Unnamed: 0
int64 0
82
| audio_path
stringlengths 38
39
| Transcribed_Text
stringlengths 29
189
|
---|---|---|
0 | Amhariksentencesplitted900k1_sent1.wav | አረንጓዴ ፡ ብጫና ፡ ቀይ ፡ ሰንደቅ ፡ ዓላማችን ፡ የአንድ ፡ ኢትዮጵያና ፡ የነፃነት ፡ ምልክታችን ፡ ነው
|
1 | Amhariksentencesplitted900k1_sent2.wav | አረንጓዴው ፡ የአገራችንን ፡ ልምላሜ ፣ ብጫው ፡ ሃይማኖታችንና ፡ ምግባራችን ፣ ቀዩ ፡ ሀገራችን ፡ ወሰንዋ ፡ ሳይደፈር ፡ ነፃነቷ ፡ ተከብሮ ፡ እንዲኖር ፡ ጀግኖች ፡ ወገኖቻችን ፡ ለከፈሉት ፡ መስዋዕትነትን ፡ የሚገልጽ ፡ ነው
|
2 | Amhariksentencesplitted900k1_sent3.wav | ለኢትዮጵያ የጥምር መንግስት ያስፈልጋታል በማለት በ ምርጫ አጥብቆ ሲከራከር የነበረውና በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ደረጃ ኢንቨስትመንት ውስጥ የገባው ሻለቃ ሃይሌ ገብረስላሴ በኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከነበሩት መንግስታትና ትውልዶች ይልቅ አሁን ላለው ትውልድ ከበሬታ እንዳለው በመግለጽ አስተያየቱን ሰነዘረ
|
3 | Amhariksentencesplitted900k1_sent4.wav | የክብር ሪኮርዶቹን በሙሉ ለቀነኒሳ ያስረከበው ሃይሌ በእጁ የሚገኘውን ብቸኛ ሃብቱን የህዝብ ክብር እያሟጠጠ መሆኑ እየተገለጸ ነው
|
4 | Amhariksentencesplitted900k1_sent5.wav | ሃይሌ ይህንን የተናገረው መስከረም 20 ቀን 2003 ዓ ም ከተለያዩ አስተያየት ሰጪዎች ጋር በመንግስት ቴሌቪዥን ኢቲቪ አስተያየት በሰጠበት ወቅት ነበር
|
5 | Amhariksentencesplitted900k1_sent6.wav | የቀድሞውን ስርዓትና ትውልድ ድንጋይ ዳቦ በነበረበት ፣ ፍራፍሬ ከጫካ ያለምንም ድካም ከሚሰበሰብበት ዘመን ጋር ያወዳደረው ሃይሌ ፣
|
6 | Amhariksentencesplitted900k1_sent7.wav | የአሁኑ ትውልድ በማለት ያሞካሸውን ስርዓት ከተፈጥሮ ጋር ጦርነት በማካሄድ ለውጥ ማስመዝገበ መቻላቸውን አስምሮበታል
|
7 | Amhariksentencesplitted900k1_sent8.wav | የባለ ራዕዩ መሪ አቶ መለስ ገድል ለመዘከር በተዘጋጀ ቅንብር ላይ በተደጋጋሚ አስተያየት ሲሰጥ የታየው ሃይሌ
|
8 | Amhariksentencesplitted900k1_sent9.wav | አሁን የት ነው ያለነው በማለት ጠይቆ አሜሪካ ኤምባሲ ቪዛ ለማግኘት ነው የምንጋፋው
|
9 | Amhariksentencesplitted900k1_sent10.wav | አውሮፓ ሄደን እዛው ለመቅረት ነው በማለት ስደትን መርጠው ከአገራቸው የሚወጡትን ሸርድዶ አልፏል
|
10 | Amhariksentencesplitted900k1_sent11.wav | አሁን ባለው የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ለስደት የሚዳርግ ጉዳይ የለም ወደ ማለት አዝምሞ ተናግሯል
