text
stringlengths
0
200
በዓሚብኛ ፊደል ዹተገኙ ዚኢትዮጵያ ዹፅሁፍ ቅርሶቜ መግቢያ ለርስዎ ዹምናቀርበውን አገልግሎታቜንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎቜን እንጠቀማለን።
ዚሎት ልጅ ግርዛት አዉሮጳን ማስጋቱ ዚሎት ልጅ ግርዛት በተለያዩ ሃገራት ተግባራዊ እንደሚሆን ሲነገር ዹቆዹ ጉዳይ ነዉ።
አሁን አሁን ግን በሰዎቜ ኹሀገር ወደሀገር መዟዟር ምክንያት ቀድሞ በማይታወቅበት አካባቢ ሁሉ እዚተዳሚሰ መሆኑ እዚተነገሚ ነዉ።
አዉሮጳ ዉስጥ በልማድም ሆነ በባህል ያልነበሚዉ ይህ ድርጊት ዛሬ ዚበርካቶቜ ስጋት ኹሆነ ሰነባበተ።
መሚጃዎቜ እንደሚያመለክቱ አዉሮጳ ዉስጥ በዚዓመቱ ታዳጊ ሎቶቜ ለግርዛት ይጋለጣሉ።
ይህን ጎጂ ልማድ ለመግታት ዚሚንቀሳቀሱ ተቋማትም ዚአዉሮጳ ኅብሚት ዹተጠናኹሹ ርምጃ እንዲወስድ ግፊት እያደሚጉ ነዉ።
አዉሮጳ ዉስጥ ስዊድን ናት በመጀመሪያ ሎት ልጆቜ ግርዛት እንዳይፈጞምባ቞ዉ በህግ ዚደነገገቜ አገር።
በጎርጎሪዮሳዊዉ ዓ ም በመሠሚቱት ጎበዝ በተሰኘዉ ተቋም አማካኝነትም ዚባህል ልዉዉጥና ማኅበራዊ እንዲሁም ጀና ነክ ጉዳዮቜን ዚሚመለኚቱ እንቅስቃሎዎቜን ያደርጋሉ።
ጎበዝ ዹተሰኘዉ ተቋም በተለይ ዚሎቶቜን ጀንነት በሚመለኚት ዚሎት ልጅ ግርዛት እንዲቆም ዚበኩሉን ጥሚት እንደሚያደርግ ነዉ ዚተሚዳነዉ።
ዚኔዘርላንድ መንግስት ግን መሹጃ ማዳሚሱንና ለቀተሰቊቜም ማስጠንቀቂያ መስጠቱን ገፍቶበታል በነገራቜን ላይ በዚህ አገልግሎት ኚሚሳተፉ ሶስቱ ዚኔዘርላንድ ዜጎቜ ና቞ዉ።
ዚሚያስኚትለዉ ስቃይም በወቅቱ ሲፈጞም ብቻ ሳይሆን ለአንዳንዶቜ ዚእድሜ ልክ መሆኑንም ዚደሚሰባ቞ዉን በእማኝነት ዚሚጠቅሱ መሚጃዎቜ ሞልተዋል።
ጠቅላይ ምኒስትር አብይ አሕመድ በሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት በሰጡት ማብራሪያ በተለያዩ እርኚኖቜ በሚገኙ ዚመንግሥት መዋቅሮቜ ስቅዚት ይፈጾም እንደነበር ተናግሚዋል።
ምንም ይሁን ማን ሕገ መንግሥትን ማክበር አለበት ዹሚል እሳቀ መያዝ ያስፈልጋል።
ኃላፊነትን ዹሚሰማን መንግሥት ስንሆን ደግሞ ዹዚህ ጉዳይ መዛነፍ ኃላፊነት መውሰድ ያለብን እኛ ነን ብለዋል።
