id
stringlengths
1
7
text
stringlengths
1
13k
3124500
ሶስተኛ ሊዘነጋ ዚማይገባው፣ እውን ሊሆን ዚሚቜል አንድ ነገር አለ። ብዙዎቜ አቶ መለስና አቶ ኢሳያስ ውስጥ ውስጡን ግንኙነት እንዳላ቞ው ይናገራሉ። ምናልባት ዛሬ ዹደፈሹሰው ዚሕወሃት/ኢሕአዎግ እና ዚሻዕቢያ ግንኙነት ነገ በቀላሉ ሊገነባ ይቜላል። ዚታሪክ መጜሃፍት እንደሚያስነብቡን ሻዕቢያ ኹዚህ በፊት ኢሕአፓን ይደግፍ ነበር። ኢሕአፓን ኚድቶ ነው ወደ ሕወሃት ዹሄደው ይባላል። ነገም ኊነግ፣ ግንቊት ሰባት ወዘተሹፈን ክዶ ኚሕወሃት ጋር ቢተቃቀፍ እነ ግንቊት ሰባት ዚት ሊገቡ ነው?
3124501
ዶ/ር ጌታ቞ው በጋሻው በግልጜ እንዳስቀመጡት በኢትዮጵያ ሰላምና ዲሞክራሲ እንዲኖር፣ ዚኢትዮጵያን አንድነት ዹሚቀበል ማንኛውም አይነት ድርጅት፣ እራሱን ኚሻዕቢያ ጥገኝነት በይፋ ማውጣት ይኖርበታል። ኚሻዕቢያ ጋር ያለንን ግንኙነት በጥሰን፣ በሻዕቢያ እዚተጎዳና እዚታሚዳ ካለው ዚኀርትራ ሕዝብ ጋር ግንኙነታ቞ን ማጠናኚሩ ዹበሰለና ዚሚያዋጣ ፖለቲካ ነው። ”በአዲስ አበባም በአስመራም ያሉ ገዢዎቜ ዚሕዝብን መብት እንዲያኚብሩ ሁሉቱንም እንታገላ቞ው” እላለሁ።
3124502
ኹኩነግ ጋር እያደሚገ ስላለው ውይይት ዶ/ር ብርሃኑ በሰጡት ትንተና እና ኚአንባቢያ በቀሚቡልኝ አስተያዚቶቜ ዙሪያ ያተኮሚ፣ ዚመጚሚሻ ክፍል ሃተታዬን á‹­á‹€ እመለሳለሁ። በዚያን ወቅትም ዚግንቊት ሰባት ንቅናቄ ቢወስዳ቞ው ይጠቅማሉ ዹምላቾውን ዚመፍትሄ ሃሳቊቜንም á‹­á‹€ እቀርባለሁ። አላማዬ ግንቊት ሰባትን እና ዚግንቊት ሰባት አመራር አባላትን ለማጥቃት ወይንም ለማዳኚም ሳይሆን፣ ዚያዙት መንገድ ውጀት እንዳላመጣና ዚትም እንዳማይደርሱ ለማሳዚት፣ በዚህም ምክንያት ቆም ብለው እንዲያስቡና መንገዳ቞ውን እንዲመርመሩ ለመምኹር ነው። እሰኚዚያው ለሁላቜንም ቾር ይግጠመን።
3124503
[1] ዚኢትዮጵያና ዚኀርትራ ዝምድናና ዚምሁራኑ ሚና እንዎት ነበር? አሁንስ ምን መሆን አለበት? - ፕ/ር ተስፋጜዮን መድሃኔ
3124504
[2] ዚኢትዮጵያ አንድነት ጥያቄ - ኹኩነግና ሌሎቜ ዹዘር ድርጅቶቜ ጋር መነጋገርና መተባበር ለምን ያስፈልጋል? - ጌታ቞ው በጋሻው
3124505
ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ኚኢሳት ጋር ያደሚጉት ቃለ-ምልልስ (ቪዲዮ)
3124506
ኩነግና ኢትዮጵያዊነት – ምላሜ ለዶ/ር ብርሃኑ ክፍል 3-ግርማ ካሣ
3124507
ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ በኢሳት ላደሚጉት ቃለ-ምልልስ መልስ
3124508
ጥቆማ ለጠ/ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ
3124509
ምሕሚት ዘገዬ ክቡር ጠቅላይ ሚንስትር፣ ሰላምታዚን ላስቀድም። ሰላም! ...