|
11 | Amhariksentencesplitted900k1_sent12.wav | ይህን ይበል እንጂ በተቃራኒው እስረኞች እንዲፈቱና የፖለቲካ እርቅ እንዲሰፍን እሰራለሁ ከሚሉት ፕሮፌሰር ይስሃቅ ጋር በሽምግልና እያገለገለ መሆኑ
|
12 | Amhariksentencesplitted900k1_sent13.wav | በአገሪቱ ውስጥ የሚታው እስርና እንግልት ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን የሚጠቅሱ አስተያየት ሰጪዎች የሃይሌን አስተያየት ለንብረት ዋስትና የሚከፈል የንግግር ቫት በማለት አጣጥለውታል
|
13 | Amhariksentencesplitted900k1_sent14.wav | ከኤርትራ ጋር ከተደረገው በቀር በኢትዮጵያ ይህ ነው የሚባል ጦርነት እንዳልተካሔደ ኢህአዴግን የሰላም አባት አስመስሎ ሃይሌ አመልክቷል
|
14 | Amhariksentencesplitted900k1_sent15.wav | በዚሁም ምክንያት ቀደም ሲል ለጦርነት ይውል የነበረው የአገሪቱ በጀት ሙሉ በሙሉ ወደ ልማት ዞሯል ብሏል
|
15 | Amhariksentencesplitted900k1_sent16.wav | የኢህአዴግ ተወካይ መስሎ አስተያየት የሰጠው ሃይሌ ይህ አሁን የታየው ለውጥ በአስርና አስራ አንድ ዓመት ውስጥ የታየ ነው
|
16 | Amhariksentencesplitted900k1_sent17.wav | አሁን ባለው አካሄድ ከአስር ዓመት በኋላ እንደርሳለን ሲል የራሱን ትንቢት አስቀምጧል
|
17 | Amhariksentencesplitted900k1_sent18.wav | ተቆራርጦ በሚቀርበው አስተያየት እነ ፕሮፌሰር እንድሪያስን በማጀብ ሃይሌ በመዝገበ ቃላት ላይ ኢትዮጵያን ረሃብ በማለት የሚተረጉማት ቃል እንደሚቀየር በልበ ሙሉነት ተናግሯል
|
18 | Amhariksentencesplitted900k1_sent19.wav | ከሃያ ዓመት በኋላ አለ ሃይሌ በመዝገበ ቃላት ላይ የኢትዮጵያ ውርስ ትርጉም ሃብታም በሚል ይቀየራል ብሏል
|
19 | Amhariksentencesplitted900k1_sent20.wav | ድሮ ትረዱን ነበር ፤ እናመሰግናለን አሁን ደግሞ እንረዳችሀዋለን እንላቸዋለን ሲል አውሮፓና አሜሪካን የመሳሰሉ ታላላቅ አገሮች የኢትዮጵያን እጅ እንደሚናፍቁ ሃይሌ ከምኞት ባለፈ ስሜት ውስጥ ሆኖ ተናግሯል
|
20 | Amhariksentencesplitted900k1_sent21.wav | አገሪቱን ለሃያ አንድ ዓመታት ሲመሩ የነበሩት አቶ መለስ ባልገለጹበት ሁኔታ ሃይሌ ከአስር እስከ ሃያ ዓመት ኢትዮጵያ ሃብታም አገር እንደምትሆን መናገሩ ከምን የመነጨ እንደሆነ ሊገባቸው እንዳልቻለ ብዙዎች እየገለጹ ነው
|
21 | Amhariksentencesplitted900k1_sent22.wav | ሙስና ከፍተኛ ደረጃ ደርሷል ሲል ኢህአዴግን የመከረው ሃይሌ የበታች ባለስልጣናት መንግስትን እንዳያሰድቡ መክሯል
|
22 | Amhariksentencesplitted900k1_sent23.wav | መንግስት ይህንን አድርጉ ላይል ይችላል የሚለው ሃይሌ የበታች ባለስልጣኖች የሚፈጽሙት ሙስና መንግስትን ያስወቅሰዋል በሚል ተቆርቋሪነቱን በይፋ አስታውቋል
