[ { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nመልከአ-ምድር አንጎላ፣ በ1,246,620 ካሬ ኪ.ሜ. ከኒጄር ቀጥላ ከዓለም 23ኛው ትልቅ አገር ናት። በስፋት ከማሊ ጋር ትነጻጸራለች። የአሜሪካ የቴክሳስ ክፍላገርን ሁለት ዕጥፍ ታክላለች። አንጎላ ከደቡብ በናሚቢያ፣ ከምሥራቅ በዛምቢያ፣ ከሰሜን-ምሥራቅ በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና ከምዕራብ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ትዋሰናለች። የአንጎላ አማካይ የባህድ ዳር የአየር ሁኔታ በክረምት 16° ሴንቲግሬድና በበጋ 21° ሴንቲግሬድ ነው። አንጎላ ሁለት ወቅቶች አሏት። እነዚህም ደረቅና ዝናባማ ናቸው። መጓጓዣ በአንድ ላይ ርዝመታቸው 2,761 ኪ.ሜ. የሆኑ ሦስት የባቡር መንገዶች፤ 76,626 ኪ.ሜ. አውራ ጎዳና ከዚህም ውስጥ 19,156 ኪ.ሜ. አስፋልት፤ 1,295 ኪ.ሜ. የውሃ መንገድስምንት ትልቅ ወደቦች፤ 243 የአውሮፕላን ማረፊያዎች ከነዚህም 32ቱ የአስፋልት መንደርደሪያ ያላቸው፤ አንጎላ የሰፋ የመጓጓዛ አውታር ቢኖራትም በጊዜ ማለፍና ጦርነት ምክንያት መንገዶች አስፈላጊ ጥገኛ አልተደረገባቸውም። በአንዳንድ ቦታዎች አሽከርካሪዎች መጥፎ ቦታዎችን ለማለፍ ሲሉ ከመንገድ ውጭ ይነዳሉ። እንደዚህ ከማድረግ በፊት ግን በመንገድ ዳር ያሉ በመሬት ውስጥ ስለተቀበሩ ፈንጂዎች የሚያስጠነቅቁ ምልክቶችን ማስተዋል ያስፈልጋል። ኢኮኖሚ የአንጎላ ኢኮኖሚ ትልቅ ለውጥ አሳይቷል። የሩብ ምእተ ዓመት ጦርነት ያሳደረበት ተጽእኖን አልፎ ዛሬ በዓለም ውስጥ በፍጥነት በማደግ ላይ ካሉት ኢኮኖሚዎች ይመደባል። በ2004 እ.ኤ.አ. የቻይና ኤክሲምባንክ ፪ ቢሊዮን ብር ለአንጎላ አበድሯል። ይህ ገንዘብ እንደ መንገዶች ያሉትን የአንጎላ መሠረታዊ ተቋሞች ለማሻሻል የሚውል ነው። ዘ ኢኮኖሚስት መጽሄት በ2008 እ.ኤ.አ. እንደዘገበው ነዳጅና ዕንቁ የአንጎላ ዋና ኤክስፖርቶችና የገቢ ምንጮች ናቸው። \n \nጥያቄ: አንጎላ በምሥራቅ በማን ነው የምትዋሰነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በዛምቢያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቴሌቪዥን ቴሌቪዥን የስዕል እና ድምጽ ምልክቶችን ከማሰራጫ የሚቀበል የመገናኛ ዘዴ ነው። «ቴሌ-» የሚለው ክፍል በግሪክ «ሩቅ» ማለት ቢሆን «-ቪዥን» ደግሞ ከሮማይስጥ visio /ዊዚዮ/ «ማየት» («ትርዒት») ተወስዷል። በአጠቃላይ ቴሌቪዥን ማለት ተንቀሳቃሽ ምስልን (ብዙ ጊዜ ከድምፅ ጋር) ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለማስተላለፍ የሚረዳ የመልዕክት ማስራጫ መንገድ ነው። ይህ ከሆነ ዘንዳ ቴሌቪዥን ምስል መቅጃውንም ሆነ ምስል መቀበያውን መሳሪያ ሁሉ ያጠቃልላል ግን በተለምዶ ቴሌቪዥን የምንለው ምስል መቀበያውን ብቻ ነው። በ1873 እ.ኤ.አ. (1865 ዓም) የእንግላንድ ኤንጅኔር ውሎቢ ስሚስ ባደረገው ጥረት ጥንተ ንጥሩ ሴሌኒይም ብርሃን-አስተላልፎሽ መሆኑን ገለጸ። በ1884 እ.ኤ.አ. ፓውል ጎትሊብ ኒፕኮው የተባለ ጀርመናዊ ክብ የሆነ ዲስክን በስፓይራል በምብሳት ይህ ዲስክ በተሽከረከረ ቁጥር ከፊትለፊቱ የሚመጣውን ብርሃን በቀዳዶቹ በማሾለክ ከሴሌኒይም በተሰራ የካሜራ ግድግዳ ላይ እንዲያርፍ አደረገ። ግድግዳው ብርሃን ሲነካው ያንን ብርሃን ወደ ኮሬንቲ ሃይል በመቀየር ምስልን በኮሬንቲ መልክ በሽቦ ለመላክ ቻለ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ አምፕሊፋየር ስላልነበር የሚላከው ምስል እምብዛም አመርቂ አልነበረም። ከ27 አመታት በኋላ በ1911 እ.ኤ.አ. የራሻው ቦሪስ ሮዚንግ ለመጀመሪያ ጊዜ የሲርቲን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፣ አሁንም ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል ቻለ። ነገር ግን የሚንቀሳቀሱት ምስሎች የጂዎሜትሪ ቅርጽ ነበራቸው ማለትም ሶስት ማዕዘን፣ አራት ማእዘን ወዘተ... ከ7 አመታት በኋላ በ1925 እ.ኤ.አ. ጆን ሎጂ ቤርድ የተሰኘው የስኮትላንድ ተመራማሪ 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለመላክ ቻለ ከዚያም በ1926 እ.ኤ.አ. ጥቁርና ነጭ የሆኑ ምስሎችን ለማስተላለፍ በቃ። በዚህ ጊዜ የሚላኩት ምስል ጥራት 30 መስመር በአንድ ጊዜ ነበር፣ በዚህም ምክንያት የሰውን ፊት ለመለየት አስቸጋሪ ቢሆንም ግን ይቻል ነበር። አቶ ቤርድ በ 1918 ዓ.ም. (26 January 1926 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የቴሌቪዥን መግለጫ ሰጠ። በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ የተሰኘው የቤል ላብራቷር ተቀጣሪ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ መላክ ቻለ። ቀጠል አድርጎም በራዲዮ ወደ ዊፓኒ ኒው ጀርሲ ለመላክ በቃ። በዚያው አመት ፊሎ ፍራንስዎርዝ የመጀመሪያውን የተሟላና በኤሌክትሪክ ስካኒንግ ብቻ የሚስራውን የቴሌቭዥን ስርዓት በተግባር አዋለ።.በጥር 1928 እ.ኤ.አ. (1920 ዓም) መጀመርያው የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያ በስከነክተዲ፣ ኒው ዮርክ ተከፈተ፤ እስከ ዛሬም ድረስ ያሰራጫል። \n \nጥያቄ: ኸርበርት አይቭስ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ የላከው መች ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ1927 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበቁርጥራጭ ብረትና ያገለገሉ ማሽኖች ንግድ የተሰማራው ሳርፌ ቢዝነስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር፣ የግንባታ ብረታ ብረቶች ማምረቻ ፋብሪካ በዱከም ከተማ ለመገንባት በዝግጅት ላይ እንደሆነ አስታወቀ፡፡ የሳርፌ ቢዝነስ መሥራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ክብርይስፋ ተክሌ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ኩባንያው እስካሁን ቁርጥራጭ ብረቶች ከውጭ በማስመጣትና ከአገር ውስጥ በመግዛት ለብረት አቅላጮች ሲያቀርብ ቆይቷል፡፡ የብረት ማቅለጫው ማሽኖች ከህንድ ተገዝተው የሚመጡ ሲሆን፣ የብረት መዋቅሩ ደግሞ ከቻይና ይገዛል፡፡ የፋብሪካው ጠቅላላ የኢንቨስትመንት ወጪ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚገመት የተናገሩት አቶ ክብርይስፋ፣ ፋብሪካው ለ300 ኢትዮጵያውያን የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡ ሳርፌ ቢዝነስ ለብረት ፋብሪካው ግንባታ የሚሆን 30,000 ካሬ ሜትር ቦታ በሊዝ ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከዱከም ከተማ አስተዳደር በቅርቡ መረከቡን ገልጸው፣ ኩባንያቸው ተገቢውን የአዋጭነት ጥናት ማሠራቱን አስረድተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ሳርፌ ቢዝነስ ዋና የንግድ ስራው ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በቁርጥራጭ ብረትና ያገለገሉ ማሽኖች ንግድ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበርግጥም የመጀመሪያው በሰፊው ተግባራዊ የሆነ የቴሌቭዥን ስርዓት ስራ ላይ የዋለው በጀርመን አገር ሲሆን ይኸውም በ1929 እ.ኤ.አ. ነው። በ1936 እ.ኤ.አ. (1928 ዓም) ጀርመን ሃገር ተደርጎ የነበረውን የኦሎምፒክ ውድድር በቴሌቭዥን ሊሰራጭ ቻለ፣ ህዝቡም ውድድሩን እቤቱ ሆኖ ቀጥታ ሲካሄድ ለማየት ቻለ። ከዚያ መጀመርያው ጥቁርና-ነጭ ፕሮግራሚንግ በዩናይትድ ኪንግደም 1928 ዓም፤ በአሜሪካ 1933 ዓም ተደረገ። በአፍሪካ መጀመርያው ጣቢያዎች በ1952 ዓም በናይጄሪያና ደቡብ ሮዴዝያ (አሁን ዚምባብዌ) ተሰራጩ፣ በኢትዮጵያ የቴሌቪዥን ስርጭት አገልግሎት (ኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን) የጀመረው በ1956 ዓም ሆነ። ሁለት አገራት - እነርሱም ቱቫሉና ኪሪባስ - ምንም የራሳቸውን ቴሌቪዥን አሁን አያሰራጩም፤ ሆኖም የሌላ አገር ስርጭት እዚያ ሊታይ ይችላል። ከዚያ ቤርድ በግንቦት 26 ቀን 1920 (ጁላይ 3, 1928 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የከለር ቴሌቪዥን ስርጨት ሙከራ አደረገ። ነገር ግን ከለር ቴሌቪዥን ቢፈጠረም ለሚከተሉት ብዙ ዓመታት ስርጭት ባብዛኛው ጥቁርና ነጭ ብቻ ሆኖ ቀረ። ይሄው ቴክኖዎሎጂው በጣም ውድ፣ በጣም ከባድና በትክክል ያልተስተካከለ ስለ ሆነ ነው። በየጥቂቱ ከ1946 ዓም (1954 እ.ኤ.አ.) ጀምሮ አገራት ወደ ከለር ስርጭትና ከለሩን ማሳየት የሚችል ቴሌቪዥን ወደ መሸጥ ይዛወሩ ጀመር። በጥር ወር 1946 ዓም NBC የተባለው አሜሪካዊ ስርጭት ጣቢያ በከፊሉ ወደ ከለር ተሸጋገረ፤ ብዙ ሰዎች ግን ያንጊዜ ከለር ማሳያ ቴሌቪዥን ለመግዛት ገና አልቻሉም ነበር። ከ1955 እስከ 1959 ዓም ድረስ ሌሎቹ ትልልቅ አሜሪካዊ ጣቢያዎች ABC እና CBS ደግሞ ወደ ከለር ተዛወሩ፣ የከለርም ተቀባዮች ዋጋ እየተቀነሰ የሚይዩት ሕዝብ ቁጥር ደግሞ ከዚህ በኋላ እየተጨመረ ሄደ፤ ከረጅሙ ጥቁርና-ነጭ ዘመን ቀጥሎ ከለርም በኅብረተሠብ ያመጣው ለውጥ ለግዙፍነቱ በኋላ ኢንተርኔት እንደ ሆነ ያሕል ነው። ጃፓን በ1952 ዓም፣ ሜክሲኮ በ1955፤ ካናዳ በ1958፣ የአውሮፓ ኅብረትና የሶቪዬት ሕብረት በ1959፣ ኮት ዲቯር በ1962፣ አውስትራሊያ በ1967 ከለር ስርጭትን ጀመሩ። በኢትዮጵያም ከለር ስርጭት ከ1976 ዓም ጀምሮ ተገኝቷል። በ1977 ዓም ሮማኒያ ከጥቁርና-ነጭ ስርጭት ወደ ከለር ማሰራጨት የለወጠ በዓለም መጨረሻው ሃገር ሆነ። \n \nጥያቄ: ጁላይ 3, 1928 እ.ኤ.አ. የመጀመሪያውን የቀለም ቴሌቪዥን ሙከራ ስርጭት ያደረገው ማነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ቤርድ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nመንግሥት እና ፖለቲካ ናይጄሪያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ ሲሆን መንግሥቷ በአሜሪካ መንግሥት ላይ ነው የተመረኮዘው። የህግ አውጪው አካል አወቃቀር የዌስትሚኒስትር ሥርዓትን ይከተላል። በአሁኑ ጊዜ ጉድላክ ጆናታን ፕሬዝዳንት ናቸው። ፕሬዝዳንቱ ለሁለት የአራት ዓመት ጊዜ ሲያገለግል በሕዝቡ ነው የሚመረጠው። የናይጄሪያ ብሔራዊ ምክር ቤት ሁለት አካሎች አሉት። እነዚህም ሴኔት እና የተወካዮች ምክር ቤት ናቸው። ሴኔቱ 109 መቀመጫዎች ሲኖሩት እያንዳንዱ ክልል በሶስት አባሎች ይወከላል። የአቡጃ ርዕሰ አካባቢም አንድ ተወካይ አለው። የሴኔት አባላት በሕዝብ ይመረጣሉ። የተወካዮች ምክር ቤት 360 መቀመጫዎች ሲኖሩት የእያንዳንዱ ክልል ወካዮች በሕዝብ ብዛት ነው የሚወሰነው። የውጭ ግንኙነቶች ነፃነቷን በ1960 እ.ኤ.አ. ካገኘች በኋላ ናይጄሪያ ለአፍሪካ ነፃነትና ክብር መታገል ዋና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ አድርጋለች። የደቡብ አፍሪካን አፓርታይድ ሥራዓት በመቃወም ትልቅ ሚና ተጫውታለች። በ1960ዎቹ እ.ኤ.አ. ናይጄሪያ ከእስራኤል ጋር የጠበቀ ግንኙነት የነበራት ሲሆን እስራኤል የናይጄሪያ ፓርላማ ህንጻዎችን አሰርታለች። ናይጄሪያ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት መስራች አገር ናት። በምዕራብ አፍሪካም ሆነ በአፍሪካ በጠቅላላ ትልቅ ተጽዕኖ አላት። በተጨማሪም እንደ ኤኮዋስ ያሉ የምዕራብ አፍሪካ የትብብር ድርጅቶች መሥራች ናች። ከ1970ዎቹ እ.ኤ.አ. ጀምሮ ናይጄሪያ ዋና የነዳች አምራች ስትሆን የኦፔክ አባል ሀገር ናት። በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ናይጄሪያውያን በኢኮኖሚ ችግር ምክንያት ወደ አውሮፓ፣ ሰሜን አሜሪካ እና አውስትራሊያ ተሰድደዋል። ከአንድ ሚሊዮን የሚበልጡ ናይጄሪያውያን በአሜሪካን እንደ ሚኖሩ ይገመታል። \n \nጥያቄ: የናይጄሪያ ሴኔት ስንት መቀመጫዎች አሉት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 109 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየጥምቀት በዓል በክርስትና ኃይማኖት ተከታዮች በተለይም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ ኢየሱስ ክርስቶስ በ፴ ዓ/ም በፈለገ ዮርዳኖስ በመጥምቁ ዮሐንስ እጅ በዮርዳኖስ ባሕር የተጠመቀበትን ዕለት የሚያስታውሰው፣ ኤጲፋንያ በመባልም የሚታወቀው ደማቅ በዓል ነው። መገለጥ፣ መታየት ማለት ነው። በአገራችን፣ ጥር ፲ ቀን፣ በከተራ፣ በገጠር ወራጅ ውሃ የሚከተርበት፣ ታቦታት ከየአቢያተ ክርስቲያናቱ በዓሉ ወደሚከበርበት ቦታ በምዕመናን ታጅበው እየዘመሩ ይሄዳሉ። እዚያም በየተዘጋጀው ድንኳን እንዲያርፉ ተደርጎ ሌሊቱን እዛው ያሳልፋሉ።በከተሞች ግን ሰው ሰራሽ ግድብ ይሰራል። ጥር ፲፩ ቀን የጥምቀት ዕለት፤ በገጠር፣ ጎኅ ሲቀድ ምእመናን እዚያው በድንኳኑ ዙሪያ አስቀድሰው ሲጨርሱ በካህናት መሪነት ሁሉም ወደከተራው ያመራና ውሃውም ተባርኮ ሕዝቡ ይረጫል። «ተጠምቀ ሰማያዊ በእደ መሬታዊ፤ ሰማያዊው በመሬታዊው እጅ ተጠመቀ» የሚለው የዕለቱ ቀለም በሊቃውንቱ አንደበት በያሬዳዊ ዜማ ጎልቶ ይሰማል። ከዚህ ሥነ ሥርዓት በኋላ በመቋሚያ፣ በከበሮና በጽናፅል በሚታጀብ ኃይማኖታዊ ዝማሬ፣ ወንዱ በሆታ፤ ሴቱ በእልልታ፤ ካህኑ በሃሌታ ታቦተ ሕጉን አጅበው፣ እንደያመጣጣቸው ወደየ ቤተክርሲያናቸው ይመለሳሉ። በየዓመቱ በመላ ኢትዮጵያ የሚከበረው የጥምቀት በዓል፣ ታቦታት ከመንበራቸው ወጥተው፣ በየጥምቀተ ባሕሩ የሚከበሩ በመኾናቸው፣ ሀገሬውን ብቻ ሳይሆን ዓለም አቀፋዊ መስህብ በመፍጠሩ፣ ቱሪስቶችን መሳቡ አልቀረም። ጥቁርና ነጭ፣ ቀይና ብጫ ያለም ዘር፣ ከአዲስ አበባ እስከ ላሊበላ፣ ከአክሱም እስከ ጎንደር በሁሉም ሥፍራዎች በዚሁ ዓይነት ደምቆ ይከበራል። የምእመናኑም ሆነ የካህናትና ዲያቆናት አለባበስ ፍፁም በሚማርክ ባህላዊ አልባሳት የተዋበ በመሆኑ ከውጭም ሆነ ከአገር ውስጥ ለሚመጡ ጎብኚዎች ሁል ጊዜ አዲስ ነው። ሊቃውንቱ እንደሚናገሩት፣ ዘመነ አስተርእዮ የሚባለው፣ ከጥር ፲፩ ቀን ጀምሮ እስከ ጾመ ነነዌ ያለው ጊዜ ነው። በዚህ ጊዜ ውስጥ አምላክ ሰው ሆኖ በሥጋ መገለጡ፣ በዮርዳኖስ በተጠመቀ ጊዜ የአንድነትና የሦስትነት ምሥጢር መታወቁ፣ በቃና ዘገሊላ በተደረገው ሠርግ ላይ የመጀመሪያው ተዐምር በመፈጸሙ፣ አምላካዊ ኃይሉ መገለጡ፣ እየታሰበ ምስጋና ይቀርባል። ይህ ሁነት ኢትዮጵያ ብሂልን ከባህል ጋር አዛምዳ ከሌላው የክርስቲያን ዓለም በተለየ አከባበር በዓሉን ማክበሯ፣ አያሌ ቱሪስቶችን ለመሳብ አስችሏታል። \n \nጥያቄ: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የት ተጠመቀ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ፈለገ ዮርዳኖስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሺስቶሶሚሲስ ሺስሰቶሶሚያሲስ (ቢልሃርዚያ እና ካታያማ ትኩሳት በመባል ይታወቃል፡፡) በሽታው የሚተላለፈው ጥገኛ ትላትሎች በሆነው የ ሺስቶሶማ የህዋስ አይነት ነው፡፡ የ ሽንት መተላለፊያ ወይም አንጀት ሊያጠቃ ይችላል። የህመሙ ምልክት የሆድ ህመም፣ ተቅማጥ፣ ደም የተቀላቀለበት ሰገራ ወይም በሽንት ላይ ደም መታየትን ያጠቃልላል። ለረጅም ጊዜ ህመሙ የቆየበት ሰው የጉበት ህመም፣ የኩላሊት ስራ ማቆም፣ መሃንነት ፣ ወይም የፊኛ ካንሰር ሊያስከትብ ይችላል፡፡ በልጆች ላይ ዝቅተኛ እድገትና የመማር ችግር ሊያስከትል ይችላል። ቢልሃርዝያ በሽታው የሚሰራጨው ትላትሎቹ ያሉበት ውሀ ላይ በሚፈጠር የቆዳ ንክኪ ነው። እነዚህ ትላትሎች የሚመነጩት ከተበከሉ ቀንድ አውጣዎች ነው፡፡ ይህ በሽታ በታዳጊ ሀገራት በሚነኙ ታዳጊዎች ላይ የተለመደ ሲሆን ምክንያቱም ልጆቹ በተበከለ ውሃ የመጫወታቸው አጋጣሚ ሰፊ በመሆኑ ነው፡፡ ሌላው ደግሞ በእለት ከእለት ስራ አማካኝነት ማለትም ገበሬዎች፣ አሳ አጥማጆችና ሌሎች የተበከለውን ውሀ የሚጠቀሙ ሰዎች የበሽታው ስጋት የሚያጠቃልላቸው ቡድኖች ናቸው። ሄልመንት በሽታዎች በሚባለው ቡድን ውስጥ ይጠቃለላሉ። ምርመመራው የሚደረገው የትሉን እንቁላሎች በሽንት ወይም ሰገራ ላይ በመመርመር ነው፡፡ በደም ላይ ፀረ እንግዳ አካል በመፈለግ ማረጋገጥም ይቻላል። በሽታውን የመከላከያ መንገድ ንፁህ ውህ አቅርቦትን ማሻሻልና የቀንድኣውጣ ቊጥርን መቀነስ ነው፡፡ ሲስቶሶሚያሲስ በዓለም ላይ ወደ 210 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ያጠቃል፣ እንዲሁም የሚገመተው ከ 12 000 እስከ 200,000 የሚሆነው ሕዝብ በአመት ውስጥ ይሞታል ተብሎ ይገመታል፡፡ በሽታው በስፋት የሚታየው በ አፍሪካ ፣ እንዲሁም በ እስያ ና ደቡም አሜሪካ ነው። ወደ 700 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ፣ ከ70 በላይ ሃገራት፣ በሽታው በስፋት በተሰራጨበት አካባቢ ይኖራል፡፡ ሲስቶሶሚሲሰ ከወባ ወይም ማላሪያ ቀፅሎ በሁለተኛነት ያለ፣ እንደ ትላትል ትልቅ የኢኮኖሚ ተፅእኖ ያለው በሽታ ነው። ከጥንት ጀምሮ እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ፣ ሲስቶሶሚሲሰ የ በሽንት ውስጥ ያለ ደም ምልክት የሚታየው በስሕተት እንደ የወንድ አይነት ወር አበባ እየተባለ በ ግብፅ እናም ለወንዶች ልጆች እንደ rite of የአምልኮ መተላለፊያ ተደርጎ ይታይ ነበር፡፡ የሚመደበው ችላ ከተባሉት የትሮፒካል በሽታ ስር ነው። \n \nጥያቄ: የቪስቶሶሚሲስ በሽታ በምን ሕዋስ አማካኝነት ይተላለፋል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሺስቶሶማ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበኢትዮጵያ የሚገኙ በርካታ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች መንግሥት ተገቢውን ክትትል እያደረገ ባለመሆኑና ኩባንያዎች በክህሎት የበቁ ኢትዮጵያዊያን በሥልጠና ዕገዛ ባለማድረጋቸው ምክንያት፣ አብዛኛዎቹ በሲሚንቶ ፋብሪካዎች ተቀጥረው የሚሠሩት ሠራተኞች የውጭ ዜጎች መሆናቸው ተገለጸ፡፡ በኢትዮጵያ ምርት በማምረትና በግንባታ ላይ የሚገኙትን ጨምሮ 17 የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የሚገኙ ሲሆን፣ 12ቱ በተለያየ የማምረት መጠን ላይ ይገኛሉ፡፡ ይሁን እንጂ በበርካታ ፋብሪካዎች በተለይም ግዙፍ በሚባሉት ዳንጎት፣ ሙገርና ደርባ ኩባንያዎች ውስጥ የውጭ ዜጎች የማኔጅመንቱንና ቴክኒካል ሥራውን በበላይነት እንደሚይዙ የኬሚካልና ኮንስትራክሽን ግብዓቶች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ ስምረት ግርማ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ በዚህም በሥራ ላይ በሚገኙት የሲሚንቶ ፋብሪካዎች በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ የውጭ ዜጎች እንዳሉ የገለጹት ምክትል ዳይሬክተሯ፣ ኢትዮጵያውያን እየሠሩባቸው ያሉ ዘርፎችም ቢሆን በዝቅተኛ ዕርከንና በጉልበት ሥራ ላይ የሚገኙ ስለመሆኑ ተናግረዋል፡፡ \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ከሚገኙ ግዙፍ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የማኔጅመንቱ እና ቴክኒካል ሥራው በከፍተኛ ሁኔታ በውጪ ሀገር ዜጎች የተያዘባቸው ኩባንያዎች የትኞቹ ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ዳንጎት፣ ሙገርና ደርባ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nከ1881 እስከ 1905 ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ በአፍሪካ ይዞታቸውን እያሰፉ የነበሩትን የአውሮፖ ሀይሎችን ጥቃት በመከላከል ኢትዮጵያን በስርዓት አስተዳድረዋል፡፡ በዚያን ጊዜ ጣልያን ኤርትራን በከፊል ቅኝ ገዝታ የነበረችበትና በ1880ዎቹ አጋማሽ ላይ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ቅኝ ገዝታት የነበረችበት ጊዜ ስለነበር ከሌሎች አውሮፖ አገራት በበለጠ ለኢትዮጵያ አስጊ ነበረች፡፡ በ1880 ግን እስከዛሬ ድረስ ዝነኛ በሆነው የአድዋ ጦርነት ኢትዮጵያ ጣልያንን ድል በማድረግ በአፍሪካ የባእዳን ገዥ ሀይሎችን ያሸነፈች ብቸኛዋ ሀገር ሆናለች፡፡ ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ የቅኝ ገዥዎችን ወረራና መስፋፋት በመመከትና ድልን በመቀዳጀት ለኢትዮጵያዉያን ብቻ ሳይሆን በባርነት ቀንበር ተጠምደዉ ለሚማቅቁ የመላዉ ዓለም ህዝቦች ከፍተኛ ክብርና ተስፋን አጎናጥፈዋል በ1908 የዳግማዊ ሚኒሊክ ልጅ የሆኑትን እቴጌ ዘውዲቱ ስልጣን ያዙ ፡፡ የሳቸው የቅርብ የስጋ ዘመድ የነበሩት ራስ ተፈሪ መኮንንም ሞግዚት አስተዳደርና ወራሽ ሆነው ተሹመዋል፡፡ እቴጌ ዘውዲቱ በ1922 ሲሞቱ ተተኪያቸው ዐጼ ሀይለስላሴ ስልጣን ያዙ ፡፡ ነገር ግን በ1928 ዓ.ም የጣልያን ሀይሎች ኢትዮጵያን ለአጭር ጊዜ ወረው ሲቆጣጠሩ ግዛታቸው ተቋርጦ ነበር፡፡ \n \nጥያቄ: ዳግማዊ ሚኒሊክ ኢትዮጵያን ያስተዳደሩት ከመቼ እስከ መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከ1881 እስከ 1905 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nፋሲለደስ ዓፄ ፋሲለደስ ወይም ዓፄ ፋሲል (የዙፋን ስማቸው ዓለም ሰገድ) ከአባታቸው አፄ ሱሰኒዮስ እና እናታቸው ልዕልት ስልጣነ ምገሴ በመገዛዝ፣ ሸዋ ህዳር 10፣ 1603 (እ.ኤ.አ) ተወለዱ። የነገሱበትም ዘመን ከ1632 እስከ ጥቅምት 18, 1667 (እ.ኤ.አ) ነበር። በስረፀ ክርስቶስ በተመራው አመፅ ምክንያት በ1630 ፋሲለደስ ለንግስና ቢበቃም፣ ዘውዱን ግን እስከ 1632 አልጫነም ነበር። ሲመተ ንግስናው በ1632 እንደተገባደደ የመጀመሪያው ስራው የተዋህዶ ቤ/ክርስቲያንን የቀድሞው ቁመና መመለስና የካቶሊኮችን መሬት በመቀማት ከደንካዝ በማባረር በፍሪሞና እንዲወሰኑ ማድረግ ነበር። ወዲያውም በማከታተል ከግብፅ አገር አዲስ ጳጳስ እንዲላክለት በማድረግ በአባቱ ዘመን እንዲደበዝዝ ተደርጎ የነበረውን የግብፅና ኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት ግንኙነት እንዲጸና አደረገ። በኬኒያ የሚገኘው የሞምባሳ ወደብ በፖርቱጋሎች መደብደቡን ሲሰማ፣ የሮማው ፓፓ ከበስትጀርባው ያለበት ሴራ ነው በማለት በምድሩ የነበሩትን የካቶሊክ ጀስዊቶች በመሰብሰብ አባረራቸው። አፄ ፋሲል አዘዞ ተብላ በምትታወቀው ከጎንደር ከተማ 5 ማይል ርቃ በምትገኘው ከተማ ጥቅምት18፣1667 እ.ኤ.አ. (ጥቅምት 10፣ 1660) ከዚህ አለም በሞት ተለዩ። አስከሬናቸውም የአገሪቱ መላ ህዝብ ባዘነበት ሁኔታ በቅዱስ እስጢፋኖስ ገዳም፣ ጣና ሃይቅ ውስጥ ደጋ ደሴት ተብላ በምትታወቀው ደሴት የዘላለም እረፍት አገኘ። \n \nጥያቄ: አፄ ፋሲል በየትኛው ቤተ-ክርስቲያን ስርአተ ቀብራቸው ተፈፀመ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በቅዱስ እስጢፋኖስ ገዳም፣ ጣና ሃይቅ ውስጥ ደጋ ደሴት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአፄ ዘርአ ያዕቆብ አጼ ዘርአ ያዕቆብ በዘውድ ስማቸው ቆስጠንጥንዮስ ከአባታቸው ቀዳማዊ ዳዊት እና ከእናታቸው ንግስት ክብረ እግዚእ በ1399 እ.ኤ.አ. ከአዋሽ ወንዝ አጠቀብ ትገኝ በነበረው ትልቅ ተብላ በምትጠራው መንደር የድሮውፈተገር ክፍለ ሐገር ተወለዱ(ከቀኝ ያለውን ካርታ ይመልከቱ) ። የነገሡበትም ዘመን 1434 - 1468 እ.ኤ.አ. ነበር። ያረፉትም በደጋ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ ነው። የዘርዓ ያዕቆብ አባት ቀዳማዊ ዳዊት ባረፉ ጊዜ፣ እንደ ጥንቱ የኢትዮጵያ ባህል ወግ መሰረት፣ ታላቅ ወንድማቸው የነበሩት ቀዳማዊ ቴወድሮስ በ1414 ሲነግሱ ታናሽ ወንድማቸውን በግዞት ወደ አምባ ግሽን እንዲሄድ አደረጉ። አጼ ዘርዓ ያእቆብ ቆየት ብለው በጻፉት መጽሀፈ ብርሃን በተሰኘው ድርሰታቸው መሰረት እስከ ነገሱበት ሰኔ 20 ፣ 1434 ዓ.ም. ድረስ በግዞት ግሸን ተራራ (አምባ ግሸን) ላይ ለሚቀጥሉት 20 አመታት በእስር ኖሩ። ሆኖም ግን በግዞት እያሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ የደጋፊያቸው መጠን እየበዛ ሄደ። በነዚህ አመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ሁኔታ ከዓመት ወደ ዓመት እይተበላሸ ሂዶ በመጨረሻ ከአምባው ላይ ለሹመት ሲወርዱ አገሪቱ በእርስበርስ ሽኩቻ እየታመሰች፣ በሃይማኖት በኩልም መከፋፈል ተፈጥሮ የውጭ ሀይሎችም ከነገ ዛሬ አጠቁን እየተባለ ይሚፈራበት ሁኔታ ገጠመው። የወደፊቱ ንጉስ ብዙ እድሜውን ያሳለፈው ከሰው ተለይቶ አምባ ላይ ስለነበር፣ የዲፕሎማሲ ጥቅሙ አልተረዳውም ነበር። ይልቁኑ ፊት ለፊት የተጋረጡትን የሃገሪቱን ችግሮች በሚያስፈራ ድፍረት እና ምንም በማያወላዳ ጽናት ተጋፈጠው። ዓፄ ዘርአ ያእቆብ ንጉስ ከሆኑ በኋላ ንግስት እሌኒን በ1434 አገቡ፣ ከዚያም በ1436 ዘውዳቸውን ጫኑ። በ1442 በሰንበት ላይ ተነስቶ የነበረውን የቤተክርስቲያን ክፍፍል ለማብረድ ቢችሉም እስከ 1450 ነገሩ ሲሰክን ቆይቱ በደብረ ምጥማቅ ጉባኤ (ተጉለት) ፣ የግብጾቹ ጳጳሳተ በተገኙበት ችግሩን ሊፈቱ ችለዋል ። ሌላው በዘመናቸው የተከሰተው ሃይማኖታዊ ንቅናቄ የደቀ እስጢፋ ወገኖች እምነት ነው። እነዚህ እስጢፋኖስ የተባለ መነኩሴ ባስተማራቸው መሰረት ለመስቀል መስገድና ለስእል አድኅኖ ለድንግል ማርያም መስገድ አይገባም የሚሉ ነበሩ።ተከራክረው አጼ ዘርዓ ያዕቆብ አሸንፈዋል። በ1445 እና ከዚያ በኋላ በተነሱ ጦርነቶች ላይ በመሳተፍ ሁሉን በድል በማጠናቀው ግዛታቸውን ያሁኒቷን ሶማልያን ሁሉ ያቅፍ ነበር። በ1456 ዓ.ም አጼ ዘርዓ ያዕቆብ በነበሩበት ቦታ ታላቅ ብርሃን ስለታየ የነበሩበትን ቦታ ደብረ ብርሃን በማለት የሃገሪቱ ዋና ከተማ አድርገው ቆርቁረዋል። እስከ እለት ህልፈታቸውም ደብረ ብርሃን የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ነበረች።ኢትዮጵያዊ መንፈሳዊ ፈላስፋ። አጼ ዘርአ ያዕቆብ በጦር ውሎአቸው ብቻ ሳይሆን የሚታወቁት፣ ከ 20 በላይ መጻህፍትንም በመድረስና ለትውልድ በማቅረብ ጭምርም ነው። \n \nጥያቄ: የአጼ ዘርአ ያዕቆብ የዘውድ ስማቸው ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ቆስጠንጥንዮስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበ596 ዓ.ም. በጃፓን 17 አንቀጽ ያለ ሕገ መንግሥት በልዑል ሾታኩ እንደተጻፈ ይታመናል። እንዲሁም በ614 ዓ.ም. ከነቢዩ መሐመድ የወጣው የመዲና ሕገ መንግሥት ዕጅግ ጥንታዊ ምሳሌ ነው። በዌልስ በ940 ዓ.ም. አካባቢ ንጉስ ህወል ዳ ሕጎቹን ጻፉ። በዛሬው ሩሲያ ደግሞ የክዬቭ ታላቅ መስፍን ያሮስላቭ ጥበበኛው ፕራቭዳ ያሮስላቫ የተባለውን ሕገ መንግሥት በ1009 ዓ.ም. ያህል ሠሩ። ይህ ሕግ በ1046 ታድሶ በኪዬቭ ሩስ በሙሉ ህጝ ሆነ። በስሜን አሜሪካ የኖሩ ኗሪ ጎሣ ሆደነሾኒ 'የአፈ ቃል' ሕገ መንግሥት «ጋያነሸጎዋ» የነበራችው ከ1080-1140 ዓ.ም. አካባቢ ጀምሮ እንደሆነ ይታመናል። ይህ ሕግ በከፊል ለአሜሪካ ሕገ መንግሥት ተጽእኖ እንደነበረው ይታመናልና የአሜሪካ ምክር ቤት በ1981 ዓ.ም. ይህንን ግንዛቤ አስታወቀ። በእንግሊዝ አገር በ1092 ዓ.ም. ንጉስ 1 ሄንሪ የነጻነት ሥርአት የተባለውን ሰነድ አዋጀ። ይህ መጀመርያ የንጉሱን ሥልጣን ወሰኖ ንጉሡ ለቤተ ካህናትና ለቤተ መሳፍንት ወገኖች የሚገባውን እንቅብቃቤ ገለጸ። ይህም መሰረት በመኳንንቱ ሲዘረጋ በ1207 ዓ.ም. የእንግሊዝ ንጉሱን ዮሃንስ (ጆን) ማግና ካርታ («ታላቅ ሥርዓት») የሚባለውን ሰነድ እንዲፈርሙት አስገደዱዋቸው። ከዚሁ መሃል ቁም ነገር የሆነው ንጉሡ ያለ ሕጋዊ ሂደት ማንንም ሰው እንዳይገድሉ፣ ከአገር እንዳያሳደዱ፣ ወይም እስር ቤት እንዳያስገቡ ከለከላቸው። በዚያ ወቅት ያ ሰነድ በእንግሊዝ አገር የነጻነት መሠረት ሆነ። በ1212 እና 1222 ዓ.ም. መካከል አንድ የሳቅሰን አስተዳዳሪ አይከ ቮን ረፕጎቭ ያቀነባበረው ሕግጋት ሳቅሰንሽፒግል በአንዳንድ ጀርመን ክፍላገር እስከ 1892 ዓ.ም. ድረስ ላይኛ ሕገ መንግሥት ሆነ። በ1228 ዓ.ም. ሱንዲያታ ከይታ ማሊ መንግሥትን ለማወሐድ የ'አፈ ቃል' ሕገ መንግሥት አወጡ። ይህ ሕግ 'ኩሩካን ፉጋ' ተብሎ ነበር። \n \nጥያቄ: በ596 ዓ.ም. በጃፓን በልዑል ሾታኩ እንደተጻፈ የሚታመነው ሕገ መንግሥት ስንት አንቀጽ ነበረው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 17 አንቀጽ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nእንደ ፕላቶ ዘገባ፣ የሶቅራጠስ እናት ፌናርት የተሰኘች አዋላጅ ነበረች። ሶቅራጠስ እናቱ ሴቶች ልጅ እንዲወልዱ እንደምትረዳ ሁሉ እርሱ ደግሞ ሰዎች አዳዲስ አሳቦችን እንዲወልዱ ለመርዳት እንደሚሞክር መናገሩ ይጠቀሳል። የሶቅራጠስ አባት ድንጋይ አናጢ የነበረው ሶፍሮኒስከስ እንደነበር ይጠቀሳል። ሶቅራጠስ በዘመኑ ድሃ የነበረ ሲሆን ለዚህ ምክንያቱ ከገንዘብ ይልቅ እውቀት ይበልጣል ብሎ ስለሚያምን ነበር። ሶቅራጠስ ስራ እንደማይሰራና በፍልስፍና ሃሳብና ክርክር ጊዜውን እንደሚያሳልፍ ፕላቶ ዘግቦት ይገኛል። ዛንቲፕ የተሰኘች ከርሱ በዕድሜ በጣም የምታንስ ሴትን አግብቶ ሶስት ልጆች እንደነበሩት ፕላቶ ጽፏል። ሶቅራጠስ 70 ዓመት በሞላው ጊዜ የአቴና መንግስት እንዲያዝና ለፍርድ እንዲቀርብ አደረገ። በወቅቱ ሁለት ክሶች ሲቀርቡበት አንደኛው \"በትምህርትህ ወጣቱን አበላሽተሃል\" የሚል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ \"ለግሪክ ጣዖታት አልተገዛህም\" የሚል ነበር። እንደ ፕላቶ ዘገባ ግን ሶቅራጠስ የግሪክ ጣኦታት አምላኪ ነበር። በአንድ አንድ ተመራማርወች ዘንድ የአቴንስ መንግስት ያቀረባቸው ክሶች በውሸት ላይ የተመሰረቱ ናቸው። የሆኖ ሆኖ፣ ክሪቶ የተሰኘው የፈላስፋው ጓደኛ ለጠባቂወቹ ጉቦ በመስጠት እንዲያመልጥ ሁኔታውን አመቻችቶ ነበር። ሶቅራጠስ ግን እምቢ በማለት ቀረ እንጂ አላመለጠም። ሶቅራጠስ ለፍርድ በቀረበ ጊዜ ሰፊ የሆነ የመከላከያ ክርክር በማቅረብ የአቴናን መንግስት ክስ ውድቅ ለማደርግ ሞክሯል። ከዚህ በኋላ ዳኞቹ ምን አይነት ቅጣት እንዲበይኑበት እንደሚፈልግ ሲጠይቁት፣ ለአቴና ህብረተሰብ ካበረከተው ጥሩ ተግባራቱ አንጻር በቀሪው ዘመኑ ሁሉ ነጻ እራት እንዲያመጡለት ተናገረ። ነገር ግን ፍርድ ቤቱ ወይ በቅጣት እንዲለቀቅ ወይንም ደግሞ እንዲገደል የእጅ ምርጫ አደረገ። ውጤቱም ሶቅራጠስ እንዲገደል የሚል ሆነ። ይሁንና ሶቅራጠስ ሞትን አይፈራም ነበር። ሞቱን ለማስቀረት ይቅርታም ሆነ ሌላ ማባበያ አላቀረበም። በርሱ ሥነ ምግባር መሰረት ላመነበት ነገር እስከመጨረሻ መቆሙ ሰናይ ድርጊት ነበር። ስለሆነም ሄምሎክ የተሰኘ መርዝ ጠጥቶ እንዲሞት ስለታዘዘ፣ መርዙን በመጠጣት አለፈ። \n \nጥያቄ: ሶቅራጥስ ደሀ የነበረበት ምክንያት ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከገንዘብ ይልቅ እውቀት ይበልጣል ብሎ ስለሚያምን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዩጋንዳ ዩጋንዳ ሪፐብሊክ (ወይም ዑጋንዳ) በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። በኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ ይዋሰናል። የዩጋንዳ ሰም የመጣው ከቡጋንዳ መንግሥት ነው። ከአረቦችና አውሮፓውያን በ1800ቹ ከመድረሳቸው በፊት ብዙ የሚታወቅ ነገር አልነበረም። በ15ተኛ መቶ ክፍለ-ዘመን ችዌዚ የተባለውን መንግስት በአፈ ታሪክ ይገኛል። አረቦችና አውሮፓውያን በ19ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሲደርሱ ብዙ መንግሥቶች በቦታው ነበሩ። እነዚህም በንዮሮ ፣ ቡሶጋ ፣ ቡጋንዳ ፣ ቶሮ እና አንኮልን ያጠቃልላሉ። ከ1894 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በታላቁ ብሪታን ስትመራ ነበር። የተለያዩ ቦታዎች ከተዋሃዱ በኋላ ዩጋንዳ በ1914 እ.ኤ.አ. ቅርጿን ያዘች። በ1966 እ.ኤ.አ. ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ ሕገ-መንግሥቱን አፍርሰው እራሳቸውን ፕሬዝዳንት አደረጉ። በ1971 እ.ኤ.አ. ኢዲ አሚን ሀገሩን መምራት ጀመሩ። የኢዲ አሚን አመራር 300,000 የሚገመቱ ዩጋንዳውያንን አስጨርሷል። በ1979 እ.ኤ.አ. የታንዛንያ ኃይሎች ኢዲ አሚንን ከሥልጣን ያስወግዳሉ። ሚልተን ኦቦቴ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ግን በ1985 እ.ኤ.አ. እንደገና ይወርዳሉ። ያሁኑ ፕሬዝዳንት ዮወሪ ሙሴቪኒ ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ናቸው። ፕሬዝዳነንቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይመርጣሉ። ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሎ ሲባምቢ ናቸው። ዩጋንዳ በመሬት የተቆለፈች ብትሆንም ታላላቅ የውሃ አካላት አሉ። ከነዚህ ውስጥም ቪክቶሪያ ሐይቅ፣ አልበርት ሐይቅ፣ ክዮጋ ሐይቅ እና ኤድዋርድ ሐይቅ ይዘረዘራሉ። ታላላቅ ከተማዎች በቪክቶሪያ ሐይቅ አቅራቢያ ይገኛሉ። እነዚህም ካምፓላንና እንትቤን ያጠቃልላል። ዩጋንዳ በ70 ወረዳዎች የተከፋፈለች ስትሆን እነዚህም በአራት አመራር ክልሎች ውስጥ ናቸው። አራቱ አመራር ክልሎች ሰሜናዊ ፣ ምሥራቃዊ ፣ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ይባላሉ። ወረዳዎቹ በዋና ከተማዎቻቸው ነው የሚሰየሙት። በዩጋንዳ ውስጥ የመዳብ እና ነጭ ብረት ክምችቶት አሉ። ግብርና ዋናው የኤኮኖሚ ሴክተር ነው። ከ80 በመቶ በላዩ የስራ ኃይል በግብርና ነው የተሰማራው። ቡና ዋናው የኤክስፖርት ትርፍ ምንጭ ነው። ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግሥቱ ከሌሎች ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን በኢዲ አሚን ጊዜ የወደቀውን ኤኮኖሚ ለማንሳት ተጣጥሯል። ዩጋንዳ ለብዙ ብሔረሰቦች ቤት ነው። ከነዚህ ውስጥ ግን አንድ ትልቁን ሕዝብ ብዛት የሚወክል የለም። 40 አካባቢ የሚሆኑ ቋንቋዎች ባሁኑ ጊዜ ይነገራሉ። ከነጻነት በኋላ እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተደርጓል። ብዙ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ ሉጋንዳ ሲሆን የአቴሶ ቋንቋ በሁለተኛነት ይከተላል። ኪስዋሂሊ ዋናው የንግድ ቋንቋ ነው። የዩጋንዳ የትምህርት ስርዐት የሰባት ዓመት መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፣ ስድስት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና ከ3 እስከ 5 ዓመት ከሁለተኛ ደረጃ በኃላ ትምህርት ያጠቃልላል። \n \nጥያቄ: ዩጋንዳ እ.ኤ.አ. ከ1894 ጀምሮ ስትገዛ የነበረው በማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በታላቁ ብሪታን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሚያዝያ ፴ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፵ ኛው ዕለትና የወርኅ ፀደይ (በልግ) ፴፭ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ ሉቃስ ፻፳፮ ቀናት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመን ማርቆስ ደግሞ ፻፳፭ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፰፻፸፬ ዓ/ም - እምባቦ በሚባል ሥፍራ የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ ሠራዊት እና የጎጃም ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ሠራዊት ውጊያ ገጥሞ ድሉ የንጉሥ ምኒልክ ሲሆን፣ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ተማረኩ። ፲፰፻፺ ዓ/ም - በጣልያ አበጋዙ ባቫ-በካሪስ ብዙ መቶ ሰልፈኞች በመድፍ ገደላቸው። ፲፱፻፳፭ ዓ/ም - የሕንድ አባት በሚል ቅጽል ስም የሚታወቀው ሞሃንድራስ ካራምቻንድ ጋንዲበአገሩ የእንግሊዝን አስተዳደር በመቃወም የሃያ አንድ ቀን የ'ረሀብ አድማ' ጀመረ። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - በአውሮፓ የሁለተኛው የዓለም ጦርነትን ማክተም ምክንያት በማድረግ 'ሴቲፍ' በተባለች የአልጄሪያ ከተማ በተካሄደ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ፻፫ አውሮፓውያን በመሞታቸው፣ የገዢው የፈረንሳይ መንግሥት ፖሊሶች እና ወታደሮች ባካሄዱት ጨካኝ በቀላ እስከ ስድስት ሺ አልጄሪያውያን ተጨፍጭፈዋል። የዚህ አረመኔያዊ ድርጊት ሳቢያ በመላው የሰሜን አፍሪቃ የፈረንሳይን ቅኝ ገዢነት ማክተሚያ አብሳሪ እንደሆነ ታሪካውያን ይዘግባሉ። ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - በሩሲያኖች የተገነባው የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ዶክቶር ምናሴ ኃይሌ እራሳቸውን ከሥልጣናቸው አስወገዱ። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - አቶ ለገሰ ዜናዊ አስረስ፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር አድዋ ላይ ተወለዱ። \n \nጥያቄ: የእንግሊዝን አስተዳደር በመቃወም ሞሃንድራስ ካራምቻንድ ጋንዲ ያደረገው ድርጊት ምን ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የሃያ አንድ ቀን የ'ረሀብ አድማ' ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኬንያ የኬንያ ሪፐብሊክ በምስራቅ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በሰሜን ከኢትዮጵያ፣ በሰሜን-ምስራቅ ከሶማሊያ፣ በደቡብ ከታንዛኒያ፣ በምስራቅ ከዩጋንዳ፣ በስሜን-ምዕራብ ከደቡብ ሱዳን፣ በደቡብ-ምስራቅ ከሕንድ ውቅያኖስ ጋር ድንበር ትጋራለች። አውሮፓውያን አካባቢውን ማሰስ የጀመሩት ከ፲፱ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ሲሆን የብሪታንያ መንግሥት የምሥራቅ አፍሪካ ፕሮቴክቶሬትን በ1895 እ.ኤ.አ. አቋቁሟል። ይህ ፕሮቴክቶሬት በ1920 እ.ኤ.አ. የኬንያ ግዛት ተብሎ ተሰይሟል። ነፃ የኬንያ ሪፐብሊክ በዲሴምበር 1963 እ.ኤ.አ. ታወጀ። የኬንያ ስም የመጣው በአፍሪካ በከፍታ ሁለተኛ ከሆነው ከደብረ ኬንያ ተራራ ነው። በዚሁ ተራራ ዙሪያ የሚኖሩት ነገዶች ስሙን «ኪኛ» (በካምባኛ)፣ «ኪሪማራ» (በአመሩኛ)፣ «ኪሬኛ» (በኤምቡኛ)፣ «ኪሪኛጋ» (በኪኩዩ)፣ ወይም «ኬሪ» (በመዓሳይኛ) ይሉታል። የነዚህ ስሞች ሁሉ ትርጉሞች «ቡራቡሬ» ሲሆኑ ይህም ደግሞ «ሰጎን» ማለት ነው፤ አመዳይ ያለበት የተራራው ጫፍ ለተመልካች ቡራቡሬ ወንድ ሰጎንን ያሳስባልና። በኦገስት 2010 እ.ኤ.አ. በተካሄደ ውሳኔ ሕዝብ መሠረት ከብሪታንያ የተወረሰው ሕገ መንግሥት በአዲስ ሕገ መንግሥት ተለውጧል። በአሁኑ ጊዜ ኬንያ በ፵፯ ካውንቲዎች (የአስተዳደር ክፍሎች) ተዋቅራለች። እነዚህ ካውንቲዎች በሕዝብ በተመረጡ ሰዎች የሚስተዳደሩ ሲሆን በናይሮቢ ከሚገኘው ማዕከላዊ መንግሥት በነፃነት ይንቀሳቀሳሉ። የኬንያ ዋና ከተማ እና ትልቋ ከተማ ናይሮቢ ናት። የኬንያ ኢኮኖሚ በምሥራቅና መካከለኛው አፍሪቃ በጂ.ዲ.ፒ. ትልቁ ነው። ግብርና በአገሪቱ ትልቅ የሥራ ዘርፍ ሲሆን ከኤክስፖርቶች መካከል ሻይ፣ ቡና እና ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ አበባዎች ይገኛሉ። እንዲሁም ቱሪስምና ፔትሮሊየም አቢይ ዘርፎች ናቸው። \n \nጥያቄ: ኬንያ በሰሜን በኩል የምትዋሰነው ከማን ጋር ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከኢትዮጵያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: የድንጋይ ዘመን አዳኞች በዚምባቡዌ ከስንት ዓመት በፊት ይኖሩ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከአምስት ሺህ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየሻይ ቅጠል ልማት ለማካሄድ ፈቃድ ወስዶ፣ ነገር ግን በሕገወጥ መንገድ ጣውላ ሲያመርት የተገኘው የህንዱ ኩባንያ ቬርዳንታ ሐርቨስት፣ አሁን ደግሞ በሕፃናት ጉልበት ብዝበዛ ተጠያቂ ሆነ፡፡ ቬርዳንታ ሐርቨስት ቀጥሮ ጉልበታቸውን ሲበዘብዝ ነበር የተባሉት አብዛኞቹ ሕፃናት ከሰባት ዓመት በታች እንደሆኑ፣ የተወሰኑት ደግሞ እስከ 15 ዓመት የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ 250 ሕፃናትን በመቅጠር ሲያሠራ መገኘቱን፣ ከጋምቤላ ክልል የተገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡ የጋምቤላ ክልል ማጃንግ ዞን፣ ጉደሬ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዮናስ ከፑምሳ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ቬርዳንታ ሐርቨስት ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ የሕፃናቱን ጉልበት ሲበዘብዝ ቆይቷል፡፡ ‹‹ሕፃናቱን ሲያሠራ ቢቆይም ቃል የገባውን ክፍያ በመቀነስ ሕፃናቱ ቅሬታቸውን ይዘው ወደኛ መጥተዋል፤›› በማለት አቶ ዮናስ ገልጸው፣ ‹‹ጉዳዩ በዞን ደረጃ እየታየ ነው፤›› በማለት ገልጸዋል፡፡ ‹‹የሕፃናቱ መብት መጠበቅ አለበት፡፡ እኛ ሕፃናት እንዲህ ያለ ሥራ መሥራት የለባቸውም የሚል አቋም ነው ያለን፤›› ብለው የህንዱ ኩባንያ የፈጸመውን ተግባር ኮንነዋል፡፡ ይህንን ሕገወጥ ተግባር የፈጸመውን ይህ ኩባንያ የሚወስድበት ዕርምጃ በቀጣይ እንደሚታወቅም አቶ ዮናስ አክለው ገልጸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ቬርዳንት ኸርቨስትያለ አግባብ በጣውላ ምርት ከመሰማራቱ በተጨማሪ በምን ጥፋት ተከሰሰ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በሕፃናት ጉልበት ብዝበዛ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nልዑል ራስ መኮንን የንጉሠ ነገሥቱ ዳግማዊ ምኒልክ ተወካይ ሆነው ሁለት ጊዜ የአውሮፓን አገሮች ጎብኝተዋል። በዚህ ጊዜ እሳቸው ኢጣሊያን ሲጎበኙ በነበረ ጊዜ የኢጣሊያ ጋዘጦች የውጫሌ ውልን በተመለከተ፤ «...በውጫሌ ውል ላይ ኢትዮጵያ የኢጣሊያን ጥገኝነት ተቀብላ ውል ከፈረመች በኋላ የጀርመን ንጉሠ ነገሥት ከኢትዮጵያ የሚላከውን ማንኛውንም ደብዳቤም ሆን ጉዳይ በኢጣሊያ መንግሥት በኩል መቀበል ሲገባቸው በቀጥታ ከምኒልክ የተጻፈውን ደብዳቤ ተቀብለዋል...» እያሉ የጻፉትን ራስ መኮንን ተቃውሞአቸውን ለኢጣሊያ መንግሥት ከነገሩ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የውሉን መበላሸት ለአጤ ምኒልክ አሳወቁ። ከኢጣሊያንም ጋር በተደረገውም ጦርነት ራስ መኮንን ፲፭ ሺህ እግረኛ ወታደሮች ይዘው ከምኒልክ እና ታላላቅ ጦር አዛዦች ጋር ዘምተዋል። በ፲፰፻፺፰ ዓ.ም መጀመሪያ ላይ በብርቱ ስለታመሙ ለኅክምና ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ጥር ፬ ቀን ከከተማቸው ከሐረር ተነሱ። ጥር ፱ቀን ቡርቃ ወንዝ አድረው የጥምቀትን በዓል አክብረው ከዋሉ በኋላ ሕመሙ ስለጸናባቸው ወደ ኋላ ተመልሰው ቁልቢ ገብተው በሐኪም ይታከሙ ጀመር። እዚሁም ሲታመሙ ከቆዩ በኋላ መጋቢት ፲፫ ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም ቁልቢ ላይ አርፈው ሐረር ላይ እሳቸው በተከሉት በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። ዐፄ ምኒልክም የአርባቸው ለቅሶ የሚለቀሰው አዲስ አበባ እንዲሆን ባዘዙት መሠረት፤ ሰኞ ሚያዝያ ፳፪ ቀን በአዲስ አበባና በዙሪያው ያሉት የየገዳማቱና የየአድባራቱ ካህናት የክርስቲያን የፍታት ጸሎት ተድርጎ በማግስቱም ማክሰኞ የጊዮርጊስ ዕለት ሚያዝያ ፳፫ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም በሰኢ ሜዳ ላይ ድንኳን ተተክሎ፤ መኳንንቱና ሠራዊቱ ተሰብስቦ የራስ መኮንን የማዕረግ ልብሳቸውና የራስ ወርቃቸው፤ ኒሻኖቻቸውና የጦር መሳሪያቸው ተይዞ ፈረስና በቅሏቸው በወርቅ እቃ ተጭነው በሠራዊቱ መካከል እየተመላለሱ ታላቅ ልቅሶ ተለቀሰላቸው። \n \nጥያቄ: ራስ መኮንን የዳግማዊ ምኒልክ ተወካይ በመሆን አውሮፓን የጎበኙት ስንት ጊዜ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሁለት ጊዜ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nለአጽዋማትና በዓላት ማውጫ ወሳኝ የሆነው ነጥብ መባጃ ሐመር ነው፡፡ መባጃ ሐመር መባጊያ ሐመር እየተባለም ይጠራል፡፡ መባጊያ ሐመር ሲሆን የበጋ መመላለሻ የሚል ትርጉም ይሰጣል፡፡ በሌላ በኩል መባጃ በራሱ ማቆያ፣ ማክረሚያ ተብሎ ይተረጎማል፡፡ ሐመር መርከብ፣ መጓጓዣ የሚለውን ትርጉም ያስገኛል፡፡ መባጃ ሐመር የመጥቅዕና የዕለታት ተውሳክ ድምር ሆኖ አጽዋማትና በዓላት የሚውሉበትን ቀን ያመለክታል፡፡ በሐመር የተመሰለውም አጽዋማትና በዓላት ወደ ላይና ወደታች የሚመላለሱበት ሥርዓት /መርከብ/ ስለሆነ ነው፡፡ በአጠቃላይ መባጃ ሐመር ማለት የአጽዋማትንና የበዓላትን መዋያ ወይም መግቢያ ቀን ለማወቅ የሚያገለግል ልዩ ቁጥር ማለት ነው፡፡ ከሰባቱ አጽዋማት መካከል አራቱ በመባጃ ሐመር መሠረት በየዓመቱ እየተቀያየሩ ወይም ቀመር እየተሠራላቸው የሚወጡ ሲሆን፣ ሦስቱ ግን ያለ መባጃ ሐመር በየዓመቱ በተመሳሳይ ወቅት ይባጃሉ፡፡ በመባጃ ሐመር የሚባጁት አራት አጽዋማት ዐቢይ ጾም፣ ጾመ ድኅነት፣ ጾመ ነነዌና ጾመ ሐዋርያት ሲሆኑ፣ ያለ ማባጃ ሐመር በየዓመቱ ቋሚ ጊዜ ይዘው የሚብቱት ሦስቱ አጽዋማት ደግሞ ጾመ ነቢያት፣ ጾመ ገሃድና ጾመ ማርያም /ፍልሰታ/ ናቸው፡፡ ከላይ በተመለከትነው መሠረት መባጃ ሐመር የአጽዋማትና የበዓላት ማስገኛ ልዩ ቁጥር ነው ካልን ቁጥሩ እንዴት እንደሚገኝ ማወቅ ያስፈልገናል፡፡ መባጃ ሐመርን ለማግኘት መጥቅዕንና በዓለ መጥቅዕ የዋለበትን ዕለት ተውሳክ እንደምራለን፡፡ \n \nጥያቄ: የአጽዋማትንና የበዓላትን መዋያ ወይም መግቢያ ቀን ለማወቅ የሚያገለግል ልዩ ቁጥር ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ መባጃ ሐመር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nጾመ ነቢያት በአራቱም ዘመናት ምን ጊዜም ኅዳር ዐሥራ አምስት እንዲጾም ተወስኗል፡፡ ጾመ ገሀድ የምትክ ጾም ነው፡፡ ይህ ጾም ዓርብንና ሮብን የሚያሽር በዓል በዓርብና በሮብ ሲውል በምትኩ በዋዜማው የሚጾም ጾም ነው፡፡ ለምሳሌ ጥምቀት ዓርብ ቢውል ሐሙስ ጾመ ገሀድ ይሆናል፡፡ ነገር ግን አበው ለጾም ማድላት አለብን በማለት ጾመ ገሀድ ምንጊዜም ጥምቀት በጾም ቀን ዋለም አልዋለም በዋዜማው እንዲጾም ወስነዋል፡፡ ጾመ ፍልሰታ ሐዋርያት የእመቤታችንን ትንሣኤ ለማየት ይበቁ ዘንድ ሱባኤ ገብተው የጾሙት ጾም ሲሆን ምንጊዜም ነሐሴ አንድ ቀን ገብቶ ከሁለት ሱባኤ በኋላ የእመቤታችን ዕርገት ይፈጸማል፡፡ \n \nጥያቄ: በአራቱም ዘመናት ኅዳር አስራ አምስት የሚጀምረው ጾም ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ጾመ ነቢያት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዩጋንዳ ዩጋንዳ ሪፐብሊክ (ወይም ዑጋንዳ) በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። በኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ ይዋሰናል። የዩጋንዳ ሰም የመጣው ከቡጋንዳ መንግሥት ነው። ከአረቦችና አውሮፓውያን በ1800ቹ ከመድረሳቸው በፊት ብዙ የሚታወቅ ነገር አልነበረም። በ15ተኛ መቶ ክፍለ-ዘመን ችዌዚ የተባለውን መንግስት በአፈ ታሪክ ይገኛል። አረቦችና አውሮፓውያን በ19ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሲደርሱ ብዙ መንግሥቶች በቦታው ነበሩ። እነዚህም በንዮሮ ፣ ቡሶጋ ፣ ቡጋንዳ ፣ ቶሮ እና አንኮልን ያጠቃልላሉ። ከ1894 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በታላቁ ብሪታን ስትመራ ነበር። የተለያዩ ቦታዎች ከተዋሃዱ በኋላ ዩጋንዳ በ1914 እ.ኤ.አ. ቅርጿን ያዘች። በ1966 እ.ኤ.አ. ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ ሕገ-መንግሥቱን አፍርሰው እራሳቸውን ፕሬዝዳንት አደረጉ። በ1971 እ.ኤ.አ. ኢዲ አሚን ሀገሩን መምራት ጀመሩ። የኢዲ አሚን አመራር 300,000 የሚገመቱ ዩጋንዳውያንን አስጨርሷል። በ1979 እ.ኤ.አ. የታንዛንያ ኃይሎች ኢዲ አሚንን ከሥልጣን ያስወግዳሉ። ሚልተን ኦቦቴ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ግን በ1985 እ.ኤ.አ. እንደገና ይወርዳሉ። ያሁኑ ፕሬዝዳንት ዮወሪ ሙሴቪኒ ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ናቸው። ፕሬዝዳነንቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይመርጣሉ። ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሎ ሲባምቢ ናቸው። ዩጋንዳ በመሬት የተቆለፈች ብትሆንም ታላላቅ የውሃ አካላት አሉ። ከነዚህ ውስጥም ቪክቶሪያ ሐይቅ፣ አልበርት ሐይቅ፣ ክዮጋ ሐይቅ እና ኤድዋርድ ሐይቅ ይዘረዘራሉ። ታላላቅ ከተማዎች በቪክቶሪያ ሐይቅ አቅራቢያ ይገኛሉ። እነዚህም ካምፓላንና እንትቤን ያጠቃልላል። ዩጋንዳ በ70 ወረዳዎች የተከፋፈለች ስትሆን እነዚህም በአራት አመራር ክልሎች ውስጥ ናቸው። አራቱ አመራር ክልሎች ሰሜናዊ ፣ ምሥራቃዊ ፣ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ይባላሉ። ወረዳዎቹ በዋና ከተማዎቻቸው ነው የሚሰየሙት። በዩጋንዳ ውስጥ የመዳብ እና ነጭ ብረት ክምችቶት አሉ። ግብርና ዋናው የኤኮኖሚ ሴክተር ነው። ከ80 በመቶ በላዩ የስራ ኃይል በግብርና ነው የተሰማራው። ቡና ዋናው የኤክስፖርት ትርፍ ምንጭ ነው። ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግሥቱ ከሌሎች ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን በኢዲ አሚን ጊዜ የወደቀውን ኤኮኖሚ ለማንሳት ተጣጥሯል። ዩጋንዳ ለብዙ ብሔረሰቦች ቤት ነው። ከነዚህ ውስጥ ግን አንድ ትልቁን ሕዝብ ብዛት የሚወክል የለም። 40 አካባቢ የሚሆኑ ቋንቋዎች ባሁኑ ጊዜ ይነገራሉ። ከነጻነት በኋላ እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተደርጓል። ብዙ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ ሉጋንዳ ሲሆን የአቴሶ ቋንቋ በሁለተኛነት ይከተላል። ኪስዋሂሊ ዋናው የንግድ ቋንቋ ነው። የዩጋንዳ የትምህርት ስርዐት የሰባት ዓመት መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፣ ስድስት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና ከ3 እስከ 5 ዓመት ከሁለተኛ ደረጃ በኃላ ትምህርት ያጠቃልላል። \n \nጥያቄ: ኢዲአሚን ከሥልጣን የወረደው መቼ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ1979 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nንጉሡ ላሊበላ የሚለውን ስም ያገኘው፣ ሲወለድ በንቦች ስለተከበበ ነው ይባላል። ላል ማለት ማር ማለት ሲሆን፤ ላሊበላ ማለትም -ላል ይበላል (ማር ይበላል) ማለት አንደሆነ ይነግራል። ውቅር ቤተክርስቲያናቱን ንጉሡ ጠርቦ የስራቸው ከመላእክት እገዛ ጋር እንደሆነ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ይነግራል። በ16ኛው ከፍለ ዘመን አውሮፓዊ ተጓዥ ላሊበላን ተመልክቶ «ያየሁትን ብናግር ማንም እንደኔ ካላየ በፍጹም አያምነኝም» ሲል ተናግሮ ነበር። በላሊበላ 11 ውቅር ዐብያተ ክርስቲያናት ያሉ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ቤተ ጊዮርጊስ (ባለ መስቀል ቅርፁ) ሲታይ ውሃልኩን የጠበቀ ይመስላል። ቤተ መድሃኔ ዓለም የተባለው ደግሞ ከሁሉም ትልቁ ነው። ላሊበላ (ዳግማዊ ኢየሩሳሌም) የገና በዓል ታህሳስ 29 በልዩ ሁኔታ ና ድምቀት ይከበራል፣ \"ቤዛ ኩሉ\" ተብሎ የሚጠራው በነግህ የሚደረገው ዝማሬ በዚሁ በዓል የሚታይ ልዩ ና ታላቅ ትዕይንት ነው።የሚደረገውም ከቅዳሴ በኋላ በቤተ ማርያም ሲሆን ከታች ባለ ነጭ ካባ ካህናት ከላይ ደግሞ ባለጥቁር ካብ ካህናት በቅዱስ ያሬድ ዜማ ቤዛ ኩሉ እያሉ ይዘምራሉ። 11ዱ የቅዱስ ላሊበላ ፍልፍል አብያተ ክርስቲያናት ቤተ መድሃኔ ዓለም፣ ቤተ ማርያም፣ ቤተ ደናግል፣ ቤተ መስቀል፣ ቤተ ደብረሲና፣ ቤተ ጎለጎታ፣ ቤተ አማኑኤል፣ ቤተ አባ ሊባኖስ፣ ቤተ መርቆሬዎስ፣ ቤተ ገብርኤል ወሩፋኤል፣ ቤተ ጊዮርጊስ ናቸው። \n \nጥያቄ: ከላሊበላ አስራ አንዱ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ቤተ ጊዮርጊስ ምን ዓይነት ቅርፅ አለው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ መስቀል ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጾመ ነቢያት በአራቱም ዘመናት ምን ጊዜም ኅዳር ዐሥራ አምስት እንዲጾም ተወስኗል፡፡ ጾመ ገሀድ የምትክ ጾም ነው፡፡ ይህ ጾም ዓርብንና ሮብን የሚያሽር በዓል በዓርብና በሮብ ሲውል በምትኩ በዋዜማው የሚጾም ጾም ነው፡፡ ለምሳሌ ጥምቀት ዓርብ ቢውል ሐሙስ ጾመ ገሀድ ይሆናል፡፡ ነገር ግን አበው ለጾም ማድላት አለብን በማለት ጾመ ገሀድ ምንጊዜም ጥምቀት በጾም ቀን ዋለም አልዋለም በዋዜማው እንዲጾም ወስነዋል፡፡ ጾመ ፍልሰታ ሐዋርያት የእመቤታችንን ትንሣኤ ለማየት ይበቁ ዘንድ ሱባኤ ገብተው የጾሙት ጾም ሲሆን ምንጊዜም ነሐሴ አንድ ቀን ገብቶ ከሁለት ሱባኤ በኋላ የእመቤታችን ዕርገት ይፈጸማል፡፡ \n \nጥያቄ: ጾመ ፍልሰታ ሲያበቃ የሚከበረው በዓል ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የእመቤታችን ዕርገት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጋና ጋና በአፍሪካ አትላንቲክ ጠረፍ ላይ የተገኘ አገር ሲሆን ከ24 ሚሊዮን ኗሪዎች በላይ አሉት። የጋና ስራ ቋንቋ እንግሊዝኛ ሲሆን፣ ሌሎች ኗሪ ቋንቋዎች በተለይም ትዊኛ (አካንኛ) በሰፊ ይነገራሉ። የ«ጋና» ስያሜ በታሪክ የድሮ «ጋና መንግሥት» ወይም «ዋጋዱጉ መንግሥት» ለማክበር በ1949 ዓም ተመረጠ። እንዲያውም ያው መንግሥት እስከ 1068 ዓም ድረስ ከጋና ወደ ስሜን-ምዕራብ በአሁኑ ማሊ ይገኝ ነበር እንጂ የዛሬውን ጋና መቸም አልገዛም። «ጋና» በትክክል የዋጋዱጉ መንግሥት አለቆች ማዕረግ ሆኖ ነበር። ዋጋዱጉ መንግሥት በ1068 ዓም ግድም ከወደቀ ቀጥሎ፣ የአካን ብሔሮች ከዚያው ፈልሰው በዛሬው ጋና ሠፈሩና መጀመርያ ግዛቶችን መሠረቱ። ከ1662 እስከ 1949 ዓም ድረስ የአሻንቲ መንግሥት ባካባቢው ቆየ፤ በ1894 ዓም ይህ የብሪታንያ አሻንቲ ጥብቅ ግዛት ሆነ። ከ1949 ዓም አስቀድሞ የዩናይትድ ኪንግደም ጥገኛ ግዛት ሲሆን በወርቅ ሀብቱ ምክንያት «የወርቅ ጠረፍ ጥገኛ ግዛት» (ጎልድ ኮስት ፕሮቴክቶሬት) በመባል ይታወቅ ነበር። ከ1984 ዓም ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ እና ፓርላሜንታዊ መንግሥት ኖሮታል። አብዛኞቹ ኗሪዎች (70%) በተለይ በደቡቡ ክርስቲያን ሲሆኑ፣ በተለይ በስሜኑ 16% የእስልምና ተከታዮች ናቸው። የተረፉትም የኗሪ አረመኔነትን እምነቶች ይከተላሉ። የጋና ዋና ምርቶች ካካዎ፣ ዘይት፣ አልማዝ ናቸው። በአለሙ ከሁሉ ትልቅ የሆነው ሠው ሰራሽ ሐይቅ፣ ቮልታ ሐይቅ፣ በጋና ይገኛል። እግር ኳስ ከሁሉ የተወደደው እስፖርት ነው። የጋና አበሳሰል በተለይ በኮቤ፣ ጐርጠብ፣ የስኳር ድንች፣ ባቄላ፣ በቆሎ፣ ኦቾሎኒ፣ ባሚያና ሩዝ ይሠራል። \n \nጥያቄ: የጋናውያን ብሔራዊ ቋንቋ ምንድን ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ እንግሊዝኛ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቴሌቪዥን ቴሌቪዥን የስዕል እና ድምጽ ምልክቶችን ከማሰራጫ የሚቀበል የመገናኛ ዘዴ ነው። «ቴሌ-» የሚለው ክፍል በግሪክ «ሩቅ» ማለት ቢሆን «-ቪዥን» ደግሞ ከሮማይስጥ visio /ዊዚዮ/ «ማየት» («ትርዒት») ተወስዷል። በአጠቃላይ ቴሌቪዥን ማለት ተንቀሳቃሽ ምስልን (ብዙ ጊዜ ከድምፅ ጋር) ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለማስተላለፍ የሚረዳ የመልዕክት ማስራጫ መንገድ ነው። ይህ ከሆነ ዘንዳ ቴሌቪዥን ምስል መቅጃውንም ሆነ ምስል መቀበያውን መሳሪያ ሁሉ ያጠቃልላል ግን በተለምዶ ቴሌቪዥን የምንለው ምስል መቀበያውን ብቻ ነው። በ1873 እ.ኤ.አ. (1865 ዓም) የእንግላንድ ኤንጅኔር ውሎቢ ስሚስ ባደረገው ጥረት ጥንተ ንጥሩ ሴሌኒይም ብርሃን-አስተላልፎሽ መሆኑን ገለጸ። በ1884 እ.ኤ.አ. ፓውል ጎትሊብ ኒፕኮው የተባለ ጀርመናዊ ክብ የሆነ ዲስክን በስፓይራል በምብሳት ይህ ዲስክ በተሽከረከረ ቁጥር ከፊትለፊቱ የሚመጣውን ብርሃን በቀዳዶቹ በማሾለክ ከሴሌኒይም በተሰራ የካሜራ ግድግዳ ላይ እንዲያርፍ አደረገ። ግድግዳው ብርሃን ሲነካው ያንን ብርሃን ወደ ኮሬንቲ ሃይል በመቀየር ምስልን በኮሬንቲ መልክ በሽቦ ለመላክ ቻለ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ አምፕሊፋየር ስላልነበር የሚላከው ምስል እምብዛም አመርቂ አልነበረም። ከ27 አመታት በኋላ በ1911 እ.ኤ.አ. የራሻው ቦሪስ ሮዚንግ ለመጀመሪያ ጊዜ የሲርቲን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፣ አሁንም ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል ቻለ። ነገር ግን የሚንቀሳቀሱት ምስሎች የጂዎሜትሪ ቅርጽ ነበራቸው ማለትም ሶስት ማዕዘን፣ አራት ማእዘን ወዘተ... ከ7 አመታት በኋላ በ1925 እ.ኤ.አ. ጆን ሎጂ ቤርድ የተሰኘው የስኮትላንድ ተመራማሪ 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለመላክ ቻለ ከዚያም በ1926 እ.ኤ.አ. ጥቁርና ነጭ የሆኑ ምስሎችን ለማስተላለፍ በቃ። በዚህ ጊዜ የሚላኩት ምስል ጥራት 30 መስመር በአንድ ጊዜ ነበር፣ በዚህም ምክንያት የሰውን ፊት ለመለየት አስቸጋሪ ቢሆንም ግን ይቻል ነበር። አቶ ቤርድ በ 1918 ዓ.ም. (26 January 1926 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የቴሌቪዥን መግለጫ ሰጠ። በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ የተሰኘው የቤል ላብራቷር ተቀጣሪ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ መላክ ቻለ። ቀጠል አድርጎም በራዲዮ ወደ ዊፓኒ ኒው ጀርሲ ለመላክ በቃ። በዚያው አመት ፊሎ ፍራንስዎርዝ የመጀመሪያውን የተሟላና በኤሌክትሪክ ስካኒንግ ብቻ የሚስራውን የቴሌቭዥን ስርዓት በተግባር አዋለ።.በጥር 1928 እ.ኤ.አ. (1920 ዓም) መጀመርያው የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያ በስከነክተዲ፣ ኒው ዮርክ ተከፈተ፤ እስከ ዛሬም ድረስ ያሰራጫል። \n \nጥያቄ: በ1927 እ.ኤ.አ. 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ የላከው ሰው ኸርበርት አይቭስ የማን ድርጅት ሰራተኛ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የቤል ላብራቷር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየላሊበላ ግሎባል ኔትወርክስ ድርጅት ተባባሪ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ (ዶ/ር) ዓለም አቀፉን ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገ አዲስ የስራ ፈጣራ ውድድር አሸነፉ። ኢትዮጵያዊቷ በየዓመቱ የሚካሄደውን ዓለም አቀፉን ፒአይቲሲኤች (PITCH) አዲስ የስራ ፈጠራ ውድድር በትላንትናው እለት ማሸነፉቸው ይፋ ሆኗል። ውድድሩ 2500 ስራ ፈጣሪዎች የተሳተፉ ሲሆን ወደ መጨረሻው ዙር ያለፉት ደግሞ 700 የሚሆኑ አዲስ ፈጣሪዎች ነበሩ። ከዚህ ውስጥ ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ(ዶ/ር) በጤና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያቀረቡት አዲስ የስራ ፈጠራ በቅርበት ተፎካካሪ ከነበሩት የአሜሪካና የእንግሊዝ የስራ ፈጣሪዎችን በመብለጥ የዓመቱ ውድድር አሸናፊ ሆኗል። ውለታ ለማ (ዶ/ር) ለውድድሩ ያቀረቡት የስራ ፈጠራ አባይ ሲ ኤች አር (ABAY CHR) የተባለ በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ህክምና ዘርፍ ያለውን ሰፊ የወረቀት ስራ ወደ ዲጂታል በመቀየር ስራን የሚያቀልና የሚያቀላጥፍ እንዲሁም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወጪን የሚያስቀር የሥራ ፈጠራ ነው ተብሏል። \n \nጥያቄ: ዶ/ር ውለታ ለማ ባሸነፉበት አዲስ የሥራ ፈጠራ ውድድር መጨረሻ ላይ ምን ያህል ተወዳዳሪዎች ነበሩ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 700 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዩጋንዳ ዩጋንዳ ሪፐብሊክ (ወይም ዑጋንዳ) በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። በኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ ይዋሰናል። የዩጋንዳ ሰም የመጣው ከቡጋንዳ መንግሥት ነው። ከአረቦችና አውሮፓውያን በ1800ቹ ከመድረሳቸው በፊት ብዙ የሚታወቅ ነገር አልነበረም። በ15ተኛ መቶ ክፍለ-ዘመን ችዌዚ የተባለውን መንግስት በአፈ ታሪክ ይገኛል። አረቦችና አውሮፓውያን በ19ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሲደርሱ ብዙ መንግሥቶች በቦታው ነበሩ። እነዚህም በንዮሮ ፣ ቡሶጋ ፣ ቡጋንዳ ፣ ቶሮ እና አንኮልን ያጠቃልላሉ። ከ1894 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በታላቁ ብሪታን ስትመራ ነበር። የተለያዩ ቦታዎች ከተዋሃዱ በኋላ ዩጋንዳ በ1914 እ.ኤ.አ. ቅርጿን ያዘች። በ1966 እ.ኤ.አ. ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ ሕገ-መንግሥቱን አፍርሰው እራሳቸውን ፕሬዝዳንት አደረጉ። በ1971 እ.ኤ.አ. ኢዲ አሚን ሀገሩን መምራት ጀመሩ። የኢዲ አሚን አመራር 300,000 የሚገመቱ ዩጋንዳውያንን አስጨርሷል። በ1979 እ.ኤ.አ. የታንዛንያ ኃይሎች ኢዲ አሚንን ከሥልጣን ያስወግዳሉ። ሚልተን ኦቦቴ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ግን በ1985 እ.ኤ.አ. እንደገና ይወርዳሉ። ያሁኑ ፕሬዝዳንት ዮወሪ ሙሴቪኒ ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ናቸው። ፕሬዝዳነንቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይመርጣሉ። ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሎ ሲባምቢ ናቸው። ዩጋንዳ በመሬት የተቆለፈች ብትሆንም ታላላቅ የውሃ አካላት አሉ። ከነዚህ ውስጥም ቪክቶሪያ ሐይቅ፣ አልበርት ሐይቅ፣ ክዮጋ ሐይቅ እና ኤድዋርድ ሐይቅ ይዘረዘራሉ። ታላላቅ ከተማዎች በቪክቶሪያ ሐይቅ አቅራቢያ ይገኛሉ። እነዚህም ካምፓላንና እንትቤን ያጠቃልላል። ዩጋንዳ በ70 ወረዳዎች የተከፋፈለች ስትሆን እነዚህም በአራት አመራር ክልሎች ውስጥ ናቸው። አራቱ አመራር ክልሎች ሰሜናዊ ፣ ምሥራቃዊ ፣ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ይባላሉ። ወረዳዎቹ በዋና ከተማዎቻቸው ነው የሚሰየሙት። በዩጋንዳ ውስጥ የመዳብ እና ነጭ ብረት ክምችቶት አሉ። ግብርና ዋናው የኤኮኖሚ ሴክተር ነው። ከ80 በመቶ በላዩ የስራ ኃይል በግብርና ነው የተሰማራው። ቡና ዋናው የኤክስፖርት ትርፍ ምንጭ ነው። ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግሥቱ ከሌሎች ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን በኢዲ አሚን ጊዜ የወደቀውን ኤኮኖሚ ለማንሳት ተጣጥሯል። ዩጋንዳ ለብዙ ብሔረሰቦች ቤት ነው። ከነዚህ ውስጥ ግን አንድ ትልቁን ሕዝብ ብዛት የሚወክል የለም። 40 አካባቢ የሚሆኑ ቋንቋዎች ባሁኑ ጊዜ ይነገራሉ። ከነጻነት በኋላ እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተደርጓል። ብዙ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ ሉጋንዳ ሲሆን የአቴሶ ቋንቋ በሁለተኛነት ይከተላል። ኪስዋሂሊ ዋናው የንግድ ቋንቋ ነው። የዩጋንዳ የትምህርት ስርዐት የሰባት ዓመት መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፣ ስድስት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና ከ3 እስከ 5 ዓመት ከሁለተኛ ደረጃ በኃላ ትምህርት ያጠቃልላል። \n \nጥያቄ: ኢዲአሚን የየት ሀገር መሪ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ዩጋንዳ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጋሞጐፋ ዞን አርባ ምንጭ ከተማ ከ1955 እስከ 1993 ዓ.ም ድረስ የጋሞ ጐፋ ጠቅላይ ግዛት፣ የሰሜን ኦሞ አስተዳደር አካባቢና ከዚያም የሰሜን ኦሞ ርዕሰ ከተማ በመሆን ለቀድሞዎቹ የጋሞ፣ የጐፋ፣ የጋርዱላና ሐመር ባኮ አውራጃዎች ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ማዕከል ሆና ያገለገለች ስትሆን ከ1993 ዓ.ም ወዲህ ባሉት ዓመታት ደግሞ አስራ አምስት ወረዳዎችንና ሁለት የከተማ አስተዳደሮችን አቅፎ ለያዘው ጋሞ ጐፋ ዞን ዋና ከተማ በመሆን እያገለገለች የምትገኝ ከተማ ነች፡፡ በዞኑ ውስጥ የሚገኙ የጋሞ፣ የጎፋ፣ የዘይሴ ፣ የጌዲቾና የኦይዳ ብሄረሰቦችን ጨምሮ ጥቂት የማይባሉ ሌሎች የሀገራችን ብሔር ብሔረሰቦች ተወላጆች ተከባብረውና ተቻችለው በፍቅርና በሰላም የሚኖሩባት አርባ ምንጭ ከተማ በቀለማት አደራደሩ ትኩረትና ተወዳጅነት የማይለየው የጋሞ ብሔረሰብ የክብርና የማዕረግ ልብስ እንዲሁም መታወቂያው የሆነውንና ዱንጉዛ በመባል የሚታወቀው ባህላዊ ልብስ ጨምሮ ሌሎች የኢትዮጵያ የሸማ ጥበብ አልባሳት ሥራዎች መፍለቅያ አካባቢዎች እምብርት ከመሆኗም በተጨማሪ በባህላዊ ቤት አሰራራቸው በለቅሶና ሠርግ ስርዓታቸው በባህላዊ የማምረቻና የመገልገያ ቁሳቁሶቻቸው የብዙዎችን አድናቆትና አግራሞትን ላስጫሩት የጋሞ፣ የጐፋ፣ የዘይሴ፣ የጌዲቾና የኦይዳ ብሔረስብ ህዝቦች መዲና ነች፡፡ ከባህር ወለል በላይ ከ1,300 እስከ 1,500 ሜትር ከፍታ ላይ ስትገኝ የአርባ ምንጭ ከተማ አየር ንብረት በተለምዶ ቆላማ የሚሉት አይነት ሲሆን፤ የከተማዋ ዓመታዊ አማካይ የሙቀት መጠኗ 240c ነው፡፡ የከተማዋ ዓመታዊ አማካይ የዝናብ መጠኗ 900 ሚሊ ሜትር ሆኖ ግንቦት፣ ሰኔ፣ መስከረምና ጥቅምት ወራት ከፍተኛ የዝናብ መጠን በዓመቱ ውስጥ የሚመዘግብባቸው ወራት ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡ በተፈጥሮ ውበት በታደለው ድንቅ ስፍራ እንደመከተሟ አርባዎቹ ምንጮች የሚመነጩባትን መንትያዎቹ የአባያና ጫሞ አስደናቂ የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ፤በአካባቢው ታይተው የማይጠገቡ የዱር እንሰሳት ያለሀሳብ የሚፈነጩባትን የነጭ ሣር ብሔራዊ ፖርክ፤ የአዞ እርባታ ጣቢያ፤ የአዞ ገበያ እና የተፈጥሮ ደኖችን ሌሎች ከህሊና ጓዳ የማይፋቅ ትዝታን ጥለው የሚያልፉ ሃብቶች ባለቤት ናት በተፈጥሮ ውበት በታደለው ድንቅ ከተማ እንደመከተሟ አርባዎቹ ምንጮች የሚመነጩባትን የአባያና ጫሞ አስደናቂ የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ያለሀሳብ የሚፈነጩባትን ፤ የነጭ ሣር ብሔራዊ ፖርክ፤ የአዞ እርባታ ጣቢያ፤ የአዞ ገበያን በአካባቢው ታይተው የማይጠገቡ የዱር እንሰሳት እና የተፈጥሮ ደኖችን ይገኛሉ፡፡ የዞኑን አስደናቂ የቱሪስት መስህቦች እንግዶቻችንን በማስጎብኘት ከታዋቂ የዓሳ ምርታችን ፣ ከማንጎ ፤ ከሙዝ እና በአፕል ማሳችን እየተንሸራሸርን የማይረሱ ትዝታዎችን ጥለው ያልፋሉ፡፡ \n \nጥያቄ: ከተማዋ ከፍተኛ የዝናብ መጠን የምታገኘው በየትኞቹ ወራት ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ግንቦት፣ ሰኔ፣ መስከረምና ጥቅምት ወራት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር፣ በጠላት ወረራ ዘመን የተመሠረተ ድርጅት ሲሆን፤ እስከ አሁን ድረስ ያሉት አዛውንት አባላቱ በዚያው የአምሥት ዓመት ትግል ዘመናት፣ መኳንንቱ፤ የጦር መሪዎቻቸውና ንጉሠ ነገሥቱም ጭምር እነዚያን ወጣት ኢትዮጵያውያን አንጀታቸውን ለረሀብ፤ እግራቸውን ለሾኽ ለጠጠር፤ ግንባራቸውን ለእርሳስ አጋልጠዋቸው በካዷቸው መራር ዘመን፤ ሞትም ቢመጣ እናት አገራችንን አሳልፈን ለጠላት አንሰጥም፤ ነፃነታችንን ለጊዜያዊ ሹመት፣ ሽልማት አንለውጥም ብለው የተጋፈጡ ጀግኖች ናቸው። ደጃዝማች ከበደ ተሰማ፤ “የታሪክ ማስታወሻ” በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ፤ ይህ ማኅበር በአርበኝነት ዘመን በሸዋ ክፍለ ሀገር በ፲፱፻፴፩ ዓ/ም «የጥንታዊት ኢትዮጵያ የጀግኖች ማኅበር» በሚል ስም ተሠይሞ የተቋቋመ ማኅበር እንደነበርና ዓላማውም «የአርበኞችን ክብ በማበረታታትና በየሀገሩ ካሉ አርበኞች ጋር በመላላክ የሚገኘውን ሥራ ፍሬ» እርስ በርስም ሆነ በስደት ላይ ከነበሩት ንጉሠ ነገሥት ጋርም መካፈል እንደነበር ይገልጻሉ። ከመሥራች ማኅበረተኞቹ በከፊሉ፦ ራስ አበበ አረጋይ፤ ወንድማማቾቹ ደጃዝማች ፀሐዩ እና ደጃዝማች ተስፋዬ ዕንቁ ሥላሴ፤ አቶ እምአእላፍ ኅሩይ፤ ደጃዝማች ኃብተ ሥላሴ በላይነህ፤ ደጃዝማች ታከለ ወልደሐዋርያት ይገኙባቸዋል። በመጀመሪያ ጊዜ የነበሩት መሥራቾች ሃያ ዘጠኝ አባላት ሲሆኑ በኋላ ጊዜ ግን ብዙ ማኅበረተኞች እየተጨመሩ የአባሎቹ ቁጥር ከሦስት መቶ በላይ ሆኖ ነበር። የጠላት ኃይል ተሸንፎ የአገሪቱ ነፃነት ከተመለሰ በኋላ፣ አርበኞቹ በየአውራጃውና በየጠቅላይ ግዛቱ ተሰማርተው ስለነበረና ማኅበሩም በመከራው ዘመናት የተቋቋመበት ዓላማ በነፃነት ጊዜ አላስፈላጊ በመሆኑ፤ የጥንታዊት ኢትዮጵያ የጀግኖች ማኅበር ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ ሳያሳይ ብዙ ዓመታት አሳለፈ። ሆኖም በሚያዝያ ወር ፲፱፻፶፬ ዓ/ም ጄኔራል ነጋ ኃይለ ሥላሴ «ከሥራ ባልደረቦቻቸውና ከዕውቅ አገር አፍቃሪዎች ጋራ፥ \"ጥንታዊት ኢትዮጵያ ሀገራዊ የዠግኖች ማኅበርን\" በታደሰ ሀገራዊ ዓላማና በተሻሻለ ደንብ አቋቋሙ። ኾኖም፥ ድርጅቱ እስከ ሰኔ ፲፱ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ/ም ድረስ ከመንግሥት ዕውቅናን ስላላገኘ ሥራው በዚሁ ምክንያት ለጊዜው ተገታ።» ጄኔራል ነጋ በዚህ ዕለት ሕጋዊ ዕውቅና ያገኘውንና ለፍጹም ሰላማዊና ሀገራዊ ዓላማ፤ ለበጎ አድራጎት የተጀመረውን የጥንታዊት ኢትዮጵያ ሀገራዊ የዠግኖች ማኅበር፤ ጠቅላይ ሥራ አመራር ሸንጎ ሊቀ-መንበር ኾነው የማኅበሩን ሥራ በሰፊው በማንቀሳቀስ ባጭር ጊዜ ውስጥ ፬ሺ የፈረሙ አባላትን ከጠቅላላው የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ እንዳስገኙ፥ አሁንም መንግሥታዊ እንቅፋት ገጥሞት ከሕገ-ወጥ በሆነ እርምጃ ፥ የድርጅቱ ጽሕፈት ቤት በጸጥታ ኀይሎች እንዲዘጋ ተደረገ። \n \nጥያቄ: የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር የተሻሻለው ሁለተኛ ስም ማን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ጥንታዊት ኢትዮጵያ ሀገራዊ የዠግኖች ማኅበር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nከ2009 ዓ.ም ህዳር ወር ጀምሮ ሲዘጋጅ የነበረው አገራዊ የጤና ደህንነት ትግበራ ዕቅድ በዛሬው ዕለት ይፋ ሆኗል፡፡ ዝርዝር እቅዱን ለመተግበር ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል፡፡ ገንዘቡ በኢትዮጵያ መንግስትና በአጋር ድርጅቶች እንደሚሸፈንም ተነግሯል፡፡ አገራዊ የጤና ደህንነት ትግበራ ዕቅድ እ.ኤ.አ እስከ 2023 ድረስ የሚቆይ ነው ተብሏል፡፡ \n \nጥያቄ: ሀገራዊ የጤና ደህንነት እቅድን ለመተግበር ምን ያህል ገንዘብ ያስፈልጋል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nነሐሴ ፲፩ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፵፩ ኛው ቀን ሲሆን የክረምት ወቅት ፵፮ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፳፭ ቀናት ሲቀሩ፣ በዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፳፬ ቀናት ይቀራሉ። ፲፰፻፶ ዓ/ም - በብሪታኒያ ንጉዛት እና በአሜሪካ ኅብረት መኻል በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የተዘረጋውን አዲሱን የቴሌግራፍ መስመር በመመረቅ ንግሥት ቪክቶሪያ እና የአሜሪካው ፕሬዚደንት ጄምስ ቡካነን የሰላምታ መልእክት ተለዋወጡ። ፲፱፻፳፩ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የአገሪቱን የመጀመሪያ አየር-ዠበብ (አውሮፕላን) በዚህ ዕለት ተረከበ። ሁለተኛው አየር-ዠበብ ከጂቡቲ ወደብ እስከ ድሬዳዋ በባቡር ተጭኖ፤ ከድሬ ዳዋ ደግሞ እስከ አዲስ አበባ አሥራ ስምንት የአውሮፓ የፖስታ ቦርሳዎችን ጭኖ እየበረረ ነሐሴ ፴ ቀን ገባ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የብሪታኒያ ዋና መላክተኛ አምባሳደር ዳግላስ ራይት በኢትዮጵያ እና በኬንያ መኻል ያለውን ድንበር ለመስማማት የተዘጋጀውን የውል ረቂቅ ለኢትዮጵያ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድ አስረከበ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ከ ፲፰፻፸፯ ዓ/ም ጀምሮ በፈረንሳይ ሥር በቅኝ ግዛትነት ትተዳደር የነበረችው ጋቦን በዚህ ዕለት ነፃ ወጣች። ሊዮን ምባ የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ሆኑ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮታዊ ሽግግር የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የክብር ዘበኛ ሠራዊት አዛዥ የነበሩት ማዮር ጄነራል ታፈሰ ለማ በደርግ ተይዘው ታሠሩ። በዚሁ ዕለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የነብሩት አቡነ ቴዎፍሎስ አዲስ በተዘጋጀው ረቂቅ ሕገ-መንግሥት ውስጥ በተካተቱ አንዳንድ አንቀጾች ላይ ቅዋሜ እንዳላቸው አስታወቁ። ፳፻፬ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቦይንግ ኩባንያ ከገዛቸው አሥር ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አየር-ዠበቦች የመጀመሪያውና በሰሌዳ ቁጥር ET-AOQ የተመዘገበው አየር-ዠበብ በዚህ ዕለት ከዋሽንግተን ዲሲ ተነስቶ አዲስ አበባ፣ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። ፲፱፻፴፬ ዓ/ም - የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ልጅ ልዕልት ፀሐይ በተወለዱ በ፳፫ ዓመታቸው በዚህ ዕለት አረፉ። \n \nጥያቄ: የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ልጅ ልዕልት ፀሐይ የሞቱት በስንት ዓመተ ምህረት ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ፲፱፻፴፬ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየፌዴራል ትራንስፖርት ባለስልጣን በአፋር ክልል ዲቼቶ አካባቢ የተገነባውን የድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሽከርካሪዎች መቆያ ተርሚናል ዛሬ ተመረቀ። ተርሚናሉ በ12 ሂክታር ላይ ያረፈ ሲሆን በአንድ ጊዜ 800 ከባድ ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ የሚችል መሆኑ ተገልጿል። የዲቾቶ የከባድ ተሽከርካሪ ተርሚናል 99 ሚሊየን 279 ሺህ 944 ብር ወጭ ተደረጎበት መገንባቱ ተነግሯል። \n \nጥያቄ: በአፋር ክልል ዲቼቶ አካባቢ የተገነባውን የጭነት መቆያ ተርሚናል በአንድ ጊዜ ስንት ከባድ ተሽከርካሪዎች ማስተናገድ ይችላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 800 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየማይዳሰሱ (ኢንታንጀብል) ባህላዊ ቅርሶችን የሚመለከተው የዩኔስኮ አካል በይነ መንግሥታዊው ኮሚቴ 10ኛ ስብሰባውን ከኅዳር 20 እስከ ኅዳር 24 ቀን 2008 ዓ.ም. በናሚቢያ መዲና ዊንድሆክ በተደረገው 10ኛ የዩኔስኮ ጉባዔ ለውሳኔ ከቀረቡት 35 (ሠላሳ አምስት) ባሕላዊ ቅርሶች መካከል የሲዳማ ብሔር የአዲስ ዓመት ዘመን መለወጫ የሆነው ፍቼ ጫምባላላ በዓል በሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ የ2003 የኢንታጀብል ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃ ዓለም አቀፍ ስምምነት መስፈርቶችን አሟልቶ በመገኘቱ አባል አገሮች ውይይት ካደረጉበት በኋላ ፍቼ ጫምባላላ ተመዝግቧል፡፡ ይህም ከመስቀል በዓል ቀጥሎ የኢትዮጵያ ሁለተኛው የማይዳሰስ ዓለም አቀፍ የሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ሆኖ ሕዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም በአገሩ ሰዓት አቆጣጠር 9፡40 በፋይል ቁጥር (01054) በውሳኔ ቁጥር 10.com.10.b.16 ተመዝግቧል፡፡ በ2004 በጀት ዓመት የመስቀል በዓል አከባበርን በዩኔስኮ ማስመዝገብ የሚያስችል የጥናት ሰነድ ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ የተላከ ሲሆን በአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ ከህዳር 23-28 ቀን 2006 ዓ.ም በተካሄደው 8ኛው የዩኔስኮ የኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃ የኢንተርገቨርንመንታል ኮሚቴ መደበኛ ጉባዔ ውሳኔ መሰረት የመስቀል በዓል አከባበር በዩኔስኮ የሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ተካቷል፡፡ በ2006 የበጀት ዓመት የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው ፊቼ ጫምበላላን በሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ለማስመዝገብ የሚያስችል የጥናት ሰነድ (ኖሚኔሽን ፋይል) ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ የተላከውና ህዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም የተመዘገበው የተደረገው ፊቼ ጫምበላላ ሰነዶች በሚከተለው የዩኔስኮ ድረ ገጽ ላይ ለመላው ዓለም ተለቀው ይገኛል፡፡ በተመሳሳይም በ2007 የበጀት ዓመት ኦሮሞ ህዝብ የማንነት መገለጫ የሆነው የገዳ ስርዓትን በሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ለማካተት የሚያስችል የኖሚኔሽን ሰነድ ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ መጋቢት 2007 ዓ.ም ተልኳል፡፡ \n \nጥያቄ: የመስቀል በዓል የተመዘገበው ስንተኛ ዙር ስብሰባ ላይ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 8ኛው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቀጭኔ ከዝሆን በስተቀር ማንኛውም ሌላ እንስሳ ሊደርስ በማይችልበት ከፍታ ላይ የሚገኙ ረዣዥም ቀንበጠቦችን ለመብላት የሚያስችል አስደናቂ አፈጣጠር አላት። ልዩ የሆነ የመቆንጠጥ ችሎታ ያለው የላይኛው ከንፈሯና እንደተፈገለው የሚተጣጠፍ ችሎታ ያለው ምላሷ ሹል በሆኑ እሾሆች የታጠሩ ቅጠሎችን ለመቀንጠብ ያስችሏታል። ቀጭኔዎች በቀን እስከ 34 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕፅዋት መመገብ ይችላሉ። የተለያዩ ዕፅዋትን የሚበሉ ቢሆኑም ይበልጥ የሚመርጡት በአፍሪካ ሜዳዎች የሚገኙትን እሾሃማ ግራሮች ነው። አንድ ወንድ ቀጭኔ ምግብ ለመፈለግ ምላሱን እስከ 42 ሳንቲ ሜትር መዘርጋት ይችላል። የቀጭኔ አንገት በጣም አስደናቂ የሆነ የመተጣጠፍ ችሎታ አለው። ይህም ላይኛዎቹን የዛፍ ቅርንጫፎች ለመቀንጠብ በምታደርገው እንቅስቃሴ ረዥሙን ራሷን እንደ ልቧ ለማዘንበልና ለማዟዟር ያስችላታል። ለቀጭኔ ወደ ላይ መንጠራራት በጣም ቀላል ነገር ሲሆን ተጎንብሶ ውኃ መጠጣት ግን ይከብዳታል። ወደ ውኃ ጉድጓድ በምትቀርብበት ጊዜ የፊት እግሮቿን ቀስ በቀስ ከፍታ ካራራቀቻቸው በኋላ ወደ ውኃው ለመድረስ እንድትችል ሁለት ጉልበቶቿን አጠፍ ታደርጋለች። ቀጭኔዋ እንዲህ ባለው አመቺ ባልሆነ ሁኔታ እያለች ረዥም አንገቷን እስከ መጨረሻ ትዘረጋለች። ደግነቱ ግን ከምትመገባቸው ቅጠላ ቅጠሎች በቂ እርጥበት ስለምታገኝ ቶሎ ቶሎ መጠጣት አያስፈልጋትም። የቀጭኔ አንገትና ትከሻ የቅጠል ቅርፅ ባላቸውና ቀጫጭን በሆኑ ነጭ መስመሮች ያጌጠ ነው። ቀለማቸው የተለያየ ሲሆን ከወርቃማ ዳለቻ አንስቶ እስከ ቡናማ እንዲያውም ጠቆር እስካለ ቀለም ይደርሳል። የቀጭኔ ዕድሜ እየገፋ በሄደ መጠን ቀለሟም እየጠቆረ ይሄዳል። ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው። አንዲት ነፍሰ ጡር ቀጭኔ ልጅዋን ከ420 እስከ 468 ለሚደርሱ እርግዝና ቀናት ከተሸከመች በኋላ ሁለት ሜትር ቁመት ያለው ግልገል ትወልዳለች። ግልገሏ በምትወለድበት ጊዜ ራስዋን ታስቀድምና ከሁለት ሜትር ከፍታ ላይ ወደ መሬት ትወረወራለች። ይሁን እንጂ በ15 ደቂቃ ውስጥ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባት እየተውተረተረች ትነሳና ጡት ለመጥባት ዝግጁ ትሆናለች። ከሁለት ወይም ከሦስት ሳምንት በኋላ በደመ ነፍስ ተመርታ የግራር ቀንበጦችን መለቃቀም ስለምትጀምር ብዙም ሳትቆይ ረዥም እርምጃ ያላትን እናትዋን ተከትላ ለመሄድ የሚያስችል ጉልበት ታገኛለች። አንዲት የቀጭኔ ግልገል በጣም ውብ መልክ ሲኖራት የወላጆችዋ አነስተኛ ግልባጭ ነች። ቁመቷ ከቀጭኔ ርዝመት ጋር ሲወዳደር አጭር ብትሆንም ከብዙ ሰዎች ቁመት ግን ትበልጣለች። በእናቷ ጥንቃቄ የተሞላበት ጥበቃ ተማምና አላንዳች መሸበር አካባቢዋን የምትማትረው ግልገል ላያት ሁሉ ልዩ መስህብ አላት። ግልገል ቀጭኔዎች በተወለዱበት ወራት በግልገል መዋያ ተሰባስበው ሙሉውን ቀን ዕረፍት በማድረግ፣ በመጫወትና በአካባቢያቸው የሚሆነውን ነገር በመመልከት ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ። የቀጭኔ ግልገል ለማመን በሚያዳግት ፍጥነት ያድ⁠ጋል። በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ አንድ ሜትር የሚያክል ቁመት ሲጨምር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በእጥፍ ያድጋል። በአንድ ሳምንት ብቻ 23 ሳንቲ ሜትር ያህል ሊያድግ ይችላል! እናትዬው ለልጅዋ ከፍተኛ ጥበቃ የምታደርግ ሲሆን ልጅዋ የተወሰነ ርቀት እንድትዘዋወር ብትፈቅድላትም ሩቅ የማየት ችሎታ ስላላት በዓይኗ ትከታተላታለች። ቀጭኔ ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ስላላት ከአንበሳ በቀር የሚያጠቃት ጠላት የለም። ቢሆንም ይህችን የምታምር ፍጥረት የሰውን ያህል በብዛት አድኖ የገደለ የለም። ቀጭኔ በሚያምር ቆዳዋ፣ በሚጣፍጥ ሥጋዋና አንዳንዶች ምትሐታዊ ኃይል አለው በሚሉት ረዥምና ጥቁር ጭራዋ ምክንያት እጅግ ተፈላጊ ስለሆነች በአሁኑ ጊዜ የዚህች ሰላማዊ ፍጡር የወደፊት ሕልውና ስጋት ላይ ወድቋል። በአንድ ወቅት በብዙ የአፍሪካ አካባቢዎች እንደ ልብ ትታይ የነበረችው ቀጭኔ በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው በቂ ጥበቃ በሚደረግላት ፓርኮች ብቻ ሆኗል። የቀጭኔ አካላዊ ቅርጽና ግዝፈት ችግሮች ማስከተሉ አይቀርም ብሎ የሚያስብ ይኖር ይሆናል። በጣም ትልቅ ቁመትና ረዥም አንገት ስላላት የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖራትና ወደ ሁሉም የአካሏ ክፍሎች ደም እንዲደርስ ማድረግ የማይቻል ነገር ሊመስል ይችላል። ለምሳሌ ያህል ቀጭኔ አንገቷን ወደ መሬት ስታጎነብስ በስበት ኃይል ምክንያት ብዙ ደም ወደ ጭንቅላቷ ፈስሶ አንጎሏን ማጥለቅለቅ ነበረበት። ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ደሟ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ልቧ ተመልሶ ራሷን እስከ መሳት ሊያደርሳት ይገባ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ነገር አይደርስም። ለምን? የቀጭኔ የደም ዝውውር ሥርዓት በዓይነቱ ልዩ ለሆነው ለዚህች እንስሳ ቅርጽና መጠን እንዲያገለግል ሆኖ በታላቅ ጥበብ የተሠራ ነው። ልቧ ራሱ በጣም ትልቅ ሲሆን ደሙን ሦስት ሜትር ተኩል ገደማ ርቆ እስከሚገኘው እስከ አንጎላ ለመግፋት የሚያስችል አቅም አለው። በደቂቃ እስከ 170 ጊዜ የሚመታውና 7 ሳንቲ ሜትር ያህል ውፍረት ባለው ጡንቻ የተገነባው የቀጭኔ ልብ ከሰው የደም ግፊት በሦስት እጥፍ የሚበልጥ ግፊት ያመነጫል። ወደ አንጎል የሚሄደውን ደም የሚሸከመው ካሮቲድ የተባለው የደም ቧንቧና ከአንጎል ወደ ልብ የሚመለሰውን ደም የሚሸከመው ጀጉላር የተባለው የደም ቧንቧ እንዲህ ያለውን ከፍተኛ ግፊት መቋቋም የሚያስችል መጠን ሊኖራቸው ይገባል። በእርግጥም እነዚህ የደም ቧንቧዎች ከ2.5 ሳንቲ ሜትር በላይ ስፋት ያላቸው ከመሆኑም በላይ ጠንካራና የመለጠጥ ችሎታ ባላቸው ሕዋሳት የተገነቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥንካሬና የመለመጥ ችሎታ አላቸው። ቀጭኔ ከጭንቅላቷ ጎንበስ በምትልበት ጊዜ ወደ አንጎሏ የሚሄደውን የደም ፍሰት የሚቆጣጠሩ ልዩ መቆጣጠሪያዎች አሏት። አንጎልና አንገት በሚገናኙበት ቦታ ላይ ትልቁ ካሮቲድ የደም ቧንቧ ሬቴ ሚራቢሌ ተብሎ ከሚጠራ አስደናቂ የሆነ መረብ መሰል አካል ይገናኛል። በከፍተኛ ኃይል ተገፍትሮ የመጣው ደም እዚህ ጋር ሲደርስ በጣም በርካታ ወደሆኑ ትናንሽ የደም ሥሮች እንዲገባ ስለሚደረግ የደሙ ግፊት ተስተካክሎ በአንጎል ላይ ጉዳት የማያስከትል ይሆናል። ቀጭኔዋ ራስዋን ጎንበስ በምታደርግበት ጊዜ ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው መረብ ይለጠጣል፤ ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ይኮማተራል። ይህም የስበት ኃይል የሚያሳድረው ተጽዕኖ ሚዛኑን የጠበቀ እንዲሆን ማድረግና የደም ግፊቷ በእጅጉ ቀንሶ ራሷን የምትስትበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ለመከላከል ይረዳታል። የሳይንስ ሊቃውንት በጣም አስደናቂ ርዝመት ያለው የቀጭኔ አንገት ያሉት አከርካሪዎች ቁጥር ከአይጥ ወይም ከብዙዎቹ አጥቢ እንስሳ ጋር እኩል መሆኑን ሲያውቁ በጣም ተደንቀዋል! ይሁን እንጂ የቀጭኔ አከርካሪዎች በጣም ረዣዥሞችና እርስ በርሳቸው ልዩ በሆነ ሁኔታ የተሰካኩ በመሆናቸው እንደ ልብ ሊተጣጠፉ ይችላሉ። ቀጭኔ አንገቷን መጠምዘዝና ማጠፍ ስለምትችል ሁሉንም የአካሏን ክፍሎች ለመላስም ሆነ ረዣዥም የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ለመድረስ ትችላለች። \n \nጥያቄ: ቀጭኔ በልቧ እና አንጎላ መካከል ያለው ምን ያህል ርቀት ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሦስት ሜትር ተኩል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቲቪ በ1950ዎቹ እንደ ብርቅ በሚታይበት ዘመን በ1957 አ.ም ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተከፈተ፡፡ ታዲያ የመጀመሪያዋ የቲቪ ሴት አንባቢ የነበሩት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ ነበሩ፡፡ ይህ ለወይዘሮ እሌኒ ትልቅ የታሪክ አጋጣሚ ነበር፡፡ በወቅቱ ሳሙኤል ፈረንጅ አንዱ ወንድ ተናጋሪ ነበር፡፡ በኢትዮጵያ ሬድዮ በጋዜጠኝነቱና በህዝብ ግንኙነት ሙያ ያገለገሉት ወይዘሮ እሌኒ ከሰው ጋር በቀላሉ የሚግባቡ ተወዳጅ ደግ እናት ነበሩ፡፡ በበጎ አድራጎት ምግባራቸው በስፋት የሚታወቁት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ የወጣት ሴቶች ክርስቲያናዊ ማህበር ውስጥ በንቃት በመሳተፍ ማህበሩን ረድተዋል፡፡ በተጨማሪም በአንሚ ሬድዮ ከ20 አመት በፊት ያገለገሉት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ ከአለም አቀፍ መገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች ጋር የጠበቀ ቁርኝት ነበራቸው፡፡ ከዚህም ባሻገር አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሀን ወደ ሀገራችን በሚመጡበት ጊዜ ሁኔታዎችን በማመቻቸት ስራ ላይ ትልቅ ሚና አበርክተዋል፡፡ ቤታቸው ሲኬድ ሁልጊዜም ከአረንጓዴ ተክል ጋር የማይታጡት ወይዘሮ እሌኒ ነፋሻማ ቦታ ልዩ ትርጉም ይሰጣቸዋል፡፡ አንድ ከዛፍ ጋር በተያያዘ በፎቶግራፍ የታገዘ መጽሀፍም ለህትመት አብቅተዋል፡፡ በዚህም መጽሀፍ አማካይነት ስለ ሀገራችን ዛፎች በቂ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ሙከራ አድርገዋል፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ የተለያዩ ሀገሮችን ቴምብሮችን ያሰባስባሉ፡፡ በተለይ ደግሞ ለታሪክ ልዩ ፍቅር ያላቸው ወይዘሮ እሌኒ የጡረታ ጊዜያቸውን በማንበብ እና በምርምር ያሳልፉ ነበር፡፡ ወይዘሮ እሌኒ በ1959 አመተ ምህረት ከኢንጂነር ሰይፉ ለማ ጋር ጋብቻን መስርተው 3 ሴት ልጆችን ወልደው አንድ ልጅ ደግሞ አሳድገዋል፡፡ ወይዘሮ እሌኒ በተወለዱ በ79 አመታቸው ሮብ ሀምሌ 14 2013 ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን የቀብር ስነስርአታቸውም ሀሙስ ሀምሌ 15 2013 ከቀኑ በ6 ሰአት በየካ ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡ \n \nጥያቄ: ወ/ሮ እሌኒ ከትዳር አጋራቸው ጋር መቼ ትዳር መሰረቱ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ1959 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጉጃራቲ ጉጃራቲ (ગુજરાતી) በህንዳዊ-አውሮፓዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ የሚገኝ ቋንቋ ነው። በዓለሙ ውስጥ በ46 ሚልዮን ሰዎች ይናገራል፤ ከነዚህም 45.5 ሚልዮን በህንደኬ፣ 250,000 በታንዛኒያ፣ 150,000 በዩጋንዳ፣ 100,000 በፓኪስታንና 50,000 በኬንያ አሉ። በሕዝብ ብዛት የዓለሙ 23ኛ ቋንቋ ነው። በምእራብ ህንደኬ ያለው የጉጃራት ክፍላገር ይፋዊ ቋንቋ ነው። የጉጃር ሕዝብ ወደ ህንደኬ የደረሱ በ5ኛው መቶ ዘመን ሲሆን በ6ኛው መቶ ዘመን ዛሬ ጉጃራት በሚባለው አገር ሰፈሩ። የራሳቸውን ቋንቋ ቶሎ ትተው እንደ አገሩ ሰዎች ሳንስክሪት ለመናገር ጀመሩ። በ12ኛው ክፍለ ዘመን ግን ሳንስክሪት ተለውጦ ብዙ አዲስ ቋንቋዎች ተወለዱ። ከነዚሁም አንድ ጉጃራቲ ነበር። አብዛኛው ተናጋሪዎቹ የህንድ ሃይማኖት ተከታዮች ቢሆኑም ለረጅም ዘመን የእስላም ገዢዎች ስለነበሩባቸው ብዙ ቃላት የተወሰዱ ከፋርስ ሆኗል። ከዚያ በላይ በንግድ ምክንያት ብዙ ቃሎች ከፖርቱጊዝ ወይም ከእንግሊዝኛ ተበደሩ። የሚጻፍበት በራሱ ጉጃራቲ ፊደል ነው፤ ይህም ከላይኛ መስመር በማጣቱ በስተቀር የህንዲ ደቫናጋሪ ፊደል ይመስላል። \n \nጥያቄ: ጉጃራቲ ቋንቋ 50,000 ያህል ተናጋሪዎች ያሉት በየት ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በኬንያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአቡነ ጴጥሮስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ቤተክርስቲያን በአደራነት የሰጠቻቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ሕዝበ ክርስቲያኑን በጸሎታቸው እየደገፉ በትምህርታቸው እያበረቱ በማስተዳደር ላይ እንዳሉ በ፲፱፳፰ ዓ.ም. አረመኔው የኢጣልያ ፋሺስት በግፍ ሀገራችንን ለመውረር ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት በማለት ባሕርን አቋርጦ መጣ፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሀገር በመጣ ወራሪ ቀጥተኛ ተጠቂናትና ሊቃውንቷ፣ ገዳማትና አድባራቷ እንዲሁም ንዋያተ ቅድሳቷ በወራሪው የኢጣልያ ኃይል ይጨፈጨፉና ይቃጠሉ ገቡ ፡፡ ይህ ግፍ በዕውቀት ኮትኩታ ባሳደገቻቸው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ሲፈጸም ያዩት ብፁዕነታቸው ወራሪውን ኃይል ከኢትዮጵያውያኑ አርበኞች ጋር በመሆን በጸሎት ሊዋጉት ወሰኑ፡፡ ይሁን እንጂ ጠላት በመላ ከተማዋ ባሰማራቸው በርካታ ባንዳዎች መካከል ብፁዕነታቸው እንዳሰቡት ሊንቀሳቀሱ አልቻሉም፡፡ በመጨረሻ እዚሁ ከተማ ተሰውሬ መኖር አልፈልግም፤ ወደ ገጠር ፊቴን አልመልስም በማለት ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም በወቅቱ የኢጣሊያ እንደራሴ ለነበሩት ራስ ኃይሉ እጃቸውን ሰጡ፡፡ እራስ ኃይሉም ወዲያውኑ ለግራዚያኒ አሳልፈው ሰጧቸው፡፡ ሐምሌ 22 ቀን 1928 አቡነ ጴጥሮስ ተይዘው ወደ ግራዚያኒ ቀረቡ ፡፡ ጠላት ድል ተደርጎ ሀገራችን ነፃነቷን ከተቀዳጀት በኋላ የብፁዕነታቸውን አኩሪ ታሪክ ትውልድ ሲያዘክርላቸው እንዲኖር መታሰቢያ ይሆናቸው ዘንድ በግርማዊ ቀዳማዊ ንጉሠ ነገሥት አሳሳቢነት ሐምሌ 16 ቀን 1938 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ እምብርት ሐውልት ቆሞላቸዋል፡፡ ከድል በኋላ የብፁዕነታቸ ሐውልት ተመርቆ የቤተ መንግሥቱም ሆኑ የቤተ ክህነቱ ባለሥልጣናት አበባ ጉንጉን ከሐውልቱ ሥር ሲያስቀምጡ ከቤተ ክህነት ካስቀመጡት አባቶች አንዱ በ1921 ዓ.ም አብረዋቸው የተሾሙት ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ ነበሩ፡፡ ትውልድ ሁሉ ለሀገር ክብርና ለነጻነት በተከፈለው፡፡ የብዕፁነታቸው ሕይወት እንዲማርበትና ሕያው ምስክር ሆኖ እንዲኖር የቆመላቸውን ሐውልት ኢትዮጵያዊያን ሁሉ በክብር ይጠብቁታል ፡፡ የእኝህን ታላቅና ቅዱስ ሰማዕት አባት ክብርና ተጋድሎ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ከአምስት ዓመት በፊት ቅዱስ /ሰማዕት/ ብሎ በማጽደቅ በስማቸው በቅድስና ማዕረግን ሰጥቶ በስማቸው ታቦት ተቀርጾ ቤተክርስቲያን እንዲሰራላቸው ወስኗል ፡፡ ይህም በተወለዱበት በሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሃገረሰብከት በፍቼ ከተማ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ተግባራዊ ሆኗል፡፡ ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ፣ አርበኛ፣ ጀግና፣ ጳጳስ፣ ሰማዕት ቅዱስም የሆኑ አባት ናቸው ፡፡ \n \nጥያቄ: ጣሊያን ፋሺስት ዳግም ወደ ኢትዮጵያ መቼ መጣ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ፲፱፳፰ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሺስቶሶሚሲስ ሺስሰቶሶሚያሲስ (ቢልሃርዚያ እና ካታያማ ትኩሳት በመባል ይታወቃል፡፡) በሽታው የሚተላለፈው ጥገኛ ትላትሎች በሆነው የ ሺስቶሶማ የህዋስ አይነት ነው፡፡ የ ሽንት መተላለፊያ ወይም አንጀት ሊያጠቃ ይችላል። የህመሙ ምልክት የሆድ ህመም፣ ተቅማጥ፣ ደም የተቀላቀለበት ሰገራ ወይም በሽንት ላይ ደም መታየትን ያጠቃልላል። ለረጅም ጊዜ ህመሙ የቆየበት ሰው የጉበት ህመም፣ የኩላሊት ስራ ማቆም፣ መሃንነት ፣ ወይም የፊኛ ካንሰር ሊያስከትብ ይችላል፡፡ በልጆች ላይ ዝቅተኛ እድገትና የመማር ችግር ሊያስከትል ይችላል። ቢልሃርዝያ በሽታው የሚሰራጨው ትላትሎቹ ያሉበት ውሀ ላይ በሚፈጠር የቆዳ ንክኪ ነው። እነዚህ ትላትሎች የሚመነጩት ከተበከሉ ቀንድ አውጣዎች ነው፡፡ ይህ በሽታ በታዳጊ ሀገራት በሚነኙ ታዳጊዎች ላይ የተለመደ ሲሆን ምክንያቱም ልጆቹ በተበከለ ውሃ የመጫወታቸው አጋጣሚ ሰፊ በመሆኑ ነው፡፡ ሌላው ደግሞ በእለት ከእለት ስራ አማካኝነት ማለትም ገበሬዎች፣ አሳ አጥማጆችና ሌሎች የተበከለውን ውሀ የሚጠቀሙ ሰዎች የበሽታው ስጋት የሚያጠቃልላቸው ቡድኖች ናቸው። ሄልመንት በሽታዎች በሚባለው ቡድን ውስጥ ይጠቃለላሉ። ምርመመራው የሚደረገው የትሉን እንቁላሎች በሽንት ወይም ሰገራ ላይ በመመርመር ነው፡፡ በደም ላይ ፀረ እንግዳ አካል በመፈለግ ማረጋገጥም ይቻላል። በሽታውን የመከላከያ መንገድ ንፁህ ውህ አቅርቦትን ማሻሻልና የቀንድኣውጣ ቊጥርን መቀነስ ነው፡፡ ሲስቶሶሚያሲስ በዓለም ላይ ወደ 210 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ያጠቃል፣ እንዲሁም የሚገመተው ከ 12 000 እስከ 200,000 የሚሆነው ሕዝብ በአመት ውስጥ ይሞታል ተብሎ ይገመታል፡፡ በሽታው በስፋት የሚታየው በ አፍሪካ ፣ እንዲሁም በ እስያ ና ደቡም አሜሪካ ነው። ወደ 700 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ፣ ከ70 በላይ ሃገራት፣ በሽታው በስፋት በተሰራጨበት አካባቢ ይኖራል፡፡ ሲስቶሶሚሲሰ ከወባ ወይም ማላሪያ ቀፅሎ በሁለተኛነት ያለ፣ እንደ ትላትል ትልቅ የኢኮኖሚ ተፅእኖ ያለው በሽታ ነው። ከጥንት ጀምሮ እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ፣ ሲስቶሶሚሲሰ የ በሽንት ውስጥ ያለ ደም ምልክት የሚታየው በስሕተት እንደ የወንድ አይነት ወር አበባ እየተባለ በ ግብፅ እናም ለወንዶች ልጆች እንደ rite of የአምልኮ መተላለፊያ ተደርጎ ይታይ ነበር፡፡ የሚመደበው ችላ ከተባሉት የትሮፒካል በሽታ ስር ነው። \n \nጥያቄ: የቪስቶሶቶሚሲስ በሽታ ሲቆይ በአዋቂዎች ላይ ምን ሊያስከትል ይችላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የጉበት ህመም፣ የኩላሊት ስራ ማቆም፣ መሃንነት ፣ ወይም የፊኛ ካንሰር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nጨኖ ጨኖ ግራጫ ቢጤ የሆነ፣ ፈርጠም ያለ፣ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እስከ ደቡብ አፍሪቃ፣ በተጨማሪም በኮንጎ ደኖች የሚገኝ ዝንጀሮ ነው። በኢትዮጵያ የሚገኘው ዓይነት ጨኖ የፀጉሩ ቀለም ግራጫና ጥቁር የሆነ፣ ፊቱ የጠቆረ ሰማያዊ የሆነ፣ አገጭና አንገቱ ነጭ ነው። የወንዶቹ ክብደት እስከ 12 ኪ.ግ. ሲሆን፤ አማካዩ 4.5 ኪ.ግ ይመዝናሉ። ጨኖ የደን ዝንጀሮ ነው። የደን ዝንጀሮች ብዙ ጊዜ ከዝናባማ ሥፍራዎች ደኖች ውጪ አይገኙም። ጨኖ ግን ከነዚህ ደኖች ውጪም በሚገኙ ደኖች ውስጥ ይኖራል። በኢትዮጵያ፣ በጎደሬ ደን ውስጥ፣ ቴፒ አጠገብ ሜጢ አካባቢ ይገኛሉ። በተራራማ ሥፍራዎች ደኖችም እስከ 3000 ሜትር ከፍታ ድረስ ይገኛሉ። እጅጉን በዛፍ ላይ የሚገኝ ዝንጀሮ ነው። የሚገኘው በደን ዛፎች ግማሽ ላይ ነው። በተለያዩ ዓይነት ተግባሮች መገለጫ የሚሆኑ ሰባት ዓይነት ድምፆች አሏቸው። በቡድናቸው ውስጥ የሚታየው አብዛኛው ፀብ፣ በዋናው ወንድና ለአካለ መጠን ባልደረሱና ጎረምሳ ወንዶች መሃል የሚታየው ነው። በሴቶቹና ሕፃናትን በሚገድሉ ወንዶች መኻከል ከባድ ግጭት ያድጋል። በቡድኖች መኻከል የሚደረግ ግጭት የሚሆነው አልፎ አልፎ ነው። እንዲህ ያለ ግጭት የሚነሳው በድንበር አካባቢ በምግብ ሽኩቻ የተነሳ ነው። የእርግዝና ጊዜአቸውን 140 ቀን ነው። የልጆቻቸውን እድገትም ቀስ ያለ ነው። ከወለዱ ወዲያ ለሚቀጥለው እርግዝና 15 ወራት መቆየት አለባቸው። \n \nጥያቄ: ጨኖዎች በተራራማ ሥፍራዎች በምን ያህል ከፍታ ላይ ይገኛሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ እስከ 3000 ሜትር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጉጃራቲ ጉጃራቲ (ગુજરાતી) በህንዳዊ-አውሮፓዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ የሚገኝ ቋንቋ ነው። በዓለሙ ውስጥ በ46 ሚልዮን ሰዎች ይናገራል፤ ከነዚህም 45.5 ሚልዮን በህንደኬ፣ 250,000 በታንዛኒያ፣ 150,000 በዩጋንዳ፣ 100,000 በፓኪስታንና 50,000 በኬንያ አሉ። በሕዝብ ብዛት የዓለሙ 23ኛ ቋንቋ ነው። በምእራብ ህንደኬ ያለው የጉጃራት ክፍላገር ይፋዊ ቋንቋ ነው። የጉጃር ሕዝብ ወደ ህንደኬ የደረሱ በ5ኛው መቶ ዘመን ሲሆን በ6ኛው መቶ ዘመን ዛሬ ጉጃራት በሚባለው አገር ሰፈሩ። የራሳቸውን ቋንቋ ቶሎ ትተው እንደ አገሩ ሰዎች ሳንስክሪት ለመናገር ጀመሩ። በ12ኛው ክፍለ ዘመን ግን ሳንስክሪት ተለውጦ ብዙ አዲስ ቋንቋዎች ተወለዱ። ከነዚሁም አንድ ጉጃራቲ ነበር። አብዛኛው ተናጋሪዎቹ የህንድ ሃይማኖት ተከታዮች ቢሆኑም ለረጅም ዘመን የእስላም ገዢዎች ስለነበሩባቸው ብዙ ቃላት የተወሰዱ ከፋርስ ሆኗል። ከዚያ በላይ በንግድ ምክንያት ብዙ ቃሎች ከፖርቱጊዝ ወይም ከእንግሊዝኛ ተበደሩ። የሚጻፍበት በራሱ ጉጃራቲ ፊደል ነው፤ ይህም ከላይኛ መስመር በማጣቱ በስተቀር የህንዲ ደቫናጋሪ ፊደል ይመስላል። \n \nጥያቄ: ጉጃራቲ ቋንቋ በኬንያ ምን ያህል ተናጋሪዎች አሉት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 50,000 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበማደግ ላይ ባሉ አገራት የሚኖሩ ህዝቦች ግንባር ቀደም ገዳይ ከሚባሉት በሽታዎች አንዱ የሆነውን የቲቢ በሽታ ለማስቆም የሚያስችል ”EndTB” የተሰኘ ንቅናቄ ተካሄደ፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ባለፈው ረቡዕ በሒልተን ሆቴል በይፋ ያስጀመረው ቲቢን እናስቁም ንቅናቄ እ.ኤ.አ በ2032 በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ከ100 ሺህ አስር ብቻ ለማድረስ የታለመ ነው፡፡ ከአዳሱ የፈረንጆች ዓመት እስከ 2032 ዓ.ም ይደረጋል በተባለው በዚሁ “ቲቢን እናስቁም” ንቅናቄ፤ አገራት ሁሉ፤ ተሳታፊ በመሆን በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ፍጥነት እየተሰራጨ ያለውን የቲቢ በሽታ ለመግታትና በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ለመቀነስ በትጋት እንደሚሰራ ተገልጿል፡፡ በሒልተን ሆቴል በተካሄደው ፕሮግራም ላይ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀረቡት የግሎባል ቲቢ ፕሮግራም ዳይሬክተር ዶ/ር ማርዮ ራቨግሊዮን እንደገለፁት፤ በሽታው በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው ስርጭት 133 ሰዎች ከ100 ሺህ ሰዎች ሲሆን በኢትዮጵያ ቁጥሩ 200 ሰዎች ከ100 ሺህ ሰዎች ይደርሳል ብለዋል፡፡ በሽታውን ለማስቆም በተያዘው ዕቅድ መሰረትም፤ እ.ኤ.አ ከ2016-2032 ዓ.ም ድረስ በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ከ100ሺ አስር ለማድረስ መታቀዱንም ተናግረዋል፡፡ ዕቅዱ እንዲሳካም አገራት ከፍተኛ ሥራ እንደሚጠበቅባቸውና ለተግባራዊነቱም የመንግስታቱን ቁርጠኝነት የሚጠይቅ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የግሎባል ቲቢ ፕሮግራም ዳይሬክተር ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ዶ/ር ማርዮ ራቨግሊዮን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአቡነ ጴጥሮስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ቤተክርስቲያን በአደራነት የሰጠቻቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ሕዝበ ክርስቲያኑን በጸሎታቸው እየደገፉ በትምህርታቸው እያበረቱ በማስተዳደር ላይ እንዳሉ በ፲፱፳፰ ዓ.ም. አረመኔው የኢጣልያ ፋሺስት በግፍ ሀገራችንን ለመውረር ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት በማለት ባሕርን አቋርጦ መጣ፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሀገር በመጣ ወራሪ ቀጥተኛ ተጠቂናትና ሊቃውንቷ፣ ገዳማትና አድባራቷ እንዲሁም ንዋያተ ቅድሳቷ በወራሪው የኢጣልያ ኃይል ይጨፈጨፉና ይቃጠሉ ገቡ ፡፡ ይህ ግፍ በዕውቀት ኮትኩታ ባሳደገቻቸው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ሲፈጸም ያዩት ብፁዕነታቸው ወራሪውን ኃይል ከኢትዮጵያውያኑ አርበኞች ጋር በመሆን በጸሎት ሊዋጉት ወሰኑ፡፡ ይሁን እንጂ ጠላት በመላ ከተማዋ ባሰማራቸው በርካታ ባንዳዎች መካከል ብፁዕነታቸው እንዳሰቡት ሊንቀሳቀሱ አልቻሉም፡፡ በመጨረሻ እዚሁ ከተማ ተሰውሬ መኖር አልፈልግም፤ ወደ ገጠር ፊቴን አልመልስም በማለት ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም በወቅቱ የኢጣሊያ እንደራሴ ለነበሩት ራስ ኃይሉ እጃቸውን ሰጡ፡፡ እራስ ኃይሉም ወዲያውኑ ለግራዚያኒ አሳልፈው ሰጧቸው፡፡ ሐምሌ 22 ቀን 1928 አቡነ ጴጥሮስ ተይዘው ወደ ግራዚያኒ ቀረቡ ፡፡ ጠላት ድል ተደርጎ ሀገራችን ነፃነቷን ከተቀዳጀት በኋላ የብፁዕነታቸውን አኩሪ ታሪክ ትውልድ ሲያዘክርላቸው እንዲኖር መታሰቢያ ይሆናቸው ዘንድ በግርማዊ ቀዳማዊ ንጉሠ ነገሥት አሳሳቢነት ሐምሌ 16 ቀን 1938 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ እምብርት ሐውልት ቆሞላቸዋል፡፡ ከድል በኋላ የብፁዕነታቸ ሐውልት ተመርቆ የቤተ መንግሥቱም ሆኑ የቤተ ክህነቱ ባለሥልጣናት አበባ ጉንጉን ከሐውልቱ ሥር ሲያስቀምጡ ከቤተ ክህነት ካስቀመጡት አባቶች አንዱ በ1921 ዓ.ም አብረዋቸው የተሾሙት ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ ነበሩ፡፡ ትውልድ ሁሉ ለሀገር ክብርና ለነጻነት በተከፈለው፡፡ የብዕፁነታቸው ሕይወት እንዲማርበትና ሕያው ምስክር ሆኖ እንዲኖር የቆመላቸውን ሐውልት ኢትዮጵያዊያን ሁሉ በክብር ይጠብቁታል ፡፡ የእኝህን ታላቅና ቅዱስ ሰማዕት አባት ክብርና ተጋድሎ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ከአምስት ዓመት በፊት ቅዱስ /ሰማዕት/ ብሎ በማጽደቅ በስማቸው በቅድስና ማዕረግን ሰጥቶ በስማቸው ታቦት ተቀርጾ ቤተክርስቲያን እንዲሰራላቸው ወስኗል ፡፡ ይህም በተወለዱበት በሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሃገረሰብከት በፍቼ ከተማ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ተግባራዊ ሆኗል፡፡ ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ፣ አርበኛ፣ ጀግና፣ ጳጳስ፣ ሰማዕት ቅዱስም የሆኑ አባት ናቸው ፡፡ \n \nጥያቄ: የብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሐውልት መቼ ተሰራ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሐምሌ 16 ቀን 1938 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአሸናፊ ከበደ ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ አዲስ አበባ ግንቦት ፰ ቀን ፲፱፻፴ ዓ/ም ተወለዱ። አባታቸው ግራዝማች ከበደ አድነው ሲሆኑ ክልጅነታቸው ጀምሮ የሙዚቃ ስሜትንና ፍቅር ያሳደሩባቸው እናታቸው ወይዘሮ ፋንታዬ ነከሬ ነበሩ። አያታቸው ሊቀመኳስ አድነው ጎሹ ደግሞ የአድዋ አርበኛ እናየንግሥት ዘውዲቱም ታማኝ አማካሪ እንደነበሩ ይነገራል። የሙዚቃ ፍቅርን ገና በልጅነታቸው ያሳደሩባቸው እናታቸው ሲሆኑ ታዳጊው አሸናፊ ገና የዘጠኝ ዓመት ልጅ ሳሉ እኒህ የሚያፈቅሯቸውና ዕድሜ ልካቸውን በኀዘን የሚስታውሷቸው እናታቸው ሞተውባቸዋል። መሠረታዊ ትምህርታቸውን በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት እና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ኮከበ ጽባሕ) ካጠናቀቁ በኋላ በሐረር የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ በኒው ዮርክ ክፍለ-ሀገር ከሚገኘው የሮቼስተር ዩኒቨርሲቲ፣ “ኢስትማን የሙዚቃ ትምህርት ቤት” በ፲፱፻፶፬ ዓ/ም በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመረቁ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው፤ የያሬድ ሙዚቃ ትምሕርት ቤትን መሠረቱ። የዚሁ ትምህርት ቤትም የመጀመሪያው ዳይሬክቶር ከመሆናቸውም ባሻገር በአዲስ አበባው የወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማኅበር (ወ.ወ.ክ.ማ Y.M.C.A.)፤ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የበጎ አድራጎት ድርጅት መርሓ-ዕውራን ትምህርት ቤት እና በመሳሰሉ የወጣቶች ማኅበራት እየተገኙ የሙዚቃ ትምህርት ይሰጡ ነበር። \n \nጥያቄ: የፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ አባት ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ግራዝማች ከበደ አድነው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nግንቦት ፳፮ ቀን፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፷፮ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት ፷፩ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፺፱ ቀናት ይቀራሉ። ፲፱፻፶፬ ዓ/ም - የኤር ፍራንስ ቦይንግ ፯፻፯ አየር ዠበብ ከፓሪስ ኦርሊ ማረፊያ ተነስቶ ወደ አትላንታ ለመብረር ሲነሳ በደረሰበት አደጋ ፻፴ መንገደኞችና የዓየር መንገዱ ባልደረቦች ሞተዋል። ፲፱፻፶፭ ዓ/ም - የአሜሪካው ‘ኖርዝ ዌስት ኤየርላይንስ’ ዲ-ሲ-፯ አየር ዠበብ በረራ በሰላማዊ ውቅያኖስ ላይ ውድቆ ሲሰምጥ ፻፩ ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኮንኮርድ አየር ዠበብ አምሳል የተሠራው የሶቪዬት ቱፖሌቭ ቲ-ዩ-፻፵፬ ፈረንሳይ ላይ በደረሰበት የበረራ አደጋ ሲከሰከስ ፲፬ ሰዎች ሞተዋል። ፲፱፻፺፰ ዓ/ም - የቀድሞዋ ዩጎዝላቪያ አካላት የነበሩት ሰርቢያ እና ሞንቴኔግሮ የውሕደት ስምምነታቸውን በሞንቴኔግሮ የሉዐላዊነት አዋጅ ምክንያት ሰረዙ። ፲፯፻፷፭ ዓ/ም - የዓፄ በካፋ ሚስት የነበሩት እቴጌ ምንትዋብ በዚህ ዕለት አርፈው በቁስቋም ደብረ ጸሐይ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። \n \nጥያቄ: በኮንኮርድ አየር ዠበብ አምሳል የተሠራው የሶቪዬት ቱፖሌቭ ቲ-ዩ-፻፵፬ ፈረንሳይ ላይ በደረሰበት የበረራ አደጋ የተከሰተው መቼ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ፲፱፻፷፭ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nመዓዛ ብሩ በእሁድ የሬዲዮ ፕሮግራም ታቀርባቸው የነበሩት ሥራዎች ይዘት ማህበራዊ ሕይወት እንዲሠምር በመጣር ላይ ያተኮሩ ሆነው ግልጽ፣ ቀላልና ለዛ ያልተለያቸው ስለነበሩ ከሶስት አሥርት ዓመታት በኋላም ትውስታቸው ከአድማጭ ህሊና አልጠፉም፡፡ በዚሁ ፕሮግራም ላይ መዓዛ ካበረከተቻቸው የፈጠራ ሥራዎቿ ውስጥ ጎልቶ የሚታወሰው “የአዲሱ ቤተሰብ” የተሰኘ ባለ ሰማንያ ስድስት ክፍል ድራማ ሲሆን በዘመኑ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ሁሉም የሚያደምጠው ተወዳጅ የቤተሰብ ድራማ ነበር፡፡ መዓዛ በ “መርሀ ስፖርት” እና በሬዲዮ መካከል ሆና ከአራት ዓመት በላይ ከቆየች በኋላ በ1979 ዓ.ም የባህል ሚኒስቴርን ለቃ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተቀጠረች፡፡ አዲሱን መስሪያ ቤቷን ከተቀላቀለችበት ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ከሬዲዮ እየራቀች መጣች፡፡ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ውስጥ የቆየችው ለሶስት ዓመታት ያህል ሲሆን ከዚያ በኋላ የግሏን የማስታወቂያ ሥራ ድርጅት መሥርታ የራስዋ ተቀጣሪ ሆናለች፡፡ ከ1979 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 1992 ዓ.ም ባሉት የአስራ ሶስት ዓመታት ጊዜ ግን መዓዛና ሬዲዮ ተራራቁ፡፡ መዓዛና ሬዲዮ ዳግም የተዋደዱት ከላይ እንደተገለጸው በ1992 ዓ.ም ሳምንታዊውን የ “ጨዋታ” ፕሮግራም በኤፍ ኤም 97.1 ከተፈሪ ዓለሙ ጋር በጋራ ማቅረብ ሲጀምሩ ነበር፡፡ የ “ጨዋታ” ፕሮግራም እስከ 1999 ዓ.ም ድረስ በአድማጮቹ እንደተወደደ በኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ላይ ሲቀርብ ቆይቷል፡፡ መንግሥት ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለት የኤፍ ኤም ሬዲዮ ፈቃዶችን ለግሉ ዘርፍ ለመስጠት ሲዘጋጅ፣ ዝርዝር የሥራ እቅድ አቅርባ ባመለከተችው መሠረት፤ ከረጅም ጊዜ ቆይታ በኋላ ከአስር አመልካቾች መካከል አንዷ ሆና የመጀመሪያ የግል የኤፍ ኤም ሬዲዮ ባለቤት ያደረጋትን ፈቃድ ተቀበለች፡፡ መዓዛ የሬዲዮ ማሰራጫ መሳሪያዎችን ውድነት፣ የማሰራጫ ቦታ እና የባለሙያ እጦትን ተቋቁማ ሸገር 102.1 ኤፍ ኤም ሬዲዮን በታህሳስ 1999 ዓ.ም አበረከተችልን፡፡ ባለትዳርና የሶስት ልጆች እናት የሆነችው መዓዛ እንደ ባለቤት፣ ሥራ አስኪያጅና ጋዜጠኛ በመሆን በኢትዮጵያ ተወዳጁንና የመጀመሪያውን የግል የኤፍ ኤም ሬዲዮ ጣቢያ ትመራለች፡ “ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!”እያለች:: \n \nጥያቄ: መዓዛ ብሩ ስንት ልጆች አሉዋት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሶስት ልጆች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአይቮሪኮስት በትምህርት ቤቶች የመማሪያ ክፍሎችን ለመገንባት የተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶችን እየተጠቀመች ነው። በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሃገር አይቮሪኮስት ከፍተኛ የመማሪያ ክፍል እጥረት እንዳለ ይነገራል። በዚህ ሳቢያም 1 ነጥብ 6 ሚሊየን ያህል ህፃናት ወደ ትምህር ቤት እንደማይሄዱ መረጃዎች ያመለክታሉ። ይህን የመማሪያ ክፍል እጥረት ለመቅረፍም አንድ የኮሎምቢያ ኩባንያ ከተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) ጋር በመተባበር በቆሻሻ መጣያ ስፍራ የተከማቹ የፕላስቲክ ውጤቶችን በመጠቀም የመማሪያ ክፍሎችን መስራት ጀምሯል። ከፈረንጆቹ 2018 ጀምሮም ከተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶች 26 የመማሪያ ክፍሎች ተሰርተዋል ነው የተባለው። በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ውስጥም 528 የመማሪያ ክፍሎችን ለመገንባት እቅድ የተያዘ ሲሆን፥ በፕላስቲክ የሚሰሩት መማሪያ ክፍሎች በመደበኛነት ከሚሰሩት ክፍሎች ከወጪ አንጻር በግማሽ ይቀንሳሉም ተብሏል። የመማሪያ ክፍሎቹ የወዳደቁ የፕላስቲክ ውጤቶችን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል ብቻ የሚሰሩና ምንም አይነት ብሎኬትም ሆነ አሸዋን የማይጠቀሙ ናቸው። አሁን የተጀመረው ይህ የፈጠራ ስራ ታዲያ በቀጣዮቹ ሁለት አመታት ትምህርትን ለ25 ሺህ ህጻናት ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያስችልም ዩኒሴፍ ገልጿል። በተጨማሪም ዩኒሴፍ በአይቮሪኮስት የፕላስቲክ ጡብ ማምረቻ ፋብሪካ አስገንብቷል። ፋብሪካው ያለውን የመማሪያ ክፍል እጥረት ከመቅረፉም ባሻገር የተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶችን ለፋብሪካው የሚያቀርቡ ሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል። አይቮሪኮስት ከምታስወግደው የፕላስቲክ ተረፈ ምርት ውስጥ 5 በመቶውን ብቻ ጥቅም ላይ ማዋሏ ለፕሮጀክቱ መሳካት ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ታምኖበታል። ምንጭ፦ ቢቢሲ \n \nጥያቄ: የኮሎምቢያ ኩባንያ ከተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) ጋር በመተባበር የተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶችን በመጠቀም የመማሪያ ክፍሎችን እየሰራ ያለው የት ሀገር ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አይቮሪኮስት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nታኅሣሥ ፳፫ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፻፲፫ተኛው እና የመፀው ወቅት ፹፰ተኛው ቀን ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየወሩ ፳፫ኛ ቀን የሰማዕታትን ዓለቃ ቅዱስ ጊዮርጊስንን ታስታውሳለች። ፲፯፻፷፰ ዓ/ም - የእንግሊዝ ሠራዊት የክዌቤክ ከተማን ከአሜሪካ አስመለሰ። ፲፯፻፺፮ ዓ/ም - በሀይቲ ደሴት የፈረንሳይ ሉዐላዊነት ሲያከትም ደሴቷ በሰሜን አሜሪካ አኅጉር ከአሜሪካ ኅብረት ተከትላ ሁለተኛዋ ነፃ ሪፑብሊክ ሆነች። ፲፰፻ ዓ/ም - በባርነት የተገዙ ሰዎች ወደ አሜሪካ ኅብረት እንዳይገቡ የሚከለክል ሕግ ተደነገገ። ፲፱፻፲፯ ዓ/ም - ብርሃንና ሰላም ጋዜጣ ተመሰረተ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የ፩ሚሊዮን ፱መቶ ሺ ኪሎ የመዳብ ሽያጭ ወደጃፓን ላከች። መዳቡ በኤርትራ ውስጥ ከሚገኘው የድባሮ መዳብ ማዕድን ቁፋሮ የተገኘ ነው። ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ የጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት ባንኮችንና የኢንሹራንስ ኩባንያዎችን የብሔራዊ ንብረት አድርጎ ወረሰ። ፲፱፻፹፱ ዓ/ም - ጋናዊው ዲፕሎማት ኮፊ አናን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ፯ተኛው ዋና ጸሐፊ ሆነው ተሾሙ። \n \nጥያቄ: በባርነት የተገዙ ሰዎች ወደ አሜሪካ ኅብረት እንዳይገቡ የሚከለክል ሕግ የተደነገገ መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ፲፰፻ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሌሎች የፍልስፍና ባህሎች ከምዕራባውያን ፍልስፍና በተለየ በነዚህ ጉዳዮች ላይ በዙም አላተኮሩም። ምንም እንኳን የሂንዱ ፍልስፍና በዚህ አንፃር ከምዕራባውያኑ ቢመሳሰለም እስከ 19ኛው ምዕት-አመት ድረስ በኮሪይኛ፣ በጃፓንኛ፣ እና በቻይንኛ ውስጥ \"ፍልስፍና\" የሚል ቃል ይገኝ አልነበረም። በተለይ የቻይና ፈላስፎች ከግሪኮቹ ለየት ያለ የምደባ ስርዓት ይከተሉ ነበር። የምዕራቡ አለም ፍልስፍና የሚጀምረው ከግሪኮች ሲሆን የመጀመሪያው ፈላስፋ ተብሎ የሚታወቀው ታሊዝ ነው። ይህ ሰው የኖረበትን ጊዜ ለማወቅ ብዙም አስቸጋሪ አይደለም። ይኸውም በ593 ዓክልበ. (ዓም) የፀሃይ ግርዶሽ እንደሚኖር በመተንበዩ ከዚህ ጊዜ የተወሰነ አመት ቀደመ ብሎ ማይሌጠስ በተባለችው የትንሹ እስያ (የአሁኑ ቱርክ) ክፍል እንደተወለደ የታወቀ ነው። ታሊዝ ዓለም እና በውስጡ ያሉ ነገሮች ሁሉ ከውሃ እንደተፈጠሩ ያምን ነበረ። ከሱ በኋላ የተነሱ የግሪክ ፈላስፎች የሱኑ መንገድ በመከተል ዓለም ከአንድ ወይም ከሌላ ነገረ እንደተፈጠረች አስተምረዋል። ለምሳሌ አናክሲሜነስ የዓለም ጥንተመሰረቷ አየር ነው ሲል፣ ሄራቅሊጠስ እሳት ነው ብሏል። አናክሲማንደር ከነዚህ ሁሉ ለየት በማለት የዓለም መሰረቷ ይህ ነው የማይባል «apeiron» ወይም የትየለሌ የሆነ ነገር ነው ይላል። የምእራቡን ዓለም ፍልስፍና እስክ 1900 ድረስ ቅርጽ እንዳስያዙ የሚነግርላቸው ፈላስፋዎች የሚከተሉት ናቸው፡ ሶቅራጥስ፣ አሪስጣጣሪስ፣ ፕላጦ፣ አክዊናስ፣ ኤራስመስ፣ ማኪአቬሌ፣ ቶማስ ሞር፣ ሞንታጝ፣ ግሮቲየስ፣ ዴካርት፣ ሆበስ፣ ስፒኖዛ፣ ሎክ፣ ሌብኒሽት፣ በርክሌ፣ ሑሜ፣ ቮልቴይ፣ ሩሶ፣ ካንት፣ ሺለር፣ ሄግል፣ ሾፐናዎር፣ ጆን ኦስቲን፣ ጄ.ኤስ. ሚል፣ ኮምቴ፣ ዳርዊን፣ ማርክስ፣ እንግልስ፣ ፍሬደሪሕ ኚሼ፣ ዱርካሂም የምስራቁ አለም ፍልስፍና መነሻ ኢትዮጲያ ናት፡፡እንደውም የመላው አለም፡፡ በተለይ ኮከባቸው ጀምኒ የሆኑት የሐበሻ ተወላጆች የኮከባቸውን ሀያልነት በመጠቀም ወደ አረቡ አለም በመገስገስ የምድራችንን የፍልስፍና መንገድ ቀይሠዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ታሊዝ የተወለደበት ቦታ የቀድሞ ስም ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ማይሌጠስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየኒያ ፋውንዴሽን እና የጆይ ኦውቲዝም ማዕከል መሥራች ወይዘሮ ዘሚ የኑስ በኮሮና ቫይረስ ፅኑ ህክምና ማዕከል ውስጥ በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ህይወታቸው ማለፉ ተነገረ። ዘሚ የኑስ በአሁኑ ሰአት ከ200 በላይ ለሚሆኑ የአእምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸውን ልጆች እንክብካቤ እያደረጉ እንደሚገኙ ከቅርብ ቤተሰቦቻቸው ያገኘውን መረጃ ጠቅሶ ኢዜአ ዘግቧል። \n \nጥያቄ: ወይዘሮ ዘሚ የኑስ በምን ምክንያት ሞቱ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በኮሮና ቫይረስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኢትዮጵያ በዓለም ዉስጥ ክሚገኙ ጥንታዊ አገሮች ኢትዮጵያ ቀዳሚ በመሆን ከሁሉም የበለጠ ረጅም እድሜ አስቆጥራለች፡፡ በግእዝ/ዓማርኛ እና በመጽሀፍ ቅዱስ ከተመዘገቡት ተጨባጭ መረጃዎች በተጨማሪ አምስት ሚሊዮን አመት የሚሆነውና በጣም ረጅም እድሜ ያስቆጠረው የሰው ቅሪት የተገኘው በኢትዮጵያ አዋሽ ሸለቆ አካባቢ ሲሆን ይህም፣ 3.2 ሚሊዮን አመት የሆነውን እዛው አካባቢ የተገኘውን የሉሲን (ድንቅነሽን) አጽም በእድሜ ይበልጣል፡፡ ግብጽን ሲገዛ የነበረው ሄሮደስ የሚባለው ንጉስ ከክርስቶስ ልደት በፊት በአምስተኛው ክፍለ ዘመን የነበረው ታሪክ ፀሀፊ የጥንቷን ኢትዮጵያ በጽሁፎቹ ላይ ይገልፃታል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ላይም ብዙ ግዜ የምትወሳ ስትሖን በተለይም ብሉይ ኪዳን ላይም የንግስት ሳባ (መከዳ) ኢየሩሳሌም መሄድና ለንጉስ ሰለሞን ከባድ የሆኑ ጥያቄዎች ማንሳቷ ተጽፏል፡፡ ኢትዮጵያ ዛሬ ያላትን መልክ እንድትይዝ ያደረጋት ንጉስ ሚኒሊክ የንግስት ሳባና የንጉስ ሰለሞን ዘር ናቸው፡፡ የንግስት ሳባ ቤተ መንግስት ፍርስራሽ ሰሜን ኢትዮጵያ ውስጥ በአክሱም አካባቢ ይገኛል፡፡ ክርስትናን ኢትዮጵያዉያን ከመቀበላቸዉ በፊት (ኣስቅድመዉ) የኦሪትን ህግ ሰለሚያዉቁ ኣመተ ዓለምን ወደታች እየቆጠሩ የጌታን መወለድ ይጠብቁ ሰለነበረ ክርስትናን ለመቀበል ኣላስቸገራቸዉም፡፡ ነገር ግን በሰባተኛው ክፍለ ዘመን በእስልምና መስፋፋት ምክንያት ኢትዮጵያ ከአውሮፖውያኑ ክርስትያን ርቃ ቆይታለች፡፡ \n \nጥያቄ: ሉሲ የተባለችው የሰው ልጅ ቅሪተ አካል ከተገኘች ስንት ዓመት ይሆናታል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 3.2 ሚሊዮን አመት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዝግመተ ለውጥ የአንድ ሕይወት ያለው ማህብረሰብ የዘር ውርስ ባህሪይ ከትውልድ ወደትውልድ እየተቀየረ መሄዱ ዝግመተ ለውጥ ይባላል። ቻርለስ ዳርዊን ይህን ኩነት በማስተዋልና በሳይንሳዊ አመክንዮ አሰደግፎ በመተንተኑ የመጀመሪያው ሰው ነው። ዳርዊን በተጨማሪ የተፈጥሮ ምርጫ ባለው ኅልዮቱ ሕይወት ያላቸው ማህበረሰቦች ዝግመተ ለውጥ እሚያካሂዱት ምንም እንኳ በዘፈቀደ ስህተት እየፈጸሙ ቢሆንም፣ ተፈጥሮ እራሷ በምትፈጥረው መሰናክሎች እኒህን መሰናክሎች አልፈው የሚሄዱትን በመምረጧ ነው። ዳርዊን የተፈጥሮ ምርጫን አስተሳሰብ ከ፫ የሚታዩ ነገሮች አንጥሮ ነበር ያወጣው፦ ፩) እንስሳትም ሆነ እጽዋት ወደፊት ሊኖር ከሚችሉ ዘሮች በላይ አተረፍርፈው ነው እሚራቡት ፪) ሕይወት ያላቸው እያንዳንዳቸው ነገሮች ሁልጊዜ የተለያየ ጸባይ ነው ያላቸው፣ ስለሆነም እያንዳንዳንቸው በቀጣይ የመኖር ዕድላቸው የተለያየ ነው ፫) ስለሆነም የአንድ ማህበረሰብ አባላት ሲሞቱ፣ የሚገላቸውን ነገር ጠንክረው እሚቋቋሙት ግለሰቦች ብቻ በሕይወት ቆይተው ወደፊት መራባች ይችላሉ። ስለሆነም ቀስ በቀስ እነዚህ በህይወት ያሉ፣ በህይወት የሌሉትን አይነቶች እየተኩ ይሄዳሉ። በ፳ኛው ክፍለ ዘመን ጄኔቲክስ (ሥነ በራሂ) እና ዝግመተ ለውጥ ተዋህደው ማህበረሰባዊ ጄኔትክስ እሚባለውን ጥናት ለመፍጠር ችለዋል። አንድ ማህበርሰብ ለየት ያለ ግለሰቦችን ለመፍጠር ከሚያስችሉት መንገዶች አንዱ ሙቴሽን የተባለው ሂደት ሲሆን፣ ሙቴሽን እሚፈጠረው የዚያ ግለሰብ ዲ ኤን ኤ ከወላጆች ሲወረስ በሚደረግ ስህተት (ወይም እቅድ) ነው። \n \nጥያቄ: ማህበረሰባዊ ጄኔትክስ መቼ ተመሰረተ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ፳ኛው ክፍለ ዘመን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዳምጠው አየለ ዳምጠው አየለ (23.11. 1944 አ/ም – 27.10. 2006 አ/ም) ባህላዊ የኢትዮጵያ ዘፋኝ ነበር። በሃምሌ 23 1944 አ/ም ከእናቱ ወይዘሮ ሸዋየ ተካና ከአባቱ አየለ ካሰኝ በመራቤቴ ሰሜን ሸዋ ተወለደ። ልጅነቱን በእረኝነት፥ በግብርና እንዲሁም በቆሎ ተማሪነት እንዳሳለፈ ይናገራል። እድሜውም ለትምህርት ሲደርስ ባቅራቢያው በሚገኘው መራኛ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገብቶ ተምሯል። ዳምጠው ህይወቱ እስካለፈችበት ጊዜ ድረስ ለረዥም ጊዜ አብሯት የኖረው ባለቤቱ አልማዝ ይመር ትባላለች። ከአልማዝ ይመር አብዩ ዳምጠውና ቤቴልሄም ዳምጠው የሚባሉ ሁለት ልጆችን አፍርቷል። ዳምጠው መራቤቴ እያለ በየባእላቱ መዝፈን፣ ማቅራራት እንዲሁም መሸለል ይወድ እንደነበር ተናግሯል። በተለይም ጥምቀትን በማድመቅ ይታወቅ ነበር። የ 6ኛ ክፍል ተማሪ እያለ ክፍሌ ሞገስ የሚባል መምህሩ ወደ አዲስ አበባ ይዞት እንደመጣ ይናገራል። ባጋጣሚም የምድር ጦር ማስታወቂያ አውጥቶ ስለነበር ይፈተንና ያልፋል። የምድር ጦር ካምፕ ውስጥም እንዲኖር ይደረጋል። የዘፋኝነት ሙያው በዚህ አጋጣሚ ነበር የጀመረው። ዳምጠው ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማዉና መነሻ የሆነው አበበ ተሰማ እንደሆነ ይናገራል። ዳምጠው አየለ በምድር ጦር ከ 30 አመት በላይ አገልግሏል። የኢትዮዽያ ምድር ጦር በ1927 አ/ም ተመስርቶ በ1983 አ/ም የፈረሰ የሙዚቃ ቡድን ነበር። ዳምጠው በመንግስት ለውጥ ምክንያት እስከፈረሰበት ጊዜ ድረስ አብሮ እንደነበር ይናገራል። ምድር ጦርም እያለ ከነታምራት ሞላ፣ ሲራክ ታደሰ፣ ተክሌ ደስታ ፣ ጥላየ ጨዋቃ፣ ክፍሌ አቦቸር እንዲሁም ሌሎች የጦሩ አባላት ጋር ሰርቷል። ከሌሎች የሙዚቃ ቡድንም ጋር አብሮ ሰርቷል። ለምሳሌ ያክል ከነ ክቡር ጥላሁን ገሰሰ፣ ሙሃሙድ አህመድ፣ ብዙነሽ በቀለ ፣ ሙሉቀን መለስ፣ ፀሃየ ዮሃንስ፣ ቴድሮስ ታደሰ፣ቴድሮስ ካሳሁን እንዲሁም ሌሎችም ጋር ሰርቷል። የዳምጠው አየለ የመጀመሪያ የህትመት ስራው በ1963 አ/ም ሲሆን ወፌ ላላ የሚለው የሸክላ ስራ ነበር። ዳምጠው አየለ ባጠቃላይ 13 ሲዲዎችን ሰርቷል። ዳምጠው አየለ ኖርዌይ ሃገር በስደት ለ 8 አመት ያክል ኖሯል። ኢትዮጵያም ከገባ በኋላ አዲስ አበባ በሚገኘው በቅ/ገብራኤል ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በተወለደ በ 62 አመቱ ሰኔ 27 2006 አ/ም ቀን ህይወቱ አልፏል። የቀብር ስነስርአቱም ወዳጅ፣ ዘመድ እንዲሁም አድናቂዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ዳምጠው አየለ በመራቤቴ ሳለ ምን ያደርግ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በየባእላቱ መዝፈን፣ ማቅራራት እንዲሁም መሸለል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዩጋንዳ ዩጋንዳ ሪፐብሊክ (ወይም ዑጋንዳ) በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። በኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ ይዋሰናል። የዩጋንዳ ሰም የመጣው ከቡጋንዳ መንግሥት ነው። ከአረቦችና አውሮፓውያን በ1800ቹ ከመድረሳቸው በፊት ብዙ የሚታወቅ ነገር አልነበረም። በ15ተኛ መቶ ክፍለ-ዘመን ችዌዚ የተባለውን መንግስት በአፈ ታሪክ ይገኛል። አረቦችና አውሮፓውያን በ19ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሲደርሱ ብዙ መንግሥቶች በቦታው ነበሩ። እነዚህም በንዮሮ ፣ ቡሶጋ ፣ ቡጋንዳ ፣ ቶሮ እና አንኮልን ያጠቃልላሉ። ከ1894 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በታላቁ ብሪታን ስትመራ ነበር። የተለያዩ ቦታዎች ከተዋሃዱ በኋላ ዩጋንዳ በ1914 እ.ኤ.አ. ቅርጿን ያዘች። በ1966 እ.ኤ.አ. ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ ሕገ-መንግሥቱን አፍርሰው እራሳቸውን ፕሬዝዳንት አደረጉ። በ1971 እ.ኤ.አ. ኢዲ አሚን ሀገሩን መምራት ጀመሩ። የኢዲ አሚን አመራር 300,000 የሚገመቱ ዩጋንዳውያንን አስጨርሷል። በ1979 እ.ኤ.አ. የታንዛንያ ኃይሎች ኢዲ አሚንን ከሥልጣን ያስወግዳሉ። ሚልተን ኦቦቴ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ግን በ1985 እ.ኤ.አ. እንደገና ይወርዳሉ። ያሁኑ ፕሬዝዳንት ዮወሪ ሙሴቪኒ ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ናቸው። ፕሬዝዳነንቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይመርጣሉ። ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሎ ሲባምቢ ናቸው። ዩጋንዳ በመሬት የተቆለፈች ብትሆንም ታላላቅ የውሃ አካላት አሉ። ከነዚህ ውስጥም ቪክቶሪያ ሐይቅ፣ አልበርት ሐይቅ፣ ክዮጋ ሐይቅ እና ኤድዋርድ ሐይቅ ይዘረዘራሉ። ታላላቅ ከተማዎች በቪክቶሪያ ሐይቅ አቅራቢያ ይገኛሉ። እነዚህም ካምፓላንና እንትቤን ያጠቃልላል። ዩጋንዳ በ70 ወረዳዎች የተከፋፈለች ስትሆን እነዚህም በአራት አመራር ክልሎች ውስጥ ናቸው። አራቱ አመራር ክልሎች ሰሜናዊ ፣ ምሥራቃዊ ፣ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ይባላሉ። ወረዳዎቹ በዋና ከተማዎቻቸው ነው የሚሰየሙት። በዩጋንዳ ውስጥ የመዳብ እና ነጭ ብረት ክምችቶት አሉ። ግብርና ዋናው የኤኮኖሚ ሴክተር ነው። ከ80 በመቶ በላዩ የስራ ኃይል በግብርና ነው የተሰማራው። ቡና ዋናው የኤክስፖርት ትርፍ ምንጭ ነው። ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግሥቱ ከሌሎች ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን በኢዲ አሚን ጊዜ የወደቀውን ኤኮኖሚ ለማንሳት ተጣጥሯል። ዩጋንዳ ለብዙ ብሔረሰቦች ቤት ነው። ከነዚህ ውስጥ ግን አንድ ትልቁን ሕዝብ ብዛት የሚወክል የለም። 40 አካባቢ የሚሆኑ ቋንቋዎች ባሁኑ ጊዜ ይነገራሉ። ከነጻነት በኋላ እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተደርጓል። ብዙ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ ሉጋንዳ ሲሆን የአቴሶ ቋንቋ በሁለተኛነት ይከተላል። ኪስዋሂሊ ዋናው የንግድ ቋንቋ ነው። የዩጋንዳ የትምህርት ስርዐት የሰባት ዓመት መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፣ ስድስት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና ከ3 እስከ 5 ዓመት ከሁለተኛ ደረጃ በኃላ ትምህርት ያጠቃልላል። \n \nጥያቄ: ዩጋንዳ የአሁኑን ቅርጽ የያዘችው መች ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ1914 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአቡነ ቴዎፍሎስ አቡነ ቴዌፍሎስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሁለተኛው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ወፓትርያርክ ጎጃም በሚገኝው በዝነኛው ደብረ ኤሊያስ አካባቢ ከአባታቸው ከአቶ ወልደ ማርያም ውቤ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ዘርትሁን አደላሁ ሚያዝያ ፲፮ ቀን ፲፱፻፪ ዓ/ም ተወለዱ። ሲወለዱም የተሰጣቸው ስም መልእክቱ ወልደ ማርያም ነበር። በልጅነታቸው ንባብ እና ዜማን በመምህር መሪ ጌታ ረዳኸኝ እና ግራ ጌታ ሣህሉ እዚያው የተወለዱበት አካባቢ ተምረዋል። ኋላ የቅኔ እና የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ዝንባሌ ስላደረባቸው እዚያው ደብረ ኤሊያስ ደብር መምህር ገብረ ሥላሴ በሚባሉ ሊቅ ሥር መማር ጀመሩ። በ፲፱፻፻፳ ዓ/ም ወደ አዲስ አበባ መጥተው ፍትሐ ነገሥትና አዲስ ኪዳንን በመምህር ተክሌ (ነቡረ ዕድ በኋላ ቢትወደድ አቡነ ዮሐንስ) በመባል የሚታወቁት መሪነት ሲከታተሉ ቆይተዋል። በዚህ ጊዜ ውስጥ የኃይማኖት ችግሮችን ለማወቅ ይፈልጉ እንደነበርና ሰፋ ያለ ዕውቀት እንደነበራቸው ይነገራል። በተጨማሪ የኃይማኖት ችግሮችን የሚመለከቱ መጻሕፍትን ሳይታክቱና ሳይሰለቹ ያነቡም ነበር። መልእክቱ ወልደ ማርያም በ፲፱፻፴ ዓ/ም ይህን ዓለም በቃኝ ብለው ደብረ ሊባኖስ ገዳም መንኩሰው ገቡ። ከጠላት ወረራ በኋላ ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀሳውስቱ በዘመናዊ የኃይማኖት ትምህርት እንዲሠለጥኑ በነበራቸው ሀሳብ መሠረት ፳ የሚሆኑ ሊቃውንት መርጠው በቤተ መንግሥቱ አካባቢ እንዲሰለጥኑ አድርገዋል። ከነኚህም አንዱ አባ መልእክቱ ወልደ ማርያም ናቸው። ቀደም ብሎ በኢትዮጵያና በግብጽ በተደረገው ስምምነት መሠረት ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያዊያን ጳጳሶች ሲሾሙ ሊቀ ሥልጣናት መልእክቱ ወልደ ማርያም ለሹመት ከተመረጡት አምስት አባቶች አንዱ ሲሆኑ ወደግብጽ ተጉዘው በእስክንድርያው ፓትርያርክ ዳግማዊ አቡነ ዮሳብ እጅ በካይሮ በትረ ካና ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን እሑድ ሐምሌ ፲፰ ቀን ፲፱፻፵ ዓ/ም ሊቀ ሥልጣናት መልእክቱ “ብጹዕ አቡነ ቴዎፍሎስ” ተብለው የሐረርጌ ጳጳስ ሆኑ። \n \nጥያቄ: አቡነ ቴዎፍሎስ የተገደሉት መቼ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሐምሌ ፲፰ ቀን ፲፱፻፵ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአዲስ ዘመን (ጋዜጣ) አዲስ ዘመን ጋዜጣ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሥር የምተዳደር ነዉ ፣ በየዕለቱ የሚታተም ብሔራዊ ጋዜጣ ነው። አዲስ ዘመን በአሁኑ ጊዜ ከ ፵ በላይ ጋዜጠኞች ያሉት ሲሆን የጋዜጣው መጠን ‘መካከለኛ’ /በርሊነር/ (31.5 cm × 47 cm (12.4 in × 18.5 in) ) ሆኖ የፊትና ጀርባ ገፆችን በሙሉ ቀለም ያቀርባል። ይህ ጋዜጣ የአገሪቱ ብቸኛው ዕለታዊ ጋዜጣ ሲሆን የመንግሥትን አቋም የሚያንፀባርቅ እና በየዕለቱ የተለያዩ ልማታዊ ዜናዎችን ይዞ ይወጣል። ከአምሥት ዓመት የኢጣልያ ወረራ በኋላ የኢትዮጵያ ነፃነት መመለሱን ተከትሎ ንጉሠ ነገሥቱ ዙፋናቸው እንደ ተረከቡ ካከናወኗቸው ፖለቲካዊና አስተዳደራዊ ተግባራት አንዱ የመገናኛ ብዙኀን በማደራጀትና በማቋቋም ላይ ያተኮረ ነበር። በዚህም መሠረት አዲስ ዘመን ጋዜጣ ቅዳሜ፣ ግንቦት ፴ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም በይፋ ሥራ ጀመረ። ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ከጠላት ወረራ በኋላ ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም በድል አድራጊነት አዲስ አበባ ሲገቡ ባደረጉት ንግግር የመግቢያው አንቀጽ፦ «የሰማይ መላእክት የምድር ሠራዊት ሊያስቡትና ሊያውቁት ይቻላቸው ባልነበረ በዚህ በዛሬው ቀን ቸር እግዚአብሔር በመካከላችሁ ለመገኘት ስላበቃኝ በሰው አፍ የሚነገር ምስጋና የሚበቃ አይደለም። ከማናቸውም አስቀድሞ ለሁላችሁ ልነግራችሁና ልትረዱት የምፈልገው፣ ይህ ቀን ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ የአዲስ ታሪክ ዘመን መክፈቻ መሆኑን ነው። በዚሁ በአዲሱ ዘመን ሁላችንም መፈጸም ያለብን አዲስ ሥራ ይጀመራል።» የሚል ነበር የጋዜጣውም ሥያሜ «ይህ ቀን ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ የአዲስ ታሪክ ዘመን መክፈቻ ነው» ማለታቸውን መሠረት ያደርጋል። የጋዜጣው ድረ-ገጽ ስለጋዜጣው ታሪክ ሲዘግብ፤«የመጀመሪያ ዕትም ባለሁለት ገፅ፣ አርበ ጠባብ /ታብሎይድ/» (43.2 cm X 27.9 cm (17 in X 11 in)) እንደነበረና ስርጭቱም ፲ሺ ቅጂ እንደነበር ይገልጽና፤በዚሁ የመጀመሪያ ዕትም ርዕሰ አንቀጽ «\"የአዲስ ዘመን ጋዜጣ መጀመር\" በሚል ርዕስ ባስነበበው ጽሑፍ ‹ይህ አዲስ ዘመን ተብሎ የተሰየመው ጋዜጣ ከዛሬ ጀምሮ ወደፊት ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የነፃነቱን ሥራ ይሠራ ዘንድ ተመሠረተ› በማለት የተቋቋመበትን ዓላማ ያስረዳል» ይለናል። ቀጥሎም ያንኑ የመጀመሪያውን ርዕሰ አንቀጽ በመጥቀስ፤ «‹ይህ ጋዜጣ የፕሮፖጋንዳ ጋዜጣ ሳይሆን እውነትን፣ አገልግሎትን፣ ረዳትነትን መሰረት አድርጐ ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ በአዲስ ሥራ ተመርቶ እንዲረዳ የቆመ ነው› ቢልም ‹አገልግሎት ስንል የኢትዮጵያን ነፃነት ሲመሰስ ራሳቸውን መስዋዕት አድርገው፤ የነበራቸውን ጥቅም ሁሉ አስወግደው፤ ለሕዝባቸውና ለአገራቸው ሲሉ የሰው አቅም ሊሸከመው የማይችለውን ድካም ተቀብለው፤ ማናቸውም ሰው ሊያደርገው ያልቻለውን በኢትዮጵያ ሕይወት ውስጥ እስከ ዛሬ ያልታየውን ሥራ ከፍፃሜ ላደረሱ ለንጉሠ ነገሥታችንና ላቆሙት መንግሥት የሚያገለግል እንዲሆነ ነው።› በማለትም በዋነኝነት የተቋቋመበትን ዓላማ በግልፅ ይተነትናል።» የሚል ዘገባ እንደነበር የጋዜጣው ድረ-ገጽ አስቀምጦታል። አዲስ ዘመን ከተጀመረበት ጊዜ እስከ ታኅሣሥ ወር ፲፱፻፶፩ ዓ/ም ድረስ በየሳምንቱ፤በአርበ-ጠባብ፣ በመካከለኛና በአርበ-ሰፊ /ብሮድሺት/ (74.9cm X 59.7cm (291⁄2 in X 231⁄2 in)) መጠን ሲታተም ከቆየ በኋላ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በ፲፱፻፶ ዓ/ም ያቋቋመው የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን፣ ጽሕፈት ቤቱን አዲስ አበባ ላይ ማድረጉን ምክንያት በማድረግ የጋዜጣው ዕትመት በሳምንት ወደ ስድስት ቀን ተሸጋግሯል። ከመስከረም ፩ ቀን ፲፱፻፺፫ ዓ/ም ጀምሮ ደግሞ ጋዜጣው ከሰኞ እስከ እሑድ በሳምንት ሰባት ቀናት ወደመታተምከተሸጋገር በኋላ የጋዜጣው መጠን ከታኅሣሥ ፫ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ጀምሮ ወደ መካከለኛ ጋዜጣነት /በርሊነር/ ዝቅ ብሏል። \n \nጥያቄ: አዲስ ዘመን ከተጀመረበት ጊዜ እስከ ታኅሣሥ ወር ፲፱፻፶፩ ዓ/ም ድረስየሚታተመው መቼ መቼ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በየሳምንቱ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን ላይ አዲስ የዲዛይን ክፍተት መገኘቱ ተገለፀ። የቦይንግ ኩባንያ እና የአሜሪካ ፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር (ኤፍ.ኤ.ኤ) በትናንትናው እለት እንዳረጋገጡት በ737 ማክስ አውሮፕላን ዲዛይን ላይ የተገኘው አዲስ ክፍተት የኤሌክትሪክ ሽቦ መቀራረብ ችግር እንደሆነ አረጋግጠዋል። የቦይንግ ቃል አቀባይ ጎርዶን ጆንድሮ “ጉዳዩ የቦይንግ አስቸጋሪ ሂደት አካል ቢሆንም፤ ተገቢውን ትንተና ለማከናወን ከአሜሪካ ፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር ጋር በጋራ እየሰራን ነው፤ አሁን የተገኘው ክፍተት የዲዛይን ለውጥ ለማድረግ ያስገድዳል የሚያስብል ደረጃ ላይ ግን አልደረሰም”ብለዋል። የቦይንግ አውሮፕላን ላይ የተገኘው አዲሱ የዲዛይን ክፍተት የሁለት ሽቦዎች በጣም መቀራረብ መሆኑን በመግለጽ፤ አብራሪዎች ችግሩን ተረድተው በአፋጣኝ ምላሽ የማይሰጡ ከሆነ የአውሮፕላን መከስከስ አደጋን ሊያስከትል ይችላል” ሲል የኒው ዮርክ ታይምስ አስነብቧል። የአሜሪካ ፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር በሰጠው መግለጫ፥ በቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን ላይ ሊደረግ በታቀደው የዲዛይን ማሻሻያ ዙሪያ ኤጀንሲው እና የቦይንግ ኩባንያ የተለያዩ ግኝቶችን እየመረመረ መሆኑን አስታውቋል። ኤጀንሲው አክሎም “በዚህ ሂደት ወቅት ተለይተው የሚታወቁ የደህንነት ችግሮች በሙሉ መፍትሔ እንዲሰጣቸው ይደረጋል ” ሲልም አስታውቋል። ቦይንግ በአሁኑ ጊዜ ተቀራርበዋል የተባሉ የኤሌክትሪክ ሽቦዎችን ለመለየት እና ስህተቱን ተከትሎ የሚደርሰውን አደጋ በተመለከተ ሰፋ ያለ ትንተና እየሰራ መሆኑን አንድ የኩባንያው ባለስልጣን አስረድተዋል። ቦይንግ በአምስት ወራት ውስጥ በሁለት አደጋዎች 346 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተከትሎ የማክስ 737 አውሮፕላን ማምረት ማቆሙ ይታወሳል።   ምንጭ፡- ሲጂቲኤን \n \nጥያቄ: በቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን ላይ የዲዛይን ክፍተት መኖሩን ያረጋገጠው ማነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የቦይንግ ኩባንያ እና የአሜሪካ ፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር (ኤፍ.ኤ.ኤ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኒኑስ ኒኑስ በጥንታዊ የግሪክ ታሪክ ጸሃፊዎች ዘንድ የነነዌ መስራችና የአሦር ንጉስ ነበረ። ለዘመናዊ ሥነ ቅርስ የታወቀ አንድ ግለሰብ አይመስልም፤ ዳሩ ግን የአያሌ ታሪካዊ ወይም አፈ ታሪካዊ ግለሰቦች ትዝታ በአንድ ስም በግሪኮች በኋለኛ ዘመን እንደ ተዘከረ አሁን ይታስባል። የንጉሥ ኒኑስና ሚስቱ ንግሥት ሴሚራሚስ ስሞች በጽሁፍ መጀመርያ የተገኘው ክቴስያስ ዘክኒዱስ (400 ዓክልበ. ገዳማ) በጻፈው በፋርስ አገር ታሪክ ነው። ክቴስያስ ለ2 አርጤክስስ (2 አርታሕሻጽታ) የመንግሥት ሀኪም ሆኖ የፋርስ ነገሥታት ታሪካዊ መዝገቦች አንብቤያለሁ ብሎ አሳመነ። ከዚህ በኋላ የግሪክ ታሪክ ጸሐፊ ዲዮዶሮስ ሲኩሉስ የክቴስያስን ወሬ አስፋፋ። የአለም ታሪክ ሊቃውንት እስከ 1880ዎቹ ድረስ የኒኑስ ታሪክ ዕውነት መሆኑን ይቈጠሩት ነበር። በዚያን ጊዜ የኩኔይፎርም ጽሕፈት ፍች ስለ ተፈታ፣ በሜስፖጦምያና በነነዌ ብዙ ቅርሶችም በመገኘታቸው፣ የአሦር ትክክለኛ ታሪክ ዕውቀት ተጨመረልን። ኒኑስ የቤሉስ ወይም ቤል ልጅ ተባለ፤ ይህም ምናልባት በሴማዊ ቋንቋ ሥር «ባል» (ጌታ) የመሰለ ማዕረግ ሊሆን ይችላል። በካስቶር ዘሮድስ ዘንድ ኒኑስ ለ52 ዓመታት ነገሰ፤ ክቴስያስም እንዳለው መጀመርያው ዓመተ መንግሥቱ 2198 ዓክልበ. ነበረ። በ17 አመታት ውስጥ ኒኑስ በአረቢያ ንጉስ አርያዎስ እርዳታ ምዕራብ እስያን በሙሉ እንዳሸነፈ ተብሏል። ከዚህ ቀጥሎ የአርመን ንጉስ ባርዛኔስን (ይቅርታ የሰጠውን) እና የሜዶን ንጉስ ፋርኖስን (በስቅለት ይሙት በቃ የሰጠውን) ድል በማድረግ የአለም መጀመርያ ንጉሠ ነገስት እንደ ሆነ ተብሏል። \n \nጥያቄ: ኑኒስ ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ኒኑስ በጥንታዊ የግሪክ ታሪክ ጸሃፊዎች ዘንድ የነነዌ መስራችና የአሦር ንጉስ ነበረ። ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጮቄ አስደሳቹ ስፊውና ማራኪው ጮቄ በቢቡኝ ወረዳ ውስጥ ከሚገኙ የተፈጥሮ የቱሪስት መስህብ ሃብቶች መካከል አንዱና ዋነኛው ሲሆን ወረዳዋ በስፋት የምትታወቅበት አስደናቂና ከፍተኛ የሆነ ተራራማ ቦታ ነው። ጮቄ ከወረዳዋ ድጓ ፅዮን ከተማ 10 ኪ/ሜ ፣ ከዞን ዋና ከተማ ከደ/ማርቆስ 61 ኪ.ሜ፣ ከክልል ዋና ከተማ ከባህር ዳር 325 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። ጮቄ በእፅዋት ብዝሀነት የታደለና ከ85 በላይ አገር በቀል እፅዋት የሚበቅልበት ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ዋና ዋናዎቹ፡- ጅባራ፣ ጓሳ፣ አስታ፣ ቅርቅሃ፣ አምጃ፣ አሸንግድየ፣ ዝግባ/ግምይ/ ተጠቃሽ ናቸው። አባይን ያረገዘ ጮቄ አካባቢው የአባይ ወንዝ የውሃ ምንጭ ሲሆን የአባይ ተፋሰስ የውሃ ማማ እንደሆናና ከአባይ 9.5% ተፋሰስ ድርሻ ያለው ተራራማ የውሃ ስፍራ ነው። እንደ አጠቃላይ ሲታይ የምስራቅ አፍሪካ የውሃ ማማ (East Africa water Tower) የሆነው ጮቄ የአባይ ገባር የሆኑ 273 ትናንሽ የውሃ ጅረትና ከ23 በላይ የሚሆኑ ታላላቅ ወንዞች መፍለቂያ ነው። ከታላላቅ ወንዞች መካከል እናት ሙጋ፣ ግልገል ሙጋ፣ ተምጫ፣ ዝምብል፣ ትልቁ አብያ፣ ትንሹ አብያ፣ ጨሞጋ፣ ጌደብ፣ ጥጃን፣ ጠፍ፣ ጦመ፣አዝዋሪ፣ ተጠቃሽ ሲሆኑ ከነዚህም ቢቡኝ ወረዳ ውስጥ የሚገኙት፡- ዝምብል፣ ትልቁ አብያና ትንሹ አብያ ናቸው። የጮቄ ተራራ ከባህር ወለል በላይ 4088 ሜትር አካባቢ ከፍታ ያለው በመሆኑ የጎጃም ጣራ ( The roof of Gojjam) በመባል ይታወቃል። የጮቄ ተራሮች በምስራቅ ጎጃምና በምዕራብ ጎጃም ዞኖች ዘጠኝ ወረዳዎች ክልል ውስጥ የሚገኝ ሲሆን ጠቅላላ ስፋቱም 53558 ሄክታር በላይ እንደሚደርስ ጥናቶች ያመለክታሉ። ጮቄ በጣም ሰፊ ከመሆኑም የተነሳ ገና ብዙ ያልታወቁ ዋሻዎች፣ ጥንታዊ መኖሪያዎችና ያልተዳሰሱ አስደሳች የተፈጥሮ መስህቦች አሉት ፡፡ የጮቄ አካባቢ፡- በስተ ምስራቅ እነማይና እናርጅ እናውጋ፣ በስተ ሰሜን ምስራቅ 2 እጁ እነሴ በስተ ሰሜን ቢቡኝ በምዕራብ ማቻከል፣ በስተ ደቡብ ስናን እንዲሁም በስተ ደቡብ ምስራቅ ደባይ ጥላት ግን ወረዳዎች ያዋስናል። ይህ ተራራ በዋናነት በቢቡኝ ወረዳ ውስጥ የሚገኙ አምስት ቀበሌዎችን ያቀፈ ነው፡፡ እነሱም፡- አሩሲ መሰሳቢያ ደድ ደብረ ፅዮን ደብረ ጊዮርጊስና ወንበር ቅዱስ ዮሐንስ ቀበሌዎች በዋናነት ይገኛሉ፡፡ \n \nጥያቄ: በቢቡኝ ወረዳ ውስጥ ከሚገኙ የተፈጥሮ የቱሪስት መስህብ ሃብቶች መካከል አንዱ ማነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ጮቄ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ እንግሊዝ ሀገር አንደደረሰም የወቅቱ የእንግሊዝ ንግስት ከነበረችው ንግስት ቪክቶሪያ ጋር ተገናኘ፡፡ ንግስቲቱም ልዑሉ የፈለገው እና ያሻው ይደረግለት ዘንድ ቀጭን ትዕዛዝ አስተላለፈች፡፡ ልዑሉ በመቅደላ የነበረውን እልቂት በመጠኑም ቢሆን በማየቱ እና የአባቱ እና የእናቱ ተከታታይ ሞትም በልጅ አዕምሮው ሊቀበለው ከሚችለው በላይ ስለነበር እጅግ ታውኮ እንደነበር በተደጋጋሚ ተፅፎ እናገኛለን፡፡ በ1861 ዓ.ም ስፒዲ ህንድ ሀገር በምትገኝ አንዲት ከተማ አዛዥ ሆኖ ስለተሾመ የ8 ዓመቱን አለማየሁን እና ሚስቱን ይዞ ወደዛው አቀና፡፡ በሄዱበት ሀገርም አለማየሁ ትምህርቱን መከታተሉን ቀጥሎ የነበረ ሲሆን ከመደበኛው ትምህርት በዘለለም ፈረስ ግልቢያ እና ሌሎች ስፖርቶችንም ያዘወትር ነበር፡፡ 1867 ዓ.ም አለማየሁ ወደ ራግቢ ትምህርት ቤት ተዛወረ፡፡ በዚህም ከቄስ ብሌክ ቤት ወጥቶ ወደ ሊው ዋርነር ቤት እንዲገባ ተደረገ፡፡ በዚህ ግን ደስተኛ ስላልነበር በቀጣዩ አመት ሚስተር ድራፐር ቤት እንዲኖር ተደረገ፡፡ ቄስ ብሌክም ካዩት የልዑሉ ባህሪ በመነሳት ልዑሉ ወታደርነት ላይ ቢያተኩር የበለጠ ውጤታማ እንደሚሆን ተናገሩ፡፡ በዚህም ንግግር መሰረት የወታደር ትምህርት ቤት እንዲገባ ተደረገ፡፡ በአንድ ወቅት አለማየሁ ወደ ሊድስ በመሄድ በሰር ራምሰን ቤት ተቀምጦ በነበረበት ወቅት በመርዝ ተመረዘ። መርዙ ህዳር 5 ቀን 1872 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3 ሰዓት ከሩብ በተወለደ በ19 ዓመቱ ከዚህ አለም እንዲሰናበት አደረገው፡፡ አስከሬኑም ዊንድሶር ባለው የነገስታት መቀበርያ በክብር አረፈ፡፡ በመቃብሩም ላይ “የሀበሻው ልዑል አለማየሁ” የሚል ፅሁፍ ሰፍሮበት እስካሁን በእንግሊዝ ሀገር ይገኛል፡፡ \n \nጥያቄ: ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ እንግሊዝ ሀገር እንደደረሰ ያገኛት ንግስት ማን ትባላለች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ንግስት ቪክቶሪያ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዲጂታል ዑደት የዲጂታል ዑደት እምንለው የ ስታቲክ ዲሲፕሊን ን የሚቀበል ማናቸውም ዓይነት የዑደት አይነትን ነው። የዲጂታል ዑደት ከአናሎግ የኤሌክትሪክ ዑደት እሚለየው በተወሰኑና የአምክንዮ ትርጓሜ ባላቸው ሲግናሎች ብቻ መስራቱ ነው። ይህን እሚፈጽመው ያልተቆራረጡ የአናሎግ ሲግናሎችን በመከፋፈል፣ ለምሳሌ ከተወሰነ ቮልቴጅ በላይ ያሉትን ቮልቴጆች እንደ አምክንዮ እውነት (1) በመውሰድ እና ከተወሰነ ቮልቴጅ በታች ያሉትን ደግሞ እንደ አመክንዮ ውሸት በመውሰድ ነው። ሆኖም ግን ለምሳሌ ከ0ቮልት እስከ 5 ቮልት ያሉትን ዋጋወች ከፍለን ከ0-2.5ቮልት ያሉትን ውሸት እንዲወክሉ ብናደርግና ከ 2.5001ቮልት - 5ቮልት ያሉትን እውነት ን እንዲወክሉ ብናደርግ፣ ምንም እንኳ ስሜት ቢሰጥም፣ እነዚህን ቮልቴጆች በመጠቀም መልዕክት ለመላክ ብንሞክር፣ ትንሽ እንኳ ኖይዝ (ግርግር ቮልቴጅ) በመሃከል ከገባ አንዱን ቮልቴጅ ወደሌላው በመቀየር የተላከውን መልዕክት ያዛባል። ያ እንዳይሆን በመሃል ቀዳዳ ማበጀት አንዱ መልዕክት ወደሌላው መልዕክት እንዳይቀየር ይረዳል። ለምሳሌ ከ 0-1.5ቮልት ያለውን ውሸት ብንል እና ከ 3.5-5ቮልት ያለውን እውነት ብንል፣ በሁለቱ ዋጋወች መካከል የ2ቮልት ልዩነት ስላለ በቀላሉ አንዱን ዋጋ ወደሌላው መቀየር አይቻልም። ስለሆነም ከአንድ የድጅታል ስርዓት ክፍል ወደ ሌላ መልዕክት ሳይዛባ ለማስተላለፍ ይቻላል። ስለሆነም በብሊዮኖች የሚቆጠር ክፍል ያለው አንድ ኮምፒዩተር ያለምንም ስህተት ስሌትን ለመፈጸም ይችላል። \n \nጥያቄ: የዲጂታል ዑደት ከአናሎግ የኤሌክትሪክ ዑደት ምን ይለየዋል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በተወሰኑና የአምክንዮ ትርጓሜ ባላቸው ሲግናሎች ብቻ መስራቱ ነው። ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nባቢሌ የዝሆን መጠለያ ባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ከአዲስ አበባ ወደ ጅጅጋ መስመር፣ ፭መቶ ፶ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። ይህ መጠለያ በቆዳ ስፋት ፮ሺ ፱መቶ ፹፪ ካሬ-ሜትር የሚመዘን ሲሆን፣ ከጠቅላላ ስፋቱም ውስጥ ፸፯ ከመቶ ያህሉ በአሁኑ አጠራር ”በሶማሌያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት” ሥር ሲካለል፤ ቀሪው ፳፫ ከመቶ ያህሉ ደግሞ ”በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት” ሥር ይገኛል። የአካባቢው የኦሮሚያ ብሔር ተወላጆች ‹‹ወረ-ሃርባ›› (ባለዝሆኖቹ) በማለት የሚጠሩትና በፌዴራል የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ሥር የሚተዳደረው የባቢሌ ዝሆኖች መጠለያ በዓፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ-መንግሥት፣ በ፲፱፻፷፪ ነው የተመሠረተው። የምሥረታውም ዋነኛ ዓላማ፥ በምሥራቅ አፍሪካ ብቻ የሚገኙትን “ሎክሶዳንታ አፍሪካና ኦርሊያንሲ” የተባሉትን ንዑስ የዝሆን ዝርያ ለማልማትና ለመጠበቅ ሲሆን ባሁን ጊዜ መጠለያው በተጨማሪም ከ፴ በላይ ጡት አጥቢ የዱር እንስሳት፣ ከ፪መቶ ፶ በላይ የአዕዋፍ ዝርያዎች፣ ፫መቶ ያህል የዕፅዋት ዝርያዎች የሚገኙበት ነው። ከሌሎች አዕዋፍ እና የዱር አራዊት ዝርያዎች ደግሞ ከገጸ ምድር የመጥፋት አደጋ ላይ ያለው የሳልቫዶሪ ዘረ-በል ወፍ እና ባለጥቁር ጎፈር አንበሳ በዚህ መጠለያ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: በምሥራቅ አፍሪካ ብቻ የሚገኙትን “ሎክሶዳንታ አፍሪካና ኦርሊያንሲ” የተባሉትን ንዑስ የዝሆን ዝርያ ለማልማትና ለመጠበቅ የተዘጋጀው መጠለያው ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአልጄሪያ አልጄሪያ (አረብኛ፦ الجزائر‎ አል ጃዝኤር; በርበርኛ፦ ድዜየር) በይፋ የአልጄሪያ ሕዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በሰሜን አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። ከቆሳ ስፋት አኳያ በሜዲቴራንያን ባህር ዙሪያ ትልቋ ስትሆን፣ ከአፍሪካ ደግሞ ከሱዳን በኋላ ሁለተኛ ናት። አልጄሪያ ከሰሜን ምሥራቅ በቱኒዚያ፣ ከምሥራቅ በሊቢያ፣ ከምዕራብ በሞሮኮ፣ ከደቡብ ምዕራብ በምዕራባዊ ሣህራ፣ ሞሪታኒያና ማሊ፣ ከደቡብ ምሥራቅ በኒጄር፣ ከሰሜን በሜዲቴራንያን ባህር ትዋሰናለች። ዋና ከተማዋ አልጂርዝ ሲሆን የ፳፻፫ ዓ.ም. ሕዝብ ብዛቷ ወደ 35.7 ሚሊዮን ይገመታል። አልጄሪያ የተባበሩት መንግሥታት፣ የአፍሪካ ሕብረት፣ ኦፔክ እና ሌሎችም ዓለም አቀፍ ድርጅቶች አባል ሀገር ናት። የሀገሯ ስም የመጣው ከአልጂርዝ ከተማ ሲሆን በድሮ ጊዜ ከዛሬዎቹ ምዕራብ ቱኒዚያና ምሥራቅ ሞርኮ አብራ ኑሚዲያ ትባል ነበር። በጥንት ጊዜ አልጄሪያ የኑሚዲያ መንግሥት ትባል የነበረ ሲሆን ነዋሪዎቿ ደግሞ ኑሚዲያውያን ይባሉ ነበር። የኑሚዲያ መንግሥት ከካርታጎ፣ ሮማና ጥንታዊ ግሪክ ጋር ግንኙነት ነበራት። አካባቢው ለምለም እንደነበረ ሲነገር ኑሚዲያውያን ደግሞ ለኃይለኛ ፈረሰኛ ጦራቸው ይታወቁ ነበር። \n \nጥያቄ: አልጄርያ ከዛሬዎቹ ቱኒዚያና ምስራቅ ሞሮኮ ጋር በጥንት ምን ተብላ ትጠራ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ኑሚዲያ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nመንግሥት እና ፖለቲካ ናይጄሪያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ ሲሆን መንግሥቷ በአሜሪካ መንግሥት ላይ ነው የተመረኮዘው። የህግ አውጪው አካል አወቃቀር የዌስትሚኒስትር ሥርዓትን ይከተላል። በአሁኑ ጊዜ ጉድላክ ጆናታን ፕሬዝዳንት ናቸው። ፕሬዝዳንቱ ለሁለት የአራት ዓመት ጊዜ ሲያገለግል በሕዝቡ ነው የሚመረጠው። የናይጄሪያ ብሔራዊ ምክር ቤት ሁለት አካሎች አሉት። እነዚህም ሴኔት እና የተወካዮች ምክር ቤት ናቸው። ሴኔቱ 109 መቀመጫዎች ሲኖሩት እያንዳንዱ ክልል በሶስት አባሎች ይወከላል። የአቡጃ ርዕሰ አካባቢም አንድ ተወካይ አለው። የሴኔት አባላት በሕዝብ ይመረጣሉ። የተወካዮች ምክር ቤት 360 መቀመጫዎች ሲኖሩት የእያንዳንዱ ክልል ወካዮች በሕዝብ ብዛት ነው የሚወሰነው። የውጭ ግንኙነቶች ነፃነቷን በ1960 እ.ኤ.አ. ካገኘች በኋላ ናይጄሪያ ለአፍሪካ ነፃነትና ክብር መታገል ዋና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ አድርጋለች። የደቡብ አፍሪካን አፓርታይድ ሥራዓት በመቃወም ትልቅ ሚና ተጫውታለች። በ1960ዎቹ እ.ኤ.አ. ናይጄሪያ ከእስራኤል ጋር የጠበቀ ግንኙነት የነበራት ሲሆን እስራኤል የናይጄሪያ ፓርላማ ህንጻዎችን አሰርታለች። ናይጄሪያ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት መስራች አገር ናት። በምዕራብ አፍሪካም ሆነ በአፍሪካ በጠቅላላ ትልቅ ተጽዕኖ አላት። በተጨማሪም እንደ ኤኮዋስ ያሉ የምዕራብ አፍሪካ የትብብር ድርጅቶች መሥራች ናች። ከ1970ዎቹ እ.ኤ.አ. ጀምሮ ናይጄሪያ ዋና የነዳች አምራች ስትሆን የኦፔክ አባል ሀገር ናት። በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ናይጄሪያውያን በኢኮኖሚ ችግር ምክንያት ወደ አውሮፓ፣ ሰሜን አሜሪካ እና አውስትራሊያ ተሰድደዋል። ከአንድ ሚሊዮን የሚበልጡ ናይጄሪያውያን በአሜሪካን እንደ ሚኖሩ ይገመታል። \n \nጥያቄ: የናይጄሪያ ብሔራዊ ምክር ቤት አካሎች እነማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሴኔት እና የተወካዮች ምክር ቤት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nስዋሂሊ ስዋሂሊ ፡ (ወይም ፡ ኪሷሂሊ Kiswahili) ፡ በምሥራቅ ፡ አፍሪቃ ፡ የሚናገር ፡ የባንቱ ፡ ቋንቋዎች ፡ ቤተሠብ ፡ ቋንቋ ፡ ነው። የስዋሂሊ ፡ ሕዝብ (፭ ፡ ሚሊዮን ፡ ተናጋሪዎች) ፡ ልደት ፡ ቋንቋ ፡ ከመሆኑ ፡ በላይ ፡ ለ ፴ ፡ እስከ ፡ ፶ ፡ ሚሊዮን ፡ ሌሎች ፡ ሰዎች ፡ ሁለተኛ ፡ ቋንቋ ፡ ሆኗል። የስዋሂሊ ፡ ስም ፡ መነሻ ፡ ከዓረብኛ ፡ ቃል ፡ «ሰዋሂል» ፡ ነበር ፤ ይህም ፡ የ«ሳኸል» ፡ (ማለት ፡ ዳር) ፡ ብዙ ፡ ቁጥር ፡ ነው። ስለዚህ ፡ የ«ስዋሂሊ» ፡ ትርጉም ፡ የ(ባሕር) ፡ ዳረኞች ፡ ቋንቋ ፡ ሊሆን ፡ ይችላል። የቋንቋው ፡ ቤተሰብ ፡ ባንቱ ፡ ሲሆን ፡ ተናጋሪዎቹ ፡ መርከበኞችና ፡ ነጋዴዎች ፡ በመሆናቸው ፡ መጠን ፡ ከዓረብኛ ፣ ከፋርስ ፣ ከህንዲ ፣ እና ፡ ከቻይንኛ ፡ ቢሆንም ፡ ብዙ ፡ ቃሎች ፡ ተበድረዋል። \n \nጥያቄ: ስዋሂሊ የምን ቋንቋ ቤተሰብ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የባንቱ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nልዑል ራስ መኮንን የንጉሠ ነገሥቱ ዳግማዊ ምኒልክ ተወካይ ሆነው ሁለት ጊዜ የአውሮፓን አገሮች ጎብኝተዋል። በዚህ ጊዜ እሳቸው ኢጣሊያን ሲጎበኙ በነበረ ጊዜ የኢጣሊያ ጋዘጦች የውጫሌ ውልን በተመለከተ፤ «...በውጫሌ ውል ላይ ኢትዮጵያ የኢጣሊያን ጥገኝነት ተቀብላ ውል ከፈረመች በኋላ የጀርመን ንጉሠ ነገሥት ከኢትዮጵያ የሚላከውን ማንኛውንም ደብዳቤም ሆን ጉዳይ በኢጣሊያ መንግሥት በኩል መቀበል ሲገባቸው በቀጥታ ከምኒልክ የተጻፈውን ደብዳቤ ተቀብለዋል...» እያሉ የጻፉትን ራስ መኮንን ተቃውሞአቸውን ለኢጣሊያ መንግሥት ከነገሩ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የውሉን መበላሸት ለአጤ ምኒልክ አሳወቁ። ከኢጣሊያንም ጋር በተደረገውም ጦርነት ራስ መኮንን ፲፭ ሺህ እግረኛ ወታደሮች ይዘው ከምኒልክ እና ታላላቅ ጦር አዛዦች ጋር ዘምተዋል። በ፲፰፻፺፰ ዓ.ም መጀመሪያ ላይ በብርቱ ስለታመሙ ለኅክምና ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ጥር ፬ ቀን ከከተማቸው ከሐረር ተነሱ። ጥር ፱ቀን ቡርቃ ወንዝ አድረው የጥምቀትን በዓል አክብረው ከዋሉ በኋላ ሕመሙ ስለጸናባቸው ወደ ኋላ ተመልሰው ቁልቢ ገብተው በሐኪም ይታከሙ ጀመር። እዚሁም ሲታመሙ ከቆዩ በኋላ መጋቢት ፲፫ ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም ቁልቢ ላይ አርፈው ሐረር ላይ እሳቸው በተከሉት በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። ዐፄ ምኒልክም የአርባቸው ለቅሶ የሚለቀሰው አዲስ አበባ እንዲሆን ባዘዙት መሠረት፤ ሰኞ ሚያዝያ ፳፪ ቀን በአዲስ አበባና በዙሪያው ያሉት የየገዳማቱና የየአድባራቱ ካህናት የክርስቲያን የፍታት ጸሎት ተድርጎ በማግስቱም ማክሰኞ የጊዮርጊስ ዕለት ሚያዝያ ፳፫ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም በሰኢ ሜዳ ላይ ድንኳን ተተክሎ፤ መኳንንቱና ሠራዊቱ ተሰብስቦ የራስ መኮንን የማዕረግ ልብሳቸውና የራስ ወርቃቸው፤ ኒሻኖቻቸውና የጦር መሳሪያቸው ተይዞ ፈረስና በቅሏቸው በወርቅ እቃ ተጭነው በሠራዊቱ መካከል እየተመላለሱ ታላቅ ልቅሶ ተለቀሰላቸው። \n \nጥያቄ: ራስ መኮንን ግብዓተ መሬታቸው የት ተፈጸመ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሐረር ላይ እሳቸው በተከሉት በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ በሃገራችን ኢትዮጵያ ስም አጠራራቸው ከከበረ አባቶች አንዱ ጻድቅ ናቸው። ጻድቁ የተወለዱት በአምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ አካባቢ ሲሆን ወላጆቻቸው ንጉሥ ይስሐቅ እና ቅድስት እድና ይባላሉ ። የተወለዱበት አካባቢም ሮም ነው ። ስማቸው ብዙ ዓይነት ነው። ወላጆቻቸው ዘሚካኤል ሲሏቸው በበርሃ ገብረአምላክ ተብለዋል። በኢትዮጵያ ደግሞ አረጋዊ ይባላሉ። አቡነ አረጋዊ ምንም የንጉሥ ልጅ ቢሆኑም በልጅነታቸው መጻሕፍትን ተምረው ነበርና ጠፍተው ገዳም ገቡ። በዚያም በገዳመ ዳውናስ (ግብጽ) የታላቁ ቅዱስ ጳኩሚስ ደቀ መዝሙር ሆነው ከነ አባ ቴዎድሮስ ጋር ሥርዓተ መነኮሳትን ተምረዋል። ከመነኮሱ ከዓመታት በኋላም ወደ ሃገራቸው ሮም ተመልሰው በማስተማር ሰባት ያህል የቤተ መንግሥት ሰዎችን ወደ ምናኔ ማርከዋል። \"የት ልሒድ?\" ብለው ሲያስቡም ቅዱስ መልአክ በክንፉ ጭኖ ወስዶ ኢትዮጵያን አሳያቸው። ተመልሰውም ለስምንት ባልንጀሮቻቸው \"ሃገርስ ባሳየኋችሁ! ሐዋርያ ሳያስተምራት በሕጉ በሥርዓቱ ጸንታ የምትኖር\" ብለው ከስምንቱ ጋር ከቃልኬዶን ጉባዔ በኋላ በ፬፻፶፩ ዓም ወደ ኢትዮጵያ መጡ ። ከዘጠኙ ቅዳሳን ወደ ኢትዮጵያ ከሮምና ከመካከለኛው ምሥራቅ ከፈለሱት አንዱ አቡነ አረጋዊ ናቸው ። በዚህ ጊዜም እናታቸው ቅድስት እድናና ደቀ መዝሙራቸው አባ ማትያስ አብረው ነበሩ። ወደ ሃገራችን የመጡ በአራት መቶ ሰባዎቹ አካባቢ ሲሆን አልዓሜዳ በክብር ተቀብሏቸዋል። በቤተ ቀጢን (አክሱም) ተቀምጠውም መጽሐፍትን እየተረጎሙ ወንጌልን እየሰበኩ ቆይተዋል ። አቡነ አረጋዊ ለብዙ ጊዜ በዓት ፍለጋ ደክመዋል ። በመጨረሻም ደብረ ዳሞ ማረካቸዋለች ። ዘጠና ዘጠኝ አመት ሲሞላቸው ጌታ በመንፈቀ ለሊት ተገልጾ ምድራዊ መንግስትህን ትተህ ስላገለገልከኝ ህልፈት ሽረት የሌለባት ሰማያዊ መንግስቴን አወርሰሃለሁብሎ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ በስምህ የተማጸነውን እስከ አስራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ አንተም ከሞት ገጽ ትሰወራለህ ብሎ ተስፋቸውን ነገራቸው፡፡ እሳቸው መነኮሳቱን ሰብስበው ከእንግዲህ በሥጋ አታዩኝም ብለው ነግረዋቸው አበምኔት (የገዳም አባት ወይም አለቃ) ሾመውላቸው ጥቅምት አሥራ አራት ቀን በዚያው በደብረ ዳሞ ተራራ በስተምስራቅ አቅጣጫ እንደሄኖክ እንደ ኤልያስ ተሰውሯል ፡፡ \n \nጥያቄ: አቡነ አረጋዊ በሮም ምን ያህል የቤተ መንግስት ሰዎች ወደ ምናኔ ማረኩ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሰባት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nተክለጻድቅ መኩርያ ተክለጻድቅ መኩርያ በ፲፱፻፮ ዓ.ም. በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ አሳግርት ልዩ ስሙ ሳር አምባ በተባለ ሥፍራ ተወለዱ። ዕድሜያቸው ለትምሕርት ሲደርስ መጀመሪያ ከአባታቸውና ቀጥሎም በአጥቢያቸው ባህላዊውን ትምሕርት እስከቅኔ ያለውን ቀስመዋል። ከዚያም አዲስ አበባ መጥተው አሊያንስ ፍራንሴዝና ተፈሪ መኮንን ትምሕርት ቤት ገብተው የጊዜውን የትምሕርት ደረጃ አጠናቀዋል። ኢጣልያ አገራችንን የወረረች ጊዜም በየካቲት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ.ም. ፍጅት ተይዘው ወደ ሶማሌ ደናኔ ተግዘው ለሦስት ዓመታት ታስረዋል። ከነጻነትም መልስ አገራቸውን በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች አገልግለዋል። መጀመሪያ ተቀጥረው ያገለገሉት በትምሕርትና ሥነጥበብ ሚኒስቴር ነበር። እዚያም ሳሉ በአገራችን ሰው የተጻፈ የአገራችን ታሪክ አንድም ባለመኖሩ በቁጭትና በመቆርቆር ነበር ‘መጻፍ አለብኝ’ ብለው በደንብ ከሚታወቀው ከቅርቡ ጊዜ በቅጡ ወደማይታወቀው የሩቁ ዘመን መጻፍ የጀመሩት። የመጀመሪያውን መጽሐፍ “የኢትዮጵያ ታሪክ ከዓፄ ቴዎድሮስ እስከ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ” የሚለውን በ ፲፱፻፴፰ ዓ.