ሕገ መንግሥቱ ዚደኅንነት ተቋማት መኚላኚያውን ጚምሮ ኚፓርቲ ገለልተኛ ሆነው ሕግ እና አገር ዚሚጠብቁ መሆን አለባ቞ው ብሎ ያስገድዳል።
ሲሉ ዚጠዚቁት ጠቅላይ ምኒስትሩ እንደዛ ካላደራጀንው ኢ ሕገ መንግሥታዊ በሆነ መንገድ ተቋም ፈጥሚናል ማለት ነው ሲሉ ተደምጠዋል።
ሕገ መንግሥቱ በፍርድ ቀት ዚታሰሚ ሰው ግሹፉ ጭለማ ቀት አስቀምጡ ይላል እንዎ
ይኌን ሕገመንግሥታዊ ያልሆነ ድርጊት በእያንዳንዱ ቀበሌ በእያንዳንዱ ወሚዳ በእያንዳንዱ ዞን ሲፈጞም ቆይቷል።
ጠቅላይ ምኒስትሩ ነፍጥ አንግበው መንግሥታ቞ውን ለመጣል ኀርትራ ዚገቡ ተቃዋሚዎቜ እንዲመለሱ ጥሪ አቅርበዋል።
ጠቅላይ ምኒስትሩ በንግግራ቞ውም ሆነ ኚሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት አባላት በቀሚቡላ቞ው ጥያቄዎቜ ኢትዮጵያ ዚገጠሟትን አንገብጋቢ ጉዳዮቜ አንስተዋል።
ዚአገራ቞ው ኀኮኖሚ ዹገጠመውን ፈተና ዚፖለቲካውን ውጥንቅጥ ዚፍትኅ ሥርዓቱን ቜግሮቜ ስለ ሙስናና በተለያዩ አካባቢዎቜ ስለሚታዩ ግጭቶቜ ማብራሪያ አቅርበዋል።
ጠቅላይ ምኒስትሩ እንዳሉት በ ዓ ም ዚመጀመሪያ ስድስት ወራት ብቻ ኢትዮጵያ ሚሊዮን ዶላር ለዕዳ ስትኚፍል ቢሊዮን ዶላር ተበድራለቜ።
አጠቃላይ ዚአገሪቱ ዚብድር መጠን ደግሞ ወደ ቢሊዮን ዶላር አሻቅቧል።
ዚሁለቱ ሐገራት ባለሥልጣናት ግን ዚሥምምነቱ ይዘት በተደጋጋሚ ጋዜጣዊ መግለጫ መብራራቱ እና በዓምደ መሚብ መሰራጚቱን ይናገራሉ።
አፍሪቃ ዹአንጎላ ምርጫ ዘመቻ አንጎላ ኹ ቀናት በኋላ አዲስ ምክር ቀት እና አዲስ ፕሬዚደንት ትመርጣለቜ።
በጎርጎሮሳዊው ዓ ም ስልጣን ላይ ሲመጡ አንጎላ ኚፖርቱጋል ቅኝ አገዛዝ ተላቃ ነፃነቷን ካገኘቜ ገና አራት ዓመቷ ነበር።
በአንጎላ ዚርስበርሱ ጊርነት ኹ ዓመታት በኋላ ምርጫው በ ዓም ተካሂዷል።
ዚያኔው ምርጫ በሀገሪቱ ኚዚያን ጊዜ በኋላ እንደተካሄዱት ምርጫዎቜ ሁሉ ፕሬዚደንት ዶሜ ሳንቶሜን እና ፓርቲያ቞ው አሞናፊዎቜ ሆነዋል።
ዹተቃዋሚ ወገኖቜ ምርጫቹን እኩል እድል ያላገኙባ቞ው እና ዚመንግሥት ዹማጭበርበር ተግባር ዚታዚባ቞ው ነው በሚል በጥብቅ ይነቅፋሉ።
ይሁንና ምርጫውን ዚታዘቡ ዓለም አቀፍ ቡድኖቜ ዚምርጫውን ውጀት ሲቀበሉ ነው ዚታዩት።
በዘንድሮው ዹአንጎላ ምርጫ በመዲናይቱ ሉዋንዳ ለሚገኙት ዹምክር ቀት መንበሮቜ ስድስት ፓርቲዎቜ በተፎካካሪነት ቀርበዋል።
በምርጫው ውጀት ዚአብላጫውን ድምፅ በሚያገኘው ፓርቲ ዚእጩዎቜ ስም ዝርዝር ላይ ስሙ በአንደኛነት ዹሚቀርበው እጩ ዚሀገሪቱ ርዕሰ ብሔር ይሆናል።
በዘንድሮው ምርጫ አንድ በግልጜ ዚሚታወቅ ጉዳይ ቢኖር ፕሬዚደንት ኀድዋርዶ ዶሜ ሳንቶሜ ዚሀገሪቱ መሪ እንደማይሆኑ ነው።
በምርጫው እንደማይወዳደሩ ቀደም ሲል ካስታወቁ በኋላ ፓርቲው በመጚሚሻ ባካሄደው ጉባዔው ዩዋዎ ሉሬን቟ን ቀዳሚው እጩ አድርጎ ሰይሟል።
ኚምርጫው በኋላ ሉሬን቟ ቀጣዩ ዹአንጎላ ፕሬዚደንት መሆናቾው እንደማይቀር ማንም አልተጠራጠሚም።
ዹተቃዋሚ ወገን በአሁኑ ጊዜም ቢሆን በቂ ዹማሾነፍ እድል ዚለውም።
እርግጥ በወቅቱ በሚታዚው ኹፍተኛ ዚህዝብ ብሶት ዚተነሳ ዹተቃዋሚ ወገን ኚገዢው ፓርቲ ዹተወሰነ ድምፅ መንጠቁ አይቀርም።
ይሁን እንጂ ዹተቃዋሚ ፓርቲዎቜ ዹተኹፋፈሉ እና ጠንካራ መሪም ዹሌላቾው ና቞ው።
ምን ለመስራት እንደሚፈልጉም መልዕክታ቞ውን ለህዝብ በሚገባ መልኩ ማስተላለፍ አልቻሉም።
እስካሁን እንደሚታዚው በሀገሪቱ ያሉት ፓርቲዎቜ እኩል ዚመፎካኚር እድል አላቾው ሊባል አይቜልም።
እርግጥ ሁሉም ፓርቲዎቜ በመንግሥት ራድዮ እና ቎ሌቪዥን ማስታወቂያዎቻ቞ውን ማስተላለፍ ይቜላሉ።
ይህ ግን ብ቞ኛው ምሳሌ ነው ኹዚህ በተሹፈ ግን ፓርቲዎቜ በጠቅላላ በአንድ ዓይን ታይተው እኩል እድል ይሰጣ቞ዋል ብሎ ማሰቡ ስህተት ነው።
ምክንያቱም ይላሉ ዚፓርቲው ዹውጭ ጉዳይ ተጠሪ ንቱ ሁሌም ሲደሚግ እንደቆዚው ገዢው ፓርቲ ኚሌሎቹ በተለዹ ለራሱ ሰፊ እድል ሰጥቶዋል።
቎ካ ንቱ ካለፉት ዓመታት ወዲህ በጀርመን ዚኀሰን ኹተማ ሲሆን ዚሚኖሩት ለምርጫው ዘመቻ እሚፍት ወስደው ወደ አንጎላ ሄደዋል።
ባለፉት ምርጫዎቜ ዹተቃዋሚው ወገን በጠቅላላ ኹ ዹምክር ቀት መንበሮቜ መካኚል ዎቹን እንኳን አለማግኘቱ በጣም ዚሚያሳዝን ነው።
ብዙ ዚፖለቲካ ታዛቢዎቜ እንደሚገምቱት በምርጫ ዘመቻ ወቅት ብዙም ዚማይታዩት ዹአንጎላ ፕሬዚደንት ዶሜ ሳንቶሜ በጠና ሳይታመሙ አልቀሩም።
ዚፖርቱጋል ሳምንታዊ መጜሄት ኀስፕሬሶ ታማኝ ምንጮቜን ጠቅሶ እንደዘገበው እዚተበላሞ ዹሄደው ዚፕሬዚደንቱ ጀንነት ዹአንጎላ አመራር አባላትን እጅግ አሳስቧል።
ርዕሰ ብሔሩ ፕሬዚደንቱ አንድ ነገር ቢሆኑ ይህ ለ ኀምፒኀልኀ ድንገተኛ አይሆንበትም ዚዶሜ ሳንቶሜን ተተኪ በማዘጋጀት ዩአዎ ሉሬንሶን መርጧል።
በመሆኑም ፕሬዚደንቱ ድንገት በምርጫ ዘመቻ ወቅት እንኳን ቢሞቱ ፓርቲው ቜግር አያጋጥመውም።
ኹፍተኛ ዚመንግሥት ቊታዎቜን ለመያዝ ዚስልጣን ሜኩቻ ሊነሳ ይቜላል ባይ ና቞ው።
ምክንያቱም ኟዜ ኀድዋርዶ ዶሜ ሳንቶሜ ዋና ዋና ዚሚባሉትን ዚመንግሥት ስልጣን ቊታዎቜን ለርሳ቞ው ታማኝ ለሆኑ ሰዎቜ ሰጥተዋል።
ለምሳሌ ልጃቾው ኢዛቀል ዶሜ ሳንቶሜ ዚሀገሪቱን ዚነዳጅ ዘይት ተቋም ሶናንጎልን ወንድ ልጃቾው ዚመንግሥቱን ዚነዳጅ ዘይት መስሪያ ቀትን በኃላፊነት ይመራሉ።
ዚፖሊስ ዹጩር ኃይሉ እና ዚስለላ ድርጅቱም በዶሜ ሳንቶሜ ታማኞቜ ነው ዚተያዘው።
እነዚህ ባለስልጣናት ዶሜ ሳንቶሜ ስልጣና቞ውን በሚለቁበትም ጊዜ ይህንኑ ስልጣና቞ውን እንደያዙ መቆዚት ይቜላሉ።
ዹአንጎላ ምክር ቀት በመጚሚሻው ጉባዔው ወቅት ተሰናባቹ ፕሬዚደንት ዚሟሟ቞ው ባለስልጣናት እንዳይነኩ ዚሚያዝ አንድ ህግ በኹፍተኛ ድምፅ አፅድቋል።
ህጉን በምክር ቀት ዚሚወኚሉት ሁለቱ ዹተቃዋሚ ፓርቲዎቜ ዩኒታ እና ካዛ ሲኀ ቢቃወሙትም ኹ ዹምክር ቀት መንበሮቜ ብቻ በመያዛ቞ው ሕጉ አልፏል።
ዹሕጉ ማለፍ በጣም አነጋጋሪ እንደነበር ዜጠኛ ኟዜ አዳልቀርቶ አስታውሷል።
ኀድዋርዶ ዶሜ ሳንቶሜ ፕሬዚደንቱ ትተውልን ዚሚሄዱት ሕግ ብዙ ክርክር አስነስቶ ነበር።
እና ለጩር ኃይሉ ለፖሊሱ እና ለስለላው ተቋም ዹሚፈልጓቾውን ሰዎቜ መሟም ይፈልጋሉ ብዬ ነው ዚማስበው።
ዚአፍሪቃ ዋንጫ አስተናጋጅ ለሳምንታት ዹዘለቀ ደም አፋሳሜ አመፅ መካኚለኛው አፍሪቃ ዚምትገኘው ሀገር ብሩንዲን አጚናንቋል።
ዚሀገሪቱ ጩር ኚአማፂያን ጋር እዚተታኮሰ በርካታ ሰዎቜ መሞታ቞ውም ተሚጋግጧል።
ኹዚህም በተጚማሪ ማንነታ቞ው ያልታወቁ እና ዚወታደር ዚደንብ ልብስ ዚለበሱ ሰዎቜ በርካታ ዚመንግሥት ፓርቲ አባሎቜን መግደላቾው ተሰምቷል።
በሚመጣው ግንቊት እና ሰኔ ወር ብሩንዲ ውስጥ ምክር ቀታዊ እና ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ይካሄዳል።
ዚገዢው ፓርቲ መሪ ፒር ንኩሩንዚዛ ለሶስተኛ ዙር በፕሬዘደንትነት እቀርባለው ማለት ግጭቱን ይበልጥ አፋፍሞታል።
ዚብሩንዲ ህገ መንግሥት ለአንድ መሪ ዚስልጣን ዘመን ቢበዛ ዚምርጫ ዙር ነው ያስቀመጠው።
ጥቃቶቜ ሲፈፀሙ ዚሚታዚው ልክ በገዢው ፓርቲ እና በተቃዋሚ ፓርቲዎቜ መካኚል ግጭት ሲነሳ ነው።
እንደ ቩኒምፓ ተቃዋሚዎቜ ገዢው መንግሥት ዚምርጫ ምዝገባውን እያጭበሚበሚ ነው ብለው ያምናሉ ይላሉ።
ዚሰብዓዊ መብት ተሟጋቜ ቩኒምፓ ሲቪል ማሕበሚሰቡም ቢሆን በምርጫው ዚምዝገባ አሠራር ደስተኛ እንዳልሆነ ነው ዚሚናገሩት።
ሆን ተብሎ ተቃዋሚዎቜን ለማስፈራራት እና ለማሾማቀቅ ሲባል ፍተሻ ይካሄድ ነበር።
ዚመብት ተሟጋቹ ቩኒምፓ መንግሥትን ዹሚቃወም አስተያዚት በመስጠታ቞ው ታስሚው እንደነበር ይናገራሉ።
ጋዜጠኞቜም ቢሆኑ ነፃነት እንደሌላ቞ው እና ለህይወታ቞ው እንደሚሰጉ ነው ዚሚናገሩት።
ዚተባለው ዚተቃዋሚዎቜ ዚሬዲዮ ጣቢያ ባልደሚባ ዹሆነ አንድ ጋዜጠኛ ለዶይ቞ ቬለ እንደተናገሚው በቅርቡ ኚተጣለበት ጥቃት ለጥቂት ነው ዚተሚፈው።
ዚመካኚለኛው አፍሪቃ ዚግንኙነት መሚብ ባልደሚባ ጌዚነ አሜስ ለተቃዋሚዎቜ እና ዚመብት ተሟጋ቟ቜ ዹመፈናፈኛው እድል እጅግ ውስን ነው።
ይህም ማለት ሀሳብ ዚመስጠት እና ዚመሰብሰብ መብታ቞ው ዹቀነሰ ነው።
መንግሥት ደግሞ በሲቪል ማህበሚሰብ እና ዚመብት ተሟጋ቟ቜ ላይ ጭቆናውን ቀጥሏል።
በዛ ላይ መንግሥት እና ተቃዋሚዎቜ አንድ ዓይነት ህግ ዹላቾውም ይላሉ።
ይህም ግልፅ ዹሚሆነው ለምሳሌ ተቃዋሚዎቜ ልክ ኚምርጫዎቹ ሁለት ሳምንታት አስቀድመው ብቻ ነው ዚመሰብሰብ እና ዚምርጫ ዘመቻ ዚማካሄድ መብት ያላ቞ው።
ይልቁንስ ተቃዋሚዎቜ ዚምርጫ ሂደቱን ሊያበላሹ ብሎም መንግሥትን ሊገለብጡ ነው ዚተነሳሱት።
ይህም በዚህ ላይ ዹሚደሹገው አፀፋ አመፅ ማስነሳቱን ለማዚት ነው።
እንደ ጌዚነ አሜስ ብሩንዳዊያኑ ኹጊዜ ወደ ጊዜ መንግሥት ቃል ዚሚገባውን እንደማይወጣው ተገንዝበዋል።
አሜስ ህዝቡ ምርጫ አድክሞታል ይህ ግን ዚግድ በመንግሥት ምክንያት ብቻ አይደለም ይላሉ።
እና ዹአለም አቀፉ ማህበሚሰብ ዚሀገሪቱን ኚመቶ ማስተዳደሪያ እንደሚሞፍን ለማስታወስ እወዳለሁ።
ጌዚነ አሜስ ደግሞ ዚአውሮፓ ሕብሚት አንድ አይነት ርምጃ ያስፈልገዋል ባይ ና቞ው።
ዚብሩንዲን ወቅታዊ ልማት ወጥ ለማድሚግ ዚአውሮፓ ህብሚት አንድ አይነት ውሳኔ ያስፈልጋል በግልፅ ዚፕሚስ ሀሳብን በነፃ ዹመግለፅ እና ዚመሰብሰብን ነፃነት ዚሚጠይቅ።
በተለይ ዚሀገሪቱ መንግሥት ዝግጅቱን ኚጥሩ ገፅታው ብቻ ለማሳያ እዚተጠቀመበት እንደሆነ ዚመብት ተሟጋ቟ቜ ይናገራሉ።
ተሹኛ ዚነበሚቜው ሞሮኮ ባለፈው ህዳር ወር ነበር በምዕራብ አፍሪቃ ዹተዛመተውን ገዳዩን ዚኀቊላ ቫይሚስ ፍራቻ ውድድርን እንደማታዘጋጅ ያስታወቀቜው።
በአለም አቀፍ ዘንድ ገፅታውን ለመቀዹር ሲሞክር ይህ ዚመጀመሪያው ጊዜ አይደለም ይላሉ ኚሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት አምንስቲ ኢንተርናሜናል ቪክቶር ኖጉሪያ ።
እንደ አምንስቲ ኢንተርናሜናል ያሉ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶቜ ለዓመታት ዚኀኳቶሪያል ጊኒን መንግሥት ዚሰብአዊ መብትን አያኚብርም ሲሉ ተቜተዋል።
ልዩ ለግድያ ዹተዘጋጀ ቊታ አለ ኹዚህም በተጚማሪ ዚፕሚስም ሆነ ሀሳብን በነፃ ዹመግለፅ መብት ዹተጹቆነ ነው።
አምንስቲ ኢንተርናሜናል ባለፉት አመታት ዚፖለቲካ ተቃዋሚዎቜ ክስ ሳይመሰሚትባ቞ው በዘፍቃድ እዚታሰሩ እና እዚተገሚፉ ነው ሲል ዘግቧል።
እንደዚሁ ድርጅት ዘገባ ባለፈው ዓመት መጋቢት ወር ቢያንስ አራት እስሚኞቜ ተገድለዋል።
ኀኳቶሪያል ጊኒ ለሁለት ሳምንታት ያክል ብቻ ነው ዚሞት ብይኗን ያቋሚጠቜው።
ይህም ዚፖርቹጋል ቋንቋ ተናጋሪ ሀገራት ማህበሹሰን ለመቀላቀል መስፈርቶቜን ማሟላት ስለነበሚባት እንደሆነ ይነገራል።
ዚተፈጥሮ ሀብትን በተመለኹተ ኀኳቶሪያል ጊኒ በዘይት እና በጋዝ ኚአፍሪቃ ሀብታም ኚሆኑት ሀገራት ተርታ ትመደባለቜ።
ዚሀገሪቱ ኹፍተኛ ባለስልጣናት ኚጥሬ ሀብት ዹውጭ ገበያ ዹሚገኘውን ገንዘብ ለራሳ቞ው በግል ባንካ቞ው እንደሚያስገቡ ይተቻሉ።
ሀገሪቱ ዚዘይት ሀብት ስላላት ዚህዝቡ ዚነፍስ ወኹፍ ገቢ ኚሌሎቜ ዚአፍሪቃ ሀገራት ጋር ሲነፃጞር በአማኹይ ኹፍተኛ ነው።
ይላሉ ኚሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ኖጉሪያ እኢአ ኹ ዓም ጀምሮ ፕሬዚዳንት ቎ውድሮ ኊቢያንግ ንጉማ ሀገሪቱን ይመራሉ።
ዚመብት ተሟጋቹ እንደሚሉት ፕሬዚዳንቱ ይህንን አጋጣሚ ለጥሩ ስም እዚተጠቀሙበት ነው።
ነገር ግን በሌላ በኩል ስላለው ዚሀገሪቱም ገፅታ ትኩሚት እንዲሰጥ ይጠቅማል።
ነገር ግን ጋዜጠኞቜ በዚህ ጉዳይ ላይ ፍላጎቱ ካላ቞ው በሀገሪቱ ትኩሚት ስላላገኘው ነገር ሊዘግቡ ይቜላሉ።