|
23 | Amhariksentencesplitted900k1_sent24.wav | ዋናዎቹን የሙስና ተዋናዮች ነጻ በማውጣት የታች ባለስልጣኖችን እያንገዋለለ አሳጥቷቸዋል
|
24 | Amhariksentencesplitted900k1_sent25.wav | ለህሊናቸው ሲሉ እንደ መንግስት በማሰብ መስራት አለባቸው ሲል ትዕዛዝ አዘል ምክርና ማሳሰቢያ ለበታች ባለስልጣናት ያስተላለፈው ሃይሌ የአስተያየቱ መነሻ ከኢህአዴግ ጋር የፈጠረው ዝምድና ውጤት እንደሆነ እየተነገረ ነው
|
25 | Amhariksentencesplitted900k1_sent26.wav | አንድ አስተያየት ሰጪ ሃይሌ ሃብቱ እየበዛ ሲሄድና የተበደረው ገንዘብ ሲጨምር ኢህአዴግን ወክሎ መናገር ጀመረ ብለዋል
|
26 | Amhariksentencesplitted900k1_sent27.wav | አትሌቶችን ሰብስቦ የአቶ መለሰን ሃዘን ሳግ በያዘው ድምጽ እያለቀሰ የገለጸው ሃይሌ ነፍሳቸውን ይማረውና በአቶ መለስ አይወደድም ነበር
|
27 | Amhariksentencesplitted900k1_sent28.wav | በህይወት እያሉም በተደጋጋሚ ያናንቁት ነበር
|
28 | Amhariksentencesplitted900k1_sent29.wav | ሃይሌን እንደሚያደንቁት ተጠይቀው አርቲስት ቻቺን በማሞገስ ጭራሹኑ እንደማያወቁት ዘለውት አልፈውት ነበር
|
29 | Amhariksentencesplitted900k1_sent30.wav | ኢህአዴግ በተለይም ህወሃት ለሃይሌ ቁብ እንደሌላቸው የሚያውቀው ሃይሌ ከአንድ ማስታወቂያ ሰራተኛ ልቆ በፕሮፓጋንዳ ተግባር ላይ መሰማራቱ በቅርብ ጓደኞቹና በአድናቂዎቹ ዘንድ መነጋገሪያ አድርጎታል
|
30 | Amhariksentencesplitted900k1_sent31.wav | ቀጭኑ ዘቄራ ለአዲስ አበባ ከተማ ክብር ያላችሁ እንስማማለን አዲስ አበባ አንጀቷ ርህሩህ ነው
|
31 | Amhariksentencesplitted900k1_sent32.wav | ከገዢዎች ክፋት በተጨማሪ አዲስ አበባ ፊቷን ብታጠቁር ምን ይኮን ነበር ሎሬት ጸጋየ ስለ አዲስ አበባ የተቀኙት ወደው አይደለም
|
32 | Amhariksentencesplitted900k1_sent33.wav | በውነት ላስተዋለው የአዲስ አበባ ቆዳና ያዲስ አበቤዎች ትከሻ ላይችል አይሰጥም የሚሉት አይነት ነው
|
33 | Amhariksentencesplitted900k1_sent34.wav | በየቀኑ አዲስ አበባ በማለዳ በቀንና በምሽት የምትሰበስባቸው ልጆቿ ተቃምሰው ማደራቸው በአድስ አበባ በረከት እንጂ በገዢዎች አቅርቦት አይመስልም
|
34 | Amhariksentencesplitted900k1_sent35.wav | ከአራቱም ማዕዘን የሰው ደራሽ ወደ አዲስ አበባ ይንፎለፎላል አዲስ አበባ ሞልታ የምትፈስ አትመስልም
|
35 | Amhariksentencesplitted900k1_sent36.wav | እምዬ ምኒሊክ ሲቆረቁሯት ጀምሮ አዲስ አበባ ተቀባይ ነች
|
36 | Amhariksentencesplitted900k1_sent37.wav | የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ፣ የአፍሪካ መዲና ፣ የሰው ልጅ እምብርት ፣ አዲስ አበባ ፣ ፊንፊኔ ምንም ትባል ምን አዲስ አበባ ሁሉም ጓዳ የተባረከች ናት
|
37 | Amhariksentencesplitted900k1_sent38.wav | ዘላለማዊነት ለአዲስ አበባ የቀጭኑ ቄራ መፈክር ነው
|
38 | Amhariksentencesplitted900k1_sent39.wav | ባለፈው ሳምንት በሬ ለምኔን አሳይቼ ፣ ዝግ ቤቶች አቆይቻችሁ ፣ እንስራ እርቃን ቤት ስለሚካሄደው ድራማ አውግተን ነበር የተለያየነው
|
39 | Amhariksentencesplitted900k1_sent40.wav | ሰላም አንባቢዎቼ ጎልጉል ድረገጽ ጋዜጣ ላይ መለቅለቅ መጀመሬ አስከሚነቃ ለመቀጠል በገባሁት ቃል መሰረት የዛሬው ተረኛ ማስታወሻዬን ከፈትኩ
|
40 | Amhariksentencesplitted900k1_sent41.wav | የመሬት ውስጥ ነዋሪዎች ከመሬት በታች የሚኖሩት ሙታኖች ብቻ ናቸው ያለው ማን ነው አዲስ አበባ ሁሉን ቻይ ነች
|
41 | Amhariksentencesplitted900k1_sent42.wav | ከርሷ የማይችለው የለውም ሁሉንም አቻችላ የመንግስትን ሚና በመጫወት ታኖራለች
|
42 | Amhariksentencesplitted900k1_sent43.wav | ሰዎቹ ሲያቅታቸው እየቀበረች የማስተዳደር ስራዋን ከሰው በላይ ታከናውናለች
|
43 | Amhariksentencesplitted900k1_sent44.wav | ሰባተኛ በመባል የሚታወቀው ያራዶች ሰፈር ላፍታ ቆምኩ ከምሽቱ አንድ ሰአት አካባቢ ይሆናል
|
44 | Amhariksentencesplitted900k1_sent45.wav | መርካቶ ሸቅለው ወደ ቤታቸው የሚተሙ ብዛታቸው ያስደነግጣል
|
45 | Amhariksentencesplitted900k1_sent46.wav | ድሮ አውሬው ሳይኖር የምታውቁት በአንድ ብርና በሽልንግ ጭን የሚሞቅበት ሰባተኛ ዛሬ የተለየ ነው
|
46 | Amhariksentencesplitted900k1_sent47.wav | ከመርካቶ ነቅለው ወደ ማደሪያቸው የሚተሙት ነዋሪዎች ሰላማዊ ሰልፍ የሚያደርጉ ወይም ከስታዲየም የሚለቀቁ እንጂ ለጉዳይ ወጥተው ወደቤታቸው የሚገቡ አይመስሉም
|
47 | Amhariksentencesplitted900k1_sent48.wav | በሰባተኛ ወደ አማኑኤል የሚተሙት ስፍር ቁጥር የሌላቸው ሰዎች ፌስታል ማንጠልጠል አይዘነጉም አብዛኞቹ የሚይዙት ላስቲክ ዳቦ የያዘ ነው
|
48 | Amhariksentencesplitted900k1_sent49.wav | ማባያውን ያዲሳባ አምላክ ይወቀው ያየሁት የሚፈሱትን ሰዎች እንጂ ማረፊያቸውን አይደለም
|
49 | Amhariksentencesplitted900k1_sent50.wav | ፈሰው እንደሚገቡት ሁሉ ማለዳ ተነስተው ወደ መርካቶም የሚፈሱት በተመሳሳይ በግፊያ ነው
|
50 | Amhariksentencesplitted900k1_sent51.wav | ግፊያው በአገሪቱ የስነ ህዝብ ፖሊሲ ስለመኖሩ ያጠራጥራል
|
51 | Amhariksentencesplitted900k1_sent52.wav | እግረ መንገዴን አነሳሁት እንጂ የዛሬው ዋና ርዕሴ ከመሬት ውስጥ በህይወት ስለመሸጉ ወገኖች ለማሳወቅ ነው