ም. አሳተሙ። ከጫፍ እስከ ጫፍ ጽፈው የመጨረቻውን መጽሐፍ፣ የታሪካችን መጀመሪያ የሚሆነውን “የኢትዮጵያ ታሪክ ኑብያ-አክሱም-ዛጉዬ እስከ ዓፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት” የሚለውን በ፲፱፻፶፩ ዓ.ም. አቅርበዋል። እኒህኑ መጻሕፍት ትምሕርት ሚኒስቴር ታሪክ ለማስተማሪያ በትምሕርት ቤት ተጠቅሞባቸዋል። ተክለጻድቅ ከታሪክ ውጭ የጻፏቸው “የሰው ጠባይና አብሮ የመኖር ዘዴ” እና በሚዮቶሎዢያ (አፈ ታሪክ) ላይ ያተኮረ “ከጣዖት አምልኮ እስከ ክርስትና” የሚሉም መጽሐፎች አሏቸው። ተክለጻድቅ በምድር ባቡር በዋና ጸሐፊነት፥ በቤተ መጻሕፍት ወመዘክር ዋና ሥራ አስኪያጅነት፥ እንዲሁም በፈረንሳይ፥ በእስራኤል፥ በዩጎዝላቪያ በዲፕሎማሲ ሥራ በመጨረሻም የትምሕርትና የባህል ሚኒስቴር ሆነው አግልግለዋል። በፈቃዳቸው ጡረታም ከወጡ በኋላ በምርምር የታገዙ ሦስት ታላላቅ የታሪክ ሥራዎችን አቅርበዋል። ተክለጻድቅ ከረጅም የአገልግሎት ዘመን በኋላ በተወለዱ በ ሰማንያ ስድስት ዓመታቸው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፱፻፺፪ ዓ.ም. አርፈዋል። \n \nጥያቄ: ተክለጻድቅ መኩርያ መቼ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፱፻፺፪ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሳህሌ ደጋጎ ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ከእናታቸው ከወይዘሮ ደጊቱ ፈይሣ እና ከባላንባራስ ደጋጎ አለቤ አብራክ በ1923 ዓ/ም በምዕራብ ወለጋ ልዩ ስሙ ነጆ ከተባለው ሥፍራ ተወለዱ። እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በነቀምት አንደኛ ደረጃ እና በአዲስ አበባ ተፈሪ መኮንን ት/ቤት ዘመናዊ ትምህርቱን ከተከታተለ በኋላ በነበረው ልዩ የውትድርና ፍቅር በቀድሞ 1ኛ ክፍለ ጦር በኋላም ማዕከላዊ ዕዝ ተብሎ በተጠራው የክ/ዘበኛ የጦር ክፍል ውስጥ በ1942 ዓ/ም ተቀጥሯል። በነበረው ሙያዊ ብቃትና ወታደራዊ ሥነ ሥርዓት አክባሪነት ከተራ ወታደርነት በአንድ ጊዜ የሃምሳ አለቅነት ማዕረግ ማግኘት የቻለው ሣህሌ፤ በሂደት እስከ ኮሎኔል ደረጃ ደርሷል። ወደ ሙዚቃ ቀማሪነት፣ ዜማና ግጥም ደራሲነት እንደዚሁም ወደ የማዕከላዊ ዕዝ የሙዚቃ ባንድ ኃላፊነት ከመሸጋገሩ በፊት በእግረኛ ባንድ ውስጥ “ክላርኔት” የተሰኘው የሙዚቃ መሣሪያ ተጫዎች የነበረው ሣህሌ ደጋጎ፣ የሙዚቃን ትምህርት የቀሰመው ከፈረንሣዊው መምህሩ ሙሴ ኒኮ መሆኑን የሕይወት ታሪኩ ላይ ተጠቅሷል። ከክላርኔት በተጨማሪ “አኮርዲዮን፣ አልቶ-ሳክስ፣ ፒያኖ” የተሰኙትን የሙዚቃ መሣሪያዎችንም በብቃት ይጫወት ነበር። በጠቅል ራዲዮ ጣቢያ (በተቋቋመ ጊዜ ) በአኮርዲዮን ጥዑም ዜማ ለጣቢያው አድማጮች ሲያንቆረቁር ከነበሩት የሙዚቃ ሰዎች መካከል ሣህሌ ደጋጎ የመጀመሪያው ነበር። ከእነ ሻለቃ ግርማ ይህደጎ፣ ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ እና ከሻለቃ ባሻ ገብረዓብ ተፈሪ ጋር በመሆን የክቡር ዘበኛ ኦርኬስትራን ስም እፁብ ድንቅ በማድረጉ በኩል የበኩሉን ሚና ተጫውቷል። ግጥምና ዜማ ደራሲ ከመሆኑም ባሻገር የአጫጭር እና ረዣዥም ድራማዎች ፀሐፊ የነበረው ሣህሌ፣ «ሁለገብ የታሪክ ማኅደር» ያሰኘውን ተግባር በሕይወት ዘመኑ አከናውኗል። \n \nጥያቄ: ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ በነበራቸው ብቃት ከተራ ወታደርነት ወደ የትኛው ማዕረግ አደጉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሃምሳ አለቅነት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሰርጌይ ብሪን ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን ኦገስት 21, 1973 እ.ኤ.አ. ተወለደ ሩሲያዊ-አሜሪካዊ ሲሆን ጉግልን በመፍጠሩ ይታወቃል። በሩሲያ የተወለደ ሲሆን፥ ብሪን ከላሪ ፔጅ ጋር ጉግልን ከመጀመሩ በፊት ኮምፒዩተር ሳይንስና ሒሳብ አጥንቷል። ብሪን ባሁኑ ጊዜ የጉግል ቴክኖሎጂ ፕሬዝዳንት በመሆኑ ወደ 14.1 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ገንዘብ አለው። ይህም ከዓለም 26ኛ እና ከአሜሪካ 12ኛው ሀብታም ሰው ያደርገዋል። ሰርጌይ በሞስኮ፣ ሩሲያ ለየይሁዳ ቤተሰብ ተወለደ። 6 ዓመቱ ሲሆን ሰርጌይና ቤተሰቡ ወደ አሜሪካ መጡ። አባቱ ሚካኤል በሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ ማቲማቲሻን ሆኖ እስክ ዛሬ ድረስ ያስተምራል። የስርጂ እናት ዩጂኒያ ብሪን ማቲማቲሻንና ሲቭል ኢንጅነር ሆና ለናሳ ትሰራለች። ሳሙኤል የሚባል ታናሽ ወንድምም አለው። ሰርጌይ በኮምፒዩተር ዕድገት ጊዜ በማደጉ የኮምፒዩተር ፍላጎቱ ከልጅነቱ ነው የጀመረው። መጀመሪያው ያገኘው ኮምፒዩተር አንድ ኮሞዶር 64 ሲሆን ይህንንም ከአባቱ ዘጠነኛው ልደት በዓሉ ላይ ነው ያገኘው። በሒሳብና ኮምፒዩተር ያለውን ተስዕጦም ገና ትንሸ እያለ ነው ያሳየው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በፔንት ብራንች ሞንቴሶሪ ትምህርት ቤት የወሰደ ሲሆን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ በኤላኖር ሩዝቬልት ትምህርት ቤት አጠናቋል። ቤተስቡም የሒሳብ ዕውቀቱንና ሩሲያኛው በማዳበር ረድተውቷል። በሴፕቴምብር 1990 እ.ኤ.አ.፣ ሰርጌይ ሒሳብና ኮምፒዩተር ሳይንስ ለማጥናት ሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ፣ ኮሌጅ ፓርክ ገባ። በሜይ 1993 እ.ኤ.አ. የባችለር ሳይንስ ካማግኘቱ በኅላ በስኮላርሺፕ ኮምፒዩተር ሳይንስን ለማጥናት ወደ ስታንፎርድ ዩኒቨርስቲ ሄደ። ከዛም ከታሰበው ጊዜ በፊት በኦገስት 1995 እ.ኤ.አ. የማስተርስ ዲግሪውን ተቀበለ። ባሁኑ ጊዜ ግን የፒ.ኤች.ዲ. ጥናቱን ላልተወስነ ጊዜ አቋርጦ ጉግል ውስጥ እየሰራ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን የዘጠነኛ ዓመት የልደት በዓሉን ሲያከብር ከአባቱ የተበረከተለት ስጦታ ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ኮምፒዩተር አንድ ኮሞዶር 64 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጋና ጋና በአፍሪካ አትላንቲክ ጠረፍ ላይ የተገኘ አገር ሲሆን ከ24 ሚሊዮን ኗሪዎች በላይ አሉት። የጋና ስራ ቋንቋ እንግሊዝኛ ሲሆን፣ ሌሎች ኗሪ ቋንቋዎች በተለይም ትዊኛ (አካንኛ) በሰፊ ይነገራሉ። የ«ጋና» ስያሜ በታሪክ የድሮ «ጋና መንግሥት» ወይም «ዋጋዱጉ መንግሥት» ለማክበር በ1949 ዓም ተመረጠ። እንዲያውም ያው መንግሥት እስከ 1068 ዓም ድረስ ከጋና ወደ ስሜን-ምዕራብ በአሁኑ ማሊ ይገኝ ነበር እንጂ የዛሬውን ጋና መቸም አልገዛም። «ጋና» በትክክል የዋጋዱጉ መንግሥት አለቆች ማዕረግ ሆኖ ነበር። ዋጋዱጉ መንግሥት በ1068 ዓም ግድም ከወደቀ ቀጥሎ፣ የአካን ብሔሮች ከዚያው ፈልሰው በዛሬው ጋና ሠፈሩና መጀመርያ ግዛቶችን መሠረቱ። ከ1662 እስከ 1949 ዓም ድረስ የአሻንቲ መንግሥት ባካባቢው ቆየ፤ በ1894 ዓም ይህ የብሪታንያ አሻንቲ ጥብቅ ግዛት ሆነ። ከ1949 ዓም አስቀድሞ የዩናይትድ ኪንግደም ጥገኛ ግዛት ሲሆን በወርቅ ሀብቱ ምክንያት «የወርቅ ጠረፍ ጥገኛ ግዛት» (ጎልድ ኮስት ፕሮቴክቶሬት) በመባል ይታወቅ ነበር። ከ1984 ዓም ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ እና ፓርላሜንታዊ መንግሥት ኖሮታል። አብዛኞቹ ኗሪዎች (70%) በተለይ በደቡቡ ክርስቲያን ሲሆኑ፣ በተለይ በስሜኑ 16% የእስልምና ተከታዮች ናቸው። የተረፉትም የኗሪ አረመኔነትን እምነቶች ይከተላሉ። የጋና ዋና ምርቶች ካካዎ፣ ዘይት፣ አልማዝ ናቸው። በአለሙ ከሁሉ ትልቅ የሆነው ሠው ሰራሽ ሐይቅ፣ ቮልታ ሐይቅ፣ በጋና ይገኛል። እግር ኳስ ከሁሉ የተወደደው እስፖርት ነው። የጋና አበሳሰል በተለይ በኮቤ፣ ጐርጠብ፣ የስኳር ድንች፣ ባቄላ፣ በቆሎ፣ ኦቾሎኒ፣ ባሚያና ሩዝ ይሠራል። \n \nጥያቄ: የጋና ዋና ምርቶች ምንድን ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ካካዎ፣ ዘይት፣ አልማዝ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቀጭኔ ቀጭኔ በአፍሪካ የሚኖር ባለሙሉ ጣት ሸሆኔ ጡት አጥቢ አራዊት ሲሆን በምድር ከሚገኙ እንሰሳት በርዝማኔ የመጀመሪያውን ደረጃ ይዞ ይገኛል። ወንዱ ከ 4.4 እስከ 5.5 ሜትር ርዝማኔና 1,360 ኪሎግራም ክብደት ያስመዘግባል። እስካሁን በሪኮርድ የተያዘው የ 5.87ሜና የ2000ኪ.ግ ቀጭኔ ነው። ሴቶቹ በጥቁቱ አነስ ብለው ይታያሉ። እነዚህን ፍጥረታት በአራዊት ማቆያ ቦታዎች አንገታቸውን ከታጠሩበት አጥር በላይ ወጣ አድርገው የተመለከተ ሰው በአፍሪካ ቁጥቋጦዎች ነፃ ሆነው ሲሮጡ ያላቸውን ውበትና ግርማ መገመት ያስቸግራል። የቀጭኔ እንቅስቃሴ ትልቅ ግርማ ያለውና እንደ ውኃ ሙላት የሚፈስ ነው። በገላጣው የግጦሽ መስክ ላይ በሚጋልቡበት ጊዜ ቁመናቸው ትንሽ እንቅፋት ቢነካቸው ወድቀው የሚሰባበሩ ያስመስላቸዋል። ይሁን እንጂ እስከ 1, 300 ኪሎ ግራም የሚደርስ ክብደት ያላቸው ወንድ ቀጭኔዎች ቀልጣፋና ምንም የማያደናቅፋቸው ሯጭ ከመሆናቸውም በላይ በሰዓት እስከ 60 ኪሎ ሜትር ሊሮጡ ይችላሉ። ይህች አስደናቂ ፍጡር የምትገኘው በአፍሪካ ብቻ ነው። እርጋታዋና ሰላማዊ ተፈጥሮዋ ዓይን ይስባል። የቀጭኔ ፊት በዓይነቱ ልዩ የሆነና ቆንጆ ሊባል የሚችል ሲሆን ረዥምና ጠባብ ጆሮዎች፣ ሁለት ትናንሽ ቀንዶች እንዲሁም ጠቆር ያለ ለስላሳ ጠጉር አላት። ዓይኖቿ በጣም ትላልቅና ጥቁር ሲሆኑ ረዣዥም በሆኑ ቅንድቦች ይጠበቃሉ። ቀጭኔ ያን በመሰለ ከፍታ ላይ ሆና ሩቅ ስትመለከት ፊቷ ላይ የየዋህነት ገጽታ ይታይባታል። በጥንት ዘመናት ቀጭኔ ባላት አስደሳች ቁመና እንዲሁም ጨዋ፣ ዓይነ አፋርና ሰላማዊ ባሕርይ ያላት በመሆኑ በጣም ተወዳጅና ትልቅ ግምት የሚሰጣት ነበረች። በብሔራት መካከል ሰላምና በጎ ፈቃድ መኖሩን ለማመልከት የቀጭኔ ግልገሎች ለነገሥታትና ለገዥዎች በገጸ በረከትነት ይሰጡ ነበር። ጥንታዊ በሆኑት የአፍሪካ አለቶች ላይ ቀለማቸው የደበዘዘ የቀጭኔ ሥዕሎች እስከ ዛሬ ይታያል። ከእንስሳት ሁሉ ቀጭኔን በቁመት የሚወዳደር የለም። ሙሉ ዕድሜ ላይ የደረሱ ወንድ ቀጭኔዎች ከእግራቸው ኮቴ አንስቶ እስከ ቀንዳቸው ድረስ ከ5.5 ሜትር የሚበልጥ ርዝመት አላቸው። በግብፃውያን ጥንታዊ ሥዕላዊ የአጻጻፍ ዘዴ ቀጭኔ በረዥም ቁመቷና አርቆ በመመልከት ችሎታዋ ምክንያት “መተንበይ” የሚለውን ግሥ ትወክል ነበር። ቀጭኔ በአፍሪካ መስኮች በሚሰማሩት የሜዳ አህዮች፣ ሰጎኖች፣ አጋዘኖችና ሌሎች እንስሳት መካከል ስትቆም እንደ ማማ ሆና ትታያለች። ቁመቷና አርቆ የማየት ችሎታዋ ማንኛውንም አደጋ ገና ከሩቅ ለማወቅ ያስችላታል። ስለዚህ የቀጭኔ መኖር ለሌሎች እንስሳት የመረጋጋት ስሜት እንደሚፈጥር ጥርጥር የለውም። \n \nጥያቄ: በብሔራት መካከል ሰላምና በጎ ፈቃድ መኖሩን ለማመልከት ለነገሥታትና ለገዥዎች ምን ዓይነት ገጸ በረከትነት ይሰጥ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የቀጭኔ ግልገሎች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቺኑዋ አቼቤ በሙሉ ስሙ ሲጠራ አልበርት ቺኑዋሉሞጉ አቼቤ ይሰኛል። ምናልባትም ናይጄሪያ ካሉዋት ምርጥ ፀሃፍት ዝርዝር ውስጥ በአንደኛ ደረጃ የሚሰለፍ ሳይሆን አይቀርም። በ1930 እ.ኤ.አ. ኦጊዲ በተባለች የናይጄሪያ ግዛት ከአዜያህ ኦካፎ እና ከጃኔት አቼቤ ተወለድ። በ1953 እ.ኤ.አ. ከለንደን ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል። ለአቼቤ ድንቅ ሥራ የተባለለት \"Things Fall Apart\" 50 ወደሚሆኑ የአለም ቁዋንቁዋዎች የተተርጎመ ሲሆን ወደ 10,000,000 ቅጂዎች እንደተሸጡለት ይነገራል። አቼቤ ከአፍሪካ ፀሃፍት ሁሉ ሥራው በበዙ ቁዋንቁዋዎች በመተርጎም ክብረ ወሰኑን እንደያዘ ነው። ብዙዎችም ይኸው ድርሰቱ በአለም እስከዛሬ ከተደረሱ ምርጥ ልበ-ወለዶች መካከል እንደሆነ ይስማማሉ። አቼቤ ከ30 ከሚበልጡ ዩኒበርስቲዎች የክብር ዶክትሬት የተቀበለ ሲሆን ብዙ ሽልማቶችንም ከተለያዩ ድርጅቶች አግኝቷል። ይሁንና እስከ አሁን ድረስ የኖቤል ሽልማት ለማግኘት አልታደለም። ይኸውም በብዙው ጽሁፉ የመራቡን አለም ዘረኛነት የሚተች በመሆኑ እንደሆነ ይነገራል። በ1990 ዓ.ም በደረሰበት የመኪና አደጋ ምክንያት ከወገቡ በታች መንቀሳቀስ የተሳነው ሲሆን ኒው ዮርክ ውስጥ በሚገኘው የባርድ ኮሌጅ የቋንቋና ሥነ-ፅሁፍ ፕሮፌሰር ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ቺኑዋ አቼቤ ሙሉ ስሙ ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አልበርት ቺኑዋሉሞጉ አቼቤ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየትነበርሽ ንጉሴ የትነበርሽ ንጉሴ በኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ እና የአካል ጉዳተኛ መብትቶች ተሟጋች ናት ፡ እ.ኤ.አ በ 2017 \"የአካል ጉዳተኞችን መብቶችን እና ማካተቶችን በማስተዋወቅ እንዲሁም በማኅበረሰቡ ውስጥ ያሉየአእምሮ ውቅርን መለወጥ የሚያበረታታ ሥራዋ\" ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድን ተሸልማለች። የትነበርሽ ንጉሴ የአይን ብርሃኗን ያጣችው በ 5 ዓመቷ ነበር ። ይህ አጋጣሚ በተወለድችበት በአማራ ክልል በስፋት ይተገበር ከነበረው ያለ አድሜ ጋብቻ አንድታመልጥ እድሉን እንደፈጠረላት ትናገራለች። ፡፡የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቷን በሻሸመኔ ካቶሊክ የዓይነ ስውራን ት/ቤት ተከታትላ ወደ ዳግማዊ ምኒልክ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (አካታች ትምህርት ቤት) ገብታ እስከ 12 ኛ ክፍል እዚያ ተማረች። በትምህርት ቤቱ ካላት አካዳሚክ ተሳትፎ በተጨማሪ የተማሪዎችን አማካሪ ጨምሮ ከ 6 በላይ የክለቦችን ክበባት መርታለች ፡፡ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን በመቀላቀል የመጀመሪያ ዲግሪ በሕግ ሁለተኛ ዲግሪ በማኅበራዊ ሥራ አግኝ ታለች፡፡ ከመደበኛ ትምህርት ውጭ በልዩ ልዩ እንቅስቃሴዎች ውስጥ በተከታታይ ትሳተፋለች በዚህም የመኢአድ የፀረ ኤድስ እንቅስቃሴን ከ2004 - 05 በመምራት በ 2006 የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ (አአዩ) ሴት ተማሪዎች ማህበርን በመመስረት እንዲሁም የማህበሩ የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት በመሆን አገልግላለች ፡፡ \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ እና የአካል ጉዳተኛ መብትቶች ተሟጋች ማን ትባላለች?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የትነበርሽ ንጉሴ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበርግጥም የመጀመሪያው በሰፊው ተግባራዊ የሆነ የቴሌቭዥን ስርዓት ስራ ላይ የዋለው በጀርመን አገር ሲሆን ይኸውም በ1929 እ.ኤ.አ. ነው። በ1936 እ.ኤ.አ. (1928 ዓም) ጀርመን ሃገር ተደርጎ የነበረውን የኦሎምፒክ ውድድር በቴሌቭዥን ሊሰራጭ ቻለ፣ ህዝቡም ውድድሩን እቤቱ ሆኖ ቀጥታ ሲካሄድ ለማየት ቻለ። ከዚያ መጀመርያው ጥቁርና-ነጭ ፕሮግራሚንግ በዩናይትድ ኪንግደም 1928 ዓም፤ በአሜሪካ 1933 ዓም ተደረገ። በአፍሪካ መጀመርያው ጣቢያዎች በ1952 ዓም በናይጄሪያና ደቡብ ሮዴዝያ (አሁን ዚምባብዌ) ተሰራጩ፣ በኢትዮጵያ የቴሌቪዥን ስርጭት አገልግሎት (ኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን) የጀመረው በ1956 ዓም ሆነ። ሁለት አገራት - እነርሱም ቱቫሉና ኪሪባስ - ምንም የራሳቸውን ቴሌቪዥን አሁን አያሰራጩም፤ ሆኖም የሌላ አገር ስርጭት እዚያ ሊታይ ይችላል። ከዚያ ቤርድ በግንቦት 26 ቀን 1920 (ጁላይ 3, 1928 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የከለር ቴሌቪዥን ስርጨት ሙከራ አደረገ። ነገር ግን ከለር ቴሌቪዥን ቢፈጠረም ለሚከተሉት ብዙ ዓመታት ስርጭት ባብዛኛው ጥቁርና ነጭ ብቻ ሆኖ ቀረ። ይሄው ቴክኖዎሎጂው በጣም ውድ፣ በጣም ከባድና በትክክል ያልተስተካከለ ስለ ሆነ ነው። በየጥቂቱ ከ1946 ዓም (1954 እ.ኤ.አ.) ጀምሮ አገራት ወደ ከለር ስርጭትና ከለሩን ማሳየት የሚችል ቴሌቪዥን ወደ መሸጥ ይዛወሩ ጀመር። በጥር ወር 1946 ዓም NBC የተባለው አሜሪካዊ ስርጭት ጣቢያ በከፊሉ ወደ ከለር ተሸጋገረ፤ ብዙ ሰዎች ግን ያንጊዜ ከለር ማሳያ ቴሌቪዥን ለመግዛት ገና አልቻሉም ነበር። ከ1955 እስከ 1959 ዓም ድረስ ሌሎቹ ትልልቅ አሜሪካዊ ጣቢያዎች ABC እና CBS ደግሞ ወደ ከለር ተዛወሩ፣ የከለርም ተቀባዮች ዋጋ እየተቀነሰ የሚይዩት ሕዝብ ቁጥር ደግሞ ከዚህ በኋላ እየተጨመረ ሄደ፤ ከረጅሙ ጥቁርና-ነጭ ዘመን ቀጥሎ ከለርም በኅብረተሠብ ያመጣው ለውጥ ለግዙፍነቱ በኋላ ኢንተርኔት እንደ ሆነ ያሕል ነው። ጃፓን በ1952 ዓም፣ ሜክሲኮ በ1955፤ ካናዳ በ1958፣ የአውሮፓ ኅብረትና የሶቪዬት ሕብረት በ1959፣ ኮት ዲቯር በ1962፣ አውስትራሊያ በ1967 ከለር ስርጭትን ጀመሩ። በኢትዮጵያም ከለር ስርጭት ከ1976 ዓም ጀምሮ ተገኝቷል። በ1977 ዓም ሮማኒያ ከጥቁርና-ነጭ ስርጭት ወደ ከለር ማሰራጨት የለወጠ በዓለም መጨረሻው ሃገር ሆነ። \n \nጥያቄ: በየት ሀገር የተካሄደው የኦሎምፒክ ውድድር ነው በቴሌቭዥን ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰራጨው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በጀርመን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኤርትራ ኤርትራ በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ አገሮች አንዷ ስትሆን በስሜን-ምዕራብ ከሱዳን፣ በሰሜን-ምስራቅ ከቀይ ባህር፣ በደቡብ ከኢትዮጵያ፣ በደቡብ-ምስራቅ ጅቡቲ ጋር ድንበር ትካለላለች። ኤርትራ የሚለው ስም ከላቲን የተወሰደ እና ስረ-መሰረቱ የግሪክ ሐረግ ሲሆን ትርጉሙም ቀይ ማለት ነው። ይህን ስም ለአካባቢው የሰጡት ጣሊያኖች በጥር ፲፰፻፺ ቅኝ ግዛታቸውን ሲያውጁ ነበር (ተመሳሳይ ስም በጀርመኖች 1870 እና ግብጾች ፲፰፻፷ወቹ በጥቅም ላይ ውለዋል፣ ነገር ግን የትኛውን ክፍል ስሙ እንደሚመለከት ግልጽ አልነበረም)። ኤርትራ፣ እንደ ሐገር፣ በጣሊያኖች ከተመሰረተች በኋላ በ5 ልዩ ሂደቶች ውስጥ በማለፍ ነው ያሁኑን ቁመናዋን የያዘችው። ከ1890 በፊት የነበረው የአካባቢው ታሪክ በ«ኤርትራ» ስር የሚጠና ባህይሆንም ስለአዲሱ ኤርትራ ግንዛቤ ስለሚያስጨብጥ ታሪክ ተመራማሪዎች ከ፲፰፻፺ በፊት ያለውንም ታሪክ ማጥናት ተገቢ እንደሆነ ይስማማሉ። በ1860ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ፣ የግብጹ መሪ ኢስማኤል ከዴቭ ፓሻ በናይል ተፋሰስ ላይ ሰፊ የግብጽ ቅኝ ግዛት ለማበጀት ተነሳ። ለዚህ አዲሱ ግዛቱ ካርቱምን ዋና ከተማው በማድረግ የሱዳን ግዛቱን አጸና። ቀጥሎም የቀይ ባህርን ጠረፎች በ1865 ከተቆጣጠረ በኋላ በ1870ዎቹ መጀመሪያ ሐረርንና ተሻግሮ ሕንድ ውቅያኖስ ውስጥ ግዛቶችን አበጀ። እንግዲህ በኒህ ግዛቶቹና በሱዳን መካከል የነበረው ብቸኛ መገናኛ መንገድ ካርቱም-ከሰላ- ከረን -ምፅዋ ብሎ የሚዘልቅ ነበር። ስለሆነም በ1872 ይህን ስልታዊ መንገድ የክዴቭ ፓሻ ሰራዊቶች ተቆጣጠሩ። መቆጣጠር ብቻ አይደለም በየመንገዱ ምሽግ እየሰሩና የአውሮጳ ምስዮናውያንን እርሻ ቦታ እየሰጡ ቅኝ ግዛት አበጁ። በዚህ ሳይቆጠቡ፣ የመንገዱን ደህንነት ዋስትና ለማስጠበቅ ሲሉ የአካባቢውን ደጋማ ክፍል መያዝ ግድ አላቸው። ደጋማው ክፍል በዚህ ወቅት በአጼ ዮሐንስ ግዛት ስር ነበር። \n \nጥያቄ: ኤርትራ የት አህጉር ትገኛለች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አፍሪካ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሊቢያ ኦይል ሊሚትድ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ኢንቨስትመንትና የነዳጅ ንግድ ሥራ ለማስፋፋት መወሰኑን አስታወቀ፡፡ ዱባይ ከሚገኘው የሊቢያ ኦይል ሆልዲንግ ዋና መሥሪያ ቤት ወደ አዲስ አበባ የመጣው ኮርፖሬት ማኔጅመንት፣ ከሁለት ሳምንት በፊት በአዲስ አበባ ሒልተን ሆቴል የአንድ ሳምንት ጉባዔ አካሂዷል፡፡ ከ18 የአፍሪካ አገሮች የሊቢያ ኦይል ሥራ አስኪያጆች በስብሰባው ላይ ተሳትፈዋል፡፡ የሊቢያ ኦይል ኢትዮጵያ የሽያጭና ማርኬቲንግ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘካሪያስ ወሊቃ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ማኔጅመንቱ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ዕድገት በመገምገም ኩባንያው ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ኢንቨስትመንትና የነዳጅ ንግድ እንቅስቃሴ ለማስፋፋት ውሳኔ አሳልፏል፡፡ የኩባንያው ባለአክሲዮኖች ካፀደቁት ኢትዮጵያ ውስጥ የ150 ሚሊዮን ብር ኢንቨስትመንት ለማካሄድ አቅዷል፡፡ \n \nጥያቄ: ሊቢያ ኦይል በኢትዮጵያ ምን ያህል መዋለ ነዋይ ለማፍሰስ ወሰነ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የ150 ሚሊዮን ብር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: በ1945 ዓ.ም. ብሪታንያ ደቡብና ሰሜን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ ጋር አንድ ላይ በማድረግ የፈጠረችው ፌዴሬሽን ምን ይባል ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየ2010 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ የ2010 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ ፲፱ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የነበረ ሲሆን ከሰኔ ፬ እስከ ሐምሌ ፬ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. በደቡብ አፍሪካ ተካሄዷል። ውድድሩን ለማቅረብ የተካሄደው ዕጣ ውስጥ የአፍሪካ ሀገሮች ብቻ እንዲሳተፉ ነበር የተፈቀደው። ደቡብ አፍሪካ ግብፅና ሞሮኮን በማሸነፍ የመጀመሪያው የዓለም ዋንጫን ያቀረበች አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ፊፋ ለውድድሩ ያቀረበው ጠቅላላ የሽልማት ገንዘብ $420 ሚሊዮን ነው። ይህም ከ2006 እ.ኤ.አ. ውድድር ሽልማት ገንዘብ የስልሳ ከመቶ ዕድገት አለው። ከዚህ ውስጥ $40 ሚሊዮን የሚሆነው ተጫዋቾቹ ለሚጫወቱበት ክለቦች ተጫዋቾቹ ለሚደርስባቸው ጉዳት መካካሻ እንዲሆን ተሰጥቷል። ከውድድሩ በፊት እያንዳንዱ ቡድን ለዝግጅት ወጪው $1 ሚሊዮን ተረከበ። ግጥሚያዎቹ በዘጠኝ ከተማዎች ውስጥ በሚገኙ አስር ስታዲየሞች ውስጥ ነው የተካሄዱት። የዋንጫ ጨዋታው በጆሃንስበርግ ከተማ በሚገኘው ሶከር ሲቲ ስታዲየም ነው የተከናወነው። የምድብ ድልድል ሥነ ስርዓቱ በኬፕ ታውን፣ ደቡብ አፍሪካ በሚገኘው ኬፕ ታውን ዓለም አቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል በኅዳር ፳፭ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. ተከናወነ። ሥነ ስርዓቱ የቀረበው በደቡብ አፍሪካዊቷ ተዋናይ ሻርሊዝ ቴሮን እና የፊፋ ዋና ጸሐፊ ዠሮም ቫልክ ነው። የዕጣ ኳሶቹን ያወጡት ዴቪድ ቤክሃም፣ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ፣ ጆን ስሚት፣ መካያ ንቲኒ፣ ማቲው ቡዝ እና ሲምፊዌ ድሉድሉ ናቸው። የፊፋ ዳኛዎች ኮሚቴ ፳፱ ዳኛዎችን ለዓለም ዋንጫ መርጧል። እነዚህም ከኤ.ኤፍ.ሲ. አራት፣ ከካፍ አስር፣ ከኮንሜቦል ስድስት፣ ከኮንካካፍ አራት፣ ከኦ.ኤፍ.ሲ. ሁለት እና ከዩኤፋ አስር ዳኛዎችን ያጠቃልላል። እንግሊዛዊው ዳኛ ሀዋርድ ዌብ የዋንጫ ጨዋታውን እንዲዳኝ ተመርጧል። \n \nጥያቄ: ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው የአለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታው የት ስታዲየም ተካሄደ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሶከር ሲቲ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nነሐሴ ፳፯ ነሐሴ ፳፯ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፯ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፱ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፰ ዕለታት ይቀራሉ። ፲፮፻፶፰ ዓ/ም ለሦስት ቀናት የጋየውና አስር ሺህ ሕንጻዎችን ያወደመው የሎንዶን ትልቁ እሳት ተነሳ። ፲፯፻፵፬ ዓ/ም የምዕራብ አውሮፓ አገራት ዘመን አቆጣጠራቸውን በለወጡ በሁለት መቶ ዓመታቸው፣ ብሪታንያ የጎርጎራዊ ዘመን አቆጣጠርን ተቀበለች። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በጠላት ወረራ ዘመን የሸዋ አርበኞች ቡልጋ ላይ ተሰባስበው የልጅ ኢያሱን ልጅ መልአከ-ፀሐይ ኢያሱን አነገሡ። አዲሱ 'ንጉሥ' ወዲያው የአርበኞች መሪ ለነበሩት ባላምባራስ አበበ አረጋይ የራስነት ማዕርግ ሰጠ። መልአከ-ፀሐይ ኢያሱ መስከረም ፳፬ ቀን ፲፱፻፴፩ ዓ/ም አረፎ አንኮበር አካባቢ በሚገኘው ዞማ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተቀብሯል። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ጃፓን በተሸናፊነቷ እጇን ሰጠች። ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ነጻነትን አስከትሎ በጃዋሃርላል ኔህሩ ምክትል ፕሬዚደንትነት የሚመራ የሕንድ ጊዜያዊ መንግሥት ተመሠረተ። ፲፱፻፺ ዓ/ም የርዋንዳን ፍጅት አስከትሎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያቋቋመው የወንጀለኛ ፍርድ ቤት ጃን ፖል አካዬሱ የተባለውን የቀድሞ ከንቲባ ላይ ፍርዱን የወንጀለኛነት ፍርድ ፈረደበት። \n \nጥያቄ: በነሐሴ ፳፯ ቀን ፲፮፻፶፰ ዓ/ም ለሦስት ቀናት የቆየው የሎንዶን ትልቁ እሳት ምን ያህል ሕንጻዎችን አቃጠለ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ አስር ሺህ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nድረ ገጽ መረብ የድረ ገጽ መረብ (ወይም ኢንተርኔት) በጣም ብዙ የኮምፒዩተር አውታሮችን የያዘ የመገናኛ መረብ ነው። በመረቡ ውስጥ ብዙ ድረ ገጽ ይገኛሉ። ከዚያ በላይ በርካታ የመነጋገርና መገናኘት መንገዶች አሉ። ከሁሉ አስቀድሞ የተፈጠረ ክፍለ-ኢንተርኔት «USENET» የሚባለው አገልግሎት ነው። ይህ በ1973 ዓ.ም. (1980 እ.ኤ.አ.) አካባቢ ሲጀመር በተለይ ለዩኒቨርሲቴዎችና ኮሌጆች ብቻ የታወቀ መገናኛ ሆኖ ቆየ። ይህ ጽሑፍ በተገናኙት ኮምፒውተሮች ላይ መልጠፍ የሚፈቅድ ሥርዓት ብቻ እንጂ ስዕል ወይም ሌላ ነገር አልነበረም። መጀመርያው e-mail አድራሳዎች የተሰጡት ከዚያ ዘመን ነው። ዛሬም ብዙዎች ተጠቃሚዎቹ ግን ስንኳ ስለ USENET መኖሩን አያውቁም። መጀመርያው ድረ ገጽ የተፈጠረው በ1983 ዓ.ም. (1990 እ.ኤ.አ.) ሆነ። \n \nጥያቄ: ብዙ የኮምፒዩሮችን የያዘ የመገናኛ መረብ ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የድረ ገጽ መረብ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቀጭኔ ከዝሆን በስተቀር ማንኛውም ሌላ እንስሳ ሊደርስ በማይችልበት ከፍታ ላይ የሚገኙ ረዣዥም ቀንበጠቦችን ለመብላት የሚያስችል አስደናቂ አፈጣጠር አላት። ልዩ የሆነ የመቆንጠጥ ችሎታ ያለው የላይኛው ከንፈሯና እንደተፈገለው የሚተጣጠፍ ችሎታ ያለው ምላሷ ሹል በሆኑ እሾሆች የታጠሩ ቅጠሎችን ለመቀንጠብ ያስችሏታል። ቀጭኔዎች በቀን እስከ 34 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕፅዋት መመገብ ይችላሉ። የተለያዩ ዕፅዋትን የሚበሉ ቢሆኑም ይበልጥ የሚመርጡት በአፍሪካ ሜዳዎች የሚገኙትን እሾሃማ ግራሮች ነው። አንድ ወንድ ቀጭኔ ምግብ ለመፈለግ ምላሱን እስከ 42 ሳንቲ ሜትር መዘርጋት ይችላል። የቀጭኔ አንገት በጣም አስደናቂ የሆነ የመተጣጠፍ ችሎታ አለው። ይህም ላይኛዎቹን የዛፍ ቅርንጫፎች ለመቀንጠብ በምታደርገው እንቅስቃሴ ረዥሙን ራሷን እንደ ልቧ ለማዘንበልና ለማዟዟር ያስችላታል። ለቀጭኔ ወደ ላይ መንጠራራት በጣም ቀላል ነገር ሲሆን ተጎንብሶ ውኃ መጠጣት ግን ይከብዳታል። ወደ ውኃ ጉድጓድ በምትቀርብበት ጊዜ የፊት እግሮቿን ቀስ በቀስ ከፍታ ካራራቀቻቸው በኋላ ወደ ውኃው ለመድረስ እንድትችል ሁለት ጉልበቶቿን አጠፍ ታደርጋለች። ቀጭኔዋ እንዲህ ባለው አመቺ ባልሆነ ሁኔታ እያለች ረዥም አንገቷን እስከ መጨረሻ ትዘረጋለች። ደግነቱ ግን ከምትመገባቸው ቅጠላ ቅጠሎች በቂ እርጥበት ስለምታገኝ ቶሎ ቶሎ መጠጣት አያስፈልጋትም። የቀጭኔ አንገትና ትከሻ የቅጠል ቅርፅ ባላቸውና ቀጫጭን በሆኑ ነጭ መስመሮች ያጌጠ ነው። ቀለማቸው የተለያየ ሲሆን ከወርቃማ ዳለቻ አንስቶ እስከ ቡናማ እንዲያውም ጠቆር እስካለ ቀለም ይደርሳል። የቀጭኔ ዕድሜ እየገፋ በሄደ መጠን ቀለሟም እየጠቆረ ይሄዳል። ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው። አንዲት ነፍሰ ጡር ቀጭኔ ልጅዋን ከ420 እስከ 468 ለሚደርሱ እርግዝና ቀናት ከተሸከመች በኋላ ሁለት ሜትር ቁመት ያለው ግልገል ትወልዳለች። ግልገሏ በምትወለድበት ጊዜ ራስዋን ታስቀድምና ከሁለት ሜትር ከፍታ ላይ ወደ መሬት ትወረወራለች። ይሁን እንጂ በ15 ደቂቃ ውስጥ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባት እየተውተረተረች ትነሳና ጡት ለመጥባት ዝግጁ ትሆናለች። ከሁለት ወይም ከሦስት ሳምንት በኋላ በደመ ነፍስ ተመርታ የግራር ቀንበጦችን መለቃቀም ስለምትጀምር ብዙም ሳትቆይ ረዥም እርምጃ ያላትን እናትዋን ተከትላ ለመሄድ የሚያስችል ጉልበት ታገኛለች። አንዲት የቀጭኔ ግልገል በጣም ውብ መልክ ሲኖራት የወላጆችዋ አነስተኛ ግልባጭ ነች። ቁመቷ ከቀጭኔ ርዝመት ጋር ሲወዳደር አጭር ብትሆንም ከብዙ ሰዎች ቁመት ግን ትበልጣለች። በእናቷ ጥንቃቄ የተሞላበት ጥበቃ ተማምና አላንዳች መሸበር አካባቢዋን የምትማትረው ግልገል ላያት ሁሉ ልዩ መስህብ አላት። ግልገል ቀጭኔዎች በተወለዱበት ወራት በግልገል መዋያ ተሰባስበው ሙሉውን ቀን ዕረፍት በማድረግ፣ በመጫወትና በአካባቢያቸው የሚሆነውን ነገር በመመልከት ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ። የቀጭኔ ግልገል ለማመን በሚያዳግት ፍጥነት ያድ⁠ጋል። በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ አንድ ሜትር የሚያክል ቁመት ሲጨምር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በእጥፍ ያድጋል። በአንድ ሳምንት ብቻ 23 ሳንቲ ሜትር ያህል ሊያድግ ይችላል! እናትዬው ለልጅዋ ከፍተኛ ጥበቃ የምታደርግ ሲሆን ልጅዋ የተወሰነ ርቀት እንድትዘዋወር ብትፈቅድላትም ሩቅ የማየት ችሎታ ስላላት በዓይኗ ትከታተላታለች። ቀጭኔ ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ስላላት ከአንበሳ በቀር የሚያጠቃት ጠላት የለም። ቢሆንም ይህችን የምታምር ፍጥረት የሰውን ያህል በብዛት አድኖ የገደለ የለም። ቀጭኔ በሚያምር ቆዳዋ፣ በሚጣፍጥ ሥጋዋና አንዳንዶች ምትሐታዊ ኃይል አለው በሚሉት ረዥምና ጥቁር ጭራዋ ምክንያት እጅግ ተፈላጊ ስለሆነች በአሁኑ ጊዜ የዚህች ሰላማዊ ፍጡር የወደፊት ሕልውና ስጋት ላይ ወድቋል። በአንድ ወቅት በብዙ የአፍሪካ አካባቢዎች እንደ ልብ ትታይ የነበረችው ቀጭኔ በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው በቂ ጥበቃ በሚደረግላት ፓርኮች ብቻ ሆኗል። የቀጭኔ አካላዊ ቅርጽና ግዝፈት ችግሮች ማስከተሉ አይቀርም ብሎ የሚያስብ ይኖር ይሆናል። በጣም ትልቅ ቁመትና ረዥም አንገት ስላላት የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖራትና ወደ ሁሉም የአካሏ ክፍሎች ደም እንዲደርስ ማድረግ የማይቻል ነገር ሊመስል ይችላል። ለምሳሌ ያህል ቀጭኔ አንገቷን ወደ መሬት ስታጎነብስ በስበት ኃይል ምክንያት ብዙ ደም ወደ ጭንቅላቷ ፈስሶ አንጎሏን ማጥለቅለቅ ነበረበት። ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ደሟ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ልቧ ተመልሶ ራሷን እስከ መሳት ሊያደርሳት ይገባ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ነገር አይደርስም። ለምን? የቀጭኔ የደም ዝውውር ሥርዓት በዓይነቱ ልዩ ለሆነው ለዚህች እንስሳ ቅርጽና መጠን እንዲያገለግል ሆኖ በታላቅ ጥበብ የተሠራ ነው። ልቧ ራሱ በጣም ትልቅ ሲሆን ደሙን ሦስት ሜትር ተኩል ገደማ ርቆ እስከሚገኘው እስከ አንጎላ ለመግፋት የሚያስችል አቅም አለው። በደቂቃ እስከ 170 ጊዜ የሚመታውና 7 ሳንቲ ሜትር ያህል ውፍረት ባለው ጡንቻ የተገነባው የቀጭኔ ልብ ከሰው የደም ግፊት በሦስት እጥፍ የሚበልጥ ግፊት ያመነጫል። ወደ አንጎል የሚሄደውን ደም የሚሸከመው ካሮቲድ የተባለው የደም ቧንቧና ከአንጎል ወደ ልብ የሚመለሰውን ደም የሚሸከመው ጀጉላር የተባለው የደም ቧንቧ እንዲህ ያለውን ከፍተኛ ግፊት መቋቋም የሚያስችል መጠን ሊኖራቸው ይገባል። በእርግጥም እነዚህ የደም ቧንቧዎች ከ2.5 ሳንቲ ሜትር በላይ ስፋት ያላቸው ከመሆኑም በላይ ጠንካራና የመለጠጥ ችሎታ ባላቸው ሕዋሳት የተገነቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥንካሬና የመለመጥ ችሎታ አላቸው። ቀጭኔ ከጭንቅላቷ ጎንበስ በምትልበት ጊዜ ወደ አንጎሏ የሚሄደውን የደም ፍሰት የሚቆጣጠሩ ልዩ መቆጣጠሪያዎች አሏት። አንጎልና አንገት በሚገናኙበት ቦታ ላይ ትልቁ ካሮቲድ የደም ቧንቧ ሬቴ ሚራቢሌ ተብሎ ከሚጠራ አስደናቂ የሆነ መረብ መሰል አካል ይገናኛል። በከፍተኛ ኃይል ተገፍትሮ የመጣው ደም እዚህ ጋር ሲደርስ በጣም በርካታ ወደሆኑ ትናንሽ የደም ሥሮች እንዲገባ ስለሚደረግ የደሙ ግፊት ተስተካክሎ በአንጎል ላይ ጉዳት የማያስከትል ይሆናል። ቀጭኔዋ ራስዋን ጎንበስ በምታደርግበት ጊዜ ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው መረብ ይለጠጣል፤ ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ይኮማተራል። ይህም የስበት ኃይል የሚያሳድረው ተጽዕኖ ሚዛኑን የጠበቀ እንዲሆን ማድረግና የደም ግፊቷ በእጅጉ ቀንሶ ራሷን የምትስትበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ለመከላከል ይረዳታል። የሳይንስ ሊቃውንት በጣም አስደናቂ ርዝመት ያለው የቀጭኔ አንገት ያሉት አከርካሪዎች ቁጥር ከአይጥ ወይም ከብዙዎቹ አጥቢ እንስሳ ጋር እኩል መሆኑን ሲያውቁ በጣም ተደንቀዋል! ይሁን እንጂ የቀጭኔ አከርካሪዎች በጣም ረዣዥሞችና እርስ በርሳቸው ልዩ በሆነ ሁኔታ የተሰካኩ በመሆናቸው እንደ ልብ ሊተጣጠፉ ይችላሉ። ቀጭኔ አንገቷን መጠምዘዝና ማጠፍ ስለምትችል ሁሉንም የአካሏን ክፍሎች ለመላስም ሆነ ረዣዥም የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ለመድረስ ትችላለች። \n \nጥያቄ: የቀጭኔ ልብ ከሰው የደም ግፊት በምን ያዕል የሚበልጥ ግፊት ያመነጫል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በሦስት እጥፍ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአማራ (ክልል) አማራ (ክልል 3) ከዘጠኙ የኢትዮጵያ ክልሎች አንዱ ሲሆን ከ 1994 በፊት አራት የሀገሪቱን ዋና ወና ክፍለ ሀገራት የ ካትት ነበር እነሱም በጌምድር ጐጃም ወሎና ሸዋ ነበሩ ።የአማራ ብሔራዊ ክልል ጅኦግራፊያዊ አቀማመጥ በ8° 45 እስከ 13° 45 ሰሜን የኬንትሮስ እና በ35° 46 እስከ 40° 25 ምስራቅ የኬንትሮስ መስመር ውስጥ ይገኛል። በምስራቅ የአፋርና የኦሮሚያ ክልሎች፣ በምዕራብ ሱዳን እና ቤንሻንጉል-ጉምዝ ክልል፣ በሰሜን የትግራይ ክልልና በደቡብ የኦሮሚያ ክልል ያዋስኑታል። የቆዳ ስፋቱ ፻፶፯ሺ፸፮ ካሬ ሜትር ሲሆን ከአገሪቱ አሥራ አምስት በመቶ ድርሻ ይይዛል። የክልሉ ሕዝብ ብዛት ደግሞ በ፳፻፪ ዓ/ም 20,875,456 እንደነበር የተገመተ ሲሆን ከአገሪቱ ጠቅላላ ሕዝብ 33.9% አካባቢ ድርሻ ይይዛል ተብሎ ይገመታል። ክልሉ በ፲ ዞኖችና በ፻፷፮ የገጠርና የከተማ ወረዳ አስተዳደሮች የተከፋፈለ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ፴፰ የሚሆኑት የከተማ አስተዳደሮች ናቸው። የአማራ፣ የአገው፣ የኦሮሞና የሌሎች ብሔረሰቦች በጋራ የሚኖሩበት ክልል ነው። እንዲሁም የአማራ ክልል አሁን ላይ የክልል ከተማው ባህር ዳር ነው። በክልሉ አልፎ አልፎ ከሚታዩ የመንግሥትና የማኅበራት ደኖች፣ በደሴቶች፣ በአብያተ ክርስቲያናት፣ በወንዞች ዳርቻና ሰው ሊደርስባቸው በማይችሉ ገደላማና ተራራማ ስፍራዎች ከሚገኙ ጥቂት ደኖች በስተቀር ሊጠቀስ የሚችል ከፍተኛ የደን ሀብት ጋር በቅርብ የተያያዘ ነው። በዚህ ረገድ በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የሚገኙ እንደ ቀይ ቀበሮ፣ ዋልያ፣ ጭላዳ ዝንጀሮ እንዲሁም በምዕራባዊው የክልሉ አካባቢ ዝሆን አንበሳና ነብር፣ ሰጐንና የተለያዩ አዕዋፋት በስተቀር ከፍተኛ የዱር እንስሳት ክምችት ካለመኖሩም በላይ በተለያዩ አካባቢዎች ባሉ ጥቂት የደን ቅሪቶችና ዋሻዎች የነበሩት አነስተኛ ቁጥር ያላቸው አራዊቶችም ለዘመናት በደረሰው የደን መጨፍጨፍና መራቆት ምክንያት ከክልሉ ወደ ሌላ አካባቢ እንደተሰደዱ ይታወቃል። ክልሉን የማዕድን ሀብት አስመልክቶ በሚገባ የተጠናከረ ጥናት ባይኖርም ከክልሉ ስነ-ምድራዊ ሁኔታዎችና ከተካሄዱ አንዳንድ ጠቋሚ ጥናቶች መረዳት እንደሚቻለው በክልሉ ውስጥ የተለያዩ ማዕድናት እንደአሉ ይገመታል። በዚህም መሠረት በሰሜን ሸዋ የኦፓል ማዕድን፣ በሰሜን ጐንደር፣ በጭልጋና በደቡብ ወሎ በአምባሰል ወረዳ የድንጋይ ከሰል ክምችት እንዳሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ከዚህም በተጨማሪ ለግንባታ ሥራ የሚውል በቂ የድንጋይ፣ የኖራ ድንጋይ፣የሸክላ አፈር፣ ጅኘሲየም፣ የጌጣጌጥ ማዕድናት እንዲሁም በዓባይ ሸለቆ የዕብነ በረድ ሐብቶች እንዳሉ ጥናቶች ይጠቁማሉ። ይሁን እንጅ በውል የሚታወቀው ሐብትም ቢሆን በበቂ ሁኔታ አልለማም። \n \nጥያቄ: የኦፓል ማዕድን በአማራ ክልል በየትኛው ዞን ይገኛል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በሰሜን ሸዋ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሰርጌይ ብሪን ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን ኦገስት 21, 1973 እ.ኤ.አ. ተወለደ ሩሲያዊ-አሜሪካዊ ሲሆን ጉግልን በመፍጠሩ ይታወቃል። በሩሲያ የተወለደ ሲሆን፥ ብሪን ከላሪ ፔጅ ጋር ጉግልን ከመጀመሩ በፊት ኮምፒዩተር ሳይንስና ሒሳብ አጥንቷል። ብሪን ባሁኑ ጊዜ የጉግል ቴክኖሎጂ ፕሬዝዳንት በመሆኑ ወደ 14.1 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ገንዘብ አለው። ይህም ከዓለም 26ኛ እና ከአሜሪካ 12ኛው ሀብታም ሰው ያደርገዋል። ሰርጌይ በሞስኮ፣ ሩሲያ ለየይሁዳ ቤተሰብ ተወለደ። 6 ዓመቱ ሲሆን ሰርጌይና ቤተሰቡ ወደ አሜሪካ መጡ። አባቱ ሚካኤል በሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ ማቲማቲሻን ሆኖ እስክ ዛሬ ድረስ ያስተምራል። የስርጂ እናት ዩጂኒያ ብሪን ማቲማቲሻንና ሲቭል ኢንጅነር ሆና ለናሳ ትሰራለች። ሳሙኤል የሚባል ታናሽ ወንድምም አለው። ሰርጌይ በኮምፒዩተር ዕድገት ጊዜ በማደጉ የኮምፒዩተር ፍላጎቱ ከልጅነቱ ነው የጀመረው። መጀመሪያው ያገኘው ኮምፒዩተር አንድ ኮሞዶር 64 ሲሆን ይህንንም ከአባቱ ዘጠነኛው ልደት በዓሉ ላይ ነው ያገኘው። በሒሳብና ኮምፒዩተር ያለውን ተስዕጦም ገና ትንሸ እያለ ነው ያሳየው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በፔንት ብራንች ሞንቴሶሪ ትምህርት ቤት የወሰደ ሲሆን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ በኤላኖር ሩዝቬልት ትምህርት ቤት አጠናቋል። ቤተስቡም የሒሳብ ዕውቀቱንና ሩሲያኛው በማዳበር ረድተውቷል። በሴፕቴምብር 1990 እ.ኤ.አ.፣ ሰርጌይ ሒሳብና ኮምፒዩተር ሳይንስ ለማጥናት ሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ፣ ኮሌጅ ፓርክ ገባ። በሜይ 1993 እ.ኤ.አ. የባችለር ሳይንስ ካማግኘቱ በኅላ በስኮላርሺፕ ኮምፒዩተር ሳይንስን ለማጥናት ወደ ስታንፎርድ ዩኒቨርስቲ ሄደ። ከዛም ከታሰበው ጊዜ በፊት በኦገስት 1995 እ.ኤ.አ. የማስተርስ ዲግሪውን ተቀበለ። ባሁኑ ጊዜ ግን የፒ.ኤች.ዲ. ጥናቱን ላልተወስነ ጊዜ አቋርጦ ጉግል ውስጥ እየሰራ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን ያለው የሀብት መጠን በዓለም እና በአሜሪካ በስንተኛ ደረጃ እንዲቀመጥ አስችሎታል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከዓለም 26ኛ እና ከአሜሪካ 12ኛው ሀብታም ሰው ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጋሞጐፋ ዞን አርባ ምንጭ ከተማ ከ1955 እስከ 1993 ዓ.ም ድረስ የጋሞ ጐፋ ጠቅላይ ግዛት፣ የሰሜን ኦሞ አስተዳደር አካባቢና ከዚያም የሰሜን ኦሞ ርዕሰ ከተማ በመሆን ለቀድሞዎቹ የጋሞ፣ የጐፋ፣ የጋርዱላና ሐመር ባኮ አውራጃዎች ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ማዕከል ሆና ያገለገለች ስትሆን ከ1993 ዓ.ም ወዲህ ባሉት ዓመታት ደግሞ አስራ አምስት ወረዳዎችንና ሁለት የከተማ አስተዳደሮችን አቅፎ ለያዘው ጋሞ ጐፋ ዞን ዋና ከተማ በመሆን እያገለገለች የምትገኝ ከተማ ነች፡፡ በዞኑ ውስጥ የሚገኙ የጋሞ፣ የጎፋ፣ የዘይሴ ፣ የጌዲቾና የኦይዳ ብሄረሰቦችን ጨምሮ ጥቂት የማይባሉ ሌሎች የሀገራችን ብሔር ብሔረሰቦች ተወላጆች ተከባብረውና ተቻችለው በፍቅርና በሰላም የሚኖሩባት አርባ ምንጭ ከተማ በቀለማት አደራደሩ ትኩረትና ተወዳጅነት የማይለየው የጋሞ ብሔረሰብ የክብርና የማዕረግ ልብስ እንዲሁም መታወቂያው የሆነውንና ዱንጉዛ በመባል የሚታወቀው ባህላዊ ልብስ ጨምሮ ሌሎች የኢትዮጵያ የሸማ ጥበብ አልባሳት ሥራዎች መፍለቅያ አካባቢዎች እምብርት ከመሆኗም በተጨማሪ በባህላዊ ቤት አሰራራቸው በለቅሶና ሠርግ ስርዓታቸው በባህላዊ የማምረቻና የመገልገያ ቁሳቁሶቻቸው የብዙዎችን አድናቆትና አግራሞትን ላስጫሩት የጋሞ፣ የጐፋ፣ የዘይሴ፣ የጌዲቾና የኦይዳ ብሔረስብ ህዝቦች መዲና ነች፡፡ ከባህር ወለል በላይ ከ1,300 እስከ 1,500 ሜትር ከፍታ ላይ ስትገኝ የአርባ ምንጭ ከተማ አየር ንብረት በተለምዶ ቆላማ የሚሉት አይነት ሲሆን፤ የከተማዋ ዓመታዊ አማካይ የሙቀት መጠኗ 240c ነው፡፡ የከተማዋ ዓመታዊ አማካይ የዝናብ መጠኗ 900 ሚሊ ሜትር ሆኖ ግንቦት፣ ሰኔ፣ መስከረምና ጥቅምት ወራት ከፍተኛ የዝናብ መጠን በዓመቱ ውስጥ የሚመዘግብባቸው ወራት ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡ በተፈጥሮ ውበት በታደለው ድንቅ ስፍራ እንደመከተሟ አርባዎቹ ምንጮች የሚመነጩባትን መንትያዎቹ የአባያና ጫሞ አስደናቂ የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ፤በአካባቢው ታይተው የማይጠገቡ የዱር እንሰሳት ያለሀሳብ የሚፈነጩባትን የነጭ ሣር ብሔራዊ ፖርክ፤ የአዞ እርባታ ጣቢያ፤ የአዞ ገበያ እና የተፈጥሮ ደኖችን ሌሎች ከህሊና ጓዳ የማይፋቅ ትዝታን ጥለው የሚያልፉ ሃብቶች ባለቤት ናት በተፈጥሮ ውበት በታደለው ድንቅ ከተማ እንደመከተሟ አርባዎቹ ምንጮች የሚመነጩባትን የአባያና ጫሞ አስደናቂ የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ያለሀሳብ የሚፈነጩባትን ፤ የነጭ ሣር ብሔራዊ ፖርክ፤ የአዞ እርባታ ጣቢያ፤ የአዞ ገበያን በአካባቢው ታይተው የማይጠገቡ የዱር እንሰሳት እና የተፈጥሮ ደኖችን ይገኛሉ፡፡ የዞኑን አስደናቂ የቱሪስት መስህቦች እንግዶቻችንን በማስጎብኘት ከታዋቂ የዓሳ ምርታችን ፣ ከማንጎ ፤ ከሙዝ እና በአፕል ማሳችን እየተንሸራሸርን የማይረሱ ትዝታዎችን ጥለው ያልፋሉ፡፡ \n \nጥያቄ: አርባ ምንጭ የየትኛው ዞን ዋና ከተማ ናት?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ጋሞ ጐፋ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኤዎስጣጤዎስ በግዕዝ ኤዎስጣቴዎስ ወይም ዮስጣቴዎስ፣ ከሐምሌ ፭ ቀን ሺ፪፻፷፭ – ሺ፪፫፵፬ በኢትዮጵያ ሰለሞናዊ መንግሥት አገዛዝ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ታላቅ መሪ የነበሩ አባት ናቸው። በጣም አጥብቀው ከሚያስተምሩት ትምህርት ስለ ሰንበት መከበር ነበረ። ተከታዮቻቸው የኤዎስጣጤዎስ ቤት ወይም በግል ሲጠሩ ኤዎስጣጤዎሳውያን ይባሉ ነበር ለተዋህዶ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ ናቸው። የኤዎስጣጤዎስ መጀመሪያ ስማቸው ማዕቀበ እግዚእ ሲሆን ከእናታቸው ከስነሕይወትና ከአባታቸው ከክርስቶስ ሞዐ ሐምሌ ፳፩ ቀን ፩ሺ፪፷፭ ተወለዱ። እኒህም ደጋግና እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎች ነበሩ ። ኤዎስጣጤዎስ የታወቀውን ደብራቸውን (ደብረ ፀራቢን) የመሠረቱት የተወለዱበት ቦታ እዛው (እንድርታ) እንደሆነ ገድላቸው ይገልፃል። በወጣትነታቸው ዘመን በሺ፪፸፪ አካባቢ ከአጎታቸው አባ ዳንኤል (የደብር ስማቸው አባ ዘካርያስ) ቆርቆር (ደብረ ማርያም) አስተዳዳሪ ጋር እንዲኖሩ ወደ ገራልታ ይላካሉ። አባ ዳንኤልም ኤዎስጣጤዎስን ተቀብለው ተገቢውን የሃይማኖት ትምህርትና የደብር ሕይወትን ካስተማሩ በኋላ ማዕቀበእግዚእ በ፲፭ ዓመቱ ቅስና ሥራዬ መሆን አለበት ብሎ በወሰደው ውሳኔ መሠረት ስሙ ኤዎስጣጤዎስ ተብሎ ተሰየመ። ኤዎስጣጤዎስ ከአባ ዳንኤል የቅስና መዐረጋቸውን ካገኙ በኋላ የራሳቸውን ደብር በ(ሰራይ) መሠረተው በዚያም በማስተማር ብዙ ተማሪዎችን አፈሩ ። በሰንበት ላይ ያተኮረ አመለካከታቸውን ለይተው ያስተምሩ ነበር ፣ የሚቃወማቸው አቡነ ያእቆብ ፫ኛው አስኪመጣ ድረስ። ከዛ ግን ከተከታዮቻቸው ከባካርሞስ ፣ መርቆርዮስ ፣ ገብረእያሱ ጋር ኢትዮጵያን ለቀው ወደ ግብፅ (ካይሮ) ገብተው በአሌክሳንድሪያው ጳጳስ ቢንያም ፪ኛው ፊት በሰንበት ባላቸው አመለካከት ፀንተው ከዛም ወደ ኢየሩሳሌም አምርተው በመጨረሻም የሕይወታቸው ማብቂያ ወደ ሆነችው አርሜኒያ ገብተው ኖሩ። \n \nጥያቄ: ኤዎስጣጤዎስ ማን ተቃወማቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አቡነ ያእቆብ ፫ኛ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዳምጠው አየለ ዳምጠው አየለ (23.11. 1944 አ/ም – 27.10. 2006 አ/ም) ባህላዊ የኢትዮጵያ ዘፋኝ ነበር። በሃምሌ 23 1944 አ/ም ከእናቱ ወይዘሮ ሸዋየ ተካና ከአባቱ አየለ ካሰኝ በመራቤቴ ሰሜን ሸዋ ተወለደ። ልጅነቱን በእረኝነት፥ በግብርና እንዲሁም በቆሎ ተማሪነት እንዳሳለፈ ይናገራል። እድሜውም ለትምህርት ሲደርስ ባቅራቢያው በሚገኘው መራኛ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገብቶ ተምሯል። ዳምጠው ህይወቱ እስካለፈችበት ጊዜ ድረስ ለረዥም ጊዜ አብሯት የኖረው ባለቤቱ አልማዝ ይመር ትባላለች። ከአልማዝ ይመር አብዩ ዳምጠውና ቤቴልሄም ዳምጠው የሚባሉ ሁለት ልጆችን አፍርቷል። ዳምጠው መራቤቴ እያለ በየባእላቱ መዝፈን፣ ማቅራራት እንዲሁም መሸለል ይወድ እንደነበር ተናግሯል። በተለይም ጥምቀትን በማድመቅ ይታወቅ ነበር። የ 6ኛ ክፍል ተማሪ እያለ ክፍሌ ሞገስ የሚባል መምህሩ ወደ አዲስ አበባ ይዞት እንደመጣ ይናገራል። ባጋጣሚም የምድር ጦር ማስታወቂያ አውጥቶ ስለነበር ይፈተንና ያልፋል። የምድር ጦር ካምፕ ውስጥም እንዲኖር ይደረጋል። የዘፋኝነት ሙያው በዚህ አጋጣሚ ነበር የጀመረው። ዳምጠው ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማዉና መነሻ የሆነው አበበ ተሰማ እንደሆነ ይናገራል። ዳምጠው አየለ በምድር ጦር ከ 30 አመት በላይ አገልግሏል። የኢትዮዽያ ምድር ጦር በ1927 አ/ም ተመስርቶ በ1983 አ/ም የፈረሰ የሙዚቃ ቡድን ነበር። ዳምጠው በመንግስት ለውጥ ምክንያት እስከፈረሰበት ጊዜ ድረስ አብሮ እንደነበር ይናገራል። ምድር ጦርም እያለ ከነታምራት ሞላ፣ ሲራክ ታደሰ፣ ተክሌ ደስታ ፣ ጥላየ ጨዋቃ፣ ክፍሌ አቦቸር እንዲሁም ሌሎች የጦሩ አባላት ጋር ሰርቷል። ከሌሎች የሙዚቃ ቡድንም ጋር አብሮ ሰርቷል። ለምሳሌ ያክል ከነ ክቡር ጥላሁን ገሰሰ፣ ሙሃሙድ አህመድ፣ ብዙነሽ በቀለ ፣ ሙሉቀን መለስ፣ ፀሃየ ዮሃንስ፣ ቴድሮስ ታደሰ፣ቴድሮስ ካሳሁን እንዲሁም ሌሎችም ጋር ሰርቷል። የዳምጠው አየለ የመጀመሪያ የህትመት ስራው በ1963 አ/ም ሲሆን ወፌ ላላ የሚለው የሸክላ ስራ ነበር። ዳምጠው አየለ ባጠቃላይ 13 ሲዲዎችን ሰርቷል። ዳምጠው አየለ ኖርዌይ ሃገር በስደት ለ 8 አመት ያክል ኖሯል። ኢትዮጵያም ከገባ በኋላ አዲስ አበባ በሚገኘው በቅ/ገብራኤል ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በተወለደ በ 62 አመቱ ሰኔ 27 2006 አ/ም ቀን ህይወቱ አልፏል። የቀብር ስነስርአቱም ወዳጅ፣ ዘመድ እንዲሁም አድናቂዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ዳምጠው አየለ በስንት ዓመቱ ሞተ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ 62 አመቱ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሜሪላንድ ሜሪላንድ (እንግሊዝኛ፦ Maryland) በአሜሪካ የምትገኝ ስቴት ስትሆን ምዕጻረ ቃሏ MD ወይም Md. ነው። ሜሪላንድ ከአሜሪካ አስራሶስት ጥንታዊ ስቴቶች አንዷ ናት። ከሜሪላንድ ጋር የሚገናኙ ስቴቶች ፔንስልቫኚያ ፣ ቨርጂኚያ ፣ ዌስት ቨርጂኚያ ፣ እና ዴላዌር እያሉ፤ ደግሞ በኮለምቢያ ክልል (ዋሽንግተን ዲ.ሲ.)ና በአትላንቲክ ውቂያኖስ ትወሰናለች። የቼሳፒክ ወሽመጥ ስቴቱን መሃል ለመሃል ይከፍለዋል። የሜሪላንድ ከፍተኛ ቦታ የባክቦን ተራራ ጫፍ ነው። የሜሪላንድ አየር ሁኔታ ከቦታ ቦታ ይለያያል። የምስራቅ ክፍሉ ሞቃታማ በጋና መካከለኛ ክረምት የአየር ሁኔታ ሲኖረው የምዕራብ ክፍሉ ደግሞ መካከለኛ በጋ እና በጣም ቀዝቃዛ ክረምት አለው። የሜሪላንድ ጠቅላላ ምርቶች በ2003 እ.ኤ.ኣ. ወደ 212 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ነው። በዚሁ ዓመት የአንድ ሰው የዓመታዊ ገቢ በኣማካይ 37,446 የአሜሪካን ዶላር ነበር ፣ ከአገሩ 5ኛ። ከፍተኛ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ፣ ወታደራዊ ካምፖች እና የሳይንስና የሕክምና ተቋማት በዚሁ ክፍላገር ይገኛሉ። የስቴቱ ዋና ያውሮፕላን ማረፊያ ባልቲሞር-ዋሽንግተን ዓለም አቀፍ ያውሮፕላን ማረፊያ (BWI) ነው። በ1996 የሜሪላንድ ጠቅላላ የህዝብ ብዛት 5,558,058 ነው ተብሎ ይገመታል። ከዚሁ ውስጥም 583,900ቹ ወይም 10.6 በመቶ ሌላ ስቴት ወይም አገር የተወለዱ ነዋሪዎች ናቸው። አብዛኛው ህዝብ የስቴቱ መዓከላዊ ክፍል ውስጥ ይኖራል። \n \nጥያቄ: በ2003 እ.ኤ.ኣ. የሜሪላንድ ስቴት ነዋሪዎች ዓመታዊ ገቢ ምን ያህል ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 37,446 የአሜሪካን ዶላር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሚያዝያ ፴ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፵ ኛው ዕለትና የወርኅ ፀደይ (በልግ) ፴፭ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ ሉቃስ ፻፳፮ ቀናት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመን ማርቆስ ደግሞ ፻፳፭ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፰፻፸፬ ዓ/ም - እምባቦ በሚባል ሥፍራ የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ ሠራዊት እና የጎጃም ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ሠራዊት ውጊያ ገጥሞ ድሉ የንጉሥ ምኒልክ ሲሆን፣ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ተማረኩ። ፲፰፻፺ ዓ/ም - በጣልያ አበጋዙ ባቫ-በካሪስ ብዙ መቶ ሰልፈኞች በመድፍ ገደላቸው። ፲፱፻፳፭ ዓ/ም - የሕንድ አባት በሚል ቅጽል ስም የሚታወቀው ሞሃንድራስ ካራምቻንድ ጋንዲበአገሩ የእንግሊዝን አስተዳደር በመቃወም የሃያ አንድ ቀን የ'ረሀብ አድማ' ጀመረ። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - በአውሮፓ የሁለተኛው የዓለም ጦርነትን ማክተም ምክንያት በማድረግ 'ሴቲፍ' በተባለች የአልጄሪያ ከተማ በተካሄደ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ፻፫ አውሮፓውያን በመሞታቸው፣ የገዢው የፈረንሳይ መንግሥት ፖሊሶች እና ወታደሮች ባካሄዱት ጨካኝ በቀላ እስከ ስድስት ሺ አልጄሪያውያን ተጨፍጭፈዋል። የዚህ አረመኔያዊ ድርጊት ሳቢያ በመላው የሰሜን አፍሪቃ የፈረንሳይን ቅኝ ገዢነት ማክተሚያ አብሳሪ እንደሆነ ታሪካውያን ይዘግባሉ። ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - በሩሲያኖች የተገነባው የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ዶክቶር ምናሴ ኃይሌ እራሳቸውን ከሥልጣናቸው አስወገዱ። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - አቶ ለገሰ ዜናዊ አስረስ፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር አድዋ ላይ ተወለዱ። \n \nጥያቄ: የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ መቼ ተጣለ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፲፱፻፶፯ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአዳም ረታ አዳም ረታ ልቦለድና ግጥም በአማርኛ የሚጽፍ ኢትዮጵያዊ ደራሲ ነው። አዳም ረታ በ1950 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ተወለደ። በትምህርት አለም - በጂኦግራፊ የመጀመሪያ ዲግሪውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተቀብሏል። ሁለተኛ (የማስተርስ) ዲግሪውን ደግሞ በውጭ ሀገር አግኝቷል። የሚፅፈው በአብዛኛው ልቦለዶችን ቢሆንም ግጥሞችንም ይፅፋል። በተለያዩ ጊዜያት ግጥሞቹ በተለያዩ መፅሔቶች ላይ ታትመዋል። ያልታተሙ ግጥሞችም አሉት። ከተደራሲው ጋር የተዋወቀበት እና በኢትዮጵያ ስነ ጽሑፍ ተከታታዮችና አንባቢዎች ልብ ውስጥ የመሠረት ድንጋይ ያስቀመጠበት “አባ ደፋር እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች” በኩራዝ አሳታሚ ድርጅት የታተመው በ1977 ዓ.ም ነው። (በዚህ መድብል ውስጥ አራት ስራዎችን አዋጥቷል፡ “ድብድብ”፣ “ዕብዱ ሺበሺ”፣ “ሲሮኮ” እና “ሲፊንክስ”) ሜጋ አሳታሚ ድርጅት በ1990 ዓ.ም ባሳተመው “ጭጋግና ጠል” የአጭር ታሪኮች ስብስብ “ዘላን” የተባለው ልቦለዱ ታትሟል። እነዚህ ሁለቱ ከሌሎች ደራሲዎች ስራዎች ጋር የታተሙለት ስለሆነ እንደ ወጥ ሳይቆጠሩ ነው ከላይ የሰፈረው የተባለው። በ1981 ዓ.ም በኩራዝ አሳታሚ የታተመው “ማህሌት” የደራሲው የመጀመሪያ ወጥ የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ መፅሀፍ ነው። በሻማ ቡክስ በ1997 ዓ.ም የታተመው “ግራጫ ቃጭሎች” እንደ ብሉይ (classic) ሥራ ሊታይ የሚችልና የደራሲው ልዩ ብቃት የታየበት ወጥ ረጅም ልብወለድ ነው። በ2001 ዓ.ም ሁለት ልዩ ስራዎች ይዞ የቀረበው አዳም፡ የአጫጭር ልብወለዶች ስብስብ የሆነው “አለንጋና ምስር” እና እርስ በርሳቸው በቀጭን የታሪክ ክር የሚገናኙ ልብወለዶች (ኖቬላዎች) ያካተተው “እቴሜቴ ሎሚ ሽታ” ለአንባቢያን አበርክቷል። ይህ የአጻጻፍ ስልቱ ሕጽናዊነት የሚባል ሲሆን ደራሲው በሌሎቹ መጻሕፍቱም ውስጥ በስፋት ተጠቅሞበታል፡፡ በቀጠሉት ሦስት ዓመታት በየዓመቱ አንዳንድ መፅሐፍ ለአንባቢያ ያደረሰ ሲሆን በ2002 ዓ.ም “ከሰማይ የወረደ ፍርፍር”፣ በ2003 ዓ.ም “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ” እና በ2004 ዓ.ም “ሕማማት እና በገና” ታትመው ለንባብ በቅተዋል። “ከሰማይ የወረደ ፍርፍር” በተሰኘው መፅሀፉ ድንቅ የፋንታሲ (“ፈንጠዚያ”) ሥራዎች የተካተቱ ሲሆን በ”ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ” ለመጀመሪያ ጊዜ መቼቱን ከሀገር ውጭ በማድረግ የውጭውን ሕይወት በስሱ የዳሰሰ ሲሆን ከሌሎቹ ስራዎቹ በተለየ መልኩ ስለሀገራችን ፖለቲካ ወጣ-ገባ መንገድ በታዛቢ አይን ምልከታው፣ ትውስታውን … አስፍሯል፡፡ ሕማማትና በገና የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ ሲሆን ለየት ያለ ቅርፅ ያላቸው አንዳንድ ልቦለዶች ተካተውበታል። ፍልስፍናውና ስልቱ ሕፅናዊነት በሚል ስያሜው ይፋ ሆኗል። \n \nጥያቄ: ለመጀመሪያ ጊዜ መቼቱን ከሀገር ውጭ ያደረገበት መፅሃፍ ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡ \n \nጥያቄ: ሳውዲ አረብያ በሰሜን ምስራቅ የሚያዋስኑዋት የትኞቹ ሀገራት ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nከ6 አመት ጦርነት በኋላ ገላውዲወስ ተገደለና ሚናስ ስልጣን ላይ ወጣ። ለሚቀጥሉት 4 አመታት፣ እንደቀደመችው ንግስት እሌኒ በመንግስቱ ውስጥ ከፍተኛ ተሰሚነትን አገኘች። ቀጥሎም በካቶሊክ እና በኦርቶዶክስ ሃይማኖት መካከል በተነሳው ሽኩቻ የኦርቶዶክስ ሃይማኖትን በመደገፍ በጽናት ቆማለች። ይሁንና በዚህ ምክንያት በተነሳው ጸብ የፖርቹጋል ካቶሊኮች ሊገደሉ ሲሉ በማማለድ ስራ ጉዳት እንዳይደርስባቸው አድርጋለች። ቤርሙዴዝ የተባለው ታውቂው የፖርቹጋል ተጓዥም ንጉሱን ገላውዲወስን በማናደዱ ከመገደል የተረፈው በሰብለ ወንጌል ተራዳኢነት ነበር። የስፔኑ ጀስዊት ፓትሪያርክ ኦቨዶም ከሞት የተረፈው በንግስቲቱ ምክንያት ነበር። ሠርፀ ድንግልን ወደስልጣን እንዲወጣም ከጦረኞቹ በላይ ያገዘችው እናት ንግስት ሰብለ ወንጌል ነበረች። ይህ ምርጫዋ የተሳካ ነበር ምክንያቱም ሰርጸ ድንግል ለ34 አመት ሲገዛ አገሪቱን በመከላከል ወደ ሰላም አሸጋግሯል። ሰብለ ወንጌል በአጼሠርፀ ድንግል ዘመን፣ በ1560 ዓ.ም. አመድ በር በተባለ ቦታ አረፈች። አጼ ልብነ ድንግል የራሱንና የሰብለ ወንጌልን ምስሎች የክሪት ሠዓሊ በመቅጥር ካሳለ በኋላ ግብጽ ወደ ሚገኘው ቅዱስ አትናቲዮስ ገዳም እንዳስላከው ተመዝግቦ ይገኛል። \n \nጥያቄ: አጼ ልብነ ድንግል የራሱንና የሰብለ ወንጌልን ምስሎች ወደ የት ላከው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ቅዱስ አትናቲዮስ ገዳም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበ1240 አካባቢ በግብጽ አገር ቅብጡ አቡል ፋዳዒል እብን አል-አሣል ፍትሐ ነገሥት በአረብኛ ጻፉ። እብን አል-አሣል ሕጎቹን የወሰዱት በከፊል ከሃዋርያት ጽህፈቶችና ከሕገ ሙሴ፤ በከፊልም ከድሮ ቢዛንታይን ነገስታት ሕጎች ነበር። መጽሐፉ በግዕዝ ተተርጉሞ ወደ ኢትዮጵያ የገባበት ወቅት በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን በ1450 አከባቢ እንደነበር የሚል ታሪካዊ መዝገብ አለ። ቢሆንም መጀመርያ እንደ ሕገ ምንግሥት መጠቀሙን የተመዘገበው በዓፄ ሠርፀ ድንግል ዘመን (ከ1555 ጀምሮ) ነው። ፍትሐ ነገስት እስከ 1923 ዓ.ም. የብሄሩን ዋና ሕግ ሆኖ ቆየ። በ1904 ዓ.ም. ዐጼ 2 ምኒልክ የዘመናዊ ሕገ መንግሥት ፅንሰ ሀሳብ ተረድተው በጸሀፊው መምሬ ብስራት አንድ ሕገ መንግሥት የሚመስል ሰነድ ታተመ፤ ይህ ግን በውነት ሕገ መንግሥት አይባልም። «በምኒሊክ ስለተቋቋሙት ሚኒስቴሮች በምሳሌ የቀረበ ጽሑፍ» በምሳሌና በትርጓሜ የእያንዳንዱን ሚኒስቴር ሥራ እንደ ሰውነት አካላት አስመሰለ። ለምሳሌ፦ ኢትዮጵያ መጀመርያ ዘመናዊ ሕገ መንግሥት የተቀበለችው በ1923 አመተ ምኅረት በአጼ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የታወጀ ሲሆን የሕግ አማካሪ ቤቶች በሁለት ያስከፈለ ነው። ይህ የመንግሥታቸው ዋና መሠረት ሆኖ እስከ 1948 አ.ም. አገለገለ፤ በዚያ አመት ተሻሽሎ በወጣ ሕገ መንግሥት ሕዝቦች በመንግሥት ሥራ የሚጫወቱት ሚና እንደገና ተስፋፋ። ይህ ብቻ የአገሪቱ ሕገ መንግሥት ሆኖ እስከ 1967 አ.ም. ቆየ፤ የዛኔ በደርግ (በሕገ መንግስት እራሱ ባልሆነ ሂደት) ተሰረዘ። \n \nጥያቄ: ፍትሐ ነገሥት ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ በሕገ መንግሥትነት አገለግሎት መስጠት የጀመረው በማን ጊዜ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በዓፄ ሠርፀ ድንግል ዘመን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሱዳን ሱዳን በይፋ የሱዳን ሪፑብሊክ (አረብኛ السودان) ከአፍሪካ በስፋት ሦስተኛ ስትሆን በአህጉሪቱ ሰሜናዊ ምስራቅ ክልል ትገኛለች። ዋና ከተማዋ ካርቱም ነው። ከግብፅ ፣ ከቀይ ባሕር ፣ ከኤርትራ ፣ ከኢትዮጵያ ፣ ከደቡብ ሱዳን፣ ከመካከለኛው የአፍሪካ ሪፑብሊክ ፣ ከቻድ ፣ እና ከሊቢያ ጋር ድንበር ትካለላለች። የአባይ ወንዝ (ናይል) ሀገሪቱዋን ወደ ምሥራቅና ምዕራብ ይከፍላል። የአረብ ባህል ደንበኛ ሲሆን አብዛኛው ሕብዝ የእስልምና ዕምነት ተከታይ ነው። ሱዳን ከግብፅ የተጣመረ ረዥም ታሪክ አላት። የመጀመሪያው የሱዳን እርስ በርስ ጦርነት ከ1955 እስከ 1972 እ.ኤ.አ. ከዚያም ሁለተኛው የሱዳን እርስ በርስ ጦርነት ከ1983 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. ተከስቷል። በ1989 እ.ኤ.አ. በሰላማዊ መፈንቅለ መንግሥት ኦማር ሀሳን አህመድ አል-በሽር ሥልጣን ላይ የወጡ ሲሆን እራሳቸውን የሱዳን ፕሬዝዳንት ብለው ሾመዋል። የእርስ በርስ ጦርነቱ በሰላም ውል የቆመ ሲሆን ይህ ውል ያኔ የሀገሪቱዋ ደቡባዊ ክፍል ለነበረው ቦታ ራስን የመምራት መብት ሰጥቷል። በጃኑዋሪ 2011 እ.ኤ.አ. በተካሄደው ውሳኔ ሕዝብ (referendum) መሠረት በሱዳን ፈቃድ ደቡብ ሱዳን ሐምሌ ፪ ቀን ፳፻፫ ዓ.ም. ሉዓላዊ ሀገር ሆነች። ዋና ከተማዋ ካርቱም የሱዳን የፖለቲካ፣ ባህል እና ንግድ ማዕከል ናት። የሀገሪቱዋ መንግሥት በይፋ ፌዴራላዊ ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ቢሆንም ስልጣን ላይ ያለው ብሔራዊ ኮንግረስ ፓርቲ (National Congress Party) በሁሉም የመንግሥት አካላት ላይ ባለው ጥብቅ ቁጥጥር ምክንያት በብዙ የዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ ዘንድ መንግሥቱ አምባገነናዊ ተብሎ ይቆጠራል። \n \nጥያቄ: ደቡብ ሱዳን ነጻ ሀገር ለመሆን ሕዝበ ውሳኔ የተሰጠው መቼ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በጃኑዋሪ 2011 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበ17ኛው ክፍለ ዘመን ፖርቱጋል ክርስትናን ለመታደግ ሚሲዮናውያንንና ወታደሮችን ወደ ኢትዮጵያ በላከችበት ወቅት ለመጀመሪያ ጊዜ ፓድሬ ፔሬዝ የተባለ ሚሲዮናዊ፣ ጢስ እሳትንና የላይኛውን አባይን ለማየቱ ምስክርነቱን ሰጠ። በ18ኛው ክፍለ ዘመን ጄምስ ብሩስ የተባለ የስኮትላንድ ተወላጅ ከካይሮ እስከ ጣና ተጉዞ ለመጀመሪያ ጊዜ የአባይ መነሾ ጣና ሐይቅ ነው በማለት አወጀ።እስከዚያ ጊዜ ድረስ ማንም የውጭ ዜጋ አባይ (Abay) ከጣና እንደሚነሳ አያውቅም ነበር። samuel bakerሳሙኤል ቤከር(1821-1893) ሪቻርድ በርተን(1821-1890)ጆን ሀኒንግ ስፔክ (1827-1864) የአባይን መነሻ ፈልገው ወደ ታንጋኒካ ሐይቅ አመሩ እንጂ አንዳቸውም ወደ ኢትዮጵያ አልመጡም። በ1937 ቡክሀርት ባልደክኼር፣የተባለ የጀርመን ተወላጅ፣ የአባይን ምንጭ ከኢትዮጵያ ተራሮች ስር ማግኘቱን ለአለም አበሰረ።ታሪካችን በነ ባልድክኬርና በብሩስ ሲፃፍ ስታሮቹ እነሱ ናቸው።የታሪካችን ሞተር የሚንቀሳቀሰው በነሱ ነው። ቢሆንም በ1937 ጀርመናዊው ቡርክኸርት ወደ ኢትዮጵያ ሳይመጣ ኢትዮጵያዊው አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ “መፅሐፈ ሰዋሰው ወግስ፡ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ በሚለው በ1929 ባሳተሙት መፅሐፍ በገፅ 313 313“ ከአፍሪቃ ወንዞች ተለይተው፣ ነጭ ኒል፣ ጥቁር ኒል የሚመስሉ፤ በኦሪትም ግዮንና ኤፌሶን የሚባሉ ነጭ አባይና ጥቁር አባይ ናቸው ይባላል። እሊህም ኹለቱ ወንድማማቾች ወንዞች ከየምንጮቻቸው በኅይል ተነስተው፣ ግርማቸውን ለብሰው፣ተሰልፈው፣በየፊታቸው ያለውን ሐይቅ እንደመርከብ ሠንጥቀው አልፈው ሠራዊታቸውን ከፊትና ከኋላ አስከትለው እንደ ኹለት ንጉሥ ካርቱም ላይ ሲገናኙ ሁለትነታቸው ይቀርና፣ አንድ ወንዝ ብቻ ይሆናሉ፤ ከካርቱም ደግሞ እስካትባራ ወርደው ከተከዜ ጋር ይገጥማሉ።ከዚያ በኋላ ግን የሌላ ወንዝ ውኃ ሳይጨምሩ ባንድነት መላ ምድረ ግብፅን ከላይ እስከታች አጠጥተው አጥግበው አርክተው፣ አልፈው ተርፈው ወደ ሰሜን ጎርፈው ሜዲተራኒ ከሚባለው ከታላቁ ባሕር ይገባሉ።” በማለት መፃፋቸውን ሳንጠቅስ አናልፍም። በ1995 ዓ.ም ግሼ ሜዳ ላይ ከብቶች የሚጠብቅ 11 ዓመት ያልሞላው የውልሰው የተባለ እረኛ አገኘሁና “የአባይ ምንጭ የት ነው ብዬ ስጠይቀው” መሬት ቸክሎ የተደገፈውን በትር ከመሬቱ ላይ ነቅሎ ወደ ግልገል አባይ እያሳየኝ ከዚህ ነዋ አለኝ። አባባሉ ስንት ፈረንጆች የአባይን ምንጭ አገኘን ብለው የቦረቁበት ግኝት አይመስልም። “ እንዴት አወቅክ?” ስለው “ከብቶቼን የማጠጣ ከዚሁም አይደል? የከተማ ሰው አላዋቂ ነውሳ!” ብሎ ሸረደደኝ። በሆዴ ፈረንጆቹ የአባይን ምንጭ ከአንተ በፊት አገኘን እንደሚሉ ባወቅክ ስል፣ ውስጤን ያነበበ ይመስል፣ “ለፈረንጅ ሁሉ የአባይን ምንጭ እጃቸውን ጎትተን የምናሳይ እኛም አይዶለን እንዴ?” ብሎ አስደመመኝ። ግልገል አባይ ጣና ገብቶ መውጣቱን ያጠኑት ፈረንጆች ካልነገሩት ይህ እረኛ በምን ያውቃል ብዬ በጥያቄ ላፋጥጠው፤ ግልገል አባይ ጣና ገብቶ አባይን ሆኖ መውጣቱን ማን ነገረህ? ስለው “ጣና” “ጣና ነገረኝ” ሲለኝ ያው የተለመደውን የጎጃምን ዘፈን “ነገረኝ ጣና ነገረኝ፡አባይ” የሚለውን ዘፈን ሊዘፍን መስሎኝ ነበር። ያ የጎጃም እረኛ “ ማስረጃህ ምንድነው?” ስለው በክረምት አባይ ሲደፈርስ ግልገል አባይ የደፈረሰ ውኃ ይዞ ጣና ይገባና ከጣና ተንሳፎ ሲወጣ ጥርት አርጎ ይታያል።” ብሎ እረኛው ጂኦሎጂስት አስገረመኝ። \n \nጥያቄ: ጄምስ ብሩስ የአባይ ወንዝ መነሻ ጣና ሐይቅ ነው ያለው ከየት እስከ የት ተጉዞ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከካይሮ እስከ ጣና ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዳምጠው አየለ ዳምጠው አየለ (23.11. 1944 አ/ም – 27.10. 2006 አ/ም) ባህላዊ የኢትዮጵያ ዘፋኝ ነበር። በሃምሌ 23 1944 አ/ም ከእናቱ ወይዘሮ ሸዋየ ተካና ከአባቱ አየለ ካሰኝ በመራቤቴ ሰሜን ሸዋ ተወለደ። ልጅነቱን በእረኝነት፥ በግብርና እንዲሁም በቆሎ ተማሪነት እንዳሳለፈ ይናገራል። እድሜውም ለትምህርት ሲደርስ ባቅራቢያው በሚገኘው መራኛ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገብቶ ተምሯል። ዳምጠው ህይወቱ እስካለፈችበት ጊዜ ድረስ ለረዥም ጊዜ አብሯት የኖረው ባለቤቱ አልማዝ ይመር ትባላለች። ከአልማዝ ይመር አብዩ ዳምጠውና ቤቴልሄም ዳምጠው የሚባሉ ሁለት ልጆችን አፍርቷል። ዳምጠው መራቤቴ እያለ በየባእላቱ መዝፈን፣ ማቅራራት እንዲሁም መሸለል ይወድ እንደነበር ተናግሯል። በተለይም ጥምቀትን በማድመቅ ይታወቅ ነበር። የ 6ኛ ክፍል ተማሪ እያለ ክፍሌ ሞገስ የሚባል መምህሩ ወደ አዲስ አበባ ይዞት እንደመጣ ይናገራል። ባጋጣሚም የምድር ጦር ማስታወቂያ አውጥቶ ስለነበር ይፈተንና ያልፋል። የምድር ጦር ካምፕ ውስጥም እንዲኖር ይደረጋል። የዘፋኝነት ሙያው በዚህ አጋጣሚ ነበር የጀመረው። ዳምጠው ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማዉና መነሻ የሆነው አበበ ተሰማ እንደሆነ ይናገራል። ዳምጠው አየለ በምድር ጦር ከ 30 አመት በላይ አገልግሏል። የኢትዮዽያ ምድር ጦር በ1927 አ/ም ተመስርቶ በ1983 አ/ም የፈረሰ የሙዚቃ ቡድን ነበር። ዳምጠው በመንግስት ለውጥ ምክንያት እስከፈረሰበት ጊዜ ድረስ አብሮ እንደነበር ይናገራል። ምድር ጦርም እያለ ከነታምራት ሞላ፣ ሲራክ ታደሰ፣ ተክሌ ደስታ ፣ ጥላየ ጨዋቃ፣ ክፍሌ አቦቸር እንዲሁም ሌሎች የጦሩ አባላት ጋር ሰርቷል። ከሌሎች የሙዚቃ ቡድንም ጋር አብሮ ሰርቷል። ለምሳሌ ያክል ከነ ክቡር ጥላሁን ገሰሰ፣ ሙሃሙድ አህመድ፣ ብዙነሽ በቀለ ፣ ሙሉቀን መለስ፣ ፀሃየ ዮሃንስ፣ ቴድሮስ ታደሰ፣ቴድሮስ ካሳሁን እንዲሁም ሌሎችም ጋር ሰርቷል። የዳምጠው አየለ የመጀመሪያ የህትመት ስራው በ1963 አ/ም ሲሆን ወፌ ላላ የሚለው የሸክላ ስራ ነበር። ዳምጠው አየለ ባጠቃላይ 13 ሲዲዎችን ሰርቷል። ዳምጠው አየለ ኖርዌይ ሃገር በስደት ለ 8 አመት ያክል ኖሯል። ኢትዮጵያም ከገባ በኋላ አዲስ አበባ በሚገኘው በቅ/ገብራኤል ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በተወለደ በ 62 አመቱ ሰኔ 27 2006 አ/ም ቀን ህይወቱ አልፏል። የቀብር ስነስርአቱም ወዳጅ፣ ዘመድ እንዲሁም አድናቂዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ዳምጠው አየለ ወደ አዲስ አበባ ሲመጣ የትምህርት ደረጃው ስንተኛ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የ 6ኛ ክፍል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአብዱልራዛቅ እ.ኤ.አ. በ1994 ላይ ያሳተሙት ‹ፓራዳይዝ› የተሰኘው ልብ ወለድ ታንዛኒያ ውስጥ በ20ኛው ምዕት ዓመት የልጅ አስተዳደግ ምን እንደሚመስል ፍንትው አድርገው ያሳዩበት ነው። በዚህ ልብ ወለድም ዓለም አቀፉን የ‹ቡከር› ሽልማት ለማግኘት መቻላቸውን ቢቢሲ ዘግቦታል፡፡ እንደ የኖቤል ኮሚቴ የሥነ ጽሑፍ ክፍል አገላለጽም፣ ‹‹[የእሳቸው] ገጸ ባህርያት ሁሌም ቢሆን በባህልና አኅጉራት መካከል የሚሽከረከሩ፣ በአሁን ሕይወትና በመጪው ሕይወት መካከል የሚመላለሱ ናቸው። በቀላሉ ሊያልፉት የማይችሉት ከባድ እውነታ ውስጥ ናቸው፡፡›› እ.ኤ.አ. በ1948 በዛንዚባር የተወለዱት አብዱልራዛቅ፣ እ.ኤ.አ. በ1960ዎቹ መገባደጃ አገረ እንግሊዝ የገቡት ስደተኛ ሆነው ነው። በቅርቡ ጡረታ እስከወጡበት ዕለት ድረስ በካንተርበሪው የኬንት ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዝኛና የድኅረ ቅኝ ግዛት ሥነ ጽሑፎች ፕሮፌሰር ነበሩ። ሽልማቱ፣ ደራሲው ያለፉበትን የስደተኞች ቀውስንና ቅኝ አገዛዝን በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ውይይት እንዲደረግባቸው ያስችላል ብለዋል፡፡ ‹‹እነዚህ በየዕለቱ ከእኛ ዘንድ ያሉ ነገሮች ናቸው። ሰዎች እየሞቱ ነው፣ ሰዎች በዓለም ዙርያ አሁንም እየተጎዱ ነው፡፡ በእነዚህን ጉዳዮች ላይ በፍፁም ቀናነትና አስተውሎት መንገድ መነጋገር መላ መምታት አለብን፤›› ብለዋል የኖቤል ተሸላሚው አብዱልራዛቅ። ዓምና በሥነ ጽሑፍ ያሸነፉት አሜሪካዊው ገጣሚ ሊዊስ ግሉክ መሆናቸው ይታወሳል። የስዊድኑ አካዴሚ በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት ከሸለማቸው ታላላቅ ደራስያን መካከል ከአፍሪካ አኅጉር ስድስት ደራስያን ይገኙበታል፡፡ እነርሱም ዎሌ ሾንካ (ናይጀሪያ)፣ ነጂብ ማኅፉዝ (ግብፅ)፣ ናዲን ጎርዲመር (ደቡብ አፍሪካ)፣ ጄ.ኤም ኮትዚ (ደቡብ አፍሪካ)፣ እና ዶሪስ ሌሲንግ (ዚምባቡዌ -እንግሊዝ) ይገኙበታል፡፡ \n \nጥያቄ: በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ ምን ያህል አፍሪካውያን የኖቤል ሽልማት አግኝተዋል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ስድስት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nካሣ አያሌው ካሣ ተወልዶ ያደገው አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ ሽሮ ሜዳ ተብሎ የሚጠራው ሰፈር ነው። አባቱ አቶ አያሌው ካሣ እና እናቱ ወ/ሮ በላይነሽ ተ/ወልድ በጋብቻ ከተጣመሩ አንስቶ ቤታቸው የልጅ ፍሬ ማግኘት ሳይችል ረጅም ዓመታትን ቆይቷል። በዚህ ምክንያት እናቱ መካን እንደሆኑ ታምኖ የአብራካቸውን ክፋይ እንደማያገኙ እርግጠኛ ሆነዋል። ነገር ግን የወላጆቹ እርግጠኛ የሆኑበት ጉዳይ ከአምላክ ዘንድ ከተፈቀደው የሚገናኝ ሆኖ እስከ መጨረሻው አልዘለቀም። ልክ እንደ ካህኑ ዘካርያስና ኤልሳቤት የልጅ ፍሬን ማየት ተስፋ በመነመነበት ትዳር ውስጥ ያልተጠበቀውና ያልታሰበው ተስፋ ባልተጠበቀና ባልታሰበ ቸጊዜ ከተፍ አለ። «መካን» ተብለው የተቆጠሩትና እርሳቸውም ይህንኑ አምነው የተቀበሉት ወ/ሮ በላይነሽ ተ/ወልድ በሆዳቸው ፅንስ ቋጠሩ። እርግዝናቸው እውን ሆኖ የቤቱን ተስፋ አንሰራራው። በዘጠነኛ ወራቸው የካቲት 8/ 1974ዓ.ም ለእኝህ እናቱ የመጀመሪያም የመጨረሻም የሆነው ልጃቸው ካሣ አያሌውን ተገላገሉ። \n \nጥያቄ: የአቶ ካሣ ወላጆች ማን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አባቱ አቶ አያሌው ካሣ እና እናቱ ወ/ሮ በላይነሽ ተ/ወልድ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበ ፰፻ (800) ዓመተ-ዓለም አካባቢ ደአማት የሚባል መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያና ኤርትራ ተቋቋመ። በሰሜን ኢትዮጵያ የምትገኘው የሀ የደአማት ዋና ከተማ ነበረች። በየመን የሚኖሩት ሳባውያን በደአማት ላይ ተፅዕኖ እንደነበራቸው የሚታመን ሲሆን ይህ ተፅዕኖ ምን ያህል እንደሆነ ግን በእርግጥ አይታወቅም። ወደ ፬፻ (400) ዓመተ-ዓለም አካባቢ የደአማት መንግስት ከስልጣን ሲወድቅ በትናንሽ መንግስቶች ተተካ። ከነዚህ ትናንሽ መንግስቶች አንዱ አክሱም ሲሆን አካባቢውን እንደገና በአንድነት ለመግዛት ችሎ ነበር። የአክሱማውያን ስፈን በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥታዊ ማኅበረሰብ ነበር። በፋርስ ፣ ሮማ እና ቻይና ይገኙ ከነበሩ ታላላቅ መንግሥታት በወደረኛነት የሚቆጠር ትልቅ ኅይል ነበር። በ4ኛው ምእተ-ዓመት አክሱም ወደ ክርስትና ተለወጠ። በ፮ኛው ምእት ዓመት የአክሱማውያን ግዛታዊ ቁጥጥር የዛሬዋን የመን ግዛት ይጨምር ነበር። ግን በ፮ኛው እና በ ፰ኛው አምኣት የአክሱም ሥልጣኔ በእስልምና መነሣት እና መስፋፋት ተዳክሞ ለውድቀት በቃ ። ተከታዩ የዛጔ ሥርወ-መንግሥት ልክ በድንገት እንደተነሳ በድንገት ሲያበቃ ፣ ይኵኖ አምላክ ሥልጣን በ ፲፪፻፷፪ (1262) ዓ. ም. ጨበጡ ፤ እንዲያም ሲል የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥትን መለሱ። ከዚያም ለብዙ ዘመናት የሰለሞናዊው መንግስት ከጠለ። \n \nጥያቄ: ደአማት የተባለው መንግስት የተቋቋመው በየት አካባቢ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በሰሜን ኢትዮጵያና ኤርትራ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየዲጂታል ኢኮኖሚውን የሚያጠናክር ሬድፎክስ የተሰኘ የመረጃ ቋት ማዕከል ይፋ ሆነ፡፡ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እዮብ ተካልኝ መረጃ አዲሱ ነዳጅ መሆኑን ገልጸው፣ የዲጂታል መሰረተ ልማቱ መጠናከር በጤና፣ በትምህርት፣ በግብርና እና በሌሎች መስኮች ላይ አስተዋጽኦን ያሳርፋል ብለዋል፡፡ ሬድፎክስ ለረጅም ዓመታት በቴሌኮም ዘርፍና በመረጃ ቴክኖሎጂ ልምድ ባካበቱ የኢትዮጵያ ዳያስፖራዎች የተቋቋመ መሆኑም ተገልጿል፡፡ ሚኒስትር ዲኤታው ዳያስፖራዎቸ በዘርፉ ላይ በመሰማራታቸው ያላቸውን አድናቆት መግለጻቸውን ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ \n \nጥያቄ: በኢትዮጰጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚውን እንዲያጠናክር የተመሰረተው ሬድፎክስ ምን ዓይነት ማዕከል ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የመረጃ ቋት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአብዱልራዛቅ እ.ኤ.አ. በ1994 ላይ ያሳተሙት ‹ፓራዳይዝ› የተሰኘው ልብ ወለድ ታንዛኒያ ውስጥ በ20ኛው ምዕት ዓመት የልጅ አስተዳደግ ምን እንደሚመስል ፍንትው አድርገው ያሳዩበት ነው። በዚህ ልብ ወለድም ዓለም አቀፉን የ‹ቡከር› ሽልማት ለማግኘት መቻላቸውን ቢቢሲ ዘግቦታል፡፡ እንደ የኖቤል ኮሚቴ የሥነ ጽሑፍ ክፍል አገላለጽም፣ ‹‹[የእሳቸው] ገጸ ባህርያት ሁሌም ቢሆን በባህልና አኅጉራት መካከል የሚሽከረከሩ፣ በአሁን ሕይወትና በመጪው ሕይወት መካከል የሚመላለሱ ናቸው። በቀላሉ ሊያልፉት የማይችሉት ከባድ እውነታ ውስጥ ናቸው፡፡›› እ.ኤ.አ. በ1948 በዛንዚባር የተወለዱት አብዱልራዛቅ፣ እ.ኤ.አ. በ1960ዎቹ መገባደጃ አገረ እንግሊዝ የገቡት ስደተኛ ሆነው ነው። በቅርቡ ጡረታ እስከወጡበት ዕለት ድረስ በካንተርበሪው የኬንት ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዝኛና የድኅረ ቅኝ ግዛት ሥነ ጽሑፎች ፕሮፌሰር ነበሩ። ሽልማቱ፣ ደራሲው ያለፉበትን የስደተኞች ቀውስንና ቅኝ አገዛዝን በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ውይይት እንዲደረግባቸው ያስችላል ብለዋል፡፡ ‹‹እነዚህ በየዕለቱ ከእኛ ዘንድ ያሉ ነገሮች ናቸው። ሰዎች እየሞቱ ነው፣ ሰዎች በዓለም ዙርያ አሁንም እየተጎዱ ነው፡፡ በእነዚህን ጉዳዮች ላይ በፍፁም ቀናነትና አስተውሎት መንገድ መነጋገር መላ መምታት አለብን፤›› ብለዋል የኖቤል ተሸላሚው አብዱልራዛቅ። ዓምና በሥነ ጽሑፍ ያሸነፉት አሜሪካዊው ገጣሚ ሊዊስ ግሉክ መሆናቸው ይታወሳል። የስዊድኑ አካዴሚ በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት ከሸለማቸው ታላላቅ ደራስያን መካከል ከአፍሪካ አኅጉር ስድስት ደራስያን ይገኙበታል፡፡ እነርሱም ዎሌ ሾንካ (ናይጀሪያ)፣ ነጂብ ማኅፉዝ (ግብፅ)፣ ናዲን ጎርዲመር (ደቡብ አፍሪካ)፣ ጄ.ኤም ኮትዚ (ደቡብ አፍሪካ)፣ እና ዶሪስ ሌሲንግ (ዚምባቡዌ -እንግሊዝ) ይገኙበታል፡፡ \n \nጥያቄ: ባለፈው ዓመት የኖቤል የሥነ ጽሑፍ ተሸላሚ ማናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሊዊስ ግሉክ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nደቡብ አፍሪካ በደቡብ አፍሪቃ ሕገ መንግሥት መሠረት 11 ልሳናት በእኩልነት ይፋዊ ኹኔታ አላቸው። ከነዚህ መካከል ኳዙሉ ከሁሉ ብዙዎች ተናጋሪዎቹ በአገሩ ውስጥ አሉት፤ ቆሣ በቁጥር ብዛት 2ኛው ነው። ከነዚያ በኋላ በተናጋሪዎች ብዛት አፍሪካንስ 3ኛው፣ ስሜን ሶጦ 4ኛው፣ እንግሊዝኛም 5ኛው፣ ጿና 6ኛው፣ ደቡብ ሶጦ 7ኛው፣ ጾንጋ 8ኛው፣ ሷቲ 9ኛው፣ ቬንዳ 10ኛው፣ ንዴቤሌም 11ኛው ነው። ብዙ ሰዎች እስከ 6 ቋንቋዎች ድረስ የመናገር ዕውቀት አላቸው፤ ከነጭም ዜጋዎች አብዛኛው አፍሪካንስና እንግሊዝኛ ሁለቱን ይችላሉ። ትልቁ ከተማ ጆሃንስበርግ ሲሆን ዋና ከተሞቹ ሦስት ናቸው፤ እነርሱም ኬፕ ታውን፣ ብሉምፎንቴንና ፕሪቶሪያ ናቸው። ይህ ፓርላሜንቱ በኬፕ ታውን፣ ላዕላይ ችሎቱ በብሉምፎንቴን፣ ቤተ መንግሥቱ በፕሪቶሪያ ስለ ሆነ ነው። ስመ ጥሩ የሆኑት የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች ሂው ማሴኬላ እና ሌዲስሚስ ብላክ ማምባዞ ናቸው። የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች አሁን የራሳቸውን ዘመናዊ ሙዚቃ ዓይነት «ኳይቶ» አላቸው። የአገሩ አበሳሰል የተለያየ ነው። ብዙ ኗሪዎች የተቀመመ በሬ ቋሊማ ጥብስ (ቡረቮርስ)፣ የበቆሎ አጥሚት (ኡምጝቁሾ)፣ የተቀመመ ዶሮ፣ እና የተቀመመ ወጥ (ካሪ) ይወድዳሉ። የተወደዱ እስፖርቶች እግር ኳስ፣ ክሪኬት እና ራግቢ ናቸው። \n \nጥያቄ: በደቡብ አፍሪካ የአፍሪካንስ ቋንቋ በተናጋሪ ብዛት ስንተኛው ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 3ኛው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኢትዮጵያ በዓለም ዉስጥ ክሚገኙ ጥንታዊ አገሮች ኢትዮጵያ ቀዳሚ በመሆን ከሁሉም የበለጠ ረጅም እድሜ አስቆጥራለች፡፡ በግእዝ/ዓማርኛ እና በመጽሀፍ ቅዱስ ከተመዘገቡት ተጨባጭ መረጃዎች በተጨማሪ አምስት ሚሊዮን አመት የሚሆነውና በጣም ረጅም እድሜ ያስቆጠረው የሰው ቅሪት የተገኘው በኢትዮጵያ አዋሽ ሸለቆ አካባቢ ሲሆን ይህም፣ 3.2 ሚሊዮን አመት የሆነውን እዛው አካባቢ የተገኘውን የሉሲን (ድንቅነሽን) አጽም በእድሜ ይበልጣል፡፡ ግብጽን ሲገዛ የነበረው ሄሮደስ የሚባለው ንጉስ ከክርስቶስ ልደት በፊት በአምስተኛው ክፍለ ዘመን የነበረው ታሪክ ፀሀፊ የጥንቷን ኢትዮጵያ በጽሁፎቹ ላይ ይገልፃታል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ላይም ብዙ ግዜ የምትወሳ ስትሖን በተለይም ብሉይ ኪዳን ላይም የንግስት ሳባ (መከዳ) ኢየሩሳሌም መሄድና ለንጉስ ሰለሞን ከባድ የሆኑ ጥያቄዎች ማንሳቷ ተጽፏል፡፡ ኢትዮጵያ ዛሬ ያላትን መልክ እንድትይዝ ያደረጋት ንጉስ ሚኒሊክ የንግስት ሳባና የንጉስ ሰለሞን ዘር ናቸው፡፡ የንግስት ሳባ ቤተ መንግስት ፍርስራሽ ሰሜን ኢትዮጵያ ውስጥ በአክሱም አካባቢ ይገኛል፡፡ ክርስትናን ኢትዮጵያዉያን ከመቀበላቸዉ በፊት (ኣስቅድመዉ) የኦሪትን ህግ ሰለሚያዉቁ ኣመተ ዓለምን ወደታች እየቆጠሩ የጌታን መወለድ ይጠብቁ ሰለነበረ ክርስትናን ለመቀበል ኣላስቸገራቸዉም፡፡ ነገር ግን በሰባተኛው ክፍለ ዘመን በእስልምና መስፋፋት ምክንያት ኢትዮጵያ ከአውሮፖውያኑ ክርስትያን ርቃ ቆይታለች፡፡ \n \nጥያቄ: የንግሥት ሳባ ቤተ መንግስት የት ይገኛል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሰሜን ኢትዮጵያ ውስጥ በአክሱም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሊቢያ ኦይል ከኢትዮጵያ የተሰናበተውን ሼል ኢትዮጵያ ሊሚትድ በመግዛት የኢትዮጵያን የነዳጅ ገበያ የተቀላቀለው በ2000 ዓ.