3124510
ማስታዋሻ ቁጥር 9፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ በኢትዮጵያ “ዚተቀደሱት ሰላም ፈጣሪዎቜ ናቾው”
3124511
ዚሕዝብ ተሳትፎ ዚሌለበት ውሳኔፀ መፍትሔ አያመጣም (ሾንጎ)
3124512
“ያለውን ዹለገሰ ንፉግ አይባልም”
3124513
ዹመደመር ቋንቋ (ሶምራን)
3124514
በማናቾውም ጉዳይ ላይ ያለዎትን ሃሳብ፣ አስተያዚት፣ ትቜት፣ ግጥም፣ ልብወለድ፣ ... በማይክሮሶፍት ወርድ ፕሮግራም በዩኒኮድ ፎንት ጜፈው ኚራስዎ ኢ-ሜይል ሳጥን ጜሑፎትን አያይዘው በኢ-ሜይል አድራሻቜን This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. ቢልኩልን ለሥራቜን ቅልጥፍና ይሚዱናል።
3124515
አዲስ አበባ ልገባ ነው!
3124516
አርበኞቜ ግንቊት 7 እና ቀጣይ ተግባሩ
3124517
ዚሚቡዕ ግጥም ፫ኛ ዓመት፣ ቁ. ፎ
3124518
ህብር (ላስ ቬጋስ)
3124519
"ደማቜን አንድ ነው!" ሻምበል በላይነህና ሃኒሻ ሰለሞን 

3124520
© ፳፻ - ፳፻፲ ዓ.ም. ኢትዮጵያ ዛሬ፣ መብቱ በሕግ ዹተጠበቀ ነው። Copyright © 2007 - 2018 Ethiopia Zare. All Rights Reserved.
3124521
3124522
Ethiopia Zare - ”ዹኔ አጋርነት በኢትዮጵያ ውስጥ ለዲሞክራሲ ሥርዓት ኚሚታገሉ ኃይሎቜ ጋር ነው” አና ጐሜዝ
3124523
”ዹኔ አጋርነት በኢትዮጵያ ውስጥ ለዲሞክራሲ ሥርዓት ኚሚታገሉ ኃይሎቜ ጋር ነው” አና ጐሜዝ
3124524
ዚአንባብያን ድምፅ: 4 / 5
3124525
'ለተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎቜ ጥሪ ዹማቀርበው ነገርፀ ህዝቡ በምርጫ እንዳይሳተፍ ዹሚኹለክል መልዕክት ማስተላለፍ አይገባ቞ውም'
3124526
በአውሮፓ ፓርላማ ዚሶሻሊስት ፓርቲ አባልና በኢትዮጵያ ግንቊት 7 ቀን 1997 ዓ.ም. ተካኺዶ በነበሹው ምርጫ ዚአውሮፓ ምርጫ ታዛቢ ልዑካን ሊቀመንበር ዚነበሩት አና ጐሜዝ በቅርቡ ኚዩሮ ጋዜጣ ጋር በኢትዮጵያ ስላለው ዚዲሞክራሲ ሁኔታ፣ ስለኊነግ (ስለዚኊሮሞ ነፃነት ግንባር)፣ በቀጠናው ስላለው መሚጋጋትና ”ዚቅርብ ወዳጃ቞ው ናቾው” ተብለው ስለሚጠቀሱት በዶ/ር ብርሀኑ ነጋ ስለተቋቋመው ዚግንቊት 7 ንቅናቄ ዙሪያ ያደሚጉትን ቃለ-ምልልስ ለኢትዮጵያውያን አንባብያን በሚመቜ መልኩ በአማርኛ ቋንቋ ተርጉመን አቅርበነዋል።
3124527
እንደሚታወቀው ዚግንቊት 7 1997 ዓ.ም. ምርጫ ውዝግብ ተኚትሎ፣ 193 ዹሚጠጉ ሰዎቜ ሞት ዚተነሳ ዚአውሮፓ ፓርላማ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ማዕቀብ እንዲደሚግ ጥሪ አቅርቩ ነበሚ። ፓርላማው ለምን ይህን ዚማዕቀብ ጥሪ ቜላ አለው?
3124528
እንደማስበው ዚአውሮፓ ኮሚሜን ጥሪውን ቜላ አላለምፀ በወቅቱ ለኢትዮጵያ ዚዕርዳታ አሰጣጥ ሁኔታ ተቀይሮ ነበር። ነገር ግን ጊዜ በሄደ ቁጥር ነገሮቜ እንደወትሮ ነው ዚተመለሱትፀ እንደውም ዚአውሮፓ ሕብሚት ለኢትዮጵያ መንግሥት ዹሚደሹገውን ድጋፍ ዚቀጠለበትና ዚጚመሚበት ሁኔታ ነው ዚሚታዚው። እኛ እንደምናውቀው ዚኢትዮጵያ መንግሥት ዚህዝቡን ፍላጐት ዚጣሰና ሙሉ በሙሉ በገዥው ፓርቲ ቁጥጥር ስር ዹወደቀ መንግሥት ነው። በአውሮፓ ኮሚሜን ወይም መንግሥታት ውስጥ ኢትዮጵያን በተመለኹተ ዚአስመሳይነት ሥራ እዚተሠራ ይገኛል። በአፍሪካ ዚዲሞክራሲና ዚሰብዓዊ መብቶቜን ለማራመድ ዚአውሮፓ ኮሚሜን መሠሚታዊ እሎቶቜና ዓላማዎቜ ወጥነት ይጐድላ቞ዋል። ይህ ድርጊት በኢትዮጵያ ህዝብም ሆነ በአፍሪካ በአጠቃላይ ዚአውሮፓን ተዓማኒነት ጥያቄ ውስጥ ዚሚኚት ነው። እኔንም በጣም ዚሚያሳዝነኝ ድርጊት ነው።
3124529
እንደተጠቀሱት ዚአውሮፓ አስመሳይነት (Hypocrisy) በሁሉም ዚዓለማቜን ክፍል ዚሚታይ ነው። ለምሳሌ ለምዕራብ ሀገሮቜ ቅርበት ያላ቞ው እንደ ሳዑዲ ዐሚቢያ በመሳሰሉ ሀገራት ዚሰብዓዊ መብቶቜ ጥሰት ይስተዋላል። በሌላ በኩል ምዕራባውያን በዝምባብዌ ፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቀ ላይ ያነጣጠሚ ዘመቻ እያካሄዱ ይገኛሉ። በአንፃሩ ምንም ምርጫ ያላደሚጉ ወይም ዚምርጫ ውጀትን ያጭበሚበሩና ዹሰው ልጆቜ ሕይወት ስለጠፋበት ሀገራት እምብዛም ትኩሚት ሲሰጡ አይስተዋሉም ይህ አስመሳይነት አልበዛም?
3124530
ዚሰብዓዊ መብት ጥሰትን በተመለኹተ ዚፕሬዝዳንት ቡሜ፣ ዚአውሮፓ መንግሥታትና ተቋማት ትልቅ ሜንፈት ነው። ምክንያቱም ሁኔታውን ስንመለኚተው በዓለም አቀፍ ሕግና ዚሰብዓዊ መብቶቜን ለማስኚበር ኹሚደሹጉ እንቅስቃሎዎቜ ጋር ይቃሚናል። ስለዚህም ነው በጥያቄህ ውስጥ እንደጠቀስኚው አይነት ምሳሌዎቜና ኢትዮጵያ ውስጥ እዚታዘብነው ያለው ሁኔታ ተመሳሳይ ነው። ለምሳሌ ባለፈው ጊዜ ዚቡድን ስምንት ስብሰባ ጃፓን በተካሄደበት ወቅት በዝምባብዌ መንግሥት ላይ ማዕቀብ ለማድሚግ ጥሪ ቀርቩ ነበር። ማዕቀቡ ዚሙጋቀን ፈላጭ ቆራጭ መንግሥት ለማስወገድ ስለሚሚዳ ተገቢ ነው። ነገር ግን በዚህ ጉባዔ ላይ ልክ እንደ ዹተኹበሹ አፍሪካዊ መሪ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ አንዱ ተጋባዥ መሪ ነበሩ። መለስ ዜናዊ ዚሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሊሆኑ ይቜላሉፀ ነገር ግን በምርጫው ወቅት እንዳዚሁት በኢትዮጵያዊያን ዘንድ ተዓማኒነት ዚላ቞ውም። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዓለም ታላቅ መሪዎቜ ፊት ሊሾለሙ ወይም ሊቀርቡ አይገባ቞ውም። ምክንያቱም ፈላጭ ቆራጭ መሪ ኹመሆናቾውም ባሻገር ዹሰው ሀገር ማለትም ሶማሊያን ዚወሚሩ ና቞ው። ስለዚህ በዓለማቜን ላይ በግልፅ ዚሚታይ ተቃርኖ ወይም ወጥነት ዹሌለው አሠራር እዚታዚ ነው።
3124531
በአጠቃላይ ሲታይ በኢትዮጵያ ባለፉት ሊስት ዓመታት ዚዲሞክራሲያዊ ሜግግር ሂደቱ እዚተሻሻለ ነው ወይስ እዚባሰበት ነው ይላሉ?
3124532
በዓለም ላይ ያለውን ዚዲሞክራሲያዊ ሜግግር ሥርዓት ስናይ ዚተለያዩ ሁኔታዎቜ አሉ። በኢትዮጵያ ግን በእርግጠኝነት እዚተሻሻለ አይደለም ማለት ይቻላል። በአንድ በኩል ዚኢትዮጵያ ህዝብ ለዲሞክራሲና ለለውጥ ያለው ፍላጐት ኹፍተኛ ነው። እ.ኀ.አ. በ2005 ዓ.ም. በተካሄደው ምርጫ (ምርጫ 97) በሠላማዊ ሁኔታ ነው ህዝቡ ዚተሳተፈው። ነገር ግን ያ ሁሉ ተስፋ በመለስ ዜናዊ ሥርዓት መና ሆኖ ቀርቷል። ስለዚህ በኢትዮጵያ ዚዲሞክራሲ ሂደት አልተሻሻለም ማለት ይቻላል። አሁን ዹምናዹው ሁኔታ ዚቡሜ አስተዳደር ማብቂያ ዚተቃሚበበትና ኚአዲሱ ዚአሜሪካን ፕሬዝዳንት ኊባማ አዲስ ዘመን ዚምናይበት ነው። አፍሪካዊ መሠሚት ላልናቾው በፕሬዝዳንት ኊባማ ዘመን ዲሞክራሲና ዚሰብዓዊ መብት አያያዝና ጥበቃ በተመለኹተ ለውጥ እንደምናይ ትልቅ ተስፋ አደርጋለሁ።
3124533
ኚቡሜ አስተዳደር በፊት ዚነበሩት ባለሥልጣናት፣ ዚሰብዓዊ መብትና ዲሞክራሲን በተመለኹተ መሚጋጋት ማምጣት እንደሚቜሉ ተናግሹው ነበር። ታዛቢዎቜና ዚሰብዓዊ መብት ተሟጋቜ ድርጅቶቜ፣ ዚቡሜ አስተዳደር በተፃራሪ ሲሠራ እንደነበር ይተቻሉ። በኊባማ አስተዳደር ምን ያህል ለውጥ ይመጣል ብለው ይጠብቃሉ?
3124534
እንደማስበው ማናቾውም ዕጩዎቜ በምርጫ ቢያሞንፉም በዓለም ዙሪያ ኹፍተኛ ቀውስ ያስኚተለው ዚቡሜ አስተዳደር ያኚትማል። በኔ በእምነት ዚፕሬዝዳንት ኊባማን ስብዕናና ዚአፍሪካዊና እስያዊ ወይም ኢንዶኔዥያ ተቋዳሜ መሆናቾው ዩናይትድ ስ቎ትስ አመራር በኩል አፋጣኝ ለውጥ ማምጣት እንዳለበት እንዲገነዘቡ ይሚዳ቞ዋል። ይህ ደግሞ ዚዲሞክራሲና ሰብዓዊ መብቶቜ መሠሚታዊ እሎቶቜና ብሎም ፍትህ በዓለማቜን ይበልጥ እንዲሠፍን ይሚዳል። በዚህ ዓለም ዲሞክራሲያዊ ያልሆነ አሠራር ማዚት አንሻም፣ ኚመሚጋጋት ዚተሻለ ብዬ ዹማምነው ዲሞክራሲና ሰብዓዊ መብቶቜ ሲኚበሩ ነው።
3124535
በብዙ ፎሚሞቜ ተቃዋሚ ዚኢትዮጵያ ፓርቲዎቜ፣ በገዥው ፓርቲ ላይ ጫና ለማሳደር አንድ መሆን ወይም መተባበር እንዳለባ቞ው ሲናገሩ ይደመጣሉ። እውነታው ግን በተቃራኒ ነው። ኅብሚት፣ ኊፌዲን እና ሌሎቜም ተቃዋሚ ፓርቲዎቜ በፓርላማ ይገኛሉ። በሌላ በኩል ፓርላማ ያልገቡ ዚቅንጅት አመራር አባላት አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ መሥርተዋል። ዚኊሮሞ ነፃነት ግንባር (ኩነግ) በምርጫ አልተሳተፉም። አሁንም ቢሆን ዚቀድሞ ቅንጅትና አንድነት ፓርቲ አመራር አባላት በተለዚዩ ፓርቲዎቜ በመቧደን እዚተኚፋፈሉ ይገኛሉ። ለምሣሌ አንዳኛው በኢንጂንዚር ኃይሉ ሻውል አመራር ስር ሲሆን፣ ሌላኛው በአቶ አዹለ ጫሚሶ ስር ይገኛል። በሌላ በኩል እንደ ኩጋዮን ብሔራዊ ነፃ አውጪ ግንባር ያሉ አንዳንድ ተቃዋሚ ፓርቲዎቜ፣ ኚኀርትራ መንግሥት ጋር በመሥራት ላይ ይገኛሉ። እርስዎ እነዚህን ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎቜ አንድ ለማድሚግ ወይም ለማዋሃድ ምን እያደሚጉ ይገኛሉ?
3124536
ኢትዮጵያውያን ዚዲሞክራሲ ሥርዓት ለመተግበር ዚሚያደርጉትን እንቅስቃሎ ኚልቀ እደግፋለሁ። ነገር ግን እኔ ዹውጭ ዜጋ ነኝ። ማንም ሰው ኢትዮጵያውያን ዚሚፈልጉትን ለውጥ ኹውጭ ሆኖ ማምጣት አይቜልም ይህ ለኢትዮጵያውያን ዹተተወ ሥራ ነውፀ ኚኢትዮጵያ ውጭ ያሉ ሰዎቜ ዚአውሮፓ መንግሥታት በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ጫና እንዲያሳድሩ ግፊት ሊያደርጉ ይቜላሉፀ ያም ሆነ ይህ ዹተወሰነ ኃላፊነት ነው። ዋናው ኃላፊነት ዹወደቀው በኢትዮጵያውያን ላይ ነው። ዹኔ አጋርነት በኢትዮጵያ ውስጥ ለዲሞክራሲ ሥርዓት ኚሚታገሉ ኃይሎቜ ጋር ነው። አሁን ያለው በማንም ያልተወኚለና ዹተናቀ ሥርዓት ህዝቡ ላይ እያደሚገ ያለው ጭቆና ዋናው ምክንያትፀ ዚኢትዮጵያ ህዝብ በተለያዚ ምክንያት በመኹፋፈሉ ነውፀ ይህ አሳዛኝ ሁኔታ ነው በጣም አሳዛኝ። ኢትዮጵያውያን በርዕዮተ ዓለም፣ በፖለቲካና በብሔሚሰብ ያላ቞ውን ልዩነት አቻቜለው፣ በአንድነት ለዲሞክራሲ ሥርዓት ኚተባበሩ ዚመለስን አስተዳደር በመጣል፣ በምትኩ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መገንባት ይቜላሉ። እንደ ኹዚህ ቀደም ዚአማራን ዚበላይነትና አብዛኛው ዚኢትዮጵያን ህዝብ ዚሚይዙት ዚኊሮሞን ህዝብ ሥጋት እዚነጣጠልን ዚምንሰብክ ኹሆነ ዚመለስ ፈላጭ ቆራጭ ሥርዓት እንዲቀጥል ዚሚያደርግ ጥሩ አማራጭ ነው። ስለዚህ ነው እኔ ኢትዮጵያውያን በዲሞክራሲ፣ መልካም አስተዳደር፣ ፍትህና ለሰብዓዊ መብቶቜ ክብርና ኢኮኖሚ ዙሪያ ባሉ አጀንዳዎቜ፣ በአንድነት እንዲቆሙ ጥሪ ዚማቀርበው። ስለሆነም እኔ በምንም ዓይነት ኢትዮጵያዊያን በራሳ቞ው ዚሚሠሩትን ሥራ መተካት አልቜልም።
3124537
ኚግንቊት 7 ቀን 1997 ዓ.ም. ምርጫ በፊት ኢሪን ለተባለ ዚተባበሩት መንግሥታት ዹዜና ምንጭ በሰጡት ቃለምልልስ/ ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎቜ ዚደጋፊዎቻ቞ውን ስሜትና ምኞት በማርገብ፣ ዚምርጫውን ውጀት እንደ እውነት እንደሚቀበሉ ተስፋ አድርገው ነበር። ተቃዋሚ ፓርቲዎቜና ገዥው ፓርቲ እርስዎ በወቅቱ ተስፋ አድርገው ዹነበሹውን ተግባራዊ ያደሚጉ ይመስልዎታል?
3124538
ደኅና! ኚምርጫው በፊትና በኋላም እንደታዚው ዚኢትዮጵያ ህዝብ በምርጫው በመሳተፍ ለዲሞክራሲ ያለውን ፍላጐትና ዝግጁነት አሳይቷል። በዚያ ወቅት አንዳንድ ተቃዋሚ ፓርቲዎቜ ገዥው ፓርቲ ዚምርጫውን ሂደት ሊያዛባው እንደሚቜል ያላ቞ውን ሥጋት ኚመጀመሪያው ጀምሮ ሲነግሩኝ ነበር። በተወሰነ ደሹጃ በወቅቱ ልክ ነበሩ። ዚአዲስ አበባ ምርጫ ውጀት እንደታወቀ ገዥው ፓርቲ ዚምርጫውን ውጀት በመላ ሀገሪቱ ማዛባት ጀመሚ። መንግሥት ዚምርጫውን ውጀት ማጭበርበር ተኚትሎ ለዲሞክራሲ ዹነበሹው ተስፋ መና ሆነ። እኔ እንደማስበው ሥርዓቱ ዚህዝቡን ፍላጐት መቀልበሱ ለራሱ መጥፎ ነውፀ ዚአዲስ አበባ ምርጫ ውጀት ዹመላ ሀገሪቱ ምርጫ ውጀት ነፀብራቅ ነው። እርግጥ አንዳንድ ቊታ ዚውጀት ልዩነት ቢኖርም ማለቮ ነው። ስለዚህ ነው አሁንም ቢሆን ለተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎቜ ጥሪ ዹማቀርበው ነገርፀ ህዝቡ በምርጫ እንዳይሳተፍ ዹሚኹለክል መልዕክት ማስተላለፍ አይገባ቞ውም፣ ህዝቡ ለመምሚጥ መጥቷል። ስለዚህ መለስ ህዝቡ ለዲሞክራሲ ዝግጁ አይደለም ብሎ መናገር አይቜልም። ዚኢትዮጵያ ህዝብ ለዲሞክራሲ ያለውን ዝግጁነት በምርጫ ወቅት በብዛት በመገኘትና በመምሚጥ አስመስክሯል።
3124539
አንዳንድ ታዛቢዎቜ በኢትዮጵያ ዹግል ፕሬስ አደጋ ውስጥ እንዳለ ይናገራሉ። ለዚህም ዹሚቀርበው ምክንያት ዚሕትመት ዋጋ መናር ነው። በዚህም ምክንያት በገዥው ፓርቲ አባላት ዚፋይናንስ ድጋፍ ዹማይደሹግላቾው ዚፕሬስ ውጀቶቜ እዚተዘጉ ይገኛሉ። ኹዚህም በተጚማሪ ዹ2005 ምርጫን (ምርጫ 97ን) ተኚትሎ ብዙ ጋዜጠኞቜ ላይ እንግልት ደርሷል። በቅርቡም አዲስ ዚፕሬስ ሕግ በፓርላማ ፀድቋል። ይህ ሕግ መንግሥት ዚሕትመት ውጀቶቜን ኚስርጭት በፊት እንዲያግድ ይፈቅድለታል። ታዛቢዎቜ ይህ እርምጃ መንግሥት ፕሬስን ለማፈን አዲስ ዓይነት እንቅስቃሎ እያደሚገ እንደሚገኝ ይናገራሉ። ዚአውሮፓ ሕብሚት በኢትዮጵያ ዹግሉን ፕሬስ ለመደገፍ ዹተለዹ ዕቅድ ካለው ቢነግሩን?
3124540
በኢትዮጵያ ብዙም ዹግል ፕሬስ ውጀቶቜን አናይም። ለዚህም ምክንያቱ መንግሥት ዚሚያሳድሚው ጫና ነው። ይህን በተለያዚ ደሹጃ ኚፋፍዬ ልነግርህ እቜላለሁ። ኚምርጫው በኋላ መንግሥት ባጠቃላይ ዹግል ፕሬስ አልፈቀደም። እኔ እስኚ ማውቀው ድሚስ መንግሥት ፕሬስን ለማፈን ውስብስብ አማራጮቜን ይወስድ ነበር። ህዝቡ በኢንተርኔት መሹጃ እንዳያገኝ በተለያዩ መንግሥታት ይደገፍ ነበርፀ እንደተነገሚኝ መንግሥት ዚኮሚኒኬሜን ግንኙነቶቜን ለማቆም ዚቻይናውያን ድጋፍ ተደርጐለታል። ስለዚህ ጥያቄው ለዲሞክራሲ ካለው ጠቀሜታ አንፃር ወሳኝ ነው። በኔ እምነት ዲሞክራሲን በኢትዮጵያ ለማስፋፋት በአውሮፓ ዹሚደሹጉ ዚገንዘብ ድጋፎቜ ዹግልና ነፃ ፕሬስን ማካተት ይገባዋል። ይህ ድጋፍ ሊደሹግላቾው ዚሚገቡ በሀገር ውስጥና ውጪ ላሉ ዹግል ፕሬስና ኀሌክትሮኒክስ ሚዲያዎቜ ነው።
3124541
ዚሬዲዮ ሥርጭት ምናልባት ውጀታማ ነው ብዬ አምናለሁ። ምክንያቱም ዚራዲዮ ሥርጭት አድማሱ ሠፊ ነው። ዚራዲዮ ፕሮግራም ዚትም ሆነህ በአማርኛም ሆነ በሌላ ቋንቋ ልታስተላልፍ ትቜላለህ። ይህ ዚገዥው ፓርቲ መሹጃን ለማፈን ወይም ለማዛባት ዚሚያደርገውን ጥሚት ያኚሜፈዋል። ይህ ለአውሮፓ ሕብሚትም ሆነ በአውሮፓ ፓርላማ በኩል ቅድሚያ ሊሰጠው ዚሚገባ ጉዳይ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ ዲሞክራሲን ለመገንባት ኹተፈለገ ነፃ ዹሆነ ዹመሹጃ ፍሰትን መደገፍ ይገባል።
3124542
ዚኢትዮ-ኀርትራ ዚድንበር ፍጥጫ እንደቀጠለ ይገኛል፣ መፍትሔው ምንድነው ብለው ያስባሉ?
3124543
ለብዙ ኢትዮጵያውያን ሕመም ቢሆንም ኢትዮጵያ በባድመ ላይ ዹተሰጠውን ብይን መቀበል ይገባታል። ኢትዮጵያ ኚኀርትራ ጋር ያላትን ግንኙነት በተመለኹተ ሌሎቜ አማራጮቜ ማዚት ይገባል። ይህ በኢትዮጵያና በኀርትራ መንግሥታት ዹሚወሰን ጉዳይ ነው። እኔ እንደማውቀው ዚኀርትራ መንግሥት ጹቋኝ ሥርዓት እንደሆነ ነው። ዚኀርትራ መንግሥት ዚጊርነት አባዜን እዚተኚተለ ይገኛል። በቀጠናው በብዙ ቜግሮቜ እጁን እያስገባ ይገኛል። ዚኢትዮጵያ መንግሥት አርቢትሬሜኑን አለመቀበሉ ዚሚያበሳጭ ነው። ኹዚህም በተጚማሪ ዹዓለም አቀፍ ማኅበሚሰብ ዚአሜሪካንን መንግሥት በግንባር ቀደምትነት ጚምሮ በኢትዮጵያ ላይ ጫና አለማሳደራ቞ው እንዲሁ ዚሚያበሳጭ ጉዳይ ነው። ስለዚህ ኢትዮጵያ ዚድንበር ውሳኔውን አለማክበሯ ዚጊርነቱ ሁኔታ በሁለቱ ሀገሮቜ እንዲቀጥል ዋነኛው ምክንያት ነው ብዬ አምናለሁ።
3124544
ዚኀርትራ መንግሥት፣ ዚተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ በኀርትራና በጅቡቲ መካኚል ያለውን ቜግር ማጋነኑ፣ ድርጅቱ ኢትዮጵያ ዚባድመን ግዛት መቆጣጠሯን ማስቆም አለመቻሉን ለመሾፈን ዚሚያደርገው ጥሚት ኀርትራን ለማሳጣት ነው ይላል።
3124545
እኔ ማለት ዚምቜለው ኢትዮጵያ በመጀመሪያ ደሹጃ ዚድንበሩን ውሳኔ መቀበል አለባት። ዚኀርትራን መንግሥት በአፍሪካ ቀንድ እያካሄደ ያለው ትርምስ በምንም ዓይነት ይቅርታ ሊደሚግለት አይገባም። በመጀመሪያ ደሹጃ ዚኀርትራ መንግሥት ልክ እንደ መለስ ሥርዓት ህዝቡን ዹሚጹቁን ሥርዓት ስለሆነ ዹሚደገፍ አይደለም። ዚኀርትራው መሪ ኚኢትዮጵያ ጋር ያለውን ውጥሚት ህዝቡን ለመጹቆን ይጠቀምበታል። ዚኀርትራ መንግሥት በቀጠናው ዚሚታወቀው በአፍራሜ መልኩ እያካሄደ ባለው እንቅስቃሎ ነው። ዚኀርትራ መንግሥት በሱዳን፣ በሶማሊያና በተለያዩ በቀጠናው በሚገኙ ሀገሮቜ ጣልቃ እዚገባ ይገኛል። እንዲሁም በሀገር ውስጥና በውጭ እያደሚሰ ባለው ዚሰብዓዊ መብቶቜ ጥሰት መጠዹቅ ይገባዋል።
3124546
አሁን አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ብሎ ራሱን ዹሰዹመው ዚቀድሞ ዚቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞራክሲ ፓርቲ ዚመጪውን እ.ኀ.አ. 2010 (2002 ዓ.ም.) ምርጫ መሳተፍ ዚለበትም ይላሉ?
3124547
ዚመለስ ሥርዓት ሥልጣን ላይ እስካለ ድሚስ በኢትዮጵያ ለሚደሹግ ምርጫ እምነት ዚለኝም። ዹ2005 ምርጫ እንደሚያስተምሚን ዚመለስ ዜናዊ ሥልጣን ላይ ለመቆዚት ዚምርጫን ሂደት ለማዛባት ወደ ኋላ አላለም። አሁንም ቢሆን በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ ያካሂዳል ዹሚል እምነት ዚለኝም። እንደኔ እምነት ዚሜግግር መንግሥት ብቻ ነው በኢትዮጵያ ነፃና ፍትሐዊ ምርጫ ሊያካሂድ ዚሚቜለው።
3124548
ጥቆማ ለጠ/ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ
3124549
ምሕሚት ዘገዬ ክቡር ጠቅላይ ሚንስትር፣ ሰላምታዚን ላስቀድም። ሰላም! ...
3124550
ማስታዋሻ ቁጥር 9፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ በኢትዮጵያ “ዚተቀደሱት ሰላም ፈጣሪዎቜ ናቾው”
3124551
ዚሕዝብ ተሳትፎ ዚሌለበት ውሳኔፀ መፍትሔ አያመጣም (ሾንጎ)
3124552
“ያለውን ዹለገሰ ንፉግ አይባልም”
3124553
ዹመደመር ቋንቋ (ሶምራን)
3124554
አዲስ አበባ ልገባ ነው!
3124555
አርበኞቜ ግንቊት 7 እና ቀጣይ ተግባሩ
3124556
ዚሚቡዕ ግጥም ፫ኛ ዓመት፣ ቁ. ፎ
3124557
ህብር (ላስ ቬጋስ)
3124558
"ደማቜን አንድ ነው!" ሻምበል በላይነህና ሃኒሻ ሰለሞን 

3124559
© ፳፻ - ፳፻፲ ዓ.ም. ኢትዮጵያ ዛሬ፣ መብቱ በሕግ ዹተጠበቀ ነው። Copyright © 2007 - 2018 Ethiopia Zare. All Rights Reserved.
3124560