|
52 | Amhariksentencesplitted900k1_sent53.wav | ጊዜው ትንሽ ቢቆይም በግራውንድ ሲቀነስ አንድ አንድ ደረጃ ወደ መሬት ዝቅ ብለው የሚኖሩ ብዙ ናቸው
|
53 | Amhariksentencesplitted900k1_sent54.wav | ለዛሬ የማስተዋውቃችሁ ከአቡነ ጴጥሮስ እስከ አውቶቡስ ተራ በየመንገዱ አካፋይ መሃል ለመሃል በተዘረጋው ውሃ መውረጃ ቱቦ ውስጥ ስለሚኖሩት ነው
|
54 | Amhariksentencesplitted900k1_sent55.wav | ግራውንድ ሲቀነስ አንዶች አቡነ ጴጥሮስን ይዛችሁ ወደ መስጊድ ስትጓዙ የመንገዱን አካፋይ ትመለከታላችሁ
|
55 | Amhariksentencesplitted900k1_sent56.wav | ለበርካታ ዓመታት መንገዱን እያየሁ ተሸጋግሬበታለሁ ከስሩ ሰው ስለመኖሩ አስቤም አልሜም አላውቅም ነበር
|
56 | Amhariksentencesplitted900k1_sent57.wav | አንድ ቀን አትክልት ተራ የሚያቆየኝ ጉዳይ አጋጠመኝ ጉዳዬ በአጋዥ የሚከናወን ነበርና አንድ ጎረምሳ እንዲተባበረኝ ጠየኩት
|
57 | Amhariksentencesplitted900k1_sent58.wav | ስራችንን እንደጨረስን በመንገዱ አካፋይ በግምት በመቶ ሜትር ርቀት የሚታየውን ጉድጓድ ስለሸፈነው ስብርባሪ መስታወት ድንገተኛ ጥያቄ አነሳሁ
|
58 | Amhariksentencesplitted900k1_sent59.wav | ጎረምሳው ተረከልኝ እንዲህ ሲል የመኖሪያ ቤት በር ነው ከላይ ከአቡነ ጴጥሮስ እስከ መስጊድ መብራቱ ድረስ ውስጡ ክፍት ነው በግንብ የተሰራ የውሃ መውረጃ ቱቦ አለ
|
59 | Amhariksentencesplitted900k1_sent60.wav | ከላይ እስከታች በስምምነት እንኖርበታለን ቤተሰብ ያፈሩ የልጅ ልጅ ያዩ አሉ ቤታችን ነው ለቤት በር ያስፈልገዋል ደነገጥኩ
|
60 | Amhariksentencesplitted900k1_sent61.wav | የመንገዱን አካፋይ በመያዝ በግምት በመቶ ሜትር ርቀት ያሉትን በሮች እየተመለከትኩ አስጎብኚዬን እቀዳው ጀመር
|
61 | Amhariksentencesplitted900k1_sent62.wav | ሃብተ ጊዮርጊስ ስንደርስ ቆመና ወደ ድልድዩ ወሰደኝ ወንዙ አፍ ላይ የሚቀረውን የአንዱን ቱቦ ጫፍ አሳየኝና የአስከሬን መውጫ በር መሆኑን ነገረኝ
|
62 | Amhariksentencesplitted900k1_sent63.wav | ይህን ጊዜ አንድ ራሱን የቻለ ማህበረሰብ ከመሬት በታች እንደሚኖሩ ተረዳሁና ዝርዝር ነገሮችን የማወቅ ጉጉቴ ነደደ
|
63 | Amhariksentencesplitted900k1_sent64.wav | አዎ አስገራሚ ታሪክና የኑሮ ወግ ያላቸው ውብ ፍጡሮች ከመሬት በታች ይኖራሉ
|
64 | Amhariksentencesplitted900k1_sent65.wav | በአገሪቱ ፖለቲካና ባገራቸው ጉዳይ አያገባቸውም የአዲስ አበባ እንብርት ውስጥ ይኖራሉ ግን አድራሻ ያለቸውም ቀበሌና ቤት ቁጥር አያውቁም
|
65 | Amhariksentencesplitted900k1_sent66.wav | ቀበሌ ስለሌላቸው አይመርጡም ለመመረጥም እድል የላቸውም የሁሉም ዜጎች መብት በተከበረባት ኢትዮጵያ ወደ አትክልት ተራ ተመልሰን ዘላለም ደስታ ሆቴል በር ፊትለፊት ባለው በራቸው
|
66 | Amhariksentencesplitted900k1_sent67.wav | ህወሓት የአጋር ፓርቲዎቹን የንግድ ተቋማትና ልማታዊ ባለሀብት እያለ የሚጠራቸውን አባላቱን በዋናነት አሰባስቦ ያቋቋመው የወጋገን ባንክ ውለታ ባስገባቸው የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች አማካይነት በቀን እስከ ሁለት ሚሊዮን የሚጠጋ ዶላር የመሰብሰብ አቅም መገንባቱ ተጠቆመ
|
67 | Amhariksentencesplitted900k1_sent68.wav | የድረገጽ ጋዜጣ የአዲስ አበባ ዘጋቢ ባካሄደው ማጣራት ወጋገን ባንክ ከፖለቲካው አመራር ባለው ቀጥተኛ ድጋፍና ሽፋን በመታገዝ ወደ ኢትዮጵያ የሚተላለፈውን የውጪ ምንዛሪ መቆጣጠር ያስቻለውን አቅም የገነባው በአስገዳጅ ደንብ ነው
|
68 | Amhariksentencesplitted900k1_sent69.wav | በሶማሌ ተወላጆችና በህወሓት ሰዎች አማካይነት በሽሪክነትና በተናጥል የተቋቋሙ የገንዘብ አዘዋዋሪ ተቋማት ስራውን መስራት የሚያስችላቸውን ፈቃድ ሲያወጡ ከወጋገን ባንክ ጋር ብቻ ለመስራት አስቀድመው ውል ይፈጽማሉ
|
69 | Amhariksentencesplitted900k1_sent70.wav | በዚሁ መሰረት ውል ከገቡት የገንዘብ አሰባሳቢ ድርጅቶች መካከል ዋንኞቹን በስም ዘርዝሯል
|
70 | Amhariksentencesplitted900k1_sent71.wav | ደሀብሺል፣ ካህ ኤክስፕሬስ ፣ ተወከል፣ ገረን ኤክስፕሬስ፣ ኦሊምፒክ ኤክስ ፣ ሆዲን ግሎባል ኤክስፕሬስ፣ ሰሃል የመሳሰሉት በኢትዮጵያ ቢሮ ከፍተው በገንዘብ ዝውውር ስራ የሚሰሩትን ድርጅቶች የዘረዘረው
|
71 | Amhariksentencesplitted900k1_sent72.wav | የድረገጽ ጋዜጣ የአዲስ አበባ ዘጋቢ የገንዘብ ዝውውሩ እንዴት እንደሚከናወን አመልክቷል
|
72 | Amhariksentencesplitted900k1_sent73.wav | ከአውሮፓ ፣ ከአሜሪካና ከአረብ አገራት ወደ ኢትዮጵያ የሚላከውን የውጪ ምንዛሪ በማስተላለፍ ኮሚሽን የሚወስዱት ክፍሎች ራሱ ወጋገን ባንክ ፣
|
73 | Amhariksentencesplitted900k1_sent74.wav | ምንዛሪውን ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች ወደ ወጋገን ባንክ የሚያስተላልፉት የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶችና እነዚህ ድርጅቶች ብር እየለቀሙ በወጋገን ባንክ በኩል እንዲላክ የሚያደርጉ ደላሎች ሲሆኑ ከሚተላለፈው ገንዘብ ሁሉም በጥቅሉ የሚካፈሉት የአምስት በመቶ ኮሚሽን አላቸው
|
74 | Amhariksentencesplitted900k1_sent75.wav | በዚሁ ስሌት መሰረት ወጋገን ባንክ ሁለት በመቶ ፣ የገንዘብ አስተላላፊው ተቋም ሁለት በመቶ ፣ ደላሎቹ ደግሞ አንድ በመቶ በዶላር ሂሳብ የሚታሰብና ባሉበት አገር ገንዘብ ተመንዝሮ የሚሰጣቸው ድርሻ አለቸው
|
75 | Amhariksentencesplitted900k1_sent76.wav | ወጋገን ባንክ ዶላሩን በራሱ ሒሳብ አካውንትt በታዋቂ አለም አቀፍ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች አማካይነት ካስገባ በኋላ ከአምስት መቶኛው ድርሻውን ከውሰዱ በተጨማሪ
|
76 | Amhariksentencesplitted900k1_sent77.wav | በያንዳንዱ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች ውስጥ በገንዘብ ተቀባይነት ካሽየር የሚሰሩ ሰራተኞችን በመመደብ ገንዘብ ለተላከላቸው ሰዎች በኢትዮጵያ ብር ክፍያ የሚያከናውነው ራሱ ነው
|
77 | Amhariksentencesplitted900k1_sent78.wav | የሚላከው የውጪ ምንዛሪ በራሱ አካውንት ከገባለት የራሱን ገንዘብ ከፋይ ለምን ይመድባል በሚል ዘጋቢያችን ላነሳው ጥያቄ ገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶቹ ከዋናው ተልዕኳቸው ውጪ በማናቸውም የገንዘብ ማቀባበል ስራ እንደሚሰሩ አይፈለግም ፤ አመኔታም የላቸውም
|
78 | Amhariksentencesplitted900k1_sent79.wav | የሚላከው ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ ብር ሲቀየር በርካታ ስለሆነ ወጋገን ባንክ ከእስልምና ጉዳዮችና ከተለያዩ እንቅስቃሴዎች ጋር ግንኙነት ሊኖረው ይችላል የሚል ስጋት ስላለበትም ጭምር ተቀባዮችንም ለመቆጣጠር ጭምር ሲባል ነው ሲሉ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው መልስ ሰጥተዋል
|
79 | Amhariksentencesplitted900k1_sent80.wav | አውሮፓ ተቀምጦ ገንዘብ በማሰባሰብ አንድ ከመቶ ኮሚሽን የሚወስድ አንድ የድለላ ሰራተኛ ለጎልጉል ፡ የድረገጽ ጋዜጣ ሪፖርተር እንደተናገረው ስራ የለም ከተባለ እስከ ሃምሳ ሺህ ዶላር በቀን ወደ ወጋገን አካውንት የሚገባ የገንዘብ ሰነድ ለቀጠረው የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅት እንደሚልክ አስታውቋል
|
80 | Amhariksentencesplitted900k1_sent81.wav | የገንዘብ አዘዋዋሪ ድርጅቶቹ የሶማሌ ተወላጆች ቢመስሉም ከጀርባቸው ተቆጣጣሪና ሽርካ እንዳላቸው የጠቆመው ይህ ደላላ
|
81 | Amhariksentencesplitted900k1_sent82.wav | ከኢትዮጵያውያን በተጨማሪ የሶማሌ ዜጎች ከፍተኛ የውጪ ምንዛሪ በመላክ ወጋገን ባንክን እያደለቡት እንደሆነ አመልክቷል
|
82 | Amhariksentencesplitted900k1_sent83.wav | ስሙ እንዳይገለጽበት የጠየቀው የሶማሌ ተወላጅ የኢትዮጵያ መንግስት በኛ መስመር ብቻ በቀን እስከ ሁለት ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ የውጪ ምንዛሪ ከአውሮፓ ብቻ ያገኛል
|
Subsets and Splits