ም. ነበር፡፡ ኩባንያው ኢትዮጵያ ውስጥ 143 የነዳጅ ማደያዎች ሲኖሩት፣ 24 በመቶ የገበያ ድርሻ አለው፡፡ ኩባንያው በየዓመቱ ዘጠኝ ማደያዎች በመክፈት እ.ኤ.አ. በ2020 የነዳጅ ማደያዎቹን ቁጥር 185 ለማድረስ፣ የገበያ ድርሻውን ወደ 30 በመቶ ለማሳደግ አቅዷል፡፡ በአሁኑ ወቅት የኩባንያው ዓመታዊ ሽያጭ 13 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተገልጿል፡፡ ሊቢያ ኦይል 50 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ የአቪዬሽን ነዳጅ ዲፖ ማስፋፊያና በአዲስ አበባ ጎተራ አካባቢ በሚገኘው የነዳጅ ዲፖ የኤታኖል ማደባለቂያ ገንብቷል፡፡ ኩባንያው እስከዛሬ እንደ አዲስ የገነባቸው ስምንት የነዳጅ ኩባንያዎችን ብቻ ነው፡፡ ይህ ሊሆን የቻለው ለግንባታ የሚሆን ቦታ የማግኘት ችግር በመኖሩ መሆኑን የሚናገሩት አቶ ዘካሪያስ፣ ከሼል ኩባንያ ግዢ ጋር የተፈጠረው የታክስ ክርክር የኩባንያውን ዕድገት እንደጎተተው ያስረዳሉ፡፡ የታክስ ክርክሩ እልባት ያገኘ በመሆኑ ኩባንያው በኢትዮጵያ ያለውን ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት ቆርጦ መነሳቱን አስታውቋል፡፡ ሊቢያ ኦይል ባለፈው ሐሙስ ነሐሴ 28 ቀን 2007 ዓ.ም. በሸራተን አዲስ አዳዲስ የሞተር ዘይትና ቅባቶችን አስተዋውቋል፡፡ የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ የሊቢያ ኦይል የነዳጅ ማደያ ባለቤቶች፣ የሊቢያ ኦይል ምርቶች አከፋፋዮችና የትራንስፖርት ኩባንያዎች የሊቢያ ኦይል ዋና ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ሙስባሕ ኤልቤሽቲ ሽልማቶች አበርክተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ሊቢያ ኦይል በኢትዮጵያ የነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ሆኖ ሥራ የጀመረው ከመቼ ጀምሮ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ2000 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም ለአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነርነት በእጩነት ቀረቡ። በሚኒስትር ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ኢትዮጵያን በመወከል ለአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነርነት በእጩነት መቅረባቸው ነው የተነገረው። የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር በመሆን ያገለገሉት ፕሮፌሰር ሂሩት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቋንቋና የቋንቋ ጥናት ክፍል ለረጅም ዓመታት በመምህርነት አገልግለዋል። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም የጠቅላይ ሚንሰትሩ የምን አማካሪ ሆነው ሰርተዋል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የማህበራዊ ጉዳዮች ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሊኦፖልድ ሴዳር ሴንጎር ሊኦፖልድ ሴዳር ሴንጎር (1906-2001) የሴኔጋል የመጀመሪያው መራሄ መንግስት በመሆን ከ1960 እስከ 1980 ድረስ ያገለገሉ፣ ኔግሪቲዩድ የሚባለው ፍልስፍና ዋነኛ አቀንቃኝ የነበሩ እና በግጥሞቹም አድናቆትን ያተረፉ አፍሪካዊ የሥነጽሁፍ ሰው ናቸው። ሴንጎር የሴኔጋል ዋና ከተማ ከሆነችው ዳካር 70 ማይልስ ያህል በምትርቅ እና ጆአል ላ ፖርቱጊዝ (ጆአል ፖርቱጊዛዊቱዋ) በምትባል ትንሽ የአሳ አጥማጆች መንደር በ1906 ተወለዱ። አባታችው ነጋዴ ከሆኑ ሴሬር ከሚባሉ ጎሳ የተወለዱ ሲሆን እናታቸው ግን ፔውል ከተባለ የሙስሊም ዘላን አርብቶአደሮች ጎሳ የተወለዱ ሴት ናቸው። ሴንጎር ኋላ ላይ ሲጽፉ «ተወልጄ ያደኩት በአፍሪካ መኸል፣ የጎሳዎች እና ዘሮች መገናኛ ላይ ነው» ብለዋል። በ12 ዓመታችው የካቶሊክ ሚሲዮን ትምህርት ቤት ተመዝግበው ትምህርታቸውን የጀመሩ ሲሆን ከዛ በኋላ በሌሎች ትምህርት ቤቶችም በመማር በ1928 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል። ከዚያም ፓሪስ ከሚገኘው ሊሴ ፓሪ ለግራንድ ከተባለው ትምህርት ቤት በ1931 ተመርቀዋል። \n \nጥያቄ: የሴኔጋል ዋና ከተማ ምን ትባላላች?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ዳካር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቻይና በማርስ ላይ የምታካሂደውን የመጀመሪያ ሳይንሳዊ ጥናት የፊታችን ሃምሌ ወር እንደምትጀምር ይፋ አድርጋለች። ጥናቱን የምታከናውነው ሳተላይት ሎንግ ማርች 5-ዋይ 4 በተሰኘ ሮኬት ወደ ህዋ እንደምትላክም የቻይና የጠፈር ምርምር ተቋም አስታውቋል። ሮኬቱ ተልዕኮውን በተሳካ ሁኔታ ማጠናቀቅ የሚያሰችል አቅም እንዳለው በሙከራ ተረጋግጧልም ነው የተባለው። ከሃይድሮጅን እና ኦክስጅን ጋዞች የተሰራ ሞተር ያለው ሮኬት በተያዘው ዓመት በርካታ ሳተላይቶችን ወደ ህዋ ያደርሳል ተብሎ ታምኖበታል። ወደ ህዋ የምትላከው ሳተላይትም በማርስ ፕላኔት ዙሪያ በርካታ አዳዲስ ግኝቶች እና መረጃዎችን ለምርምር ተቋሙ ታደርሳለች ተብሎ ይጠበቃል። \n \nጥያቄ: ቻይና የምትልከው ሳተላይት ምን በሚባል ሮኬት ወደ ህዋ ይላካል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሎንግ ማርች 5-ዋይ 4 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nመስከረም 24 ቀን 2012 የደቡብ ክልልን ሁለንተናዊ መረጃ የያዘ አትላስ እና የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ሥርአት ተመርቀው ለአገልግለት ተዘጋጁ፡፡ በደቡብ ክልል ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ አማካይነት በአዲስ መልክ ተዘጋጅቶ ትናንት የተመረቀው አትላስ የክልሉን ኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ ፣ ዲሞግራፊያዊና መልክአ-ምድራዊ መረጃዎችን አካቶ መያዙ ተገልጿል። የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ስርአቱም (የመረጃ ቋቱ) ላለፉት 10 ተከታታይ ዓመታት የነበሩ ሁለንተናዊ መረጃዎችን በድህረ-ገጽ አማካይነት ለማሰራጨት የሚያስችል ነው፡፡ በምርቃ ሥነ-ሥርዐቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የደቡብ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ሄለን ደበበ የስታቲስቲክስና መልክዐ-ምድር መረጃ ሥርዐት አስተዳደር የክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ከያዛቸው የትኩረት አቅጣጫዎች አንዱ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የደቡብ ክልል ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ታምራት ዲላ ከዚህ በፊት የነበረው የክልሉን አኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ ፣ ዲሞግራፊያዊና መልክዐ ምድራዊ መረጃዎችን የያዘ አትላስ ላለፉት 15 ዓመታት ማገልግሉንና በአሁኑ ወቅት ያለውን ሁለንተናዊ የክልሉን እድገት ያካተተ እንዳልሆነ ተናግረዋል። ዛሬ ይፋ የተደረገው አትላስ አስከ 2009 ዓ.ም ያለውን ክልላዊ መረጃ የያዘ እንደሆነ ገልጸው አጠቃላይ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፍ የተመዘገቡትን ውጤቶች፣ የመሰረተልማት ስርጭቶችን፣ ዴሞግራፊያዊ፣ መልክዐ-ምድራዊና ሌሎች መረጃዎችን ማካተቱን ተናግረዋል ፡፡ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ በበኩላቸው ከዚህ በፊት ለዕቅድ መነሻ የሚሆኑ መረጃዎች ታች ካሉ መዋቅሮች ብቻ እንደሚሰበሰቡ ገልፀው ይህም ተአማኒ መረጃ ለማግኘት የሚስቸግር አሰራር እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ ይፋ የተደረጉት አትላስና የመረጃ ቋት ይህንን የመረጃ ክፍተት የሚሸፍኑና በቀላሉም ተደራሽ የሚሆኑ በመሆናቸው በፍትሀዊነት ላይ የተመሰረቱ ዕቅዶችን ለማዘጋጀት ትልቅ እገዛ ያደርጋሉ ብለዋል ፡፡ በምረቃ ሥነ-ሥርዐቱ ላይ የደቡብ ክልል፣ የዞኖችና የልዩ ወረዳዎች አመራሮች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲ አስተዳደር አካላት ተገኝተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የመረጃ አያያዝ ምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ የተገኙ አካላት እነማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የደቡብ ክልል፣ የዞኖችና የልዩ ወረዳዎች አመራሮች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአዶልፍ ሂትለር አዶልፍ ሂትለር (ጀርመንኛ Adolf Hitler አዶልፍ ሂትለ) እ.አ.አ. ከ1933 ጀምሮ የጀርመን ቻንስለር እንዲሁም ከ1934 ጀምሮ ደግሞ የጀርመን መሪም (Führer) ጭምር የነበረ ሰው ነው። ሂትለር በሚያዝያ 13 ቀን 1881 ዓ.ም. (20 አፕሪይል 1889 እ.ኤ.አ.) በዛሬይቷ ኦስትሪያ ተወለደ። በሚያዝያ 22 ቀን 1937 ዓ.ም. (30 አፕሪይል 1945 እ.ኤ.አ.) በርሊን ውስጥ ከአንድ ቀን በፊት ካገባት ሚስቱ ኤቫ ብራውን ጋር የራሱን ህይወት አጠፋ። በ1925 ዓ.ም. መጀመርያ የሂትለር ናዚ ወገን ከጓደኞቹ ወገን ጋር በራይክስታግ ምክር ቤት ትብብር መንግሥት ለመሥራት በቂ መንበሮች አልነበራቸውም። ተቃራኒዎቻቸው የኰሙኒስት ወገን 17% መንበሮች ስለ ነበራቸው የሂትለር ወገኖች የድምጽ ብዛት ሊያገኙ አልተቻላቸውም ነበር። በዚያው ዓመት ግን ከምርጫው ትንሽ በፊት የራይክስታግ ሕንጻ በእሳት ተቃጠለ። ይህ የኰሙኒስቶች ሥራ ነው ብለው የሂትለር ወገን ኰሙኒስት ፓርቲ ቶሎ እንዲከለከል አደረጉ። ስለዚህ ከምርጫው በኋላ የኰሙኒስትን መንበሮች ስለ አጡ የሂትለርም ወገኖች አሁን ከ50% መንበሮች በላይ ስላገኙ፣ የትብብር መንግሥት ሠሩና ወዲያው በድንጋጌ አቶ ሂትለር ባለሙሉ ሥልጣን አደረጉት። ሂትለር የጻፈው የርዮተ አለሙ ጽሑፍ «የኔ ትግል» (Mein Kampf) ሟርት ብቻ ነው። ለመጥቀስ ያህል፦ «ትኩረቴ ወደ አይሁዶች ስለ ተሳበ፣ ቪየናን ከበፊት በሌላ ብርሃን ለማየት ጀመርኩ። በሄድኩበት ሁሉ አይሁዶችን አየሁዋቸው፤ በብዛትም እያየኋቸው፣ ከሌሎች ሰዎች ፈጽሞ እንድለያቸው ጀመርኩ።»... «የግዛቱ (ኦስትሪያ-ሀንጋሪ) ዋና ከተማ የከሠተውን የዘሮች ውሑድ ጠላሁት፤ የዚህን ሁሉ የቼኮች፣ ፖሎች፣ ሀንጋርዮች፣ ሩጤኖች፣ ሰርቦች፣ ክሮዋቶች ወዘተ. የዘሮች ድብልቀት፤ በሁላቸውም መካከል፣ እንደ ሰው ልጅ መከፋፈል ሻገቶ፣ አይሁዶችና ተጨማሪ አይሁዶች።» በነበረው ዘረኛ አስተዳደሩ 6 ሚሊዮን የአውሮፓ አይሁዶችን እና 5 ሚሊዮን ሌሎች የተለያዩ ሀገራት ህዝቦችን (በተለይም ስላቮችን) በገፍ (በሆሎኮስት) አስጨርሷል። በሂትለር ሥር የናዚዎች ፍልስፍና በሂንዱኢዝም እንደሚገኘው በዘር የተከፋፈለ ካስት ሲስተም መመሥረት አይነተኛ ነበር። «አርያኖች» የተባሉት ዘሮች በተለይም የጀርመናውያን ብሔሮች ከሁሉ ላዕላይነት እንዲገኙ አሠቡ። ይህ ዝብረት የተነሣ በርግ ቬዳ ዘንድ በ1500 ዓክልበ. ያህል ወደ ሕንድ የወረሩት ነገዶች «አርያን» ስለ ተባሉ ነው፤ በጥንትም «አሪያና» የአፍጋኒስታን አካባቢ ስም የዘመናዊው ኢራንም ሞክሼ ነበር። በናዚዎቹ እንደ ተዛበው ግን ታሪካዊ ባይሆንም የ«አርያኖች» ትርጓሜ ጀርመናውያን ብቻ ነበሩ፤ ስላቮች (በተለይ የሩስያና የፖሎኝ ሕዝቦች) ግን አርያኖች ሳይሆኑ እንደ ዝቅተኞች ተቆጠሩ። የሂትለር እብደት እየተራመደ በ1926 ዓም የሀንጋሪ ሕዝብ ደግሞ «አርያኖች» ተደረጉ፣ በ1928 ዓም የጃፓን ሕዝብ እንኳን በይፋ «አርያኖች» ተደረጉ፤ በ1934 ዓም የፊንላንድ ሕዝብ ወደ «አርያኖች» በሂትለር ዐዋጅ ተጨመሩ። በሙሶሊኒ ሥር የፋሺስት ጣልያኖች እኛም አርያኖች ነን ቢሉም ጣልያኖች አርያን መሆናቸው በናዚዎች ዘንድ መቸም አልተቀበለም ነበር። \n \nጥያቄ: የአዶልፍ ሂትለር የትውልድ ቦታ የት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ኦስትሪያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአዲስ አበባ አዲስ አበባ ተብላ የተሠየመችው እቴጌ ጣይቱ ኅዳር ፲፬ ቀን ፲፰፻፸፱ (1879) ዓ.ም. ፍልውሃ ፊን-ፊን ወደሚልበት መስክ ወርደው ሳሉ ከዚህ በፊት አይተዋት የማያውቋት አንዲት ልዩ አበባ አይተ ስለማረከቻቸው ቦታውን ‹‹አዲስ አበባ!›› አሉ ይባላል። አዲስ አበባ (ኣዲስ ኣበባ) ኢትዮጵያ ዋና ከተማ ስትሆን በተጨማሪ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ እንዲሁም የብዙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቅርንጫፎችና ሌሎችም የዓለም የዲፕሎማቲክ (የሰላማዊ ግንኙነት) ልዑካን መሰብሰቢያ ከተማ ናት። ራስ-ገዝ አስተዳደር ስላላት የከተማና የክልል ማዕረግ ይዛ ትገኛለች። አብዛኞቹን የሀገሩ ቋንቋዎች የሚናገሩ ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞች የሚኖሩባት ከተማ ናት። ከባሕር ጠለል በ2500 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኘው ከተማ በግምት 2,757,729 በላይ ሕዝብ የሚኖርባት በመሆኗ የሀገሪቱ አንደኛ ትልቅ ከተማ ናት። ከተማዋ እቴጌ ጣይቱ በመረጡት ቦታ ማለትም በፍል ውሐ አካባቢ ላይ በባላቸው በዳግማዊ ምኒልክ በ፲፰፻፸፰ (1878) ዓ.ም. ተቆረቆረች። የሕዝቧ ብዛት በያመቱ 8% (ስምንት በመቶ) እየጨመረ አሁን አምስት ሚሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከእንጦጦ ጋራ ግርጌ ያለችው መዲና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መገኛ ሆናለች። ይህም በመስራቹ የቀድሞው ንጉሠ-ነገሥት ስም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ይባል ነበር። \n \nጥያቄ: አዲስ አበባ ከተማ ከባህር ጠለል በምን ያህል ከፍታ ትገኛለች?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ2500 ሜትር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዓረብኛ ዓረብኛ የሴማዊ ቋንቋዎች ቤተሠብ አባል ሆኖ የዕብራይስጥ የአረማያ እንዲሁም የአማርኛ ቅርብ ዘመድ ነው። ፪፻፶ (250) ሚሊዮን የሚያሕሉ ሰዎች እንደ እናት ቋንቋ ይናገሩታል። ከዚህም በላይ በጣም ብዙ ሰዎች እንደ ፪ኛ ቋንቋ ተምረውታል። የሚጻፈው በዓረብኛ ፊደል ነው። በዓረብ አለም ውስጥ አያሌ ቀበሌኞች ይገኛሉ። ቋንቋው በእስልምና ታላቅ ሚና አጫውቷል። እስላሞች አላህ ለሙሐማድ ቁርዓንን ሲገልጽ በዓረብኛ እንደ ሆነ ስለሚያምኑ እንደ ቅዱስ ቋንቋ ይቆጥሩታል። አብዛኛው ዓረብኛ ተናጋሪዎች ሙስሊሞች ናቸው። ዛሬ በምዕራብ ዓለም ደግሞ ብዙ ሰዎች አረብኛ እያጠኑ ነው። በታሪክ ከፍተኛ ሚና በማጫወቱ መጠን ፤ ብዙ የዓረብኛ ቃላት ወደ ሌሎች ቋንቋዎች ገብተዋል። \n \nጥያቄ: ለዓረብኛ ቋንቋ የቅርብ ዘመድ ተብለው ከሚጠቀሱት ቋንቋዎች መካከል መን ይገኛል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የአማርኛ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየላሊበላ ግሎባል ኔትወርክስ ድርጅት ተባባሪ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ (ዶ/ር) ዓለም አቀፉን ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገ አዲስ የስራ ፈጣራ ውድድር አሸነፉ። ኢትዮጵያዊቷ በየዓመቱ የሚካሄደውን ዓለም አቀፉን ፒአይቲሲኤች (PITCH) አዲስ የስራ ፈጠራ ውድድር በትላንትናው እለት ማሸነፉቸው ይፋ ሆኗል። ውድድሩ 2500 ስራ ፈጣሪዎች የተሳተፉ ሲሆን ወደ መጨረሻው ዙር ያለፉት ደግሞ 700 የሚሆኑ አዲስ ፈጣሪዎች ነበሩ። ከዚህ ውስጥ ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ(ዶ/ር) በጤና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያቀረቡት አዲስ የስራ ፈጠራ በቅርበት ተፎካካሪ ከነበሩት የአሜሪካና የእንግሊዝ የስራ ፈጣሪዎችን በመብለጥ የዓመቱ ውድድር አሸናፊ ሆኗል። ውለታ ለማ (ዶ/ር) ለውድድሩ ያቀረቡት የስራ ፈጠራ አባይ ሲ ኤች አር (ABAY CHR) የተባለ በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ህክምና ዘርፍ ያለውን ሰፊ የወረቀት ስራ ወደ ዲጂታል በመቀየር ስራን የሚያቀልና የሚያቀላጥፍ እንዲሁም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወጪን የሚያስቀር የሥራ ፈጠራ ነው ተብሏል። \n \nጥያቄ: ውለታ ለማ (ዶ/ር) ያሸነፉበት አባይ ሲ ኤች አር (ABAY CHR) የተባለ የሥራ ፈጠራቸው በህክምናው ዘርፍ ለኢትዮጵያ ምን ፋይዳ አለው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የወረቀት ስራ ወደ ዲጂታል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኤንመርካር ኤንመርካር በሱመር (ሳንጋር) ነገስታት ዝርዝር ዘንድ የኡሩክ (ኦሬክ) ከተማ መስራች ነበረ። በዚያ ዝርዝር ጽህፈት 420 (ወይም በሌላ ቅጂ 900) ዓመታት እንደ ነገሰ ይላል። ደግሞ አባቱ የኡቱ ልጅ መስኪያጝካሸር ወደ ባሕር ገብቶ ኤንመርካር መንግስቱን ከኤአና ከተማ እንዳመጣ ይጨምራል። የኤንመርካር ስም በሌላ የሱመር ጽሑፍ ደግሞ ተገኝቷል። «ኤንመርካርና የአራታ ንጉስ» በተባለው ተረት እሱ የኡቱ ልጅ ይባላል። (ኡቱ በሱመር እምነት የጸሓይ አምላክ ነበር።) ይህ ተረት የሰው ልጅ ልሳናት መደባለቁን ይናገራል። ኡሩክን ከመመስረቱ በላይ ታላቅ መስጊድ በኤሪዱም እንዳሰራ ይተረታል። ለመሆኑም፣ አራታ እንዲገዛለት የሚለው መልእክት በአፍ መናገር ስለሚከብድ፣ ኤንመርካር ጽሕፈት በሸክላ ጽላት ላይ መጻፍ እንደ ፈጠረ ይላል። በተጨማሪ በዚሁ ጽሑፍ ኤንመርካር የዙሪያው አገሮች ልዩ ልዩ ልሳናት እንደገና አንድ እንዲሆኑ ይጸልያል። እነዚህ አገራት ሹቡር፣ ሐማዚ፣ ሱመር፣ ኡሪ-ኪ (የአካድ ዙርያ) እና የማርቱ አገር ናቸው። ከዚህ በላይ የኤንመርካርን መንግሥት የሚገልጹ ሦስት ተጨማሪ ጽሑፎች አሉ። «ኤንመርካርና ኤንሱሕጊርዓና» የሚባል ተረት የኤንመርካርና የአራታ መቀያየም ሲገልጽ፣ ሐማዚ ተሸንፎ እንደ ነበር ይጠቅሳል። በ«ሉጋልባንዳ በተራራ ዋሻ»፣ ኤንመርካር በአራታ ላይ ዘመቻ ሲመራ ይታያል። አራተኛውና መጨረሻውም ጽላት፣ «ሉጋልባንዳና የአንዙድ ወፍ» ኤንመርካርና ሠራዊቱ በአራታ ዙሪያ ለ1 አመት እንደ ከበቡት ይላል። ለመሆኑ ኤንመርካር 50 አመት ከነገሰ በኋላ፣ የማርቱ ሕዝብ (አሞራውያን) በሱመርና በአካድ ሁሉ ተነሥተው ኡሩክን ለመጠብቅ ግድግዳ በበረሃ መስራት እንደ ነበረበት ይጠቅሳል። በነዚህ መጨረሻ 2 ጽላቶች፣ ከኤንመርካር ጦር አለቆች አንድ የሚሆን ሉጋልባንዳ የሚባል ሰው ይተረታል። በሱመር ነገሥታት ዝርዝር ዘንድ፣ ይህ ሉጋልባንዳ «እረኛው» ኤንመርካርን ወደ ኡሩክ ዙፋን ተከተለው። ይህ ሉጋልባንዳ ደግሞ በጊልጋመሽ ትውፊት በተባለው ግጥም ዘንድ የኋለኛው ኡሩክ ንጉሥ የጊልጋመሽ አባት ነበረ። ዴቪድ ሮኅል የሚባል አንድ የታሪክ ሊቅ የኤንመርካርና የናምሩድ ተመሳሳይነት አመልክቷል። «-ካር» የሚለው ክፍለ-ቃል በሱመር ቋንቋ ማለት «አዳኝ» ነው። ኡሩክ ከተማ የተመሠረተ በኤንመር-ካር ነበር ሲባል፣ ደግሞ ናምሩድ፣ አዳኝ፣ በኦሪት ዘፍጥረት ምእራፍ 10 ዘንድ ኦሬክን ሰራ። በሌላ ትውፊቶች ዘንድ ይህ ናምሩድ የባቢሎን ግንብ መሪ የሆነ ነበር። በተጨማሪም አቶ ሮህል የኤሪዱ መጀመርያ ስም «ባቤል» እንደ ነበር ያምናል፤ እዚያም የሚገኘው የግንብ ፍረስራሽ የባቢሎን ግንብ ፍርስራሽ መሆኑን ገመተ። «ባቢሎን» ማለት የኤሪዱ መጠሪያ እንደ ነበር የሚል ማስረጃ በሌሎችም ጥናቶች አለ። ሮማዊው ጸሐፊ ክላውዲዩስ አይሊያኑስ በጻፈ አንድ ትውፊት ዘንድ (200 ዓ.ም. ግድም)፣ የባቢሎን ንጉስ «ኤወኮሮስ» የተከታዩን «ጊልጋሞስ» አያት ይባላል። ይህ «ጊልጋሞስ» ማለት የኡሩክ ንጉስ ጊልጋመሽ መሆኑን የአሁኑ ሊቃውንት ስለ ገነዘቡ፣ እንዲሁም «ኤወኮሮስ» ማለት ኤንመርካር ሳይሆን አይቀርም የሚል አስተሳሰብ ያቀርባሉ። ከዚህ በላይ የከላውዴዎን ታሪክ ጸሐፊ ቤሮሶስ በጻፈው ዝርዝር መሰረት፣ ከማየ አይህ ቀጥሎ የከላውዴዎንና የአሦር መጀመርያው ንጉስ «ኤወኮዮስ» ይባላል፤ ስለዚህ የዚሁ «ኤወኮዮስ»ና የናምሩድ መታወቂያ አንድ ናቸው የሚለው አሳብ ለረጅም ዘመን የቆየ ነው። \n \nጥያቄ: በሱመር እምነት መሰረት ኡቱ ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የጸሓይ አምላክ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበ ፰፻ (800) ዓመተ-ዓለም አካባቢ ደአማት የሚባል መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያና ኤርትራ ተቋቋመ። በሰሜን ኢትዮጵያ የምትገኘው የሀ የደአማት ዋና ከተማ ነበረች። በየመን የሚኖሩት ሳባውያን በደአማት ላይ ተፅዕኖ እንደነበራቸው የሚታመን ሲሆን ይህ ተፅዕኖ ምን ያህል እንደሆነ ግን በእርግጥ አይታወቅም። ወደ ፬፻ (400) ዓመተ-ዓለም አካባቢ የደአማት መንግስት ከስልጣን ሲወድቅ በትናንሽ መንግስቶች ተተካ። ከነዚህ ትናንሽ መንግስቶች አንዱ አክሱም ሲሆን አካባቢውን እንደገና በአንድነት ለመግዛት ችሎ ነበር። የአክሱማውያን ስፈን በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥታዊ ማኅበረሰብ ነበር። በፋርስ ፣ ሮማ እና ቻይና ይገኙ ከነበሩ ታላላቅ መንግሥታት በወደረኛነት የሚቆጠር ትልቅ ኅይል ነበር። በ4ኛው ምእተ-ዓመት አክሱም ወደ ክርስትና ተለወጠ። በ፮ኛው ምእት ዓመት የአክሱማውያን ግዛታዊ ቁጥጥር የዛሬዋን የመን ግዛት ይጨምር ነበር። ግን በ፮ኛው እና በ ፰ኛው አምኣት የአክሱም ሥልጣኔ በእስልምና መነሣት እና መስፋፋት ተዳክሞ ለውድቀት በቃ ። ተከታዩ የዛጔ ሥርወ-መንግሥት ልክ በድንገት እንደተነሳ በድንገት ሲያበቃ ፣ ይኵኖ አምላክ ሥልጣን በ ፲፪፻፷፪ (1262) ዓ. ም. ጨበጡ ፤ እንዲያም ሲል የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥትን መለሱ። ከዚያም ለብዙ ዘመናት የሰለሞናዊው መንግስት ከጠለ። \n \nጥያቄ: የአክሱም መንግስት ወደ ስልጣን የመጣው መቼ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ4ኛው ምእተ-ዓመት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአዲስ አበባ መስከረም 23/2012 የኢትዮጵያ ብሔራዊ አክሬዲቴሽን ጽህፈት ቤት በኢንስፔክሽን አክሬዲቴሽን አይኤስኦ/አይኢሲ 17020 /2012 ዓለም ዓቀፍ እውቅና ማግኘቱን ገለፀ፡፡ ይህ እውቅና በህክምና ላቦራቶሪ አይ ኤስ ኦ (ISO) 15189፡2012 እና የፍተሻ ላቦራቶሪ አይ ኤስ ኦ/አይ ኢ ሲ 170252017 ካገኘው ዓለም አቀፍ እውቅና በተጨማሪ የተገኘ ነው። በመሆኑም በኢንስፔክሽን አክሬዲቴሽን አይ ኤስ ኦ/አይ ኢ ሲ 17020 /2012 ዓለም ዓቀፍ እውቅና ማግኘቱን ፅህፈት ቤቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ አመልክቷል። ያገኘውን ዓለም ዓቀፍ እውቅና በማስጠበቅ በሰርቲፍኬሽንና በካሊብሬሽን ዘርፎች የዓለም ዓቀፍ እውቅና ለማግኘት እየሰራ መሆኑንም ጠቁሟል፡፡ በኢንስፔክሽን ዘርፍ ዓለም ዓቀፍ እውቅና ለማግኘት በአፍሪካ አክሬዲቴሽንና በዓለም አቀፍ የላቦራቶሪ አክሬዲቴሽን ትብብር ከግንቦት 5 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ በተከታታይ ለአምስት ቀናት ግምገማ ተደርጎበት ነበር፡፡ በግምገማው የተገኙ ክፍተቶችን አስተካክሎ ለገምጋሚ ቡድኑ በማቅረቡ በኢንስፔክሽን አይኤስኦ/አይኢሲ 17020 / 2012 ዘርፉ ዓለም ዓቀፍ እውቅና ማግኘት ችሏል፡፡ ዘርፉ ዓለም ዓቀፍ እውቅና ማግኘቱ በተለይ ሃገሪቱ ወደ ውጭ የምትልካቸው ጥራጥሬ፣ የቅባት እህሎችና ሌሎች ምርቶች የኢንስፔክሽን ሥራ እየሰሩ ሰርተፍኬት ለሚሰጡ ተቋማት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለውም መግለጫው ጠቅሷል፡፡     \n \nጥያቄ: በአዲስ አበባ መስከረም 23/2012 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ አክሬዲቴሽን ጽ/ቤት ምን አይነት እውቅና ነው ያገኘው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አይኤስኦ/አይኢሲ 17020 /2012 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበኦስትሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ላይ ከባድ የሳይበር ጥቃት መፈጸሙ ተሰምቷል። የሳይበር ጥቃቱ በሌላ ሀገር አማካኝነት የተቀነባበረ ሳይሆን እንዳልቀረ የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት አስታውቋል። ጥቃቱ የተፈፀመውም አረንጓዴ የተሰኘው የኦስትሪያ ፓርቲ ከወግ አጥባቂ ፓርቲዎች ጋር ጥምረት ለመመስረት የቀረበው ሃሳብ በደገፈበት ቀን ነው ተብሏል። የሳይበር ጥቃቱ ትናንት ማታ የተጀመረ ሲሆን፥ በቀጣይ ቀናት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚችል የዘርፉ ባለሙያዎች አሳስበዋል። የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጠው መግለጫ፥ የተፈፀመውን ጥቃት ተከትሎ ክስተቱን በፍጥነት በመረዳት አስፈላጊ እርምጃዎች መወሰዳቸውን አስታውቋል። ይን እንጂ መስሪያ ቤቱ በተፈጸመው የሳይበር ጥቃት ምን ያህል ጉዳት ስለመድረሱ ያለው ነገር የለም። በሌላ በኩል አሁን ላይ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ከማድረግ ባለፈ ወደ ፊት ሊፈጸም የሚችልን የሳይበር ጥቃት መቶ በመቶ መቆጣጠር አስቸጋሪ መሆኑ ተመላክቷል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ጀምሮ የአውሮፓ ሀገራት በርካታ የሳይበር ጥቃቶችን እያስተናገዱ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ። ምንጭ ፦ቢቢሲ   \n \nጥያቄ: በኦስትሪያ በየትኛም የመንግስት መስሪያ ቤት ላይ ነው ከባድ የሳይበር ጥቃት የተፈጸመው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበ628 ዓክልበ.፣ ድራኮ የሚባል ጸሃፊ የአቴና ከተማ ሕግጋት ጻፈ፤ ይህም ሕግ እጅግ ጨካኝ ሆኖ ይሙት በቃ ለማንኛውም ጥፋት ወሰነ። በ600 ዓክልበ.፣ የአቴና አለቃ ሶሎን አዲስ ሕገ መንግሥት ፈጠረ። የሰራተኞች ሸክም አቀለለ፣ ነገር ግን ባላባትነት በልደት ሳይሆን በንብረት ብዛት እንዲቈጠር አስደረገ። ክሊስቴኔስ እንደገና በ516 ዓክልበ. በዴሞክራሲያዊ መሠረት የተሻሸለ ለአቴና ሕገ መንግሥት አወጣ። የግሪክ ፈላስፋ አሪስጣጣሊስ በ350 ዓክልበ. ግድም የሕገ መንግሥት ሀሣብ ለይቶ ዐወቀ። በጽሑፎቹ የአቴና፣ የስፓርታና የካርታግና ሕገ መንግሥቶች ያነጻጽራል። በመደምደሚያው የተሻለው ሕገ መንግሥት ከንጉሣዊ፣ ከመኳንንታዊና ከሕዝባዊ ወገኖች የተደባለቀ መሆኑን ገመተ። በሀሣቡ በመንግሥት የሚከፋፈሉ ዜጎች ከማይከፋፈሉ ከባርዮችና ዜጎች ካልሆኑ ሰዎች ልዩነት አደረገ። ሮማውያን መጀመርያ «12ቱ ሰንተረዦች» የተባለውን ሕገ መንግሥት ያወጡ በ457 ዓክልበ. ነበር። ከዚያ በኋላ አንዳንዴ የተለያዩ ሕጎችና ትእዛዛት ይጨምሩበት ነበር እንጂ እስከ መጽሐፈ ቴዎዶስዮስ ድረስ (430 ዓ.ም.) ሌላ ክምቹ ሕገ መንግሥት አልኖረም ነበር። በኋላም በምሥራቁ መንግሥት (ቢዛንታይን) በኩል መጽሐፈ ዩስጢኒያኖስ (526 ዓ.ም.) ለአውሮፓ ከፍ ያለ ተጽእኖ ነበረው። ይህም በምስራቁ ነገሥታት 3ኛ ሌዎን ኢሳውራዊ «ኤክሎጋ» (732 ዓ.ም.) እና በ1ኛ ባሲሌዎስ «ባሲሊካ» (870 ዓ.ም.) በተባሉት ሕገ ፍትሐን ተከተለ። \n \nጥያቄ: 12ቱ ሰንተረዦች የተባለ ሕገ መንግስት በ457 ዓክልበ. ለመጀመሪያ ጊዜ ያዘጋጁት እነማን ነበሩ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሮማውያን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: በዚምባቡዌ የሚገኙ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የምን ስልጣኔ እንደ ነበር ያሳያሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የባንቱ ስልጣኔ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአልፍሬድ ኢልግ ቢትወደድ አልፍሬድ ኢልግበዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ኑሮውን ኢትዮጵያ ውስጥ የመሠረተ፤ የስዊትዘርላንድ ዜጋ ነበር። ኢልግ በምሕንድስና ሙያው ባቡር እና የቧንቧ ውሐ ለአገራችን ካስተዋወቃቸው ብዙ ዘመናዊ የሥልጣኔ መስመሮች ሁለቱ ሲሆኑ በንጉሠ ነገሥቱ ፊት ታላቅ ታማኝነትን በማፍራቱ የዘውድ አማካሪ እና የአገሪቱን የውጭ ጉዳይ እስከመምራትም የበቃ ሰው ነበር። ቢትወደድ ኢልግ በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ብዙ ሚና ከተጫወቱ አውሮፓውያን መሃል ባገሪቱ ባሳለፋቸው ሃያ ሰባት ዓመታት እና ባስቀመጣቸው የልማት አሻራዎቹ የታሪክ ሥፍራው በጣም የጎላ ሆኖ እናገኘዋለን። ኢልግ በስዊትዘርላንድ፣ ፍራውንፌልድ በሚባል ከዙሪክ ከተማ በሰሜን-ምሥራቅ አቅጣጫ በሚገኝ ሥፍራ በ መጋቢት ወር ፲፰፻፵፮ ዓ/ም ተወልዶ በስድሳ ሁለት ዓመቱ የገና ዕለት (ታሕሣሥ ፳፱ ቀን) ፲፱፻፰ ዓ/ም ዙሪክ ላይ በልብ ምታት ምክንያት አረፈ። ታዋቂው የታሪክ ምሁር ሪቻርድ ፓንክኸርስት ዳግማዊ ምኒልክ ገና በልጅነታቸው የዓፄ ተዎድሮስ እስረኛ በነበሩ ጊዜ ቴዎድሮስ አጠገባቸው የነበሩትን አውሮፓዊ ወንጌላያን መድፍና መሣሪያዎች እንዲሠሩላቸው ማግባባታቸውን ልብ አድርገው ነበርና የሸዋ ንጉሥ ሲሆኑ በ ኤደን ላይ የነበረ አንድ የስዊትዘርላንድ ዜጋ ነጋዴ ምሕንድስና የሚያውቁ አውሮፓውያን ባለሙያዎችን እንዲፈልግላቸው ጠይቀውት ነበር ይላል። ኢልግ እና ሁለት የአገሩ ሰዎች በ፲፰፻፸ ዓ/ም አካባቢ ጉዞዋቸውን ወደኢትዮጵያ አምርተው ሸዋ ሲገቡ ንጉሥ ምኒልክ መጫሚያ እንዲሠራላቸው ያዙትና ሠርቶ ባበረከተላቸውም መጫሚያ እጅግ እንደተደሰቱ ይነገራል። በሌላ ዘገባ ደግሞ ንጉሡ ኢልግን ጠመንጃ እንዲሠራላቸው አዘዙት። ኢልግ ጠመንጃ ለመሥራት ሙያ እንደሌለውና ከውጭ የሚመጣ መሣሪያ እሱ ከሚሠራው እጅግ የላቀ እንደሚሆን ቢያስረዳም፤ ምኒልክ ኃሳባቸውን የማይለውጡ ሆኑ። እሱም እንደተጠየቀው የሙከራውን ውጤት ሲያሳቸው ንጉሡ ተደስተው ይሄንኑ ጠመንጃ በግምጃ ቤታቸው የክብር ቦታ ሰጡት። ያም ሆነ ይህ ኢልግ በንጉሡ በኩል ዘለቄታ የነበረው የበጎ አስተያየትን እንዳተረፈ ግልጽ ነው። ወዲያው በምሕንድስና ሥራ በደሞዘኝነት ቀጥረውት በየወሩ ሰባት ወይም ስምንት ፓውንድ በጠገራ ብር ይከፍሉት እንደነበር ፓንክኸርስት ዘግቧል። \n \nጥያቄ: አልፍሬድ ኢልግ ለሞት ያበቃው ምን ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ልብ ምታት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዝናሽ ማሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ በእሁድ ጠዋት ፕሮግራም ከ1979 ጀምሮ በመስራት ትታወቃለች፡፡ በኢትዮጵያ ሬድዮ ለ 16 አመት ያገለገለችው ዝናሽ ከእነ ታደሰ ሙሉነህ ፤ ታምራት አሰፋ ጋር በትጋት የሰራች ሲሆን ከ20 አመት በፊት ከእነ ቤተሰቦችዋ ወደ ምድረ አሜሪካ አቅንታለች፡፡ እምብዛም ልደት መከበር ባልተለመደበት በዚያን ዘመን ከተወለደች ከአንድ አመቷ ጀምሮ እስከ 16 አመቷ ድረስ ቤተሰቦቿ የልደት በዐልዋን እያከበሩላት ያደገችው ዝናሽ ማሞ አብዲበአዲስ አበባ ከተማ ግንቦት 21 ቀን 1954 አ.ም መወለድዋን ለማስታወስ አልተቸገረችም:: ትውልዷም እድገቷም ጠብመንጃ ያዥ ወይም በቅሎ ቤትበሚባለው አካባቢ ነበርእናትና አባቷ ወ/ሮ ሽብሬ ወ/ሃናና አቶ ማሞ አብዲ ይባላሉ:: ዝናሽ ማሞ መጀመሪያ በቄስ ትምህርት ቤት ከፊደል እስከ መልእክተ ዮሀንስ ተምራ ፊደላትን ከለየች በኋላ በበቅሎ ቤት አካባቢ በነበረው አስቀድሞ ኤስ አይ ኤም የልጃገረዶች ክርስቲያን አካዳሚ ተብሎ ይታወቅ በነበረው ጂሲኤ የልጃገረዶች ት/ቤት ከ አንደኛ እስከ ስድስተኛቀጥሎም ይኸው ት/ቤት የፀጋ ክርስቲያን አካዳሚ በመባል ስሙ ተቀይሮ ወንዶችም አብረው መማር በጀመሩበት ት/ቤት ከሰባተኛ እስከ አስረኛበመጨረሻም በጊዜው የነበረው የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግስት ት/ቤቱን ወደ መንግስት ንብረትነት በማዘዋወር የአብዬት ቅርስ ተብሎ ከሰየመው በኋላ አስራ አንደኛና አስራ ሁለተኛ ክፍልን እዚያው ተምራለች:: \n \nጥያቄ: የዝናሽ እናት እና አባት ማን ይባላሉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ አባቷ ወ/ሮ ሽብሬ ወ/ሃናና አቶ ማሞ አብዲ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ አ.ማ ኢንደስትሪያል ኮምፕሌክስ የመሰረት ድንጋይ የማኖር ስነስርአት ተካሄደ። የፋብሪካው ግንባታ በ2 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር የሚከናወን ሲሆን በሀገሪቱ ያለውን የሲሚንቶ እጥረት ሊቀርፍ እንደሚችል ተጠቁሟል፡፡ \n \nጥያቄ: የለሚ ናሽናል ፋብሪካ ግንባታ የምን እጥረትን ሊቀርፍ ይችላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የሲሚንቶ እጥረት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየባሕል ጥናት የባህል ጥናት፣ ሥነ ኅብረተሠብ ወይን ሥነ ማኅበረሰብ ሌላ ስሙ ሶሲዮሎጂ የሰው ልጆች በቡድንና በተናጥል ያላቸውን ባሕል፣ ጠባይና አደረጃጀት የሚያጠና ክፍል ነው። በዚህም ውስጥ አንትሮፖሎጂ ወይም የሰው ልጅ ጥናት (ሥነ ሰብእ) አለ። ሶሲዮሎጂ የሚለው ቃል በፈረንሳያዊው ጸሐፊ ኤማኑወል-ዦሰፍ ሲዬ በ1772 ዓ.ም. ከሮማይስጥ ሶኪውስ (ባልንጀራ፣ ጓደኛ) እና ከግሪክ ሎጎስ (ቃል ወይም ጥናት) በማጋጠም ተፈጠረ። የፈረንሳይ ፈላስፋ ኦጉስት ኮምፕት ከ1830 ዓ.ም. ጀምሮ በሰፊ ጠቀመው። የኅብረተሰብ ጥናት ሲሆን የኅብረተሰብ ጽንሰ ሀሣብ በሮማይስጥ ትርጉም ሶኪየታስ ወይም የባልንጀሮች ግንኙነት ያመልከታል። \n \nጥያቄ: ሶሲዮሎጂ የሚለው ቃል ከሮማስጥ እና ከግሪክ በተውጣጡ ቃላት በማጋጠም የፈጠረው ፈረንሳዊው ሰው ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ኤማኑወል-ዦሰፍ ሲዬ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአፋር (ክልል) አፋር ክልል (ክልል 2) በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙት ዘጠኝ ክልሎች አንዱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ዋና ከተማው ሰመራ ሲሆን የቀድሞዋ ከተማ ግን አሳይታ ነበረች። 96,707 ካሬ ኪ.ሜ. ሲሸፍን በ1999 እ.ኤ.አ. የሕዝብ ብዛቱ 1,188,000 ነው። የድንቅ ነሽ ወይም ሉሲ አጽም በአፋር ክልል ውስጥ በ, 1967 (Nov. 24, 1974 እ.ኤ.አ.) ነው የተገኘው። በማርች 5, 2005 ደግሞ ሌላ 3.8 ሚሊዮን ዓመት የሚገመት አጽምም በዚሁ ክልል ተገኝቷል። \n \nጥያቄ: አፋር ክልል በ1999 እ.ኤ.አ. በተደረገ ቆጠራ ምን ያህል ሰው ይኖራል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 1,188,000 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nማርኮ ፖሎ ማርኮ ፖሎ (1254 - ጥር 8፣ 1324) ጥንታዊው የጣሊያን ተጓዥ እና ነጋዴ ነበር። ታዋቂነትም ያተረፈው በተለይ ወደቻይና እና ሞንጎሊያ ከተጓዙት አውሮጳውያን ቀደምትነት ስለነበረው ነው። በዚህ ምክንያት ከሱ በኋላ ዘግይተው የተነሱት እነ ክርስቶፎር ኮሎምበስ ሳይቀር ለሱ ከፍተኛ ግምት እና አድንቆት እንደነበራቸው ታሪክ ይዘክራል። 17 አመት ሲሞላው ከጣሊያን ቬኒስ ከተማ በመነሳት፣ መጀመሪያ በጀልባ ከዚያም በእግሩና በግመል ተራሮችን በርሃን አቆራርጦ ቤይቺንግ ቻይና (በድሮ ስሟ ካቴ) ለመድረስ ችሏል። በጊዜው ቻይና ትመራ የነበረው በሞንጎሉ መሪ ኩብላ ካህን የሚባለው የጌንጊዝ ካህን ልጅ ነበር። ስርዓቱም የዩዋን ሥርወ መንግስት ይባል ነበር። ለሚቀጥሉት 17 ዓመታት በኩብላ ካህን ቤተመንግስት አስተዳደር ተሰጥቶት መንግስቱን አገልግሏል። ከዚያም ወደ ጣሊያን በውቅያኖሶች አቋርጦ ተመልሷል። ወደ 600 የሚሆኑ አብሮ ተጓዦች ግን በበሽታና በጥቃት ሞተዋል። ይህ ተጓዥ ኑድል የተባለውን የቻይኖች የምግብ አይነት ወደ አገሩ ጣልያን በማምጣት የፓስታ ስራ አሰራርን ለጣሊያኖች ለመጀመሪያ ጊዜ አስተዋውቋል። በጣሊያኖች እርስ በርስ ጦርነት ተማርኮ እስር ቤት ከገባ በኋላ ለእስር ጓደኛው ርስቲቸሎ የነገረውን ታሪክ ረስቲቸሎ ጽፎ በማሳተም ለማርኮ ፖሎ በአውሮጳ ዙርያ ታላቅ መታወቅን አስገኝቶለታል። \n \nጥያቄ: ማርኮ ፖሎ የእድሜ ዘመኑ ከመቼ እስከ መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 1254 - ጥር 8፣ 1324 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአዲስ አበባ መስከረም 23/2012 ዕውቁና አንጋፋው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ በውጭ አገራት የሚሰሩ ኢትዮጵያዊያን ሳይንቲስቶች ወጣቶችን በሳይንስ በማነጽ ተግባር እንዲሰማሩ፤ መንግስትም ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጥሪ አቀረቡ። ፕሮፌሰር ጥላሁን በቻይና ከሚገኙ የምርምር ተቋማት ጋር በመተባበር ኢትዮጵያ ውስጥ የአፍሪካ ሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል ሊያቋቁሙ መሆኑን ይፋ አድርገዋል። የአሜሪካው ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ትምህርት ቤት ዕውቁ ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ በሚዘጋጀው ወርኃዊ የሳይንስ ገለጻ መድረክ ወጣቱን ትውልድ ማስተማርና ማነጽ ለኢትዮጵያ ተስፋ፤ የቻይና ተምሳሌትነት በሚል ትናንት ምሽት ገለጻ አድርገዋል። በአውሮጳዊያኑ ዘመን አቆጣጠር 1943 በኢትዮጵያ የተወለዱት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በናዝሬት፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጅማ የግብርና ቴክኒካል ትምህርት ቤቶች አጠናቀው በቀድሞው የአለማያ እርሻ ኮሌጅ ለሁለት ዓመት ተከታትለዋል። ከዛሬ 55 ዓመታት በፊት በኮሌጅ ቆይታቸው ባሳዩት የላቀ ውጤትም አሜሪካን አገር በሚገኘው የካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምና ትምህር ቤት ተልከው ትምህርታቸውን በማጥናት ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው በቢሾፍቱ የእንስሳት ህክምና ትምህርት ቤት አስተምረዋል። ከሁለት ዓመታት በኋላም ወደ ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ በመመለስ የ3ኛ ዲግሪያቸውን በደቂቀ ሥነ ሕይወት መስክ በማጥናት በአውሮጳዊያኑ አቆጣጠር ከ1980-2006 በተማሩበት ካሊፎርኒያ በዋሽንግተን ስቴት ዩኒቨርሲቲ ከረዳት እስከ ሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አስተምረዋል፤ ተመራምረዋል። እ.አ.አ ከ2017 ጀምሮ ደግሞ የዲስቲንጉሽድ ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ማዕረግ ያገኙ ሲሆን እ.አ.አ ከ1990 ጀምሮ እስካሁን ድረስ ዓለም አቀፍ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል በማቋቋም በዳይሬክተርነት እየመሩ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ 3ኛ ዲግሪያቸውን የሰሩት በምን ላይ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በደቂቀ ሥነ ሕይወት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቢል ክሊንተን ያደጉት በሆት ስፕሪንግስ፣ አርካንሳው ነው። የቢል ክሊንተን አባት ዊሊያም ጄፈርሰን ብላይዝ ጁኚየር፣ ቢል ክሊንተን ከመወለዱ ሶስት ወር በፊት በመኪና አደጋ ሞተዋል። የቢል ክሊንተን እናት ቨርጂኒያ ክሊንተን ኬሊ፣ በ1950 እ.ኤ.ኣ. ሮጀር ክሊንተን የሚባል ሰዉ አገባች። 14 ዓመቱ ሲሆን ቢል ክሊንተን የመጨረሻ ስሙን ወደ ክሊንተን ለወጠ። ክሊንተን በጆርጅታውን ዩኒቨርሲቲ፥ ዋሽንግተን ዲ.ሲ.፣ ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ፥ ኢንግላንድ፣ እና ዬል ዩኒቨርሲቲ፥ ኮነቲኬት ተምረዋል። በ1975 እ.ኤ.ኣ. ሂለሪ ሮድሃምን አገቡና በሊትል ሮክ፥ አርካንሳው መኖር ጀመሩ። ከዚያም በዩኒቨርሲቴ ኦፍ አርካንሳው የሕግ ፐሮፌሰር ሆነው አገልግለዋል። ቢል ክሊንተን የአርካንሳው አስተዳዳሪ ሆኖ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመረጡት በ1978 እ.ኤ.ኣ. ነው። በዛ ጊዜ ከአሜሪካ በዕድሜ ትንሹ አስተዳዳሪ ነበሩ። በ1980 እ.ኤ.ኣ. በፍራንክ ዲ ዋይት ከተሸነፉ በኋላ በ1982 እ.ኤ.ኣ. እንደገና ተመረጡ። ከዛ ጀምሮ እስከ 1992 እ.ኤ.ኣ. ድረስ ለአራት ጊዜ አስተዳዳሪ ሆነው መርተዋል። በ1984 እ.ኤ.ኣ. የአስተዳዳሪ የስልጣን ዕድሜ ከ2 ዓመት ወደ 4 ዓመት አራዝመዋል። በ1992 እ.ኤ.ኣ. ለፕሬዝዳንትነት ተወዳድርው አሸንፈዋል። በ1996 እንደገና ተወዳድረው አሸንፈዋል። \n \nጥያቄ: ቢል ክሊንተን ለሁለተኛ ጊዜ የአሜሪካ ፕሬዝደንት ሆነው ያሸነፉት መች ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ1996 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበደቡብ ሱዳን መከላከያ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጀኔራል ጆንሰን ጁማ ኡኮት የተመራ ልዑክ አዲስ አበባ ገብቷል፡፡ ልዑኩ አዲስ አበባ ሲገባ በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጀኔራል ብርሀኑ ጁላ እና በሌሎች ከፍተኛ የመከላከያ አዛዦች አቀባበል ተደርጎለታል፡፡ በቆይታቸውም በሁለቱ ሀገራት የመከላከያ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚመክሩ ከመከላከያ ሰራዊት ገጽ የተገኘው መረጃ አመላክቷል፡፡ \n \nጥያቄ: የደቡብ ሱዳን ጠቅላይ ኤታማዦር ለምን ኢትዮጵያ መጡ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በሁለቱ ሀገራት የመከላከያ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚመክሩ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ እንግሊዝ ሀገር አንደደረሰም የወቅቱ የእንግሊዝ ንግስት ከነበረችው ንግስት ቪክቶሪያ ጋር ተገናኘ፡፡ ንግስቲቱም ልዑሉ የፈለገው እና ያሻው ይደረግለት ዘንድ ቀጭን ትዕዛዝ አስተላለፈች፡፡ ልዑሉ በመቅደላ የነበረውን እልቂት በመጠኑም ቢሆን በማየቱ እና የአባቱ እና የእናቱ ተከታታይ ሞትም በልጅ አዕምሮው ሊቀበለው ከሚችለው በላይ ስለነበር እጅግ ታውኮ እንደነበር በተደጋጋሚ ተፅፎ እናገኛለን፡፡ በ1861 ዓ.ም ስፒዲ ህንድ ሀገር በምትገኝ አንዲት ከተማ አዛዥ ሆኖ ስለተሾመ የ8 ዓመቱን አለማየሁን እና ሚስቱን ይዞ ወደዛው አቀና፡፡ በሄዱበት ሀገርም አለማየሁ ትምህርቱን መከታተሉን ቀጥሎ የነበረ ሲሆን ከመደበኛው ትምህርት በዘለለም ፈረስ ግልቢያ እና ሌሎች ስፖርቶችንም ያዘወትር ነበር፡፡ 1867 ዓ.ም አለማየሁ ወደ ራግቢ ትምህርት ቤት ተዛወረ፡፡ በዚህም ከቄስ ብሌክ ቤት ወጥቶ ወደ ሊው ዋርነር ቤት እንዲገባ ተደረገ፡፡ በዚህ ግን ደስተኛ ስላልነበር በቀጣዩ አመት ሚስተር ድራፐር ቤት እንዲኖር ተደረገ፡፡ ቄስ ብሌክም ካዩት የልዑሉ ባህሪ በመነሳት ልዑሉ ወታደርነት ላይ ቢያተኩር የበለጠ ውጤታማ እንደሚሆን ተናገሩ፡፡ በዚህም ንግግር መሰረት የወታደር ትምህርት ቤት እንዲገባ ተደረገ፡፡ በአንድ ወቅት አለማየሁ ወደ ሊድስ በመሄድ በሰር ራምሰን ቤት ተቀምጦ በነበረበት ወቅት በመርዝ ተመረዘ። መርዙ ህዳር 5 ቀን 1872 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3 ሰዓት ከሩብ በተወለደ በ19 ዓመቱ ከዚህ አለም እንዲሰናበት አደረገው፡፡ አስከሬኑም ዊንድሶር ባለው የነገስታት መቀበርያ በክብር አረፈ፡፡ በመቃብሩም ላይ “የሀበሻው ልዑል አለማየሁ” የሚል ፅሁፍ ሰፍሮበት እስካሁን በእንግሊዝ ሀገር ይገኛል፡፡ \n \nጥያቄ: በስንት አመተ ምህረት ነው ስፒዲ ህንድ ሀገር በምትገኝ ከተማ አዛዥ ሆና የተሾመው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ1861 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየእስክንድርያ ማስተማርያ ቤት የእስክንድርያ ማስተማርያ ቤት በእስክንድርያ፣ ግብጽ በጥንት (54-373 ዓም ያህል) የተገኘ የክርስትና ሥነ መለኮት ትምህርት ተቋም ነበረ። ተቋሙን የመሠረተው የኢየሱስ ሐዋርያ እና መጀመርያው የእስክንድርያ ጳጳስ፣ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ በ54 ዓም እንደ ሆነ ተጽፏል። የተቋሙ መጀመርያው መሪ በኋላ የእስክንድያ ፮ኛው ጳጳስ የሆነው ዩስቱስ እንደ ተሾመ ይታመናል። ተቋሙ ያስተማረው ከሥነ መለኮት፣ መጽሐፍ ቅዱስና ክርስትናን ጭምር፣ የግሪክኛና የሮማይስጥ ስነ ጽሁፍ፣ ሥነ ጥበብ፣ ስነ አመክንዮ፣ ሥነ ቁጥርና ስነ-ተፈጥሮ ጥናቶች ነበሩ። ለዕውሮችም ማስተማርያ አገልግሎት አቀረቡ። በፓንታይኖስ መሪነት (173-182 ዓም) ተቋሙ ስለ ትምህርቱ ዝነኛ ሆነ። ፓንታይኖስ በክርስትና ከመጠመቁ በፊት፣ የግሪኮች «ስቶዊሲሲም» ፍልስፍና ተከታይ ሆኖ ነበር። ፓንታይኖስ የግሪክ ፍልስፍና ከክርስትና ርዕዮተ አለም ጋር እንዳዋሐደ ይታስባል። ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ ከ182-194 ዓም በተቋሙ መሪነት ተከተለው። ብዙ አረመኔዎች በዚያን ጊዜ ለትምህርት ስለመጡ ከፍልስፍና መሠረት ጀምሮ የክርስትናን ትምህርት ያሳውቃቸው ነበር። በ194 ዓም የሮሜ መንግሥት ቄሣር በክርስቲያኖች ላይ ስላዘረጋው ማሳደድ፣ ቀሌምንጦስ ለጊዜው ከእስክንድርያ ሸሸ። እሱም የጻፋቻው ትልቅ መጻሕፍት ተርፈውልናል። የቀሌምንጦስ ተከታይ ኦሪገኔስ በመከራ ጊዜ ቢሆንም ተቋሙን በ195 ዓም ዳግመኛ አቆመ። ኦሪገኔስ ደግሞ ብሉይ ኪዳን በስድስት ትይዩ ዕብራይስጥና ግሪክኛ ትርጉሞች (ሄክሳፕላ) ያሳተመው እና ብዙ አንድምታ የጻፈው ዝነኛ መምህር ነው። በ373 ዓም በተካሄደው በቁስጥንጥንያ ጉባኤ፣ የጵጵሳት ቅድምንትነት ለሮሜ ፓፓ፣ ከርሱም ቀጥሎ ለአንጾኪያ ጳጳስ እንዲሰጥ የሚል ብያኔ ወረደ። ስለሆነም፣ የእስክንድርያ ጳጳስ የቀድሞ ቀድምትነቱን በማጣቱ፣ በእስክንድርያ ከተማ ውስጥ ትልቅ ሁከት ደረሰ። በዚያም ጊዜ በተደረገው ጉዳት የማስተማርያ ተቋሙ ጠፋ። \n \nጥያቄ: ከቀሌምንጦስ በኋላ ማን ተቋሙን ተረከበ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ኦሪገኔስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nእንቁላሎቿን ሆዷ ውስጥ የምትታቀፈው የአውስትራሊያ የእንቁራሪት ዝርያ (ጋስትሪክ ብሩዲንግ ፍሮግ) ያልተለመደ ዓይነት የመራቢያ ሥርዓት አላት፤ የዚህች እንቁራሪት ዝርያ ከ2002 ጀምሮ እንደጠፋ ይታሰባል የሚለው ጄደብሊው ዶት ኦርግ ድረ ገጽ ነው። \n \nጥያቄ: እንቁላሏን በሆዷ የምትታቀፈው የእንቁራሪት ዝርያ የየት ሀገር ነች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የአውስትራሊያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሮማንሽ ሮማንሽ ወይም ሩማንች (Rumantsch) ከስዊስ አገር 4 ብሔራዊ ቋንቋዎች 1ዱ ሆኖ ሌሎቹ 3 ጀርመንኛ ጣልኛና ፈረንሳይኛ ናቸው። ከሮማይስጥ የታደገ ቋንቋ በመሆኑ የሮማንስ ቋንቋ ቤተሠብ አባል ነውና በተለይ የሚመስለው ፈረንሳይኛ ወይም እጣልኛ ነው። የሚናገረው በግራውብውንደን (ግሪዞን) ካንቶን ስዊስ በሚኖሩ 60,000 ሰዎች ነው። ይህ ከስዊስ አገር ሕዝብ ብዛት 1% ብቻ ሲሆን ከስዊስ አገር ብሔራዊ ቋንቋዎች ሁሉ ትንሹ ነው። እንኳን በስዊስ አገር ከሚኖሩት ስርቦ-ክሮዌሽኛ ተናጋሪዎች ቁጥር ብዛት (111,000) በግማሽ ያንሳል። በስሜን እጣልያ አገር ዛሬ ለሚናገሩ ቋንቋዎች ለፍሪዩልያንና ለላዲን ቅርብ ዘመድ ነው። \n \nጥያቄ: ከስዊስ አገር ብሔራዊ ቋንቋዎች ሁሉ ትንሽ ተናጋሪ ያለው ቋንቋ የቱ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሮማንሽ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: ማሊ የምትገኘው የት አህጉር ውስጥ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አፍሪካ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበኢትዮጵያ ካሉ የኢንተርኔት አገልግሎቶች ተጠቃሚዎች ውስጥ 59 ነጥብ 5 ከመቶ የሚሆኑት ስልክ ቁጥርን እንደ ይለፍ-ቃል /password/ እንደሚጠቀሙ ጥናት አመለከተ። ተጠቃሚዎች የስልክ ቁጥርን መጠቀማቸው ጠንካራ የይለፍ-ቃል እንደተጠቀሙ እንደሚሰማቸውም በጥናቱ ተመላክቷል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የሳይበር ጥቃት በከፍተኛ መጠን እያደገ መምጣቱም ነው የተነገረው። በኢትዮጵያ ያለው በሳይበር ደህንነት የግንዛቤ መጠንም ዝቅተኛ እንደሆነ የኢንፎርሜሽን መረብና ደህንነት ኤጀንሲ ጥናት ያመለክታለል። ኤጀንሲው በ2011 ዓ.ም 1 ሺህ 635 የሚሆኑ ግለሰቦች ላይ ሀገር-አቀፍ የሳይበር ደህንነት ምዘና ጥናት አከናውኗል። በጥናቱ ከተሳተፉት መካከል 975 (59 ነጥብ 5 በመቶ) ያክሉ ስልክ ቁጥርን እንደ ይለፍ-ቃል/password/ በመጠቀም ጠንካራ የይለፍ-ቃል እንደተጠቀሙ እንደሚሰማቸው ጥናቱ ያመለክታል። በተጨማሪም 59 ነጥብ 1 በመቶ ያክሉ የጥናቱ ተሳታፊዎች የይለፍ ቃሎቻቸውን የሚታይ ቦታ ላይ ጽፈው ማስቀመጥን እንደ ማስታወሻ መንገድ እንደሚጠቀሙበት ገልጸዋል። 67 ነጥብ 6 ከመቶ የሚሆኑት የጥናቱ ተሳታፊዎች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚሰራጩ መረጃዎች ትክክለኛ ናቸው ብለው እንደሚያምኑም ነው የተነገረው። በመሆኑም የሳይበር ደህንነት ጉዳይ በቸልታ ሊታለፍ የማይገባውና የለት ተለት የህይወታችን አካል እየሆነ በመምጣቱ ተገቢውን ትኩረትና ጥናቃቄ ልናደርግ እንደሚገባ የኢንፎርሜሽን መረብና ደህንነት ኤጀንሲ የሰራውን ጥናት አስመልክቶ ያወጣው መረጃ ያመለክታል። \n \nጥያቄ: የኢንፎርሜሽን መረብና ደህንነት ኤጀንሲ በ2011 ባደረገው ጥናት በመቶኛ ምን ያህል ሰዎች በማኅበራዊ ሚዲያ የሚለቀቁ መረጃዎች እውነት እንደሆኑ ያመናሉ ብሏል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 67 ነጥብ 6 ከመቶ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበእንግሊዝ የተሰራውና የመንገድ ላይ ምልክት ማድረጊያው ሮቦት ሙከራውን አድርጓል። ሮቦቱ የተለያዩ የመንገድ ምልክቶችን በማስመር ወጪና ጊዜን ይቆጥባል ተብሏል። የሙከራ ስራውን ባደረገበት ወቅት ውጤታማነት ታይቶበታል የተባለውቅ ሮቦት፥ በአራት ሰዓት በ12 ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር መንገድ ላይ ምልክቶችን ማድረጉ ተነግሯል። ይህ ቴክኖሎጂ ጊዜን በመቆጠብ ስራውን የሚሰሩ ሰራተኞች ያጋጥማቸው የነበረውን ድካም፣ የሚደርሰውን የወገብ ጉዳት እና ምልክት በሚያደርጉበት ወቅት የሚከሰተውን የመኪና አደጋ ይቀንሳል ነው የተባለው። ይህን ቴክኖሎጂ የተቀበሉት ዋይ ጂ የመንገድ ተቋራጭ ቡድን ሥራ አስኪያጅ ዌን ጆንስተን፥ ቴክኖሎጂው መጨናነቅን ለመቀነስ፣ ጊዜን እና ገንዘብን ለመቆጠብ እንዲሁም ለኢኮኖሚያዊ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅዖ አለው ነው ያሉት። እንዲሁም ለተሻለ እና ጥራት ላለው የመንገድ ላይ ምልክት ያገለግላልም ብለዋል። ምንጭ፡- traffictechnologytoday.com ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ! https://t.me/fanatelevision \n \nጥያቄ: የመንገድ ላይ ምልክት ማድረጊያው ሮቦት የሚያስገኛቸው ጥቅሞች ምን ምን ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሰራተኞች ያጋጥማቸው የነበረውን ድካም፣ የሚደርሰውን የወገብ ጉዳት እና ምልክት በሚያደርጉበት ወቅት የሚከሰተውን የመኪና አደጋ ይቀንሳል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአብርሀም ሊንከን (የካቲት ፮ ቀን ፲፰፻፩ ዓ.ም. - ሚያዝያ ፰ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም.) ድረስ የኖሩ ከ፲፰፻፶፫ ዓ.ም. እስከ ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ድረስ ፲፮ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ከአሜሪካ የእርስ በርስ ጦርነት ፍጻሜ በኋላ ጆን ዊልክስ ቡዝ በተባለ ነፍሰ ገዳይ እጅ በጥይት ተመትተው ተገደሉ። የአብርሀም አባት ማሀይም ገበሬ ቢሆንም፣ አብርሀም ከልጅነት ጀምሮ እራሱን በትጋት ያስተምር ነበር። በ፲፰፻፳፮ ዓ.ም. ለኢሊኖይ ክፍለ ሀገር ምክር ቤት መቀመጫ ተመረጡ። የሕግ ትምህርት በጠንካራ ትጉነት አጥንቶ የሕግ ባለሙያ ሆነ። ከ፲፰፻፳፱ ዓ.ም. ጀምሮ የባርነት ተቃዋሚ ሆነ። ከአፍሪካ የተወሰዱት ጥቁር ሕዝቦች በግብርና መሥራት እንዲገደዱ ትክክለኛ ወይም ጥሩ ሀሣብ አይደለም ብለው አመኑ። ዳሩ ግን በ1834 ብዙ ባርያዎች ባገለገሉበት ቤተሠብ ውስጥ ያደገችውን ሚስታቸውን ሜሪ ቶድን አገቡ። ሜሪ ያለ ባርያዎች ከባልዋ ጋር መኖር ትንሽ የተቸገሩ ቢሆነም ከጊዜ ብዛት ግን ለምደዉ 4 ወንድ ልጆችን በተከተሉት አመታት ወለዱ። በ፲፰፻፵፮ ዓ.ም. የባርነት ተቃዋሚዎች ወገን ሪፐብሊካን ፓርቲ መሥርተው አብርሀም ከፍተኛ ሚና ተጫወቱ። በ፲፰፻፶፪ ዓ.ም. የፕሬዚዳንትነት ምርጫ ዘመቻ፣ እሳቸው የሪፐብሊካን ዕጩ ሆኑ። ምርጫው በተደረገበት ቀን በጥቅምት ፳፰ ቀን ፲፰፻፶፫ ዓ.ም.፣ ሊንከን አሸነፉ። በጦርነቱ የስሜን ሠራዊት ከብዛታቸው የተነሣ በአራት ዓመት ውስጥ አሸነፉ። በዚህ ጊዜ ላይ ሊንከን ለአመጸኖቹ ባርዮች ነጻነት አዋጁ። ያላመጹ ዜጎች ባርያዎች ግን በዚያን ጊዜ ነጻ አልወጡም። በ፲፰፻፶፮ዓ.ም.ምርጫ ሊንከን በቀላል ለሁለተኛ ጊዜ ለፕሬዚዳንትነት ተመረጡ። በሚያዝያ ፪ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. የኮንፌደራት ሠራዊት እጁን ሰጠ። ነገር ግን ሚያዝያ ፯ ቀን የመድረክ ትርዒት ሲያዩ በነፍሰ ገዳዩ በጆን ዊልክስ ቡዝ እጅ በጥይት ተመትተው በማግሥቱ ሞቱ። ከዚህም ትንሽ በኋላ ባርነት በሕግ በሙሉ ተክለክሎ የተረፉት ባርያዎች ነጻነት አገኙ። \n \nጥያቄ: አብርሃም ሊንከን መቼ ሞተ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየ2010 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ የ2010 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ ፲፱ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የነበረ ሲሆን ከሰኔ ፬ እስከ ሐምሌ ፬ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. በደቡብ አፍሪካ ተካሄዷል። ውድድሩን ለማቅረብ የተካሄደው ዕጣ ውስጥ የአፍሪካ ሀገሮች ብቻ እንዲሳተፉ ነበር የተፈቀደው። ደቡብ አፍሪካ ግብፅና ሞሮኮን በማሸነፍ የመጀመሪያው የዓለም ዋንጫን ያቀረበች አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ፊፋ ለውድድሩ ያቀረበው ጠቅላላ የሽልማት ገንዘብ $420 ሚሊዮን ነው። ይህም ከ2006 እ.ኤ.አ. ውድድር ሽልማት ገንዘብ የስልሳ ከመቶ ዕድገት አለው። ከዚህ ውስጥ $40 ሚሊዮን የሚሆነው ተጫዋቾቹ ለሚጫወቱበት ክለቦች ተጫዋቾቹ ለሚደርስባቸው ጉዳት መካካሻ እንዲሆን ተሰጥቷል። ከውድድሩ በፊት እያንዳንዱ ቡድን ለዝግጅት ወጪው $1 ሚሊዮን ተረከበ። ግጥሚያዎቹ በዘጠኝ ከተማዎች ውስጥ በሚገኙ አስር ስታዲየሞች ውስጥ ነው የተካሄዱት። የዋንጫ ጨዋታው በጆሃንስበርግ ከተማ በሚገኘው ሶከር ሲቲ ስታዲየም ነው የተከናወነው። የምድብ ድልድል ሥነ ስርዓቱ በኬፕ ታውን፣ ደቡብ አፍሪካ በሚገኘው ኬፕ ታውን ዓለም አቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል በኅዳር ፳፭ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. ተከናወነ። ሥነ ስርዓቱ የቀረበው በደቡብ አፍሪካዊቷ ተዋናይ ሻርሊዝ ቴሮን እና የፊፋ ዋና ጸሐፊ ዠሮም ቫልክ ነው። የዕጣ ኳሶቹን ያወጡት ዴቪድ ቤክሃም፣ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ፣ ጆን ስሚት፣ መካያ ንቲኒ፣ ማቲው ቡዝ እና ሲምፊዌ ድሉድሉ ናቸው። የፊፋ ዳኛዎች ኮሚቴ ፳፱ ዳኛዎችን ለዓለም ዋንጫ መርጧል። እነዚህም ከኤ.ኤፍ.ሲ. አራት፣ ከካፍ አስር፣ ከኮንሜቦል ስድስት፣ ከኮንካካፍ አራት፣ ከኦ.ኤፍ.ሲ. ሁለት እና ከዩኤፋ አስር ዳኛዎችን ያጠቃልላል። እንግሊዛዊው ዳኛ ሀዋርድ ዌብ የዋንጫ ጨዋታውን እንዲዳኝ ተመርጧል። \n \nጥያቄ: ደቡብ አፍሪካ ስንተኛውን የፊፋ የዓለም ዋንጫ አዘጋጀች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ፲፱ኛው ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሴኔጋል ከ፹ በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሏት። ፓርላማዋ ሁለት ምክር ቤቶች አሉት። አንዱ ፻፳ መቀመጫዎች ያሉት የብሔራዊ ስብሰባ (እንግሊዝኛ፦ National Assembly) ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ፻ መቀመጫዎች ያሉት ሴኔት ነው። ሴኔጋል ራሱን የቻለ ህግ ተርጓሚ አካል አላት። ዳኛዎቹ የሚሾሙት በፕሬዝዳንቱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ሴኔጋል የዴሞክራሲ ሂደት ስኬታማ ነው ከሚባሉት የቀድሞ ቅኝ ተገዢ ሀገራት መካከል የምትጠቀስ ናት። የአካባቢ አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። ማራባውት የሚባሉ የእስልምና ሃይማኖት መሪዎችም በሴኔጋል ጠንካራ የፖለቲካ ተፅእኖ አላቸው፡ ከ፪ ሚሊዮን ነዋሪዎች ያሉበት የሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር የሀገሩ ትልቁ ከተማ ነው። ሁለተኛው ፭፻ ሺህ ሰዎች የሚኖሩበት ቱባ ከተማ ነው። ሴኔጋል ከ12.5 ሚልዮን በላይ የሚሆን ሕዝብ አላት። ከዚህ ውስጥም ወደ ፵፪ ከመቶ በገጠር ነው የሚኖረው። የአሜሪካ የስደተኖች ኮሚቴ ባቀረበው የ2008 እ.ኤ.አ. የዓለም ስደተኞች አጠቃላይ ቅኝት መሠረት ሴኔጋል በ2007 እ.ኤ.አ. ወደ 23,800 የሚገመቱ ስደተኞች ይኖሩባታል። ከዚህ አብዛኛዎቹ የመጡት ከሞሪታኒያ ነው። ስደተኞቹ በንድዮም፣ ዶዴል እና በሴኔጋል ወንዝ አቅራቢያ በሚገኙ ሠፈሮች ይኖራሉ። የአገር ይፋዊ ብሔራዊ ቋንቋ ፈረንሳይኛ ሲሆን ከብዙ ኗሪ ቋንቋዎች 11ዱ በተለይም ዎሎፍኛ አገራዊ ዕውቅና አላቸው። ሌሎቹ ባላንታኛ፣ ማንዲንክኛ፣ ፑላርኛ (ፉላኒኛ)፣ ሰረርኛ፣ ሶኒንክኛ፣ ኖንኛ፣ ማንካኛኛ፣ ማንጃክኛ፣ ጆላኛ እና ሀሣኒያ አረብኛ ናቸው። ፖርቱጊዝኛም በትምህርት ቤት ይማራል፣ የካቦ ቨርዴ እና የጊኔ-ቢሳው ኅብረተሠቦችም ፖርቱጊዝኛ ክሬዮል ይናገራሉ። ከሴኔጋል ሕዝብ 94% የእስልምና አማኞች፣ 5% ክርስትና (ባብዛኛው ካቶሊክ)፣ 1% የኗሪ አርመኔነት ተከታዮች ናቸው። የመንግሥት ሃይማኖት የለውም። በሴኔጋል ልማዳዊ ባሕል ግሪዮት የተባሉ ሽማግሎች ታሪኮቻቸውን በአፍ ቃል ይደግማሉ። ሴኔጋል ለሙዚቃዊ ስልቶቹ ይታወቃል፤ በተለይ የሚወድደው ዘመናዊው ስልት ምባላክስ ተብሏል። በሴኔጋል አበሳሰል በተለይ አሣ፣ ዶሮ፣ በግ፣ አተር፣ ዕንቁላል፣ በሬ ይጠቀማሉ፤ እስላም አገር እንደ ሆነው መጠን ግን አሳማ አይበላም። ኩስኩስ፣ ሩዝ፣ ስኳር ድንች፣ ምስር፣ ጥቁር-ዐይን አተር ደግሞ በሴኔጋል አበሳሰል በሰፊ ይገኛሉ። በእስፖርት በኩል፣ ከሁሉ የሚወደደው ባህላዊው የሴኔጋል ትግል ግጥሚያ ሲሆን፣ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ ደግሞ እጅግ ይወደዳሉ። \n \nጥያቄ: የሴኔጋል ፓርላማ ስንት ምክር ቤት አለው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሁለት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nባህር ዛፍ ባህር ዛፍ በተፈጥሮው ከአውስትራሊያ የሚገኝ አበባ ሚያብብ የዛፍ ወገን ነው። በአለም ላይ 700 አይነት የባህር ዛፍ ዝርያዎች አሉ፣ ከነዚህ ውስጥ 15ቱ ከአዉስትራሊያ ውጭ በተፈጥሮ ሲገኙ ከ700ው 9ኙ ዘር ብቻ አውስትራሊያ ውስጥ በተፈጥሮ አይገኝም። በኢትዮጵያ በተለይ የታወቁት፦ ነጭ ባሕር ዛፍ ቀይ ባሕር ዛፍ ናቸው። በአዲስ አበባ ከተማ ዳግማዊ ምኒልክ የባህር ዛፍ ፍሬ አስመጥተው ካስተከሉ በኋላ ይሄ አዲስ ዕጽ ዓየሩ ተስማምቶት ለከተማዋ የአረንጓዴ መቀነት ይመስል በጥቂት ዓመታት አሸበረቃት። በ፲፱፻፵ ዎቹ ይሄ መቀነት እስከ አርባ ካሬ ኪሎ ሜትር ስፋት በመያዙ ከተማዋን በሰፊው የባህር ዛፍ ከተማ የተባለ ቅጽል ስምን አትርፎላት ነበር። በአሁኑ ወቅት ባህር ዛፍ አለም አቀፍ ተፈላጊነት አግኝቷል። ይህም የሆነበት ምክንያት ቶሎ በማደግ አስፈላጊ እንጨት ይሰጣል የዛፉ ዘይት ለጽዳት እና እንዲሁም በራሪ ትንኞችን ለማባረር እንዲሁም ለመግደል ይረዳል:: አልፎ አልፎ ለወባ ትንኝ ማደግ ምቹ የሆኑ አረንቋወችን ለማድረቅ ይረዳል። ሆኖም ግን ባህር ዛፍ ከላይ ለተጠቀሱት አላማወች ቢያገለግልም ትልቁ ችግሩ ውሃ በጣም ይወዳል። ስለሆንም እርሱ በተተከለበት ሌሎች አትክልቶች የማደግ እድላቸው ዝቅተኛ ነው። ኢትዮጵያም ውስጥ በአዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች ምንጮችን እንዳደረቀ መረጃ አለ። \n \nጥያቄ: በዓለም ላይ ምን ያህል የባሕር ዛፍ ዝርያዎች አሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 700 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዩጋንዳ ዩጋንዳ ሪፐብሊክ (ወይም ዑጋንዳ) በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። በኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ ይዋሰናል። የዩጋንዳ ሰም የመጣው ከቡጋንዳ መንግሥት ነው። ከአረቦችና አውሮፓውያን በ1800ቹ ከመድረሳቸው በፊት ብዙ የሚታወቅ ነገር አልነበረም። በ15ተኛ መቶ ክፍለ-ዘመን ችዌዚ የተባለውን መንግስት በአፈ ታሪክ ይገኛል። አረቦችና አውሮፓውያን በ19ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሲደርሱ ብዙ መንግሥቶች በቦታው ነበሩ። እነዚህም በንዮሮ ፣ ቡሶጋ ፣ ቡጋንዳ ፣ ቶሮ እና አንኮልን ያጠቃልላሉ። ከ1894 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በታላቁ ብሪታን ስትመራ ነበር። የተለያዩ ቦታዎች ከተዋሃዱ በኋላ ዩጋንዳ በ1914 እ.ኤ.አ. ቅርጿን ያዘች። በ1966 እ.ኤ.አ. ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ ሕገ-መንግሥቱን አፍርሰው እራሳቸውን ፕሬዝዳንት አደረጉ። በ1971 እ.ኤ.አ. ኢዲ አሚን ሀገሩን መምራት ጀመሩ። የኢዲ አሚን አመራር 300,000 የሚገመቱ ዩጋንዳውያንን አስጨርሷል። በ1979 እ.ኤ.አ. የታንዛንያ ኃይሎች ኢዲ አሚንን ከሥልጣን ያስወግዳሉ። ሚልተን ኦቦቴ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ግን በ1985 እ.ኤ.አ. እንደገና ይወርዳሉ። ያሁኑ ፕሬዝዳንት ዮወሪ ሙሴቪኒ ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ናቸው። ፕሬዝዳነንቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይመርጣሉ። ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሎ ሲባምቢ ናቸው። ዩጋንዳ በመሬት የተቆለፈች ብትሆንም ታላላቅ የውሃ አካላት አሉ። ከነዚህ ውስጥም ቪክቶሪያ ሐይቅ፣ አልበርት ሐይቅ፣ ክዮጋ ሐይቅ እና ኤድዋርድ ሐይቅ ይዘረዘራሉ። ታላላቅ ከተማዎች በቪክቶሪያ ሐይቅ አቅራቢያ ይገኛሉ። እነዚህም ካምፓላንና እንትቤን ያጠቃልላል። ዩጋንዳ በ70 ወረዳዎች የተከፋፈለች ስትሆን እነዚህም በአራት አመራር ክልሎች ውስጥ ናቸው። አራቱ አመራር ክልሎች ሰሜናዊ ፣ ምሥራቃዊ ፣ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ይባላሉ። ወረዳዎቹ በዋና ከተማዎቻቸው ነው የሚሰየሙት። በዩጋንዳ ውስጥ የመዳብ እና ነጭ ብረት ክምችቶት አሉ። ግብርና ዋናው የኤኮኖሚ ሴክተር ነው። ከ80 በመቶ በላዩ የስራ ኃይል በግብርና ነው የተሰማራው። ቡና ዋናው የኤክስፖርት ትርፍ ምንጭ ነው። ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግሥቱ ከሌሎች ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን በኢዲ አሚን ጊዜ የወደቀውን ኤኮኖሚ ለማንሳት ተጣጥሯል። ዩጋንዳ ለብዙ ብሔረሰቦች ቤት ነው። ከነዚህ ውስጥ ግን አንድ ትልቁን ሕዝብ ብዛት የሚወክል የለም። 40 አካባቢ የሚሆኑ ቋንቋዎች ባሁኑ ጊዜ ይነገራሉ። ከነጻነት በኋላ እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተደርጓል። ብዙ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ ሉጋንዳ ሲሆን የአቴሶ ቋንቋ በሁለተኛነት ይከተላል። ኪስዋሂሊ ዋናው የንግድ ቋንቋ ነው። የዩጋንዳ የትምህርት ስርዐት የሰባት ዓመት መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፣ ስድስት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና ከ3 እስከ 5 ዓመት ከሁለተኛ ደረጃ በኃላ ትምህርት ያጠቃልላል። \n \nጥያቄ: በዩጋንዳ በሁለተኛነት ደረጃ የሚነገረው ቋንቋ ምንድን ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የአቴሶ ቋንቋ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሳህሌ ደጋጎ ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ከእናታቸው ከወይዘሮ ደጊቱ ፈይሣ እና ከባላንባራስ ደጋጎ አለቤ አብራክ በ1923 ዓ/ም በምዕራብ ወለጋ ልዩ ስሙ ነጆ ከተባለው ሥፍራ ተወለዱ። እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በነቀምት አንደኛ ደረጃ እና በአዲስ አበባ ተፈሪ መኮንን ት/ቤት ዘመናዊ ትምህርቱን ከተከታተለ በኋላ በነበረው ልዩ የውትድርና ፍቅር በቀድሞ 1ኛ ክፍለ ጦር በኋላም ማዕከላዊ ዕዝ ተብሎ በተጠራው የክ/ዘበኛ የጦር ክፍል ውስጥ በ1942 ዓ/ም ተቀጥሯል። በነበረው ሙያዊ ብቃትና ወታደራዊ ሥነ ሥርዓት አክባሪነት ከተራ ወታደርነት በአንድ ጊዜ የሃምሳ አለቅነት ማዕረግ ማግኘት የቻለው ሣህሌ፤ በሂደት እስከ ኮሎኔል ደረጃ ደርሷል። ወደ ሙዚቃ ቀማሪነት፣ ዜማና ግጥም ደራሲነት እንደዚሁም ወደ የማዕከላዊ ዕዝ የሙዚቃ ባንድ ኃላፊነት ከመሸጋገሩ በፊት በእግረኛ ባንድ ውስጥ “ክላርኔት” የተሰኘው የሙዚቃ መሣሪያ ተጫዎች የነበረው ሣህሌ ደጋጎ፣ የሙዚቃን ትምህርት የቀሰመው ከፈረንሣዊው መምህሩ ሙሴ ኒኮ መሆኑን የሕይወት ታሪኩ ላይ ተጠቅሷል። ከክላርኔት በተጨማሪ “አኮርዲዮን፣ አልቶ-ሳክስ፣ ፒያኖ” የተሰኙትን የሙዚቃ መሣሪያዎችንም በብቃት ይጫወት ነበር። በጠቅል ራዲዮ ጣቢያ (በተቋቋመ ጊዜ ) በአኮርዲዮን ጥዑም ዜማ ለጣቢያው አድማጮች ሲያንቆረቁር ከነበሩት የሙዚቃ ሰዎች መካከል ሣህሌ ደጋጎ የመጀመሪያው ነበር። ከእነ ሻለቃ ግርማ ይህደጎ፣ ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ እና ከሻለቃ ባሻ ገብረዓብ ተፈሪ ጋር በመሆን የክቡር ዘበኛ ኦርኬስትራን ስም እፁብ ድንቅ በማድረጉ በኩል የበኩሉን ሚና ተጫውቷል። ግጥምና ዜማ ደራሲ ከመሆኑም ባሻገር የአጫጭር እና ረዣዥም ድራማዎች ፀሐፊ የነበረው ሣህሌ፣ «ሁለገብ የታሪክ ማኅደር» ያሰኘውን ተግባር በሕይወት ዘመኑ አከናውኗል። \n \nጥያቄ: ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ በየትኛው የሙዚቃ ዘርፎች ይሰሩ ነብር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሙዚቃ ቀማሪነት፣ ዜማና ግጥም ደራሲነት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nባሕር-ዳር ባሕር-ዳር በድሮ ስሙ ባሕር ዳር ጊዮርጊስ በሰሜን-ምዕራብ ኢትዮጵያ የምትገኝ ከተማ ስትሆን የአማራ ክልል ዋና ከተማ ናት። ከተማዋ በቀድሞው ጎጃም ክፍለ ሓገር ውስጥ ከጣና ሐይቅ ደቡባዊ ጫፍ ላይ ተቀምጣ ስትገኝ ባህር ዳር እንደ መቀሌና ደሴ የወረዳ ደረጃ ያላት ስፔሻል(ልዩ) ዞን ናት። በማዕከላዊ ስታትስቲክ ትመና የ167,261 ህዝብ ከነሱም መሃከል የ86,355 ወንዶችና የ80,906 ሴቶች መኖሪያ ከተማ ናት። 1700 ሜትር ከባሕር ወለል በላይ ትገኛለች። ባሕር-ዳር ከአዲስ አበባ 565 ኪ.ሜ ወደ ሰሜን-ሰሜን ምዕራብ ትገኛለች። ባህር ዳር ከጢስ አባይ በ30 ኪሎሜትር ስለምትርቅ ለጎብኚዎች አመቺ ቦታ ላይ ናት። ባህር ዳር የአንድ የአስፋልት ንጣፍ ያለው ኤርፖርት የሰፊ ገበያና የተለያዩ የመዝናኛ ቦታዎች እና ታሪካዊ እና ጥንታዊ ግዳማት መግኛ ቦታ ናት። ባሕርዳር ከተማ የምትገኘዉ በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍል፣ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት፣ በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ከአዲስ አበባ በ 565 ኪሜ ርቀት ላይ ነው፡፡ አስትሮኖሚያዊ መገኛ ቦታዋ በ 11º 38’ በሰሜን ላቲቲውድ እና በ37º15’ ምስራቅ ሎንግቲውድ ነው፡፡ በአፈ ታሪክ እንደሚነገረው የባሕር-ዳር ስያሜን ያወጡት አፄ ሠርጸ ድንግል ሲሆኑ እሳቸውም ይሕን ታቦት የት እናስቀምጥ ተብለው በተጠየቁ ጊዜ \"ከባሕሩ-ዳር\" አድርጉ የተባሉ ሰወች ለመንደሩ ባሕር-ዳር ብለው ስያሜ አወጡለት ይባላል። ባሕር-ዳር ከተማ የተቆረቆረችው በ1915 ዓ.ም ነው ፡፡ ባሕር-ዳር በክልሉ ከሚገኙ የሪፎርም ከተሞች አንድዋ ስትሆን፤ የከተማ አስተዳደር፣ 3 ሜትሮፖሊታን ክ/ከተማዎች፣ የከተማ አገልግሎት ጽ/ቤት፣ 9 የከተማ ቀበሌዎችና 4 የገጠር ቀበሌዎች አሏት፡፡ ከተማዋ በ1998 ዓ.ም የተቀናጀ ልማት ፕላን አላት፡፡ የተቆረቆረችበትን ዓመት፣ የቆረቆሩትን ቀደምት ሠዎች፣ የሠፈሮችን ስሞች፣ ለባሕር-ዳር የተገጠሙትና የተዘፈኑ ታሪካዊ ግጥሞችና ስነ ቃሎች፣ ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከጎጆ ቤት ወደ አሁኑ ይዞታው አመጣጥ (ባሕር-ዳርን ስናስብ ጊዮርጊስን ሚካኤልን እና ገበያውን ከገበያው አካባቢ የነበረውን ፍርድ ቤት ነጣጥሎ ማየት አይቻልም የሚል አስተያየት ስላለ ነው)፣ ባሕር-ዳር እንደባሕር ዳርነቱ ከመቆርቆሩ በፊት በሚካኤል እና በሽመምብጥ ሠፈር አካባቢ ስለነበረው አሰፋፈር፣ ስለማዘጋጃቤቱ፣ ስለ አውቶቡስ ተራው፣ ስለ ድባነቄ ተራራ፣ እና ስለ መሳሉት፣ ስለፖሊቴክኒክ፣ ስለዓባይ ወንዝና ድልድዩ፣ ስለዓባይ ወንዝና ስለጣና ሐይቅ መገናኛ እና ስለሌሎችም ቁልፍ ነገሮችን ማቅረብ የሚችሉ አፈታሪኮች አሉ። \n \nጥያቄ: ባሕር ዳር ስንት ክፍለ ከተሞች አሏት?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 3 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአዳማ /ኢዜአ/መስከረም 23/2012 የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በ86 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ስምንት የምርምርና የልህቀት ማእከላት እያደራጀ መሆኑን ገለጸ። የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ተሾመ አብዶ ለኢዜአ እንደገለጹት ግንባታቸው ከ90 በመቶ በላይ የተጠናቀቀው የምርምር ፓርኮችንና የልህቀት ማዕከላትን በመሳሪያ ለማደራጀት 86 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በጀት ተመድቦ እየተሰራ ነው ብለዋል። በዚህም ሁለት ሊትል ስታር የተባሉ ሳተላይቶች በደቡብ ኮሪያና ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች በመገጣጠም ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የፋርማቲካል የልህቀት ማእከሉ የባህል መድኋኒቶችን በመቀመምና በምርምር በማዘጋጀት ወደ ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ምርት እንዲገቡ የሚያስችል መሆኑን የጠቀሱት ዶክተር ተሾመ በተለይም በባህላዊ መድኋኒቶች ዙሪያ በትኩረት የምርምር ሥራ ለማከናወን የሚያስችል ነው ብለዋል። የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ በ19 የትምህርት ፕሮግራሞች ከ6 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በመደበኛና በኤክስቴሽን ፕሮግራም ተቀብሎ ማስተማር ላይ ይገኛል። \n \nጥያቄ: የአዳማ ሳይንስ ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በስንት ትምህርት ፕሮግራሞች ተማሪዎችን እያስተማረ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ19 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአፄ ዘርአ ያዕቆብ አጼ ዘርአ ያዕቆብ በዘውድ ስማቸው ቆስጠንጥንዮስ ከአባታቸው ቀዳማዊ ዳዊት እና ከእናታቸው ንግስት ክብረ እግዚእ በ1399 እ.ኤ.አ. ከአዋሽ ወንዝ አጠቀብ ትገኝ በነበረው ትልቅ ተብላ በምትጠራው መንደር የድሮውፈተገር ክፍለ ሐገር ተወለዱ(ከቀኝ ያለውን ካርታ ይመልከቱ) ። የነገሡበትም ዘመን 1434 - 1468 እ.ኤ.አ. ነበር። ያረፉትም በደጋ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ ነው። የዘርዓ ያዕቆብ አባት ቀዳማዊ ዳዊት ባረፉ ጊዜ፣ እንደ ጥንቱ የኢትዮጵያ ባህል ወግ መሰረት፣ ታላቅ ወንድማቸው የነበሩት ቀዳማዊ ቴወድሮስ በ1414 ሲነግሱ ታናሽ ወንድማቸውን በግዞት ወደ አምባ ግሽን እንዲሄድ አደረጉ። አጼ ዘርዓ ያእቆብ ቆየት ብለው በጻፉት መጽሀፈ ብርሃን በተሰኘው ድርሰታቸው መሰረት እስከ ነገሱበት ሰኔ 20 ፣ 1434 ዓ.ም. ድረስ በግዞት ግሸን ተራራ (አምባ ግሸን) ላይ ለሚቀጥሉት 20 አመታት በእስር ኖሩ። ሆኖም ግን በግዞት እያሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ የደጋፊያቸው መጠን እየበዛ ሄደ። በነዚህ አመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ሁኔታ ከዓመት ወደ ዓመት እይተበላሸ ሂዶ በመጨረሻ ከአምባው ላይ ለሹመት ሲወርዱ አገሪቱ በእርስበርስ ሽኩቻ እየታመሰች፣ በሃይማኖት በኩልም መከፋፈል ተፈጥሮ የውጭ ሀይሎችም ከነገ ዛሬ አጠቁን እየተባለ ይሚፈራበት ሁኔታ ገጠመው። የወደፊቱ ንጉስ ብዙ እድሜውን ያሳለፈው ከሰው ተለይቶ አምባ ላይ ስለነበር፣ የዲፕሎማሲ ጥቅሙ አልተረዳውም ነበር። ይልቁኑ ፊት ለፊት የተጋረጡትን የሃገሪቱን ችግሮች በሚያስፈራ ድፍረት እና ምንም በማያወላዳ ጽናት ተጋፈጠው። ዓፄ ዘርአ ያእቆብ ንጉስ ከሆኑ በኋላ ንግስት እሌኒን በ1434 አገቡ፣ ከዚያም በ1436 ዘውዳቸውን ጫኑ። በ1442 በሰንበት ላይ ተነስቶ የነበረውን የቤተክርስቲያን ክፍፍል ለማብረድ ቢችሉም እስከ 1450 ነገሩ ሲሰክን ቆይቱ በደብረ ምጥማቅ ጉባኤ (ተጉለት) ፣ የግብጾቹ ጳጳሳተ በተገኙበት ችግሩን ሊፈቱ ችለዋል ። ሌላው በዘመናቸው የተከሰተው ሃይማኖታዊ ንቅናቄ የደቀ እስጢፋ ወገኖች እምነት ነው። እነዚህ እስጢፋኖስ የተባለ መነኩሴ ባስተማራቸው መሰረት ለመስቀል መስገድና ለስእል አድኅኖ ለድንግል ማርያም መስገድ አይገባም የሚሉ ነበሩ።ተከራክረው አጼ ዘርዓ ያዕቆብ አሸንፈዋል። በ1445 እና ከዚያ በኋላ በተነሱ ጦርነቶች ላይ በመሳተፍ ሁሉን በድል በማጠናቀው ግዛታቸውን ያሁኒቷን ሶማልያን ሁሉ ያቅፍ ነበር። በ1456 ዓ.ም አጼ ዘርዓ ያዕቆብ በነበሩበት ቦታ ታላቅ ብርሃን ስለታየ የነበሩበትን ቦታ ደብረ ብርሃን በማለት የሃገሪቱ ዋና ከተማ አድርገው ቆርቁረዋል። እስከ እለት ህልፈታቸውም ደብረ ብርሃን የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ነበረች።ኢትዮጵያዊ መንፈሳዊ ፈላስፋ። አጼ ዘርአ ያዕቆብ በጦር ውሎአቸው ብቻ ሳይሆን የሚታወቁት፣ ከ 20 በላይ መጻህፍትንም በመድረስና ለትውልድ በማቅረብ ጭምርም ነው። \n \nጥያቄ: አጼ ዘርአ ያዕቆብ ያረፉት በየት ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በደጋ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየፀሓይ አካል ለፍጹም ሉል የቀረበ ቅርጽ አለው፤ ዋልታዎቿን የሚያገናኘው ዳያሜትር ከወገቧ ዳያሜትር የሚያንሰው በ10 ኪሎ ሜትር ብቻ ነውና። ኮከባችን ፀሓይ በሥነ ፈለክ ሊቃውንት እጅግ ብዙ ጥናት ተደርጎባታል። ኾኖም ኮከቢቱን በተመለከተ ብዙ ጥያቄዎች ገና አልተመለሱም። ለምሳሌ በገሃድ የሚታየው የፀሓይ ገጽ ስኂን 6,000 ኬ (ኬልቪን) ኾኖ ሳለ፣ የዳርቻ ከባቢ አየሯ ስኂን ከሚሊዮን ኬ በላይ እንዴት ሊኾን እንደቻለ አይታወቅም። የፀሓይ ዕድሜ በአንዳንድ ሊቃውንት እሳቤ 4.6 ቢሊዮን ዓመት ገደማ ነውና በዕድሜ እኩሌታዋ ላይ የምትገኝ ኮከብ ተደርጋ ትታያለች። የኮከቢቱ መጠነ-ቁስ ጥንቅር 74% ሃይድሮጂን፣ 25% ሂሊየም ሲኾን፣ ቀሪው 1% ደግሞ ክብደት ያላቸው ርዝራዥ የብረቴ ንጥረ-ነገሮች ጥርቅም ነው። ስለ ፀሓይ የሰው ልጅ ቀዳሚ መሠረታዊ ግንዛቤ ብርሃን-ሰጭ ሰማያዊ ጻሕል መኾኗን፣ ደግሞም ከአድማስ በላይ እና በታች በመኾን ለመዓልትና ሌሊት መኖር ምክንያት መኾኗን መረዳት ነበር። በብዙ የቅድመ-ታሪክ እና የጥንት ዘመን ባህሎች ፀሓይ እንደ ብርሃናዊ አምላክ ወይም እንደ ዲበ-ተፈጥሯዊ ክሥተት ትታይ ነበር። የፀሓይ አምልኮ ለምሳሌ የ-ኢንካ (ደቡብ አሜሪካ) እና አዝቴክ (የዛሬዋ ሜክሲኮ) ጥንታዊ ሥልጣኔዎች ዐይነተኛ ገጽታ ነበር። ከፀሓያዊ ክሥትቶች ጋር የተያያዙ ብዙ ጥንታዊ ሐውልቶች ተገንብተው እንደነበር ለማሰብ የሐጋይ ሶልስቲስን ለማስታወቅ የተገነቡትን የድንጋይ ሜጋሊት በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል። ከችንክር ከዋክብት አንጻር ስትታይ ፀሓይ የግርዶሽ መስመርን ተከትላ በዞዲያክ ውስጥ በዓመት አንድ ዑደት የምታደርግ ትመስላለች። ስለዚህ በጥንት የግሪክ የሥነ-ከዋክብት ሊቃውንት ዘንድ ፀሓይ ታዋቂ ከነበሩ ሰባት ፈለኮች እንደ አንዱ ትቈጠር ነበር። በአንዳንድ ቋንቋዎች ሰባቱ የሳምንት ዕለታት በነዚህ ፈለኮች ይጠራሉ። \n \nጥያቄ: ከፀሀይ የመጠነ ቁስ ጥንቅር ነገሮች መካከል የሂሊየም መጠን ምን ያህል ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 25% ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nከ1936 ጀምሮ ኤርትራ የኢኮኖሚ እድገት ማሳየት ችሏል። በ30ዎቹ መጨረሻ 2፣198 የኢንደስትሪ ተቋሞች በአገሪቱ ተመስርተዋል። ይሁንና ጣሊያኖች አገሪቱ እራሷን እንድትችል ሳይሆን የነርሱ ጥገኛ እንድትሆን ነበር ያደረጉት፣ ለዚህ ሲሉ አብዛኛው ምርት ከውጭ ያስመጡ ነበር። ከ10-15% የሚሆነው የአገሬው ወንድ ሃይል በኢንደስትሪ፣ በእርሻና በጥቃቅን የተላላኪ ስራወች ተቀጥርው ይሰሩ ነበር። ከ1936-41 ድረስ አብዛኛውን የአግሬውን ወንድ ቀጥሮ ያሰራ የነበረው የቅኝ ገዥው ውትድርና ተቋም ነበር (40% ወይም 60፣000 ለአቅመ አዳም የደርሱ ወንዶችን)። እኒህ ወታደሮች ኢትዮጵያን ለመውረር ያገለገሉ ሲሆን ለዚህ ታማኝነታቸው ምክንያቱ ቅኝ ገዥወች በኤርትራ ላይ ያሰፈኑት ፖለቲካዊ መረጋጋት እንደምክንያት ይጠቀሳል። የጤና፣ የገበያ ኢኮኖሚ እንዲሁም ቁሳዊ ፍጆታ መስፋፋት በ1905ዓ.ም. 250 ሺህ ብቻ የነበረው የኤርትራ ህዝብ ወደ 614 ሺሕ በ1935 ዓ.ም. እንዲያድግ አድርጓል። ትግርኛ ተናጋሪው ክፍል በዚህ ጊዜ 54% የአገሪቱ ክፍል ነበር። እኒህ ለውጦች በአገሬው ላይ የስነ ልቦና ለውጥን አስከተሉ፣ ስለሆነም ከኢትዮጵያውያን ጐረቤቶቻቸው የተለዩ ህዝቦች የመሆን ማንነትን ፈጠረ። ሁለተኛው የአለም ጦርነትን ተከትሎ እንግሊዞች ከአንግሎ ግብጻዊ ሱዳን በመነሳት ጥር 1941 በኤርትራ ላይ ጥቃት አደረሱ። ከሶስት ወር በኋላ የከረን ጦርነትን በማሸነፍ ሚያዝያ 1941 ሙሉ ኤርትራን ተቆጣጠሩ። የእንግሊዝ ወታደራዊ አገዛዝ(BMA) በጣሊያኖች ምትክ አገሪቱን ማስተዳደር ጀመረ። 1947 ጣሊያን በፈረመችው የሰላም ውል መሰረት ኤርትራ ለአራቱ ሃይላት ተሰጠች። ከዚህ በኋላ ኤርትራ የጣሊያን ቅኝ መሆኗ አበቃላት። \n \nጥያቄ: በ1935 የኤርትራ ሕዝብ ብዛት ስንት ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 614 ሺሕ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ለወጣት ለአዛውንት የሚመቹ ደግ እናት፡፡ በኢትዮጵያ የሚድያ ታሪክ ስም ያተረፉ፡፡ ለምርምር የማይደክሙ፡፡ ተወዳጅ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን እነሆ ታሪካቸውን አቀረበ፡፡ ጋዜጠኛዋ በ79 አመታቸው ሀምሌ 14 2013 ህይወታቸው አልፏል፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ በ1934 አመተ ምህረት ከአባታቸው ከአቶ መኩሪያ ወልደስላሴ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ሶስና ወርቅነህ ተወለዱ፡፡ እናታቸው ወይዘሮ ሶስና ወርቅነህ የሀኪም ወርቅነህ እሸቴ ልጅ ናቸው፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ የአንደኛ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በሳንፎርድ ተማሪ ቤት ነበር የተከታተሉት፡፡ ወይዘሮ እሌኒ ያደጉት ካዛንቺስ አካባቢ ሲሆን የልጅነት ዘመናቸው በደስታ የተሞላ ነበር፡፡ በተለይ በሳንፎርድ ተማሪ ቤት ጥሩ የእንግሊዝኛ ችሎታቸውን ከማዳበራቸው በላይ ደስ የሚል የመዝናኛ ጊዜን አሳለፈው ነበር፡፡ ቴኒስ መጫወት ፤ ዋና መዋኘት ፣ ቴአትር ማየት እና መተወን ደስ ይላቸው ነበር፡፡ እንዲያውም ለልኡል መኮንን ሆስፒታል ማሰሪያ የገቢ ማሰባሰቢያ ላይ ቴአትር መስራታቸውን ወይዘሮ እሌኒ በህይወት በነበሩ ጊዜ ተናግረዋል፡፡ በተለይ አያታቸው ክቡር ሀኪም ወርቅነህ እሸቴ ዳንስ ያለማምዷቸው እንደነበር አይዘነጉትም፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ፣ ማህበራዊ ሳይንስ የማጥናት ግብ ቢኖራቸውም ቤሩት የነጻ የትምህርት እድል አግኝተው ወደዚያ በ1951 ግድም ያቀናሉ፡፡ ነገር ግን የነርስነትን ትምህርት ቢጀምሩም አቋርጠው ወደ እናት ሀገራቸው ይመለሳሉ፡፡ በመቀጠልም ወደ ብስራተ ወንጌል ሬድዮ በማቅናት በእንግሊዝኛው ክፍል ተቀጠሩ፡፡ ያኔ በሬድዮ ከወይዘሮ እሌኒ ጋር ይሰሩ ከነበሩት ባለሙያዎች መካከልም ጋዜጠኛ ልኡልሰገድ ኩምሳ ይጠቀሳል፡፡ ወይዘሮ እሌኒና ጋዜጠኛ ልኡልሰገድ ዜና ሲያቀርቡ ያለበት ቪድዮ ከዚህ ጽሁፍ አዘጋጅ ዘንድ ይገኛል፡፡ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ቻርተር በግንቦት 18 1955 ሲፈረም ጋዜጠኛ ከነበሩት መካከል ወይዘሮ እሌኒ ይጠቀሳሉ፡፡ በወቅቱ ገና የ21 አመት ወጣት የነበሩት ወይዘሮ እሌኒ መሪዎች ሲመጡ የተደረገውን ታሪካዊ አቀባበል በፍጹም አይዘነጉትም፡፡ \n \nጥያቄ: ወ/ሮ እሌኒ በስንት አመታቸው አረፉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ79 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በ84ኛው የየካቲት 12 ሰማዕታት መታሰቢያ ቀን ላይ በመገኘት የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የአባት አርበኞች ማህበር ፕሬዚዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን ተገኝተዋል። በሰመዕታት መታሰቢያ ቀን የካቲት 12 ቀን በየአመቱ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት፤አባት አርበኞች፤ እና የህብረተሰብ ክፍሉ በስድስት ኪሎ ታስቦ ይውላል፡፡ \n \nጥያቄ: በአዲስ አበባ ለ84ኛ ጊዜ የተከበረው የመቼ ሰማዕታት መታሰቢያ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የየካቲት 12 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአዶልፍ ሂትለር አዶልፍ ሂትለር (ጀርመንኛ Adolf Hitler አዶልፍ ሂትለ) እ.አ.አ. ከ1933 ጀምሮ የጀርመን ቻንስለር እንዲሁም ከ1934 ጀምሮ ደግሞ የጀርመን መሪም (Führer) ጭምር የነበረ ሰው ነው። ሂትለር በሚያዝያ 13 ቀን 1881 ዓ.ም. (20 አፕሪይል 1889 እ.ኤ.አ.) በዛሬይቷ ኦስትሪያ ተወለደ። በሚያዝያ 22 ቀን 1937 ዓ.ም. (30 አፕሪይል 1945 እ.ኤ.አ.) በርሊን ውስጥ ከአንድ ቀን በፊት ካገባት ሚስቱ ኤቫ ብራውን ጋር የራሱን ህይወት አጠፋ። በ1925 ዓ.ም. መጀመርያ የሂትለር ናዚ ወገን ከጓደኞቹ ወገን ጋር በራይክስታግ ምክር ቤት ትብብር መንግሥት ለመሥራት በቂ መንበሮች አልነበራቸውም። ተቃራኒዎቻቸው የኰሙኒስት ወገን 17% መንበሮች ስለ ነበራቸው የሂትለር ወገኖች የድምጽ ብዛት ሊያገኙ አልተቻላቸውም ነበር። በዚያው ዓመት ግን ከምርጫው ትንሽ በፊት የራይክስታግ ሕንጻ በእሳት ተቃጠለ። ይህ የኰሙኒስቶች ሥራ ነው ብለው የሂትለር ወገን ኰሙኒስት ፓርቲ ቶሎ እንዲከለከል አደረጉ። ስለዚህ ከምርጫው በኋላ የኰሙኒስትን መንበሮች ስለ አጡ የሂትለርም ወገኖች አሁን ከ50% መንበሮች በላይ ስላገኙ፣ የትብብር መንግሥት ሠሩና ወዲያው በድንጋጌ አቶ ሂትለር ባለሙሉ ሥልጣን አደረጉት። ሂትለር የጻፈው የርዮተ አለሙ ጽሑፍ «የኔ ትግል» (Mein Kampf) ሟርት ብቻ ነው። ለመጥቀስ ያህል፦ «ትኩረቴ ወደ አይሁዶች ስለ ተሳበ፣ ቪየናን ከበፊት በሌላ ብርሃን ለማየት ጀመርኩ። በሄድኩበት ሁሉ አይሁዶችን አየሁዋቸው፤ በብዛትም እያየኋቸው፣ ከሌሎች ሰዎች ፈጽሞ እንድለያቸው ጀመርኩ።»... «የግዛቱ (ኦስትሪያ-ሀንጋሪ) ዋና ከተማ የከሠተውን የዘሮች ውሑድ ጠላሁት፤ የዚህን ሁሉ የቼኮች፣ ፖሎች፣ ሀንጋርዮች፣ ሩጤኖች፣ ሰርቦች፣ ክሮዋቶች ወዘተ. የዘሮች ድብልቀት፤ በሁላቸውም መካከል፣ እንደ ሰው ልጅ መከፋፈል ሻገቶ፣ አይሁዶችና ተጨማሪ አይሁዶች።» በነበረው ዘረኛ አስተዳደሩ 6 ሚሊዮን የአውሮፓ አይሁዶችን እና 5 ሚሊዮን ሌሎች የተለያዩ ሀገራት ህዝቦችን (በተለይም ስላቮችን) በገፍ (በሆሎኮስት) አስጨርሷል። በሂትለር ሥር የናዚዎች ፍልስፍና በሂንዱኢዝም እንደሚገኘው በዘር የተከፋፈለ ካስት ሲስተም መመሥረት አይነተኛ ነበር። «አርያኖች» የተባሉት ዘሮች በተለይም የጀርመናውያን ብሔሮች ከሁሉ ላዕላይነት እንዲገኙ አሠቡ። ይህ ዝብረት የተነሣ በርግ ቬዳ ዘንድ በ1500 ዓክልበ. ያህል ወደ ሕንድ የወረሩት ነገዶች «አርያን» ስለ ተባሉ ነው፤ በጥንትም «አሪያና» የአፍጋኒስታን አካባቢ ስም የዘመናዊው ኢራንም ሞክሼ ነበር። በናዚዎቹ እንደ ተዛበው ግን ታሪካዊ ባይሆንም የ«አርያኖች» ትርጓሜ ጀርመናውያን ብቻ ነበሩ፤ ስላቮች (በተለይ የሩስያና የፖሎኝ ሕዝቦች) ግን አርያኖች ሳይሆኑ እንደ ዝቅተኞች ተቆጠሩ። የሂትለር እብደት እየተራመደ በ1926 ዓም የሀንጋሪ ሕዝብ ደግሞ «አርያኖች» ተደረጉ፣ በ1928 ዓም የጃፓን ሕዝብ እንኳን በይፋ «አርያኖች» ተደረጉ፤ በ1934 ዓም የፊንላንድ ሕዝብ ወደ «አርያኖች» በሂትለር ዐዋጅ ተጨመሩ። በሙሶሊኒ ሥር የፋሺስት ጣልያኖች እኛም አርያኖች ነን ቢሉም ጣልያኖች አርያን መሆናቸው በናዚዎች ዘንድ መቸም አልተቀበለም ነበር። \n \nጥያቄ: የአዶልፍ ሂትለር መንግሥት የጃፓን ሕዝቦችን መቼ ነበር እንደ አርያኖች ዘር የቆጠረው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ1928 ዓም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቶክ ፒሲን ቶክ ፒሲን (Tok Pisin) በስሜን ፓፑዋ ኒው ግኒ የሚናገር የእንግሊዝኛ ቋንቋ ዲቃላ ነው። ከእንግሊዝኛ ስዋሰው በጣም ተለውጧልና ዛሬ እንደ ራሱ ቋንቋ ይቆጠራል። የፓፑዋ ኒው ግኒ መደበኛ ቋንቋ ሆኖ በ120,000 ያሕል ተናጋሪዎችና በ4 ሚሊዮን እንደ 2ኛ ቋንቋ ይነገራል። የቶክ ፒሲን አጀማመር በፓሲፊክ ውቅያኖስ ደሴቶች ላይ የሚኖሩ የተላያዩም ልሣናት የሚችሉ ሰራተኞች አንድላይ ለአትክልት ስፍራዎች ሲሰሩ ነበር። ብዙ ጊዜ የእነዚህ ሰራተኞች የጋራ ቋንቋ ጥቂት ቀላል እንግሊዝኛ ቃሎች ብቻ ነበር። ስለዚህ አዲስ \"የቋንቋ ዲቃላ\" ተወለደ። ከእንግሊዝኛ ብቻ ሳይሆን ብዙ ቃላት የተወሰዱ ከደሴተኞቹ ቋንቋዎች፣ ከጀርመንኛ፣ ወይም ከፖርቱጊዝ ነበር። ይህ ቋንቋ \"ፕጅን\" ተብሎ አሁን ሶስት ተወላጆች አሉት፣ እነሱም ቢስላማ (በቫኑዋቱ) ፒጂን (በሰሎሞን ደሴቶች) እና ቶክ ፒሲን ይባላሉ። ቶክ ፒሲን በአንዳንድ ትምህርት ቤት የትምህርት ቋንቋ ነው። \n \nጥያቄ: የቶክ ፒሲን አጀማመር በየትኛው ውቅያኖስ ላይ ባሉ ደሴቶች የነበሩ ሰዎች ነበሩ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በፓሲፊክ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቦሌ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ በአዲስ አበባ ከተማ በደቡብ-ምሥራቅ አቅጣጫ ከአራዳ በስምንት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ የአገሪቱ ዋና አድማሳዊ የንግድና የግንኙነት በር ነው። አውሮፕላን ወደ ኢትዮጵያ መግባት የጀመሩት በንግሥት ዘውዲቱ ዘመን ሲሆን በአዲስ አበባ ዙሪያ በጃን ሜዳ እና አቃቂ ያርፉ እንደነበር በታሪክ ተዘግቧል። የመጀመሪያው ቋሚ የአውሮፕላን ጣቢያ ግን የተሠራው በአምሥቱ የፋሺስት ዘመናት ሲሆን የካቲት ፳፬ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ/ም አክሱም አካባቢ ላይ ከነጥያራው ተከስክሶ በሞተው አብራሪያቸው፣ “ኢቮ ኦሊቬቲ” ስም ሠይመውት የነበረው የልደታ የጥያራ ጣቢያ ነው። በዚሁ በፋሺስት ወረራ ዘመን ‘አላ ሊቶሪያ’ የተሰኘው ኩባንያ በአገር ውስጥ ከአዲስ አበባ ተነስቶ ነገሌን፤ ሞቃዲሾን፤ ድሬ ዳዋን፤ ጎራኄን፤ ጂቡቲን፤ አሰብን፤ ጂማን፣ ጋምቤላን ደምቢ ዶሎን፤ ጎንደርን አስመራን፤ ደሴን፤ ለቀምትን እና አሶሳን የሚያገለግሉ የበረራ መሥመሮች ሲኖረው ከአድማስ ባሻገር ደግሞ ከተማዋን በካርቱም፣ ዋዲ ሃይፋ፤ ካይሮ፣ ቤንጋዚ እና ሲራኩሳ አድርጎ ከሮማ ጋር የሚያገናኝ የበረራ መሥመርም ነበረው። ከድል ወዲህ ልደታ አውሮፕላን ጣቢያ፤ የብሪታኒያ ጦር ኃይሎች ሲገለገሉበት ከቆየ በኋላ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ታኅሣሥ ፳፩ ቀን ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ሲመሠረት ዋና ጣቢያው እዚያው ነበር። ዳሩ ግን የአየር መንገዱ አገልግሎት እየተስፋፋ ሲመጣና ትላልቅ ጄት አውሮፕላኖች እንደሚያስፈልጉት ግልጽ ሲሆን፣ የልደታ አየር ጣቢያ ብቃት እንደሌለው እና ለጄት አየር ዠበቦችም ማሳረፊያ የማይስማማ መሆኑ ታምኖበት የአማራጭ ሥፍራ ፍለጋ ተጀመረ። የአዲሱንም አየር ጣቢያ ዝርዝር ጥናት እንዲያዘጋጅ ውሉ ለአሜሪካዊው ‘አማን እና ዊትኒ’ ኩባንያ ተሰጥቶ፤ ጥናቱ በ፲፱፻፶ ዓ/ም ተገባዶ አማራጩ ሥፍራ ቦሌ እንዲሆን ተወሰነ። የአየር ጣቢያውን የግንባታ ወጪ ከአሜሪካዊው ‘ኤክስፖርት-ኢምፖርት’ ባንክ በተገኘ ብድር ተሸፍኖ ሥራው ተጀመረ። ጠቅላላ ግንባታው ተጠናቆ ሲያልቅ ኅዳር ፲፩ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ/ም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተብሎ፣ በንጉሠ ነገሥቱ ተመርቆ ተከፈተ። \n \nጥያቄ: ቦሌ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ከምን ቦታ በስምንት ኪሎሜትር ርቀት ላይ ይገኛል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከአራዳ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጋና ጋና በአፍሪካ አትላንቲክ ጠረፍ ላይ የተገኘ አገር ሲሆን ከ24 ሚሊዮን ኗሪዎች በላይ አሉት። የጋና ስራ ቋንቋ እንግሊዝኛ ሲሆን፣ ሌሎች ኗሪ ቋንቋዎች በተለይም ትዊኛ (አካንኛ) በሰፊ ይነገራሉ። የ«ጋና» ስያሜ በታሪክ የድሮ «ጋና መንግሥት» ወይም «ዋጋዱጉ መንግሥት» ለማክበር በ1949 ዓም ተመረጠ። እንዲያውም ያው መንግሥት እስከ 1068 ዓም ድረስ ከጋና ወደ ስሜን-ምዕራብ በአሁኑ ማሊ ይገኝ ነበር እንጂ የዛሬውን ጋና መቸም አልገዛም። «ጋና» በትክክል የዋጋዱጉ መንግሥት አለቆች ማዕረግ ሆኖ ነበር። ዋጋዱጉ መንግሥት በ1068 ዓም ግድም ከወደቀ ቀጥሎ፣ የአካን ብሔሮች ከዚያው ፈልሰው በዛሬው ጋና ሠፈሩና መጀመርያ ግዛቶችን መሠረቱ። ከ1662 እስከ 1949 ዓም ድረስ የአሻንቲ መንግሥት ባካባቢው ቆየ፤ በ1894 ዓም ይህ የብሪታንያ አሻንቲ ጥብቅ ግዛት ሆነ። ከ1949 ዓም አስቀድሞ የዩናይትድ ኪንግደም ጥገኛ ግዛት ሲሆን በወርቅ ሀብቱ ምክንያት «የወርቅ ጠረፍ ጥገኛ ግዛት» (ጎልድ ኮስት ፕሮቴክቶሬት) በመባል ይታወቅ ነበር። ከ1984 ዓም ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ እና ፓርላሜንታዊ መንግሥት ኖሮታል። አብዛኞቹ ኗሪዎች (70%) በተለይ በደቡቡ ክርስቲያን ሲሆኑ፣ በተለይ በስሜኑ 16% የእስልምና ተከታዮች ናቸው። የተረፉትም የኗሪ አረመኔነትን እምነቶች ይከተላሉ። የጋና ዋና ምርቶች ካካዎ፣ ዘይት፣ አልማዝ ናቸው። በአለሙ ከሁሉ ትልቅ የሆነው ሠው ሰራሽ ሐይቅ፣ ቮልታ ሐይቅ፣ በጋና ይገኛል። እግር ኳስ ከሁሉ የተወደደው እስፖርት ነው። የጋና አበሳሰል በተለይ በኮቤ፣ ጐርጠብ፣ የስኳር ድንች፣ ባቄላ፣ በቆሎ፣ ኦቾሎኒ፣ ባሚያና ሩዝ ይሠራል። \n \nጥያቄ: በጋና ከ1662 እስከ 1949 ዓም የቆየው መንግሥት ምን ተብሎ ይጠራ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የአሻንቲ መንግሥት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቅዱስ ባስሊዮስ ዘቄሣርያ ባስሊዮስ ዘቄሣርያ በሌላ አጠራሩ ታላቁ ቅዱስ ባስሊዮስ በቀጰዶቂያ የቄሣርያ ኤጲስ ቆጶስ ነበር። የንቂያን የሊቃውንት ጉባዔ የሚደግፍና አርያኒዝምንና የአፖሊናረስን ተከታዮችን የክርስትና አመለካከት ተቃውሞ ትክክለኛውን መንገድ ያስተማረ ታላቅ አሳማኝ የሃይማኖት ፈላስፋና መሪ ነበር ። ቅዱስ ባስሊዮስ ከሃይማኖት ፈላስፋነቱ ሌላ ድሆችንና ኑሮን ማሸነፍ ያቃታቸውን በመንከባከብ ይታወቃል ። በተጨማሪም የማኅበራዊ ኑሮ ፣ የሥርዐተ ጸሎትና የጉልበት ሥራ ለገዳማዊ ኑሮ መመሪያን መሥርቷል። ባስሊዮስ ከቅዱስ ጳኩሚስ ጋር የማኅበራዊ ገዳማዊነት አባት ተብሎ በምሥራቃዊ ክርስትና ይታሰባል ። ዳሮግን በምሥራቅም በምዕራብም በቅዱስ ደረጃ ነው የሚከበረው ። እነዚህ ሁለት ጎራዎች ታላቅ የቤተክርስቲያን አባት የሚለውን ስያሜ ከዮሐንስ አፍወርቅና ከግሬጎሪዮ ናዚያንዘስ ጋር ሰተውታል። ባስሊዮስ ከቀዳማዊ ባስሊዮስና ከኤሚልያ የቄሣሪያዋ በ፫፻፳ ዓም አካባቢ በቀጰዶቂያ ተወለደ ። እናትና አባቱ እግዚአአብሔርን በጣም የሚወዱና ጸሎተኞች የነበሩ ሰዎች ነበሩ ። የእናቱ አባት ከቆስጠጢኖስ ፩ኛ በክርስትና ማመን በፊት ሰማዕት ሆኖ ያለፈ ሰው ነበረ። ጸሎተኛ ባልቴቱ ማክሪናም የጎርጎርዮስ ታውማታርገስ (የኒዎ ቄሣርያን ቤተክርስቲያን በአቅራቢያው የመሠረተ) ተከታይ የነበረች ባስሊዎስንና አራቱን ወንድሞቹንና እህቱን ፣ ወጣትዋ ማክሪና ፣ ናውክራቲየስ ፣ ጴጥሮስ የሰባስቴውንና ፣ ጎርጎርዮስ የኒሳውን (ወደፊት ታላቅና የተከበሩ ቅዱሳን የሚሆኑ) በክርስትና ሃይማኖት ሥርዐት አሳደገች ። ባስሊዮስ በቄሣርያ ማዛካ ቀጰዶቂያ በአሁኑ ዘመን አጠራር ካይዜሪ (ቱርክ) ትምህርት ቤት በ፫፻፵፪ ፵፫ ዓ.ም.አካባቢ ተምሩዋል ። እዛም ጎርጎርዮስ ናዚያንዘስን የረጅም ጊዜ ጉዋደኛ የሚሆነውን ተዋውቋል። ባስሊዮስና ጎርጎርዮስ አንድላይ በመሆን ለከፍተኛ ትምህርትና በተጨማሪ የሊባኒየስን ትምህርታዊ ንግግር ለማጥናት ወደ ቁስጥጥኒያ አምርተዋል ። ሁለቱ በአቴንስ በ፫፵፪ ዓ.ም. አካባቢ ጀምሮ ለስድስት ዓመት ተቀምጠዋል። በዛም ቆይታቸው ጁሊያን ዘአፖስቴት ወደፊት ንጉሥ የሚሆን ተማሪ ተዋውቀዋል። ባስሊዮስ አቴንስን በ፫፵፰ ለቆ ወደ ግብፅና ሶርያ ከተጉዋዘ በኋላ አገሩ ቄሣርያ የሕግ ሥራ በመለማመድና የንግግር ችሎታ ሲያስተምር ቆየ። \n \nጥያቄ: የቅዱስ ባስሊዮስ ዘቄሣርያ ጋደኛ ማን ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ጎርጎርዮስ ናዚያንዘስን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nመጋቢት ፪ ፲፰፻፷፰ ዓ/ም - አሌክሳንደር ግራሃም ቤል ለመጀመሪያ ጊዜ በስልክ ረዳቱን አነጋገረ። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በልሚ ወቼ ሞሹ የኢትዮጵያ አርበኞችና የፋሺስት ኢጣሊያ ወገኖች ጦር ውጊያ ፲፱፻፴፫ ዓ/ም - ከኮንጎ የመጣ የቤልጅግ ሠራዊት የጣልያንን ሠራዊት አሸንፎ ፩ሺ፭፻ ወታደሮች በመማረክ አሶሳን ያዘ። ፲፱፻፵፱ ዓ/ም - የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት (በኋላ ፕሬዚዳንት) ሪቻርድ ኒክሰን ኢትዮጵያን ጎበኙ ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - ኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበራቸውን የሚወስን የጋራ ጉባዔ ለመመሥረት መወሰናቸውን አስታወቁ። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኢትዮጵያ ርዕሰ ከተማ፣ አራት ኪሎ ላይ በሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ተማሪዎችን ፖሊሶች በጢስ ቦምብ እና በዱላ በታተኑ። ተማሪዎቹ የጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድን የአሻንጉልት ምስል አቃጠሉ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮት ሽብር የአየር በረራ አስተዳደር ሠራተኞች አድማ ተጀመረ። አድማው እስከ መጋቢት ፳፫ ቀን ድረስ ተካሂዷል። ፲፱፻፹፪ ዓ/ም - ሊትዌኒያ እራሷን ከሶቭየት ኅብረት አስተዳደር ውጭ ነጻ መሆኗን አወጀች። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - ፔኒሲሊንን ያገኘው የብሪታኒያ ተወላጁ አሌክሳንደር ፍሌሚንግ በልብ ምታት አረፈ። \n \nጥያቄ: ከኮንጎ የመጣ የቤልጅግ ሠራዊት የጣልያንን ሠራዊት አሸንፎ ፩ሺ፭፻ ወታደሮች በመማረክ አሶሳን የያዘው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ፲፱፻፴፫ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን የዓለም አቀፍ የአስትሮኖሚካል ኅብረት ሲምፖዚየም ልታካሂድ መሆኑን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ገለፀ። ዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ኅብረት ሲምፖዚየምና የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማኅበር የምክክር መድረክ ከመስከረም 26-30 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ይህን አስመልክቶ በተሰጠው መግለጫ እንደተብራራው በሁለቱ መድረኮች ከ30 አገራት ከ200 በላይ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶች፣ ኢትዮጵያዊያን ተመራማሪዎችና ባለድርሻ ተቋማት ስለ አስትሮኖሚና ስፔስ ሳይንስ ይመክራሉ። በኢንስቲትዩቱ የአስትሮኖሚና አስትሮፊዚክስ ምርምር ክፍል ኃላፊ ዶክተር ማሪያና ፖቪች እንዳሉት በዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ኅብረት በተለያዩ አገራት በየዓመቱ የሚዘጋጁ ሲምፖዚየሞች አሉ። ኅብረቱ መቶኛ ዓመቱን እያከበረ ይህንንም ክብረ በዓል ያከናወናቸውን ስራዎችና ስኬቶች እየገመገመ በተለያዩ ሁነቶች እያከበረ ነው። እስካሁን 355 ሲምፖዚየሞች የተካሄዱ ሲሆን በኢትዮጵያ ብሎም በምስራቅ አፍሪካ ሲካሄድ የመጀመሪያው መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ሲምፖዚየሙን የምታካሂድ ሶስተኛዋ የአፍሪካ አገር ስትሆን በደቡብ አፍሪካና ቡርኪናፋሶ መሰል ሲምፖዚየም ተካሂዷል። ሲምፖዚየሙ በዘርፉ ልምድና እውቀት ያካበቱ ተመራማሪዎች ልምዳቸውን የሚያጋሩበትና ኢትዮጵያ ብሎም አፍሪካ በሳይንስ ዘርፍ እየከወኗቸው ያሉ ተግባራትን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስገንዘብ የሚያስችል ነው ብለዋል። የምስራቅ አፍሪካ አስትሮኖሚ ለልማት ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ዳይሬክተር አቶ አለምዬ ማሞ በበኩላቸው እንደገለጹት የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማኅበር የሚያዘጋጀው የአፍሪካ አስትሮኖሚ የሳይንስ ምክክር መድረክ መስከረም 29 እና 30 ቀን 2012 ዓ.ም ይካሄዳል። መድረኩ በአፍሪካ አስትሮኖሚ ምን አይነት አስተዋፅኦ ማበርከት እንደሚችል የሚያመላክት ራዕይና ስትራቴጂ ሰነድ የሚነደፍበት ይሆናል ነው ያሉት። የማኅበሩን እንቅስቃሴ ለሳይንስና ለጠቅላላ ማኅበረሰቡ ማስተዋወቅ፣ የአህጉሪቱ ወጣት ተመራማሪዎች ነፃ የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ማስቻል፣ በአፍሪካ በአስትሮኖሚና ስፔስ ሳይንስ ዘርፍ የሚሰሩ ሳይንሳዊ ምርምሮችን ማጎልበት የመድረኩ ዓላማዎች መሆናቸውን አንስተዋል። መድረኩ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ትብብርና ትስስር መፍጠር ያስችላልም ነው ያሉት። ነገና ከነገ በስቲያ አራት ኪሎ በሚገኘው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ካምፓስ በዘርፉ ሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪያቸውን እየሰሩ ላሉ ተማሪዎች የእውቀትና ክህሎት ስልጠናም ይሰጣል። ከሁለቱ መድረኮች ጎን ለጎን በተመረጡ 10 የህዝብ ትምህርት ቤቶች በተግባር የታገዘ አስትሮኖሚን የማስገንዘብ ስራ እንደሚሰራም ተገልጿል። ለበርካታ የማኅበረሰብ ክፍሎች ስለ አስትሮኖሚ ሳይንስ ግንዛቤ የመፍጠር እንዲሁም ለሁለተኛ ደረጃ መምህራን የሚሰጥ ስልጠና መኖሩም ተጠቁሟል።     \n \nጥያቄ: በአዲስ አባባ ዩኒቨርስቲ አራት ኪሎ ካምፓስ ለሚገኙ ስንተኛ ዲግሪ ተማሪዎች ነው ስልጠና ለመስጠት የታሰበው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሁለተኛና ሶስተኛ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: የኢያን ስሚዝ መንግሥት በዚምባቡዌ ከሦስት መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ የተፈራረመው ስምምነት መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በማርች 1978 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአብዱልራዛቅ እ.ኤ.አ. በ1994 ላይ ያሳተሙት ‹ፓራዳይዝ› የተሰኘው ልብ ወለድ ታንዛኒያ ውስጥ በ20ኛው ምዕት ዓመት የልጅ አስተዳደግ ምን እንደሚመስል ፍንትው አድርገው ያሳዩበት ነው። በዚህ ልብ ወለድም ዓለም አቀፉን የ‹ቡከር› ሽልማት ለማግኘት መቻላቸውን ቢቢሲ ዘግቦታል፡፡ እንደ የኖቤል ኮሚቴ የሥነ ጽሑፍ ክፍል አገላለጽም፣ ‹‹[የእሳቸው] ገጸ ባህርያት ሁሌም ቢሆን በባህልና አኅጉራት መካከል የሚሽከረከሩ፣ በአሁን ሕይወትና በመጪው ሕይወት መካከል የሚመላለሱ ናቸው። በቀላሉ ሊያልፉት የማይችሉት ከባድ እውነታ ውስጥ ናቸው፡፡›› እ.ኤ.አ. በ1948 በዛንዚባር የተወለዱት አብዱልራዛቅ፣ እ.ኤ.አ. በ1960ዎቹ መገባደጃ አገረ እንግሊዝ የገቡት ስደተኛ ሆነው ነው። በቅርቡ ጡረታ እስከወጡበት ዕለት ድረስ በካንተርበሪው የኬንት ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዝኛና የድኅረ ቅኝ ግዛት ሥነ ጽሑፎች ፕሮፌሰር ነበሩ። ሽልማቱ፣ ደራሲው ያለፉበትን የስደተኞች ቀውስንና ቅኝ አገዛዝን በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ውይይት እንዲደረግባቸው ያስችላል ብለዋል፡፡ ‹‹እነዚህ በየዕለቱ ከእኛ ዘንድ ያሉ ነገሮች ናቸው። ሰዎች እየሞቱ ነው፣ ሰዎች በዓለም ዙርያ አሁንም እየተጎዱ ነው፡፡ በእነዚህን ጉዳዮች ላይ በፍፁም ቀናነትና አስተውሎት መንገድ መነጋገር መላ መምታት አለብን፤›› ብለዋል የኖቤል ተሸላሚው አብዱልራዛቅ። ዓምና በሥነ ጽሑፍ ያሸነፉት አሜሪካዊው ገጣሚ ሊዊስ ግሉክ መሆናቸው ይታወሳል። የስዊድኑ አካዴሚ በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት ከሸለማቸው ታላላቅ ደራስያን መካከል ከአፍሪካ አኅጉር ስድስት ደራስያን ይገኙበታል፡፡ እነርሱም ዎሌ ሾንካ (ናይጀሪያ)፣ ነጂብ ማኅፉዝ (ግብፅ)፣ ናዲን ጎርዲመር (ደቡብ አፍሪካ)፣ ጄ.ኤም ኮትዚ (ደቡብ አፍሪካ)፣ እና ዶሪስ ሌሲንግ (ዚምባቡዌ -እንግሊዝ) ይገኙበታል፡፡ \n \nጥያቄ: አብዱልራዛቅ የየት ዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰር ነበሩ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በካንተርበሪው የኬንት ዩኒቨርሲቲ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቴክኖ ካሞን 17 በዘጋቢ ፊልም ታግዞ ወደ ገበያ መግባቱን ኩባንያው አስታወቀ :: በዓለም አቀፍ ደረጃ በአዲሱ ትውልድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈው ቴክኖ ሞባይል ግንቦት 4 ቀን 2013 ዓ.ም በለቀቀው አዲሱ የCAMON 17 ተከታታይ ስልክ የብዙዎችን ቀልብ መሳብ መቻሉን ኩባንያው አስታውቋል:: ይህ ፈጠራ የታከለበት ቴክኖ ካሞን 17 ስልክ ማጠንጠኛውን በሰልፊ ላይ ባደረገ ዘጋቢ ፊልም የተመረቀ ሲሆን ድርጅቱ ምርቱን ከማስተዋወቅ ባለፈ በኢንዱስትሪ፣ በማኅበራዊና በሰብዓዊነት ዘርፎች ላይ የበለጠ ጥረት ለማድረግ ያለውን ፍላጎት የሚያንጸባርቅ ነው ተብሏል:: “The Rise of Selfie” በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ይህ ዘጋቢ ፊልም ፊልም በማስመረቂያ ፕሮግራሙ ላይ የቀረበ ሲሆን ታዳሚዎቹ በእርግጥም ቴክኖ የዚህን ትውልድ ፍላጎት ለማሟላት በተጨባጭ እና በስሜት እየሰራ መሆኑን ስለመገንዘባቸው ድርጅቱ ገልጿል:: አዲሱ የቴክኖ የንግድ አምባሳደር ክሪስ ኢቫንስ “ሕያው እና በስሜት የተሞላ ምስል ትፈልጉ ይሆናል፣ ነገር ግን መልካም ምስል የሚያደርገው ‘እጅግ ግለሰባዊ’ ስለሆነ ነው። ይህ ደግሞ ሁሌም ቴክኖ በፅኑ ከሚያምንበት እና ከሚታወቅበት ሃሳብ ጋር ይጣጣማል ብለዋል፡፡ የስማርት ስልክ ፅንሰ ሃሳብ ብራንዱ ላይ ሳይሆን ተጠቃሚው ላይ ማውጠንጠን እንዳለበትም ነው የንግድ አምባሳደሯ የጠቆሙት፡፡ የፋሽን ሞዴል የሆኑት ሣራ በፊልሙ ላይ እንዳሉት እንደ ቴክኖ ካሞን 17 ያሉ የሰልፊ ስልኮች ተጠቃሚዎች የራሳቸውን ምስል ለመቆጣጠር የሚያስችላቸውን ተወዳጅ ፎቶዎችን በማንሳት ምስላቸውን እንዲቆጣጠሩ ያስችላቸዋል:: በተጨማሪም የተሻለ ማንነት እንዲኖር ለማድረግ እዲሁም በደመነብስ ወደተሻለ እኛነት እንድንመጣ ለራሳችን የምንጠቁምበት መንገድ ነው ብለዋል:: ቴክኖ ካሞን 17 ሁልጊዜ “በልባቸው ወጣት” ለሆኑ እና ለአዳዲስ ነገሮች ራሳቸውን ለሚያነሳሱ ተጠቃሚዎች ምልክት ለመሆን የተሰራ ነው ያለው ድርጅቱ፥ ሰዎች ራሳቸውን በይበልጥ ለመግለጽ እንዲችሉ ያስችላቸዋልም ብሏል፡፡ ኮቪድ19 ባስከተለው ተጽዕኖ ሰዎች ከሚወዷቸው ሰዎች ጋር ለመገናኘት ሰልፊን ማዘውተራቸው የሰልፊን ተግባር ይበልጥ አስፈላጊ ያደረገው በመሆኑ ጉዳዩን ቴክኖ እና ሌሎች የስልክ አምራቾች በአጽንኦት እንዲያጤኑት አድርጓቸዋል:: በቴክኖ ካሞን 17 ስልክ ሰዎች ህይወት ያላቸው የሚመስሉ ፎቶዎችን ማጣጣም ብቻ ሳይሆን በFHD ስክሪን ላይ በጣም ግልጽ የሆነ ምስልን ማየት እንደሚያስችላቸው ነው የተገለጸው:: ይህ ከፍተኛ ጥራት ያለው ስክሪን ተጠቃሚዎች በቪዲዮ ጥሪዎች ላይ በሚሆኑበት ጊዜ ተወዳዳሪ የሌለው ግልጽነት የሚሰጣቸው ሲሆን ተጠቃሚዎች ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን ተንቀሳቃሽ ምስሎችን መመልከት እና ከፍተኛ አቅም የሚፈልጉ ጌሞችን መጫወት እንደሚችሉም ነው ኩባንያው የገለጸው፡፡ ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!   \n \nጥያቄ: ቴክኖ ካሞን 17 የተባለው አዲሱ የቴክኖ ኩባንያ ስልክ መቼ ለገበያ ቀረበ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ግንቦት 4 ቀን 2013 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአሜሪካ ለሁዋዌ ተጨማሪ ሽያጮችን ልታግድ መሆኑን አስታወቀች። አሜሪካ የምታመርታቸውን ጨምሮ በተለያዩ ሃገራት የተመረቱ የቴሌኮም ምርቶችን ለግዙፉ የቻይና የቴክኖሎጅ ኩባንያ እንዳይሸጡ ለማገድ ስለመዘጋጀቷም ነው የገለጸችው። የትራምፕ አስተዳደር ሁዋዌ የሃገሪቱን ደህንነት ስጋት ላይ ይጥላል በሚል ኩባንያው ላይ ጫና እያሳደረ ነው። የአሜሪካ ግምጃ ቤት ባለፈው አመት ሰኔ ወር ላይ ኩባንያውን በጥቁር መዝገብ አስፍሮት እንደነበር ይታወሳል። አሁን ላይም ለኩባንያው ከአሜሪካም ሆነ ከሌሎች ሃገራት የሚጓጓዙ የቴክኖሎጅ ቁሳቁሶች ላይ ገደብ መጣል የሚያስችል ረቂቅ እየተዘጋጀ መሆኑንም ገልጻለች። የአሜሪካ ግምጃ ቤት አሁን ባለው ህግ የአሜሪካ የቴክኖሎጅ ምርቶች ከፍ ያለውን ዋጋ ከያዙ ወደ ቻይና የሚላኩ የሌሎች ሃገራትን የቴክኖሎጅ ምርቶች የማገድ ወይም የማስገቢያ ፈቃድ መጠየቅ ይችላል። አሜሪካ ባለፈው ዓመት በደህንነት ስጋት ምክንያት ለሁዋዌ እና 68 ተዛማጅ ኩባንያዎች የቴክኖሎጂና ሌሎች መሳሪያዎችን እንዳይሸጡ ገደብ መጣሏ የሚታወስ ነው። አሜሪካ የቻይና የቴክኖሎጅ ኩባንያዎችን አገልግሎት መጠቀም ሊያስከትል የሚችለውን የደህንነት ስጋት የሚያሳይ ማስረጃ በማቅረብ በተለይም ምዕራባውያን አጋሮቿ እንዳይጠቀሙ እየወተወተች ትገኛለች። ምንጭ፦ አልጀዚራ \n \nጥያቄ: የአሜሪካ ግምጃ ቤት ባለፈው አመት ሰኔ ወር ላይ በጥቁር መዝገብ የያዘው የቻይና ኩባንያ ስሙ ማን ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሁዋዌ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጎፋ የጎፋ ብሔረሰብ ቋንቋ ‹ጎፍኛ› ሲሆን፣ ቋንቋው ከማዕከላዊ ኦማዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ ይመደባል። በ1999 ዓ.ም በተደረገው የሕዝብና ቤቶች ቆጠራ ውጤት የብሔረሰቡ ሕዝብ ብዛት 363ሺ9 ነው፡፡ የጎፋ ብሔረሰብ በጋሞጎፋ ዞን ውስጥ ከሚገኙ ብሔረሰቦች መካከል አንዱ ሲሆን፣ ብሔረሰቡ በዋናነነት በጎፋ ዙሪያ፣ ዛላ፣ ዑባ፣ ደብረፀሐይ እና መሎካዛ በሚባሉ ወረዳዎች ይገኛል፡፡ የብሔረሰቡ ዋና የሀብት መሠረት ጥምር ግብርና ሲሆን፤ የገቢ ምንጭ በሚያስገኙ ምርቶች ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ የጎፋ ብሔረሰብ የራሱ የሆነ ነባር ባህላዊ አስተዳደር አለው፡፡ ጥንት በጎፋ ግዛት ክልል ሥር የነበሩ አካባቢዎች በሰባት የካዎ (ነጉሥ) ግዛቶች ተከፋፍለው የተደራደሩ ነበሩ፡፡ እያንዳንዱ ከአዎ የአስተዳደር ማዕከል ቤተ-መንግሥት(ጋዶ) ነበረው፡፡ ማዕከላዊ አስተዳደሩ የተለየ ሥልጣንና የሥራ ድርሻ ያላቸውን አስፈፃሚ አካላትን የያዘ ነበር፡፡ ካዎ (ንጉሥ)- የባህላዊ አስተዳደሩ ቁንጮና ከፍተኛ የሥልጣን አካል ሲሆን፤ ከእርሱ ቀጥሎ የሚገኙትን የሥልጣን አካላትንና አማካሪዎችን የመሾምና የመሻር ሥልጣን ነበረው። ጠንከር ያለ ውሳኔን የሚሹ ጉዳዮች የመጨረሻ ብይን የሚያገኙትም በካዎ ነበር፡፡ ብሔረሰቡ ጋብቻ የማፈጸመው የጎሣ አቻነትን፣ የሀብት ደረጃ በማስተያየትና የሥጋ ዝምድና አለመኖርን መሠረት በማድረግ ነው፡፡ ወንዶች ከ17-25፤ ሴቶች ደግሞ ከ14-19 ባለው የዕድሜ ክልል ጋብቻ ይፈጽማሉ፡፡ ሴቶችም ሆኑ ወንዶች ጋብቻ ከመፈጸማቸው በፊት ይገረዛሉ፡፡ ጋብቻ ከመፈጸማቸው በፊት ሴቷ ጥጥ ፈትላ አልባሳት ስታዘጋጅ ወንድም በፊናው የመኖሪያ ቤትና የራሱን የእርሻ ቦታ ያደራጃል፡፡ በብሔረሰቡ የተለያዩ የጋብቻ አፈጻጸም ሥርዓቶች አሉት፡፡ በቤተሰብ ስምምነት፣ በጠለፋ የሚፈጸሙ ጋብቻዎች ኣሉት። በተጋቢዎችም ሆነ በቤተሰብ መካከል ያለመግባባት ሲከሰት ወይም የአግቢው ገቢ ሀብት አቅም ውሱንነት ሲከሰት ተጋቢዎቹ ሳይተዋወቁ የወንዱ አባት ሽማግሌ ይዞ የልጅቷን ቤተሰብ ከ1-2 ቀን ደጅ በመጥናት የሚፈጸም የሽምግልና ጋብቻም ኣለው። የምትክ ጋብቻ የሚባለው ደግሞ፤ ሚስት ከሞተች እህቷ ወይም የቅርብ ዘመዷ በምትክ ሚስትነት የምትሰጥበት የጋብቻ ኣይነት ነው፡፡ ወዶ ገብ ጋብቻ ደሞ ሌላው በብሔረሰቡ የሚፈጸም የጋብቻ ዓይነት ነው፡፡ ይኸውም፤ ሳታገባ የቆየች ሴት የራሷን ንብረት በመያዝ ወደ ወንዱ ቤት በፈቃዷ ሄዳ በመግባት የሚፈጸም የጋብቻ ዓይነት ነው፡፡ በብሔረሰቡ በበዓላት ቀናት ከሚዘጋጁት ምግቦች መካከል ሸንዴራ ይገኝበታል፡፡ ከበቆሎና ከገብስ ዱቄት የሚሠራ ሆኖ ቅመማቅመምና ቅቤ በማጣፈጫነት ገብቶበት የሚበላ ጥሩ ምግባቸው ነው፡፡ ቡላ በአይብ ጎመንና ቅቤ ገብቶበት የማሠራው ባጭራ የተባለው ምግባቸውና ቅንጬ በበዓላት ቀን ከሚያዘጋጇቸው ተጠቃሾች ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: በጎፋ ብሔረሰብ ባህላዊ አስተዳደሩ ቁንጮ፣ ከእርሱ ቀጥሎ የሚገኙትን ባለሥልጣናትና አማካሪዎችን የመሾምና የመሻር ሥልጣን ያለው ማነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ካዎ (ንጉሥ) ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nእንደ ፕላቶ ዘገባ፣ የሶቅራጠስ እናት ፌናርት የተሰኘች አዋላጅ ነበረች። ሶቅራጠስ እናቱ ሴቶች ልጅ እንዲወልዱ እንደምትረዳ ሁሉ እርሱ ደግሞ ሰዎች አዳዲስ አሳቦችን እንዲወልዱ ለመርዳት እንደሚሞክር መናገሩ ይጠቀሳል። የሶቅራጠስ አባት ድንጋይ አናጢ የነበረው ሶፍሮኒስከስ እንደነበር ይጠቀሳል። ሶቅራጠስ በዘመኑ ድሃ የነበረ ሲሆን ለዚህ ምክንያቱ ከገንዘብ ይልቅ እውቀት ይበልጣል ብሎ ስለሚያምን ነበር። ሶቅራጠስ ስራ እንደማይሰራና በፍልስፍና ሃሳብና ክርክር ጊዜውን እንደሚያሳልፍ ፕላቶ ዘግቦት ይገኛል። ዛንቲፕ የተሰኘች ከርሱ በዕድሜ በጣም የምታንስ ሴትን አግብቶ ሶስት ልጆች እንደነበሩት ፕላቶ ጽፏል። ሶቅራጠስ 70 ዓመት በሞላው ጊዜ የአቴና መንግስት እንዲያዝና ለፍርድ እንዲቀርብ አደረገ። በወቅቱ ሁለት ክሶች ሲቀርቡበት አንደኛው \"በትምህርትህ ወጣቱን አበላሽተሃል\" የሚል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ \"ለግሪክ ጣዖታት አልተገዛህም\" የሚል ነበር። እንደ ፕላቶ ዘገባ ግን ሶቅራጠስ የግሪክ ጣኦታት አምላኪ ነበር። በአንድ አንድ ተመራማርወች ዘንድ የአቴንስ መንግስት ያቀረባቸው ክሶች በውሸት ላይ የተመሰረቱ ናቸው። የሆኖ ሆኖ፣ ክሪቶ የተሰኘው የፈላስፋው ጓደኛ ለጠባቂወቹ ጉቦ በመስጠት እንዲያመልጥ ሁኔታውን አመቻችቶ ነበር። ሶቅራጠስ ግን እምቢ በማለት ቀረ እንጂ አላመለጠም። ሶቅራጠስ ለፍርድ በቀረበ ጊዜ ሰፊ የሆነ የመከላከያ ክርክር በማቅረብ የአቴናን መንግስት ክስ ውድቅ ለማደርግ ሞክሯል። ከዚህ በኋላ ዳኞቹ ምን አይነት ቅጣት እንዲበይኑበት እንደሚፈልግ ሲጠይቁት፣ ለአቴና ህብረተሰብ ካበረከተው ጥሩ ተግባራቱ አንጻር በቀሪው ዘመኑ ሁሉ ነጻ እራት እንዲያመጡለት ተናገረ። ነገር ግን ፍርድ ቤቱ ወይ በቅጣት እንዲለቀቅ ወይንም ደግሞ እንዲገደል የእጅ ምርጫ አደረገ። ውጤቱም ሶቅራጠስ እንዲገደል የሚል ሆነ። ይሁንና ሶቅራጠስ ሞትን አይፈራም ነበር። ሞቱን ለማስቀረት ይቅርታም ሆነ ሌላ ማባበያ አላቀረበም። በርሱ ሥነ ምግባር መሰረት ላመነበት ነገር እስከመጨረሻ መቆሙ ሰናይ ድርጊት ነበር። ስለሆነም ሄምሎክ የተሰኘ መርዝ ጠጥቶ እንዲሞት ስለታዘዘ፣ መርዙን በመጠጣት አለፈ። \n \nጥያቄ: ሶቅራጥስ ምን የሚባል መርዝ ጠጥቶ እንዲሞት ተፈረደበት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሄምሎክ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበ1240 አካባቢ በግብጽ አገር ቅብጡ አቡል ፋዳዒል እብን አል-አሣል ፍትሐ ነገሥት በአረብኛ ጻፉ። እብን አል-አሣል ሕጎቹን የወሰዱት በከፊል ከሃዋርያት ጽህፈቶችና ከሕገ ሙሴ፤ በከፊልም ከድሮ ቢዛንታይን ነገስታት ሕጎች ነበር። መጽሐፉ በግዕዝ ተተርጉሞ ወደ ኢትዮጵያ የገባበት ወቅት በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን በ1450 አከባቢ እንደነበር የሚል ታሪካዊ መዝገብ አለ። ቢሆንም መጀመርያ እንደ ሕገ ምንግሥት መጠቀሙን የተመዘገበው በዓፄ ሠርፀ ድንግል ዘመን (ከ1555 ጀምሮ) ነው። ፍትሐ ነገስት እስከ 1923 ዓ.ም. የብሄሩን ዋና ሕግ ሆኖ ቆየ። በ1904 ዓ.ም. ዐጼ 2 ምኒልክ የዘመናዊ ሕገ መንግሥት ፅንሰ ሀሳብ ተረድተው በጸሀፊው መምሬ ብስራት አንድ ሕገ መንግሥት የሚመስል ሰነድ ታተመ፤ ይህ ግን በውነት ሕገ መንግሥት አይባልም። «በምኒሊክ ስለተቋቋሙት ሚኒስቴሮች በምሳሌ የቀረበ ጽሑፍ» በምሳሌና በትርጓሜ የእያንዳንዱን ሚኒስቴር ሥራ እንደ ሰውነት አካላት አስመሰለ። ለምሳሌ፦ ኢትዮጵያ መጀመርያ ዘመናዊ ሕገ መንግሥት የተቀበለችው በ1923 አመተ ምኅረት በአጼ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የታወጀ ሲሆን የሕግ አማካሪ ቤቶች በሁለት ያስከፈለ ነው። ይህ የመንግሥታቸው ዋና መሠረት ሆኖ እስከ 1948 አ.ም. አገለገለ፤ በዚያ አመት ተሻሽሎ በወጣ ሕገ መንግሥት ሕዝቦች በመንግሥት ሥራ የሚጫወቱት ሚና እንደገና ተስፋፋ። ይህ ብቻ የአገሪቱ ሕገ መንግሥት ሆኖ እስከ 1967 አ.ም. ቆየ፤ የዛኔ በደርግ (በሕገ መንግስት እራሱ ባልሆነ ሂደት) ተሰረዘ። \n \nጥያቄ: በግብጽ ሀገር አቡል ፋዳዒል እብን አል-አሣል ያዘጋጀው ፍትሐ ነገሥት በምን ቋንቋ ተጻፈ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በአረብኛ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአቡነ ቴዎፍሎስ አቡነ ቴዌፍሎስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሁለተኛው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ወፓትርያርክ ጎጃም በሚገኝው በዝነኛው ደብረ ኤሊያስ አካባቢ ከአባታቸው ከአቶ ወልደ ማርያም ውቤ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ዘርትሁን አደላሁ ሚያዝያ ፲፮ ቀን ፲፱፻፪ ዓ/ም ተወለዱ። ሲወለዱም የተሰጣቸው ስም መልእክቱ ወልደ ማርያም ነበር። በልጅነታቸው ንባብ እና ዜማን በመምህር መሪ ጌታ ረዳኸኝ እና ግራ ጌታ ሣህሉ እዚያው የተወለዱበት አካባቢ ተምረዋል። ኋላ የቅኔ እና የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ዝንባሌ ስላደረባቸው እዚያው ደብረ ኤሊያስ ደብር መምህር ገብረ ሥላሴ በሚባሉ ሊቅ ሥር መማር ጀመሩ። በ፲፱፻፻፳ ዓ/ም ወደ አዲስ አበባ መጥተው ፍትሐ ነገሥትና አዲስ ኪዳንን በመምህር ተክሌ (ነቡረ ዕድ በኋላ ቢትወደድ አቡነ ዮሐንስ) በመባል የሚታወቁት መሪነት ሲከታተሉ ቆይተዋል። በዚህ ጊዜ ውስጥ የኃይማኖት ችግሮችን ለማወቅ ይፈልጉ እንደነበርና ሰፋ ያለ ዕውቀት እንደነበራቸው ይነገራል። በተጨማሪ የኃይማኖት ችግሮችን የሚመለከቱ መጻሕፍትን ሳይታክቱና ሳይሰለቹ ያነቡም ነበር። መልእክቱ ወልደ ማርያም በ፲፱፻፴ ዓ/ም ይህን ዓለም በቃኝ ብለው ደብረ ሊባኖስ ገዳም መንኩሰው ገቡ። ከጠላት ወረራ በኋላ ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀሳውስቱ በዘመናዊ የኃይማኖት ትምህርት እንዲሠለጥኑ በነበራቸው ሀሳብ መሠረት ፳ የሚሆኑ ሊቃውንት መርጠው በቤተ መንግሥቱ አካባቢ እንዲሰለጥኑ አድርገዋል። ከነኚህም አንዱ አባ መልእክቱ ወልደ ማርያም ናቸው። ቀደም ብሎ በኢትዮጵያና በግብጽ በተደረገው ስምምነት መሠረት ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያዊያን ጳጳሶች ሲሾሙ ሊቀ ሥልጣናት መልእክቱ ወልደ ማርያም ለሹመት ከተመረጡት አምስት አባቶች አንዱ ሲሆኑ ወደግብጽ ተጉዘው በእስክንድርያው ፓትርያርክ ዳግማዊ አቡነ ዮሳብ እጅ በካይሮ በትረ ካና ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን እሑድ ሐምሌ ፲፰ ቀን ፲፱፻፵ ዓ/ም ሊቀ ሥልጣናት መልእክቱ “ብጹዕ አቡነ ቴዎፍሎስ” ተብለው የሐረርጌ ጳጳስ ሆኑ። \n \nጥያቄ: አቡነ ቴዎፍሎስ የሐረርጌ ጳጳስ ሆነው የተሾሙት የት ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በካይሮ በትረ ካና ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአሜሪካ ለሁዋዌ ተጨማሪ ሽያጮችን ልታግድ መሆኑን አስታወቀች። አሜሪካ የምታመርታቸውን ጨምሮ በተለያዩ ሃገራት የተመረቱ የቴሌኮም ምርቶችን ለግዙፉ የቻይና የቴክኖሎጅ ኩባንያ እንዳይሸጡ ለማገድ ስለመዘጋጀቷም ነው የገለጸችው። የትራምፕ አስተዳደር ሁዋዌ የሃገሪቱን ደህንነት ስጋት ላይ ይጥላል በሚል ኩባንያው ላይ ጫና እያሳደረ ነው። የአሜሪካ ግምጃ ቤት ባለፈው አመት ሰኔ ወር ላይ ኩባንያውን በጥቁር መዝገብ አስፍሮት እንደነበር ይታወሳል። አሁን ላይም ለኩባንያው ከአሜሪካም ሆነ ከሌሎች ሃገራት የሚጓጓዙ የቴክኖሎጅ ቁሳቁሶች ላይ ገደብ መጣል የሚያስችል ረቂቅ እየተዘጋጀ መሆኑንም ገልጻለች። የአሜሪካ ግምጃ ቤት አሁን ባለው ህግ የአሜሪካ የቴክኖሎጅ ምርቶች ከፍ ያለውን ዋጋ ከያዙ ወደ ቻይና የሚላኩ የሌሎች ሃገራትን የቴክኖሎጅ ምርቶች የማገድ ወይም የማስገቢያ ፈቃድ መጠየቅ ይችላል። አሜሪካ ባለፈው ዓመት በደህንነት ስጋት ምክንያት ለሁዋዌ እና 68 ተዛማጅ ኩባንያዎች የቴክኖሎጂና ሌሎች መሳሪያዎችን እንዳይሸጡ ገደብ መጣሏ የሚታወስ ነው። አሜሪካ የቻይና የቴክኖሎጅ ኩባንያዎችን አገልግሎት መጠቀም ሊያስከትል የሚችለውን የደህንነት ስጋት የሚያሳይ ማስረጃ በማቅረብ በተለይም ምዕራባውያን አጋሮቿ እንዳይጠቀሙ እየወተወተች ትገኛለች። ምንጭ፦ አልጀዚራ \n \nጥያቄ: አሜሪካ የቻይና የቴክኖሎጅ ኩባንያዎች ላይ እገዳ የጣለችው በምን ምክንያት ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የሃገሪቱን ደህንነት ስጋት ላይ ይጥላል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቱርክ በዊኪፒዲያ ላይ ላለፉት ሶስት ዓመታት ጥላው የነበረውን እገዳ በማንሳት ተጠቃሚዎች ድረ ገፁን ማግኘት እንዲችሉ ፈቀደች። የሀገሪቱ ህገ መንግስታዊ ፍርድ ቤት እገዳው የመናገር መብትን ይጥሳል ሲል እግዱ እንዲነሳ ውሳኔ አሳልፏል። ዊኪፒዲያ በፈረንጆቹ ሚያዚያ ወር 2017 የቱርክን መንግስት የሚተች ፅሁፍ ለማንሳት ፈቃደኛ አለመሆኑን ተከትሎ የቱርክ መንግስት እገዳ ማሳላፉ ይታወሳል። በወቅቱ በዊኪፒዲያ ላይ የሰፈረው ፅሁፍ የቱርክ መንግስት ከአይ ኤስ እና አል ቃይዳ ጋር ትብብር አለው የሚል መሆኑን ዘገባው አመልክቷል። ይህንን ተከትሎም እገዳው ላለፉት 991 ቀናት ተግባራዊ ሆኖ መቆየቱን የኢንተርኔት ክትትል ተቋም የሆነው ኔትብሎክስ አስታውቋል። እገዳው በሂደት ቀስ በቀስ የሚነሳ በመሆኑ እና የተወሰኑ የኢንተርኔት አገልግሎት አቅራቢዎች ዊኪፒዲያን ለመመለስ እየሰሩ በመሆኑ በቱርክ የሚገኙ ሁሉም ተጠቃሚዎች ድረ ገፁን ማግኘት አይችሉም ተብሏል፡፡ ዊኪፒዲያ በበርካታ የዓለም ሀገራት ሳንሱር የሚደረግ ሲሆን በቻይና አሁንም ታግዶ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ዊኪፒዲያ በቱርክ ለስንተ ቀናት ታገደ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 991 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nፐርል በክ ፐርል በክ በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ (1938) ለመሆን የበቃች አሜሪካዊት ደራሲ ናት። በክ ጁን 26 ቀን 1982 ዓ.ም በምእራብ ቨርጂኒያ ሂልዝቦሮ በተባለ ቦታ ተወለደች። ወላጆቿ ፕሬስብቴርያዊ ሚሲዮኖች የነበሩ ሲሆን ብዙውን የሚሲዮን ስራቸውን በቻይና ነው ያሳለፉት። በዚሁ የተነሳ በክ ከልጅነቷ ጀምሮ እንግሊዝኛን ብቻ ሳይሆን ቻይንኛንም አቀላጥፋ ትናገር ነበር። ትምህርቷን በ1914 እንዳጠናቀቀች ወደ ቻይና ነው ያቀናችው። በ1915 የወደፊት ባሏ ከሚሆነውን ከጆን ሎሲንግ በክ ጋር ተገናነች። በ1917 ጋብቻቸውን ከፈጸሙ በኋላ ኑሯቸውን ናንሹ በተባለችው የገጠራማዋ አንህዌ ግዛት አደረጉ። በዚሁ ቆይታዋ ነው ወደፊት የሥነ-ጽሁፍ ስራዋ ጉልላት ለመሆን የበቃውን ስሙር መሬት (The Good Earth) ለተባለው መጽሃፏ የሚሆናትን መረጃ የሰበሰበችው። በክ ጽሁፎቿን ማሳተም የጀመረችው ከ1920ዎቹ ጀምራ ሲሆን አጫጭር ስራዎቿ \"The Nation\"፣ \"The Chinese Recorder\"፣ \"Asia\" እና \"The Atlantic Monthly\" በተሰኙ መጽሄቶች ታትመውላታል። የመጀመሪያው ወጥ ልብ-ወለድ ድርሰቷ (East Wind, West Wind) በ1930 በጆን ዴይ ኩባንያ ታትሟል። የጆን ዴይ ኩባንያ አሳታሚ የነበረው ሪቻርድ ዋልሽ ኋላ ላይ (1935) የፐርል በክ ሁለተኛ ባሏ ለመሆን በቅቷል። በ1931 ጆን ዴይ ኩባንያ የፐርል በክን ሁለተኛ ወጥ ልብ-ወለድ ድርስት የሆነውን ስሙር መሬትን አሳተመ። ይኸው ሥራዋ በተከታታይ በ1931 እና በ1932 ዓ.ም በገበያ ላይ አንደኛ ተፈላጊ ሆኖ ለመዝለቅ የቻለ ሲሆን ለሷም በ1935 ዓ.ም የፑሊትዘር ሽልማት እና የሃዌልስ ሜዳልያ አስገኝቶላታል። ስሙር መሬት በ1937 ዓ.ም በኤም.ጂ.ኤም አማካይነት በፊልም መልክ ተቀናብሮ ለተመልካች ቀርቧል። ከዛ በተከታታይ ሌሎች ድርሰቶችን ለአንባቢ አቅርባለች። በክ በ1938 ዓ.ም በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን በመቀበል የመጀመሪያዋ (ሴት) አሜሪካዊት ሆናለች። ፐርል በክ በ1973 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ስትለይ ከ70 በላይ ስራዎቿ ታትመውላታል። መቃብሯም ፔንሲልቬንያ ውስጥ በክስ በተባለው ቀበሌ ይገኛል። \n \nጥያቄ: የጆን ዴይ ኩባንያ አሳታሚ የነበረው በ1935 የፐርል በክ ሁለተኛ ባሏ ለመሆን የበቃው ማን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሪቻርድ ዋልሽ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቀጭኔ ከዝሆን በስተቀር ማንኛውም ሌላ እንስሳ ሊደርስ በማይችልበት ከፍታ ላይ የሚገኙ ረዣዥም ቀንበጠቦችን ለመብላት የሚያስችል አስደናቂ አፈጣጠር አላት። ልዩ የሆነ የመቆንጠጥ ችሎታ ያለው የላይኛው ከንፈሯና እንደተፈገለው የሚተጣጠፍ ችሎታ ያለው ምላሷ ሹል በሆኑ እሾሆች የታጠሩ ቅጠሎችን ለመቀንጠብ ያስችሏታል። ቀጭኔዎች በቀን እስከ 34 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕፅዋት መመገብ ይችላሉ። የተለያዩ ዕፅዋትን የሚበሉ ቢሆኑም ይበልጥ የሚመርጡት በአፍሪካ ሜዳዎች የሚገኙትን እሾሃማ ግራሮች ነው። አንድ ወንድ ቀጭኔ ምግብ ለመፈለግ ምላሱን እስከ 42 ሳንቲ ሜትር መዘርጋት ይችላል። የቀጭኔ አንገት በጣም አስደናቂ የሆነ የመተጣጠፍ ችሎታ አለው። ይህም ላይኛዎቹን የዛፍ ቅርንጫፎች ለመቀንጠብ በምታደርገው እንቅስቃሴ ረዥሙን ራሷን እንደ ልቧ ለማዘንበልና ለማዟዟር ያስችላታል። ለቀጭኔ ወደ ላይ መንጠራራት በጣም ቀላል ነገር ሲሆን ተጎንብሶ ውኃ መጠጣት ግን ይከብዳታል። ወደ ውኃ ጉድጓድ በምትቀርብበት ጊዜ የፊት እግሮቿን ቀስ በቀስ ከፍታ ካራራቀቻቸው በኋላ ወደ ውኃው ለመድረስ እንድትችል ሁለት ጉልበቶቿን አጠፍ ታደርጋለች። ቀጭኔዋ እንዲህ ባለው አመቺ ባልሆነ ሁኔታ እያለች ረዥም አንገቷን እስከ መጨረሻ ትዘረጋለች። ደግነቱ ግን ከምትመገባቸው ቅጠላ ቅጠሎች በቂ እርጥበት ስለምታገኝ ቶሎ ቶሎ መጠጣት አያስፈልጋትም። የቀጭኔ አንገትና ትከሻ የቅጠል ቅርፅ ባላቸውና ቀጫጭን በሆኑ ነጭ መስመሮች ያጌጠ ነው። ቀለማቸው የተለያየ ሲሆን ከወርቃማ ዳለቻ አንስቶ እስከ ቡናማ እንዲያውም ጠቆር እስካለ ቀለም ይደርሳል። የቀጭኔ ዕድሜ እየገፋ በሄደ መጠን ቀለሟም እየጠቆረ ይሄዳል። ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው። አንዲት ነፍሰ ጡር ቀጭኔ ልጅዋን ከ420 እስከ 468 ለሚደርሱ እርግዝና ቀናት ከተሸከመች በኋላ ሁለት ሜትር ቁመት ያለው ግልገል ትወልዳለች። ግልገሏ በምትወለድበት ጊዜ ራስዋን ታስቀድምና ከሁለት ሜትር ከፍታ ላይ ወደ መሬት ትወረወራለች። ይሁን እንጂ በ15 ደቂቃ ውስጥ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባት እየተውተረተረች ትነሳና ጡት ለመጥባት ዝግጁ ትሆናለች። ከሁለት ወይም ከሦስት ሳምንት በኋላ በደመ ነፍስ ተመርታ የግራር ቀንበጦችን መለቃቀም ስለምትጀምር ብዙም ሳትቆይ ረዥም እርምጃ ያላትን እናትዋን ተከትላ ለመሄድ የሚያስችል ጉልበት ታገኛለች። አንዲት የቀጭኔ ግልገል በጣም ውብ መልክ ሲኖራት የወላጆችዋ አነስተኛ ግልባጭ ነች። ቁመቷ ከቀጭኔ ርዝመት ጋር ሲወዳደር አጭር ብትሆንም ከብዙ ሰዎች ቁመት ግን ትበልጣለች። በእናቷ ጥንቃቄ የተሞላበት ጥበቃ ተማምና አላንዳች መሸበር አካባቢዋን የምትማትረው ግልገል ላያት ሁሉ ልዩ መስህብ አላት። ግልገል ቀጭኔዎች በተወለዱበት ወራት በግልገል መዋያ ተሰባስበው ሙሉውን ቀን ዕረፍት በማድረግ፣ በመጫወትና በአካባቢያቸው የሚሆነውን ነገር በመመልከት ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ። የቀጭኔ ግልገል ለማመን በሚያዳግት ፍጥነት ያድ⁠ጋል። በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ አንድ ሜትር የሚያክል ቁመት ሲጨምር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በእጥፍ ያድጋል። በአንድ ሳምንት ብቻ 23 ሳንቲ ሜትር ያህል ሊያድግ ይችላል! እናትዬው ለልጅዋ ከፍተኛ ጥበቃ የምታደርግ ሲሆን ልጅዋ የተወሰነ ርቀት እንድትዘዋወር ብትፈቅድላትም ሩቅ የማየት ችሎታ ስላላት በዓይኗ ትከታተላታለች። ቀጭኔ ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ስላላት ከአንበሳ በቀር የሚያጠቃት ጠላት የለም። ቢሆንም ይህችን የምታምር ፍጥረት የሰውን ያህል በብዛት አድኖ የገደለ የለም። ቀጭኔ በሚያምር ቆዳዋ፣ በሚጣፍጥ ሥጋዋና አንዳንዶች ምትሐታዊ ኃይል አለው በሚሉት ረዥምና ጥቁር ጭራዋ ምክንያት እጅግ ተፈላጊ ስለሆነች በአሁኑ ጊዜ የዚህች ሰላማዊ ፍጡር የወደፊት ሕልውና ስጋት ላይ ወድቋል። በአንድ ወቅት በብዙ የአፍሪካ አካባቢዎች እንደ ልብ ትታይ የነበረችው ቀጭኔ በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው በቂ ጥበቃ በሚደረግላት ፓርኮች ብቻ ሆኗል። የቀጭኔ አካላዊ ቅርጽና ግዝፈት ችግሮች ማስከተሉ አይቀርም ብሎ የሚያስብ ይኖር ይሆናል። በጣም ትልቅ ቁመትና ረዥም አንገት ስላላት የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖራትና ወደ ሁሉም የአካሏ ክፍሎች ደም እንዲደርስ ማድረግ የማይቻል ነገር ሊመስል ይችላል። ለምሳሌ ያህል ቀጭኔ አንገቷን ወደ መሬት ስታጎነብስ በስበት ኃይል ምክንያት ብዙ ደም ወደ ጭንቅላቷ ፈስሶ አንጎሏን ማጥለቅለቅ ነበረበት። ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ደሟ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ልቧ ተመልሶ ራሷን እስከ መሳት ሊያደርሳት ይገባ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ነገር አይደርስም። ለምን? የቀጭኔ የደም ዝውውር ሥርዓት በዓይነቱ ልዩ ለሆነው ለዚህች እንስሳ ቅርጽና መጠን እንዲያገለግል ሆኖ በታላቅ ጥበብ የተሠራ ነው። ልቧ ራሱ በጣም ትልቅ ሲሆን ደሙን ሦስት ሜትር ተኩል ገደማ ርቆ እስከሚገኘው እስከ አንጎላ ለመግፋት የሚያስችል አቅም አለው። በደቂቃ እስከ 170 ጊዜ የሚመታውና 7 ሳንቲ ሜትር ያህል ውፍረት ባለው ጡንቻ የተገነባው የቀጭኔ ልብ ከሰው የደም ግፊት በሦስት እጥፍ የሚበልጥ ግፊት ያመነጫል። ወደ አንጎል የሚሄደውን ደም የሚሸከመው ካሮቲድ የተባለው የደም ቧንቧና ከአንጎል ወደ ልብ የሚመለሰውን ደም የሚሸከመው ጀጉላር የተባለው የደም ቧንቧ እንዲህ ያለውን ከፍተኛ ግፊት መቋቋም የሚያስችል መጠን ሊኖራቸው ይገባል። በእርግጥም እነዚህ የደም ቧንቧዎች ከ2.5 ሳንቲ ሜትር በላይ ስፋት ያላቸው ከመሆኑም በላይ ጠንካራና የመለጠጥ ችሎታ ባላቸው ሕዋሳት የተገነቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥንካሬና የመለመጥ ችሎታ አላቸው። ቀጭኔ ከጭንቅላቷ ጎንበስ በምትልበት ጊዜ ወደ አንጎሏ የሚሄደውን የደም ፍሰት የሚቆጣጠሩ ልዩ መቆጣጠሪያዎች አሏት። አንጎልና አንገት በሚገናኙበት ቦታ ላይ ትልቁ ካሮቲድ የደም ቧንቧ ሬቴ ሚራቢሌ ተብሎ ከሚጠራ አስደናቂ የሆነ መረብ መሰል አካል ይገናኛል። በከፍተኛ ኃይል ተገፍትሮ የመጣው ደም እዚህ ጋር ሲደርስ በጣም በርካታ ወደሆኑ ትናንሽ የደም ሥሮች እንዲገባ ስለሚደረግ የደሙ ግፊት ተስተካክሎ በአንጎል ላይ ጉዳት የማያስከትል ይሆናል። ቀጭኔዋ ራስዋን ጎንበስ በምታደርግበት ጊዜ ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው መረብ ይለጠጣል፤ ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ይኮማተራል። ይህም የስበት ኃይል የሚያሳድረው ተጽዕኖ ሚዛኑን የጠበቀ እንዲሆን ማድረግና የደም ግፊቷ በእጅጉ ቀንሶ ራሷን የምትስትበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ለመከላከል ይረዳታል። የሳይንስ ሊቃውንት በጣም አስደናቂ ርዝመት ያለው የቀጭኔ አንገት ያሉት አከርካሪዎች ቁጥር ከአይጥ ወይም ከብዙዎቹ አጥቢ እንስሳ ጋር እኩል መሆኑን ሲያውቁ በጣም ተደንቀዋል! ይሁን እንጂ የቀጭኔ አከርካሪዎች በጣም ረዣዥሞችና እርስ በርሳቸው ልዩ በሆነ ሁኔታ የተሰካኩ በመሆናቸው እንደ ልብ ሊተጣጠፉ ይችላሉ። ቀጭኔ አንገቷን መጠምዘዝና ማጠፍ ስለምትችል ሁሉንም የአካሏን ክፍሎች ለመላስም ሆነ ረዣዥም የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ለመድረስ ትችላለች። \n \nጥያቄ: የቀጭኔ ግልገል በምትወለድበት ጊዜ የምታስቀድመው የሰውነት ክፍል የቱን ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ራስዋን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአሸናፊ ከበደ ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ አዲስ አበባ ግንቦት ፰ ቀን ፲፱፻፴ ዓ/ም ተወለዱ። አባታቸው ግራዝማች ከበደ አድነው ሲሆኑ ክልጅነታቸው ጀምሮ የሙዚቃ ስሜትንና ፍቅር ያሳደሩባቸው እናታቸው ወይዘሮ ፋንታዬ ነከሬ ነበሩ። አያታቸው ሊቀመኳስ አድነው ጎሹ ደግሞ የአድዋ አርበኛ እናየንግሥት ዘውዲቱም ታማኝ አማካሪ እንደነበሩ ይነገራል። የሙዚቃ ፍቅርን ገና በልጅነታቸው ያሳደሩባቸው እናታቸው ሲሆኑ ታዳጊው አሸናፊ ገና የዘጠኝ ዓመት ልጅ ሳሉ እኒህ የሚያፈቅሯቸውና ዕድሜ ልካቸውን በኀዘን የሚስታውሷቸው እናታቸው ሞተውባቸዋል። መሠረታዊ ትምህርታቸውን በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት እና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ኮከበ ጽባሕ) ካጠናቀቁ በኋላ በሐረር የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ በኒው ዮርክ ክፍለ-ሀገር ከሚገኘው የሮቼስተር ዩኒቨርሲቲ፣ “ኢስትማን የሙዚቃ ትምህርት ቤት” በ፲፱፻፶፬ ዓ/ም በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመረቁ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው፤ የያሬድ ሙዚቃ ትምሕርት ቤትን መሠረቱ። የዚሁ ትምህርት ቤትም የመጀመሪያው ዳይሬክቶር ከመሆናቸውም ባሻገር በአዲስ አበባው የወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማኅበር (ወ.ወ.ክ.ማ Y.M.C.A.)፤ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የበጎ አድራጎት ድርጅት መርሓ-ዕውራን ትምህርት ቤት እና በመሳሰሉ የወጣቶች ማኅበራት እየተገኙ የሙዚቃ ትምህርት ይሰጡ ነበር። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ የሙዚቃ ስሜትንና ፍቅር ያሳደሩባቸው ማናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ እናታቸው ወይዘሮ ፋንታዬ ነከሬ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኒሺ ፍሬደሪክ ዊልሄልም ኒትሸ (ኦክቶበር 15, 1844 - ኦገስት 25, 1900) ጀርመናዊ ጻህፊና ፈላስፋ ሲሆን አለምን ይቀይራሉ ብሎ ያመነባቸውን ብዙ መጻህፍት በመድረስ ይታወቃል። እርግጥ ኒሺ፣ በነበረበትም ሆነ በኋላ ዘመኑ ብዙ ተቃዋሚወች ቢነሱበትም በዚያው ልክ ብዙ ሰወች ስራወቹን እንደ ታላቅ የፍልስፍና እና ስነ ጽሁፍ ስራ ይወስዷቸዋል። ኒትሸ አብዛኛው ጽሁፉ የሚያተኩረው ሰወች እንዴት ሊኖሩ ይገባቸዋል? በሚለው ጥያቄ ነው። በዚህ ምክንያት እሱ ይኖርበት የነበረውን ዘመን የጀርመን ሥነ ምግባር (ኤቲክስ) በመንቀፍ ብዙ ጽፎአል። ሠናይ እና እኩይ (ጥሩና መጥፎ) ተብለው ተለይተው ይሰራባቸው የነበሩትን የጊዜውን ሥነ ምግባር ዋጋወች በመተቸት ሰወች አዲስ ሥነ ምግባር ፈጥረው ለሁሉም ምግባር አዲስ የሠናይነትና እኩይነት (ጥሩ እና መጥፎ) ዋጋ እንዲሰጡ በጽሑፎቹ ብዙ ሞክሯል።በዚህ መሰረት፣ ለምሳሌ፣ በክርስቲያኖች ዘንድ የሚሰራበትን ለደካሞች ማዘንን ሠናይነት ተቃውሟል። በሱ አስተያየት ደካሞች ሲታዘንላቸው የበለጠ ይዳከማሉ የሚል ነው ምክንያቱም በሱ አስተያየት ደካሞቹ በጠንካሮቹ ላይ የበለጠ ጥገኛ በመሆን መላው ህብረተሰብ ይዳከማል የሚል ነው። በተጨማሪም፣ የሰው ልጅ የሚኖርበትን ተጨባጩን አለም መገንዘብ እና ክሁሉ በላይ ስለዚሁ ዓለም ማተኮር አለበት ብሏል። ሰማይና ሌሎች አለማትን በማጣጣል፣ የሰው ልጅ እነዚህን አይነት አለሞች የሚፈጥረው አሁን ያለበትን ተጨባጩ የውኑ አለም ችግሮች መፍታት ሲያቅተው ለመፈርጠጥ ነው በማለት የሰው ልጅ ስለዚህ ምድር ብቻ እንዲያስብ ይወተውታል። ኒሽ የሰው ልጅ እራሱን በራሱ ማሸነፍ እንዲችል አጥብቆ ያምናል። በኒሺ ፍልስፍና፣ አንድ እራሱን ያሽነፈ ሰው በጣም የተለወጠ እና የተሻለ ስለሚሆን \"ሱፐር ማን\" ወይም \"የበላይ ሰው\" እንዲባል ሰይሟል። የበላይ ሰው እንግዴህ ጠንካራና በሌሎች ሰወች \"ሠናይ\" እና \"እኩይ\" ወይም ደግሞ \"ጥሩ\" ና \"መጥፎ\" ዋጋወች የማይመራ፣ ይልቁኑ የራሱን ሥነ ምግባር የሚፈጥር ነው። \n \nጥያቄ: የኒሽ አቁዋም ምን ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የሰው ልጅ እራሱን በራሱ ማሸነፍ እንዲችል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበቁርጥራጭ ብረትና ያገለገሉ ማሽኖች ንግድ የተሰማራው ሳርፌ ቢዝነስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር፣ የግንባታ ብረታ ብረቶች ማምረቻ ፋብሪካ በዱከም ከተማ ለመገንባት በዝግጅት ላይ እንደሆነ አስታወቀ፡፡ የሳርፌ ቢዝነስ መሥራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ክብርይስፋ ተክሌ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ኩባንያው እስካሁን ቁርጥራጭ ብረቶች ከውጭ በማስመጣትና ከአገር ውስጥ በመግዛት ለብረት አቅላጮች ሲያቀርብ ቆይቷል፡፡ የብረት ማቅለጫው ማሽኖች ከህንድ ተገዝተው የሚመጡ ሲሆን፣ የብረት መዋቅሩ ደግሞ ከቻይና ይገዛል፡፡ የፋብሪካው ጠቅላላ የኢንቨስትመንት ወጪ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚገመት የተናገሩት አቶ ክብርይስፋ፣ ፋብሪካው ለ300 ኢትዮጵያውያን የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡ ሳርፌ ቢዝነስ ለብረት ፋብሪካው ግንባታ የሚሆን 30,000 ካሬ ሜትር ቦታ በሊዝ ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከዱከም ከተማ አስተዳደር በቅርቡ መረከቡን ገልጸው፣ ኩባንያቸው ተገቢውን የአዋጭነት ጥናት ማሠራቱን አስረድተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የሳርፌ ብረታ ብረት ማምረቻ ፋብሪካ ግንባታ ሲጠናቀቅ ለምን ያህል ሰው የሥራ እድል ይፈጥራል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ለ300 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በ84ኛው የየካቲት 12 ሰማዕታት መታሰቢያ ቀን ላይ በመገኘት የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የአባት አርበኞች ማህበር ፕሬዚዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን ተገኝተዋል። በሰመዕታት መታሰቢያ ቀን የካቲት 12 ቀን በየአመቱ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት፤አባት አርበኞች፤ እና የህብረተሰብ ክፍሉ በስድስት ኪሎ ታስቦ ይውላል፡፡ \n \nጥያቄ: የአባት አርበኞች ማህበር ፕሬዚዳንት ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nክዋሜ ንክሩማህ የተወለዱት በ1909 እ.ኤ.አ. ደቡባዊ ምዕራብ ጋና (ቀደም ሲል ጎልድ ኮስት) ንክሮፉል በምትባል ከተማ ነው። ንክሩማህ በካቶሊክ ሚሽነሪ ትምህርት ቤት ይማሩበት በነበረ ወቅት ብሩህ አዕምሮ እንደነበራቸው የተመሰከረላቸው ሲሆን ገና በአሥራዎቹ እድሜ ውስጥ እያሉ ነው በአቅራቢያቸው በሚገኝ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት አስተማሪ የሆኑት። ይሁንና ያለሥልጠና የጀመሩትን ትምህርት በ1926 እ.ኤ.አ. የአክራውን አቺሞታ ኮሌጅ ተቃለቅለው የመምህርነት ምሥክር ወረቀት በማግኘት በተለያዩ የካቶሊክ ትምህርት ቤቶች አስተምረዋል። በ1935 እ.ኤ.አ. ወደ አሜሪካ በማቅናትም የፔንሴልቬኒያውን ሊንከን ዩኒቨርሲቲ ተቀላቅለው በኢኮኖሚክስና ሶሲዮሎጂ የመጀመሪያ ድግሪያቸውን በ1939 የተቀበሉ ሲሆን በ1942ም በሥነ-መለኮት ሌላ ድግሪ ከዚሁ ዪኒቨርሰቲ አግኝተዋል። በ1942 እና በ1943ም የማስተርስ ድግሪያቸውን ከፔንሴልቬኒያ ዩኒቨርሲቲ በሥነ-ትምህርትና በፍልስፍና ሠርተዋል። በአሜሪካ ቆይታቸውም በግራ ዘመም አሰተሳሰቦች በመማረከቸው የተነሳ በወቅቱ በሥርነቀል ለውጥ ፈላጊነታቸው ከሚታወቁ ምሁራን ጋር ቅርብ ግንኙነት መሥርተው ነበር። አፍሪካውያንን ያሰባሰበ የተማሪዎች እንቅስቃሴ መሥራችና ግንባር ቀደም ተናጋሪ እንዲሁም የአፍሪካ አገራት ነፃ እንዲወጡና የአውሮፓ ቅኝ ግዛት እንዲያበቃ ቁርጠኛ አቋም ነበራቸው። ከዚሁ ጎን ለጎንም የተባበረች አፍሪካ አስፈላጊነትን በማመን አፍሪካውያንና የአፍሪካ ዝርያ ያላቸው ሕዝቦች በአንድነት እንዲቆሙ የሚሰብከው ፓንአፍሪካኒዝም አቀንቃኝ ነበሩ። በ1945 ወደ ለንደን ሕግና ኢኮኖሚክስ ለማጥናት ባመሩበት ወቅትም በማንችስተር እንግሊዝ የተካሄደውን 5ኛው የፓን አፍሪካን ጉባዔ እንዲካሄድ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የአፍሪካን ከቅኝ ግዛት የመውጣት እንቅስቃሴ ለማስተባበርና ቅኝ አገዛዝን ለመቃውም የተደራጀው ጉባዔ ንክሩማህ ታዋቂ የጥቁር መብት ታጋዮችና የፀረ-ቅኝ ግዛት ንቅናቄ መሪዎች ጋር እንዲገናኙ ዕድል የሰጣቸው ሲሆን በ1946ም ጥናታቸውን ትተው በ5ኛው ጉባኤ የተቋቋመው የምዕራብ አፍሪካ ብሔራዊ ጽ/ቤት ዋና ጸኃፊና የምዕራብ አፍሪካ ተማሪዎች ማኅበር ምክትል ፕሬዝዳንት በመሆን አገልግለዋል። \n \nጥያቄ: የተክዋሜ ንክሩማህ መቼና የት ተወለደ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ1909 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየ2014 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ የ2014 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ ፳ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሲሆን ከሰኔ ፭ እስከ ሐምሌ ፮ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. በብራዚል ይካሄዳል። ብራዚል ይህን ውድድር ስታዘጋጅ ይሄ ሁለተኛ ጊዜዋ ነው። ፊፋ የ2014 እ.ኤ.አ. ውድድር በደቡብ አሜሪካ እንደሚካሄድ በ2007 እ.ኤ.አ. ካወጀ በኋላ ብራዚል ያለማንም ተቀናቃኝ አዘጋጅ አገር ሆና ተመርጣለች። የ፴፩ አገራት ብሔራዊ ቡድኖች ከጁን 2011 እ.ኤ.አ. ጀምሮ የተካሄዱ የማጣሪያ ውድድሮችን በማለፍ ከብራዚል ጋር በመጨረሻው ውድድር ላይ ለመሳተፍ በቅተዋል። በጠቅላላው ፷፬ ጨዋታዎች በ፲፪ ከተማዎች ውስጥ በሚገኙ አዲስ የተገነቡ ወይም የተሻሻሉ ስታዲየሞች ይከናወናሉ። በዓለም ዋንጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የጎል ላይን ቴክኖሎጂ በጥቅም ላይ ውሏል። በ1930 እ.ኤ.አ. ከተካሄደው የመጀመሪያው የዓለም ዋንጫ ጀምሮ ሁሉም የዓለም ዋንጫ ሻምፕዮን አገራት (ብራዚል፣ አርጀንቲና፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሣይ፣ ጀርመን፣ ኢጣልያ፣ እስፓንያ እና ኡራጓይ) በዚህ ውድድር ውስጥ ተሳታፊ ናቸው። ከዚህ በፊት በደቡብ አሜሪካ የተዘጋጁትን ዋንጫዎች እንዳለ የወሰዱት የደቡብ አሜሪካ ቡድኖች ናቸው። ፊፋ ለውድድሩ ያቀረበው ጠቅላላ የሽልማት ገንዘብ $576 ሚሊዮን ነው። ይህም ከ2010 እ.ኤ.አ. ውድድር ሽልማት ገንዘብ የ፴፯ ከመቶ ዕድገት አለው። ከዚህ ውስጥ $70 ሚሊዮን የሚሆነው ተጫዋቾቹ ለሚጫወቱበት ክለቦች ተጫዋቾቹ ለሚደርስባቸው ጉዳት መካካሻ እንዲሆን ተሰጥቷል። ከውድድሩ በፊት እያንዳንዱ ቡድን ለዝግጅት ወጪው $1.5 ሚሊዮን የተረከበ ሲሆን ቀሪው ገንዘብ እንደሚመለከተው ተከፋፍሏል፦ $8 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በምድብ ደረጃ የወደቀ ቡድን (፲፮ ቡድኖች) $9 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በየ፲፮ ዙር የወደቀ ቡድን (፰ ቡድኖች) $14 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በሩብ ፍፃሜ የወደቀ ቡድን (፬ ቡድኖች) $20 ሚሊዮን - በአራተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $22 ሚሊዮን - በሶስተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $25 ሚሊዮን - በሁለተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $35 ሚሊዮን - ለአሸናፊው ቡድን በአስራ ሁለት ከተማዎች የሚገኙ አስራ ሁለት ስታዲየሞች ለውድድሩ ተዘጋጅተዋል። ሰባቱ አዲስ የተገነቡ ሲሆን አምስቱ ደግሞ የተሻሻሉ ስታዲየሞች ናቸው። \n \nጥያቄ: ፳ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ በየት ሀገር ይዘጋጃል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በብራዚል ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሚያዝያ ፴ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፵ ኛው ዕለትና የወርኅ ፀደይ (በልግ) ፴፭ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ ሉቃስ ፻፳፮ ቀናት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመን ማርቆስ ደግሞ ፻፳፭ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፰፻፸፬ ዓ/ም - እምባቦ በሚባል ሥፍራ የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ ሠራዊት እና የጎጃም ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ሠራዊት ውጊያ ገጥሞ ድሉ የንጉሥ ምኒልክ ሲሆን፣ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ተማረኩ። ፲፰፻፺ ዓ/ም - በጣልያ አበጋዙ ባቫ-በካሪስ ብዙ መቶ ሰልፈኞች በመድፍ ገደላቸው። ፲፱፻፳፭ ዓ/ም - የሕንድ አባት በሚል ቅጽል ስም የሚታወቀው ሞሃንድራስ ካራምቻንድ ጋንዲበአገሩ የእንግሊዝን አስተዳደር በመቃወም የሃያ አንድ ቀን የ'ረሀብ አድማ' ጀመረ። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - በአውሮፓ የሁለተኛው የዓለም ጦርነትን ማክተም ምክንያት በማድረግ 'ሴቲፍ' በተባለች የአልጄሪያ ከተማ በተካሄደ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ፻፫ አውሮፓውያን በመሞታቸው፣ የገዢው የፈረንሳይ መንግሥት ፖሊሶች እና ወታደሮች ባካሄዱት ጨካኝ በቀላ እስከ ስድስት ሺ አልጄሪያውያን ተጨፍጭፈዋል። የዚህ አረመኔያዊ ድርጊት ሳቢያ በመላው የሰሜን አፍሪቃ የፈረንሳይን ቅኝ ገዢነት ማክተሚያ አብሳሪ እንደሆነ ታሪካውያን ይዘግባሉ። ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - በሩሲያኖች የተገነባው የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ዶክቶር ምናሴ ኃይሌ እራሳቸውን ከሥልጣናቸው አስወገዱ። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - አቶ ለገሰ ዜናዊ አስረስ፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር አድዋ ላይ ተወለዱ። \n \nጥያቄ: የሰሜን አፍሪቃ የፈረንሳይን ቅኝ ገዢነት ማክተሚያ አብሳሪ እንደሆነ የሚገረው ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የገዢው የፈረንሳይ መንግሥት ፖሊሶች እና ወታደሮች ባካሄዱት ጨካኝ በቀላ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአሸናፊ ከበደ ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ አዲስ አበባ ግንቦት ፰ ቀን ፲፱፻፴ ዓ/ም ተወለዱ። አባታቸው ግራዝማች ከበደ አድነው ሲሆኑ ክልጅነታቸው ጀምሮ የሙዚቃ ስሜትንና ፍቅር ያሳደሩባቸው እናታቸው ወይዘሮ ፋንታዬ ነከሬ ነበሩ። አያታቸው ሊቀመኳስ አድነው ጎሹ ደግሞ የአድዋ አርበኛ እናየንግሥት ዘውዲቱም ታማኝ አማካሪ እንደነበሩ ይነገራል። የሙዚቃ ፍቅርን ገና በልጅነታቸው ያሳደሩባቸው እናታቸው ሲሆኑ ታዳጊው አሸናፊ ገና የዘጠኝ ዓመት ልጅ ሳሉ እኒህ የሚያፈቅሯቸውና ዕድሜ ልካቸውን በኀዘን የሚስታውሷቸው እናታቸው ሞተውባቸዋል። መሠረታዊ ትምህርታቸውን በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት እና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ኮከበ ጽባሕ) ካጠናቀቁ በኋላ በሐረር የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ በኒው ዮርክ ክፍለ-ሀገር ከሚገኘው የሮቼስተር ዩኒቨርሲቲ፣ “ኢስትማን የሙዚቃ ትምህርት ቤት” በ፲፱፻፶፬ ዓ/ም በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመረቁ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው፤ የያሬድ ሙዚቃ ትምሕርት ቤትን መሠረቱ። የዚሁ ትምህርት ቤትም የመጀመሪያው ዳይሬክቶር ከመሆናቸውም ባሻገር በአዲስ አበባው የወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማኅበር (ወ.ወ.ክ.ማ Y.M.C.A.)፤ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የበጎ አድራጎት ድርጅት መርሓ-ዕውራን ትምህርት ቤት እና በመሳሰሉ የወጣቶች ማኅበራት እየተገኙ የሙዚቃ ትምህርት ይሰጡ ነበር። \n \nጥያቄ: የአሜሪካው ሮችስተር ዩኒቨርሲቲ በየት ክፍለ-ሀገር ይገኛል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በኒው ዮርክ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡ \n \nጥያቄ: ሳውዲ አረብያ በደቡብ ምስራቅ የሚያዋስናት ሀገር የትኛው ነው ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የመን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nተክለጻድቅ መኩርያ ተክለጻድቅ መኩርያ በ፲፱፻፮ ዓ.ም. በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ አሳግርት ልዩ ስሙ ሳር አምባ በተባለ ሥፍራ ተወለዱ። ዕድሜያቸው ለትምሕርት ሲደርስ መጀመሪያ ከአባታቸውና ቀጥሎም በአጥቢያቸው ባህላዊውን ትምሕርት እስከቅኔ ያለውን ቀስመዋል። ከዚያም አዲስ አበባ መጥተው አሊያንስ ፍራንሴዝና ተፈሪ መኮንን ትምሕርት ቤት ገብተው የጊዜውን የትምሕርት ደረጃ አጠናቀዋል። ኢጣልያ አገራችንን የወረረች ጊዜም በየካቲት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ.ም. ፍጅት ተይዘው ወደ ሶማሌ ደናኔ ተግዘው ለሦስት ዓመታት ታስረዋል። ከነጻነትም መልስ አገራቸውን በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች አገልግለዋል። መጀመሪያ ተቀጥረው ያገለገሉት በትምሕርትና ሥነጥበብ ሚኒስቴር ነበር። እዚያም ሳሉ በአገራችን ሰው የተጻፈ የአገራችን ታሪክ አንድም ባለመኖሩ በቁጭትና በመቆርቆር ነበር ‘መጻፍ አለብኝ’ ብለው በደንብ ከሚታወቀው ከቅርቡ ጊዜ በቅጡ ወደማይታወቀው የሩቁ ዘመን መጻፍ የጀመሩት። የመጀመሪያውን መጽሐፍ “የኢትዮጵያ ታሪክ ከዓፄ ቴዎድሮስ እስከ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ” የሚለውን በ ፲፱፻፴፰ ዓ.ም. አሳተሙ። ከጫፍ እስከ ጫፍ ጽፈው የመጨረቻውን መጽሐፍ፣ የታሪካችን መጀመሪያ የሚሆነውን “የኢትዮጵያ ታሪክ ኑብያ-አክሱም-ዛጉዬ እስከ ዓፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት” የሚለውን በ፲፱፻፶፩ ዓ.ም. አቅርበዋል። እኒህኑ መጻሕፍት ትምሕርት ሚኒስቴር ታሪክ ለማስተማሪያ በትምሕርት ቤት ተጠቅሞባቸዋል። ተክለጻድቅ ከታሪክ ውጭ የጻፏቸው “የሰው ጠባይና አብሮ የመኖር ዘዴ” እና በሚዮቶሎዢያ (አፈ ታሪክ) ላይ ያተኮረ “ከጣዖት አምልኮ እስከ ክርስትና” የሚሉም መጽሐፎች አሏቸው። ተክለጻድቅ በምድር ባቡር በዋና ጸሐፊነት፥ በቤተ መጻሕፍት ወመዘክር ዋና ሥራ አስኪያጅነት፥ እንዲሁም በፈረንሳይ፥ በእስራኤል፥ በዩጎዝላቪያ በዲፕሎማሲ ሥራ በመጨረሻም የትምሕርትና የባህል ሚኒስቴር ሆነው አግልግለዋል። በፈቃዳቸው ጡረታም ከወጡ በኋላ በምርምር የታገዙ ሦስት ታላላቅ የታሪክ ሥራዎችን አቅርበዋል። ተክለጻድቅ ከረጅም የአገልግሎት ዘመን በኋላ በተወለዱ በ ሰማንያ ስድስት ዓመታቸው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፱፻፺፪ ዓ.ም. አርፈዋል። \n \nጥያቄ: የተክለጻድቅ መኩርያ የመጨረሻው መጽሐፍ ምን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የኢትዮጵያ ታሪክ ኑብያ-አክሱም-ዛጉዬ እስከ ዓፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየባቢሎን ግንብ በመጽሐፍ ቅዱስ ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 11 ዘንድ፣ የባቢሎን ግንብ ሰማይን እንዲደርሱ የተባበሩት ሰው ልጆች የሠሩ ግንብ ነበር። ያ ዕቅድ እንዳይከናወንላቸው ለመከልከል፣ እግዚአብሔር እያንዳንዱ በተለየ ቋንቋ እንዲናገርበት ልሳናታቸውን አደባለቀ። መግባባት አልተቻላቸውምና ስራው ቆመ። ከዚያ በኋላ፣ ሕዝቦቹ ወደ ልዩ ልዩ መሬት ክፍሎች ሄዱ። ይህ ታሪክ ብዙ የተለያዩ ዘሮችና ቋንቋዎች መኖሩን ለመግለጽ እንደሚጠቅም ይታስባል። በትንተና የሰው ልጆች ሁሉ አንድ ኅብረተሰብ ሆነው የሠፈሩባት አገር ሰናዖር ለኤፍራጥስ ወንዝ ቅርብ ነበረች። ባቢሎን በጥንታዊ አካድኛ ምንጭ በተገኘ ባቢሉ (ባብ-ኢሉ) ማለት «የአማልክት በር» ለማለት ነው። በዕብራይስጥ ትርጉም ግን የ«ባቤል» ስም «መደባለቅ» ለማለት ለሚለው ቃል ይመስላል። ከውድቀቱ በፊት የተናገረው ቋንቋ አንዳንዴ «የአዳም ቋንቋ» መሆኑ ይባላል። በታሪክ አንዳንድ ሰው በግምት ያም ሆነ ይህ ቋንቋ መጀመርያው ቋንቋ እንደ ነበር የሚለው ክርክር አቅርቧል። ለምሳሌ ቋንቋው ዕብራይስጥ፣ አራማይስጥ፣ ግዕዝ ወይም ባስክኛ ቢሆንም እንደ ነበር በልዩ ልዩ አስተያየቶች ዘንድ ተብልዋል። \n \nጥያቄ: ሰዎች ወደ ሰማይ ለመውጣት የሰሩት ግንብ ትታሪክ በመጽሐፍ ቅዱስ የት ይገኛል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 11 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nነሐሴ ፳፯ ነሐሴ ፳፯ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፯ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፱ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፰ ዕለታት ይቀራሉ። ፲፮፻፶፰ ዓ/ም ለሦስት ቀናት የጋየውና አስር ሺህ ሕንጻዎችን ያወደመው የሎንዶን ትልቁ እሳት ተነሳ። ፲፯፻፵፬ ዓ/ም የምዕራብ አውሮፓ አገራት ዘመን አቆጣጠራቸውን በለወጡ በሁለት መቶ ዓመታቸው፣ ብሪታንያ የጎርጎራዊ ዘመን አቆጣጠርን ተቀበለች። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በጠላት ወረራ ዘመን የሸዋ አርበኞች ቡልጋ ላይ ተሰባስበው የልጅ ኢያሱን ልጅ መልአከ-ፀሐይ ኢያሱን አነገሡ። አዲሱ 'ንጉሥ' ወዲያው የአርበኞች መሪ ለነበሩት ባላምባራስ አበበ አረጋይ የራስነት ማዕርግ ሰጠ። መልአከ-ፀሐይ ኢያሱ መስከረም ፳፬ ቀን ፲፱፻፴፩ ዓ/ም አረፎ አንኮበር አካባቢ በሚገኘው ዞማ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተቀብሯል። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ጃፓን በተሸናፊነቷ እጇን ሰጠች። ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ነጻነትን አስከትሎ በጃዋሃርላል ኔህሩ ምክትል ፕሬዚደንትነት የሚመራ የሕንድ ጊዜያዊ መንግሥት ተመሠረተ። ፲፱፻፺ ዓ/ም የርዋንዳን ፍጅት አስከትሎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያቋቋመው የወንጀለኛ ፍርድ ቤት ጃን ፖል አካዬሱ የተባለውን የቀድሞ ከንቲባ ላይ ፍርዱን የወንጀለኛነት ፍርድ ፈረደበት። \n \nጥያቄ: በነሐሴ ፳፯ ቀን ፲፮፻፶፰ ዓ/ም አስር ሺህ ሕንጻዎችን ያወደመው የሎንዶን ትልቁ እሳት ለስንት ቀን ቆየ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ለሦስት ቀናት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየኢትዮጵያ ሙዚቃ የመጀመሪያውን ግራማፎን ወይም የሸክላ ማጫወቻ በ፲፰፻፹፱ ዓ.ም. ሄንሪ ደ አርሊንስ እና ኒኮላስ ሊዋንቲቭ ለዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ አመጡላቸው። ይኸውም ማጫወት ብቻ እንጂ ድምጽ አይቀዳም ነበር። በኋላ ግን በዓመቱ በ፲፱፻፺ ዓ.ም. ከንግሥት ቪክቶሪያ የተላኩ የእንግሊዝ መልዕክተኞች በመጡ ጊዜ ግራማፎኑንና ድምፅ መቅጃውን ይዘውላቸው መጡ። ኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ድምፃቸው በዲስክ የተቀረፁት ዓፄ ምኒልክና እቴጌ ጣይቱ ናቸው። ዛሬ በእንግሊዝ አገር በለንደን ከተማ ብሪቲሽ ኢንስቲቲውት ኦፍ ሪኮርድ ሳውንድ በተባለው ሙዚየም ውስጥ ይገኛል። በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ በሸክላ የተቀረፀው የመጀመሪያው ዜማ የነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ስራዎች ሲሆኑ ዘመኑም በዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ነበር። ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ በጀርመን ቆይታቸው ወቅት የጀርመን የሙዚቃ ድርጅት ጠይቋቸው የኢትዮጵያ መዲናና ዘለሰኛ ዜማዎች በ፲፯ አይነት ስልት እየተጫወቱ ተቀርፀዋል። ኩባንያው የተሰማ እሸቴን ዜማዎች በ፲፯ ሸክላዎች የቀረፀው ሲሆን ለዜማው ባለቤት የድካም ዋጋ እንዲሆን በወቅቱ ፲፯ ሺህ የጀርመን ማርክ ከፍሏቸዋል። በዘመኑ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያም አሁንም እነዚህ የነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ብርቅዬ ሸክላዎች በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ውስጥ ተሰብስበው ይገኛሉ። እነዚህ በተቋሙ እጅ ያሉት ፲፮ ሸክላዎች እያንዳንዳቸው ሁለት ዜማዎችን የያዙ ሲሆኑ ባጠቃላይ ፴፪ ዜማዎች ተቀርፀውባቸዋል። እያንዳንዱ የሸክላው ገፅ ላይ A ወይም B ተብሎ ተሰይሟል፣ የዜማው ስም ተፅፎበታል፣ የዜማው ባለቤት ተሰማ እሸቴ ስም አለ፣ ሸክላው ጀርመን ሀገር መሰራቱ እንዲሁም የሸክላው ቁጥር ተጠቅሷል። በ፲፱፻፳፭-፳፮ ዓ.ም. አካባቢ የእነ ፈረደ ጎላ፣ ንጋቷ ከልካይና ተሻለ መንግሥቱ የዜማ ሸክላዎች ብቅ እስከሚሉ ድረስ የነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ሸክላዎች ከ፳ ዓመታት በላይ አቅም ባላቸው ቤተሰቦች ዘንድ በብቸኝነት በግራማፎን ሲደመጡ ቆይተዋል። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ በሸክላ የተቀረፀው የመጀመሪያው ሙዚቀኛ ዜማ የማን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአፍሪካ አፍሪካ (አፍሪቃ) ከዓለም ሁለተኛ ትልቅ አህጉር ነች። ከ869 ሚሊዮን በላይ ህዝብ በዚች አህጉር የሚኖር ሲሆን በጠቅላላ 54 ሀገሮች ይገኛሉ። ከእነዚህም ሀገሮች መሀል ናይጄሪያ በህዝብ ብዛት (127 ሚሊዮን) የመጀመሪያውን ደረጃ ስትይዝ፤ ግብፅና ኢትዮጵያ በ73 ሚሊዮን እና በ72 ሚሊዮን ህዝብ በሁለተኛና በሶስተኛ ደረጃ ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት የህዝብ ብዛት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር ከሌሎች የፖለቲካና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች ጋር በመደማመር ድህነትን በማባባስ ደረጃ ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡ ጂዎግራፊና ሕዝብ ከስድስቱ ዓለማት አንዱ አፍሪካ ነው። አፍሪካ ሰፊ ነው። የዓለምም አራተኛ ክፍል ይሆናል። ከኤውሮጳ የሚለየው በሜዴቲራኒያን ባሕር ነው። ከአሜሪካም በአትላንቲክ ውቅያኖስ ይለያል። ከኒው ዮርክም ቢሆን ወይም ከቦስቶን ከአሜሪካ የሚቀርበው ክፍል ሦስት ሺህ ማይል ይሆናል። ነገር ግን በጊብሮልታር (ጂብራልታር) በኩል የሆነ እንደ ሆነ ለኤውሮጳ በጣም ቅርብ ነው። ከእስያ በኤርትራ ባሕር ይለያያል። የሆነ ሆኖ እስያ ባንድ ወገን ሱዝ ካናል በሚባለው በኩል ከአፍሪካ ጋር ተጋጥሞአል። ሙሴ ሌስፖስ መርከብ እንዲተላለፍ ብሎ አስቆፍሮ ያስከፈተው በዚህ በኩል ነው። \n \nጥያቄ: በአፍሪካ በሕዝብ ብዛት አንደኛ ሀገር ማን ነች?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ናይጄሪያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቢል ክሊንተን ዊልያም ጄፈርሰን «ቢል» ክሊንተን (William Jefferson Bill Clinton) (የትውልድ ስም፦ ዊልያም ጄፈርስን ብላይዝ ፬ኛ፣ እንግሊዘኛ፡ William Jefferson Blythe IV) በነሐሴ 13 ቀን፣ 1938 ዓ.ም.(1946 እ.ኤ.አ.) በሆፕ አርካንሳው የተወለዱ ሲሆን ከ1993 እስከ 2001 እ.ኤ.ኣ. ድረስ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ነበሩ። ፕሬዝዳንት ከመሆናቸዉ በፊት አምስት ጊዜ የአርካንሳው ስቴት አስተዳዳሪ ነበሩ። \n \nጥያቄ: ቢል ክሊንተን ፕሬዝደንት ሳይሆኑ በፊት ስንቴ የአርካንሳው ግዛት አስተዳዳሪ ሆነው ሰሩ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አምስት ጊዜ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: ደቡባዊ ሮዴዢያ ራሱን የሚያስተዳድር የእንግሊዝ ግዛት የሆነው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ1916 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: ከ1981 እ.ኤ.ኣ. ለሃያ ዓመት የሴኔጋል ፕሬዝዳንት የነበሩትት አብዱ ዲዮፍ መጀመሪያ ወደ ስልጣን የመጡት በማን አማካኝነት ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በሊዎፖልድ ሴንግሆር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኤዎስጣጤዎስ በግዕዝ ኤዎስጣቴዎስ ወይም ዮስጣቴዎስ፣ ከሐምሌ ፭ ቀን ሺ፪፻፷፭ – ሺ፪፫፵፬ በኢትዮጵያ ሰለሞናዊ መንግሥት አገዛዝ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ታላቅ መሪ የነበሩ አባት ናቸው። በጣም አጥብቀው ከሚያስተምሩት ትምህርት ስለ ሰንበት መከበር ነበረ። ተከታዮቻቸው የኤዎስጣጤዎስ ቤት ወይም በግል ሲጠሩ ኤዎስጣጤዎሳውያን ይባሉ ነበር ለተዋህዶ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ ናቸው። የኤዎስጣጤዎስ መጀመሪያ ስማቸው ማዕቀበ እግዚእ ሲሆን ከእናታቸው ከስነሕይወትና ከአባታቸው ከክርስቶስ ሞዐ ሐምሌ ፳፩ ቀን ፩ሺ፪፷፭ ተወለዱ። እኒህም ደጋግና እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎች ነበሩ ። ኤዎስጣጤዎስ የታወቀውን ደብራቸውን (ደብረ ፀራቢን) የመሠረቱት የተወለዱበት ቦታ እዛው (እንድርታ) እንደሆነ ገድላቸው ይገልፃል። በወጣትነታቸው ዘመን በሺ፪፸፪ አካባቢ ከአጎታቸው አባ ዳንኤል (የደብር ስማቸው አባ ዘካርያስ) ቆርቆር (ደብረ ማርያም) አስተዳዳሪ ጋር እንዲኖሩ ወደ ገራልታ ይላካሉ። አባ ዳንኤልም ኤዎስጣጤዎስን ተቀብለው ተገቢውን የሃይማኖት ትምህርትና የደብር ሕይወትን ካስተማሩ በኋላ ማዕቀበእግዚእ በ፲፭ ዓመቱ ቅስና ሥራዬ መሆን አለበት ብሎ በወሰደው ውሳኔ መሠረት ስሙ ኤዎስጣጤዎስ ተብሎ ተሰየመ። ኤዎስጣጤዎስ ከአባ ዳንኤል የቅስና መዐረጋቸውን ካገኙ በኋላ የራሳቸውን ደብር በ(ሰራይ) መሠረተው በዚያም በማስተማር ብዙ ተማሪዎችን አፈሩ ። በሰንበት ላይ ያተኮረ አመለካከታቸውን ለይተው ያስተምሩ ነበር ፣ የሚቃወማቸው አቡነ ያእቆብ ፫ኛው አስኪመጣ ድረስ። ከዛ ግን ከተከታዮቻቸው ከባካርሞስ ፣ መርቆርዮስ ፣ ገብረእያሱ ጋር ኢትዮጵያን ለቀው ወደ ግብፅ (ካይሮ) ገብተው በአሌክሳንድሪያው ጳጳስ ቢንያም ፪ኛው ፊት በሰንበት ባላቸው አመለካከት ፀንተው ከዛም ወደ ኢየሩሳሌም አምርተው በመጨረሻም የሕይወታቸው ማብቂያ ወደ ሆነችው አርሜኒያ ገብተው ኖሩ። \n \nጥያቄ: የኤዎስጣጤዎስ ወላጆች ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ እናታቸው ከስነሕይወትና ከአባታቸው ከክርስቶስ ሞዐ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ በሃገራችን ኢትዮጵያ ስም አጠራራቸው ከከበረ አባቶች አንዱ ጻድቅ ናቸው። ጻድቁ የተወለዱት በአምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ አካባቢ ሲሆን ወላጆቻቸው ንጉሥ ይስሐቅ እና ቅድስት እድና ይባላሉ ። የተወለዱበት አካባቢም ሮም ነው ። ስማቸው ብዙ ዓይነት ነው። ወላጆቻቸው ዘሚካኤል ሲሏቸው በበርሃ ገብረአምላክ ተብለዋል። በኢትዮጵያ ደግሞ አረጋዊ ይባላሉ። አቡነ አረጋዊ ምንም የንጉሥ ልጅ ቢሆኑም በልጅነታቸው መጻሕፍትን ተምረው ነበርና ጠፍተው ገዳም ገቡ። በዚያም በገዳመ ዳውናስ (ግብጽ) የታላቁ ቅዱስ ጳኩሚስ ደቀ መዝሙር ሆነው ከነ አባ ቴዎድሮስ ጋር ሥርዓተ መነኮሳትን ተምረዋል። ከመነኮሱ ከዓመታት በኋላም ወደ ሃገራቸው ሮም ተመልሰው በማስተማር ሰባት ያህል የቤተ መንግሥት ሰዎችን ወደ ምናኔ ማርከዋል። \"የት ልሒድ?\" ብለው ሲያስቡም ቅዱስ መልአክ በክንፉ ጭኖ ወስዶ ኢትዮጵያን አሳያቸው። ተመልሰውም ለስምንት ባልንጀሮቻቸው \"ሃገርስ ባሳየኋችሁ! ሐዋርያ ሳያስተምራት በሕጉ በሥርዓቱ ጸንታ የምትኖር\" ብለው ከስምንቱ ጋር ከቃልኬዶን ጉባዔ በኋላ በ፬፻፶፩ ዓም ወደ ኢትዮጵያ መጡ ። ከዘጠኙ ቅዳሳን ወደ ኢትዮጵያ ከሮምና ከመካከለኛው ምሥራቅ ከፈለሱት አንዱ አቡነ አረጋዊ ናቸው ። በዚህ ጊዜም እናታቸው ቅድስት እድናና ደቀ መዝሙራቸው አባ ማትያስ አብረው ነበሩ። ወደ ሃገራችን የመጡ በአራት መቶ ሰባዎቹ አካባቢ ሲሆን አልዓሜዳ በክብር ተቀብሏቸዋል። በቤተ ቀጢን (አክሱም) ተቀምጠውም መጽሐፍትን እየተረጎሙ ወንጌልን እየሰበኩ ቆይተዋል ። አቡነ አረጋዊ ለብዙ ጊዜ በዓት ፍለጋ ደክመዋል ። በመጨረሻም ደብረ ዳሞ ማረካቸዋለች ። ዘጠና ዘጠኝ አመት ሲሞላቸው ጌታ በመንፈቀ ለሊት ተገልጾ ምድራዊ መንግስትህን ትተህ ስላገለገልከኝ ህልፈት ሽረት የሌለባት ሰማያዊ መንግስቴን አወርሰሃለሁብሎ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ በስምህ የተማጸነውን እስከ አስራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ አንተም ከሞት ገጽ ትሰወራለህ ብሎ ተስፋቸውን ነገራቸው፡፡ እሳቸው መነኮሳቱን ሰብስበው ከእንግዲህ በሥጋ አታዩኝም ብለው ነግረዋቸው አበምኔት (የገዳም አባት ወይም አለቃ) ሾመውላቸው ጥቅምት አሥራ አራት ቀን በዚያው በደብረ ዳሞ ተራራ በስተምስራቅ አቅጣጫ እንደሄኖክ እንደ ኤልያስ ተሰውሯል ፡፡ \n \nጥያቄ: ለአቡነ አረጋዊ ወላጆቻቸው ያወጡላቸው ስም ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ዘሚካኤል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nመርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ ብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ጅሩ ቆላ ውስጥ እምባጮ መግደላዊት በሚባል ሥፍራ መጋቢት ፲፯ ቀን በ፲፰፻፺፩ ዓ/ም ተወለዱ። በቤተ ክርስቲያን የመጀመሪያ ትምህርታቸውን እስከ ዳዊት ድረስ ካጠናቀቁ በኋላ የዜማ ትምህርት ተከታትለው ጾመ ድጓ እና ድጓን ዘልቀዋል። ቀጥሎም የቅኔ ትምህርታችውን አጠናቀው በ ፲፱፻፭ ዓ/ም በአሥራ አራት ዓመት ዕድሜያቸው በወንበር ፀሐፊነት የመጀመሪያ ሥራቸውን ጀመሩ። የመጻሕፍተ ሐዲሳትን ትርጓሜ፤ የዮሐንስ አፈወርቅን ትርጓሜ፤ እንዲሁም የመቅድመ ወንጌልን ትርጓሜ ትምህርት ያጠናቀቁት እኝህ ታላቅ ሰው ብርሃንና ሰላም (ጋዜጣ) የተሰኘው ጋዜጣ ሲመሠረት የጋዜጣው ዋና አዘጋጅ በመሆን፣ ቀጥለውም በተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት የግዕዝና የአማርኛ አስተማሪ በመሆን አገልግለዋል። ከፋሺስት ወረራ በኋላ ከ፲፱፻፴፫ ዓ/ም እስከ ፲፱፻፷፫ ዓ/ም ድረስ በተለያዩ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በኃላፊነት ሲያገለግሉ ቆይተዋል። ሥነ ጽሑፍንና ታሪክን በተመለከተ፣ አሥራ ሦስት መጻሕፍትን የደረሱ ሲሆን፣ ሰባት መጻሕፍት ደግሞ ተርጉመው አቅርበዋል። እንዲሁም የተለያዩ ጽሑፎችን አሰባስበው ከማዘጋጀታቸው ባሻገር፣ የቅዱሳት መጻሕፍት ሥራዎችም ከሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ጋር በትብብር አዘጋጅተዋል። \n \nጥያቄ: ብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ መቼ ተወለዱ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ መጋቢት ፲፯ ቀን በ፲፰፻፺፩ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቦትስዋና ቦትስዋና ወይም በይፋ የቦትስዋና ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ Republic of Botswana ሰጿና፡ Lefatshe la Botswana) በደቡባዊ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ አገር ናት። ቦትስዋና የቀድሞ የብሪታንያ ቅኝ ግዛት ስትሆን ነፃነቷን በመስከረም ፳ ቀን ፲፱፻፶፱ ዓ.ም. ከተቀዳጀች በኋላ መሪዎቿ በነፃ ዴሞክራሲያዊ ምርጫዎች ተመርጠዋል። ቦትስዋና ሜዳማ ስትሆን ከሰባ ከመቶ በላይ በካለሃሪ በርሃ የተሸፈነች ናት። በደቡብና ደቡብ ምሥራቅ ከደቡብ አፍሪካ፣ በምዕራብና ሰሜን ከናሚቢያ እና በሰሜን ምሥራቅ ከዚምባብዌ ጋር ትዋሰናለች። ከዛምቢያም ጋር በደንብ ያልተወሰነ ቢበዛ በመቶ ሜትር የሚቆጠር ወሰን አላት። \n \nጥያቄ: ቦትስዋና የት አህጉር የምትገኝ ሀገር ነች?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አፍሪካ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቴምፕላርስ ቴምፕላር ወይም በሙሉ ስማቸው የክርሰቶስ እና የሰለሞን መቅደስ ምስኪን ወታደሮች የሚባሉት በጣም ታላቅ እና ሃይለኛ ከነበሩት ክርስቲያናዊ ወታደራዊ ስርአቶች ውስጥ ዋነኞቹ ናቸው። ይህ ስርዓት በ1088 ዓ.ም. ከተካሄደው አንደኛው የመስቀል ጦርነት በኋላ ማለትም በ1110 ዓ.ም. አዲስ የተቋቋመውን የእየሩሳሌም መንግስት ከእስላሞች ለመከላከልና ወደ ከአውሮፓ ወደ እየሩሳሌም የሚጎርፉትን ተሳላሚዎች ደህንነት ለመጠበቅ የተመሰረተ ነው። ቴምፕላሮች የተዋቀሩት በገዳማዊ ስርዓት ሲሆን ይኸውም የሲሰተርሲያን ስርዓት መስራች የነበረው የክላርቮው በርናርድ በዘረጋላቸው ህግጋት መሰረት ነው። ቴምፕላሮች ከብዙ መሳፍንት ጋር ግንኙነት ስለነበራቸው እና ጳጳሱም እነሱ ከሚቆጣጠሩዓቸው ቦታዎች ሁሉ ግብርና አስራት እንዲሰበስቡ ስለፈቀደላቸው በአጭር ጊዜ ውስጥ ዝነኛና ሃይለኛ ለመሆን ችለዋል። ቴምፕላሮቹ አራት ዋና ክፍሎች የነበሩአቸው ሲሆን እነዚሁም ዋነኞቹ ወታደሮች ወይም ናይትስ የሚባሉት ሙሉ የፈረሰኛ ትጥቅ የታጠቁ ከዝቅተኛ የህብረተሰቡ ክፍል የተውጣጡት ወይም ሰርጀንትስ በመባል የሚታወቁት፤ መለስተኛ የፈረሰኛ ትጥቅ የታጠቁ ገበሬዎች ዋነኛው ስራቸው የስርዓቱን ንብረት ማስተዳደር የነበረ፤ እንዲሁም ካህናት ስራቸው የስርዓቱን መንፈሳዊ ህይወት መከታተል የነበረ ናቸው። \n \nጥያቄ: ክላርቮው በርናርድ የመሰረተው የገዳማውያን ሥርዓት ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የሲሰተርሲያን ስርዓት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nነሐሴ ፳፰ ነሐሴ ፳፰ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፰ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፰ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፯ ዕለታት ይቀራሉ። 1862 - የፕሩሲያ (ጀርመን) ሠራዊት 3ኛ ናፖሊዎንን ከ100,000 ጭፍሮች ጋር በሰዳን ውግያ አሸነፈ። 1890 - በኦምዱርማን ውግያ ሱዳንን የእንግሊዝ ሠራዊት ድል በማድረግ ቅኝ አገር አደረጉት። 1935 - በ2ኛ አለማዊ ጦርነት ኢጣልያ በጓደኞቿ ሃያላት (በጀርመን ኃይል) ተወረረች። 1946 - የቻይና ኃያላት የደቡብ ኮርያ ደሴቶችን በቦምብ ደበደቡ። ፲፱፻፸፱ ዓ/ም በቡሩንዲ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ሻለቃ ፒዬር ቡዮያ የአገሪቱን ፕሬዚደንት ዣን ባፕቲስት ባጋዛን ከሥልጣን አስወረዱ። \n \nጥያቄ: በ1890 በተደረገው የኦምዱርማን ውግያ ሱዳንን ድል ያደረጋት የማን ሀገር ሠራዊት ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የእንግሊዝ ሠራዊት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nላሊበላ ላሊበላ በኢትዮጵያ፣ በአማራ ክልል በቀድሞው የወሎ ክፍለ ሃገር የምትገኝ ከተማ ነች። በ ላይ የምትገኘው የላሊበላ ከተማ ከባህር ጠለል በላይ 2,500 ሜትር ከፍታ ያላት ስትሆን የህዝቡም ብዛት ወደ 11,152 ነው። 1 ላሊበላ ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት ቅዱሳን ከተማዎች መካከል ከአክሱም ቀጥላ በሁለተኛነት ደረጃ የምትገኝ ከተማ ስትሆን፣ ለአብዛኞቹ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንደ ዋና የእምነት ማእከል በመሆን ታገለግላለች። የላሊበላ ነዋሪዎች በአብዛኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች ናቸው። የላሊበላን ከተማ በዋነኛነት ታዋቂ ያረጉዋት ከክ.ል. በኋላ በ13ኛው መቶ ክፍለዘመን እንደ ተሰሩ የሚነገርላቸው 11 አብያተ-ክርስቲያናት ናቸው። በኢትዮጵያ ትውፊት መሰረት እነዚህ አብያተ-ክርስቲያናት በንጉሥ ላሊበላ ዘመን በቅዱሳን መላዕክት እረዳትነት እንደተሰሩ የሚታመን ሲሆን ግርሃም ሃንኮክ የተባለው እንግሊዛዊ ፀሃፊ ግን እኤአ በ1993 ዓ.ም ባሳተመውና The Sign and the Seal በተባለው መጽሃፉ አብያተ-ክርስቲያናቱን በማነፁ ሥራ ላይ ቴምፕላርስ የሚባሉት የመስቀል ጦረኞች ተካፍለዋል ሲል አትቷል ነገር ግን ማረጋገጫ አልነበረውም። እነዚሀ አብያተ-ክርስቲያናት ውስጥ አርባ ትንንሽ ቤተክርስቲያኖች አሉ። \n \nጥያቄ: ላሊበላ ከባህር ጠለል በምን ያህል ከፍታ ላይ ትገኛለች?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 2,500 ሜትር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nባሕር-ዳር ባሕር-ዳር በድሮ ስሙ ባሕር ዳር ጊዮርጊስ በሰሜን-ምዕራብ ኢትዮጵያ የምትገኝ ከተማ ስትሆን የአማራ ክልል ዋና ከተማ ናት። ከተማዋ በቀድሞው ጎጃም ክፍለ ሓገር ውስጥ ከጣና ሐይቅ ደቡባዊ ጫፍ ላይ ተቀምጣ ስትገኝ ባህር ዳር እንደ መቀሌና ደሴ የወረዳ ደረጃ ያላት ስፔሻል(ልዩ) ዞን ናት። በማዕከላዊ ስታትስቲክ ትመና የ167,261 ህዝብ ከነሱም መሃከል የ86,355 ወንዶችና የ80,906 ሴቶች መኖሪያ ከተማ ናት። 1700 ሜትር ከባሕር ወለል በላይ ትገኛለች። ባሕር-ዳር ከአዲስ አበባ 565 ኪ.ሜ ወደ ሰሜን-ሰሜን ምዕራብ ትገኛለች። ባህር ዳር ከጢስ አባይ በ30 ኪሎሜትር ስለምትርቅ ለጎብኚዎች አመቺ ቦታ ላይ ናት። ባህር ዳር የአንድ የአስፋልት ንጣፍ ያለው ኤርፖርት የሰፊ ገበያና የተለያዩ የመዝናኛ ቦታዎች እና ታሪካዊ እና ጥንታዊ ግዳማት መግኛ ቦታ ናት። ባሕርዳር ከተማ የምትገኘዉ በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍል፣ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት፣ በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ከአዲስ አበባ በ 565 ኪሜ ርቀት ላይ ነው፡፡ አስትሮኖሚያዊ መገኛ ቦታዋ በ 11º 38’ በሰሜን ላቲቲውድ እና በ37º15’ ምስራቅ ሎንግቲውድ ነው፡፡ በአፈ ታሪክ እንደሚነገረው የባሕር-ዳር ስያሜን ያወጡት አፄ ሠርጸ ድንግል ሲሆኑ እሳቸውም ይሕን ታቦት የት እናስቀምጥ ተብለው በተጠየቁ ጊዜ \"ከባሕሩ-ዳር\" አድርጉ የተባሉ ሰወች ለመንደሩ ባሕር-ዳር ብለው ስያሜ አወጡለት ይባላል። ባሕር-ዳር ከተማ የተቆረቆረችው በ1915 ዓ.ም ነው ፡፡ ባሕር-ዳር በክልሉ ከሚገኙ የሪፎርም ከተሞች አንድዋ ስትሆን፤ የከተማ አስተዳደር፣ 3 ሜትሮፖሊታን ክ/ከተማዎች፣ የከተማ አገልግሎት ጽ/ቤት፣ 9 የከተማ ቀበሌዎችና 4 የገጠር ቀበሌዎች አሏት፡፡ ከተማዋ በ1998 ዓ.ም የተቀናጀ ልማት ፕላን አላት፡፡ የተቆረቆረችበትን ዓመት፣ የቆረቆሩትን ቀደምት ሠዎች፣ የሠፈሮችን ስሞች፣ ለባሕር-ዳር የተገጠሙትና የተዘፈኑ ታሪካዊ ግጥሞችና ስነ ቃሎች፣ ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከጎጆ ቤት ወደ አሁኑ ይዞታው አመጣጥ (ባሕር-ዳርን ስናስብ ጊዮርጊስን ሚካኤልን እና ገበያውን ከገበያው አካባቢ የነበረውን ፍርድ ቤት ነጣጥሎ ማየት አይቻልም የሚል አስተያየት ስላለ ነው)፣ ባሕር-ዳር እንደባሕር ዳርነቱ ከመቆርቆሩ በፊት በሚካኤል እና በሽመምብጥ ሠፈር አካባቢ ስለነበረው አሰፋፈር፣ ስለማዘጋጃቤቱ፣ ስለ አውቶቡስ ተራው፣ ስለ ድባነቄ ተራራ፣ እና ስለ መሳሉት፣ ስለፖሊቴክኒክ፣ ስለዓባይ ወንዝና ድልድዩ፣ ስለዓባይ ወንዝና ስለጣና ሐይቅ መገናኛ እና ስለሌሎችም ቁልፍ ነገሮችን ማቅረብ የሚችሉ አፈታሪኮች አሉ። \n \nጥያቄ: ባሕር ዳር ከተማ በሰሜናዊ ጫፍ የምትገናኘው ከየትኛው ሐይቅ ጋር ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከጣና ሐይቅ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nነሐሴ ፳፯ ነሐሴ ፳፯ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፯ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፱ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፰ ዕለታት ይቀራሉ። ፲፮፻፶፰ ዓ/ም ለሦስት ቀናት የጋየውና አስር ሺህ ሕንጻዎችን ያወደመው የሎንዶን ትልቁ እሳት ተነሳ። ፲፯፻፵፬ ዓ/ም የምዕራብ አውሮፓ አገራት ዘመን አቆጣጠራቸውን በለወጡ በሁለት መቶ ዓመታቸው፣ ብሪታንያ የጎርጎራዊ ዘመን አቆጣጠርን ተቀበለች። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በጠላት ወረራ ዘመን የሸዋ አርበኞች ቡልጋ ላይ ተሰባስበው የልጅ ኢያሱን ልጅ መልአከ-ፀሐይ ኢያሱን አነገሡ። አዲሱ 'ንጉሥ' ወዲያው የአርበኞች መሪ ለነበሩት ባላምባራስ አበበ አረጋይ የራስነት ማዕርግ ሰጠ። መልአከ-ፀሐይ ኢያሱ መስከረም ፳፬ ቀን ፲፱፻፴፩ ዓ/ም አረፎ አንኮበር አካባቢ በሚገኘው ዞማ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተቀብሯል። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ጃፓን በተሸናፊነቷ እጇን ሰጠች። ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ነጻነትን አስከትሎ በጃዋሃርላል ኔህሩ ምክትል ፕሬዚደንትነት የሚመራ የሕንድ ጊዜያዊ መንግሥት ተመሠረተ። ፲፱፻፺ ዓ/ም የርዋንዳን ፍጅት አስከትሎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያቋቋመው የወንጀለኛ ፍርድ ቤት ጃን ፖል አካዬሱ የተባለውን የቀድሞ ከንቲባ ላይ ፍርዱን የወንጀለኛነት ፍርድ ፈረደበት። \n \nጥያቄ: በነሐሴ ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ/ም በጣልያን ወረራ ዘመን የሸዋ አርበኞች ቡልጋ ላይ ተሰባስበው ያነገሡት ማንን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ መልአከ-ፀሐይ ኢያሱን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጎግል ስለኮሮና ቫይረስ መረጃዎችን ለማቅረብ የኤስ ኦ ኤስ ማንቂያን ወደ ስራ ማስገባቱን አስታወቀ። ኩባንያው በትናንትናው ዕለት ወደ ስራ ያስገባው ማንቂያ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ አስፈላጊ መረጃዎችን ለማድረስ ያግዛል ተብሏል። ስለኮሮና ቫይረስ እና ተያያዥ ጉዳዮች ሰዎች መረጃዎችን በሚፈልጉበት ወቅት ጎግል “በነጭ ካርድ መደብ” ላይ የኤስ ኦ ኤስ ማንቂያውን በማሳየት ተፈላጊውን መረጃ ለተጠቃሚዎቹ በቀጥታ ያጋራልም ነው የተባለው። ጎግል ለዓለም አቀፍ መረጃ ፈላጊዎች በማንቂያው ላይ የዓለም ጤና ድርጅት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዳይሬክተር ጄኔራሎችን አድራሻ ማካተቱንም አስታውቋል። አስፈላጊ ከሆነም በሂደት ማንቂያውን ለአካባቢያዊ መረጃ ፈላጊዎች በሚሆን መልኩ እንደሚያካትትም ገልጿል። በቀጣይም ስለ ኮሮና ቫይረስ ጠቃሚ መረጃ፣ ያለበትን ሁኔታ እና ጥያቄና መልሶችን ያካተቱ አንቀጾች ያሉበት “የእርዳታ እና መረጃ” ማፈላለጊያን ከዓለም ጤና ድርጅት አድራሻ ጋር በማያያዝ አቀርባለሁ ብሏል። ኩባንያው በአስፈላጊ እና ወሳኝ ወቅት ላይ ተጨማሪ የመረጃ ማሻሻያ እንደሚያደርግ በመግለፅ የማንቂያ ስርዓቱ ለኮሮና ቫይረስ ግብዓት የሚሆኑ መረጃዎችን በቀላሉ እንዲገኙ ያስችላል ነው ያለው። በሞባይሎች እና ድረ ገፆች ላይ የሚገኘው ኤስ ኦ ኤስ ማንቂያ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ ችግሮች በሚፈጠሩበት ወቅት እንዲሁም በአጠቃላይ የሰዎች ደህንነት አደጋ ላይ በሚሆንበት ወቅት ጥቅም ላይ የሚውል ነው። ከዚህ ባለፈም ኩባንያው ለቻይና የቀይ መስቀል ማህበር የ250 ሺህ ዶላር ድጋፍ ያደረገ ሲሆን፥ በመረጃ ማፈላለጊያ ገጹ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ በተከፈተ ዘመቻ ከ800 ሺህ ዶላር በላይ መሰብሰብ ተችሏል። ምንጭ፦ ጎግል \n \nጥያቄ: ስለኮሮና ቫይረስ መረጃዎችን ለማቅረብ የኤስ ኦ ኤስ ማንቂያን ወደ ስራ ያስገባው ድርጅት ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ጎግል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኢትዮ ሬይን ሜከርስ ኢትዮ ሬይን ሜከርስ (Ethio Rain Maker) በኢትዮጵያ ውስጥ ዛፎች በመትከል ረሃብን ለመከልከል የተቋቋመ ቡድን ነው። አሁን ወደ ምድረ በዳ መጥተው በወንድማማችነት ገነት ይሠራሉ። በድርቅ አፈር ውስጥ የሚተክሉት ዘር ታላቅ ደን ይሆናል፤ ምድሪቱ እንደገና በሙሉ እስክትሸፈን ድረስ ረጀም ዛፎች በዝተው አረንጓዴ ክንፎቻቸውን ይዘረጋሉ። ሀገራችን ኢትዮጵያ በአለም መገናኛ ብዙሃን በረሃብ ስትጠራ፣ ህዝቦችዋ በጠኔ ሲሰቃዩ ዘመናት ተቆጥረዋል። የወገኖቻችን ስቃይ፣ የሀገራችን ኋላ ቀርነት በኢትዮጲያዊነታችን እያንዳንዳችንን ይመለከተናል። ላለፉት ሰላሳ አመታት በጎ አድራጊ ድርጅቶች በአይነትም ሆነ በጥሬ ገንዘብ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እንደረዱን መረጃ አውጥተዋል። የኛ ስቃይ ግን አላበቃም። መከር ሲመጣ ሰብል ከማጨድና ምርት ከመሰብሰብ ይልቅ ለልመና እጁን የሚዘረጋ ኢትዮጲያዊ ቁጥር በሶስት እጥፍ ጨመረ። ይህ ሂደት መቆም አለበት። እንዴት? አበው “ነገርን ከስሩ …” እንደሚሉት የሁሉም ችግር መፍትሔው ያለው ከመነሻው ላይ ነው። የኛ ረሐብ መንስዔው ምንድነው? በአጭሩ ለመግለጽ ያህል ለረሐባችን መንስዔ የዝናብ አለመኖር (ድርቅ) መሆኑን ከረሐባችን ታሪክም ሆነ ጥናቱን ካካሄዱት ምሁራን መረዳት ይቻላል። ዛሬም ቢሆን ገበሬው ዝናብ በማጣቱ ሰብሉ መበላሸቱን ከአንደበቱ እየሰማን ነው። ጦርነትን ለማቆም የጦርነት መነሻ ሃሳቦችን ማስወገድ እንጂ ጦርነትን ከጦር ሜዳ ማስቆም እንደማይቻል ሁሉ የሃገራችንንም ረሃብ ከመንስዔው እንንቀለው። ኢትዮ ሬይን ሜከርስ፣ ኢትዮጵያ ዉስጥ ደን ማደነን (አፎረስቴሽን) ችግራችንን ከመቅረፊያ መንገዶች አንዱ እንደሆነ በማመን የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም ችግኞችን መትከል ጀምሯል። በ1995 ዓ.ም. ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለ አደራ ጋር በመተባበር በእንጦጦ የተፈጥሮ መናፈሻ አስር ሺህ ችግኞችን ተክሎ ሰባ ሁለት ከመቶው (7167) ፀድቋል። በ1996 ክረምት ደግሞ ሀምሳ ሺህ ችግኞችን ለመትከል አቅዶ ሀያ ከመቶው ተጠናቋል። በአሰላ፣ በመቀሌና በባህር ዳር አንድ ሺህ ዛፎችን የሚይዙ የተፈጥሮ መናፈሻዎችንን በመስራት ላይ ነን። በ1997 ለሀገራችን የሺህ አመት ስጦታ እንስጥ በሚል መነሻ ሀሳብ እያንዳንዱ ኢትዮጲያዊ አንድ ዛፍ ተክሎ የሚንከባከብበትን እቅድ አውጥተናል። ከነዚህም አንዱ አንድ ዛፍ ለአንድ ተማሪ ነው። የሃገራችን የዘመናት ችግር በአንድ አመትና በጥቂት ሰዎች ጥረት አይፈታም። ለዚህ አላማ መሳካት የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥረትና እገዛ ያስፈልጋልና ሃገራችንን ከረሐብ ለመታደግ አብረን ዛፍ እንትከል። እንንከባከብም። \n \nጥያቄ: ኢትዮ ሬይን ሜከርስ በ1995ዓ.ም. እንጦጦ አካባቢ ከማን ጋር በመሆን አስር ሺህ ያህል ችግኝ ተከሉ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለ አደራ ጋ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም ለአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነርነት በእጩነት ቀረቡ። በሚኒስትር ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ኢትዮጵያን በመወከል ለአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነርነት በእጩነት መቅረባቸው ነው የተነገረው። የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር በመሆን ያገለገሉት ፕሮፌሰር ሂሩት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቋንቋና የቋንቋ ጥናት ክፍል ለረጅም ዓመታት በመምህርነት አገልግለዋል። \n \nጥያቄ: ለአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነርነት እጩ የቀረቡት ማን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቅልልቦሽ ቅልልቦሽ የኢትዮጵያ ህጻናት በጠጠር የሚጫወቱት ሲሆን አጨዋወቱም አንዱዋን ጠጠር ወደአየር በማጉናት እሱዋ ባየር ላይ እያለች የተቻለን ያክል ጠጠር ከመሬት ማፈስ ነው። ባየር ላይ ያለችው ጠጠር ስትመለስ በተጫዋቹ እጅ \"መቀለብ\" ወይም \"መያዝ\" ይኖርባታል። ሳትያዝ መሬት ላይ ከወደቀች፣ ጨዋታው አለቀ ማለት ነው። ጨዋታው \"ጠጠር\" በመባልም ይጠራል። ብዙ አይነት የቅልልብልቦሽ ጨዋታዎች ሲኖሩ፡ በጣም የታወቀው \"ዓይጥ አለብሽ\" በመባባል የሚጫወቱት ነው። ልጆቹ ሁለት ወይም ሶስት ይሆኑና፡ አምስት ቆንጆ ድብልብል ጠጠሮች፡ ስፋትና ርዝመታቸው ከግማሽ ኢንች የማይበልጡ፡ ይለቅሙና መሬት ይቀመጣሉ። ቀድሞ \"ብጀ\" ያለ መጀመርያ ይጀምራል። ብጀ ማለት ብጀምር ማለት ነው። ያንን ለማለት እሽቅድምድም ነው።\"ብቀ\" ያለ ከርሱ የሚከተል ነው ማለት ነው፡፡ ብቀ ማለት ብቀጥል ማለት ነው። ሁለት ልጆች እኩል \"ብቀ\" ካሉ በድምጽም ቢሆን ቀድሞ \"ብ!\" ከአፉ የወጣው ሰው ሁለተኛነቱን ያገኛል። \"ብቀጣጥል!\" ያለ ሶስተኛ ነው። \"እንጀራ ብጋግር!\" ያለ አራተኛ ነው። አምስተኛ ካለ \"ወጥ ብሰራ!\" ብሎ ተራውን ያሳውቃል። በዚህ ተራ ተስማምተው ጀማሪው ይጀምራል። \n \nጥያቄ: በቅልብልቦሽ ጨዋታ አራተኛ ለሆነ ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ እንጀራ ብጋግር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአሦር አሦር (አሹር) ማለት በጥንታዊ ዘመን በላይኛ ጤግሮስ ወንዝ አጠገብ የተገኘ ከተማና አካባቢው ነበረ። በኋለኛ ጊዜ የአሦር መንግሥት ሃይለኛ ሆኖ መላ መሬት እስከ ግብጽ ድረስ ገዛ። በጥንታዊ አሦር ከተማና በጤግሮስ አጠገብ ያሉትም ተራሮች እስከ ዛሬው አርሜንያ ድረስ 'የአሦር ተራሮች' ይሰየሙ ነበር። በኦሪት ዘፍጥረት መሠረት አሦር (አሹር) ከኖኅ ልጅ ሴም ልጆች አንዱ ሲሆን፥ ከሰናዖር ወጥቶ አንዳንድ ከተማ ሠራ። በአሦራውያንም እምነት ዘንድ 'አሹር' ከተማውን የመሠረተው አምላክ ስም ነበረ። ከቅድመኛው ዘመን አውራጃው ሹቡር ተብሎ ከሰናዖር (ሹመር)፣ ማሪ ወይም ከአካድ ይገዛ ነበር። ሹቡር በታላቁ ሳርጎን መንግሥት ውስጥ ክፍል ሆኖ ጉታውያን እስከ አጠፉት ድረስ ቆየ። በኋላ እስከ 1879 ዓክልበ. ግ. ከኡር 3ኛ ሥርወ መንግሥት ይቆጣጠር ነበር። የዑር መንግሥት ሲወድቅ የአሦር ከተማ ነገሥታት ሊሙ ስሞች ይመዘገባሉ። በዚህ ወቅት አሦር ከተማ-አገር ብቻ ነበረ። ሆኖም አሦራውያን የብረታብረት ንግዳቸውን ለማስፋፋት በማሰብ አንዳንድ ቅኝ-ከተማ (ካሩም) በሐቲ (ዛሬው ቱርክ) ውስጥ መሠረቱ። ከነዚህም ዋነኛው ካነሽ የተባለው ከተማ ነበር። በ1720 ዓክልበ. ግ. አሞራዊው ንጉሥ 1 ሻምሺ-አዳድ አገሩን ከነአሦር ከተማ አቀና። ልጁን 1 እሽመ-ዳጋን (1688-1678 ዓክልበ.) በአሦር ላይ ሾመው። ነገር ግን የባቢሎን ንጉስ ሃሙራቢ ድል አድርጎት ዙሪያው ወደ ባቢሎን መንግሥት ተሳለፈ። ከትንሹ እስያ ይካሄድ የነበረው የብረታብረት ንግድ በዚያን ጊዜ ተቋረጠ። ለሚከተለው መቶ አመት አሦር ለባቢሎን ተገዥ ነበር። በ1507 ዓክልበ. ግ. ባቢሎን ለካሣውያን ከወደቀ በኋላ፥ አሦር በሚታኒ መንግሥት (ሑራውያን) በ1441 ዓክልበ.ግ. ይሸነፍ ነበር። ሚታኒ በኬጢያውያን ግፊት ሲወድቅ ግን የአሦር ንጉስ አሹር-ኡባሊት ነጻነቱን አዋጀ (1366 ዓክልበ. ያህል)። ከዚህ በላይ ይህ አሹር-ኡባሊት የራሱን ልጅ ኩሪጋልዙን በባቢሎን ዙፋን ላይ አሾመው። በ1290 ዓክልበ. የአሦር ንጉስ 1 አዳድ-ኒራሪ የሚታኒን መንግሥት አሸነፈ። የአዳድ-ኒራሪ ተከታይ 1 ስልምናሶር መንግሥቱን በከጢያውያን አግጣጫ እስከ ከርከሚሽ ድረስ አስፋፋ። የስልምናሶርም ልጅ 1 ቱኩልቲ-ኒኑርታ እንኳን በባቢሎን ላይ ገዛ። ሆኖም በቅርብ ጊዜ ባቢሎን በአሦር ላይ አመጽ ታደርግ ነበር። በ1200 ዓክልበ.. አካባቢ የኬጢያውያን መንግሥት በሙሽኪ (ፍሩጋውያን) ግፊት ስለ ወደቀ፥ ባቢሎንና አሦር ለአሞራውያን መሬት ተወዳዳሪዎች ሆኑ። የአሦር ንጉስ 1 አሹር-ረሽ-ኢሺ በዚህ አቅራቢያ በ1140 ዓክልበ. በባቢሎንን ንጉሥ 1 ናቡከደነጾር ላይ አሸነፈ። የአሹር-ረሽ-ኢሺ ልጅ 1 ቴልጌልቴልፌልሶር የመንግሥቱን ጠረፍ በጣም አስፋፋ። ከርከሚሽን ከመማረኩ በላይ በሙሽኪ ላይ እስከ ጥቁር ባሕር ድረስ ዘመቻ አደረገ። ደግሞ እስከ ሜድትራኒያን ባሕር ድረስ ሲዘረጋ ፊንቄን (ሊባኖስ) ያዘ። ከ1 ቴልጌልቴልፌልሶር በኋላ ከጎረቤቶቹ ከአራማውያንና ከኡራርቱ የተነሣ የአሦር ኅይል ደክሞ ነበር። በ920 ዓክልበ. ግን 2 አዳድ ኒራሪ ንጉሥ ሆሞ የአሦር ሃይል ታደሰ። ደግሞ ወደ ስሜን የኖሩትን ሕዝቦች በሙሉ በሰፈራ አፈለሳቸው። ይሁንና መንግሥቱ ከአቦር ወንዝ ወደ ምዕራብ አልዘረጋም። ንጉስ አሹር-ናሲር-ፓል ከ890 ዓክልበ. ጀምሮ ነግሦ ያለ ምኅረት ጠረፎቹም አስፋፋ። ከአቦርና ከኤፍራጥስ መካከል ያሉትን አራማውያን ድል አድርጎ በሜድትራኒያን ሲደርስ ፊንቄን ቀረጠ። ካልሁንም ዋና ከተማው እንዲሆን አደረገው። በልጁ 3 ስልምናሶር 34 አመት ዘመን (865-831 ዓክልበ.) አሦር በየአመቱ ለጦርነት ሠለፈ። ባቢሎን ተወርሮ ተቀረጠ። የሶርያ (አራም-ደማስቆ) ንጉስ ወልደ አዴር (አድርአዛር) ከእስራኤል ንጉስ አክዓብ ጋራ በቃርቃር ፍልሚያ ስልምናሶርን አጋጠመው። ስልምናሶርም ፊንቄንና የእስራኤል ንጉስ ኢዩን አስቀረጠ። በዋና ከተማው በካልሁ የተገኘው ጥቁር ሐውልት ስለ 3 ስልምናሶር ዘመን ድርጊቶች ይመሰክራል። \n \nጥያቄ: የሚታኒን መንግሥት በ1290 ዓክልበ. ያሸነፈው የአሦር ንጉስ ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የአሦር ንጉስ 1 አዳድ-ኒራሪ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየላሊበላ ግሎባል ኔትወርክስ ድርጅት ተባባሪ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ (ዶ/ር) ዓለም አቀፉን ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገ አዲስ የስራ ፈጣራ ውድድር አሸነፉ። ኢትዮጵያዊቷ በየዓመቱ የሚካሄደውን ዓለም አቀፉን ፒአይቲሲኤች (PITCH) አዲስ የስራ ፈጠራ ውድድር በትላንትናው እለት ማሸነፉቸው ይፋ ሆኗል። ውድድሩ 2500 ስራ ፈጣሪዎች የተሳተፉ ሲሆን ወደ መጨረሻው ዙር ያለፉት ደግሞ 700 የሚሆኑ አዲስ ፈጣሪዎች ነበሩ። ከዚህ ውስጥ ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ(ዶ/ር) በጤና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያቀረቡት አዲስ የስራ ፈጠራ በቅርበት ተፎካካሪ ከነበሩት የአሜሪካና የእንግሊዝ የስራ ፈጣሪዎችን በመብለጥ የዓመቱ ውድድር አሸናፊ ሆኗል። ውለታ ለማ (ዶ/ር) ለውድድሩ ያቀረቡት የስራ ፈጠራ አባይ ሲ ኤች አር (ABAY CHR) የተባለ በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ህክምና ዘርፍ ያለውን ሰፊ የወረቀት ስራ ወደ ዲጂታል በመቀየር ስራን የሚያቀልና የሚያቀላጥፍ እንዲሁም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወጪን የሚያስቀር የሥራ ፈጠራ ነው ተብሏል። \n \nጥያቄ: ዶ/ር ውለታ ለማ ያሸነፉበት አዲስ የሥራ ፈጠራ ውድድር በምን ዘርፍ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በጤና ቴክኖሎጂ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ ፈጥራው የነበረው ኮንፌደሬሽን ስምምንት መቼ ፈረሰ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ1989 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nፐርል በክ ፐርል በክ በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ (1938) ለመሆን የበቃች አሜሪካዊት ደራሲ ናት። በክ ጁን 26 ቀን 1982 ዓ.ም በምእራብ ቨርጂኒያ ሂልዝቦሮ በተባለ ቦታ ተወለደች። ወላጆቿ ፕሬስብቴርያዊ ሚሲዮኖች የነበሩ ሲሆን ብዙውን የሚሲዮን ስራቸውን በቻይና ነው ያሳለፉት። በዚሁ የተነሳ በክ ከልጅነቷ ጀምሮ እንግሊዝኛን ብቻ ሳይሆን ቻይንኛንም አቀላጥፋ ትናገር ነበር። ትምህርቷን በ1914 እንዳጠናቀቀች ወደ ቻይና ነው ያቀናችው። በ1915 የወደፊት ባሏ ከሚሆነውን ከጆን ሎሲንግ በክ ጋር ተገናነች። በ1917 ጋብቻቸውን ከፈጸሙ በኋላ ኑሯቸውን ናንሹ በተባለችው የገጠራማዋ አንህዌ ግዛት አደረጉ። በዚሁ ቆይታዋ ነው ወደፊት የሥነ-ጽሁፍ ስራዋ ጉልላት ለመሆን የበቃውን ስሙር መሬት (The Good Earth) ለተባለው መጽሃፏ የሚሆናትን መረጃ የሰበሰበችው። በክ ጽሁፎቿን ማሳተም የጀመረችው ከ1920ዎቹ ጀምራ ሲሆን አጫጭር ስራዎቿ \"The Nation\"፣ \"The Chinese Recorder\"፣ \"Asia\" እና \"The Atlantic Monthly\" በተሰኙ መጽሄቶች ታትመውላታል። የመጀመሪያው ወጥ ልብ-ወለድ ድርሰቷ (East Wind, West Wind) በ1930 በጆን ዴይ ኩባንያ ታትሟል። የጆን ዴይ ኩባንያ አሳታሚ የነበረው ሪቻርድ ዋልሽ ኋላ ላይ (1935) የፐርል በክ ሁለተኛ ባሏ ለመሆን በቅቷል። በ1931 ጆን ዴይ ኩባንያ የፐርል በክን ሁለተኛ ወጥ ልብ-ወለድ ድርስት የሆነውን ስሙር መሬትን አሳተመ። ይኸው ሥራዋ በተከታታይ በ1931 እና በ1932 ዓ.ም በገበያ ላይ አንደኛ ተፈላጊ ሆኖ ለመዝለቅ የቻለ ሲሆን ለሷም በ1935 ዓ.ም የፑሊትዘር ሽልማት እና የሃዌልስ ሜዳልያ አስገኝቶላታል። ስሙር መሬት በ1937 ዓ.ም በኤም.ጂ.ኤም አማካይነት በፊልም መልክ ተቀናብሮ ለተመልካች ቀርቧል። ከዛ በተከታታይ ሌሎች ድርሰቶችን ለአንባቢ አቅርባለች። በክ በ1938 ዓ.ም በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን በመቀበል የመጀመሪያዋ (ሴት) አሜሪካዊት ሆናለች። ፐርል በክ በ1973 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ስትለይ ከ70 በላይ ስራዎቿ ታትመውላታል። መቃብሯም ፔንሲልቬንያ ውስጥ በክስ በተባለው ቀበሌ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ፐርል በክ የመጀመሪያ ጋብቻዋን የፈጸመችው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ1917 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nነሐሴ ፳፯ ነሐሴ ፳፯ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፯ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፱ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፰ ዕለታት ይቀራሉ። ፲፮፻፶፰ ዓ/ም ለሦስት ቀናት የጋየውና አስር ሺህ ሕንጻዎችን ያወደመው የሎንዶን ትልቁ እሳት ተነሳ። ፲፯፻፵፬ ዓ/ም የምዕራብ አውሮፓ አገራት ዘመን አቆጣጠራቸውን በለወጡ በሁለት መቶ ዓመታቸው፣ ብሪታንያ የጎርጎራዊ ዘመን አቆጣጠርን ተቀበለች። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በጠላት ወረራ ዘመን የሸዋ አርበኞች ቡልጋ ላይ ተሰባስበው የልጅ ኢያሱን ልጅ መልአከ-ፀሐይ ኢያሱን አነገሡ። አዲሱ 'ንጉሥ' ወዲያው የአርበኞች መሪ ለነበሩት ባላምባራስ አበበ አረጋይ የራስነት ማዕርግ ሰጠ። መልአከ-ፀሐይ ኢያሱ መስከረም ፳፬ ቀን ፲፱፻፴፩ ዓ/ም አረፎ አንኮበር አካባቢ በሚገኘው ዞማ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተቀብሯል። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ጃፓን በተሸናፊነቷ እጇን ሰጠች። ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ነጻነትን አስከትሎ በጃዋሃርላል ኔህሩ ምክትል ፕሬዚደንትነት የሚመራ የሕንድ ጊዜያዊ መንግሥት ተመሠረተ። ፲፱፻፺ ዓ/ም የርዋንዳን ፍጅት አስከትሎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያቋቋመው የወንጀለኛ ፍርድ ቤት ጃን ፖል አካዬሱ የተባለውን የቀድሞ ከንቲባ ላይ ፍርዱን የወንጀለኛነት ፍርድ ፈረደበት። \n \nጥያቄ: በጃን ፖል አካዬሱ ላይ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያቋቋመው የወንጀለኛ ፍርድ ቤት ለምን ፈረደበት?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የርዋንዳን ፍጅት አስከትሎ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኤንመርካር ኤንመርካር በሱመር (ሳንጋር) ነገስታት ዝርዝር ዘንድ የኡሩክ (ኦሬክ) ከተማ መስራች ነበረ። በዚያ ዝርዝር ጽህፈት 420 (ወይም በሌላ ቅጂ 900) ዓመታት እንደ ነገሰ ይላል። ደግሞ አባቱ የኡቱ ልጅ መስኪያጝካሸር ወደ ባሕር ገብቶ ኤንመርካር መንግስቱን ከኤአና ከተማ እንዳመጣ ይጨምራል። የኤንመርካር ስም በሌላ የሱመር ጽሑፍ ደግሞ ተገኝቷል። «ኤንመርካርና የአራታ ንጉስ» በተባለው ተረት እሱ የኡቱ ልጅ ይባላል። (ኡቱ በሱመር እምነት የጸሓይ አምላክ ነበር።) ይህ ተረት የሰው ልጅ ልሳናት መደባለቁን ይናገራል። ኡሩክን ከመመስረቱ በላይ ታላቅ መስጊድ በኤሪዱም እንዳሰራ ይተረታል። ለመሆኑም፣ አራታ እንዲገዛለት የሚለው መልእክት በአፍ መናገር ስለሚከብድ፣ ኤንመርካር ጽሕፈት በሸክላ ጽላት ላይ መጻፍ እንደ ፈጠረ ይላል። በተጨማሪ በዚሁ ጽሑፍ ኤንመርካር የዙሪያው አገሮች ልዩ ልዩ ልሳናት እንደገና አንድ እንዲሆኑ ይጸልያል። እነዚህ አገራት ሹቡር፣ ሐማዚ፣ ሱመር፣ ኡሪ-ኪ (የአካድ ዙርያ) እና የማርቱ አገር ናቸው። ከዚህ በላይ የኤንመርካርን መንግሥት የሚገልጹ ሦስት ተጨማሪ ጽሑፎች አሉ። «ኤንመርካርና ኤንሱሕጊርዓና» የሚባል ተረት የኤንመርካርና የአራታ መቀያየም ሲገልጽ፣ ሐማዚ ተሸንፎ እንደ ነበር ይጠቅሳል። በ«ሉጋልባንዳ በተራራ ዋሻ»፣ ኤንመርካር በአራታ ላይ ዘመቻ ሲመራ ይታያል። አራተኛውና መጨረሻውም ጽላት፣ «ሉጋልባንዳና የአንዙድ ወፍ» ኤንመርካርና ሠራዊቱ በአራታ ዙሪያ ለ1 አመት እንደ ከበቡት ይላል። ለመሆኑ ኤንመርካር 50 አመት ከነገሰ በኋላ፣ የማርቱ ሕዝብ (አሞራውያን) በሱመርና በአካድ ሁሉ ተነሥተው ኡሩክን ለመጠብቅ ግድግዳ በበረሃ መስራት እንደ ነበረበት ይጠቅሳል። በነዚህ መጨረሻ 2 ጽላቶች፣ ከኤንመርካር ጦር አለቆች አንድ የሚሆን ሉጋልባንዳ የሚባል ሰው ይተረታል። በሱመር ነገሥታት ዝርዝር ዘንድ፣ ይህ ሉጋልባንዳ «እረኛው» ኤንመርካርን ወደ ኡሩክ ዙፋን ተከተለው። ይህ ሉጋልባንዳ ደግሞ በጊልጋመሽ ትውፊት በተባለው ግጥም ዘንድ የኋለኛው ኡሩክ ንጉሥ የጊልጋመሽ አባት ነበረ። ዴቪድ ሮኅል የሚባል አንድ የታሪክ ሊቅ የኤንመርካርና የናምሩድ ተመሳሳይነት አመልክቷል። «-ካር» የሚለው ክፍለ-ቃል በሱመር ቋንቋ ማለት «አዳኝ» ነው። ኡሩክ ከተማ የተመሠረተ በኤንመር-ካር ነበር ሲባል፣ ደግሞ ናምሩድ፣ አዳኝ፣ በኦሪት ዘፍጥረት ምእራፍ 10 ዘንድ ኦሬክን ሰራ። በሌላ ትውፊቶች ዘንድ ይህ ናምሩድ የባቢሎን ግንብ መሪ የሆነ ነበር። በተጨማሪም አቶ ሮህል የኤሪዱ መጀመርያ ስም «ባቤል» እንደ ነበር ያምናል፤ እዚያም የሚገኘው የግንብ ፍረስራሽ የባቢሎን ግንብ ፍርስራሽ መሆኑን ገመተ። «ባቢሎን» ማለት የኤሪዱ መጠሪያ እንደ ነበር የሚል ማስረጃ በሌሎችም ጥናቶች አለ። ሮማዊው ጸሐፊ ክላውዲዩስ አይሊያኑስ በጻፈ አንድ ትውፊት ዘንድ (200 ዓ.ም. ግድም)፣ የባቢሎን ንጉስ «ኤወኮሮስ» የተከታዩን «ጊልጋሞስ» አያት ይባላል። ይህ «ጊልጋሞስ» ማለት የኡሩክ ንጉስ ጊልጋመሽ መሆኑን የአሁኑ ሊቃውንት ስለ ገነዘቡ፣ እንዲሁም «ኤወኮሮስ» ማለት ኤንመርካር ሳይሆን አይቀርም የሚል አስተሳሰብ ያቀርባሉ። ከዚህ በላይ የከላውዴዎን ታሪክ ጸሐፊ ቤሮሶስ በጻፈው ዝርዝር መሰረት፣ ከማየ አይህ ቀጥሎ የከላውዴዎንና የአሦር መጀመርያው ንጉስ «ኤወኮዮስ» ይባላል፤ ስለዚህ የዚሁ «ኤወኮዮስ»ና የናምሩድ መታወቂያ አንድ ናቸው የሚለው አሳብ ለረጅም ዘመን የቆየ ነው። \n \nጥያቄ: ከሱመር ነገስታት መካከል የኡሩክ ከተማ መስራች ማነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ኤንመርካር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nፍሬምናጦስ የተወለዱት ታይር በምትባል ቦታ በምሥራቃዊ የሮማ ነገሥት በ፬ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያዎቹ ሲሆን ማንም መርምሮ ሊደርስበት በማይችለው በእግዚአብሔር ሀሳብ ወደ ኢትዮጵያ መተው ክርስትናን ከመሠረቱት ዋነኛው አባት ሆኖ በመቆጠር ፣ አገራችንን ከሌሎች ክርስቲያን አገሮች ጋር ያስተዋወቁ ፣ ያስተካከሉ ፣ በአክሱም ዘመነ መንግሥትና መንግሥት የተወደዱና የተከበሩ ፣ በመላው ኢትዮጵያ የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች የተከበሩ ታላቅ አባት ናቸው ። አባታችን ፍሬምናጦስ የ፲፪ ዓመት ልጅ እያለ ሜሮጵዮስ የተባለ ነጋዴ ፈላስፋም የነበረ መርከበኛ ይዞት ወደ አገራችን መጣ ። ከእርሱም ጋር ወንድሙ ኤድስዮስ የተባለም አብሮት እንደነበረ ይታወቃል ። እነዚህን ሁለት ወጣቶች አስከትሎ የመጣው ሜሮጵዮስ በቀይ ባሕር አካባቢ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች በጣሉለት አደጋ በዚሁ እንደ ሞተ ታሪክ ይነግረናል ። ይህም በንጉሥ ዒዛና ዘመነ መንግሥት ሆነ ። ፍሬምናጦስና ኤድስዮስ ግን በወቅቱ የአክሱም ንጉሥ የነበረው ንጉሥ ታዜር ጋር አድገዋል ። ንጉሡ በአእምሮ መብሰላቸውን ተመልክቶ ፍሬምናጦስ በጅሮንድ ኤድስዮስም ጋሻ ጃግሬው አድርጎ ሾማቸው ። ከዚያ በኋላ ንጉሥ ታዜር ሲያርፍ ወደ ፈለጉበት እንድሄዱ ነፃ ስለተለቀቁ ኤድስዮስ ወደ አገሩ ተመልሶ ሄዷል ። አባታችን አቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ግን ወንድሙን ሸኝቶ \"በጨለማ የሚኖረውን ሕዝብ ትቼ ወደ አገሬ አልመለስም\" በማለት የኢትዮጵያን ሕዝብ በማፍቀር እንደቀረ ታሪክ ያስረዳናል ። የቅዱሳን ፍቅራቸው እውነትም ልብ ይነካል ። በዚያን ዘመን በአገራችን ኢትዮጵያ ክርስትና ነገሥታቱ የታወቀ ቢሆንምኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ስርዓተ ንስሐ ፣ ስርዓተ ጥምቀት ፣ ስርዓተ ቅዳሴ ፣ ስርዓተ ቅዱስ ቁርባን የሚያከናውን ጳጳስ ስላልነበረ ይህን የተመለከቱ ነገስታት ኢዛናና ሳይዛና ጵጵስና እንዲያመጣ አባታችን አቡነ ሰላማን ወደ ግብጽ ላኩት ። አባታችንም ወደ ግብጽ በመሄድ ስርዓቶቹን በመማር በቅዱስ አትናትዮስ አንብሮተ እድ \"ኤጲስ ቆጶስ ዘአክሱም ወዘኩላ ኢትዮጵያ\" ተብሎ ጵጵስና ተቀበለ። \n \nጥያቄ: አባ ፍሬምናጦስ በሮማ የት አካባቢ ተወለዱ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ታይር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየእብድ ውሻ በሽታ የእብድ ውሻ በሽታ የየቫይረስ በሽታ ሆኖ ከፍተኛ የየአንጎል መጉረብረብን በሰዎች እና በሌሎች ደመ-ሞቃት እንስሳት ላይ የሚያስከትል ነው። ቅድሚያ ምልክቶቹ ትኩሳት እና በተነከሱበት ቦታ ማሳከክ/ማቃጠልን ያካትታል። እነዚህ ምልክቶች ከሚከተሉት አንድ ወይም የበለጡ ምልክቶች አስከትለው ይመጣሉ- ሃይል የታከለባቸው የሰውነት እንቅስቃሴዎች፣ ከቁጥጥር ወጭ የሆ መሸበር፣ የውሀ ፍራቻ, የሰውነት ክፍለን ለማንቀሳቀስ አለመቻል፣ ግራ መጋባት፣ እና ህሊናን መሳት። ምልክቶቹ ከታዩ በኋላ፣ የእብድ ውሻ በሽታ በአብላጫው ሁልጊዜ ሞትን ያስከትላል። በበሽታው በመያዘዎ እና ምልክቶቹ መታየት የሚጀምሩበት የጊዜ ገደብ በአብዛኛውን ጊዜ ከአንድ እሰከ ሶስት ወራት ባሉት ጊዜ ውስጥ ነው። ሆኖም ግን፣ ይህ የጊዜ ገደብ ከሳምንት ባነሰ እና ከአመት በበለጠ ጊዜ ሊለያይ ይችላል። የጊዜ ገደቡ የሚወስነው የበሽታ አምጭው ረቂቅ ህዋስ ወደ የማዕከላዊ የነርብ ስርዓትለመድረስ በሚፈጅበት እርቀት ነው። የእብድ ውሻ በሽታ በአለም ዙሪያ በአመት ከ26,000 እሰከ 55,000 ሞቶች ምክንያት ነው። ከ95% በላይ እነዚህ ሞቶች የተከሰቱት በኢሲያ እና አፍሪቃነው። የእብድ ውሻ በሽታ ከ150 ሀገራት በላይ እና ከአንታርቲካ በቀር በሁሉም አሀጉራት ይገኛል። ከ3 ቢሊዮን ሰዎች በላይ የእብድ ወሻ በሽታ በሚከሰትበት የአለማችን ከፍሎች ውስጥ ይኖራሉ። እጅግ በአብዛኛው አውሮፓ እና አውስትራሊያ፣ የእብድ ወሻ በሽታ የሚገኘው በሌሊት ወፎች ላይ ነው። \n \nጥያቄ: የእብድ ውሻ በሽታ በአለም ደረጃ ምን ያህል ሰዎችን ለሞት እየዳረገ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ26,000 እሰከ 55,000 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: በማሊ ፓርላማ ውስጥ ስንት የሕዝብ ተወካዮች አሉ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 147 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nመስከረም 23/12 ዓ ም ሽሬ ኢዜአ የተለያዩ የፈጠራ ውጤቶችን ለተጠቃሚዎች በማቅረብ ይሁንታ ያገኘው የ35 ዓመት ወጣት ሔሊኮፕተር ሰርቶ ለሙከራ እየተዘጋጀ መሆኑን አስታወቀ ። ወጣት ዕበ ለገሰ ይባላል ። በመደበኛ ትምህርት ብዙ ገፍቶ ባይሔድም በፈጣራ ብቃቱ ግን በርካታ ስራዎች ለህዝብ እንዲያደርስ አድርጎታል ። የ10ኛ ክፍል ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ በኤሌክትሪክ ሃይል የሚሰራ ምጣድ ጥገና ሥራ የጀመረው ወጣት አሁን ላይ ትልቅ ራእይ አንግቦ የራሱ የሆኑ የፈጠራ ስራዎችን በማቅረብ ውጤታማነቱን በተጠቃሚዎች ዘንድ እየተመሰከረለት መጥቷል ። የምጣድ ጥገና ስራው ለታናሽ ወንድሙ በመልቀቅ የወርቅ መአድን መፈለጊያ መሳሪያ ወደ ማሻሻል መሸጋገሩን ይገልፃል ። በራሱ ፈጠራ ያሻሻለው የወርቅ መፈለጊያ መሳሪያ በባህላዊ መንገድ ወርቅ ለሚያመርቱ ሰዎች በሽያጭ በማቅረብ የፍለጋ ሥራቸውን እንዲቃለል እንዳስቻላቸው ተጠቃሚዎቹ ይናገራሉ ። ቀደም ሲል የነበረው ‘’ጂ አር ዜድ’’ የተባለው የወርቅ መፈለጊያ መሳሪያ ከ70 እስከ 80 ሳንቲ ሜትር ጥልቀት ባለው መሬት ውስጥ የሚገኝ የደለል ወርቅ የሚጠቁም ነበር ። ወጣቱ ያሻሸለው ግን በአንድ ሜትር ጥልቀት የሚገኘውን የደለል ወርቅ በቀላሉ መለየት የሚያስችል መሳርያ ሆኖ ተገኝቷል ። እንዲሁም ከድንጋይ ጋር ተደባልቆ የሚገኝ ወርቅ በቀላሉ መለየት የሚያስችል የድንጋይ ወፍጮ በመፍጠር ለተጠቃሚዎቹ በማቅረብ ላይ እንደሚገኝም ወጣት ለገሰ ይናገራል ። ባለፉት አምስት ዓመታት አምስት የድንጋይ ወፍጮዎችን በመስራት ለተጣቀሚዎቹ በተመጣጣኝ ዋጋ አቅርቧል ። በተጠናቀቀው ዓመት በራሱ ፈጠራ ሶስት ሰዎች የማሳፈር አቅም ያለት ሔሊኮፕተር ሰርቶ በሙከራ ደረጃ ለህዝብ እይታ አቅርቦ የነበረው ወጣቱ ዘንድሮ ለማብረር እየተዘጋጀ መሆኑንም ተናግሯል ። የፈጠራ ሥራዬ ስኬትና ሚስጥር “ይቻላል” የሚል ጽኑ እምነት ስላለኝ ነው የሚለው ወጣቱ ከኢንተርኔት የሚያገኛቸው የፈጠራ ሥራዎችም እገዛ እንዳደረጉለት ጠቁሟል። ሥራ ፈጣሪ ወጣቱ ወደ ገበያ በሚያቀርባቸው የፈጠራ ውጤቱ ጥሩ ገቢ ከማግኘቱም ባሻገር ለሌሎች 10 ወጣቶች የስራ እድል መፍጠሩን ተናግሯል። የወጣቱ የፈጠራ ወጤት ተጠቃሚ ከሆኑትና በባህላዊ መንገድ በደለል ወርቅ ምርት ፍለጋ ከተሰማሩ ማህበራት መካከል የ“ስምረት” ማህበር አንዱ ነው። የማህበሩ አባል የሆነው ወጣት በላይ ተክለሃይማኖት በሰጠው አስተያየት ” ከወጣቱ የገዛነው የደለል ወርቅ ጠቋሚ መሳርያ ሥራችንን ከማቃለል በተጨማሪ በወርቅ ፍለጋው ስኬታማ እንድንሆን አግዞናል” ብሏል። ሌላው የማህበሩ አባል ወጣት ተስፋይ በላይ በበኩሉ ” ከድንጋይ ጋር ተደባልቆ የሚገኝ ወርቅ ለመለየት እጅግ አድካሚ የነበረው ሥራ ወጣቱ ባቀረበልን አነስተኛ የድንጋይ ወፍጮ በመጠቀም የድካማችንን ዋጋ ማግኘት አስችሎናል ” በማለት አድናቆቱን ገልፆለታል ። የሽሬ እንዳስላሴ ከተማ የወጣቶችና ስፖርት ጉዳይ ጽህፈት ቤት ምክትል ሃላፊ አቶ ጎይቶኦም ይሰማ እንዳሉትም ደግሞ የወጣቱን የፈጠራ ክህሎት እንዲሰፋና ሄሊኮፕተሯ ለህዝብ እይታ እንድትበቃ አስፈላጊውን ድጋፍ ይደረግለታል ። የሽሬ እንደስላሴ ፖሊ ቴክኒክና ኮሌጅ ዲን አቶ ፀጋይ ገብረሚካኤል በበኩላቸው የፈጠራ ባለቤት የሆነው ወጣት እበ ለገሰ የፈጠራ ስራዎች የሚያተኩሩት በአካባቢው ህብረተሰብ ላይ በሚታዩ መሰረታዊ ችግሮች ዙሪያ በመሆናቸው ተቀባይነታቸው የጎላ ነው ብለዋል ። ወጣቱ የሚያሳየው ትጋት የተሞላበት የፈጠራ ስራ ለሌሎች ወጣቶችም አርአያ በመሆን መነቃቃት መፍጠሩን የኮሌጁ ዲን መስክረውለታል ። \n \nጥያቄ: በሽሬ ከተማ ለሙከራ ሔሊኮፕተር ሰርቶ ያቀረበው ወጣት ዕበ ለገሰ የስንተኛ ክፍል ተማሪ ነበረ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የ10ኛ ክፍል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአዳኝ አንበሶች በጣም ቀልጣፋና ፈጣን ቢሆኑም እንኳ በአደን ጊዜ የሚሳካላቸው 30 በመቶ ብቻ ነው። በመሆኑም አንበሶች ከተደቀኑባቸው ትልልቅ አደጋዎች አንዱ ረኃብ ነው። ለአካለ መጠን የደረሰ አንድ አንበሳ ያለው ጥንካሬ እጅግ የሚያስገርም ነው። በቤተሰብ ደረጃ የሚያድኑ እንደ መሆናቸው መጠን ከ1,300 ኪሎ ግራም በላይ ክብደት ያላቸውን እንስሳት የመጣልና የመግደል አቅም እንዳላቸው ይነገራል። አንበሶች በመጀመሪያ ላይ በሰዓት እስከ 59 ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሮጡ ይችላሉ፤ ሆኖም ይህ ፍጥነታቸው እስከ መጨረሻ አይዘልቅም። በዚህ ምክንያት ቀለባቸውን ለማግኘት አድብቶ የመያዝ ዘዴ ይጠቀማሉ። የማደኑን ተግባር 90 በመቶ የሚያከናውኑት ሴቶቹ አንበሶች ቢሆኑም በሚበሉበት ጊዜ ትልቁን ድርሻ የሚያገኙት ትልልቆቹ ወንድ አንበሶች ናቸው። አደን በሚጠፋበት ጊዜ አንዳንዴ አንበሶች በጣም ስለሚርባቸው ያገኙትን መብል ለራሳቸው ግልገሎች እንኳ ለማካፈል ፈቃደኛ አይሆኑም። ታዳኝ ከብዙ ዓመታት በፊት ባለ ግርማ ሞገሱ አንበሳ በመላው የአፍሪካ አህጉር እንዲሁም በእስያ፣ በአውሮፓ፣ በህንድና በፍልስጤም አንዳንድ ቦታዎች ይገኝ ነበር። አዳኝ እንደመሆኑ መጠን ሰውን እየተቀናቀነ የሚኖር እንስሳ ነው። በከብቶች ላይ አደጋ የሚጥልና በሰዎች ላይ ጉዳት የሚያደርስ በመሆኑ አንበሳ ገና እንደታየ በጥይት የሚገደል ፍጡር ሆነ። የሕዝብ ቁጥር ፍንዳታ የአንበሳን መኖሪያ በእጅጉ አመናምኖታል። ዛሬ ከአፍሪካ ውጪ ባለው የዓለም ክፍል በዱር የሚኖሩት አንበሶች በጥቂት መቶዎች ብቻ የሚቆጠሩ ሆነዋል። በአሁኑ ጊዜ አንበሶች ሰው ከሚያደርስባቸው ጥቃት ሙሉ በሙሉ ተጠብቀው መኖር የሚችሉት ጥበቃ በሚደረግባቸው ክልሎች ውስጥና በዱር አራዊት መጠበቂያ ቦታዎች ብቻ ሆኗል። አንበሳ ሲያገሣ አንበሶች በሚያገሡበት ጊዜ በብዙ ኪሎ ሜትር ርቀት ሊሰማ የሚችል ከፍተኛ ድምፅ የማውጣት ልዩ ችሎታ አላቸው። አንበሳ ሲያገሣ የሚያሰማው ድምፅ “እጅግ ማራኪ ከሆኑት የተፈጥሮ ድምፆች” አንዱ እንደሆነ ይነገራል። ብዙውን ጊዜ አንበሶች በጨለማ ሰዓትና ንጋት ላይ ያገሣሉ። ወንዶቹም ሆኑ ሴቶቹ አንበሶች የሚያገሡ ሲሆን አንዳንዴም የመንጋው አባላት በአንድነት ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ያገሣሉ። በአንበሶች ላይ ጥናት የሚያካሂዱ ሳይንቲስቶች አንበሶች የሚያገሡባቸው የተወሰኑ ምክንያቶች እንዳሉ ይናገራሉ። ወንዶቹ አንበሶች የሚኖሩበትን ክልል ድንበር ለማሳወቅ እንዲሁም ሌሎች ወንድ አንበሶች ወደ ክልላቸው እንዳይገቡ ለማስጠንቀቅ ሲሉ ያገሣሉ። በርቀት ወይም በጨለማ ተነጣጥለው ያሉ የአንድ መንጋ አባላት ያሉበትን ቦታ ለመጠቆም ያገሣሉ። በተጨማሪም አንድ እንስሳ ከገደሉ በኋላ ለሌሎቹ የቤተሰቡ አባላት ምግቡ ያለበትን ቦታ ለማሳወቅ ያገሣሉ። አንበሶች በሚያድኑበት ጊዜ የሚያድኗቸውን እንስሳት ለማስደንበር ብለው አያገሡም። ሪቻርድ ኤስቲዝ ዘ ቢሄቭየር ጋይድ ቱ አፍሪካን ማማልስ በተባለው መጽሐፋቸው ላይ “አንበሶች የሚያድኑትን እንስሳ ለማጥመድ ሲሉ ሆን ብለው እንደሚያገሡ የሚጠቁም ምንም ነገር የለም (በተሞክሮዬ እንዳየሁት በአንበሳ የሚታደኑ እንስሳት አንበሳ ለሚያሰማው የግሣት ድምፅ ብዙም ትኩረት አይሰጡም)። \n \nጥያቄ: ብዙውን ጊዜ አንበሶች የሚያገሱበት ሰዓት የትኛው ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በጨለማ ሰዓትና ንጋት ላይ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሱዳን ሱዳን በይፋ የሱዳን ሪፑብሊክ (አረብኛ السودان) ከአፍሪካ በስፋት ሦስተኛ ስትሆን በአህጉሪቱ ሰሜናዊ ምስራቅ ክልል ትገኛለች። ዋና ከተማዋ ካርቱም ነው። ከግብፅ ፣ ከቀይ ባሕር ፣ ከኤርትራ ፣ ከኢትዮጵያ ፣ ከደቡብ ሱዳን፣ ከመካከለኛው የአፍሪካ ሪፑብሊክ ፣ ከቻድ ፣ እና ከሊቢያ ጋር ድንበር ትካለላለች። የአባይ ወንዝ (ናይል) ሀገሪቱዋን ወደ ምሥራቅና ምዕራብ ይከፍላል። የአረብ ባህል ደንበኛ ሲሆን አብዛኛው ሕብዝ የእስልምና ዕምነት ተከታይ ነው። ሱዳን ከግብፅ የተጣመረ ረዥም ታሪክ አላት። የመጀመሪያው የሱዳን እርስ በርስ ጦርነት ከ1955 እስከ 1972 እ.ኤ.አ. ከዚያም ሁለተኛው የሱዳን እርስ በርስ ጦርነት ከ1983 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. ተከስቷል። በ1989 እ.ኤ.አ. በሰላማዊ መፈንቅለ መንግሥት ኦማር ሀሳን አህመድ አል-በሽር ሥልጣን ላይ የወጡ ሲሆን እራሳቸውን የሱዳን ፕሬዝዳንት ብለው ሾመዋል። የእርስ በርስ ጦርነቱ በሰላም ውል የቆመ ሲሆን ይህ ውል ያኔ የሀገሪቱዋ ደቡባዊ ክፍል ለነበረው ቦታ ራስን የመምራት መብት ሰጥቷል። በጃኑዋሪ 2011 እ.ኤ.አ. በተካሄደው ውሳኔ ሕዝብ (referendum) መሠረት በሱዳን ፈቃድ ደቡብ ሱዳን ሐምሌ ፪ ቀን ፳፻፫ ዓ.ም. ሉዓላዊ ሀገር ሆነች። ዋና ከተማዋ ካርቱም የሱዳን የፖለቲካ፣ ባህል እና ንግድ ማዕከል ናት። የሀገሪቱዋ መንግሥት በይፋ ፌዴራላዊ ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ቢሆንም ስልጣን ላይ ያለው ብሔራዊ ኮንግረስ ፓርቲ (National Congress Party) በሁሉም የመንግሥት አካላት ላይ ባለው ጥብቅ ቁጥጥር ምክንያት በብዙ የዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ ዘንድ መንግሥቱ አምባገነናዊ ተብሎ ይቆጠራል። \n \nጥያቄ: ሱዳን በአፍሪካ በቆዳ ስፋት ስንተኛ ናት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሦስተኛ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ላሉት መጻሕፍት አርእስት የሰጡት ሠለስቱ ምዕት ናቸው፡፡ በምን ምክንያት ቢሉ ድዮቅልጥያኖስ መክስምያኖስ የሚባለ ሁለት ዓላውያን ነገስታት ተነስተው \"አብያተ ጣዖታት ይትረኃዋ አብያተ ክርስቲያናት ይትዓፀዋ\" ብለው አዋጅ አስነገሩ፡፡ አብያተ ክርስቲያናትና ቅዱሳት መፃህፍት ተዘረፉ፤ ተቃጠሉ፡፡ ከምዕመናን ወገን ብዘዎች ሞቱ የተረፉትም ተሰደዱ፡፡ እጅግ ከፍተኛ እልቂትና ስደት በቤተክርስቲያን ላይ ሆነ፡፡ ከመከራው ጽናት የተነሳ ዘመኑ ዘመነ ሰማዕታት ተባለ (ከ285 - 395)፡፡ ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር መፍቀሬ ሃይማኖት የሆነውን ቆስጠንጢኖስን አነገሰው፡፡ የቆስጠንጢኖስ አባቱ ኮስታንዲዮስ(ቁንስጣ) ሲሆን እናቱ ደግሞ እላኒ ትባላለች፡፡ ቆስጠንጢኖስም የድዮቅልጥያኖስን አዋጅ በአዋጅ ሽሮ \"አብያተ ክርስቲያናት ይትረኃዋ አብያተ ጣዖታት ይትዓፀዋ\" ብሎ አወጀ፡፡ በዘመኑ አርዮስ የተባለ መናፍቅ ወልድ ፍጡር በመለኮቱ ብሎ ተነሳ፡፡ በዚህ ጊዜ ጉባኤ በኒቂያ ተደረገ፡፡ ሶስት መቶ ዓሥራ ስምንት የቤተክርስቲያን ሉቃውንት ተሰብስበው አርዮስን በማውገዝ ሃይማኖትን አጽንተው በሚለያዩበት ጊዜ ለመጻህፍት ሁሉ አርእስት ሰጥተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የእላኒና የቁንስጣ ልጅ ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ቆስጠንጢኖስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nልዑል ራስ መኮንን የንጉሠ ነገሥቱ ዳግማዊ ምኒልክ ተወካይ ሆነው ሁለት ጊዜ የአውሮፓን አገሮች ጎብኝተዋል። በዚህ ጊዜ እሳቸው ኢጣሊያን ሲጎበኙ በነበረ ጊዜ የኢጣሊያ ጋዘጦች የውጫሌ ውልን በተመለከተ፤ «...በውጫሌ ውል ላይ ኢትዮጵያ የኢጣሊያን ጥገኝነት ተቀብላ ውል ከፈረመች በኋላ የጀርመን ንጉሠ ነገሥት ከኢትዮጵያ የሚላከውን ማንኛውንም ደብዳቤም ሆን ጉዳይ በኢጣሊያ መንግሥት በኩል መቀበል ሲገባቸው በቀጥታ ከምኒልክ የተጻፈውን ደብዳቤ ተቀብለዋል...» እያሉ የጻፉትን ራስ መኮንን ተቃውሞአቸውን ለኢጣሊያ መንግሥት ከነገሩ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የውሉን መበላሸት ለአጤ ምኒልክ አሳወቁ። ከኢጣሊያንም ጋር በተደረገውም ጦርነት ራስ መኮንን ፲፭ ሺህ እግረኛ ወታደሮች ይዘው ከምኒልክ እና ታላላቅ ጦር አዛዦች ጋር ዘምተዋል። በ፲፰፻፺፰ ዓ.ም መጀመሪያ ላይ በብርቱ ስለታመሙ ለኅክምና ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ጥር ፬ ቀን ከከተማቸው ከሐረር ተነሱ። ጥር ፱ቀን ቡርቃ ወንዝ አድረው የጥምቀትን በዓል አክብረው ከዋሉ በኋላ ሕመሙ ስለጸናባቸው ወደ ኋላ ተመልሰው ቁልቢ ገብተው በሐኪም ይታከሙ ጀመር። እዚሁም ሲታመሙ ከቆዩ በኋላ መጋቢት ፲፫ ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም ቁልቢ ላይ አርፈው ሐረር ላይ እሳቸው በተከሉት በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። ዐፄ ምኒልክም የአርባቸው ለቅሶ የሚለቀሰው አዲስ አበባ እንዲሆን ባዘዙት መሠረት፤ ሰኞ ሚያዝያ ፳፪ ቀን በአዲስ አበባና በዙሪያው ያሉት የየገዳማቱና የየአድባራቱ ካህናት የክርስቲያን የፍታት ጸሎት ተድርጎ በማግስቱም ማክሰኞ የጊዮርጊስ ዕለት ሚያዝያ ፳፫ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም በሰኢ ሜዳ ላይ ድንኳን ተተክሎ፤ መኳንንቱና ሠራዊቱ ተሰብስቦ የራስ መኮንን የማዕረግ ልብሳቸውና የራስ ወርቃቸው፤ ኒሻኖቻቸውና የጦር መሳሪያቸው ተይዞ ፈረስና በቅሏቸው በወርቅ እቃ ተጭነው በሠራዊቱ መካከል እየተመላለሱ ታላቅ ልቅሶ ተለቀሰላቸው። \n \nጥያቄ: የኢጣልያ ጋዜጦች የውጫሌ ውል ስምምነትን አላከበሩም ብለው የጀርመንን ንጉሠ ነገስት የወቀሱት ምን በማድረጋቸው ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከኢትዮጵያ የሚላከውን ማንኛውንም ደብዳቤም ሆን ጉዳይ በኢጣሊያ መንግሥት በኩል መቀበል ሲገባቸው በቀጥታ ከምኒልክ የተጻፈውን ደብዳቤ ተቀብለዋል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዓጼ ኃይለ ሥላሴ ዘውድ እንደጫኑ የአገሪቱን የመጀመሪያ ሕገ-መንግሥት እንዲዘጋጅ አዝዘው በዘውዱ አንደኛ ዓመት በዓል ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፬ ዓ.ም. በአዲሱ ምክር ቤት (ፓርላማ) ለሕዝብ ቀረበ። ከዚህም በላይ ብዙ የቴክኖዎሎጂ ስራዎችና መሻሻያዎች ወደ ኢትዮጵያ ከውጭ አገር አስገቡ። በ፲፱፻፳፰ ዓ.ም. የሙሶሊኒ ፋሺስት ሠራዊት ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ጃንሆይ ሕዝባቸውን ወራሪውን በሙሉ ለመቃወም እንዳስነሡና የከተት ዐዋጆቻቸው በታሪክ ገጾች ይዘገባሉ። በዐዋጅ መሠረት የዘመቻው ጊዜ እስቲያልቅ ድረስ ለሚታግሉ ነጋዶች ከቀረጥ አስተስርየት ሰጣቸው። እራሳቸው በቆራጥነት ከታገሉ በኋላ የጠላቱ ጦር ኅይል ግን በመጨረሻ ወደ እንግሊዝ አገር ለጊዜው አሰደዳቸው። ወደ ጄኔቭ ስዊስ ወደ ዓለም መንግሥታት ማኅበር ሄደው ስለ ጣልያኖች የዓለምን እርዳታ በመጠየቅ ተናገሩ። የዓለም መንግሥታት ግን ብዙ አላደረጉም። በ፲፱፻፴፪ ዓ.ም. ግን አውሮፓ ሁሉ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ተያዘ። የእንግሊዝ ሠራዊቶች ለኢትዮጵያ አርበኞች እርዳታ በመስጠት ጣልያኖች ተሸንፈው በ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. ኢትዮጵያን ተዉ። ዓፄ ኃይለ ሥላሴ አዲስ አበባን እንደገና የገቡበት ቀን ከወጡበት ቀን በልኩ ዕለት አምስት ዓመት በኋላ ነበረ። ከዚህ በኋላ በ1948 ዓ.ም. ተሻሽሎ የወጣ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት የሕዝቦችን መብቶችና ተከፋይነት በመንግሥት አስፋፍቶ ሁለቱ ምክር ቤቶች እንደመረጡ አደረገ። በ፲፱፻፶፭ ዓ.ም. ግርማዊነታቸው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በአዲስ አበባ እንዲመሠረት ብዙ ድጋፍ ሰጡ። በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. ወደ ካሪቢያን ጉብኝት አድርገው የጃማይካ ራስታዎች ተገኛኙ። በ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. በማርክሲስት አብዮት ደርግ ሥልጣን ያዙና እሳቸው በእሥር ቤት ታሰሩ። በሚከተለው ዓመት ከተፈጥሮ ጠንቅ እንደ አረፉ አሉ ፤ ሆኖም ለምን እንደ ሞቱ ስለሚለው ጥያቄ ትንሽ ክርክር አለ። ብዙ ራስታዎች ደግሞ አሁን እንደሚኖሩ ይላሉ። የዓፄ ኃይለ ሥላሴ የትውልድ ስም ልጅ ተፈሪ መኮንን ነው። ስመ-መንግሥታቸው ግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ነበር። ሞዓ አንበሣ ዘእምነገደ ይሁዳ ሥዩመ እግዚአብሔር ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ የሚለው የሰሎሞናዊ ሥረወ-መንግሥት ነገሥታት መጠሪያም በንጉሠ-ነገሥቱ አርማ እና ሌሎች ይፋዊ ጽሑፎች ላይ ከመደበኛው ማዕረግ ጋር ይጠቀስ ነበር። ጃንሆይ ፣ ታላቁ መሪ እና አባ ጠቅል በመባልም ይታወቁ ነበር። \n \nጥያቄ: የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ንጉሣዊ አስተዳደር የሥልጣን ዘመን ሲያከትም ሥልጣኑን የያዘው መንግሥት ርዕዮቱ ምን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ማርክሲስት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nመጋቢት ፪ ፲፰፻፷፰ ዓ/ም - አሌክሳንደር ግራሃም ቤል ለመጀመሪያ ጊዜ በስልክ ረዳቱን አነጋገረ። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በልሚ ወቼ ሞሹ የኢትዮጵያ አርበኞችና የፋሺስት ኢጣሊያ ወገኖች ጦር ውጊያ ፲፱፻፴፫ ዓ/ም - ከኮንጎ የመጣ የቤልጅግ ሠራዊት የጣልያንን ሠራዊት አሸንፎ ፩ሺ፭፻ ወታደሮች በመማረክ አሶሳን ያዘ። ፲፱፻፵፱ ዓ/ም - የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት (በኋላ ፕሬዚዳንት) ሪቻርድ ኒክሰን ኢትዮጵያን ጎበኙ ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - ኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበራቸውን የሚወስን የጋራ ጉባዔ ለመመሥረት መወሰናቸውን አስታወቁ። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኢትዮጵያ ርዕሰ ከተማ፣ አራት ኪሎ ላይ በሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ተማሪዎችን ፖሊሶች በጢስ ቦምብ እና በዱላ በታተኑ። ተማሪዎቹ የጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድን የአሻንጉልት ምስል አቃጠሉ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮት ሽብር የአየር በረራ አስተዳደር ሠራተኞች አድማ ተጀመረ። አድማው እስከ መጋቢት ፳፫ ቀን ድረስ ተካሂዷል። ፲፱፻፹፪ ዓ/ም - ሊትዌኒያ እራሷን ከሶቭየት ኅብረት አስተዳደር ውጭ ነጻ መሆኗን አወጀች። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - ፔኒሲሊንን ያገኘው የብሪታኒያ ተወላጁ አሌክሳንደር ፍሌሚንግ በልብ ምታት አረፈ። \n \nጥያቄ: ፔኒሲሊንን ያገኘው የብሪታኒያ ተወላጁ ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አሌክሳንደር ፍሌሚንግ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቴምፕላርስ ቴምፕላር ወይም በሙሉ ስማቸው የክርሰቶስ እና የሰለሞን መቅደስ ምስኪን ወታደሮች የሚባሉት በጣም ታላቅ እና ሃይለኛ ከነበሩት ክርስቲያናዊ ወታደራዊ ስርአቶች ውስጥ ዋነኞቹ ናቸው። ይህ ስርዓት በ1088 ዓ.ም. ከተካሄደው አንደኛው የመስቀል ጦርነት በኋላ ማለትም በ1110 ዓ.ም. አዲስ የተቋቋመውን የእየሩሳሌም መንግስት ከእስላሞች ለመከላከልና ወደ ከአውሮፓ ወደ እየሩሳሌም የሚጎርፉትን ተሳላሚዎች ደህንነት ለመጠበቅ የተመሰረተ ነው። ቴምፕላሮች የተዋቀሩት በገዳማዊ ስርዓት ሲሆን ይኸውም የሲሰተርሲያን ስርዓት መስራች የነበረው የክላርቮው በርናርድ በዘረጋላቸው ህግጋት መሰረት ነው። ቴምፕላሮች ከብዙ መሳፍንት ጋር ግንኙነት ስለነበራቸው እና ጳጳሱም እነሱ ከሚቆጣጠሩዓቸው ቦታዎች ሁሉ ግብርና አስራት እንዲሰበስቡ ስለፈቀደላቸው በአጭር ጊዜ ውስጥ ዝነኛና ሃይለኛ ለመሆን ችለዋል። ቴምፕላሮቹ አራት ዋና ክፍሎች የነበሩአቸው ሲሆን እነዚሁም ዋነኞቹ ወታደሮች ወይም ናይትስ የሚባሉት ሙሉ የፈረሰኛ ትጥቅ የታጠቁ ከዝቅተኛ የህብረተሰቡ ክፍል የተውጣጡት ወይም ሰርጀንትስ በመባል የሚታወቁት፤ መለስተኛ የፈረሰኛ ትጥቅ የታጠቁ ገበሬዎች ዋነኛው ስራቸው የስርዓቱን ንብረት ማስተዳደር የነበረ፤ እንዲሁም ካህናት ስራቸው የስርዓቱን መንፈሳዊ ህይወት መከታተል የነበረ ናቸው። \n \nጥያቄ: የሲሰተርሲያን ገዳማዊ ስርዓት መስራች ማነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ክላርቮው በርናርድ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበርግጥም የመጀመሪያው በሰፊው ተግባራዊ የሆነ የቴሌቭዥን ስርዓት ስራ ላይ የዋለው በጀርመን አገር ሲሆን ይኸውም በ1929 እ.ኤ.አ. ነው። በ1936 እ.ኤ.አ. (1928 ዓም) ጀርመን ሃገር ተደርጎ የነበረውን የኦሎምፒክ ውድድር በቴሌቭዥን ሊሰራጭ ቻለ፣ ህዝቡም ውድድሩን እቤቱ ሆኖ ቀጥታ ሲካሄድ ለማየት ቻለ። ከዚያ መጀመርያው ጥቁርና-ነጭ ፕሮግራሚንግ በዩናይትድ ኪንግደም 1928 ዓም፤ በአሜሪካ 1933 ዓም ተደረገ። በአፍሪካ መጀመርያው ጣቢያዎች በ1952 ዓም በናይጄሪያና ደቡብ ሮዴዝያ (አሁን ዚምባብዌ) ተሰራጩ፣ በኢትዮጵያ የቴሌቪዥን ስርጭት አገልግሎት (ኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን) የጀመረው በ1956 ዓም ሆነ። ሁለት አገራት - እነርሱም ቱቫሉና ኪሪባስ - ምንም የራሳቸውን ቴሌቪዥን አሁን አያሰራጩም፤ ሆኖም የሌላ አገር ስርጭት እዚያ ሊታይ ይችላል። ከዚያ ቤርድ በግንቦት 26 ቀን 1920 (ጁላይ 3, 1928 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የከለር ቴሌቪዥን ስርጨት ሙከራ አደረገ። ነገር ግን ከለር ቴሌቪዥን ቢፈጠረም ለሚከተሉት ብዙ ዓመታት ስርጭት ባብዛኛው ጥቁርና ነጭ ብቻ ሆኖ ቀረ። ይሄው ቴክኖዎሎጂው በጣም ውድ፣ በጣም ከባድና በትክክል ያልተስተካከለ ስለ ሆነ ነው። በየጥቂቱ ከ1946 ዓም (1954 እ.ኤ.አ.) ጀምሮ አገራት ወደ ከለር ስርጭትና ከለሩን ማሳየት የሚችል ቴሌቪዥን ወደ መሸጥ ይዛወሩ ጀመር። በጥር ወር 1946 ዓም NBC የተባለው አሜሪካዊ ስርጭት ጣቢያ በከፊሉ ወደ ከለር ተሸጋገረ፤ ብዙ ሰዎች ግን ያንጊዜ ከለር ማሳያ ቴሌቪዥን ለመግዛት ገና አልቻሉም ነበር። ከ1955 እስከ 1959 ዓም ድረስ ሌሎቹ ትልልቅ አሜሪካዊ ጣቢያዎች ABC እና CBS ደግሞ ወደ ከለር ተዛወሩ፣ የከለርም ተቀባዮች ዋጋ እየተቀነሰ የሚይዩት ሕዝብ ቁጥር ደግሞ ከዚህ በኋላ እየተጨመረ ሄደ፤ ከረጅሙ ጥቁርና-ነጭ ዘመን ቀጥሎ ከለርም በኅብረተሠብ ያመጣው ለውጥ ለግዙፍነቱ በኋላ ኢንተርኔት እንደ ሆነ ያሕል ነው። ጃፓን በ1952 ዓም፣ ሜክሲኮ በ1955፤ ካናዳ በ1958፣ የአውሮፓ ኅብረትና የሶቪዬት ሕብረት በ1959፣ ኮት ዲቯር በ1962፣ አውስትራሊያ በ1967 ከለር ስርጭትን ጀመሩ። በኢትዮጵያም ከለር ስርጭት ከ1976 ዓም ጀምሮ ተገኝቷል። በ1977 ዓም ሮማኒያ ከጥቁርና-ነጭ ስርጭት ወደ ከለር ማሰራጨት የለወጠ በዓለም መጨረሻው ሃገር ሆነ። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ የቀለም ቴሌቭዥን ስርጭት የተጀመረው ከመቼ ጀምሮ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከ1976 ዓም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቅዱስ ላሊበላ ቅዱስ ላሊበላ በ 1101 አ.ም ትህሳስ 29 ቀን ከ እናቱ ከኬርዮርና ከአባቱ ዛንስዮም ላሰታ ቡግና ወረዳ ሮሃ ከተባለች ቦታ ከፍልፍል ቤተ መቅደስ ውስጥ ተወለደ በዚህ ፍልፍል ቤተ-መቅደስ ውስጥ እድገቱን አደረገ ስድስት አመት ሲሞላው ቤተ-መንግስት አባ ዳንእል የተባሉ መምህር ተቀጥረውለት ከ ፊደል እስከ ዳዊት አጠናቆ ከዚያም የተማረውን የዕሁፍ ጥበብ በቤተ ጎሎጎታ ደብረ ሲና በሚገኘው ከ ኪዳነ ምህረት መንበር ታቦት ዙሪያ ላይ እራሱ የተዓፋቸው የሚዐለይበት ዕሁፎቸች ይገኛሉ፡፡ ቅዱስ ላሊበላ 12 አመት ሲሞላው አባቱ ዘንሳዮም 40 አመት ነግሶ በተወለደ በ 76 አመቱ ከዚህ አለም በ ሞት ተለየ ወድያው ብዙም ሳይቖይ እናቱ ኬርዮርና በሞት ተለየች፡፡ ቅዱስ ላሊበላ በ እናቱ ና አባቱ ህልፈተ ህይወተ በደረሰበት ሀዘን የተነሳ ሁሉን ነገር ለመርሳት ና የትምህርት ፍላጎት ለሞሞላት ጉዞውን ወደ ጎጃም በማድረገ አለም ስላሴ ከተባለው ደብር ከመምህር ኬፋ ሃዲሳቱን አጠናቖ በመመረቅ ወደ ሀገሩ ተመለሰ፡፡ በወቅቱም በኤትዮጵያ ላይ ነግሶ የነበረው ታላቅ ወንድሙ ቅዱሰ ገብረ ማሪያም ነበር ይህ እንዲህ እያለ በእህቱ ላይ እሱ ሊነግስ መሆኑ ቅናት አሳደረባት ቅዱስ ላሊበላ ሁሌም እሚጠጣው ባህላዊ መድሃኒት ውስጥ መርዝ በመጨመር ታስቀምጥለታለች አትሙት ያላት ነፍስ ግን የሃገሬውን በሃል ምክንያት አድርጎ ሳይቀመስ አይሰጥምና አብሮት የነበረው ዲያቖን የተቀመጠውን መድሃኒት ቀምሶ ወደ ነበረበት ጠረቤዛ ላይ አንዳሰቀመጠው ወድያውኑ ህይወቱ ታልፋለች ቅዱስ ላሊበላ ይህን ባየ ጊዚ እኔን ለማጥፋት የመጣው መድሃኒት የሌላውን ነፍስ አጠፋች በማለት የቀረውን መድሃኒት በመጠጣት ለሶሰት ለሊት እንደ ወደቀ ቀረ ከዚያም ነዋሪው ገንዞ ለመቅበር ሲዘጋጁ የሰውነቱ ሙቀት አልተለየውም ነበር ይሄን ጊዜ ወድያው ቅዱስ ላሊበላ ነቃ የተመለከቱት ሰዎች ተደናገጡ ከዚያም ይህ ሁሉ ነገር በእህቱ መደረጉ ያሳዘነው ቅዱስ ላሊበላ በመነሳት ጉዞውን ወደ ጫካ አደረገ ኑሮውንም ለረጅም አመት እዚያው አደረገ ይህ እንዲ እንዳለ ሚስት እምትሆነውን ሴት አገኝ ቤተሰቧን በማስጠየቅ በቤተክርስትያን ስርአት ተጋብተው ጥቂት አመት እንደቆዩ ጉዞውን እየሩሳሌም አደረገ ለተከታታይ 13 አመታትም ቆይታ በኋላ ወደ ባለቤቱ ተመልሶ ከወንድሙ ከ ቅዱስ ገብረ ማሪያም ጋር እርቅ በማውረድ ቅዱስ ገብረ ማሪያም ንግስናውን ለቅዱስ ላሊበላ በተወለደ በ57 አመቱ በማስረከብ ኑሮውን በገዳም አደረገ፡፡ \n \nጥያቄ: የቅዱስ ላሊበላ ወላጆች እነማን ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ እናቱ ከኬርዮርና ከአባቱ ዛንስዮም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nእንቁላሎቿን ሆዷ ውስጥ የምትታቀፈው የአውስትራሊያ የእንቁራሪት ዝርያ (ጋስትሪክ ብሩዲንግ ፍሮግ) ያልተለመደ ዓይነት የመራቢያ ሥርዓት አላት፤ የዚህች እንቁራሪት ዝርያ ከ2002 ጀምሮ እንደጠፋ ይታሰባል የሚለው ጄደብሊው ዶት ኦርግ ድረ ገጽ ነው። \n \nጥያቄ: እንቁላሏን በሆዷ የምትታቀፈው የአውስትራሊያ እንቁራሪት ዝርያ ከ2002 ጀምሮ እንደጠፋች የገለጸው ድረ ገጽ ስያሜው ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ጄደብሊው ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \n125ኛውን የአድዋ ድል በዓል በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለማክበር የባሕልና ቱሪዝም ሚኒስትር ሂሩት ካሳው አሶሳ ከተማ ገቡ። በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሌ ሀሰን የተመራው የክልሉ ከፍተኛ አመራርም ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል። በዓሉም ከዛሬ ጀምሮ በፓናል ውይይት እና ታሪካዊ ቦታዎችን በመጎብኘት እንደሚካሄድ ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ \n \nጥያቄ: የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ማን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሂሩት ካሳው ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኃይሌ ገብረሥላሴ ኃይሌ ገብረሥላሴ በ ሚያዝያ ፲ ቀን ፲፱፻፷፭ (1965) ዓ.ም. በአሰላ ከተማ ፣ አርሲ ክፍለ ሀገር የተወለደ አቻ ያልተገኘለት ድንቅ የረጅም ርቀት ኢትዮጵያዊ ሯጭ ነው። ኃይሌ በሩጫ ዘመኑ በ ፲ ሺህ ፣ በ ፭ ሺህ፣ በግማሽ ማራቶን፣ በማራቶንና እንዲሁም በሌሎቹ የሩጫ ዓይነቶች ከ ፲፩ በላይ የዓለም ክብረ-ወሰን ሰብሯል። ኃይሌ በሩጫ ችሎታው ጠንካራ የሆነበት ምናልባትም ከመንደሩ ከባሕር ጠለል በላይ ከፍታ ነው ተብሎ ቢታመንም የተፈጥሮ ጥንካሬው ዓለምን ያስደነቀ ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ነው። ኃይሌ ሦስት ጊዜ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ከመሆኑም በላይ በ፴፫ ዓመት ዕድሜው ፪ ሰዓት ከ፬ ደቂቃ በሆነ ጊዜ በመግባት የዓለምን ማራቶን ክብረ-ወሰን ሊሰብር ችሏል። ኃይሌ ገብረሥላሴ እስካሁን ድረስ ፳፮ የዓለም ክብረ-ወሰኖችን ሰብሯል። ሯጭ ኃይሌ ገብረሥላሴ በሲድኒ እና በአትላንታ ኦሊምፒኮች በ፲ ሺህ ሜትር ሩጫዎች ወርቅ አስመዝግቧል። በ ፲፱፻፺፪ (1992) ዓ.ም. ኤንዱራንስ (Endurance) የተባለ ስለ እራሱ የእሩጫ ድል ፊልም ተሠርቷል። \n \nጥያቄ: ኃይሌ ገብረሥላሴ የተወለደው የት ሀገር ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ኢትዮጵያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም የዚምባቡዌ ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የተፈራረሙት ስምምነት ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የላንካስተር ቤት ስምምነት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቴሌቪዥን ቴሌቪዥን የስዕል እና ድምጽ ምልክቶችን ከማሰራጫ የሚቀበል የመገናኛ ዘዴ ነው። «ቴሌ-» የሚለው ክፍል በግሪክ «ሩቅ» ማለት ቢሆን «-ቪዥን» ደግሞ ከሮማይስጥ visio /ዊዚዮ/ «ማየት» («ትርዒት») ተወስዷል። በአጠቃላይ ቴሌቪዥን ማለት ተንቀሳቃሽ ምስልን (ብዙ ጊዜ ከድምፅ ጋር) ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለማስተላለፍ የሚረዳ የመልዕክት ማስራጫ መንገድ ነው። ይህ ከሆነ ዘንዳ ቴሌቪዥን ምስል መቅጃውንም ሆነ ምስል መቀበያውን መሳሪያ ሁሉ ያጠቃልላል ግን በተለምዶ ቴሌቪዥን የምንለው ምስል መቀበያውን ብቻ ነው። በ1873 እ.ኤ.አ. (1865 ዓም) የእንግላንድ ኤንጅኔር ውሎቢ ስሚስ ባደረገው ጥረት ጥንተ ንጥሩ ሴሌኒይም ብርሃን-አስተላልፎሽ መሆኑን ገለጸ። በ1884 እ.ኤ.አ. ፓውል ጎትሊብ ኒፕኮው የተባለ ጀርመናዊ ክብ የሆነ ዲስክን በስፓይራል በምብሳት ይህ ዲስክ በተሽከረከረ ቁጥር ከፊትለፊቱ የሚመጣውን ብርሃን በቀዳዶቹ በማሾለክ ከሴሌኒይም በተሰራ የካሜራ ግድግዳ ላይ እንዲያርፍ አደረገ። ግድግዳው ብርሃን ሲነካው ያንን ብርሃን ወደ ኮሬንቲ ሃይል በመቀየር ምስልን በኮሬንቲ መልክ በሽቦ ለመላክ ቻለ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ አምፕሊፋየር ስላልነበር የሚላከው ምስል እምብዛም አመርቂ አልነበረም። ከ27 አመታት በኋላ በ1911 እ.ኤ.አ. የራሻው ቦሪስ ሮዚንግ ለመጀመሪያ ጊዜ የሲርቲን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፣ አሁንም ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል ቻለ። ነገር ግን የሚንቀሳቀሱት ምስሎች የጂዎሜትሪ ቅርጽ ነበራቸው ማለትም ሶስት ማዕዘን፣ አራት ማእዘን ወዘተ... ከ7 አመታት በኋላ በ1925 እ.ኤ.አ. ጆን ሎጂ ቤርድ የተሰኘው የስኮትላንድ ተመራማሪ 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለመላክ ቻለ ከዚያም በ1926 እ.ኤ.አ. ጥቁርና ነጭ የሆኑ ምስሎችን ለማስተላለፍ በቃ። በዚህ ጊዜ የሚላኩት ምስል ጥራት 30 መስመር በአንድ ጊዜ ነበር፣ በዚህም ምክንያት የሰውን ፊት ለመለየት አስቸጋሪ ቢሆንም ግን ይቻል ነበር። አቶ ቤርድ በ 1918 ዓ.ም. (26 January 1926 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የቴሌቪዥን መግለጫ ሰጠ። በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ የተሰኘው የቤል ላብራቷር ተቀጣሪ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ መላክ ቻለ። ቀጠል አድርጎም በራዲዮ ወደ ዊፓኒ ኒው ጀርሲ ለመላክ በቃ። በዚያው አመት ፊሎ ፍራንስዎርዝ የመጀመሪያውን የተሟላና በኤሌክትሪክ ስካኒንግ ብቻ የሚስራውን የቴሌቭዥን ስርዓት በተግባር አዋለ።.በጥር 1928 እ.ኤ.አ. (1920 ዓም) መጀመርያው የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያ በስከነክተዲ፣ ኒው ዮርክ ተከፈተ፤ እስከ ዛሬም ድረስ ያሰራጫል። \n \nጥያቄ: ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል የሚያስችል መሳሪያ ሲርቲን ቴክኖሎጂ በመጠቀም የፈጠረው ማነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ቦሪስ ሮዚንግ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቅዱስ ላሊበላ ቅዱስ ላሊበላ በ 1101 አ.ም ትህሳስ 29 ቀን ከ እናቱ ከኬርዮርና ከአባቱ ዛንስዮም ላሰታ ቡግና ወረዳ ሮሃ ከተባለች ቦታ ከፍልፍል ቤተ መቅደስ ውስጥ ተወለደ በዚህ ፍልፍል ቤተ-መቅደስ ውስጥ እድገቱን አደረገ ስድስት አመት ሲሞላው ቤተ-መንግስት አባ ዳንእል የተባሉ መምህር ተቀጥረውለት ከ ፊደል እስከ ዳዊት አጠናቆ ከዚያም የተማረውን የዕሁፍ ጥበብ በቤተ ጎሎጎታ ደብረ ሲና በሚገኘው ከ ኪዳነ ምህረት መንበር ታቦት ዙሪያ ላይ እራሱ የተዓፋቸው የሚዐለይበት ዕሁፎቸች ይገኛሉ፡፡ ቅዱስ ላሊበላ 12 አመት ሲሞላው አባቱ ዘንሳዮም 40 አመት ነግሶ በተወለደ በ 76 አመቱ ከዚህ አለም በ ሞት ተለየ ወድያው ብዙም ሳይቖይ እናቱ ኬርዮርና በሞት ተለየች፡፡ ቅዱስ ላሊበላ በ እናቱ ና አባቱ ህልፈተ ህይወተ በደረሰበት ሀዘን የተነሳ ሁሉን ነገር ለመርሳት ና የትምህርት ፍላጎት ለሞሞላት ጉዞውን ወደ ጎጃም በማድረገ አለም ስላሴ ከተባለው ደብር ከመምህር ኬፋ ሃዲሳቱን አጠናቖ በመመረቅ ወደ ሀገሩ ተመለሰ፡፡ በወቅቱም በኤትዮጵያ ላይ ነግሶ የነበረው ታላቅ ወንድሙ ቅዱሰ ገብረ ማሪያም ነበር ይህ እንዲህ እያለ በእህቱ ላይ እሱ ሊነግስ መሆኑ ቅናት አሳደረባት ቅዱስ ላሊበላ ሁሌም እሚጠጣው ባህላዊ መድሃኒት ውስጥ መርዝ በመጨመር ታስቀምጥለታለች አትሙት ያላት ነፍስ ግን የሃገሬውን በሃል ምክንያት አድርጎ ሳይቀመስ አይሰጥምና አብሮት የነበረው ዲያቖን የተቀመጠውን መድሃኒት ቀምሶ ወደ ነበረበት ጠረቤዛ ላይ አንዳሰቀመጠው ወድያውኑ ህይወቱ ታልፋለች ቅዱስ ላሊበላ ይህን ባየ ጊዚ እኔን ለማጥፋት የመጣው መድሃኒት የሌላውን ነፍስ አጠፋች በማለት የቀረውን መድሃኒት በመጠጣት ለሶሰት ለሊት እንደ ወደቀ ቀረ ከዚያም ነዋሪው ገንዞ ለመቅበር ሲዘጋጁ የሰውነቱ ሙቀት አልተለየውም ነበር ይሄን ጊዜ ወድያው ቅዱስ ላሊበላ ነቃ የተመለከቱት ሰዎች ተደናገጡ ከዚያም ይህ ሁሉ ነገር በእህቱ መደረጉ ያሳዘነው ቅዱስ ላሊበላ በመነሳት ጉዞውን ወደ ጫካ አደረገ ኑሮውንም ለረጅም አመት እዚያው አደረገ ይህ እንዲ እንዳለ ሚስት እምትሆነውን ሴት አገኝ ቤተሰቧን በማስጠየቅ በቤተክርስትያን ስርአት ተጋብተው ጥቂት አመት እንደቆዩ ጉዞውን እየሩሳሌም አደረገ ለተከታታይ 13 አመታትም ቆይታ በኋላ ወደ ባለቤቱ ተመልሶ ከወንድሙ ከ ቅዱስ ገብረ ማሪያም ጋር እርቅ በማውረድ ቅዱስ ገብረ ማሪያም ንግስናውን ለቅዱስ ላሊበላ በተወለደ በ57 አመቱ በማስረከብ ኑሮውን በገዳም አደረገ፡፡ \n \nጥያቄ: ቅዱስ ላሊበላ ለምን ያህል ጊዜ ነገሰ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 40 አመት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቲቪ በ1950ዎቹ እንደ ብርቅ በሚታይበት ዘመን በ1957 አ.ም ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተከፈተ፡፡ ታዲያ የመጀመሪያዋ የቲቪ ሴት አንባቢ የነበሩት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ ነበሩ፡፡ ይህ ለወይዘሮ እሌኒ ትልቅ የታሪክ አጋጣሚ ነበር፡፡ በወቅቱ ሳሙኤል ፈረንጅ አንዱ ወንድ ተናጋሪ ነበር፡፡ በኢትዮጵያ ሬድዮ በጋዜጠኝነቱና በህዝብ ግንኙነት ሙያ ያገለገሉት ወይዘሮ እሌኒ ከሰው ጋር በቀላሉ የሚግባቡ ተወዳጅ ደግ እናት ነበሩ፡፡ በበጎ አድራጎት ምግባራቸው በስፋት የሚታወቁት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ የወጣት ሴቶች ክርስቲያናዊ ማህበር ውስጥ በንቃት በመሳተፍ ማህበሩን ረድተዋል፡፡ በተጨማሪም በአንሚ ሬድዮ ከ20 አመት በፊት ያገለገሉት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ ከአለም አቀፍ መገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች ጋር የጠበቀ ቁርኝት ነበራቸው፡፡ ከዚህም ባሻገር አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሀን ወደ ሀገራችን በሚመጡበት ጊዜ ሁኔታዎችን በማመቻቸት ስራ ላይ ትልቅ ሚና አበርክተዋል፡፡ ቤታቸው ሲኬድ ሁልጊዜም ከአረንጓዴ ተክል ጋር የማይታጡት ወይዘሮ እሌኒ ነፋሻማ ቦታ ልዩ ትርጉም ይሰጣቸዋል፡፡ አንድ ከዛፍ ጋር በተያያዘ በፎቶግራፍ የታገዘ መጽሀፍም ለህትመት አብቅተዋል፡፡ በዚህም መጽሀፍ አማካይነት ስለ ሀገራችን ዛፎች በቂ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ሙከራ አድርገዋል፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ የተለያዩ ሀገሮችን ቴምብሮችን ያሰባስባሉ፡፡ በተለይ ደግሞ ለታሪክ ልዩ ፍቅር ያላቸው ወይዘሮ እሌኒ የጡረታ ጊዜያቸውን በማንበብ እና በምርምር ያሳልፉ ነበር፡፡ ወይዘሮ እሌኒ በ1959 አመተ ምህረት ከኢንጂነር ሰይፉ ለማ ጋር ጋብቻን መስርተው 3 ሴት ልጆችን ወልደው አንድ ልጅ ደግሞ አሳድገዋል፡፡ ወይዘሮ እሌኒ በተወለዱ በ79 አመታቸው ሮብ ሀምሌ 14 2013 ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን የቀብር ስነስርአታቸውም ሀሙስ ሀምሌ 15 2013 ከቀኑ በ6 ሰአት በየካ ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡ \n \nጥያቄ: ወ/ሮ እሌኒ በየትኛው የበጎ አድራጎት ድርጅት ውስጥ ትልቅ ስራን ሰርተዋል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የወጣት ሴቶች ክርስቲያናዊ ማህበር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቦትስዋና ቦትስዋና ወይም በይፋ የቦትስዋና ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ Republic of Botswana ሰጿና፡ Lefatshe la Botswana) በደቡባዊ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ አገር ናት። ቦትስዋና የቀድሞ የብሪታንያ ቅኝ ግዛት ስትሆን ነፃነቷን በመስከረም ፳ ቀን ፲፱፻፶፱ ዓ.ም. ከተቀዳጀች በኋላ መሪዎቿ በነፃ ዴሞክራሲያዊ ምርጫዎች ተመርጠዋል። ቦትስዋና ሜዳማ ስትሆን ከሰባ ከመቶ በላይ በካለሃሪ በርሃ የተሸፈነች ናት። በደቡብና ደቡብ ምሥራቅ ከደቡብ አፍሪካ፣ በምዕራብና ሰሜን ከናሚቢያ እና በሰሜን ምሥራቅ ከዚምባብዌ ጋር ትዋሰናለች። ከዛምቢያም ጋር በደንብ ያልተወሰነ ቢበዛ በመቶ ሜትር የሚቆጠር ወሰን አላት። \n \nጥያቄ: ቦትስዋና ከቅኝ ግዛት ነጻነቷን ያገኘችው መቼ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በመስከረም ፳ ቀን ፲፱፻፶፱ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nታንዛኒያዊው ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ የ2021 የኖቤል የሥነ ጽሑፍ አሸናፊ መሆናቸውን የስዊድን አካዴሚ መስከረም 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1986 ዎሌ ሾይንካ በሥነ ጽሑፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑ ከ35 ዓመታት በኋላ አብዱልራዛቅ ጉራህ ሁለተኛው ጥቁር አፍሪካዊ ያሰኛቸውን ክብር ተቀዳጅተዋል፡፡ በመላው አፍሪካ ደረጃ ስድስተኛ ተሸላሚ ናቸው፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው፣ አብዱልራዛቅ ለአሸናፊነታቸው ከስዊድኑ የኖቤል ሽልማት ድርጀት 10 ሚሊዮን ክራውን ወይም 1.14 ሚሊዮን ዶላር ያገኛሉ፡፡ የ73 ዓመቱ አዛውንት ጉራህ ጎልተው የሚታወቁትን ‹‹ፓራዳይዝ›› (Paradise) እና ‹‹ዲዘርሽን›› (Desertion) ጨምሮ የ10 ልብ ወለዶች ደራሲ ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: ደራሲ አብዱልራዛቅ በ2021 የሥነ ጽሑፍ ኖቤል ሽልማት በማሸነፋቸው ምን ያህል ገንዘብ ያገኛሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 10 ሚሊዮን ክራውን ወይም 1.14 ሚሊዮን ዶላር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቀጭኔ ከዝሆን በስተቀር ማንኛውም ሌላ እንስሳ ሊደርስ በማይችልበት ከፍታ ላይ የሚገኙ ረዣዥም ቀንበጠቦችን ለመብላት የሚያስችል አስደናቂ አፈጣጠር አላት። ልዩ የሆነ የመቆንጠጥ ችሎታ ያለው የላይኛው ከንፈሯና እንደተፈገለው የሚተጣጠፍ ችሎታ ያለው ምላሷ ሹል በሆኑ እሾሆች የታጠሩ ቅጠሎችን ለመቀንጠብ ያስችሏታል። ቀጭኔዎች በቀን እስከ 34 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕፅዋት መመገብ ይችላሉ። የተለያዩ ዕፅዋትን የሚበሉ ቢሆኑም ይበልጥ የሚመርጡት በአፍሪካ ሜዳዎች የሚገኙትን እሾሃማ ግራሮች ነው። አንድ ወንድ ቀጭኔ ምግብ ለመፈለግ ምላሱን እስከ 42 ሳንቲ ሜትር መዘርጋት ይችላል። የቀጭኔ አንገት በጣም አስደናቂ የሆነ የመተጣጠፍ ችሎታ አለው። ይህም ላይኛዎቹን የዛፍ ቅርንጫፎች ለመቀንጠብ በምታደርገው እንቅስቃሴ ረዥሙን ራሷን እንደ ልቧ ለማዘንበልና ለማዟዟር ያስችላታል። ለቀጭኔ ወደ ላይ መንጠራራት በጣም ቀላል ነገር ሲሆን ተጎንብሶ ውኃ መጠጣት ግን ይከብዳታል። ወደ ውኃ ጉድጓድ በምትቀርብበት ጊዜ የፊት እግሮቿን ቀስ በቀስ ከፍታ ካራራቀቻቸው በኋላ ወደ ውኃው ለመድረስ እንድትችል ሁለት ጉልበቶቿን አጠፍ ታደርጋለች። ቀጭኔዋ እንዲህ ባለው አመቺ ባልሆነ ሁኔታ እያለች ረዥም አንገቷን እስከ መጨረሻ ትዘረጋለች። ደግነቱ ግን ከምትመገባቸው ቅጠላ ቅጠሎች በቂ እርጥበት ስለምታገኝ ቶሎ ቶሎ መጠጣት አያስፈልጋትም። የቀጭኔ አንገትና ትከሻ የቅጠል ቅርፅ ባላቸውና ቀጫጭን በሆኑ ነጭ መስመሮች ያጌጠ ነው። ቀለማቸው የተለያየ ሲሆን ከወርቃማ ዳለቻ አንስቶ እስከ ቡናማ እንዲያውም ጠቆር እስካለ ቀለም ይደርሳል። የቀጭኔ ዕድሜ እየገፋ በሄደ መጠን ቀለሟም እየጠቆረ ይሄዳል። ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው። አንዲት ነፍሰ ጡር ቀጭኔ ልጅዋን ከ420 እስከ 468 ለሚደርሱ እርግዝና ቀናት ከተሸከመች በኋላ ሁለት ሜትር ቁመት ያለው ግልገል ትወልዳለች። ግልገሏ በምትወለድበት ጊዜ ራስዋን ታስቀድምና ከሁለት ሜትር ከፍታ ላይ ወደ መሬት ትወረወራለች። ይሁን እንጂ በ15 ደቂቃ ውስጥ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባት እየተውተረተረች ትነሳና ጡት ለመጥባት ዝግጁ ትሆናለች። ከሁለት ወይም ከሦስት ሳምንት በኋላ በደመ ነፍስ ተመርታ የግራር ቀንበጦችን መለቃቀም ስለምትጀምር ብዙም ሳትቆይ ረዥም እርምጃ ያላትን እናትዋን ተከትላ ለመሄድ የሚያስችል ጉልበት ታገኛለች። አንዲት የቀጭኔ ግልገል በጣም ውብ መልክ ሲኖራት የወላጆችዋ አነስተኛ ግልባጭ ነች። ቁመቷ ከቀጭኔ ርዝመት ጋር ሲወዳደር አጭር ብትሆንም ከብዙ ሰዎች ቁመት ግን ትበልጣለች። በእናቷ ጥንቃቄ የተሞላበት ጥበቃ ተማምና አላንዳች መሸበር አካባቢዋን የምትማትረው ግልገል ላያት ሁሉ ልዩ መስህብ አላት። ግልገል ቀጭኔዎች በተወለዱበት ወራት በግልገል መዋያ ተሰባስበው ሙሉውን ቀን ዕረፍት በማድረግ፣ በመጫወትና በአካባቢያቸው የሚሆነውን ነገር በመመልከት ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ። የቀጭኔ ግልገል ለማመን በሚያዳግት ፍጥነት ያድ⁠ጋል። በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ አንድ ሜትር የሚያክል ቁመት ሲጨምር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በእጥፍ ያድጋል። በአንድ ሳምንት ብቻ 23 ሳንቲ ሜትር ያህል ሊያድግ ይችላል! እናትዬው ለልጅዋ ከፍተኛ ጥበቃ የምታደርግ ሲሆን ልጅዋ የተወሰነ ርቀት እንድትዘዋወር ብትፈቅድላትም ሩቅ የማየት ችሎታ ስላላት በዓይኗ ትከታተላታለች። ቀጭኔ ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ስላላት ከአንበሳ በቀር የሚያጠቃት ጠላት የለም። ቢሆንም ይህችን የምታምር ፍጥረት የሰውን ያህል በብዛት አድኖ የገደለ የለም። ቀጭኔ በሚያምር ቆዳዋ፣ በሚጣፍጥ ሥጋዋና አንዳንዶች ምትሐታዊ ኃይል አለው በሚሉት ረዥምና ጥቁር ጭራዋ ምክንያት እጅግ ተፈላጊ ስለሆነች በአሁኑ ጊዜ የዚህች ሰላማዊ ፍጡር የወደፊት ሕልውና ስጋት ላይ ወድቋል። በአንድ ወቅት በብዙ የአፍሪካ አካባቢዎች እንደ ልብ ትታይ የነበረችው ቀጭኔ በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው በቂ ጥበቃ በሚደረግላት ፓርኮች ብቻ ሆኗል። የቀጭኔ አካላዊ ቅርጽና ግዝፈት ችግሮች ማስከተሉ አይቀርም ብሎ የሚያስብ ይኖር ይሆናል። በጣም ትልቅ ቁመትና ረዥም አንገት ስላላት የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖራትና ወደ ሁሉም የአካሏ ክፍሎች ደም እንዲደርስ ማድረግ የማይቻል ነገር ሊመስል ይችላል። ለምሳሌ ያህል ቀጭኔ አንገቷን ወደ መሬት ስታጎነብስ በስበት ኃይል ምክንያት ብዙ ደም ወደ ጭንቅላቷ ፈስሶ አንጎሏን ማጥለቅለቅ ነበረበት። ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ደሟ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ልቧ ተመልሶ ራሷን እስከ መሳት ሊያደርሳት ይገባ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ነገር አይደርስም። ለምን? የቀጭኔ የደም ዝውውር ሥርዓት በዓይነቱ ልዩ ለሆነው ለዚህች እንስሳ ቅርጽና መጠን እንዲያገለግል ሆኖ በታላቅ ጥበብ የተሠራ ነው። ልቧ ራሱ በጣም ትልቅ ሲሆን ደሙን ሦስት ሜትር ተኩል ገደማ ርቆ እስከሚገኘው እስከ አንጎላ ለመግፋት የሚያስችል አቅም አለው። በደቂቃ እስከ 170 ጊዜ የሚመታውና 7 ሳንቲ ሜትር ያህል ውፍረት ባለው ጡንቻ የተገነባው የቀጭኔ ልብ ከሰው የደም ግፊት በሦስት እጥፍ የሚበልጥ ግፊት ያመነጫል። ወደ አንጎል የሚሄደውን ደም የሚሸከመው ካሮቲድ የተባለው የደም ቧንቧና ከአንጎል ወደ ልብ የሚመለሰውን ደም የሚሸከመው ጀጉላር የተባለው የደም ቧንቧ እንዲህ ያለውን ከፍተኛ ግፊት መቋቋም የሚያስችል መጠን ሊኖራቸው ይገባል። በእርግጥም እነዚህ የደም ቧንቧዎች ከ2.5 ሳንቲ ሜትር በላይ ስፋት ያላቸው ከመሆኑም በላይ ጠንካራና የመለጠጥ ችሎታ ባላቸው ሕዋሳት የተገነቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥንካሬና የመለመጥ ችሎታ አላቸው። ቀጭኔ ከጭንቅላቷ ጎንበስ በምትልበት ጊዜ ወደ አንጎሏ የሚሄደውን የደም ፍሰት የሚቆጣጠሩ ልዩ መቆጣጠሪያዎች አሏት። አንጎልና አንገት በሚገናኙበት ቦታ ላይ ትልቁ ካሮቲድ የደም ቧንቧ ሬቴ ሚራቢሌ ተብሎ ከሚጠራ አስደናቂ የሆነ መረብ መሰል አካል ይገናኛል። በከፍተኛ ኃይል ተገፍትሮ የመጣው ደም እዚህ ጋር ሲደርስ በጣም በርካታ ወደሆኑ ትናንሽ የደም ሥሮች እንዲገባ ስለሚደረግ የደሙ ግፊት ተስተካክሎ በአንጎል ላይ ጉዳት የማያስከትል ይሆናል። ቀጭኔዋ ራስዋን ጎንበስ በምታደርግበት ጊዜ ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው መረብ ይለጠጣል፤ ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ይኮማተራል። ይህም የስበት ኃይል የሚያሳድረው ተጽዕኖ ሚዛኑን የጠበቀ እንዲሆን ማድረግና የደም ግፊቷ በእጅጉ ቀንሶ ራሷን የምትስትበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ለመከላከል ይረዳታል። የሳይንስ ሊቃውንት በጣም አስደናቂ ርዝመት ያለው የቀጭኔ አንገት ያሉት አከርካሪዎች ቁጥር ከአይጥ ወይም ከብዙዎቹ አጥቢ እንስሳ ጋር እኩል መሆኑን ሲያውቁ በጣም ተደንቀዋል! ይሁን እንጂ የቀጭኔ አከርካሪዎች በጣም ረዣዥሞችና እርስ በርሳቸው ልዩ በሆነ ሁኔታ የተሰካኩ በመሆናቸው እንደ ልብ ሊተጣጠፉ ይችላሉ። ቀጭኔ አንገቷን መጠምዘዝና ማጠፍ ስለምትችል ሁሉንም የአካሏን ክፍሎች ለመላስም ሆነ ረዣዥም የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ለመድረስ ትችላለች። \n \nጥያቄ: አንድ ወንድ ቀጭኔ ምግብ ለመፈለግ ምላሱን ምን ያህል መዘርጋት ይችላሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 42 ሳንቲ ሜትር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየ2010 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ የ2010 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ ፲፱ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የነበረ ሲሆን ከሰኔ ፬ እስከ ሐምሌ ፬ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. በደቡብ አፍሪካ ተካሄዷል። ውድድሩን ለማቅረብ የተካሄደው ዕጣ ውስጥ የአፍሪካ ሀገሮች ብቻ እንዲሳተፉ ነበር የተፈቀደው። ደቡብ አፍሪካ ግብፅና ሞሮኮን በማሸነፍ የመጀመሪያው የዓለም ዋንጫን ያቀረበች አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ፊፋ ለውድድሩ ያቀረበው ጠቅላላ የሽልማት ገንዘብ $420 ሚሊዮን ነው። ይህም ከ2006 እ.ኤ.አ. ውድድር ሽልማት ገንዘብ የስልሳ ከመቶ ዕድገት አለው። ከዚህ ውስጥ $40 ሚሊዮን የሚሆነው ተጫዋቾቹ ለሚጫወቱበት ክለቦች ተጫዋቾቹ ለሚደርስባቸው ጉዳት መካካሻ እንዲሆን ተሰጥቷል። ከውድድሩ በፊት እያንዳንዱ ቡድን ለዝግጅት ወጪው $1 ሚሊዮን ተረከበ። ግጥሚያዎቹ በዘጠኝ ከተማዎች ውስጥ በሚገኙ አስር ስታዲየሞች ውስጥ ነው የተካሄዱት። የዋንጫ ጨዋታው በጆሃንስበርግ ከተማ በሚገኘው ሶከር ሲቲ ስታዲየም ነው የተከናወነው። የምድብ ድልድል ሥነ ስርዓቱ በኬፕ ታውን፣ ደቡብ አፍሪካ በሚገኘው ኬፕ ታውን ዓለም አቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል በኅዳር ፳፭ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. ተከናወነ። ሥነ ስርዓቱ የቀረበው በደቡብ አፍሪካዊቷ ተዋናይ ሻርሊዝ ቴሮን እና የፊፋ ዋና ጸሐፊ ዠሮም ቫልክ ነው። የዕጣ ኳሶቹን ያወጡት ዴቪድ ቤክሃም፣ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ፣ ጆን ስሚት፣ መካያ ንቲኒ፣ ማቲው ቡዝ እና ሲምፊዌ ድሉድሉ ናቸው። የፊፋ ዳኛዎች ኮሚቴ ፳፱ ዳኛዎችን ለዓለም ዋንጫ መርጧል። እነዚህም ከኤ.ኤፍ.ሲ. አራት፣ ከካፍ አስር፣ ከኮንሜቦል ስድስት፣ ከኮንካካፍ አራት፣ ከኦ.ኤፍ.ሲ. ሁለት እና ከዩኤፋ አስር ዳኛዎችን ያጠቃልላል። እንግሊዛዊው ዳኛ ሀዋርድ ዌብ የዋንጫ ጨዋታውን እንዲዳኝ ተመርጧል። \n \nጥያቄ: በደቡብ አፍሪካ የተካሄደው ፲፱ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ከመቼ እስከ መቼ ተካሄደ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከሰኔ ፬ እስከ ሐምሌ ፬ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየባቢሎን ግንብ በመጽሐፍ ቅዱስ ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 11 ዘንድ፣ የባቢሎን ግንብ ሰማይን እንዲደርሱ የተባበሩት ሰው ልጆች የሠሩ ግንብ ነበር። ያ ዕቅድ እንዳይከናወንላቸው ለመከልከል፣ እግዚአብሔር እያንዳንዱ በተለየ ቋንቋ እንዲናገርበት ልሳናታቸውን አደባለቀ። መግባባት አልተቻላቸውምና ስራው ቆመ። ከዚያ በኋላ፣ ሕዝቦቹ ወደ ልዩ ልዩ መሬት ክፍሎች ሄዱ። ይህ ታሪክ ብዙ የተለያዩ ዘሮችና ቋንቋዎች መኖሩን ለመግለጽ እንደሚጠቅም ይታስባል። በትንተና የሰው ልጆች ሁሉ አንድ ኅብረተሰብ ሆነው የሠፈሩባት አገር ሰናዖር ለኤፍራጥስ ወንዝ ቅርብ ነበረች። ባቢሎን በጥንታዊ አካድኛ ምንጭ በተገኘ ባቢሉ (ባብ-ኢሉ) ማለት «የአማልክት በር» ለማለት ነው። በዕብራይስጥ ትርጉም ግን የ«ባቤል» ስም «መደባለቅ» ለማለት ለሚለው ቃል ይመስላል። ከውድቀቱ በፊት የተናገረው ቋንቋ አንዳንዴ «የአዳም ቋንቋ» መሆኑ ይባላል። በታሪክ አንዳንድ ሰው በግምት ያም ሆነ ይህ ቋንቋ መጀመርያው ቋንቋ እንደ ነበር የሚለው ክርክር አቅርቧል። ለምሳሌ ቋንቋው ዕብራይስጥ፣ አራማይስጥ፣ ግዕዝ ወይም ባስክኛ ቢሆንም እንደ ነበር በልዩ ልዩ አስተያየቶች ዘንድ ተብልዋል። \n \nጥያቄ: ሰዎች ወደ ሰማይ ለመውጣት የሰሩት ግንብ ምን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የባቢሎን ግንብ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ በሃገራችን ኢትዮጵያ ስም አጠራራቸው ከከበረ አባቶች አንዱ ጻድቅ ናቸው። ጻድቁ የተወለዱት በአምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ አካባቢ ሲሆን ወላጆቻቸው ንጉሥ ይስሐቅ እና ቅድስት እድና ይባላሉ ። የተወለዱበት አካባቢም ሮም ነው ። ስማቸው ብዙ ዓይነት ነው። ወላጆቻቸው ዘሚካኤል ሲሏቸው በበርሃ ገብረአምላክ ተብለዋል። በኢትዮጵያ ደግሞ አረጋዊ ይባላሉ። አቡነ አረጋዊ ምንም የንጉሥ ልጅ ቢሆኑም በልጅነታቸው መጻሕፍትን ተምረው ነበርና ጠፍተው ገዳም ገቡ። በዚያም በገዳመ ዳውናስ (ግብጽ) የታላቁ ቅዱስ ጳኩሚስ ደቀ መዝሙር ሆነው ከነ አባ ቴዎድሮስ ጋር ሥርዓተ መነኮሳትን ተምረዋል። ከመነኮሱ ከዓመታት በኋላም ወደ ሃገራቸው ሮም ተመልሰው በማስተማር ሰባት ያህል የቤተ መንግሥት ሰዎችን ወደ ምናኔ ማርከዋል። \"የት ልሒድ?\" ብለው ሲያስቡም ቅዱስ መልአክ በክንፉ ጭኖ ወስዶ ኢትዮጵያን አሳያቸው። ተመልሰውም ለስምንት ባልንጀሮቻቸው \"ሃገርስ ባሳየኋችሁ! ሐዋርያ ሳያስተምራት በሕጉ በሥርዓቱ ጸንታ የምትኖር\" ብለው ከስምንቱ ጋር ከቃልኬዶን ጉባዔ በኋላ በ፬፻፶፩ ዓም ወደ ኢትዮጵያ መጡ ። ከዘጠኙ ቅዳሳን ወደ ኢትዮጵያ ከሮምና ከመካከለኛው ምሥራቅ ከፈለሱት አንዱ አቡነ አረጋዊ ናቸው ። በዚህ ጊዜም እናታቸው ቅድስት እድናና ደቀ መዝሙራቸው አባ ማትያስ አብረው ነበሩ። ወደ ሃገራችን የመጡ በአራት መቶ ሰባዎቹ አካባቢ ሲሆን አልዓሜዳ በክብር ተቀብሏቸዋል። በቤተ ቀጢን (አክሱም) ተቀምጠውም መጽሐፍትን እየተረጎሙ ወንጌልን እየሰበኩ ቆይተዋል ። አቡነ አረጋዊ ለብዙ ጊዜ በዓት ፍለጋ ደክመዋል ። በመጨረሻም ደብረ ዳሞ ማረካቸዋለች ። ዘጠና ዘጠኝ አመት ሲሞላቸው ጌታ በመንፈቀ ለሊት ተገልጾ ምድራዊ መንግስትህን ትተህ ስላገለገልከኝ ህልፈት ሽረት የሌለባት ሰማያዊ መንግስቴን አወርሰሃለሁብሎ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ በስምህ የተማጸነውን እስከ አስራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ አንተም ከሞት ገጽ ትሰወራለህ ብሎ ተስፋቸውን ነገራቸው፡፡ እሳቸው መነኮሳቱን ሰብስበው ከእንግዲህ በሥጋ አታዩኝም ብለው ነግረዋቸው አበምኔት (የገዳም አባት ወይም አለቃ) ሾመውላቸው ጥቅምት አሥራ አራት ቀን በዚያው በደብረ ዳሞ ተራራ በስተምስራቅ አቅጣጫ እንደሄኖክ እንደ ኤልያስ ተሰውሯል ፡፡ \n \nጥያቄ: አቡነ አረጋዊ በየት አካባቢ ተወለዱ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሮም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nፋሽስት ቅዲስቲቱዋን ኢትዮጵያን ለማዋረድ ለመዝረፍና ለመግዛት ለሁለተኛ ጊዜ ከፍተኛ ዝግጅቱን አጠናቆ በ1928 ዓም 300, 000 ሰራዊት 160 ቦንብ ጣይ አውሮፕላኖች 450 ታንኮች 2000 የመጉዋጉዋዣ መኪናዎችን በማሰማራት ድንበር አልፎ ጦርነት በመክፈት ከገጠር እስከ ከተማ ህዝቡን ያለ እርህራሄ ጨፈጨፈ። በዚህ የጅምላ ጭፍጨፋ ላይ የመጀመሪያውን ህይወት ያለዉን ነገር ሁሉ የሚያጠፋውን “ማስተርድ ጋዝ” የሚባል ኬሚካል መሳሪያ በመጠቀም ታሪክ ይቅር የማይለው ወንጀል ፈጸመ። በዚያን ክፉ ቀን የነጻነትና የሀገር ትርጉም የገባቸው የቁርጥ ቀን ልጆች በየአካባቢያቸው ፋኖዎችን በመምራት የእብሪተኛዉን የፋሽ ስት ጦር መግቢያ መዉጫ በማሳጣት ኢትዮጵያ ዉስጥ በሰላም መኖር እንደማይችል ተስፋ አስቆርጠዉታል። ከነዚህ ነበልባል የቁርጥ ቀን የኢትዮጵያ ልጆች መካከል ጠላትን በተከታታይ ዝርክርኩን አዉጥተው ከደቡብ ያሳደዱትና በመጨረሻው ዉጊያ ላይ ኢትዮጵያዊ በሚመስሉ የትግሬ ስርጎ ገብ ባንዶች ቆሰለው የተያዙትና በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉት ዉዱ የኢትዮጵያ የክፉ ቀን ልጅ ራስ ደስታ ዳምጠው ነበሩ። ራስ ደስታ ዳምጠዉን ያስያዛቸው የባንዳ ጦር መሪ ደግሞ የትግሬው ተክሉ መሸሻ የሚባል የጣሊያን ሎሌ ሲሆን የስብሃት ነጋ አጎት የናቱ ታላቅ ወንድም መሆኑ ተረጋግጦአል ተክሉ መሸሻ በጣሊያን ደጃዝማችነት ተሰጥቶት በደቡብ ኢትዮጵያ የኢጣልያ ባንዳ ጦር አዛዥ ሆኖ በአካባቢው ኢትዮጵያ ጦር አዛዥ የነበሩት ራስ ደስታ ዳምጠው ከበርካታ አስደናቂ ጀብዱ በሁዋላ ቆስለው በጉራጌ አካባቢ መስቃ ከተባለው ሥፍራ ተኝተው በስቃይ ላይ እያሉ ተክሉ የስለላ መረቡን ዘርግቶ እግር በግር ተከታትሎ በመያዝ ከግንድ ጋር አስሮ በጭካኔ ደብድቦ ከገደላቸው በኋላ ራሳቸውን ረግጦ በመቆም ፎተግራፍ በመነሳት ለጣልያኑ ጌታው ግዳይ ካቀረቡት እርካሽ የትግሬ ከሃዲዎች አን ዱ ነበር። የፋሽስት ጣሊያን ጦር ኢትዮጵያን ወሮ መናገሻ ከተማዋን አዲስ አበባን ለመያዝ ሲገሰግስ ጀምሮ ሶስቱ ቆራጥ የኢትዮጵያ ሌጆች (የሸንቁጥ) ልጆች አበበ ሸንቁጥ ተሾመ ሸንቁጥና ጥላሁን ሸንቁጥ በመርሃቤቴ በጅሩና በዠማ ወንዝ አካባቢ በመንቀሳቀስ “ዱሩ ቤቴ” በማለት ብዙ የአካባቢውን ጀግኖች አስከትለው የጣሊያንን ሀይል በመመከትና ከአገር በማባረር ከፍተኛ ገድል ፈጽመዋል። \n \nጥያቄ: ጣልያን ኢትዮጵያን ለመውረር ድጋሚ ሲመጣ ስንት ጦር ሠራዊት ነበረው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 300, 000 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nራስ መኮንን ልዑል ራስ መኮንን ወልደሚካኤል የሸዋ ንጉሥ የነበሩት የሣህለ ሥላሴ ልጅ የልዕልት ተናኘወርቅ እና የደጃዝማች ወልደሚካኤል ልጅ ናቸው። ግንቦት ፩ ቀን ፲፰፻፵፬ ዓ.ም ጎላ ወረዳ ደረፎ ማርያም በሚባል ሥፍራ ተወልደው፤ እስከ ፲፬ ዓመት ዕድሜያቸው ከአባታቸው ጋር ከኖሩ በኋላ ያጐታቸው የንጉሥ ኃይለ መለኮት ልጅ ዳግማዊ ምኒልክ ገና የሸዋ ንጉሥ እንደነበሩ፡ ወደርሳቸው ቤተ መንግሥት መጥተው፡ ባለሟል ሆኑ። በ፲፰፻፷፰ ዓ.ም ዕድሜያቸው ሀያ አራት ዓመት ሲሆን ከወይዘሮ የሺ እመቤት ጋር ተጋብተው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም የወደፊቱን ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ወለዱ። \n \nጥያቄ: ልዑል ራስ መኮንን ከባለቤታቸው ልዕልት ተናኘወርቅ ንጉሠ ነገሥት የሆኑትን ልጃቸውን የወለዱት መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nማርኮ ፖሎ ማርኮ ፖሎ (1254 - ጥር 8፣ 1324) ጥንታዊው የጣሊያን ተጓዥ እና ነጋዴ ነበር። ታዋቂነትም ያተረፈው በተለይ ወደቻይና እና ሞንጎሊያ ከተጓዙት አውሮጳውያን ቀደምትነት ስለነበረው ነው። በዚህ ምክንያት ከሱ በኋላ ዘግይተው የተነሱት እነ ክርስቶፎር ኮሎምበስ ሳይቀር ለሱ ከፍተኛ ግምት እና አድንቆት እንደነበራቸው ታሪክ ይዘክራል። 17 አመት ሲሞላው ከጣሊያን ቬኒስ ከተማ በመነሳት፣ መጀመሪያ በጀልባ ከዚያም በእግሩና በግመል ተራሮችን በርሃን አቆራርጦ ቤይቺንግ ቻይና (በድሮ ስሟ ካቴ) ለመድረስ ችሏል። በጊዜው ቻይና ትመራ የነበረው በሞንጎሉ መሪ ኩብላ ካህን የሚባለው የጌንጊዝ ካህን ልጅ ነበር። ስርዓቱም የዩዋን ሥርወ መንግስት ይባል ነበር። ለሚቀጥሉት 17 ዓመታት በኩብላ ካህን ቤተመንግስት አስተዳደር ተሰጥቶት መንግስቱን አገልግሏል። ከዚያም ወደ ጣሊያን በውቅያኖሶች አቋርጦ ተመልሷል። ወደ 600 የሚሆኑ አብሮ ተጓዦች ግን በበሽታና በጥቃት ሞተዋል። ይህ ተጓዥ ኑድል የተባለውን የቻይኖች የምግብ አይነት ወደ አገሩ ጣልያን በማምጣት የፓስታ ስራ አሰራርን ለጣሊያኖች ለመጀመሪያ ጊዜ አስተዋውቋል። በጣሊያኖች እርስ በርስ ጦርነት ተማርኮ እስር ቤት ከገባ በኋላ ለእስር ጓደኛው ርስቲቸሎ የነገረውን ታሪክ ረስቲቸሎ ጽፎ በማሳተም ለማርኮ ፖሎ በአውሮጳ ዙርያ ታላቅ መታወቅን አስገኝቶለታል። \n \nጥያቄ: ማርኮ ፖል በስንት ዓመቱ ነበር ከጣልያን ቬኒስ ከተማ ተነስቶ ጉዞ የጀመረው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 17 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበ ፰፻ (800) ዓመተ-ዓለም አካባቢ ደአማት የሚባል መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያና ኤርትራ ተቋቋመ። በሰሜን ኢትዮጵያ የምትገኘው የሀ የደአማት ዋና ከተማ ነበረች። በየመን የሚኖሩት ሳባውያን በደአማት ላይ ተፅዕኖ እንደነበራቸው የሚታመን ሲሆን ይህ ተፅዕኖ ምን ያህል እንደሆነ ግን በእርግጥ አይታወቅም። ወደ ፬፻ (400) ዓመተ-ዓለም አካባቢ የደአማት መንግስት ከስልጣን ሲወድቅ በትናንሽ መንግስቶች ተተካ። ከነዚህ ትናንሽ መንግስቶች አንዱ አክሱም ሲሆን አካባቢውን እንደገና በአንድነት ለመግዛት ችሎ ነበር። የአክሱማውያን ስፈን በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥታዊ ማኅበረሰብ ነበር። በፋርስ ፣ ሮማ እና ቻይና ይገኙ ከነበሩ ታላላቅ መንግሥታት በወደረኛነት የሚቆጠር ትልቅ ኅይል ነበር። በ4ኛው ምእተ-ዓመት አክሱም ወደ ክርስትና ተለወጠ። በ፮ኛው ምእት ዓመት የአክሱማውያን ግዛታዊ ቁጥጥር የዛሬዋን የመን ግዛት ይጨምር ነበር። ግን በ፮ኛው እና በ ፰ኛው አምኣት የአክሱም ሥልጣኔ በእስልምና መነሣት እና መስፋፋት ተዳክሞ ለውድቀት በቃ ። ተከታዩ የዛጔ ሥርወ-መንግሥት ልክ በድንገት እንደተነሳ በድንገት ሲያበቃ ፣ ይኵኖ አምላክ ሥልጣን በ ፲፪፻፷፪ (1262) ዓ. ም. ጨበጡ ፤ እንዲያም ሲል የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥትን መለሱ። ከዚያም ለብዙ ዘመናት የሰለሞናዊው መንግስት ከጠለ። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ታሪክ ከአክሱም መንግሥት ቀጥሎ ስልጣን ላይ የወጣው መንግስት ማን ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የዛጔ ሥርወ-መንግሥት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nፋሽስት ቅዲስቲቱዋን ኢትዮጵያን ለማዋረድ ለመዝረፍና ለመግዛት ለሁለተኛ ጊዜ ከፍተኛ ዝግጅቱን አጠናቆ በ1928 ዓም 300, 000 ሰራዊት 160 ቦንብ ጣይ አውሮፕላኖች 450 ታንኮች 2000 የመጉዋጉዋዣ መኪናዎችን በማሰማራት ድንበር አልፎ ጦርነት በመክፈት ከገጠር እስከ ከተማ ህዝቡን ያለ እርህራሄ ጨፈጨፈ። በዚህ የጅምላ ጭፍጨፋ ላይ የመጀመሪያውን ህይወት ያለዉን ነገር ሁሉ የሚያጠፋውን “ማስተርድ ጋዝ” የሚባል ኬሚካል መሳሪያ በመጠቀም ታሪክ ይቅር የማይለው ወንጀል ፈጸመ። በዚያን ክፉ ቀን የነጻነትና የሀገር ትርጉም የገባቸው የቁርጥ ቀን ልጆች በየአካባቢያቸው ፋኖዎችን በመምራት የእብሪተኛዉን የፋሽ ስት ጦር መግቢያ መዉጫ በማሳጣት ኢትዮጵያ ዉስጥ በሰላም መኖር እንደማይችል ተስፋ አስቆርጠዉታል። ከነዚህ ነበልባል የቁርጥ ቀን የኢትዮጵያ ልጆች መካከል ጠላትን በተከታታይ ዝርክርኩን አዉጥተው ከደቡብ ያሳደዱትና በመጨረሻው ዉጊያ ላይ ኢትዮጵያዊ በሚመስሉ የትግሬ ስርጎ ገብ ባንዶች ቆሰለው የተያዙትና በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉት ዉዱ የኢትዮጵያ የክፉ ቀን ልጅ ራስ ደስታ ዳምጠው ነበሩ። ራስ ደስታ ዳምጠዉን ያስያዛቸው የባንዳ ጦር መሪ ደግሞ የትግሬው ተክሉ መሸሻ የሚባል የጣሊያን ሎሌ ሲሆን የስብሃት ነጋ አጎት የናቱ ታላቅ ወንድም መሆኑ ተረጋግጦአል ተክሉ መሸሻ በጣሊያን ደጃዝማችነት ተሰጥቶት በደቡብ ኢትዮጵያ የኢጣልያ ባንዳ ጦር አዛዥ ሆኖ በአካባቢው ኢትዮጵያ ጦር አዛዥ የነበሩት ራስ ደስታ ዳምጠው ከበርካታ አስደናቂ ጀብዱ በሁዋላ ቆስለው በጉራጌ አካባቢ መስቃ ከተባለው ሥፍራ ተኝተው በስቃይ ላይ እያሉ ተክሉ የስለላ መረቡን ዘርግቶ እግር በግር ተከታትሎ በመያዝ ከግንድ ጋር አስሮ በጭካኔ ደብድቦ ከገደላቸው በኋላ ራሳቸውን ረግጦ በመቆም ፎተግራፍ በመነሳት ለጣልያኑ ጌታው ግዳይ ካቀረቡት እርካሽ የትግሬ ከሃዲዎች አን ዱ ነበር። የፋሽስት ጣሊያን ጦር ኢትዮጵያን ወሮ መናገሻ ከተማዋን አዲስ አበባን ለመያዝ ሲገሰግስ ጀምሮ ሶስቱ ቆራጥ የኢትዮጵያ ሌጆች (የሸንቁጥ) ልጆች አበበ ሸንቁጥ ተሾመ ሸንቁጥና ጥላሁን ሸንቁጥ በመርሃቤቴ በጅሩና በዠማ ወንዝ አካባቢ በመንቀሳቀስ “ዱሩ ቤቴ” በማለት ብዙ የአካባቢውን ጀግኖች አስከትለው የጣሊያንን ሀይል በመመከትና ከአገር በማባረር ከፍተኛ ገድል ፈጽመዋል። \n \nጥያቄ: ጣልያን ኢትዮጵያን ለመውረር ድጋሚ የመጣበት ዓመት መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ1928 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nህንድ ፈጣን የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ ሰርታለች፡፡ ሃገሪቱ የሰራችው መመርመሪያ ልክ እንደ እርግዝና መመርመሪያ ውጤቱን በፍጥነት ሊያሳይ የሚችል ነው ተብሏል፡፡ በዚህም ከአንድ ሰዓት በታች በሆነ ጊዜ ውስጥ ውጤቱን እንደሚያደርስ ነው የተነገረው፡፡ በ2 ሺህ ህሙማን ላይ ምርመራ ተደርጎም ውጤታማነቱ መረጋገጡ ተገልጿል፡፡ ፌሉዳ የተባለው ይህ መመርመሪ ኪት ዋጋው 500 የህንድ ሩፒ ወይም ሰባት ዶላር አካባቢ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የህንድ መንግስት ዋና የሳይንስ አማካሪ ፕሮፌሰር ኬ ቪጃይ ራጋቫን እንዳሉትም ሙከራው ቀላል ፣ ትክክለኛ፣ አስተማማኝ እና ወጪ ቆጣቢ ነው ፡፡ ህንድ በአሁኑ ጊዜ ከ1 ሺህ 200 በላይ ላቦራቶሪዎች ያሏት ሲሆን በቀን 1 ሚሊየን ናሙናዎችን እየመረመረች ትገኛለች፡፡ \n \nጥያቄ: ሕንድ ምን ያህል የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ ላቦራቶሪዎች አሉዋት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከ1 ሺህ 200 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበ596 ዓ.ም. በጃፓን 17 አንቀጽ ያለ ሕገ መንግሥት በልዑል ሾታኩ እንደተጻፈ ይታመናል። እንዲሁም በ614 ዓ.ም. ከነቢዩ መሐመድ የወጣው የመዲና ሕገ መንግሥት ዕጅግ ጥንታዊ ምሳሌ ነው። በዌልስ በ940 ዓ.ም. አካባቢ ንጉስ ህወል ዳ ሕጎቹን ጻፉ። በዛሬው ሩሲያ ደግሞ የክዬቭ ታላቅ መስፍን ያሮስላቭ ጥበበኛው ፕራቭዳ ያሮስላቫ የተባለውን ሕገ መንግሥት በ1009 ዓ.ም. ያህል ሠሩ። ይህ ሕግ በ1046 ታድሶ በኪዬቭ ሩስ በሙሉ ህጝ ሆነ። በስሜን አሜሪካ የኖሩ ኗሪ ጎሣ ሆደነሾኒ 'የአፈ ቃል' ሕገ መንግሥት «ጋያነሸጎዋ» የነበራችው ከ1080-1140 ዓ.ም. አካባቢ ጀምሮ እንደሆነ ይታመናል። ይህ ሕግ በከፊል ለአሜሪካ ሕገ መንግሥት ተጽእኖ እንደነበረው ይታመናልና የአሜሪካ ምክር ቤት በ1981 ዓ.ም. ይህንን ግንዛቤ አስታወቀ። በእንግሊዝ አገር በ1092 ዓ.ም. ንጉስ 1 ሄንሪ የነጻነት ሥርአት የተባለውን ሰነድ አዋጀ። ይህ መጀመርያ የንጉሱን ሥልጣን ወሰኖ ንጉሡ ለቤተ ካህናትና ለቤተ መሳፍንት ወገኖች የሚገባውን እንቅብቃቤ ገለጸ። ይህም መሰረት በመኳንንቱ ሲዘረጋ በ1207 ዓ.ም. የእንግሊዝ ንጉሱን ዮሃንስ (ጆን) ማግና ካርታ («ታላቅ ሥርዓት») የሚባለውን ሰነድ እንዲፈርሙት አስገደዱዋቸው። ከዚሁ መሃል ቁም ነገር የሆነው ንጉሡ ያለ ሕጋዊ ሂደት ማንንም ሰው እንዳይገድሉ፣ ከአገር እንዳያሳደዱ፣ ወይም እስር ቤት እንዳያስገቡ ከለከላቸው። በዚያ ወቅት ያ ሰነድ በእንግሊዝ አገር የነጻነት መሠረት ሆነ። በ1212 እና 1222 ዓ.ም. መካከል አንድ የሳቅሰን አስተዳዳሪ አይከ ቮን ረፕጎቭ ያቀነባበረው ሕግጋት ሳቅሰንሽፒግል በአንዳንድ ጀርመን ክፍላገር እስከ 1892 ዓ.ም. ድረስ ላይኛ ሕገ መንግሥት ሆነ። በ1228 ዓ.ም. ሱንዲያታ ከይታ ማሊ መንግሥትን ለማወሐድ የ'አፈ ቃል' ሕገ መንግሥት አወጡ። ይህ ሕግ 'ኩሩካን ፉጋ' ተብሎ ነበር። \n \nጥያቄ: በ596 ዓ.ም. በልዑል ሾታኩ የተደነገገው ባለ 17 አንቀጽ ሕገ መንግሥት ጥቅም ላይ የዋለው የት ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በጃፓን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቀጭኔ ቀጭኔ በአፍሪካ የሚኖር ባለሙሉ ጣት ሸሆኔ ጡት አጥቢ አራዊት ሲሆን በምድር ከሚገኙ እንሰሳት በርዝማኔ የመጀመሪያውን ደረጃ ይዞ ይገኛል። ወንዱ ከ 4.4 እስከ 5.5 ሜትር ርዝማኔና 1,360 ኪሎግራም ክብደት ያስመዘግባል። እስካሁን በሪኮርድ የተያዘው የ 5.87ሜና የ2000ኪ.ግ ቀጭኔ ነው። ሴቶቹ በጥቁቱ አነስ ብለው ይታያሉ። እነዚህን ፍጥረታት በአራዊት ማቆያ ቦታዎች አንገታቸውን ከታጠሩበት አጥር በላይ ወጣ አድርገው የተመለከተ ሰው በአፍሪካ ቁጥቋጦዎች ነፃ ሆነው ሲሮጡ ያላቸውን ውበትና ግርማ መገመት ያስቸግራል። የቀጭኔ እንቅስቃሴ ትልቅ ግርማ ያለውና እንደ ውኃ ሙላት የሚፈስ ነው። በገላጣው የግጦሽ መስክ ላይ በሚጋልቡበት ጊዜ ቁመናቸው ትንሽ እንቅፋት ቢነካቸው ወድቀው የሚሰባበሩ ያስመስላቸዋል። ይሁን እንጂ እስከ 1, 300 ኪሎ ግራም የሚደርስ ክብደት ያላቸው ወንድ ቀጭኔዎች ቀልጣፋና ምንም የማያደናቅፋቸው ሯጭ ከመሆናቸውም በላይ በሰዓት እስከ 60 ኪሎ ሜትር ሊሮጡ ይችላሉ። ይህች አስደናቂ ፍጡር የምትገኘው በአፍሪካ ብቻ ነው። እርጋታዋና ሰላማዊ ተፈጥሮዋ ዓይን ይስባል። የቀጭኔ ፊት በዓይነቱ ልዩ የሆነና ቆንጆ ሊባል የሚችል ሲሆን ረዥምና ጠባብ ጆሮዎች፣ ሁለት ትናንሽ ቀንዶች እንዲሁም ጠቆር ያለ ለስላሳ ጠጉር አላት። ዓይኖቿ በጣም ትላልቅና ጥቁር ሲሆኑ ረዣዥም በሆኑ ቅንድቦች ይጠበቃሉ። ቀጭኔ ያን በመሰለ ከፍታ ላይ ሆና ሩቅ ስትመለከት ፊቷ ላይ የየዋህነት ገጽታ ይታይባታል። በጥንት ዘመናት ቀጭኔ ባላት አስደሳች ቁመና እንዲሁም ጨዋ፣ ዓይነ አፋርና ሰላማዊ ባሕርይ ያላት በመሆኑ በጣም ተወዳጅና ትልቅ ግምት የሚሰጣት ነበረች። በብሔራት መካከል ሰላምና በጎ ፈቃድ መኖሩን ለማመልከት የቀጭኔ ግልገሎች ለነገሥታትና ለገዥዎች በገጸ በረከትነት ይሰጡ ነበር። ጥንታዊ በሆኑት የአፍሪካ አለቶች ላይ ቀለማቸው የደበዘዘ የቀጭኔ ሥዕሎች እስከ ዛሬ ይታያል። ከእንስሳት ሁሉ ቀጭኔን በቁመት የሚወዳደር የለም። ሙሉ ዕድሜ ላይ የደረሱ ወንድ ቀጭኔዎች ከእግራቸው ኮቴ አንስቶ እስከ ቀንዳቸው ድረስ ከ5.5 ሜትር የሚበልጥ ርዝመት አላቸው። በግብፃውያን ጥንታዊ ሥዕላዊ የአጻጻፍ ዘዴ ቀጭኔ በረዥም ቁመቷና አርቆ በመመልከት ችሎታዋ ምክንያት “መተንበይ” የሚለውን ግሥ ትወክል ነበር። ቀጭኔ በአፍሪካ መስኮች በሚሰማሩት የሜዳ አህዮች፣ ሰጎኖች፣ አጋዘኖችና ሌሎች እንስሳት መካከል ስትቆም እንደ ማማ ሆና ትታያለች። ቁመቷና አርቆ የማየት ችሎታዋ ማንኛውንም አደጋ ገና ከሩቅ ለማወቅ ያስችላታል። ስለዚህ የቀጭኔ መኖር ለሌሎች እንስሳት የመረጋጋት ስሜት እንደሚፈጥር ጥርጥር የለውም። \n \nጥያቄ: ቀጭኔዎች በሰዓት ምን ያህል ኪ.ሜ ሊሮጡ ይችላሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በሰዓት እስከ 60 ኪሎ ሜትር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየስማርት ምሰሶ ቴክኖሎጂ ስማርት ከተሞችን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት አንዱ ግብዓት መሆኑን ስማርት ሲቲ ፕረስ ያትታል፡፡ ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ ኢትዮ ቴሌኮም ደምበኞች የዳታ አገልግሎት ማግኘት የሚያስችላቸውን ስማርት ምሰሶ በእንጦጦ ፓርክ ማስመረቁ ይታወሳል፡፡ የስማርት ምሰሶ ቴክኖሎጂ ከተለመዱት የመንገድ ዳር ምሰሶዎች ጋር የሚመሳሰል ነገር ግን ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን የያዘ ነው፡፡ ከሚሰጠው አገልግሎት መካከል አንዱ፥ ሰፊ አካባቢን መሸፈን የሚችል እጅግ ፈጣን የአራተኛ ትውልድ (4ጂ)፣ አምስተኛ ትውልድ ( 5ጂ) እና የዋይፋይ አገልግሎት ይሰጣል፡፡ ሌላው መኪና እና ታርጋን በቀላሉ መለየት የሚችሉ፣ የፊት ገፅታ ልየታን የሚያከናውኑ፣ ከፍተኛ የሆነ የቀለም ጥራት እና አጉልቶ የማሳየት አቅም ያላቸው የደህንነት ካሜራዎች ይኖሩታል፡፡ በተጨማሪም የአየር እና የድምፅ ብክለትን የሚለዩ፣ አደጋዎችን እና ወንጀሎችን በፍጥነት ለይቶ በመጠቆም የድንገተኛ ጊዜ ምላሽ አሰጣጡን የሚያቀላጥፉ መጠቆሚያዎችን ይይዛል፡፡ እንዲሁም የመንገድ መጨናነቅ እና አደጋን የመሰሉ እንዲሁም ሌሎች የድንገተኛ ጊዜ መልዕክቶች የሚሰራጩበት ዲጂታል ስክሪንም የሚኖረው ይሆናል፡፡ የስማርት ምሰሶ አገልግሎቶች በዚህ ብቻ የተገደበ ሳይሆን “ሁሉን በአንድ” በሚለው የቴክኖሎጂው መርህ መሰረት ሰዎች ከያዙት መሳሪያ ጋር በቀላሉ ተናቦ ለሌሎች አገልግሎቶች እንደሚውል ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ማዕከል ያገኘነው መረጃ ያመለክታል ፡፡ \n \nጥያቄ: ኢትዮ ቴሌኮም በእንጦጦ ፓርክ ያስመረቀው የስማርት ምሰሶ ቴክኖሎጂ ምን ጥቅም አለው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ስማርት ከተሞችን ለመገንባት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nፍቅር እስከ መቃብር ፍቅር እስከ መቃብር በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. በደራሲ ሀዲስ አለማየሁ የቀረበ ልብ ወለድ ሲሆን ሰብለ ወንጌል እና በዛብህ የሚባሉ የሁለት ገፀ ባህሪያትን ፍቅር ይተርካል። ይህ ድርሰት ከሌሎች ልብወለድ ሥራዎች ለየት የሚያደርገው ደራሲው ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ በፊደል አጠቃቀም ላይ ለውጥ አድርገው በማቅረባቸው ነው። ይኸውም ለምሳሌ ያህል ሦስት «ሀ»ዎች፣ ሁለት «ሰ»ዎች፣ ሁለት «ኣ»ዎች የመሳሰሉትን እንደ አንድ ወይም የመጀመሪያውን ብቻ በመያዝ ነው። በተጨማሪም ጠብቀው በሚነገሩ ቃላት ላይ ከላይ አንድ ነጥብ በማስቀመጥ ይታወቃሉ።ሀዲስ ኣለማየሁ በኢትዮጵያ ስነ-ፅሑፍ የራሳቸው ትልቅ አሻራ አኑረው ያለፉ አንጋፋ ደራሲ ናቸው። የታሪኩ ማጠቃለያ በዛብህ‌ ‌ጎጃም‌ ‌ማንኩሳ‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከእናቱ‌ ‌ከውድነሽ‌ ‌በጣሙና‌ ‌ከአባቱን‌ ‌ከቦጋለ‌ ‌መብራት‌ ‌ይወለዳል።‌ ‌በሽታ‌ ‌ይበዛበትና‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይባላል።‌ ‌እናቱ‌ ‌ከበሽታው‌ ‌እንዲድን‌ ‌ስእለት‌ ‌ይሳላሉ።‌ ‌ዕድል‌ ‌ሆኖ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይተርፋል፤‌ ‌አድጎ‌ ‌ጎበዝ‌ ‌ልጅ‌ ‌ይሆናል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌በሽታ፣‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ዕውቀትና‌ ‌ፍቅር‌ ‌(የሰው‌ ‌መውደድ)‌ ‌ይበዛበታል።‌ ‌በወጣትነቱ‌ ‌ይቀድስና‌ ‌ለቤተሰቡ‌ ‌ገንዘብ‌ ‌ማምጣት‌ ‌ይጀምራል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌የስእለት‌ ‌ልጅ‌ ‌መባልን‌ ‌አይጠላም‌ ‌ነበር።‌ ‌ሲያድግ‌ ‌ግን‌ ‌ትርጉሙን‌ ‌በመረዳቱ‌ ‌ነጻነቱን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌ዲማን‌ ‌ጥሎ‌ ‌ወደደብረ‌ ‌ወርቅ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌እዚያም‌ ‌ከእመት‌ ‌ጠጂቱ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይጠጋል።‌ ‌ትንሽ‌ ‌ዜማና‌ ‌ቅኔም‌ ‌ይማራል።‌ ‌ደብተራ‌ ‌በየነ‌ ‌መጥቶ‌ ‌የወላጆቹን‌ ‌ሞት‌ ‌ሲያረዳው‌ ‌ወደዲማ‌ ‌ይወርዳል።‌ ‌በተክለ‌ ‌አልፍአው‌ ‌በዓል‌ ‌በመልካም‌ ‌ድምጹ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻንና‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትን‌ ‌ያወድሳል።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻም‌ ‌የሰብለ‌ ‌መምህር‌ ‌አድርገው‌ ‌ይቀጥሩታል።‌ ‌ሰብለና‌ ‌በዛብህ‌ ‌የሕይወት‌ ‌ገጠመኞቻቸው‌ ‌በመጠኑ‌ ‌ስለሚመሳሰል‌ ‌ይግባባሉ።‌ ‌በመሃል‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌አሰጋኸኝ‌ ‌ሰብለን‌ ‌በፈት‌ ‌ወግ‌ ‌አገባለሁ‌ ‌በማለቱ‌ ‌በርሱና‌ ‌በፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌መካከል‌ ‌ጥል‌ ‌ተፈጠረ፤‌ ‌ሆኖም‌ ‌በሃይማኖት‌ ‌ጣልቃገብነት‌ ‌ሳይዋጉ‌ ‌ቀሩ።‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከባላገሮች‌ ‌ጋራ‌ ‌በግብር‌ ‌ጉዳይ‌ ‌ተጣሉ።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ተማርከው‌ ‌ሳለ‌ ‌የበዛብህንና‌ ‌የሰብለወንጌልን‌ ‌የፍቅር‌ ‌ዜና‌ ‌ይሰማሉ።‌ ‌ወዲያውም‌ ‌መጥተው‌ ‌ሰብለን‌ ‌በሌሊት‌ ‌ያስሯታል።‌ ‌የሰብለ‌‌አጎት‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ሁለቱን‌ ‌ለማስመለጥ‌ ‌ወጣ፣‌ ‌ወረደ።‌ ‌የዕጣ‌ ‌ነገር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ግን‌ ‌ሳይሳካ‌ ‌ቀረ።‌ ‌በዛብህ‌ ‌ግን‌ ‌በግራጌታ‌ ‌ቀለመወርቅና‌ ‌በጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጥረት‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌በራጉኤል‌ ‌ቤተክርስቲያንም‌ ‌የቅኔ‌ ‌መምህር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ይቀጠራል።‌ ‌ባደረጉላቸው‌ ‌ውለታ‌ ‌ምክንያት‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌ሰብለን‌ ‌ለፊታውራሪ‌ ‌ታፈሰ‌ ‌ሊድሯት‌ ‌ይሞክራሉ።‌ ‌የሰብለን‌ ‌አቋም‌ ‌አውቀው‌ ‌አባ‌ ‌ተክለሃይማኖት‌ ‌በተባሉ‌ ‌መነኩሴ‌ ‌ያስጠብቋቷል።‌ ‌መነኩሴው‌ ‌ግን‌ ‌ሰክረው‌ ‌ሰብለ‌ ‌ታመልጣለች።‌ ‌ፍለጋ‌ ‌ሲሄዱ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከፈረስ‌ ‌ላይ‌ ‌ተወርውረው፣‌ ‌ተንኮታክተው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትም‌ ‌ቤተክርስቲያን‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከደረጃ‌ ‌ላይ‌ ‌ተንሸራትተው‌ ‌ወድቀው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ሰብለ‌ ‌ደግሞ‌ ‌በዛብህን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌መነኩሴ‌ ‌መስላ‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ትሄዳለች።‌ ‌ደርሳም‌ ‌በዛብህ‌ ‌አለመኖሩን‌ ‌ትሰማና‌ ‌ጎሃጽዮን‌ ‌ትወርዳለች።‌ ‌በዚያም‌ ‌በዛብህ‌ ‌ተደብድቦ፣‌ ‌ነፍስ‌ ‌ውጪ‌ ነፍስ‌ ‌ግቢ‌ ‌አይነት‌ ‌ሁኔታ‌ ‌ላይ‌ ‌ሳለ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌እንደምንም‌ ‌ብለው‌ ‌ሥጋ‌ ‌ወደሙን‌ ‌ይቀበላሉ።‌ ‌ጥቂት‌ ‌ቆይቶ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይሞታል።‌ ‌ሰብለም‌ ‌መንኩሳ፣‌ ‌የበዛብህን‌ ‌አስከሬን‌ ‌ባጠገቧ‌ ‌አድርጋ‌ ‌ስትኖር‌ ‌ከጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጋራ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌ጉዱ‌ ‌የተሰኘው‌ ‌ካሳ‌ ‌ዳምጤም‌ ‌እርሷ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይቀመጣል።‌ ‌አስራ‌ ‌አምስት‌ ‌ቀናት‌ ‌አንድ‌ ‌ላይ‌ ‌ይኖሩና‌ ‌ሰብለ‌ ‌የልብ‌ ‌በሽታዋ‌ ‌ተነሥቶባት‌ ‌ትሞታለች፣‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ከበዛብህ‌ ‌አጠገብ‌ ‌ያስተኛታል።‌ ‌በሦስተኛው‌ ‌አመት‌ ‌ጉዱም‌ ‌አረፍተ‌ ‌ዘመን‌ ‌ይገታዋል።‌ \n \nጥያቄ: የሰብለ እናት ማን ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትም‌ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nብርቱካን በዓለሙ ውስጥ ሙቅ አየር በሚገኝበት በሰፊ ይበቅላል፤ የብርቱካንም ጣዕም ከጣፋጭ እስከ ኮምጣጣ ድረስ ይለያል። ፍሬው በተለመደ ይላጣል ጥሬም ሆኖ ይበላል፤ አለዚያ ለጭማቂው ይጨመቃል። ወፍራምና መራራ ልጣጩ በተለመደ ወደ ቆሻሻ ይጣላል፤ ነገር ግን በክብደትና በሙቀት አማካኝነት ውሃውን በማስወግድ፣ ለመኖ ሊጠቅም ይችላል። ባንዳንድ የምግብ አሠራር ዘዴ ደግሞ፣ እንደ ጣዕም ወይም እንደ መከሸን ይጨመራል። የልጣጩ አፍአዊው ቆዳ በልዩ መሣርያ በቀጭን ይፋቃልና ይሄ ጣዕሙ ለወጥ የሚወደድ ቅመም ያስገኛል። ከልጣጩ በታች ያለው ነጭና ሥሥ ሽፋን ስለማይረባ ይጣላል። ደግሞ የብርቱካን ዘይት አስታጋሽ መዓዛ ስላለው በሕክምና ይጠቅማል። \n \nጥያቄ: ብርቱካን በምን የአየር ጸባይ ይበቅላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሙቅ አየር በሚገኝበት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nክቡር ዶ/ር ጥላሁን ገሠሠ ከተጫወታቸው ሙዚቃዎች ውስጥ “ስቆ መኖር”፣ “እውነት ማሪኝ”፣ የሚሉትን ግጥሞች፣ “ዋይ ዋይ ሲሉ”፣ “ውሸት ለመናገር”፣ “ልብሽን ለአፈርሰው”፣ “ኮቱሜ”፣ የሚሉትን ዘፈኖች ግጥምና ዜማዎች የደረሰው ሌ /ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ እንደሆነ ይታወቃል። ከዚህም ሌላ ለድምፃዊት ብዙነሽ በቀለ “አይወጣኝም ክፉ ነገር” በሚል የዘፈነችውና በብዙኀን ዘንድ ተወዳጅነት ያለውን (“ወደመጣሁበት ምድር፣ እስክመለስባት በክብር፣ ሰውን ከማስደሰት በቀር፣ አይወጣኝም ክፉ ነገር፣ ...” ) ሙዚቃውን ያቀናበረው ሌ /ኮሎኔል ሣህሌ ነው። ሌ /ኮሎኔል ሣህሌ “ፍላጎቴ”፣ “ምን ነበር”፣ “ምንድነው ትዝታህ”፣ ... የተሰኙትን የብዙነሽ በቀለን ዘፈኖች ያቀናበረ ሲሆን፣ “ከንቱ ሥጋ” የሚለውንና ሌሎችንም ዘፈኖችዋን ግጥም ደርሶላታል። “አታሳየኝ ጭንቁን”፣ “የፍቅር ወጋገን”፣ “ቃልኪዳን”፣ “በብር አይጋዛም”፣ “ፍቅርህ ቀሰቀሰኝ”፣ … የተሰኙትን ዜማና ግጥሞች ያዘጋጀው ሣህሌ ደጋጎ እንደነበረ ይታወቃል። “ሰው ከተሰማራ” በተሰኘው ዘፈኗ ለምትታወቀው ለድምፃዊት መንበረ በየነ ደግሞ “እንዴት ከረማችሁ” የሚለውን ዘፈን ግጥም የደረሰው ሌ /ኮ /ል ሣህሌ ነበር። “የቆራጡ መሪ ፍሬው ጎመራ” የተሰኘውንና ለቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት መንግሥቱ ኃይለማርያም ላቀነቀነችው ለድምፃዊት ውብሻው ስለሺ ደግሞ “ይህ ነው ጌትነት”፣ “የምድር ፈተና” የተሰኙትንና በ 1966 ዓ /ም የታተሙትን ዘፈኖችዋን ያቀናበረላት ሌ /ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ነበር። በዕድሜ ዘመን የኪነ ጥበብ አገልግሎት የክብር ሜዳሊያ እና የ 20 ሺህ ብር ተሸላሚ የሆነው ሣህሌ ደጋጎ፤ የ 30፣ የ 20 እና የ 10 ዓመት የረዥም ዘመን አገልግሎት የወርቅ፣ የብርና የነኀስ እንደዚሁም የተዋጊ ወታደርነት የደረት ዓርማ ኒሻን ተሸለሚም ነበር። ሙዚቃ ቀማሪው ሣህሌ ደጋጎ ከባለቤታቸው ከወ /ሮ ወይንሸት ተክሉ 4 ሴት እና 3 ወንድ ልጆችን አፍርቶ የ 10 ልጆች አያት ለመሆን በቅቷል። በቀብር ሥነ ሥርዓቱም ላይ ከቤተሰቡ ውጪ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ወዳጅ ዘመዶቹ፣ የቀድሞ የሥራ ባልደረቦቹ እና አድናቂዎቹ፣ የመኖሪያ አካባቢያው ሰዎች ተገኝተው በዕንባ ሸኝተውታል። የአበባ ጉንጉንም አኑረዋል። ኢህአዲግ ግንቦት 20 ቀን 1983 ዓ .ም . ኢትዮጵያን ከተቆጣጠረ በኋላ ሌ /ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ለሰባት ወራት በጦላይ የጦር ማሠልጠኛ ማዕከል ታስሮ እንደነበር ይታወቃል። \n \nጥያቄ: ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ስንት ልጅ እና የልጅ ልጅ አሉዋቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 4 ሴት እና 3 ወንድ ልጆችን አፍርቶ የ 10 ልጆች አያ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአንበሳ አንበሳ ጡት አጥቢ የእንስሶች መደብ ውስጥ ሲሆን ግዙፍ ድመቶች ከሚባሉት 4 አራዊት አንዱ ነው። ከነዚህም መካከል ነብር ከሚባለው ግሥላ መሳይ አውሬ ቀጥሎ በቁመቱና ክብደቱ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። አንበሳ ዛሬ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በህንድ ብቻ የሚገኝ ሲሆን በታሪክ እስያና በደቡብ አውሮፓ እንደነበርና እንደጠፋ ይታወቃል። አንበሶች በጣም ቁጡ ሊሆኑ ይችላሉ፤ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የሙጭሊትን ያህል ገራምና ተጫዋች ይሆናሉ። ሲጠግቡ በዝግታ የሚያንኮራፉ ቢሆንም እንኳ እስከ ስምንት ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሰማ በሚችል ኃይለኛ ድምፅ ሊያገሡ ይችላሉ። አንዳንድ ጊዜ ሰነፎችና ልፍስፍሶች ይመስሉ ይሆናል፤ ሆኖም በሚያስገርም ፍጥነት የመንቀሳቀስ ችሎታ አላቸው። የሰው ልጅ፣ አንበሳ ባለው ድፍረት ለዘላለም ሲወሳ እንዲኖር አድርጓል፤ በመሆኑም ደፋር ሰው አንበሳ ተብሎ ይጠራል። አንበሶች በማኅበር ከሚኖሩት የድመት ወገን የሆኑ እንስሶች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። በትልልቅ መንጋ ተከፋፍለው የሚኖሩ ሲሆን እያንዳንዱ መንጋ ከጥቂት አባሎች አንስቶ ከ30 በላይ ሊደርስ ይችላል። አንድ መንጋ የጠበቀ ዝምድና ያላቸው በርከት ያሉ ሴት አንበሶች ይኖሩታል። አንድ ላይ ይኖራሉ፣ ያድናሉ እንዲሁም ይወልዳሉ። ዕድሜ ልካቸውን ሊዘልቅ የሚችለው ይህ የጠበቀ ትስስር ለመንጋው ጠንካራ መሠረት የሚጥል ከመሆኑም በላይ ለመንጋው ሕልውና ጥሩ ዋስትና ይሆናል። እያንዳንዱ መንጋ እየተዘዋወሩ የሚጠብቁና የመንጋውን የክልል ወሰን የሚያወጡ አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ለአካለ መጠን የደረሱ ወንድ አንበሶች ይኖሩታል። እነዚህ ዕጹብ ድንቅ የሆኑ አውሬዎች ከጥቁሩ የአፍንጫቸው ጫፍ አንስቶ እስከ ጭራቸው ጫፍ ድረስ ከሦስት ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ሲሆን ከ225 ኪሎ ግራም በላይ ሊመዝኑ ይችላሉ። ቤተሰቡን በበላይነት የሚቆጣጠሩት ወንዶቹ ቢሆኑም አመራር የሚሰጡት ግን ሴቶቹ ናቸው። ወደ ጥላ ሥፍራ መሄድን ወይም አደን መጀመርን በመሳሰሉት ሁኔታዎች ብዙውን ጊዜ መንጋውን ለአንድ ዓይነት እንቅስቃሴ የሚያነሳሱት ሴቶቹ አንበሶች ናቸው። ሴት አንበሶች በአብዛኛው በየሁለት ዓመቱ ይወልዳሉ። ግልገሎቹ በሚወለዱበት ጊዜ ምንም ዓይነት አቅም አይኖራቸውም። ግልገሎችን ማሳደግ የሁሉም የጋራ ሥራ ነው፤ በመሆኑም ሴቶቹ አንበሶች በሙሉ በመንጋው ውስጥ ያሉትን ግልገሎች ይጠብቃሉ እንዲሁም ያጠባሉ። የግልገሎቹ ዕድገት ፈጣን ሲሆን በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ መሮጥና መቦረቅ ይጀምራሉ። ልክ እንደ ሙጭሊቶች እየተንደባለሉ ይጫወታሉ፤ ከሚያጫውቷቸው ጋር ይታገላሉ፤ እንዲሁም በረጃጅሙ ሣር ውስጥ ወዲያና ወዲህ ይዘላሉ። እያንዳንዱ የሚንቀሳቀስ ነገር ሁሉ ስሜታቸውን ይማርከዋል፤ ቢራቢሮዎችን ለመያዝ ይዘላሉ፣ ትናንሽ ነፍሳትን ያሳድዳሉ፣ ከየጭራሮና ከየሐረጉ ጋር ይታገላሉ። ይበልጥ ስሜታቸውን የሚማርከው ግን እነርሱን ለማጫወት እናታቸው ወዲያና ወዲህ የምታወናጭፈው ጭራዋ ነው። እያንዳንዱ መንጋ የሚኖርበት በደንብ የተከለለ ቦታ ያለው ሲሆን ይህ መኖሪያ ብዙ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ሊኖረው ይችላል። አንበሶች ውኃ እንደ ልብ ባለበትና ከቀትር ሐሩር የሚከላከል ጥላ በሚያገኙበት ከፍ ያለ ቦታ ላይ መኖር ይመርጣሉ። በእንዲህ ዓይነቱ ሥፍራ ከዝሆኖች፣ ከቀጭኔዎች፣ ከጎሽና ከሌሎች ሜዳማ በሆኑ ሥፍራዎች ከሚኖሩ እንስሶች ጋር በአንድነት ይኖራሉ። አንበሳ አብዛኛውን ጊዜውን በእንቅልፍ ጥቂቱን ጊዜ ደግሞ በአደንና በተዋስቦ ያሳልፋል። እንዲያውም አንበሶች በቀን ውስጥ ወደ 20 የሚጠጋውን ሰዓት የሚያሳልፉት በዕረፍት፣ በመተኛት ወይም በመቀመጥ ነው። ከባድ እንቅልፍ ተኝተው ሲታዩ ሰላማዊና ለማዳ ይመስላሉ። ይሁን እንጂ በዚህ መታለል የለብህም፤ አንበሳ እጅግ ቁጡ ከሆኑት አራዊት መካከል አንዱ ነው! \n \nጥያቄ: አንበሳ አብዛኛውን ጊዜውን የሚያሳልፈው ምን በማድረግ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በእንቅልፍ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nከ1881 እስከ 1905 ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ በአፍሪካ ይዞታቸውን እያሰፉ የነበሩትን የአውሮፖ ሀይሎችን ጥቃት በመከላከል ኢትዮጵያን በስርዓት አስተዳድረዋል፡፡ በዚያን ጊዜ ጣልያን ኤርትራን በከፊል ቅኝ ገዝታ የነበረችበትና በ1880ዎቹ አጋማሽ ላይ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ቅኝ ገዝታት የነበረችበት ጊዜ ስለነበር ከሌሎች አውሮፖ አገራት በበለጠ ለኢትዮጵያ አስጊ ነበረች፡፡ በ1880 ግን እስከዛሬ ድረስ ዝነኛ በሆነው የአድዋ ጦርነት ኢትዮጵያ ጣልያንን ድል በማድረግ በአፍሪካ የባእዳን ገዥ ሀይሎችን ያሸነፈች ብቸኛዋ ሀገር ሆናለች፡፡ ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ የቅኝ ገዥዎችን ወረራና መስፋፋት በመመከትና ድልን በመቀዳጀት ለኢትዮጵያዉያን ብቻ ሳይሆን በባርነት ቀንበር ተጠምደዉ ለሚማቅቁ የመላዉ ዓለም ህዝቦች ከፍተኛ ክብርና ተስፋን አጎናጥፈዋል በ1908 የዳግማዊ ሚኒሊክ ልጅ የሆኑትን እቴጌ ዘውዲቱ ስልጣን ያዙ ፡፡ የሳቸው የቅርብ የስጋ ዘመድ የነበሩት ራስ ተፈሪ መኮንንም ሞግዚት አስተዳደርና ወራሽ ሆነው ተሹመዋል፡፡ እቴጌ ዘውዲቱ በ1922 ሲሞቱ ተተኪያቸው ዐጼ ሀይለስላሴ ስልጣን ያዙ ፡፡ ነገር ግን በ1928 ዓ.ም የጣልያን ሀይሎች ኢትዮጵያን ለአጭር ጊዜ ወረው ሲቆጣጠሩ ግዛታቸው ተቋርጦ ነበር፡፡ \n \nጥያቄ: በ1980 ኢትዮጵያ ጣልያንን ያሸነፈችበት ጦርነት ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የአድዋ ጦርነት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nካሣ አያሌው ካሣ ተወልዶ ያደገው አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ ሽሮ ሜዳ ተብሎ የሚጠራው ሰፈር ነው። አባቱ አቶ አያሌው ካሣ እና እናቱ ወ/ሮ በላይነሽ ተ/ወልድ በጋብቻ ከተጣመሩ አንስቶ ቤታቸው የልጅ ፍሬ ማግኘት ሳይችል ረጅም ዓመታትን ቆይቷል። በዚህ ምክንያት እናቱ መካን እንደሆኑ ታምኖ የአብራካቸውን ክፋይ እንደማያገኙ እርግጠኛ ሆነዋል። ነገር ግን የወላጆቹ እርግጠኛ የሆኑበት ጉዳይ ከአምላክ ዘንድ ከተፈቀደው የሚገናኝ ሆኖ እስከ መጨረሻው አልዘለቀም። ልክ እንደ ካህኑ ዘካርያስና ኤልሳቤት የልጅ ፍሬን ማየት ተስፋ በመነመነበት ትዳር ውስጥ ያልተጠበቀውና ያልታሰበው ተስፋ ባልተጠበቀና ባልታሰበ ቸጊዜ ከተፍ አለ። «መካን» ተብለው የተቆጠሩትና እርሳቸውም ይህንኑ አምነው የተቀበሉት ወ/ሮ በላይነሽ ተ/ወልድ በሆዳቸው ፅንስ ቋጠሩ። እርግዝናቸው እውን ሆኖ የቤቱን ተስፋ አንሰራራው። በዘጠነኛ ወራቸው የካቲት 8/ 1974ዓ.ም ለእኝህ እናቱ የመጀመሪያም የመጨረሻም የሆነው ልጃቸው ካሣ አያሌውን ተገላገሉ። \n \nጥያቄ: ካሣ አያሌው የትና መቼ ተወለደ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ ሽሮ ሜዳ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቲቪ በ1950ዎቹ እንደ ብርቅ በሚታይበት ዘመን በ1957 አ.ም ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተከፈተ፡፡ ታዲያ የመጀመሪያዋ የቲቪ ሴት አንባቢ የነበሩት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ ነበሩ፡፡ ይህ ለወይዘሮ እሌኒ ትልቅ የታሪክ አጋጣሚ ነበር፡፡ በወቅቱ ሳሙኤል ፈረንጅ አንዱ ወንድ ተናጋሪ ነበር፡፡ በኢትዮጵያ ሬድዮ በጋዜጠኝነቱና በህዝብ ግንኙነት ሙያ ያገለገሉት ወይዘሮ እሌኒ ከሰው ጋር በቀላሉ የሚግባቡ ተወዳጅ ደግ እናት ነበሩ፡፡ በበጎ አድራጎት ምግባራቸው በስፋት የሚታወቁት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ የወጣት ሴቶች ክርስቲያናዊ ማህበር ውስጥ በንቃት በመሳተፍ ማህበሩን ረድተዋል፡፡ በተጨማሪም በአንሚ ሬድዮ ከ20 አመት በፊት ያገለገሉት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ ከአለም አቀፍ መገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች ጋር የጠበቀ ቁርኝት ነበራቸው፡፡ ከዚህም ባሻገር አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሀን ወደ ሀገራችን በሚመጡበት ጊዜ ሁኔታዎችን በማመቻቸት ስራ ላይ ትልቅ ሚና አበርክተዋል፡፡ ቤታቸው ሲኬድ ሁልጊዜም ከአረንጓዴ ተክል ጋር የማይታጡት ወይዘሮ እሌኒ ነፋሻማ ቦታ ልዩ ትርጉም ይሰጣቸዋል፡፡ አንድ ከዛፍ ጋር በተያያዘ በፎቶግራፍ የታገዘ መጽሀፍም ለህትመት አብቅተዋል፡፡ በዚህም መጽሀፍ አማካይነት ስለ ሀገራችን ዛፎች በቂ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ሙከራ አድርገዋል፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ የተለያዩ ሀገሮችን ቴምብሮችን ያሰባስባሉ፡፡ በተለይ ደግሞ ለታሪክ ልዩ ፍቅር ያላቸው ወይዘሮ እሌኒ የጡረታ ጊዜያቸውን በማንበብ እና በምርምር ያሳልፉ ነበር፡፡ ወይዘሮ እሌኒ በ1959 አመተ ምህረት ከኢንጂነር ሰይፉ ለማ ጋር ጋብቻን መስርተው 3 ሴት ልጆችን ወልደው አንድ ልጅ ደግሞ አሳድገዋል፡፡ ወይዘሮ እሌኒ በተወለዱ በ79 አመታቸው ሮብ ሀምሌ 14 2013 ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን የቀብር ስነስርአታቸውም ሀሙስ ሀምሌ 15 2013 ከቀኑ በ6 ሰአት በየካ ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡ \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ውስጥ የመጀመሪያ ሴት የነበሩት ማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቦሌ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ በአዲስ አበባ ከተማ በደቡብ-ምሥራቅ አቅጣጫ ከአራዳ በስምንት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ የአገሪቱ ዋና አድማሳዊ የንግድና የግንኙነት በር ነው። አውሮፕላን ወደ ኢትዮጵያ መግባት የጀመሩት በንግሥት ዘውዲቱ ዘመን ሲሆን በአዲስ አበባ ዙሪያ በጃን ሜዳ እና አቃቂ ያርፉ እንደነበር በታሪክ ተዘግቧል። የመጀመሪያው ቋሚ የአውሮፕላን ጣቢያ ግን የተሠራው በአምሥቱ የፋሺስት ዘመናት ሲሆን የካቲት ፳፬ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ/ም አክሱም አካባቢ ላይ ከነጥያራው ተከስክሶ በሞተው አብራሪያቸው፣ “ኢቮ ኦሊቬቲ” ስም ሠይመውት የነበረው የልደታ የጥያራ ጣቢያ ነው። በዚሁ በፋሺስት ወረራ ዘመን ‘አላ ሊቶሪያ’ የተሰኘው ኩባንያ በአገር ውስጥ ከአዲስ አበባ ተነስቶ ነገሌን፤ ሞቃዲሾን፤ ድሬ ዳዋን፤ ጎራኄን፤ ጂቡቲን፤ አሰብን፤ ጂማን፣ ጋምቤላን ደምቢ ዶሎን፤ ጎንደርን አስመራን፤ ደሴን፤ ለቀምትን እና አሶሳን የሚያገለግሉ የበረራ መሥመሮች ሲኖረው ከአድማስ ባሻገር ደግሞ ከተማዋን በካርቱም፣ ዋዲ ሃይፋ፤ ካይሮ፣ ቤንጋዚ እና ሲራኩሳ አድርጎ ከሮማ ጋር የሚያገናኝ የበረራ መሥመርም ነበረው። ከድል ወዲህ ልደታ አውሮፕላን ጣቢያ፤ የብሪታኒያ ጦር ኃይሎች ሲገለገሉበት ከቆየ በኋላ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ታኅሣሥ ፳፩ ቀን ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ሲመሠረት ዋና ጣቢያው እዚያው ነበር። ዳሩ ግን የአየር መንገዱ አገልግሎት እየተስፋፋ ሲመጣና ትላልቅ ጄት አውሮፕላኖች እንደሚያስፈልጉት ግልጽ ሲሆን፣ የልደታ አየር ጣቢያ ብቃት እንደሌለው እና ለጄት አየር ዠበቦችም ማሳረፊያ የማይስማማ መሆኑ ታምኖበት የአማራጭ ሥፍራ ፍለጋ ተጀመረ። የአዲሱንም አየር ጣቢያ ዝርዝር ጥናት እንዲያዘጋጅ ውሉ ለአሜሪካዊው ‘አማን እና ዊትኒ’ ኩባንያ ተሰጥቶ፤ ጥናቱ በ፲፱፻፶ ዓ/ም ተገባዶ አማራጩ ሥፍራ ቦሌ እንዲሆን ተወሰነ። የአየር ጣቢያውን የግንባታ ወጪ ከአሜሪካዊው ‘ኤክስፖርት-ኢምፖርት’ ባንክ በተገኘ ብድር ተሸፍኖ ሥራው ተጀመረ። ጠቅላላ ግንባታው ተጠናቆ ሲያልቅ ኅዳር ፲፩ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ/ም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተብሎ፣ በንጉሠ ነገሥቱ ተመርቆ ተከፈተ። \n \nጥያቄ: ከጣልያን ድል ወዲህ ልደታ አውሮፕላን ጣቢያን እነማን ይገለገሉበት ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የብሪታኒያ ጦር ኃይሎች ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nፍራንክሊን ሮዘቨልት ፍራንክሊን ዴላኖ ሮዘቨልት (1874-1937 ዓ.ም.) የኒው ዮርክ አገረ ገዥና የአሜሪካ 32ኛ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ሮዘቨልት በቀድሞ ፕሬዚዳንት ዉድሮው ዊልሶን ዘመን የባሕር ኅይል ምክትል ሚኒስትር ነበሩ። በ1913 ምርጫ የምክትል ፕሬዚዳንት ዕጩ ሆኑ። ጄምስ ኮክስም የፕሬዚዳንት ዕጩ ነበሩ። ነገር ግን ኮክስና ሮዘቨልት በዋረን ሃርዲንግና በካልቪን ኩሊጅ ተሸነፉ። ሮዘቨልት በ1920 ዓ.ም. የኒው ዮርክ አገረ ገዥ ሆኑ። በታላቁ ጭፍግግ ሳቢያ ፕሬዚዳንት ሄርበርት ሁቨር በጣም ስላልተወደደ በ1925 ምርጫ ሮዘቨልት ሁቨርን አሸነፏቸው። ሮዘቨልት በጣም ስለተወደደ በ1929 ዓ.ም. ምርጫ ለሁለተኛ የ4 አመት ዘመን ተመለሱ። እንዲሁም በ1933 ምርጫ ለሦስተኛ ዘመንና በ1937 ምርጫ ለአራተኛ ዘመን ተመረጡ። በጠቅላላ 4 ዘመኖች ተቀበሉ። በ2ኛ አለማዊ ጦርነትም የአሜሪካ መሪ ነበሩ። ነገር ግን ፖሊዮ ከሚባል በሽታ የተነሣ አካለ ስንኩል ሆነው ባለ መንኮራኩር ወምበር ነበራቸውና በአራተኛው ዘመን መሃል ሞቱ። ምክትላቸው ሃሪ ትሩማን ወዲያው ፕሬዚዳንት ሆኑ። ፍራንክሊን ሮዘቨልት አራት ጊዜ በመመረጣቸው ከሁሉ ይልቅ ለረጅም ዘመን ገዙ። ከሳቸው በኋላ የመንግሥት አንደኛ ዘርፍ የሆነ የሕግ አማካሪ ቤት ወደፊት ሌላ ፕሬዚዳንት እንደሱ 3 ወይም 4 ዘመናት እንዳይቀብል አንፈልግም የሚል ድምጽ አሰሙ። ስለዚህ በ1943 ዓ.ም. የአሜሪካ መንግሥት 2ኛ ዘርፍ የሆኑት ፕሬዚዳንቶች ከ2 ጊዜ (እነሱም 8 አመታት) በላይ ሊያገለግሉ አይችሉም የሚለው የአሜሪካ ሕገ መንግሥት 22ኛ ማሻሻያ አንቀጽ ሕጋዊ ደንብ ሆነ። \n \nጥያቄ: ፍራንክሊን ዴላኖ ሮዘቨልት ለአካለ ስንኩልነት የዳረጋቸው በሽታ ምን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ፖሊዮ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nፈረንሳይ የዜጎቿን የማህበራዊ ሚዲያ ገፅ በመፈተሽ ግብር ሰዋሪዎችን ልትለይ እንደሆነ ተገለፀ፡፡ ይህም ባለፈው ሳምንት ከግብር ክፍያ ጋር በተያያዘ የወጣው ሕግ አካል ሲሆን የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች በገፃቸው ላይ የሚለጥፉትን የግል መረጃ ዝርዝር በማየት ነው ግብር የከፈለ እና ያልከፈለ የሚለየው፡፡ እርምጃው የዜጎች ራስን በነፃነት የመግለጽ እና የግላዊነት መብት ላይ ጫና ሊያሳድር ቢችልም ድንጋጌው የሚተገበርበት ቅድመ ሁኔታዎች አሉ ተብሏል። ከቅድመ ሁኔታዎቹ አንዱ በሚስጥራዊ ይለፍ ቃል የተቆለፉ ገጾችን ሰብሮ አለመግባት ነው፡፡ ከዚህ ባለፈ ግን ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ለሕዝብ ይፋ የተደረጉ መረጃዎችን መጠቀም እንደሚችል ነው የተነገረው። የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የፈረንሳይ የመረጃ ደህንነት ክፍል ሕጉ እንደሚያሰጋቸው ተናግረዋል። የበጀት ሚንስትሩ ጄራልድ ዳርማኒን በበኩላቸው አጭበርባሪዎችን የምንገታበት አንድ መንገድ ነው ብለዋል፡፡ ምንጭ፡-ቢቢሲ በፌቨን ቢሻው \n \nጥያቄ: ፈረንሳይ የዜጎቿን የማህበራዊ ሚዲያ ገፅ በመፈተሽ ግብር ሰዋሪዎችን መለየቷ የዜጎችን የትኛውን መብት ይጋፋል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ራስን በነፃነት የመግለጽ እና የግላዊነት መብት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበኢትዮጵያ የተለያዩ የቤተሰብ ሕግጋት ያሉ ሲሆን፣ እነዚህ ሕግጋት በሰው ፊት ዋጋ ያለው ግንኙነት የሚፈጠርበትን ጥምረት በተለያየ መንገድ ይደነግጋሉ፡፡ በቤተሰብ ሕግ ዕውቅና የተሰጣቸው የተቃራኒ ፆታዎች ጥምረት ሦስት ናቸው፡፡ የመጀመሪያውና ዋናው ጋብቻ ሲሆን፣ አሥራ ስምንት ዓመት የሞላቸው ወንድና ሴት ጥንዶች ለዘለቄታው አብረው በትዳር ለመኖር በማሰብ የሚመሠርቱት ተቋም ነው፡፡ ይህ ተቋም በሕገ መንግሥቱ ዕውቅና የተሰጠው ሲሆን፣ ወጣቶች በሕጉ የተቀመጡትን የዕድሜ፣ የፈቃድና የዝምድና ሁኔታዎችን ካከበሩ ሊመሠርቱት የሚችሉት ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት ጥምረት በክብር በመዝገብ ሹም ፊት፣ በሃይማኖት ሥርዓት ወይም በባህል ሥርዓት መሠረት ሊፈጸም ይችላል፡፡ ሁለተኛው ሕጉ ዕውቅና የሚሰጠው ጥምረት፣ ጋብቻ ሳይፈጸም እንደ ባልና ሚስት አብሮ መኖር ነው፡፡ ጋብቻ ሳይፈጽሙ እንደ ባልና ሚስት አብሮ መኖር ማለት አንድ ወንድና አንዲት ሴት በሕግ በሚጸና አኳኋን ጋብቻ ሳይፈጽሙ በትዳር መልክ የኖሩ ሲሆን ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት ግንኙነት አለ የሚባለው ሰዎቹ እንደተጋቡ ዓይነት ሰዎች ዓይነት አኗኗር ማሳየታቸው እንደሆነ እንጂ በታወቀና በተደጋገመ ሁኔታ የሩካቤ ሥጋ ግንኙነት መፈጸማቸው ብቻ አለመሆኑ በሕጉ በግልጽ ተመልክቷል፡፡ ሦስተኛው ሕጉ ዕውቅና የሚሰጠው መተጫጨትን ነው፡፡ መተጫጨት በተወሰኑ የክልል የቤተሰብ ሕግጋት ዕውቅና የተሰጠው እጮኛውና እጮኛይቱ ለወደፊት በመካከላቸው ጋብቻ ለመፈጸም የሚያደርጉት ስምምነት ነው፡፡ መተጫጨት ወደፊት በሚጋቡት ሰዎች ነፃ ፈቃድና ስምምነት ላይ የተመሠረተ ሲሆን፣ ለአንድ ዓመት ብቻ የሚቆይ ጥምረት ነው፡፡ \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ቤተሰብ ሕግ መተጫጨት ለምን ያህል ጊዜ ነው የሚጸናው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ለአንድ ዓመት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጋና ጋና በአፍሪካ አትላንቲክ ጠረፍ ላይ የተገኘ አገር ሲሆን ከ24 ሚሊዮን ኗሪዎች በላይ አሉት። የጋና ስራ ቋንቋ እንግሊዝኛ ሲሆን፣ ሌሎች ኗሪ ቋንቋዎች በተለይም ትዊኛ (አካንኛ) በሰፊ ይነገራሉ። የ«ጋና» ስያሜ በታሪክ የድሮ «ጋና መንግሥት» ወይም «ዋጋዱጉ መንግሥት» ለማክበር በ1949 ዓም ተመረጠ። እንዲያውም ያው መንግሥት እስከ 1068 ዓም ድረስ ከጋና ወደ ስሜን-ምዕራብ በአሁኑ ማሊ ይገኝ ነበር እንጂ የዛሬውን ጋና መቸም አልገዛም። «ጋና» በትክክል የዋጋዱጉ መንግሥት አለቆች ማዕረግ ሆኖ ነበር። ዋጋዱጉ መንግሥት በ1068 ዓም ግድም ከወደቀ ቀጥሎ፣ የአካን ብሔሮች ከዚያው ፈልሰው በዛሬው ጋና ሠፈሩና መጀመርያ ግዛቶችን መሠረቱ። ከ1662 እስከ 1949 ዓም ድረስ የአሻንቲ መንግሥት ባካባቢው ቆየ፤ በ1894 ዓም ይህ የብሪታንያ አሻንቲ ጥብቅ ግዛት ሆነ። ከ1949 ዓም አስቀድሞ የዩናይትድ ኪንግደም ጥገኛ ግዛት ሲሆን በወርቅ ሀብቱ ምክንያት «የወርቅ ጠረፍ ጥገኛ ግዛት» (ጎልድ ኮስት ፕሮቴክቶሬት) በመባል ይታወቅ ነበር። ከ1984 ዓም ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ እና ፓርላሜንታዊ መንግሥት ኖሮታል። አብዛኞቹ ኗሪዎች (70%) በተለይ በደቡቡ ክርስቲያን ሲሆኑ፣ በተለይ በስሜኑ 16% የእስልምና ተከታዮች ናቸው። የተረፉትም የኗሪ አረመኔነትን እምነቶች ይከተላሉ። የጋና ዋና ምርቶች ካካዎ፣ ዘይት፣ አልማዝ ናቸው። በአለሙ ከሁሉ ትልቅ የሆነው ሠው ሰራሽ ሐይቅ፣ ቮልታ ሐይቅ፣ በጋና ይገኛል። እግር ኳስ ከሁሉ የተወደደው እስፖርት ነው። የጋና አበሳሰል በተለይ በኮቤ፣ ጐርጠብ፣ የስኳር ድንች፣ ባቄላ፣ በቆሎ፣ ኦቾሎኒ፣ ባሚያና ሩዝ ይሠራል። \n \nጥያቄ: በጋና ምን ያህል ሕዝብ ይኖራል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከ24 ሚሊዮን ኗሪዎች በላይ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በህፃናት ልብ ህክምን ዘርፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱት ዶክተር በላይ አበጋዝ እና 30ኛ አመቱን በማክበር ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ልብ ህክምና ማዕከል ያላቸውን አስተዋፅኦ በማድነቅ ሽልማት አበረከቱ። \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ ልብ ህክምና ማዕከል 30ኛ ዓመት ክብረ በዓል ላይ በዶ/ር ዓብይ ሽልማት የተሰጣቸው ዶክተር ማናቸው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ዶክተር በላይ አበጋዝ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሞሪታኒያ ሞሪታኒያ (አረብኛ፡ موريتانيا‎) በይፋ የሞሪታኒያ እስላማዊ ሪፐብሊክ፣ በሰሜን ምስራቅ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በምዕራብ ከአትላንቲክ ውቂያኖስ፣ በደቡብ-ምዕራብ ከሴኔጋል፣ በምሥራቅና ደቡብ-ምሥራቅ ከማሊ፣ በሰሜን-ምሥራቅ ከአልጄሪያ፣ እና በሰሜን-ምዕራብ ከምዕራባዊ ሣህራ ጋር ትዋሰናለች። የአገሩዋ ስም የመጣው ከጥንቱ የሞሪታኒያ መንግሥት ነው። ዋና እና ትልቁዋ ከተማዋ ኑዋክሾት ናት። በዛሬው ሞሪታንኒያ በመጀመሪያ የሠፈሩት የባፎር ሰዎች ነበሩ። እነዚህ ስዎች ከዘላን ሕይወት ወደ ግብርና ከተቀየሩት የመጀመሪያ የሰሃራ ሕዝቦች አንዱ ናቸው። ከ5ኛው እስከ 7ኛው ምዕተ ዓመት፣ ባፎሮች በበርበር ህዝቦች ፍልሰት ምክኒያት ተፈናቀሉ። ብዙዎቹ የሞሪታኒያ ሕዝብ በመቆያ ግብርና ቢኖሩም ይሄ ወደ ውጭ አገር ለመላክ አይደለም። በተለይ ወደ ውጭ የሚላከው ብረት፣ ፔትሮሊየም፣ እና ዓሣ ናቸው። ሞሪታኒያ በ12 ዊላያ በሚባሉ ክልሎችና በአንድ የአስተዳደር አካባቢ ተከፍላልች። እነዚህም ክልሎች በ44 ሙጋታ በሚባሉ ክፍሎች ተከፍለዋል። \n \nጥያቄ: ሞሪታንያ በአፍሪካ በየት አቅጣጫ ትገኛለች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በሰሜን ምስራቅ አፍሪካ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም ለአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነርነት በእጩነት ቀረቡ። በሚኒስትር ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ኢትዮጵያን በመወከል ለአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነርነት በእጩነት መቅረባቸው ነው የተነገረው። የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር በመሆን ያገለገሉት ፕሮፌሰር ሂሩት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቋንቋና የቋንቋ ጥናት ክፍል ለረጅም ዓመታት በመምህርነት አገልግለዋል። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም ለአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነርነት የታጩት ማንን ወክለው ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ኢትዮጵያን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nልዑል ራስ መኮንን የንጉሠ ነገሥቱ ዳግማዊ ምኒልክ ተወካይ ሆነው ሁለት ጊዜ የአውሮፓን አገሮች ጎብኝተዋል። በዚህ ጊዜ እሳቸው ኢጣሊያን ሲጎበኙ በነበረ ጊዜ የኢጣሊያ ጋዘጦች የውጫሌ ውልን በተመለከተ፤ «...በውጫሌ ውል ላይ ኢትዮጵያ የኢጣሊያን ጥገኝነት ተቀብላ ውል ከፈረመች በኋላ የጀርመን ንጉሠ ነገሥት ከኢትዮጵያ የሚላከውን ማንኛውንም ደብዳቤም ሆን ጉዳይ በኢጣሊያ መንግሥት በኩል መቀበል ሲገባቸው በቀጥታ ከምኒልክ የተጻፈውን ደብዳቤ ተቀብለዋል...» እያሉ የጻፉትን ራስ መኮንን ተቃውሞአቸውን ለኢጣሊያ መንግሥት ከነገሩ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የውሉን መበላሸት ለአጤ ምኒልክ አሳወቁ። ከኢጣሊያንም ጋር በተደረገውም ጦርነት ራስ መኮንን ፲፭ ሺህ እግረኛ ወታደሮች ይዘው ከምኒልክ እና ታላላቅ ጦር አዛዦች ጋር ዘምተዋል። በ፲፰፻፺፰ ዓ.ም መጀመሪያ ላይ በብርቱ ስለታመሙ ለኅክምና ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ጥር ፬ ቀን ከከተማቸው ከሐረር ተነሱ። ጥር ፱ቀን ቡርቃ ወንዝ አድረው የጥምቀትን በዓል አክብረው ከዋሉ በኋላ ሕመሙ ስለጸናባቸው ወደ ኋላ ተመልሰው ቁልቢ ገብተው በሐኪም ይታከሙ ጀመር። እዚሁም ሲታመሙ ከቆዩ በኋላ መጋቢት ፲፫ ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም ቁልቢ ላይ አርፈው ሐረር ላይ እሳቸው በተከሉት በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። ዐፄ ምኒልክም የአርባቸው ለቅሶ የሚለቀሰው አዲስ አበባ እንዲሆን ባዘዙት መሠረት፤ ሰኞ ሚያዝያ ፳፪ ቀን በአዲስ አበባና በዙሪያው ያሉት የየገዳማቱና የየአድባራቱ ካህናት የክርስቲያን የፍታት ጸሎት ተድርጎ በማግስቱም ማክሰኞ የጊዮርጊስ ዕለት ሚያዝያ ፳፫ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም በሰኢ ሜዳ ላይ ድንኳን ተተክሎ፤ መኳንንቱና ሠራዊቱ ተሰብስቦ የራስ መኮንን የማዕረግ ልብሳቸውና የራስ ወርቃቸው፤ ኒሻኖቻቸውና የጦር መሳሪያቸው ተይዞ ፈረስና በቅሏቸው በወርቅ እቃ ተጭነው በሠራዊቱ መካከል እየተመላለሱ ታላቅ ልቅሶ ተለቀሰላቸው። \n \nጥያቄ: ራስ መኮንን መቼና የት ሞቱ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ መጋቢት ፲፫ ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም ቁልቢ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጉጃራቲ ጉጃራቲ (ગુજરાતી) በህንዳዊ-አውሮፓዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ የሚገኝ ቋንቋ ነው። በዓለሙ ውስጥ በ46 ሚልዮን ሰዎች ይናገራል፤ ከነዚህም 45.5 ሚልዮን በህንደኬ፣ 250,000 በታንዛኒያ፣ 150,000 በዩጋንዳ፣ 100,000 በፓኪስታንና 50,000 በኬንያ አሉ። በሕዝብ ብዛት የዓለሙ 23ኛ ቋንቋ ነው። በምእራብ ህንደኬ ያለው የጉጃራት ክፍላገር ይፋዊ ቋንቋ ነው። የጉጃር ሕዝብ ወደ ህንደኬ የደረሱ በ5ኛው መቶ ዘመን ሲሆን በ6ኛው መቶ ዘመን ዛሬ ጉጃራት በሚባለው አገር ሰፈሩ። የራሳቸውን ቋንቋ ቶሎ ትተው እንደ አገሩ ሰዎች ሳንስክሪት ለመናገር ጀመሩ። በ12ኛው ክፍለ ዘመን ግን ሳንስክሪት ተለውጦ ብዙ አዲስ ቋንቋዎች ተወለዱ። ከነዚሁም አንድ ጉጃራቲ ነበር። አብዛኛው ተናጋሪዎቹ የህንድ ሃይማኖት ተከታዮች ቢሆኑም ለረጅም ዘመን የእስላም ገዢዎች ስለነበሩባቸው ብዙ ቃላት የተወሰዱ ከፋርስ ሆኗል። ከዚያ በላይ በንግድ ምክንያት ብዙ ቃሎች ከፖርቱጊዝ ወይም ከእንግሊዝኛ ተበደሩ። የሚጻፍበት በራሱ ጉጃራቲ ፊደል ነው፤ ይህም ከላይኛ መስመር በማጣቱ በስተቀር የህንዲ ደቫናጋሪ ፊደል ይመስላል። \n \nጥያቄ: ጉጃራቲ በምን ቋንቋ ወገን ይገኛል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በህንዳዊ-አውሮፓዊ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nፍራንክሊን ሮዘቨልት ፍራንክሊን ዴላኖ ሮዘቨልት (1874-1937 ዓ.ም.) የኒው ዮርክ አገረ ገዥና የአሜሪካ 32ኛ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ሮዘቨልት በቀድሞ ፕሬዚዳንት ዉድሮው ዊልሶን ዘመን የባሕር ኅይል ምክትል ሚኒስትር ነበሩ። በ1913 ምርጫ የምክትል ፕሬዚዳንት ዕጩ ሆኑ። ጄምስ ኮክስም የፕሬዚዳንት ዕጩ ነበሩ። ነገር ግን ኮክስና ሮዘቨልት በዋረን ሃርዲንግና በካልቪን ኩሊጅ ተሸነፉ። ሮዘቨልት በ1920 ዓ.ም. የኒው ዮርክ አገረ ገዥ ሆኑ። በታላቁ ጭፍግግ ሳቢያ ፕሬዚዳንት ሄርበርት ሁቨር በጣም ስላልተወደደ በ1925 ምርጫ ሮዘቨልት ሁቨርን አሸነፏቸው። ሮዘቨልት በጣም ስለተወደደ በ1929 ዓ.ም. ምርጫ ለሁለተኛ የ4 አመት ዘመን ተመለሱ። እንዲሁም በ1933 ምርጫ ለሦስተኛ ዘመንና በ1937 ምርጫ ለአራተኛ ዘመን ተመረጡ። በጠቅላላ 4 ዘመኖች ተቀበሉ። በ2ኛ አለማዊ ጦርነትም የአሜሪካ መሪ ነበሩ። ነገር ግን ፖሊዮ ከሚባል በሽታ የተነሣ አካለ ስንኩል ሆነው ባለ መንኮራኩር ወምበር ነበራቸውና በአራተኛው ዘመን መሃል ሞቱ። ምክትላቸው ሃሪ ትሩማን ወዲያው ፕሬዚዳንት ሆኑ። ፍራንክሊን ሮዘቨልት አራት ጊዜ በመመረጣቸው ከሁሉ ይልቅ ለረጅም ዘመን ገዙ። ከሳቸው በኋላ የመንግሥት አንደኛ ዘርፍ የሆነ የሕግ አማካሪ ቤት ወደፊት ሌላ ፕሬዚዳንት እንደሱ 3 ወይም 4 ዘመናት እንዳይቀብል አንፈልግም የሚል ድምጽ አሰሙ። ስለዚህ በ1943 ዓ.ም. የአሜሪካ መንግሥት 2ኛ ዘርፍ የሆኑት ፕሬዚዳንቶች ከ2 ጊዜ (እነሱም 8 አመታት) በላይ ሊያገለግሉ አይችሉም የሚለው የአሜሪካ ሕገ መንግሥት 22ኛ ማሻሻያ አንቀጽ ሕጋዊ ደንብ ሆነ። \n \nጥያቄ: ፍራንክሊን ዴላኖ ሮዘቨልት ሲሞቱ ቦታውን የተረከቧቸው ምክትላቸው ማን ይባላሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሃሪ ትሩማን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዓጼ ኃይለ ሥላሴ ዘውድ እንደጫኑ የአገሪቱን የመጀመሪያ ሕገ-መንግሥት እንዲዘጋጅ አዝዘው በዘውዱ አንደኛ ዓመት በዓል ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፬ ዓ.ም. በአዲሱ ምክር ቤት (ፓርላማ) ለሕዝብ ቀረበ። ከዚህም በላይ ብዙ የቴክኖዎሎጂ ስራዎችና መሻሻያዎች ወደ ኢትዮጵያ ከውጭ አገር አስገቡ። በ፲፱፻፳፰ ዓ.ም. የሙሶሊኒ ፋሺስት ሠራዊት ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ጃንሆይ ሕዝባቸውን ወራሪውን በሙሉ ለመቃወም እንዳስነሡና የከተት ዐዋጆቻቸው በታሪክ ገጾች ይዘገባሉ። በዐዋጅ መሠረት የዘመቻው ጊዜ እስቲያልቅ ድረስ ለሚታግሉ ነጋዶች ከቀረጥ አስተስርየት ሰጣቸው። እራሳቸው በቆራጥነት ከታገሉ በኋላ የጠላቱ ጦር ኅይል ግን በመጨረሻ ወደ እንግሊዝ አገር ለጊዜው አሰደዳቸው። ወደ ጄኔቭ ስዊስ ወደ ዓለም መንግሥታት ማኅበር ሄደው ስለ ጣልያኖች የዓለምን እርዳታ በመጠየቅ ተናገሩ። የዓለም መንግሥታት ግን ብዙ አላደረጉም። በ፲፱፻፴፪ ዓ.ም. ግን አውሮፓ ሁሉ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ተያዘ። የእንግሊዝ ሠራዊቶች ለኢትዮጵያ አርበኞች እርዳታ በመስጠት ጣልያኖች ተሸንፈው በ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. ኢትዮጵያን ተዉ። ዓፄ ኃይለ ሥላሴ አዲስ አበባን እንደገና የገቡበት ቀን ከወጡበት ቀን በልኩ ዕለት አምስት ዓመት በኋላ ነበረ። ከዚህ በኋላ በ1948 ዓ.ም. ተሻሽሎ የወጣ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት የሕዝቦችን መብቶችና ተከፋይነት በመንግሥት አስፋፍቶ ሁለቱ ምክር ቤቶች እንደመረጡ አደረገ። በ፲፱፻፶፭ ዓ.ም. ግርማዊነታቸው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በአዲስ አበባ እንዲመሠረት ብዙ ድጋፍ ሰጡ። በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. ወደ ካሪቢያን ጉብኝት አድርገው የጃማይካ ራስታዎች ተገኛኙ። በ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. በማርክሲስት አብዮት ደርግ ሥልጣን ያዙና እሳቸው በእሥር ቤት ታሰሩ። በሚከተለው ዓመት ከተፈጥሮ ጠንቅ እንደ አረፉ አሉ ፤ ሆኖም ለምን እንደ ሞቱ ስለሚለው ጥያቄ ትንሽ ክርክር አለ። ብዙ ራስታዎች ደግሞ አሁን እንደሚኖሩ ይላሉ። የዓፄ ኃይለ ሥላሴ የትውልድ ስም ልጅ ተፈሪ መኮንን ነው። ስመ-መንግሥታቸው ግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ነበር። ሞዓ አንበሣ ዘእምነገደ ይሁዳ ሥዩመ እግዚአብሔር ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ የሚለው የሰሎሞናዊ ሥረወ-መንግሥት ነገሥታት መጠሪያም በንጉሠ-ነገሥቱ አርማ እና ሌሎች ይፋዊ ጽሑፎች ላይ ከመደበኛው ማዕረግ ጋር ይጠቀስ ነበር። ጃንሆይ ፣ ታላቁ መሪ እና አባ ጠቅል በመባልም ይታወቁ ነበር። \n \nጥያቄ: የጣልያን ፋሺስት ጦር ኢትዮጵያን በ፲፱፻፳፰ ሲወር ንጉሠ ነገሥት የነበሩት ማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ዓጼ ኃይለ ሥላሴ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሊቢያ ኦይል ሊሚትድ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ኢንቨስትመንትና የነዳጅ ንግድ ሥራ ለማስፋፋት መወሰኑን አስታወቀ፡፡ ዱባይ ከሚገኘው የሊቢያ ኦይል ሆልዲንግ ዋና መሥሪያ ቤት ወደ አዲስ አበባ የመጣው ኮርፖሬት ማኔጅመንት፣ ከሁለት ሳምንት በፊት በአዲስ አበባ ሒልተን ሆቴል የአንድ ሳምንት ጉባዔ አካሂዷል፡፡ ከ18 የአፍሪካ አገሮች የሊቢያ ኦይል ሥራ አስኪያጆች በስብሰባው ላይ ተሳትፈዋል፡፡ የሊቢያ ኦይል ኢትዮጵያ የሽያጭና ማርኬቲንግ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘካሪያስ ወሊቃ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ማኔጅመንቱ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ዕድገት በመገምገም ኩባንያው ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ኢንቨስትመንትና የነዳጅ ንግድ እንቅስቃሴ ለማስፋፋት ውሳኔ አሳልፏል፡፡ የኩባንያው ባለአክሲዮኖች ካፀደቁት ኢትዮጵያ ውስጥ የ150 ሚሊዮን ብር ኢንቨስትመንት ለማካሄድ አቅዷል፡፡ \n \nጥያቄ: የሊቢያ ኦይል ዋና መስሪያ ቤት የት ይገኛል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ዱባይ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: ብሪታንያ የፈጠረችው የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን መቼ ተበተነ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ1956 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበ1240 አካባቢ በግብጽ አገር ቅብጡ አቡል ፋዳዒል እብን አል-አሣል ፍትሐ ነገሥት በአረብኛ ጻፉ። እብን አል-አሣል ሕጎቹን የወሰዱት በከፊል ከሃዋርያት ጽህፈቶችና ከሕገ ሙሴ፤ በከፊልም ከድሮ ቢዛንታይን ነገስታት ሕጎች ነበር። መጽሐፉ በግዕዝ ተተርጉሞ ወደ ኢትዮጵያ የገባበት ወቅት በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን በ1450 አከባቢ እንደነበር የሚል ታሪካዊ መዝገብ አለ። ቢሆንም መጀመርያ እንደ ሕገ ምንግሥት መጠቀሙን የተመዘገበው በዓፄ ሠርፀ ድንግል ዘመን (ከ1555 ጀምሮ) ነው። ፍትሐ ነገስት እስከ 1923 ዓ.ም. የብሄሩን ዋና ሕግ ሆኖ ቆየ። በ1904 ዓ.ም. ዐጼ 2 ምኒልክ የዘመናዊ ሕገ መንግሥት ፅንሰ ሀሳብ ተረድተው በጸሀፊው መምሬ ብስራት አንድ ሕገ መንግሥት የሚመስል ሰነድ ታተመ፤ ይህ ግን በውነት ሕገ መንግሥት አይባልም። «በምኒሊክ ስለተቋቋሙት ሚኒስቴሮች በምሳሌ የቀረበ ጽሑፍ» በምሳሌና በትርጓሜ የእያንዳንዱን ሚኒስቴር ሥራ እንደ ሰውነት አካላት አስመሰለ። ለምሳሌ፦ ኢትዮጵያ መጀመርያ ዘመናዊ ሕገ መንግሥት የተቀበለችው በ1923 አመተ ምኅረት በአጼ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የታወጀ ሲሆን የሕግ አማካሪ ቤቶች በሁለት ያስከፈለ ነው። ይህ የመንግሥታቸው ዋና መሠረት ሆኖ እስከ 1948 አ.ም. አገለገለ፤ በዚያ አመት ተሻሽሎ በወጣ ሕገ መንግሥት ሕዝቦች በመንግሥት ሥራ የሚጫወቱት ሚና እንደገና ተስፋፋ። ይህ ብቻ የአገሪቱ ሕገ መንግሥት ሆኖ እስከ 1967 አ.ም. ቆየ፤ የዛኔ በደርግ (በሕገ መንግስት እራሱ ባልሆነ ሂደት) ተሰረዘ። \n \nጥያቄ: በ1240 በግብጽ ሀገር በአረብኛ ፍትሐ ነገሥት ያዘጋጀው ማን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አቡል ፋዳዒል እብን አል-አሣል ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሥነ ቁጥር ሥነ ቁጥር ወይንም በእንግሊዝኛ \"አርቲሜቲክስ\" ከሁሉ የሒሳብ ዘርፎች አንጋፋውና በሁሉም ሰው ጥቅም ላይ የሚውል ክፍል ነው። ሥነ ቁጥር የቁጥሮችን ቅልቅል ውጤት የሚያጠና ሲሆን ብዙ ጊዜ ቁጥሮች ሲደመሩ፣ ሲቀነሱ፣ ሲባዙና ሲካፈሉ የሚያሳዩትን ባህርይ ይመረምራል። ሒሳብ ተማሪዎች የቁጥር ኅልዮት ውጤቶችን ከፍተኛ ሥነ ቁጥር በማለት ከለተ ተለት መደመርና መቀነስ ጥናቶች ይለዩዋቸዋል። የሰው ልጆች ከጥንት ጀምሮ ሥነ ቁጥርን ተጠቅመዋል። ለምሳሌ አፍሪቃ ውስጥ የተገኘ 22፣000 ዓመት እንዳለው የሚቆጠር የአጥንቶች ቁርጥራጭ ለመቁጠርና ለመደመር ያገለግል እንደነበር ይጠቀሳል። በኋላም የግብጽ እና ባቢሎን ሰወች ቁጥርን መጻፍ እንደጀመሩና ይህን ፈጠራቸውን ለመደመርና ለመቀነስ እንደተገለገሉበት አሁን የተገኙ ቅርሶች ያስገነዝባሉ። የግብጽን የአጻጻፍ ስልት የተከተሉ ግሪኮችም በዩክሊድ እና ሌሎች የግሪክ ተማሪዎች አማካይነት ጥናቱን ለማሳደግ ችለዋል። ሆኖም እስከዚህ ዘመን የነበረው የቁጥር አጻጻፍ ስልት አቀማመጣዊ አልነበረም። ስለሆነም ለመደመርና ለመቀነስ፣ በተለይ ደግሞ ለማባዛትና ለማካፈል እጅግ የተወሳሰበና አሰልቺ ነበር። የሒሳብና የሥነ ቁጥር እድገት ከፍተኛ እመርታ ያሳየው ሕንዳውያን ተማሪዎች ዜሮና አቀማመጣዊ አጻጻፍ ስልትን በ4ኛው ክፍለዘመን ሲፈለስፉ ነበር። ይህም አሁን በመላው አለም የሚሰራበት ህንዲ-አረብ ቁጥር (ማለቱ፡ 0 1 2 3 4 5 6 7 8 9 ) እንዲፈጠር አደረገ። ፊቦናቺ የተሰኘው የጣሊያን ነጋዴ የዚህን ድንቅ ቁጥር ቀመርና ጥቅም በመጽሐፉ በ1202 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ) በመጻፍና በአውሮጳ አገራት ሁሉ በማሰራጨት ታዋቂነቱ እንዲገን ሆነ። የህንዲ-አረብ ቁጥር ስርዓት በጣም ቀላል ከመሆኑ የተነሳ የሒሳብ ትምህርት በአውሮጳ እንዲያድግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አደረገ። ይሄው አዲሱ ስልት ለሒሳብ ጥናት መሰረት በመሆን የጥንቶቹን ሒሳብ ተማሪዎች ድንቅ ውጤቶች ከአዲሱ ስርዓት ጋር ሲነጻጻሩ እምብዛም ሆነው እንዲታዩ አደረጉ። የሂንዲ አረብ ቁጥር ስርዓት ለዘመናዊው የሒሳብ ትምህርት መነሳት ምክንያት ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። \n \nጥያቄ: የቁጥሮችን ቅልቅል ውጤት የሚያጠና ሲሆን ብዙ ጊዜ ቁጥሮች ሲደመሩ፣ ሲቀነሱ፣ ሲባዙና ሲካፈሉ የሚያሳዩትን ባህርይ የሚመረምር ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሥነ ቁጥር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየፀሓይ አካል ለፍጹም ሉል የቀረበ ቅርጽ አለው፤ ዋልታዎቿን የሚያገናኘው ዳያሜትር ከወገቧ ዳያሜትር የሚያንሰው በ10 ኪሎ ሜትር ብቻ ነውና። ኮከባችን ፀሓይ በሥነ ፈለክ ሊቃውንት እጅግ ብዙ ጥናት ተደርጎባታል። ኾኖም ኮከቢቱን በተመለከተ ብዙ ጥያቄዎች ገና አልተመለሱም። ለምሳሌ በገሃድ የሚታየው የፀሓይ ገጽ ስኂን 6,000 ኬ (ኬልቪን) ኾኖ ሳለ፣ የዳርቻ ከባቢ አየሯ ስኂን ከሚሊዮን ኬ በላይ እንዴት ሊኾን እንደቻለ አይታወቅም። የፀሓይ ዕድሜ በአንዳንድ ሊቃውንት እሳቤ 4.6 ቢሊዮን ዓመት ገደማ ነውና በዕድሜ እኩሌታዋ ላይ የምትገኝ ኮከብ ተደርጋ ትታያለች። የኮከቢቱ መጠነ-ቁስ ጥንቅር 74% ሃይድሮጂን፣ 25% ሂሊየም ሲኾን፣ ቀሪው 1% ደግሞ ክብደት ያላቸው ርዝራዥ የብረቴ ንጥረ-ነገሮች ጥርቅም ነው። ስለ ፀሓይ የሰው ልጅ ቀዳሚ መሠረታዊ ግንዛቤ ብርሃን-ሰጭ ሰማያዊ ጻሕል መኾኗን፣ ደግሞም ከአድማስ በላይ እና በታች በመኾን ለመዓልትና ሌሊት መኖር ምክንያት መኾኗን መረዳት ነበር። በብዙ የቅድመ-ታሪክ እና የጥንት ዘመን ባህሎች ፀሓይ እንደ ብርሃናዊ አምላክ ወይም እንደ ዲበ-ተፈጥሯዊ ክሥተት ትታይ ነበር። የፀሓይ አምልኮ ለምሳሌ የ-ኢንካ (ደቡብ አሜሪካ) እና አዝቴክ (የዛሬዋ ሜክሲኮ) ጥንታዊ ሥልጣኔዎች ዐይነተኛ ገጽታ ነበር። ከፀሓያዊ ክሥትቶች ጋር የተያያዙ ብዙ ጥንታዊ ሐውልቶች ተገንብተው እንደነበር ለማሰብ የሐጋይ ሶልስቲስን ለማስታወቅ የተገነቡትን የድንጋይ ሜጋሊት በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል። ከችንክር ከዋክብት አንጻር ስትታይ ፀሓይ የግርዶሽ መስመርን ተከትላ በዞዲያክ ውስጥ በዓመት አንድ ዑደት የምታደርግ ትመስላለች። ስለዚህ በጥንት የግሪክ የሥነ-ከዋክብት ሊቃውንት ዘንድ ፀሓይ ታዋቂ ከነበሩ ሰባት ፈለኮች እንደ አንዱ ትቈጠር ነበር። በአንዳንድ ቋንቋዎች ሰባቱ የሳምንት ዕለታት በነዚህ ፈለኮች ይጠራሉ። \n \nጥያቄ: የፀሀይ ዋልታዎቿን የሚያገናኘው ዲያሜትር እርዝመት ከወገቧ ዲያሜትር በምን ያህል መጠን ያንሳል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ10 ኪሎ ሜትር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nግንቦት ፳፮ ቀን፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፷፮ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት ፷፩ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፺፱ ቀናት ይቀራሉ። ፲፱፻፶፬ ዓ/ም - የኤር ፍራንስ ቦይንግ ፯፻፯ አየር ዠበብ ከፓሪስ ኦርሊ ማረፊያ ተነስቶ ወደ አትላንታ ለመብረር ሲነሳ በደረሰበት አደጋ ፻፴ መንገደኞችና የዓየር መንገዱ ባልደረቦች ሞተዋል። ፲፱፻፶፭ ዓ/ም - የአሜሪካው ‘ኖርዝ ዌስት ኤየርላይንስ’ ዲ-ሲ-፯ አየር ዠበብ በረራ በሰላማዊ ውቅያኖስ ላይ ውድቆ ሲሰምጥ ፻፩ ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኮንኮርድ አየር ዠበብ አምሳል የተሠራው የሶቪዬት ቱፖሌቭ ቲ-ዩ-፻፵፬ ፈረንሳይ ላይ በደረሰበት የበረራ አደጋ ሲከሰከስ ፲፬ ሰዎች ሞተዋል። ፲፱፻፺፰ ዓ/ም - የቀድሞዋ ዩጎዝላቪያ አካላት የነበሩት ሰርቢያ እና ሞንቴኔግሮ የውሕደት ስምምነታቸውን በሞንቴኔግሮ የሉዐላዊነት አዋጅ ምክንያት ሰረዙ። ፲፯፻፷፭ ዓ/ም - የዓፄ በካፋ ሚስት የነበሩት እቴጌ ምንትዋብ በዚህ ዕለት አርፈው በቁስቋም ደብረ ጸሐይ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። \n \nጥያቄ: ፲፱፻፶፬ ዓ/ም የተከሰከሰው አየር ዠበብ አውሮፕላን ስሙ ማን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የኤር ፍራንስ ቦይንግ ፯፻፯ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየ2010 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ የ2010 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ ፲፱ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የነበረ ሲሆን ከሰኔ ፬ እስከ ሐምሌ ፬ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. በደቡብ አፍሪካ ተካሄዷል። ውድድሩን ለማቅረብ የተካሄደው ዕጣ ውስጥ የአፍሪካ ሀገሮች ብቻ እንዲሳተፉ ነበር የተፈቀደው። ደቡብ አፍሪካ ግብፅና ሞሮኮን በማሸነፍ የመጀመሪያው የዓለም ዋንጫን ያቀረበች አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ፊፋ ለውድድሩ ያቀረበው ጠቅላላ የሽልማት ገንዘብ $420 ሚሊዮን ነው። ይህም ከ2006 እ.ኤ.አ. ውድድር ሽልማት ገንዘብ የስልሳ ከመቶ ዕድገት አለው። ከዚህ ውስጥ $40 ሚሊዮን የሚሆነው ተጫዋቾቹ ለሚጫወቱበት ክለቦች ተጫዋቾቹ ለሚደርስባቸው ጉዳት መካካሻ እንዲሆን ተሰጥቷል። ከውድድሩ በፊት እያንዳንዱ ቡድን ለዝግጅት ወጪው $1 ሚሊዮን ተረከበ። ግጥሚያዎቹ በዘጠኝ ከተማዎች ውስጥ በሚገኙ አስር ስታዲየሞች ውስጥ ነው የተካሄዱት። የዋንጫ ጨዋታው በጆሃንስበርግ ከተማ በሚገኘው ሶከር ሲቲ ስታዲየም ነው የተከናወነው። የምድብ ድልድል ሥነ ስርዓቱ በኬፕ ታውን፣ ደቡብ አፍሪካ በሚገኘው ኬፕ ታውን ዓለም አቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል በኅዳር ፳፭ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. ተከናወነ። ሥነ ስርዓቱ የቀረበው በደቡብ አፍሪካዊቷ ተዋናይ ሻርሊዝ ቴሮን እና የፊፋ ዋና ጸሐፊ ዠሮም ቫልክ ነው። የዕጣ ኳሶቹን ያወጡት ዴቪድ ቤክሃም፣ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ፣ ጆን ስሚት፣ መካያ ንቲኒ፣ ማቲው ቡዝ እና ሲምፊዌ ድሉድሉ ናቸው። የፊፋ ዳኛዎች ኮሚቴ ፳፱ ዳኛዎችን ለዓለም ዋንጫ መርጧል። እነዚህም ከኤ.ኤፍ.ሲ. አራት፣ ከካፍ አስር፣ ከኮንሜቦል ስድስት፣ ከኮንካካፍ አራት፣ ከኦ.ኤፍ.ሲ. ሁለት እና ከዩኤፋ አስር ዳኛዎችን ያጠቃልላል። እንግሊዛዊው ዳኛ ሀዋርድ ዌብ የዋንጫ ጨዋታውን እንዲዳኝ ተመርጧል። \n \nጥያቄ: በደቡብ አፍሪካ በየተካሄደው የአለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ የዳኙት እንግሊዛዊ ዳኛ ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሀዋርድ ዌብ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nትዊተር ተጠቃሚወች የሚለጥፏቸውን መረጃወች ተከትሎ የሚሰጡ ምላሾችን መቆጣጠር የሚያስችል አሰራር ሊሞክር መሆኑን አስታወቀ። ኩባንያው ሙከራው ደንበኞች በነጻነት እንዲሳተፉ ለማድረግ ያለመ ስለመሆኑም ገልጿል። ከዚህ አንጻርም ተጠቃሚዎች የሚለጥፏቸውን መረጃዎች መሰረት አድርገው የሚሰጡ ምላሾችን መቆጣጠርና መገደብ የሚያስችለውን ሙከራ አደርጋለሁ ብሏል። የአሁኑ እርምጃ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ማህበራዊ ትስስር ገጾች በበይነ መረብ አማካኝነት የሚፈጸምን ዘለፋና ማንቋሸሽ መቆጣጠር አልቻሉም በሚል እየቀረበ ያለውን ወቀሳ ተከትሎ የሚወሰድ ነው ተብሏል። በቅርቡ ይሞከራል በተባለው አዲስ አሰራር ተጠቃሚዎች በአራት አማራጮች ለተለጠፉ መረጃዎች መልስ እንዲሰጡ የሚያስችል መሆኑንም ነው ኩባንያው የገለጸው። በዚህም ዓለም አቀፍ በሆኑ ገጾች ላይ ማንኛውም ሰው ምላሽ መስጠት የሚችል ሲሆን፥ ቡድን አልያም የማህበረሰብ ገጾች ላይ ለተለጠፉ መረጃዎች ደግሞ የዛ ቡድን ተከታይና በመረጃው ውስጥ የተጠቀሱ ሰዎች ብቻ ምላሽ እንዲሰጡ ያስገድዳል። በተጨማሪም መወያያ አጀንዳዎችና ጉዳዮች ላይ ደግሞ በዛ መወያያ ሃሳብ ላይ የተጠቀሱ አካላት ብቻ ምላሽ ይሰጣሉ። የተለጠፉ መግለጫዎች ላይ ደግሞ ማንኛውም አካል ምላሽ እንዳይሰጥ ይደረጋል ብሏል ትዊተር ባወጣው መግለጫ። ኩባንያው ከዚህ ቀደም ተጠቃሚዎች ገጻቸው ላይ ለለጠፉት መረጃ የሚሰጡ ምላሾችን መደበቅ እንዲችሉ የሚያግዝ አሰራር ተግባራዊ ማድረጉ ይታወሳል። ምንጭ፦ ቢቢሲ \n \nጥያቄ: ተጠቃሚወች የሚለጥፏቸን መረጃዎች ተከትሎ የሚሰጡ ምላሾችን መቆጣጠር የሚያስችል አሰራር ሊሞክር መሆኑን ያሳወቀው የማኅበራዊ ድኅረ ገጽ ስም ማን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ትዊተር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሴኔጋል ሴኔጋል ወይም የሴኔጋል ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። ሴኔጋል ከምዕራብ በሴኔጋል ወንዝ፣ ከሰሜን በሞሪታንያ፣ ክምሥራቅ በማሊ እና ክደቡብ በጊኒና ጊኒ-ቢሳው ይዋሰናል። የጋምቢያ ግዛት እንዳለ በሴኔጋል ውስጥ ነው የሚገኘው። የሴኔጋል የቆዳ ስፋት 197,000 ካሬ ኪ.ሜ. የሚጠጋ ሲሆን የሕዝብ ብዛቱ ደግሞ ወደ 14 ሚሊዮን እንደሆነ ይገመታል። የሴኔጋል የአየር ሁኔታ የየምድር ወገብ ሲሆን ደረቅና ዝናባማ ወራት ተብሎ ወደ ሁለት ይከፈላል። የሴኔጋል ርዕሰ ከተማ ዳካር በሀገሩ የምዕራብ ጫፍ በካፕ-ቨርት ልሳነ ምድር ላይ ይገኛል። ከባህር ጠረፍ ወደ ፭፻ ኪ.ሜ. ገደማ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የኬፕ ቨርድ ደሴቶች ይገኛሉ። በ፲፯ኛው ና ፲፰ኛው ክፍለ ዘመናት በቅኝ ገዢ መንግሥታት የተሠሩ የንግድ ተቋማት ከባህር ዳር ይገኛሉ። በአካባቢው ያሉ ግኝቶች ሴኔጋል ከጥንት ጀምሮ የሚኖርበት እንደነበረ ያሳያሉ። እስልምና የአካባቢው ዋና ሀይማኖት ሲሆን ወደ ሴኔጋል የተዋወቀውም በ11ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን እንደሆነ ይታመናል። በ13ኛውና 14ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን የማንዲንጎ ግዛት በአካባቢው ላይ ተጽኖ ያደርግ ነበር። በዚሁም ጊዜ ነው የጆሎፍ ግዛት የተመሠረተው። በ15ኛው ክፍለ-ዘመን ፖርቱጋል፣ ኔዘርላንድስ እና ኢንግላንድ በአካባቢው ለመነገድ ይወዳደሩ ነበር። በ1677 እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ጎሪ የሚባለውን ዋና የባሪያ ንግድ ደሴት ተቆጣጠረች። ከዛም በ1850ዎቹ እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ቁጥጥሩዋን ወደ መላው ሴኔጋል ማስፋፋት ጀመረች። \n \nጥያቄ: ዳካር የሴኔጋል ምንድን ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ርዕሰ ከተማ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአሦር አሦር (አሹር) ማለት በጥንታዊ ዘመን በላይኛ ጤግሮስ ወንዝ አጠገብ የተገኘ ከተማና አካባቢው ነበረ። በኋለኛ ጊዜ የአሦር መንግሥት ሃይለኛ ሆኖ መላ መሬት እስከ ግብጽ ድረስ ገዛ። በጥንታዊ አሦር ከተማና በጤግሮስ አጠገብ ያሉትም ተራሮች እስከ ዛሬው አርሜንያ ድረስ 'የአሦር ተራሮች' ይሰየሙ ነበር። በኦሪት ዘፍጥረት መሠረት አሦር (አሹር) ከኖኅ ልጅ ሴም ልጆች አንዱ ሲሆን፥ ከሰናዖር ወጥቶ አንዳንድ ከተማ ሠራ። በአሦራውያንም እምነት ዘንድ 'አሹር' ከተማውን የመሠረተው አምላክ ስም ነበረ። ከቅድመኛው ዘመን አውራጃው ሹቡር ተብሎ ከሰናዖር (ሹመር)፣ ማሪ ወይም ከአካድ ይገዛ ነበር። ሹቡር በታላቁ ሳርጎን መንግሥት ውስጥ ክፍል ሆኖ ጉታውያን እስከ አጠፉት ድረስ ቆየ። በኋላ እስከ 1879 ዓክልበ. ግ. ከኡር 3ኛ ሥርወ መንግሥት ይቆጣጠር ነበር። የዑር መንግሥት ሲወድቅ የአሦር ከተማ ነገሥታት ሊሙ ስሞች ይመዘገባሉ። በዚህ ወቅት አሦር ከተማ-አገር ብቻ ነበረ። ሆኖም አሦራውያን የብረታብረት ንግዳቸውን ለማስፋፋት በማሰብ አንዳንድ ቅኝ-ከተማ (ካሩም) በሐቲ (ዛሬው ቱርክ) ውስጥ መሠረቱ። ከነዚህም ዋነኛው ካነሽ የተባለው ከተማ ነበር። በ1720 ዓክልበ. ግ. አሞራዊው ንጉሥ 1 ሻምሺ-አዳድ አገሩን ከነአሦር ከተማ አቀና። ልጁን 1 እሽመ-ዳጋን (1688-1678 ዓክልበ.) በአሦር ላይ ሾመው። ነገር ግን የባቢሎን ንጉስ ሃሙራቢ ድል አድርጎት ዙሪያው ወደ ባቢሎን መንግሥት ተሳለፈ። ከትንሹ እስያ ይካሄድ የነበረው የብረታብረት ንግድ በዚያን ጊዜ ተቋረጠ። ለሚከተለው መቶ አመት አሦር ለባቢሎን ተገዥ ነበር። በ1507 ዓክልበ. ግ. ባቢሎን ለካሣውያን ከወደቀ በኋላ፥ አሦር በሚታኒ መንግሥት (ሑራውያን) በ1441 ዓክልበ.ግ. ይሸነፍ ነበር። ሚታኒ በኬጢያውያን ግፊት ሲወድቅ ግን የአሦር ንጉስ አሹር-ኡባሊት ነጻነቱን አዋጀ (1366 ዓክልበ. ያህል)። ከዚህ በላይ ይህ አሹር-ኡባሊት የራሱን ልጅ ኩሪጋልዙን በባቢሎን ዙፋን ላይ አሾመው። በ1290 ዓክልበ. የአሦር ንጉስ 1 አዳድ-ኒራሪ የሚታኒን መንግሥት አሸነፈ። የአዳድ-ኒራሪ ተከታይ 1 ስልምናሶር መንግሥቱን በከጢያውያን አግጣጫ እስከ ከርከሚሽ ድረስ አስፋፋ። የስልምናሶርም ልጅ 1 ቱኩልቲ-ኒኑርታ እንኳን በባቢሎን ላይ ገዛ። ሆኖም በቅርብ ጊዜ ባቢሎን በአሦር ላይ አመጽ ታደርግ ነበር። በ1200 ዓክልበ.. አካባቢ የኬጢያውያን መንግሥት በሙሽኪ (ፍሩጋውያን) ግፊት ስለ ወደቀ፥ ባቢሎንና አሦር ለአሞራውያን መሬት ተወዳዳሪዎች ሆኑ። የአሦር ንጉስ 1 አሹር-ረሽ-ኢሺ በዚህ አቅራቢያ በ1140 ዓክልበ. በባቢሎንን ንጉሥ 1 ናቡከደነጾር ላይ አሸነፈ። የአሹር-ረሽ-ኢሺ ልጅ 1 ቴልጌልቴልፌልሶር የመንግሥቱን ጠረፍ በጣም አስፋፋ። ከርከሚሽን ከመማረኩ በላይ በሙሽኪ ላይ እስከ ጥቁር ባሕር ድረስ ዘመቻ አደረገ። ደግሞ እስከ ሜድትራኒያን ባሕር ድረስ ሲዘረጋ ፊንቄን (ሊባኖስ) ያዘ። ከ1 ቴልጌልቴልፌልሶር በኋላ ከጎረቤቶቹ ከአራማውያንና ከኡራርቱ የተነሣ የአሦር ኅይል ደክሞ ነበር። በ920 ዓክልበ. ግን 2 አዳድ ኒራሪ ንጉሥ ሆሞ የአሦር ሃይል ታደሰ። ደግሞ ወደ ስሜን የኖሩትን ሕዝቦች በሙሉ በሰፈራ አፈለሳቸው። ይሁንና መንግሥቱ ከአቦር ወንዝ ወደ ምዕራብ አልዘረጋም። ንጉስ አሹር-ናሲር-ፓል ከ890 ዓክልበ. ጀምሮ ነግሦ ያለ ምኅረት ጠረፎቹም አስፋፋ። ከአቦርና ከኤፍራጥስ መካከል ያሉትን አራማውያን ድል አድርጎ በሜድትራኒያን ሲደርስ ፊንቄን ቀረጠ። ካልሁንም ዋና ከተማው እንዲሆን አደረገው። በልጁ 3 ስልምናሶር 34 አመት ዘመን (865-831 ዓክልበ.) አሦር በየአመቱ ለጦርነት ሠለፈ። ባቢሎን ተወርሮ ተቀረጠ። የሶርያ (አራም-ደማስቆ) ንጉስ ወልደ አዴር (አድርአዛር) ከእስራኤል ንጉስ አክዓብ ጋራ በቃርቃር ፍልሚያ ስልምናሶርን አጋጠመው። ስልምናሶርም ፊንቄንና የእስራኤል ንጉስ ኢዩን አስቀረጠ። በዋና ከተማው በካልሁ የተገኘው ጥቁር ሐውልት ስለ 3 ስልምናሶር ዘመን ድርጊቶች ይመሰክራል። \n \nጥያቄ: በጥንታዊ ዘመን በላይኛ ጤግሮስ ወንዝ አጠገብ የተገኘ ከተማና ስሙ ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አሦር (አሹር) ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበውሃ ላይ የሚሰራ የኤሌክትሪክ ብስክሌት በገበያ ላይ መዋሉ ተነገረ። ማንታ 5 የተባለው የኒውዝላንድ ኩባንያ ኤክስ ኢ 1 የተሰኘችውን እና በውሃ ላይ የምትሰራውን የኤሌክትሪክ ብስክሌት በላስ ቬጋስ አስተዋውቋል። ብስክሌቱ በፔዳል የሚሰራ ሲሆን፥ አንድ ጊዜ ባትሪ ከተሞላ በኋላ ለአንድ ሰዓት ያክል መጠቀም ይቻላል። በሰዓትም እስከ 20 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር ድረስ መጓዝ ይችላልም ነው የተባለው። አዲሱ ብስክሌት የ6 ሺህ ፓውንድ ዋጋ ተቆርጦለታል። ብስክሌቱን ለዕይታ ለማብቃት እስከ 10 አመት ጊዜ እንደፈጀ ኩባንያው ምርቱን ባስተዋወቀበት ወቅት ገልጿል። አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 29፣ 2012 (ኤፍቢሲ) \n \nጥያቄ: ኤክስኢ 1 በውሃ ላይ የምትሰራ የኤሌክትሪክ ብስክሌት ባለቤት ማንታ 5 ምርቱን ለመጀመሪያ ጊዜ ያስተዋወቀው የት ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በላስ ቬጋስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበውሃ ላይ የሚሰራ የኤሌክትሪክ ብስክሌት በገበያ ላይ መዋሉ ተነገረ። ማንታ 5 የተባለው የኒውዝላንድ ኩባንያ ኤክስ ኢ 1 የተሰኘችውን እና በውሃ ላይ የምትሰራውን የኤሌክትሪክ ብስክሌት በላስ ቬጋስ አስተዋውቋል። ብስክሌቱ በፔዳል የሚሰራ ሲሆን፥ አንድ ጊዜ ባትሪ ከተሞላ በኋላ ለአንድ ሰዓት ያክል መጠቀም ይቻላል። በሰዓትም እስከ 20 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር ድረስ መጓዝ ይችላልም ነው የተባለው። አዲሱ ብስክሌት የ6 ሺህ ፓውንድ ዋጋ ተቆርጦለታል። ብስክሌቱን ለዕይታ ለማብቃት እስከ 10 አመት ጊዜ እንደፈጀ ኩባንያው ምርቱን ባስተዋወቀበት ወቅት ገልጿል። አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 29፣ 2012 (ኤፍቢሲ) \n \nጥያቄ: ኤክስ ኢ 1 በውሃ ላይ የሚሄድ የኤሌክትሪክ ብስክሌት የስንት ብር መጠን ተቆርጦለታል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የ6 ሺህ ፓውንድ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጉጃራቲ ጉጃራቲ (ગુજરાતી) በህንዳዊ-አውሮፓዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ የሚገኝ ቋንቋ ነው። በዓለሙ ውስጥ በ46 ሚልዮን ሰዎች ይናገራል፤ ከነዚህም 45.5 ሚልዮን በህንደኬ፣ 250,000 በታንዛኒያ፣ 150,000 በዩጋንዳ፣ 100,000 በፓኪስታንና 50,000 በኬንያ አሉ። በሕዝብ ብዛት የዓለሙ 23ኛ ቋንቋ ነው። በምእራብ ህንደኬ ያለው የጉጃራት ክፍላገር ይፋዊ ቋንቋ ነው። የጉጃር ሕዝብ ወደ ህንደኬ የደረሱ በ5ኛው መቶ ዘመን ሲሆን በ6ኛው መቶ ዘመን ዛሬ ጉጃራት በሚባለው አገር ሰፈሩ። የራሳቸውን ቋንቋ ቶሎ ትተው እንደ አገሩ ሰዎች ሳንስክሪት ለመናገር ጀመሩ። በ12ኛው ክፍለ ዘመን ግን ሳንስክሪት ተለውጦ ብዙ አዲስ ቋንቋዎች ተወለዱ። ከነዚሁም አንድ ጉጃራቲ ነበር። አብዛኛው ተናጋሪዎቹ የህንድ ሃይማኖት ተከታዮች ቢሆኑም ለረጅም ዘመን የእስላም ገዢዎች ስለነበሩባቸው ብዙ ቃላት የተወሰዱ ከፋርስ ሆኗል። ከዚያ በላይ በንግድ ምክንያት ብዙ ቃሎች ከፖርቱጊዝ ወይም ከእንግሊዝኛ ተበደሩ። የሚጻፍበት በራሱ ጉጃራቲ ፊደል ነው፤ ይህም ከላይኛ መስመር በማጣቱ በስተቀር የህንዲ ደቫናጋሪ ፊደል ይመስላል። \n \nጥያቄ: ጉጃራቲ ቋንቋ 45.5 ሚልዮን ያህል ተናጋሪዎች ያሉት በየት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በህንደኬ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጭ ኢትዮጵያዊው ሊቅና ጻድቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጭ የተወለዱት በ፲፫፻፶፯ ዓ.ም. በወሎ ክፍለ ሀገር በቦረና ወረዳ ሸግላ/ሰግላ በተሰኘች ቦታ ነው። አባታቸው ሕዝበ ጽዮን ከተከበሩ መምህራን ወገን የሆኑ የቤተ መንግሥት ባለሟል ፤ መጽሐፍትን የሚያውቁ ጥበብ የተሞሉ ሲሆን የሰግላ አገረ ገዢም ነበሩ ። እናታቸው እምነጽዮንም ከወለቃ ሹማምንት ወገን የሆኑ ደግ ሰው ነበሩ። ሲጀመር እናታቸው ፈሪሃ እግዚአብሔርን እያስተማሩ በጥበብና በዕውቀት አሳደጓቸው ። አባ ጊዮርጊስ የተመረጠ የሆነ ሰማዕቱን ቅዱስ ጊዮርጊስን በመማፀን የተወለዱ ልጃቸው ስለሆኑ እንደሰማዕቱ የእውነት ምስክር እንዲሆኑላቸው በመመኘት ስማቸውን ጊዮርጊስ ብለው ጠርተዋቸዋል ። ከተወለዱበትም ሀገር በመነሳት ጊዮርጊስ ሰግላዊ ተብለው ሲጠሩ በጊዮርጊስ ዘጋስጭና በጊዮርጊስ ሰግላዊ መካከል ምንም ልዩነት የለም። ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ እንደ ሰማዕት ግርፋትንና እሥራትን የተቀበሉ ፣ እንደ ሊቃውንት የመናፍቃንና የከሀድያንን ክርክር የረቱ ፣ እንደ መሐንዲስ ሐናጺ ፣ የሕግና የሥርዐት የሚስጥራትና የትርጉዋሜያት መምህር ፣ የጸሎትና የትምህርት መጻሐፍት ደራሲ ፣ የሥርዓተ ገዳምና ማኅበረ መነኰሳት አባት እንዲሁም ቢያንስ የአንድ ትምህርት መሥራች ሲሆኑ በግዞት በሄዱባቸውና በታሰሩባቸው ቦታዎችም ሆነ በተሾሙባቸው እንደ ደብረዳሞ ገዳም በመሰሉ ቦታዎች ሁሉ ሲያስተምሩና ሲገስጹ ኖረዋል ። በድርሰቱም እስካሁን በሃገራችን ተወዳዳሪ የላቸውም ። እጃቸው ከብዕር ተጨማሪ ከጠንካራ ሥራ ሳይቦዝኑ ዋሻ ሲፈለፍሉ የውሃ ጉድጉዋድ ሲቆፍሩ ድልድይ ሲሠሩ ኖረዋል ። አንደበታቸውና ሕሊናቸው ከምስጋና ሳያቁዋርጡ ለቤተክርስቲያን ጸሎትና ምስጋና ሥርዓት ሲተጉ ኖረው በፅድቅና በቅድስና ሕይወት እንዳጌጡ ለተዋህዶ ኮከብ ሆነው በተወለዱ በ፷ ዓመታቸው በ፲፬፻፲፯ ዓ.ም. ሐምሌ ፯ ቀን አርፈዋል ። ተማሪዎቻቸውም በመረረ ሐዘን ሆነው አፅማቸውን በጋስጫ ራሳቸው ፈልፍለው በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም በሠሩት ገዳም ውስጥ አስቀምጠውታል። \n \nጥያቄ: አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጭ መቼ አረፉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ፲፬፻፲፯ ዓ.ም. ሐምሌ ፯ ቀን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየኢትዮጵያ ምርት ገበያ እስካሁን ግብይት የሚያስፈጽመው ግዥና ሻጭን መድረክ ላይ በማገናኘት በድምፅ ዋጋ በመንገርና በመጫረት ነው፡፡ ይህ የተለመደው አሠራር የበለጠ ውጤታማ የሚሆነው ግን በድረ ገጽ ግብይት ሲደረግ በመሆኑ ይህንን የድረ ገጽ ግብይት ለማስጀመር ከሦስት ዓመት በፊት ሥራው የተጀመረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ሥራው ተጠናቅቆ ወደ ትግበራ ሊገባ ችሏል፡፡ በተለመደው የመድረክ የግብይት አሠራር በቀን የሚፈጸመው የግብይት መጠን ከ200 እስከ 300 የሚደርስ ነው፡፡ ይህም የግብይት መጠኑ ውሱን መሆኑን ያሳያል፡፡ ስለዚህ የድረ ገጽ ግብይት መጀመሩ ግን ይህንን በመለወጥ ከፍተኛ አቅም ይሰጣል፡፡ ይህም አሠራሩን ተግባራዊ ከማድረጉ በፊትም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ባለው ተቋም ጭምር ዕውቅና አግኝቶበታል፡፡ እንደ የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ያሉ ተቋማትም ይህንን አገልግሎት ፈትሸው ማረጋገጫ ተሰጥቶት እየተሠራበት ስለመሆኑም የምርት ገበያው የሥራ ኃላፊዎች ያስረዳሉ፡፡ ይህንን ዘመናዊ አገልግሎት ሥራ ለማስጀመር ከመጀመሪያው ጀምሮ የገንዘብ ድጋፍ ሲያደርግ የቆየው የኢንቨስትመንት ክላይሜት ፋሲሊቲ ፎር አፍሪካ (ICF) የተባለው ተቋም ሲሆን፣ ለዚህ ፕሮጀክት 2.2 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አድርጓል፡፡ ይህ ግብይት በቡና የተጀመረ ሲሆን፣ ሁሉም በዚህ የግብይት ሥርዓት እንዲጠቀሙ ይደረጋል፡፡ የግብይት ሥርዓቱ አዲስ በመሆኑ በዚህ ለመጠቀም ተገበያዮች ሥልጠና እንዲወስዱ ተደርጓል፡፡ እስካሁንም 380 ተገበያዮች በድረ ገጽ ለመገበያየት ሥልጠና ወስደው ብቁ መሆናቸው ተረጋግጦ ሰርተፊኬት ተሰጥቷቸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ ምርት ገበያ የድረ ገጽ የግብይት ሥርዓትን ለማበልጸግ የገንዘብ ድጋፍ ያገኘው ከማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የኢንቨስትመንት ክላይሜት ፋሲሊቲ ፎር አፍሪካ (ICF) ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበ1240 አካባቢ በግብጽ አገር ቅብጡ አቡል ፋዳዒል እብን አል-አሣል ፍትሐ ነገሥት በአረብኛ ጻፉ። እብን አል-አሣል ሕጎቹን የወሰዱት በከፊል ከሃዋርያት ጽህፈቶችና ከሕገ ሙሴ፤ በከፊልም ከድሮ ቢዛንታይን ነገስታት ሕጎች ነበር። መጽሐፉ በግዕዝ ተተርጉሞ ወደ ኢትዮጵያ የገባበት ወቅት በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን በ1450 አከባቢ እንደነበር የሚል ታሪካዊ መዝገብ አለ። ቢሆንም መጀመርያ እንደ ሕገ ምንግሥት መጠቀሙን የተመዘገበው በዓፄ ሠርፀ ድንግል ዘመን (ከ1555 ጀምሮ) ነው። ፍትሐ ነገስት እስከ 1923 ዓ.ም. የብሄሩን ዋና ሕግ ሆኖ ቆየ። በ1904 ዓ.ም. ዐጼ 2 ምኒልክ የዘመናዊ ሕገ መንግሥት ፅንሰ ሀሳብ ተረድተው በጸሀፊው መምሬ ብስራት አንድ ሕገ መንግሥት የሚመስል ሰነድ ታተመ፤ ይህ ግን በውነት ሕገ መንግሥት አይባልም። «በምኒሊክ ስለተቋቋሙት ሚኒስቴሮች በምሳሌ የቀረበ ጽሑፍ» በምሳሌና በትርጓሜ የእያንዳንዱን ሚኒስቴር ሥራ እንደ ሰውነት አካላት አስመሰለ። ለምሳሌ፦ ኢትዮጵያ መጀመርያ ዘመናዊ ሕገ መንግሥት የተቀበለችው በ1923 አመተ ምኅረት በአጼ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የታወጀ ሲሆን የሕግ አማካሪ ቤቶች በሁለት ያስከፈለ ነው። ይህ የመንግሥታቸው ዋና መሠረት ሆኖ እስከ 1948 አ.ም. አገለገለ፤ በዚያ አመት ተሻሽሎ በወጣ ሕገ መንግሥት ሕዝቦች በመንግሥት ሥራ የሚጫወቱት ሚና እንደገና ተስፋፋ። ይህ ብቻ የአገሪቱ ሕገ መንግሥት ሆኖ እስከ 1967 አ.ም. ቆየ፤ የዛኔ በደርግ (በሕገ መንግስት እራሱ ባልሆነ ሂደት) ተሰረዘ። \n \nጥያቄ: ፍትሐ ነገሥት ወደ ግእዝ ተተርጉሞ ኢትዮጵያ የገባው በማን ዘመን ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nከዛሬ ፶00 ዓመት በፊት የሶሎሞን ስረወ መንግስት ሸዋ (መንዝንና ተጉለት) ላይ ሆኖ ለረጅም ዘመን ኢትዮጵያን ካስተዳደረ በሁዋል የግራኝ መሃመድ ወረራ በአጼ ልብነድንግል ዘመን ተካሄደ። ኢትዮጵውያን በግራኝ መሃመድ ወረራ የተነሳ ከፖርቱጋሎች ጋር ግንኙነትን መሰረቱ፡ በ፩፮፴ ተጀምሮ ለረጅም ጊዜ የተካሄደው ግጭት ከውጪ የመጡትን ሚሲዮናዊያን በሙሉ ከኢትዮጵያ በማባረር ሰላም ተመልሷል፡፡ ይህ የከፋ የግጭት ጊዜ ኢትዮጵያ የውጭ ክርስትያኖች ላይ እና አውሮፖውያኖች ላይ እስከ ሀያኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ፊቷን እንድታዞር አስተዋጾ ከማድረጉም በተጨማሪ እስከ 19ኛው ክ/ዘመን አጋማሽ ድረስ ኢትዮጵያ ከመላው አለም ተገልላ እንድትቆይ አድርጓታል፡፡ ከ1700 ጀምሮ 100 ለሚሆኑ አመታት ኢትዮጵያ ማዕከላዊ አገዛዝ ሳይኖሯት ቆይታለች፡፡ ይህም “ዘመነ መሳፍንት” ሲሆን በ1869 አፄ ቴዎድሮስ መሳፍንቶቹን ሁሉ አስገብረው ኢትዮጵያን አንድ አድርገዋል \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ ማእከላዊ አስተዳደር ሳይኖራት የቆየችበት ጊዜ ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ዘመነ መሳፍንት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nግንቦት ፳፮ ቀን፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፷፮ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት ፷፩ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፺፱ ቀናት ይቀራሉ። ፲፱፻፶፬ ዓ/ም - የኤር ፍራንስ ቦይንግ ፯፻፯ አየር ዠበብ ከፓሪስ ኦርሊ ማረፊያ ተነስቶ ወደ አትላንታ ለመብረር ሲነሳ በደረሰበት አደጋ ፻፴ መንገደኞችና የዓየር መንገዱ ባልደረቦች ሞተዋል። ፲፱፻፶፭ ዓ/ም - የአሜሪካው ‘ኖርዝ ዌስት ኤየርላይንስ’ ዲ-ሲ-፯ አየር ዠበብ በረራ በሰላማዊ ውቅያኖስ ላይ ውድቆ ሲሰምጥ ፻፩ ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኮንኮርድ አየር ዠበብ አምሳል የተሠራው የሶቪዬት ቱፖሌቭ ቲ-ዩ-፻፵፬ ፈረንሳይ ላይ በደረሰበት የበረራ አደጋ ሲከሰከስ ፲፬ ሰዎች ሞተዋል። ፲፱፻፺፰ ዓ/ም - የቀድሞዋ ዩጎዝላቪያ አካላት የነበሩት ሰርቢያ እና ሞንቴኔግሮ የውሕደት ስምምነታቸውን በሞንቴኔግሮ የሉዐላዊነት አዋጅ ምክንያት ሰረዙ። ፲፯፻፷፭ ዓ/ም - የዓፄ በካፋ ሚስት የነበሩት እቴጌ ምንትዋብ በዚህ ዕለት አርፈው በቁስቋም ደብረ ጸሐይ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። \n \nጥያቄ: የኤር ፍራንስ ቦይንግ ፯፻፯ አየር ዠበብ በደረሰ አደጋ የሟቹች ቁጥር ስንት ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ፻፴ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኮምፒዩተር ኮምፕዩተር ማለት ማንኛውንም ኢንፎርሜሽን ፕሮሰስ የሚያደርግ ማሽን ነው። ይህንም የሚያደርገው በተርታ የተቀመጡ ትዕዛዞች በመፈጸም ነው። ለብዙ ሰዎች ኮምፒዩተር ሲባል ዐዕምሯቸው ላይ የሚመጣው የግል (ፐርሰናል) ኮምፒዩተር ነው። ነገር ግን ኮምፒዩተር ሲባል በጣም ብዙ ነገሮችን ያጠቃልላል። ላፕቶፕ ፣ ዴስክቶፕ ፣ ማይክሮ-ኮምፒዩተር ፣ ሱፐር-ኮምፒዩተር ፣ ካልኩሌተር ፣ዲጂታል ካሜራ እና ሌሎችንም ያጠቃልላል። ቀድሞ አስሊ ማለት አንድ በሒሳባዊ ትዕዛዝ የተለያዩ የጥንት መሣሪያዎችን እየተጠቀመ ቁጥሮችን የሚያሰላ ሰው ነበር። እስከ 20ኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ የተለያዩ ጠቃሚ መሣሪያዎች ተሰርተዋል። ከዛ በኋላ ትልልቅ ማሸኖች መሠራት ጀመሩ። እነዚህ ማሽኖች ከዛሬው ኮምፒዩተሮች(አስሊዎች) ጋር ሲወዳደሩ በጣም ትልቅና ቀርፋፋ ናቸው። የኮምፕዩተር የውስጥ ክፍሎች የሚከተሉት ናቸው፡- 1.ሞኒተር - የምንሰራውን ነገር እንዲያሳየን፤ምስል፣ጽሑፍ፣ ቪዲዮ ወይም ማንኛውም ነገር ሊሆን ይችላል፡፡ ሞኒተር 14 ኢንች፣ 15 ኢንች፣ ወዘተ. እየተባለ ይገላጻል፡፡ 2.ማዘርቦርድ - እናት ሰሌዳ ሁሉም የኮምፕዩተር ክፍሎች(ዕቃዎች)የሚቀዳጁበት 3.ሲፒዩ - የኮምፕዩተሩ አእማሮ እንደማለት ነው፡፡ ይህ ሲባል ግን ሲፒዩን ከሰው አእምሮ ጋር አንድ ነው ማለት አይደለም፡፡ 4.ሜሞሪ - የምንሰራውን ስራ ወይም ፋይል በጊዚያዊነት አስቀምጠንበት የምንሰራበት፡፡ ሜሞሪበባይት (Bytes) ይለካል፡፡ ከ Bytes ፊት Kilo፣ ማለትም ኪሎባይት (kilobytes)([1,024 ባይቶች ወይም Bytes ማለት ነው፡፡ ] ፣ Mega[1,048,576 ባይቶች ወይም Bytes ] ፣ Giga [1,073,741,824 ባይቶች ወይም Bytes]፣ ወዘተ የሚሉትን ቃላት በመጠቀም ኪሎባይት(kilobyte)፣ ሜጋባይት (megabyte)፣ ጊጋባይት (gigabyte) እያልን የኮምፒዩተር ሜሞሪ መግለፅ እንገልጻለን፡፡ ለምሳሌ 10 MegaBytes ወይም ባጭሩ ሲጸፍ 10MB ይህ ማለት 10,485,760 Bytes ይሆናል ማለት ነው፡፡ 5.ኤክስፓንሽ ስሎት 6.የኤሌክትሪክ ሀይል ማቅረቢያ (power supply) 7.የሲዲ ማሰሪያ (cd drive) 8.ሀርድ ዲስክ (የምንሰራውን ወይም የምንጠቀምበትን ፋይል በቋሚነት ለማስቀመጥ) 9. መሎጊያ (ማውስ) 10.የፊደል ገበታ (ኪቦርድ) የመጀመሪያቹ ኮምፕዩተሮች የሚሠሩት በእንግሊዝኛ ፊደል ብቻ ነበር። ቀስ በቀስ ግን የተለያዩ ኣገሮች ሊቃውንት በየራሳቸው ፊደላት እንዲሠሩ ኣደረጉ። ኮምፕዩተር በእያንዳንዱ የግዕዝ ፊደል፣ ኣኃዝና ምልክት እንዲሠራ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈጠረው ኢትዮጵያዊው ዶክተር ኣበራ ሞላ ነው። በቅርቡም አያንዳንዱ የግዕዝ ፊደል፣ ኣኃዝና ምልክት ዩኒኮድ የሚባል የዓለም ፊደላት መደብ ውስጥ መግባት ቀጥሏል። \n \nጥያቄ: ማንኛውም በኮምፒዩተር ፕሮሰስ የሚያደረጉ ነገሮችን በጊዜያዊነት የሚያጠራቅም የኮምፒዩተሩ ክፍል ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሜሞሪ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nግሥላ ግሥላ በእስያ፣ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በመካከለኛው ምሥራቅ የሚገኝ አጥቢ አውሬ ነው። በእስያ የተገኘው ነብር የግስላ ቅርብ ዘመድ ሆኖ፣ በአነጋገር «ግስላ»ና «ነብር» የሚሉ ስሞች ሊለዋወጡ ይችላሉ። የአንድ ጎልማሳ ግሥላ ክብደት ከ35 እስከ 80 ኪ.ግ ሲደርስ በርዝመት ከ90 ሴ.ሜ እስከ 1,60 ሜ.ና በአፍሪካ የሚገኘው ዘር እስከ 1,90 ሜ ይደርሳል ። ከመሬት እስከ ሆዱ ከ50 እስከ 70 ሴ.ሜ ቁመት ሲኖረው ጭራው ደግሞ እስከ 100 ሴ.ሜ ርዝማኔ ያሳያል ። ሴቲቱ ከወንዱ አነስ ትላለች ። በዱር ሲኖር እስከ 10 አመት እንደሚኖር ሲታወቅ በሰው ተይዘው ሲኖሩ እስከ 20 አመት እድሜ ያስመዘገቡ ግሥሎች አሉ። \n \nጥያቄ: ግስላ ከመሬት እስከ ሆዱ ቁመቱ ስንት ሴ. ሜ ይሆናል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከ50 እስከ 70 ሴ.ሜ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nውትድርና የናይጄሪያ ጦር ሠራዊት ሀገሯን የመከላከል፣ የሀገሯን ፍላጎት የማስጠበቅ እና ፀጥታ አስጠባቂ ጥረቶችን የመደገፍ ግዴታ አለበት። ሠራዊቱ የምድር፣ የባህርና የአየር ኃይል አለው። ሠራዊቱ ከነፃነት ጀምሮ በሀገሯ ታሪክ ላይ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። በተለያዩ ጊዜያት የውትድርና ጁንታዎች ሥልጣን በመያዝ አገሯን አስተዳድረዋል። የናይጄራያ ሠራዊት በፀጥታ ጠባቂነት ደረጃ ከ1995 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በላይቤሪያ (1997 እ.ኤ.አ.)፣ አይቮሪ ኮስት (ከ1997 እስከ 1999 እ.ኤ.አ. ) እና ሲየራ ሊዮን (ከ1997 እ.ኤ.አ. 1999 እ.ኤ.አ.) ተሰማርቷል። ምጣኔ ሀብት በግብርና ናይጄሪያ በዋናነት ለአለም የምታቀርበው ምርቶች በተለይ ካካውና ጎማ ናቸው። እንዲሁም ፔትሮሊየም ከሚያቀርቡት አገራት 12ኛ ነች። በተጨማሪ፣ የመኪና ሥራ ድርጅት (ኢኖሶን ተሽከርካሪ መፈብረክ) ይኖራል። መልከዓ ምድር ናይጄሪያ በምዕራብ አፍሪካ በጊኒ ባሕረ ሰላጤ ላይ ትገኛለች። የቆዳ ስፋቷ 923,768 ካሬ ኪ.ሚ. ሲሆን ከዓለም ፴፪ኛዋ ትልቅ ሀገር ናት። ድንበሯ 4,047 ኪ.ሜ. ርዝመት ሲኖረው ከቤኒን 773 ኪ.ሜ.፣ ኒጄር 1,497 ኪ.ሜ.፣ ቻድ 87 ኪ.ሜ.፣ ካሜሩን 1,690 ኪ.ሜ. ትዋሰናለች። በተጨማሪም 853 ኪ.ሜ. ርዝመት ያለው ጠረፍ አላት። በናይጄሪያ ውስጥ ከፍተኛው ቦታ ቻፓል ዋዲ ተራራ ሲሆን ከፍታው 2,419 ሜትር ከባህር ጠለል በላይ ነው። የአገሯ ዋና ወንዞች ኒጄር እና ቤንዌ ሲሆን ወደ ኒጄር ደለል ይፈሳሉ። \n \nጥያቄ: ናይጄሪያ በቆዳ ስፋት ከዓለም ስንተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ፴፪ኛ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nእንደ ፕላቶ ዘገባ፣ የሶቅራጠስ እናት ፌናርት የተሰኘች አዋላጅ ነበረች። ሶቅራጠስ እናቱ ሴቶች ልጅ እንዲወልዱ እንደምትረዳ ሁሉ እርሱ ደግሞ ሰዎች አዳዲስ አሳቦችን እንዲወልዱ ለመርዳት እንደሚሞክር መናገሩ ይጠቀሳል። የሶቅራጠስ አባት ድንጋይ አናጢ የነበረው ሶፍሮኒስከስ እንደነበር ይጠቀሳል። ሶቅራጠስ በዘመኑ ድሃ የነበረ ሲሆን ለዚህ ምክንያቱ ከገንዘብ ይልቅ እውቀት ይበልጣል ብሎ ስለሚያምን ነበር። ሶቅራጠስ ስራ እንደማይሰራና በፍልስፍና ሃሳብና ክርክር ጊዜውን እንደሚያሳልፍ ፕላቶ ዘግቦት ይገኛል። ዛንቲፕ የተሰኘች ከርሱ በዕድሜ በጣም የምታንስ ሴትን አግብቶ ሶስት ልጆች እንደነበሩት ፕላቶ ጽፏል። ሶቅራጠስ 70 ዓመት በሞላው ጊዜ የአቴና መንግስት እንዲያዝና ለፍርድ እንዲቀርብ አደረገ። በወቅቱ ሁለት ክሶች ሲቀርቡበት አንደኛው \"በትምህርትህ ወጣቱን አበላሽተሃል\" የሚል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ \"ለግሪክ ጣዖታት አልተገዛህም\" የሚል ነበር። እንደ ፕላቶ ዘገባ ግን ሶቅራጠስ የግሪክ ጣኦታት አምላኪ ነበር። በአንድ አንድ ተመራማርወች ዘንድ የአቴንስ መንግስት ያቀረባቸው ክሶች በውሸት ላይ የተመሰረቱ ናቸው። የሆኖ ሆኖ፣ ክሪቶ የተሰኘው የፈላስፋው ጓደኛ ለጠባቂወቹ ጉቦ በመስጠት እንዲያመልጥ ሁኔታውን አመቻችቶ ነበር። ሶቅራጠስ ግን እምቢ በማለት ቀረ እንጂ አላመለጠም። ሶቅራጠስ ለፍርድ በቀረበ ጊዜ ሰፊ የሆነ የመከላከያ ክርክር በማቅረብ የአቴናን መንግስት ክስ ውድቅ ለማደርግ ሞክሯል። ከዚህ በኋላ ዳኞቹ ምን አይነት ቅጣት እንዲበይኑበት እንደሚፈልግ ሲጠይቁት፣ ለአቴና ህብረተሰብ ካበረከተው ጥሩ ተግባራቱ አንጻር በቀሪው ዘመኑ ሁሉ ነጻ እራት እንዲያመጡለት ተናገረ። ነገር ግን ፍርድ ቤቱ ወይ በቅጣት እንዲለቀቅ ወይንም ደግሞ እንዲገደል የእጅ ምርጫ አደረገ። ውጤቱም ሶቅራጠስ እንዲገደል የሚል ሆነ። ይሁንና ሶቅራጠስ ሞትን አይፈራም ነበር። ሞቱን ለማስቀረት ይቅርታም ሆነ ሌላ ማባበያ አላቀረበም። በርሱ ሥነ ምግባር መሰረት ላመነበት ነገር እስከመጨረሻ መቆሙ ሰናይ ድርጊት ነበር። ስለሆነም ሄምሎክ የተሰኘ መርዝ ጠጥቶ እንዲሞት ስለታዘዘ፣ መርዙን በመጠጣት አለፈ። \n \nጥያቄ: ሶቅራጥስ ማን የምትባል ሴት አገባ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ዛንቲፕ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአፋር (ክልል) አፋር ክልል (ክልል 2) በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙት ዘጠኝ ክልሎች አንዱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ዋና ከተማው ሰመራ ሲሆን የቀድሞዋ ከተማ ግን አሳይታ ነበረች። 96,707 ካሬ ኪ.ሜ. ሲሸፍን በ1999 እ.ኤ.አ. የሕዝብ ብዛቱ 1,188,000 ነው። የድንቅ ነሽ ወይም ሉሲ አጽም በአፋር ክልል ውስጥ በ, 1967 (Nov. 24, 1974 እ.ኤ.አ.) ነው የተገኘው። በማርች 5, 2005 ደግሞ ሌላ 3.8 ሚሊዮን ዓመት የሚገመት አጽምም በዚሁ ክልል ተገኝቷል። \n \nጥያቄ: የአፋር ክልል የቆዳ ስፋቱ ምን ያህል ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 96,707 ካሬ ኪ.ሜ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቅልልቦሽ ቅልልቦሽ የኢትዮጵያ ህጻናት በጠጠር የሚጫወቱት ሲሆን አጨዋወቱም አንዱዋን ጠጠር ወደአየር በማጉናት እሱዋ ባየር ላይ እያለች የተቻለን ያክል ጠጠር ከመሬት ማፈስ ነው። ባየር ላይ ያለችው ጠጠር ስትመለስ በተጫዋቹ እጅ \"መቀለብ\" ወይም \"መያዝ\" ይኖርባታል። ሳትያዝ መሬት ላይ ከወደቀች፣ ጨዋታው አለቀ ማለት ነው። ጨዋታው \"ጠጠር\" በመባልም ይጠራል። ብዙ አይነት የቅልልብልቦሽ ጨዋታዎች ሲኖሩ፡ በጣም የታወቀው \"ዓይጥ አለብሽ\" በመባባል የሚጫወቱት ነው። ልጆቹ ሁለት ወይም ሶስት ይሆኑና፡ አምስት ቆንጆ ድብልብል ጠጠሮች፡ ስፋትና ርዝመታቸው ከግማሽ ኢንች የማይበልጡ፡ ይለቅሙና መሬት ይቀመጣሉ። ቀድሞ \"ብጀ\" ያለ መጀመርያ ይጀምራል። ብጀ ማለት ብጀምር ማለት ነው። ያንን ለማለት እሽቅድምድም ነው።\"ብቀ\" ያለ ከርሱ የሚከተል ነው ማለት ነው፡፡ ብቀ ማለት ብቀጥል ማለት ነው። ሁለት ልጆች እኩል \"ብቀ\" ካሉ በድምጽም ቢሆን ቀድሞ \"ብ!\" ከአፉ የወጣው ሰው ሁለተኛነቱን ያገኛል። \"ብቀጣጥል!\" ያለ ሶስተኛ ነው። \"እንጀራ ብጋግር!\" ያለ አራተኛ ነው። አምስተኛ ካለ \"ወጥ ብሰራ!\" ብሎ ተራውን ያሳውቃል። በዚህ ተራ ተስማምተው ጀማሪው ይጀምራል። \n \nጥያቄ: በጣም የታወቀው የቅልብልቦሽ አይነት የትኛው ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ዓይጥ አለብሽ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nረጅሙ የቦይንግ አውሮፕላን የመጀመሪያ በረራውን በስኬት አጠናቋል። ቦይንግ 777- 9 ኤክስ የተሰኘው ይህ አውሮፕላን ባለ ሁለት ሞተር እና 76 ሜትር ርዝመት እንዳለው ተገልጿል። አዲሱ አውሮፕላን በኩባንያው ምርቶች ላይ በሚፈጠሩ እክሎች ምክንያት የሚደርሱ አደጋዎችን ለመቀነስ ያስችላል ነው የተባለው። የአውሮፕላኑ የተሳካ የበረራ ሙከራ ሲያትል ከተማ አካባቢ የተከናወነ ሲሆን፥ ይህ ሙከራ ከመካሄዱ በፊት በአየር ፀባይ ችግር ምክንያት ሊካሄዱ የነበሩ ሁለት የሙከራ በረራዎች እንዲቋረጡ ተደርጓል። ኩባንያው እስካሁን 309 የሚሆኑ 777 ኤክስ አውሮፕላኖችን የሸጠ ሲሆን፥ የአንዱ ዋጋም 442 ሚሊየን ዶላር ነው ተብሏል። ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖቹ ላይ በተፈጠረ የቴክኒክ ችግር ምክንያት ንብረትነታቸው የኢትዮጵያ እና ኢንዶኔዢያ የሆኑ ሁለት አውሮፕላኖች ተከስክሰው የ346 ሰዎች ህይወት ማለፉ ይታወሳል። ይህን ተከትሎም ኩባንያው የሚያመርታቸው አውሮፕላኖች ደህንነት አስተማማኝ አይደለም በሚል በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እና በባለሙያዎች ከፍተኛ ወቀሳ ሲቀርብበት ቆይቷል። ምንጭ፦ ሲ ኤን ኤን   \n \nጥያቄ: ቦይንግ 777- 9 ኤክስ የተሰኘው አውሮፕላን በምን ያህል ዋጋ እየሸጠ ይገኛል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 442 ሚሊየን ዶላር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአማራ (ክልል) አማራ (ክልል 3) ከዘጠኙ የኢትዮጵያ ክልሎች አንዱ ሲሆን ከ 1994 በፊት አራት የሀገሪቱን ዋና ወና ክፍለ ሀገራት የ ካትት ነበር እነሱም በጌምድር ጐጃም ወሎና ሸዋ ነበሩ ።የአማራ ብሔራዊ ክልል ጅኦግራፊያዊ አቀማመጥ በ8° 45 እስከ 13° 45 ሰሜን የኬንትሮስ እና በ35° 46 እስከ 40° 25 ምስራቅ የኬንትሮስ መስመር ውስጥ ይገኛል። በምስራቅ የአፋርና የኦሮሚያ ክልሎች፣ በምዕራብ ሱዳን እና ቤንሻንጉል-ጉምዝ ክልል፣ በሰሜን የትግራይ ክልልና በደቡብ የኦሮሚያ ክልል ያዋስኑታል። የቆዳ ስፋቱ ፻፶፯ሺ፸፮ ካሬ ሜትር ሲሆን ከአገሪቱ አሥራ አምስት በመቶ ድርሻ ይይዛል። የክልሉ ሕዝብ ብዛት ደግሞ በ፳፻፪ ዓ/ም 20,875,456 እንደነበር የተገመተ ሲሆን ከአገሪቱ ጠቅላላ ሕዝብ 33.9% አካባቢ ድርሻ ይይዛል ተብሎ ይገመታል። ክልሉ በ፲ ዞኖችና በ፻፷፮ የገጠርና የከተማ ወረዳ አስተዳደሮች የተከፋፈለ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ፴፰ የሚሆኑት የከተማ አስተዳደሮች ናቸው። የአማራ፣ የአገው፣ የኦሮሞና የሌሎች ብሔረሰቦች በጋራ የሚኖሩበት ክልል ነው። እንዲሁም የአማራ ክልል አሁን ላይ የክልል ከተማው ባህር ዳር ነው። በክልሉ አልፎ አልፎ ከሚታዩ የመንግሥትና የማኅበራት ደኖች፣ በደሴቶች፣ በአብያተ ክርስቲያናት፣ በወንዞች ዳርቻና ሰው ሊደርስባቸው በማይችሉ ገደላማና ተራራማ ስፍራዎች ከሚገኙ ጥቂት ደኖች በስተቀር ሊጠቀስ የሚችል ከፍተኛ የደን ሀብት ጋር በቅርብ የተያያዘ ነው። በዚህ ረገድ በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የሚገኙ እንደ ቀይ ቀበሮ፣ ዋልያ፣ ጭላዳ ዝንጀሮ እንዲሁም በምዕራባዊው የክልሉ አካባቢ ዝሆን አንበሳና ነብር፣ ሰጐንና የተለያዩ አዕዋፋት በስተቀር ከፍተኛ የዱር እንስሳት ክምችት ካለመኖሩም በላይ በተለያዩ አካባቢዎች ባሉ ጥቂት የደን ቅሪቶችና ዋሻዎች የነበሩት አነስተኛ ቁጥር ያላቸው አራዊቶችም ለዘመናት በደረሰው የደን መጨፍጨፍና መራቆት ምክንያት ከክልሉ ወደ ሌላ አካባቢ እንደተሰደዱ ይታወቃል። ክልሉን የማዕድን ሀብት አስመልክቶ በሚገባ የተጠናከረ ጥናት ባይኖርም ከክልሉ ስነ-ምድራዊ ሁኔታዎችና ከተካሄዱ አንዳንድ ጠቋሚ ጥናቶች መረዳት እንደሚቻለው በክልሉ ውስጥ የተለያዩ ማዕድናት እንደአሉ ይገመታል። በዚህም መሠረት በሰሜን ሸዋ የኦፓል ማዕድን፣ በሰሜን ጐንደር፣ በጭልጋና በደቡብ ወሎ በአምባሰል ወረዳ የድንጋይ ከሰል ክምችት እንዳሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ከዚህም በተጨማሪ ለግንባታ ሥራ የሚውል በቂ የድንጋይ፣ የኖራ ድንጋይ፣የሸክላ አፈር፣ ጅኘሲየም፣ የጌጣጌጥ ማዕድናት እንዲሁም በዓባይ ሸለቆ የዕብነ በረድ ሐብቶች እንዳሉ ጥናቶች ይጠቁማሉ። ይሁን እንጅ በውል የሚታወቀው ሐብትም ቢሆን በበቂ ሁኔታ አልለማም። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የት ክልል ይገኛል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አማራ (ክልል 3) ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nመዓዛ ብሩ መዓዛ የተወለደችው እዚህ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሲሆን ዘመኑም 1951 ዓ.ም ነበር፡፡ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ክፍል በሐረርጌ ክፍለ ሀገር በሒርና ከተማ ተምራ፣ ከአራተኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን ትምህርቷን ደግሞ በቅድስት ማርያም ትምህርት ቤት ተከታትላ ፈጽማለች፡፡ መዓዛ በትምህርት ቤቷ በክፍል ውስጥ አጫጭር ታሪኮችን ለተማሪዎች በማንበብ ከመታወቋም ሌላ ከፍ ያለ የሥነ - ጽሑፍ ዝንባሌ እንደነበራት የሚያስታውሱት መምህራኗ “አንድ ቀን ታላቅ የጥበብ ሰው እንደሚወጣት እናውቅ ነበር” ይላሉ፡፡ መዓዛ በ1971 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሥነ - ቋንቋ ጥናት ተቋም ውስጥ በሥነ-ልሣን ትምህርት ክፍል ተመደበች፡፡ ሥነ-ልሣን መዓዛ የምትፈልገው ጥናት ባለመሆኑ በምደባው ቅር ብትሰኝም፤ በንዑስ ትምህርት ደረጃ የምትወስደው የውጭ ቋንቋና ሥነ - ጽሑፍ በመሆኑ ለነበራት ቅሬታ እንደማካካሻ ሆኖላታል፡፡ በዚህ ዩኒቨርሲቲ የሶስተኛ ዓመት ተማሪ ሳለች የተፈጠረ አንድ አጋጣሚ ደግሞ መዓዛንና ሬዲዮንን የሚያስተሳስር ይሆናል፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ ሬዲዮ የፕሮግራሞች ኃላፊ የነበረው አቶ ታደሰ ሙሉነህ ለሚያዘጋጀው የእሁድ የሬዲዮ ፕሮግራም ድራማ የሚጫወቱ ሸጋ ድምጽ ያላቸው ወጣቶችን ሲያፈላልግ ከመዓዛ ጋር ይተዋወቃል፡፡ ድራማው አስታጥቃቸው ይሁን ያሰናዳው ሲሆን የመዓዛ ድምጽ ለሙከራ በስቱዲዮ ተቀርጾ ሲሰማው፣ ታደሰ ሙሉነህ የሚፈልገውና የሚወደው ድምጽ ሆኖ ስላገኘው ይደሰታል፡፡ ከዚህ በኋላም ለእሁድ ፕሮግራም የሚሆኑ ጽሑፎችን በየሳምንቱ እንድታነብለት ያግባባትና የመዓዛና የሬዲዮ ፍቅር በኢትዮጵያ ሬዲዮ ይወለዳል፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የመዓዛ ድምጽ በእሁድ የሬዲዮ ፕሮግራም አድማጮች ዘንድ የተለመደና የተወደደ ሆነ፡፡ መዓዛም የሌሎችን ጽሑፎች በማንበብ ብቻ ሳትወሰን የራሷን ጽሁፎች እያዘጋጀች የምታቀርብ ንቁ ተሳታፊ በመሆን ከሬዲዮ ፕሮግራሙ ቤተሰቦች እንደ አንዱ ሆነች፡፡ በ1974 ዓ.ም ከዩኒቨርሲቲ ተመርቃ ትምህርቷ ፍጻሜውን እስካገኘ ድረስም መዓዛ ሬዲዮና ትምህርትን ጎን ለጎን ስታስኬድ ቆይታለች፡፡ የመዓዛ የሥራ ዓለም የተጀመረው ግን በምትወደውና በምትፈልገው በኢትዮጵያ ሬዲዮ ውስጥ ሳይሆን መንግስት በመደባት በባህል ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ውስጥ ነበር፡፡ ስራዋም ባህልና ስፖርት የተባለው የመስሪያ ቤቱ መምሪያ በሚያሳትመው “መርሐ ስፖርት” የተሰኘ ወርሃዊ የስፖርት መጽሔት (በኋላ ጋዜጣ) ላይ ሆነ፡፡ ምንም እንኳ አዲሱ ስራዋ ከራዲዮ የሚያርቃት ቢሆንም መዓዛ ግን ሳትሸነፍ ሬዲዮን በትርፍ ጊዜ ሥራነት ተያያዘችው፡፡ ሬዲዮ ጣቢያው የሚሠጣትን አነስተኛ ክፍያ እየተቀበለችም ልዩ ልዩ ጭውውቶችን እና መጣጥፎችን በግልና በጋራ በማቅረብ ተወዳጅ ሥራዎቿን ለሕዝብ አበርክታለች፡፡ \n \nጥያቄ: መዓዛ ብሩ ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ክፍል ድረስ የት ተማረች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በሐረርጌ ክፍለ ሀገር በሒርና ከተማ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡ \n \nጥያቄ: ሳውዲ አረብያ በምን ትታወቃለች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በቆዳ ስፋቷ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዋዝንቢት ዋዝንቢት የሦስት አጽቄ አይነት ነው። የፌንጣና የአንበጣ ዘመድ ነው። ሁለንተናው ትንሽ ለጥ ይላል፤ ረጃጅም አንቴኖችም አሉት። ዋዝንቢት የሚታወቀው በሚያሰማው ድምጽ ነው። ድምጽ ማውጣትና ማሰማት የሚችለው አውራው ዋዝንቢት ብቻ ነው። የተባዕቱ ዋዝንቢት ክንፍ እንደ \"ሚዶና ሞረድ\" የሚመስል ፍርግርግ ነው። ክንፎቹን በማፋተግ ድምጽ ይፈጥራል፤ የድምጹ ቅላፄ እንደየ ዋዝንቢቱ ወገን ይለያያል። ሁለት ዓይነት የዋዝንቢት ዘፈኖች አሉ፤ የጥሪ ዘፈንና የመርቢያ ዘፈን ናቸው። የጥሪ ዘፈን ዓላማ አንስት ዋዝንቢ ለመሳብ ሲሆን ረጅምና ከፍተኛ ድምፅ ነው። ለመራባት ሲባል የሚዘፈነው ድምፅ አንስቲቱ እንስቲቱን ለማቅረብ ስለሆነ ቀስ ያለና ለስላሳ ነው። አንስት ዋዝንቢት መርፌ የሚመስል ረጅም የዕንቁላል መጣያ አላት። በምድር ላይ 900 የሚያሕሉ የዋዝንቢት ዝርያዎች ይገኛሉ። አንዳንድ ዝርያ ሣርና ተክል ብቻ ሲበላ፣ ሌሎች ዝርዮች ደግሞ ነፍሳት ያድናሉ። ዋዝንቢት ሌሊት የሚነቃ ፍጥረት ነው። ብዙ ጊዜ ከፌንጣ ጋር ይመሳሰላል፣ በተለይ የመዝለያ እግሮቹ ከፊንጣ እግሮች አይለዩም። በ1963 ዓ.ም. ዶ/ር ዊሊያም ከይድ ምርመራ አድርጎ አንዲት ተባይ ዝንብ ደግሞ በተባዕቱ ዘፈን እንደምትሳብ፤ ዕጯንም እንድታስቀምጥበት ቦታውን ለማወቅ እንደሚጠቅማት አገኘ። የመርባትን ድምጽ በመጠቀም የአስተናጋጇን ቦታ ለምታገኝ የተፈጥሮ ጠላት ይህች መጀመርያ ምሳሌ ሆነች። ከዚያ በኋላ ብዙ የዋዝንቢት ወገኖች ይህችን ተባይ ዝንብ ሲሸክሙ በምድር ላይ ተገኝተዋል። በእስያ በተላይም በቻይና ዋዝንቢት ዝነኛ ለማዳ እንስሳ ሆኖ መያዙ እንደ መልካም እድል ይቈጠራል። የተያዘ ዋዝንቢት ሁሉ ማናቸውም አትክልት ወይም ሥጋ ቢሰጥ ይበላል። በአንዳንድ ባሕል ደግሞ ዋዝንቢት እንደ ምግብ ሊበላ ይችላል። \n \nጥያቄ: ዋዝንቢት ከምን ወገን የሚመደብ ነፍሳት ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የፌንጣና የአንበጣ ዘመድ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየፌዴራል ትራንስፖርት ባለስልጣን በአፋር ክልል ዲቼቶ አካባቢ የተገነባውን የድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሽከርካሪዎች መቆያ ተርሚናል ዛሬ ተመረቀ። ተርሚናሉ በ12 ሂክታር ላይ ያረፈ ሲሆን በአንድ ጊዜ 800 ከባድ ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ የሚችል መሆኑ ተገልጿል። የዲቾቶ የከባድ ተሽከርካሪ ተርሚናል 99 ሚሊየን 279 ሺህ 944 ብር ወጭ ተደረጎበት መገንባቱ ተነግሯል። \n \nጥያቄ: በአፋር ክልል ዲቼቶ አካባቢ የተገነባውን የጭነት መቆያ ተርሚናል ያስመረቀው ማነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የፌዴራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሄርበርት ሁቨር (1866 - 1957 ዓ.ም.) ከ1921 እስከ 1925 ዓ.ም. ድረስ 31ኛ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ነበሩ። የሁቨር ቤተሠብ ከስዊስና ጀርመን ትውልድ ሲሆን ሃይማኖቱ የክዌከር ('የሚንቀጠቀጡ' ማለት ነው) ቤተ ክርስቲያን ነበረ። ወላጆቹ በልጅነቱ ጊዜ ካረፉ አንስቶ ድሃ አደግ ሆነና ከአጎቱ ጋር አደገ። በስታንፎርድ ዩኒቨርሲቴ መጀመርያ ክፍል በመሆኑ ትምህርቱ በነጻ ተቀበለ። ከዚያ በላይ የዩኒቬርሲቴው የቤስባልና የፉትቦል ቡድኖች አለቃ ሆነ። በ1887 ዓ.ም. የጂዮሎጂ ዲግሪ ይዘው ተመረቁ። ለ20 ዓመት የማዕደን ሊቅ ሲሆኑ እንኳን በአውስትራልያና በእንግሊዝ በማዕደን ዘርፍ የሠሩት ሥራ ስመ ጥሩ ሆነ። መጀመርያው ታላቅ አለማዊ ጦርነት በ1906 ዓ.ም. በጀመረበት ወቅት ሁቨር ከራሳቸው ኪስ ለጋሥነት አውጥተው 120,000 አሜሪካውያን ቱሪስቶችና ሠራተኞችን ከአውሮፓ ወደ አገራቸው አስመለሷቸው። ከዚያ በጀርመኖች በተወረረው በቤልጅግ ውስጥ የኖሩት ረሃብተኞች ምግብ እንዲደርሳቸው ብዙ አደረጉ። በዚህ አይነት ሥራ በጦርነት ጊዜ የሁቨር ስም ጀግና እንዳለው ሁኔታ በመገኘት ላይ ሄዶ ነበር። ጦርነቱም ከተጨረሰ በኋላ ለምሥራቅ አውሮጳ ድሃ ሕዝብ እስከ ሩስያም ድረስ በረሃብ ላሉት ሰዎች ምግብ አደረሷቸው። \n \nጥያቄ: ሄርበርት ሁቨር ከመቼ እስከ መቼ የአሜሪካ ፕሬዝደንት ነበሩ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከ1921 እስከ 1925 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየ2014 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ የ2014 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ ፳ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሲሆን ከሰኔ ፭ እስከ ሐምሌ ፮ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. በብራዚል ይካሄዳል። ብራዚል ይህን ውድድር ስታዘጋጅ ይሄ ሁለተኛ ጊዜዋ ነው። ፊፋ የ2014 እ.ኤ.አ. ውድድር በደቡብ አሜሪካ እንደሚካሄድ በ2007 እ.ኤ.አ. ካወጀ በኋላ ብራዚል ያለማንም ተቀናቃኝ አዘጋጅ አገር ሆና ተመርጣለች። የ፴፩ አገራት ብሔራዊ ቡድኖች ከጁን 2011 እ.ኤ.አ. ጀምሮ የተካሄዱ የማጣሪያ ውድድሮችን በማለፍ ከብራዚል ጋር በመጨረሻው ውድድር ላይ ለመሳተፍ በቅተዋል። በጠቅላላው ፷፬ ጨዋታዎች በ፲፪ ከተማዎች ውስጥ በሚገኙ አዲስ የተገነቡ ወይም የተሻሻሉ ስታዲየሞች ይከናወናሉ። በዓለም ዋንጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የጎል ላይን ቴክኖሎጂ በጥቅም ላይ ውሏል። በ1930 እ.ኤ.አ. ከተካሄደው የመጀመሪያው የዓለም ዋንጫ ጀምሮ ሁሉም የዓለም ዋንጫ ሻምፕዮን አገራት (ብራዚል፣ አርጀንቲና፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሣይ፣ ጀርመን፣ ኢጣልያ፣ እስፓንያ እና ኡራጓይ) በዚህ ውድድር ውስጥ ተሳታፊ ናቸው። ከዚህ በፊት በደቡብ አሜሪካ የተዘጋጁትን ዋንጫዎች እንዳለ የወሰዱት የደቡብ አሜሪካ ቡድኖች ናቸው። ፊፋ ለውድድሩ ያቀረበው ጠቅላላ የሽልማት ገንዘብ $576 ሚሊዮን ነው። ይህም ከ2010 እ.ኤ.አ. ውድድር ሽልማት ገንዘብ የ፴፯ ከመቶ ዕድገት አለው። ከዚህ ውስጥ $70 ሚሊዮን የሚሆነው ተጫዋቾቹ ለሚጫወቱበት ክለቦች ተጫዋቾቹ ለሚደርስባቸው ጉዳት መካካሻ እንዲሆን ተሰጥቷል። ከውድድሩ በፊት እያንዳንዱ ቡድን ለዝግጅት ወጪው $1.5 ሚሊዮን የተረከበ ሲሆን ቀሪው ገንዘብ እንደሚመለከተው ተከፋፍሏል፦ $8 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በምድብ ደረጃ የወደቀ ቡድን (፲፮ ቡድኖች) $9 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በየ፲፮ ዙር የወደቀ ቡድን (፰ ቡድኖች) $14 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በሩብ ፍፃሜ የወደቀ ቡድን (፬ ቡድኖች) $20 ሚሊዮን - በአራተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $22 ሚሊዮን - በሶስተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $25 ሚሊዮን - በሁለተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $35 ሚሊዮን - ለአሸናፊው ቡድን በአስራ ሁለት ከተማዎች የሚገኙ አስራ ሁለት ስታዲየሞች ለውድድሩ ተዘጋጅተዋል። ሰባቱ አዲስ የተገነቡ ሲሆን አምስቱ ደግሞ የተሻሻሉ ስታዲየሞች ናቸው። \n \nጥያቄ: ብራዚል ፳ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ያዘጋጀችው በስንት ዓመተ ምህረት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 2014 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበውሃ ላይ የሚሰራ የኤሌክትሪክ ብስክሌት በገበያ ላይ መዋሉ ተነገረ። ማንታ 5 የተባለው የኒውዝላንድ ኩባንያ ኤክስ ኢ 1 የተሰኘችውን እና በውሃ ላይ የምትሰራውን የኤሌክትሪክ ብስክሌት በላስ ቬጋስ አስተዋውቋል። ብስክሌቱ በፔዳል የሚሰራ ሲሆን፥ አንድ ጊዜ ባትሪ ከተሞላ በኋላ ለአንድ ሰዓት ያክል መጠቀም ይቻላል። በሰዓትም እስከ 20 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር ድረስ መጓዝ ይችላልም ነው የተባለው። አዲሱ ብስክሌት የ6 ሺህ ፓውንድ ዋጋ ተቆርጦለታል። ብስክሌቱን ለዕይታ ለማብቃት እስከ 10 አመት ጊዜ እንደፈጀ ኩባንያው ምርቱን ባስተዋወቀበት ወቅት ገልጿል። አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 29፣ 2012 (ኤፍቢሲ) \n \nጥያቄ: በውሃ ላይ የሚሰራ ብስክሌት ያስተዋወቀው ማንታ 5 ኩባንያ የየት ሀገር ድርጅት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የኒውዝላንድ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአሪዞና አሪዞና (Arizona) በምዕራባዊ ዩናይትድ ስቴትስ የሚገኝ ክፍላገር ነው። ኒው ሜክሲኮ ፣ ዩታህ ፣ ኔቫዳ ፣ ካሊፎርኒያ እና ኮሎራዶ ያዋስኑታል። የአሪዞና ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ የ30 ሰው ሴኔት እና የ60 ሰው ምክር-ቤት አለው። የሪፑብሊካን ፓርቲ በስቴቱ ዋነኛው ፓርቲ ነው። በ2002 እ.ኤ.አ. የአሪዞና ስቴት ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ በጀት 14.3 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በጀት ደግሞ 13.8 ቢሊዮን ዶላር ነው። የስቴቱ ሴኔተሮች እና ምክር-ቤት ተወካዮች ለሁለት-ዓመት ጊዜ ላልተወሰነ ብዛት ይመረጣሉ። ከ4 ጊዜ በላይ በተካካይ መመረጥ ግን አይችሉም። የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በአስተዳዳሪ የሚመራ ሲሆን ለ4 ዓመት ሥልጣን ላይ ይቆያል። ያልተወሰነ ጊዜ መወዳደር ሲቻል ከሁለት ጊዜ በላይ ግን በተካካይ መመረጥ አይፈቀድም። \n \nጥያቄ: በአሪዞና ሴናተሮችና የምክር ቤት አባላት ከስንት ጊዜ በላይ በተከታታይ መመረጥ አይችሉም?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ4 ጊዜ በላይ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየሚጠቀሙባቸው ኮምፒውተሮች ከአገልግሎት ጋር ተያይዞ ለተለያዩ ውስጣዊና ውጫዊ ጥቃቶች የመጋለጥ እድላቸው ሰፊ ነው። የኮምፒውተሮችን አጠቃላይ ባህሪ መረዳት፣ በየጊዜው ማሻሻልና መቀየር ያለባቸውን ስርዓቶች በማወቅ መረጃዎች እንዳይጠፉ ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል። ከዚህ አንጻር የኮምፒውተሮችን ደህንነት ለመጠበቅ .ጠቃሚ ፋይሎችን መጠባበቂያ ወይም ባክአፕ መያዝ . የኮምፒውተር ፕሮግራሞች ሥርዓት ለደህንነት ሥጋት እንዳይጋለጡ የኦፕሬቲንግ ሲስተም ክፍተት መሙላት . ፀረ ቫይረስ ሶፍትዌሮችን መጠቀም፣ በየጊዜው መተግበሪያዎችን ማዘመን . ቢያንስ በወር አንድ ጊዜ አጠቃላይ የኮምፒውተር ስርዓት ስካን ማድረግ .አጥፊ ሶፍትዌሮችን የሚከላከሉ ፀረ አጥፊ ሶፍትዌሮችን መጠቀም እና ቢያንስ በወር አንድ ጊዜ ስካን ማድረግ እንዲሁም . የተመጠነ የፋይል አስተዳደር መተግበር እና ዲስኮችን በየጊዜው ማፅዳት መረጃው የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ነው \n \nጥያቄ: የኮምፒውተር ፕሮግራሞች ሥርዓት ለደህንነት ሥጋት እንዳይጋለጡ በምን ያህል ጊዜ ፀረ ቫይረስ ሶፍትዌሮችን መጠቀም አለብን?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ቢያንስ በወር አንድ ጊዜ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nመስከረም 22/2012 በአገሪቷ ወጥ የምርምር ስርአት ለመዘርጋት ብሄራዊ የሳይንስና ምርምር ካውንስል ማቋቋም አስፈላጊ መሆኑን የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ አስታወቀ። በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የተዘጋጀ የሳይንስና ምርምር አውደ ጥናት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል። በአውደ ጥናቱ ላይ ከከፍተኛ ትምህርት ፣ ከምርምር ተቋማትና ከሞያ ማህበራት የተውጣጡ ተመራማሪዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈውበታል። የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጽጌ ገብረ ማርያም እንደተናገሩት በአገሪቷ በሳይንስ ዘርፉ ብቃትና አቅም ያላቸው ተማራማሪዎች ቢኖሩም ምርምሮች ወጥ ባልሆነና ቅንጅት በጎደለው መልኩ እየተከናወኑ ይገኛል። በመሆኑም በተለያዩ የከፍተኛ ትምህርትና የምርምር ተቋማት የሚከናወኑ ምርምሮችን በተቀናጀ መልኩ ለማከናወንና ምርምሮች ላይ ድጋፍና ክትትል የሚያደርግ ብሄራዊ የሳይንስና ምርምር ካውንስል ማቋቋም ያስፈልጋል ብለዋል። የካውንስሉ መቋቋም በአገሪቷ ወጥ የሆነ የምርምር አሰራር ስርአት ለመዘርጋት፣ በዘርፉ ያለውን የሰው ኃይል፣ በጀትና የምርምር መሰረተ ልማቶችን በአግባቡ ለመጠቀም እንደሚያስችል ጠቁመዋል። በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚንስቴር የሳይንስና የምርምር ዘርፍ ጉዳዮች ዳይሬክተር ዶክተር ሰለሞን ቢኖር በበኩላቸው ካውንስል ቢቋቋም የሳይንስ ዘርፍ ለአገሪቷ ዕድገትና ልማት ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው ገልጸዋል። በሳይንስ ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ አገራት ተሞክሮም የካውንስሉን መቋቋም ጠቀሜታ ያረጋግጣል ብለዋል። የሚንስቴሩን አደረጃጀት የመፈተሽና በተገቢው መልኩ የማዋቀር ምርምሮችን ለመከታተል የሚያስችል የመረጃ ስርዓት የመዘርጋት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጸዋል። በአገር ወስጥ የሚታተሙ የምርምር ጆርናሎችን ጥራት ለማሳደግ የሚያስችል የአሰራር ስርዓት የመዘርጋት እየተሰራ መሆኑንም አክለዋል። የዩንቨርስቲ ኢንደሰትሪ ትስስር ያለመጎልበት፣ የምርምር ተቋማት ቅንጅት ክፍተት፣ በሳይንስ ፖሊሲና አገራዊ ልማት አጀንዳ ላይ የምሁራን ተሳትፎ ዝቅተኛ መሆን በዘርፉ ከሚጠቀሱ ችግሮች መሆናቸውንም ዶክተር ሰለሞን አብራርተዋለ። የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚንስትር ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም እንዳሉትም የሳይንስና ምርምር አውደ ጥናቱ ዋነኛ ትኩረት በተለያዩ ዘርፎች የተከናወኑ ምርምሮች ጥራት፣ በጀት፣ ስርጭትና ውጤቶችን ለመዳሰስ ነው። በዘርፉ ያሉ ማነቆዎችን መለየትና በተለያዩ ተቋማት የሚከናወኑ ምርምሮች ተግባራዊነትን መዳሰስም የአውደ ጥናቱ ትኩረት መሆኑን አንስተዋል። ከአውደ ጥናቱ በሳይንስ ዘርፉ ያሉ ጠንካራና ደካማ ጎኖች ተለይተው ዘርፉን ለማሳደግ አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶች ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል። \n \nጥያቄ: የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ማን ይባላሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሞሪታኒያ ሞሪታኒያ (አረብኛ፡ موريتانيا‎) በይፋ የሞሪታኒያ እስላማዊ ሪፐብሊክ፣ በሰሜን ምስራቅ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በምዕራብ ከአትላንቲክ ውቂያኖስ፣ በደቡብ-ምዕራብ ከሴኔጋል፣ በምሥራቅና ደቡብ-ምሥራቅ ከማሊ፣ በሰሜን-ምሥራቅ ከአልጄሪያ፣ እና በሰሜን-ምዕራብ ከምዕራባዊ ሣህራ ጋር ትዋሰናለች። የአገሩዋ ስም የመጣው ከጥንቱ የሞሪታኒያ መንግሥት ነው። ዋና እና ትልቁዋ ከተማዋ ኑዋክሾት ናት። በዛሬው ሞሪታንኒያ በመጀመሪያ የሠፈሩት የባፎር ሰዎች ነበሩ። እነዚህ ስዎች ከዘላን ሕይወት ወደ ግብርና ከተቀየሩት የመጀመሪያ የሰሃራ ሕዝቦች አንዱ ናቸው። ከ5ኛው እስከ 7ኛው ምዕተ ዓመት፣ ባፎሮች በበርበር ህዝቦች ፍልሰት ምክኒያት ተፈናቀሉ። ብዙዎቹ የሞሪታኒያ ሕዝብ በመቆያ ግብርና ቢኖሩም ይሄ ወደ ውጭ አገር ለመላክ አይደለም። በተለይ ወደ ውጭ የሚላከው ብረት፣ ፔትሮሊየም፣ እና ዓሣ ናቸው። ሞሪታኒያ በ12 ዊላያ በሚባሉ ክልሎችና በአንድ የአስተዳደር አካባቢ ተከፍላልች። እነዚህም ክልሎች በ44 ሙጋታ በሚባሉ ክፍሎች ተከፍለዋል። \n \nጥያቄ: ሞሪታንያ ከአልጄሪያ ጋር በየት አቅጣጫ ትዋሰናለች?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በሰሜን-ምሥራቅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየማይዳሰሱ (ኢንታንጀብል) ባህላዊ ቅርሶችን የሚመለከተው የዩኔስኮ አካል በይነ መንግሥታዊው ኮሚቴ 10ኛ ስብሰባውን ከኅዳር 20 እስከ ኅዳር 24 ቀን 2008 ዓ.ም. በናሚቢያ መዲና ዊንድሆክ በተደረገው 10ኛ የዩኔስኮ ጉባዔ ለውሳኔ ከቀረቡት 35 (ሠላሳ አምስት) ባሕላዊ ቅርሶች መካከል የሲዳማ ብሔር የአዲስ ዓመት ዘመን መለወጫ የሆነው ፍቼ ጫምባላላ በዓል በሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ የ2003 የኢንታጀብል ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃ ዓለም አቀፍ ስምምነት መስፈርቶችን አሟልቶ በመገኘቱ አባል አገሮች ውይይት ካደረጉበት በኋላ ፍቼ ጫምባላላ ተመዝግቧል፡፡ ይህም ከመስቀል በዓል ቀጥሎ የኢትዮጵያ ሁለተኛው የማይዳሰስ ዓለም አቀፍ የሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ሆኖ ሕዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም በአገሩ ሰዓት አቆጣጠር 9፡40 በፋይል ቁጥር (01054) በውሳኔ ቁጥር 10.com.10.b.16 ተመዝግቧል፡፡ በ2004 በጀት ዓመት የመስቀል በዓል አከባበርን በዩኔስኮ ማስመዝገብ የሚያስችል የጥናት ሰነድ ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ የተላከ ሲሆን በአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ ከህዳር 23-28 ቀን 2006 ዓ.ም በተካሄደው 8ኛው የዩኔስኮ የኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃ የኢንተርገቨርንመንታል ኮሚቴ መደበኛ ጉባዔ ውሳኔ መሰረት የመስቀል በዓል አከባበር በዩኔስኮ የሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ተካቷል፡፡ በ2006 የበጀት ዓመት የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው ፊቼ ጫምበላላን በሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ለማስመዝገብ የሚያስችል የጥናት ሰነድ (ኖሚኔሽን ፋይል) ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ የተላከውና ህዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም የተመዘገበው የተደረገው ፊቼ ጫምበላላ ሰነዶች በሚከተለው የዩኔስኮ ድረ ገጽ ላይ ለመላው ዓለም ተለቀው ይገኛል፡፡ በተመሳሳይም በ2007 የበጀት ዓመት ኦሮሞ ህዝብ የማንነት መገለጫ የሆነው የገዳ ስርዓትን በሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ለማካተት የሚያስችል የኖሚኔሽን ሰነድ ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ መጋቢት 2007 ዓ.ም ተልኳል፡፡ \n \nጥያቄ: የገዳ ስርአት በዩኔስኮ ለማስመዝገብ ጥናታዊ ሰነድ መቼ ተላከ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ መጋቢት 2007 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአንጎላ አንጎላ፣ በይፋ የአንጎላ ሪፑብሊክ በደቡብ-ምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ስትሆን ከናሚቢያ ፣ ከኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ ፣ እና ከዛምቢያ ጋር ድንበር ትጋራላች። በምዕራብ ጫፍ ከአትላንቲክ ውቅያኖስ ጋር ትገናኛለች። የፖርቹጋል ቅኝ-ተገዥ ነበረች። ነዳጅ እና አልማዝ ከተፈጥሮ ሀብቶቿ የሚመደቡ ናቸው። የአንጎላ የሕግ-አስፈጻሚ ፕሬዝዳንቱን ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩን እና የሚኒስትሮች ካውንስሉን ያጠቃልላል። ሁሉም ሚኒስትሮችና ምክትል ሚኒስትሮች የሚኒስተሮች ካውንስሉን ሲሰሩ በየጊዜው እየተሰበሰቡ ስለተለያዩ የፖለቲካ ጉዳዮች ውሳኔ ይሰጣሉ። የአስራ ስምንቱ ክልሎች መሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚመረጡት። በ1992 እ.ኤ.ኣ. የወጣ ሕገ-መንግስት የመንግስቱን አወቃቀር እና የዜጎችን መብትና ግዴታ ይዘረዝራል። ፕሬዝዳንቱ መንግሥቱ በ2006 እ.ኤ.ኣ. ምርጫ ለማድረግ ዕቅድ እነዳለው ገልጸዋል። ይህ ምርጫ ከ1992 አ.ኤ.ኣ. በኋላ የመጀመሪያው ምርጫ ነው የሚሆነው። አንጎላ ውስጥ ሶስት ዋና ብሔረሰቦች ይገኛሉ። ኦቪምቡንዱ 37% ፣ ኪምቡንዱ 25% ፣ እና ባኮንጎ 13%። ሌሎች ብሔረሰቦች ቾክዌ (ሉንዳ)፣ ጋንጉዌላ፣ ንሀኔካ-ሁምቤ፣ አምቦ፣ ሄሬሮ፣ እና ዢንዱንጋን ያጠቃልላሉ። በተጨማሪም ክልሶች (አውሮፓና አፍሪካዊ) 2% ይሆናሉ። ፖርቱጋሎች አንጎላዊ ካልሆኑ ሰዎች ብዙዎቹ ናቸው። ታሪክ በአንጎላ መጀመሪያ የሠፈሩት የኮይሳን ሰዎች ነበሩ። በባንቱ ፍልሰቶች ጊዜ እነዚህ ሰዎች ወደ ደቡብ አንጎላ ሄዱ። በ1483 እ.ኤ.አ. ፖርቱጋሎች በኮንጎ ወንዝ አጠገብ ሠፈሩ። በ1575 እ.ኤ.አ. ፖርቱጋል ካቢንዳ ጋር በባሪያ ንግድ ላይ ያቶከረ ግዛት መሠረተች። በ16ኛው ክፍለ ዘመን፣ ፖርቱጋል የአንጎላ የባህር ጠረፍን ተቆጣጠረች። በተለያዩ ውሎችና ጦርነቶች የፖርቱጋል ቅኝ-ግዛት አንጎላ ተስፋፋ። የፖርቱጋል መመለሻ ጦርነትን ምክኒያት በማድረግ የደች ሪፐብሊክ ሏንዳን ከ1641 እስከ 1648 እ.ኤ.ኣ. ድረስ ተቆጣጠረች። \n \nጥያቄ: አንጎላ ከአትላንቲክ ውቅያኖስ ጋር የምትዋሰነው በየት አቅጣጫ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በምዕራብ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር፣ በጠላት ወረራ ዘመን የተመሠረተ ድርጅት ሲሆን፤ እስከ አሁን ድረስ ያሉት አዛውንት አባላቱ በዚያው የአምሥት ዓመት ትግል ዘመናት፣ መኳንንቱ፤ የጦር መሪዎቻቸውና ንጉሠ ነገሥቱም ጭምር እነዚያን ወጣት ኢትዮጵያውያን አንጀታቸውን ለረሀብ፤ እግራቸውን ለሾኽ ለጠጠር፤ ግንባራቸውን ለእርሳስ አጋልጠዋቸው በካዷቸው መራር ዘመን፤ ሞትም ቢመጣ እናት አገራችንን አሳልፈን ለጠላት አንሰጥም፤ ነፃነታችንን ለጊዜያዊ ሹመት፣ ሽልማት አንለውጥም ብለው የተጋፈጡ ጀግኖች ናቸው። ደጃዝማች ከበደ ተሰማ፤ “የታሪክ ማስታወሻ” በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ፤ ይህ ማኅበር በአርበኝነት ዘመን በሸዋ ክፍለ ሀገር በ፲፱፻፴፩ ዓ/ም «የጥንታዊት ኢትዮጵያ የጀግኖች ማኅበር» በሚል ስም ተሠይሞ የተቋቋመ ማኅበር እንደነበርና ዓላማውም «የአርበኞችን ክብ በማበረታታትና በየሀገሩ ካሉ አርበኞች ጋር በመላላክ የሚገኘውን ሥራ ፍሬ» እርስ በርስም ሆነ በስደት ላይ ከነበሩት ንጉሠ ነገሥት ጋርም መካፈል እንደነበር ይገልጻሉ። ከመሥራች ማኅበረተኞቹ በከፊሉ፦ ራስ አበበ አረጋይ፤ ወንድማማቾቹ ደጃዝማች ፀሐዩ እና ደጃዝማች ተስፋዬ ዕንቁ ሥላሴ፤ አቶ እምአእላፍ ኅሩይ፤ ደጃዝማች ኃብተ ሥላሴ በላይነህ፤ ደጃዝማች ታከለ ወልደሐዋርያት ይገኙባቸዋል። በመጀመሪያ ጊዜ የነበሩት መሥራቾች ሃያ ዘጠኝ አባላት ሲሆኑ በኋላ ጊዜ ግን ብዙ ማኅበረተኞች እየተጨመሩ የአባሎቹ ቁጥር ከሦስት መቶ በላይ ሆኖ ነበር። የጠላት ኃይል ተሸንፎ የአገሪቱ ነፃነት ከተመለሰ በኋላ፣ አርበኞቹ በየአውራጃውና በየጠቅላይ ግዛቱ ተሰማርተው ስለነበረና ማኅበሩም በመከራው ዘመናት የተቋቋመበት ዓላማ በነፃነት ጊዜ አላስፈላጊ በመሆኑ፤ የጥንታዊት ኢትዮጵያ የጀግኖች ማኅበር ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ ሳያሳይ ብዙ ዓመታት አሳለፈ። ሆኖም በሚያዝያ ወር ፲፱፻፶፬ ዓ/ም ጄኔራል ነጋ ኃይለ ሥላሴ «ከሥራ ባልደረቦቻቸውና ከዕውቅ አገር አፍቃሪዎች ጋራ፥ \"ጥንታዊት ኢትዮጵያ ሀገራዊ የዠግኖች ማኅበርን\" በታደሰ ሀገራዊ ዓላማና በተሻሻለ ደንብ አቋቋሙ። ኾኖም፥ ድርጅቱ እስከ ሰኔ ፲፱ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ/ም ድረስ ከመንግሥት ዕውቅናን ስላላገኘ ሥራው በዚሁ ምክንያት ለጊዜው ተገታ።» ጄኔራል ነጋ በዚህ ዕለት ሕጋዊ ዕውቅና ያገኘውንና ለፍጹም ሰላማዊና ሀገራዊ ዓላማ፤ ለበጎ አድራጎት የተጀመረውን የጥንታዊት ኢትዮጵያ ሀገራዊ የዠግኖች ማኅበር፤ ጠቅላይ ሥራ አመራር ሸንጎ ሊቀ-መንበር ኾነው የማኅበሩን ሥራ በሰፊው በማንቀሳቀስ ባጭር ጊዜ ውስጥ ፬ሺ የፈረሙ አባላትን ከጠቅላላው የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ እንዳስገኙ፥ አሁንም መንግሥታዊ እንቅፋት ገጥሞት ከሕገ-ወጥ በሆነ እርምጃ ፥ የድርጅቱ ጽሕፈት ቤት በጸጥታ ኀይሎች እንዲዘጋ ተደረገ። \n \nጥያቄ: የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር የተዘጋበት ምክንያት ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከመንግሥት ዕውቅናን ስላላገኘ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዳምጠው አየለ ዳምጠው አየለ (23.11. 1944 አ/ም – 27.10. 2006 አ/ም) ባህላዊ የኢትዮጵያ ዘፋኝ ነበር። በሃምሌ 23 1944 አ/ም ከእናቱ ወይዘሮ ሸዋየ ተካና ከአባቱ አየለ ካሰኝ በመራቤቴ ሰሜን ሸዋ ተወለደ። ልጅነቱን በእረኝነት፥ በግብርና እንዲሁም በቆሎ ተማሪነት እንዳሳለፈ ይናገራል። እድሜውም ለትምህርት ሲደርስ ባቅራቢያው በሚገኘው መራኛ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገብቶ ተምሯል። ዳምጠው ህይወቱ እስካለፈችበት ጊዜ ድረስ ለረዥም ጊዜ አብሯት የኖረው ባለቤቱ አልማዝ ይመር ትባላለች። ከአልማዝ ይመር አብዩ ዳምጠውና ቤቴልሄም ዳምጠው የሚባሉ ሁለት ልጆችን አፍርቷል። ዳምጠው መራቤቴ እያለ በየባእላቱ መዝፈን፣ ማቅራራት እንዲሁም መሸለል ይወድ እንደነበር ተናግሯል። በተለይም ጥምቀትን በማድመቅ ይታወቅ ነበር። የ 6ኛ ክፍል ተማሪ እያለ ክፍሌ ሞገስ የሚባል መምህሩ ወደ አዲስ አበባ ይዞት እንደመጣ ይናገራል። ባጋጣሚም የምድር ጦር ማስታወቂያ አውጥቶ ስለነበር ይፈተንና ያልፋል። የምድር ጦር ካምፕ ውስጥም እንዲኖር ይደረጋል። የዘፋኝነት ሙያው በዚህ አጋጣሚ ነበር የጀመረው። ዳምጠው ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማዉና መነሻ የሆነው አበበ ተሰማ እንደሆነ ይናገራል። ዳምጠው አየለ በምድር ጦር ከ 30 አመት በላይ አገልግሏል። የኢትዮዽያ ምድር ጦር በ1927 አ/ም ተመስርቶ በ1983 አ/ም የፈረሰ የሙዚቃ ቡድን ነበር። ዳምጠው በመንግስት ለውጥ ምክንያት እስከፈረሰበት ጊዜ ድረስ አብሮ እንደነበር ይናገራል። ምድር ጦርም እያለ ከነታምራት ሞላ፣ ሲራክ ታደሰ፣ ተክሌ ደስታ ፣ ጥላየ ጨዋቃ፣ ክፍሌ አቦቸር እንዲሁም ሌሎች የጦሩ አባላት ጋር ሰርቷል። ከሌሎች የሙዚቃ ቡድንም ጋር አብሮ ሰርቷል። ለምሳሌ ያክል ከነ ክቡር ጥላሁን ገሰሰ፣ ሙሃሙድ አህመድ፣ ብዙነሽ በቀለ ፣ ሙሉቀን መለስ፣ ፀሃየ ዮሃንስ፣ ቴድሮስ ታደሰ፣ቴድሮስ ካሳሁን እንዲሁም ሌሎችም ጋር ሰርቷል። የዳምጠው አየለ የመጀመሪያ የህትመት ስራው በ1963 አ/ም ሲሆን ወፌ ላላ የሚለው የሸክላ ስራ ነበር። ዳምጠው አየለ ባጠቃላይ 13 ሲዲዎችን ሰርቷል። ዳምጠው አየለ ኖርዌይ ሃገር በስደት ለ 8 አመት ያክል ኖሯል። ኢትዮጵያም ከገባ በኋላ አዲስ አበባ በሚገኘው በቅ/ገብራኤል ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በተወለደ በ 62 አመቱ ሰኔ 27 2006 አ/ም ቀን ህይወቱ አልፏል። የቀብር ስነስርአቱም ወዳጅ፣ ዘመድ እንዲሁም አድናቂዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ዳምጠው አየለ መቼ ተወለደ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በሃምሌ 23 1944 አ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nጋና ጋና በአፍሪካ አትላንቲክ ