠበቅ ያለው ቁርጠኝነት የቡድኑ አባላትና አመራሮች ወደ ክልላቸው በመመለስ በሰላማዊ መንገድ እንዲንቀሳቀሱ የሚያስገድድ መሆኑን አቶ አሻድሊ አስገንዝበዋል ።የውጭና የውስጥ ፀረ ሰላም ሀይሎች ኤርትራን የመሳሰሉ አገራትን ማእከል በማድረግ ሰላምና ልማትን ለማደናቀፍ ጥረት እንደሚያደርጉ ጠቅሰዋል።የቡድኑ አባላትና አመራሮች ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ በተደረገው ጥረት ውስጥ ድርሻ ለነበራቸው አካላት ርእሰ መስተዳድሩ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ለተመለሱት የቡድኑ አባላት በህገ መንግስቱ ዙሪያ ስልጠና እንደሚሰጣቸውና በተለያዩ የስራ መስኮች በመሰማራት የራሳቸው መተዳደሪያ እንዲኖራቸው ክልሉ እገዛ ያደርጋልም ብለዋል።እራሱን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ነፃነት ንቅናቄ ብሎ የሚጠራው ቡድን ዘጠና አምስት አባላት የአመፅ ድርጊታቸውን ትተው ከመንግስት ጋር በመስማማት በቅርቡ ወደ ሀገራቸው መግባታቸውንና ከመካከላቸውም ቱ በካርቱም ይኖሩ የነበሩ የድርጅቱ አመራር አካላት እንደሆኑ ይታወቃል ኢዜአ ።
የ ቤህነን ቡድን መመለስ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ የተደረገው ጥረት ውጤት ነው አቶ አሻድሊ ሀሰን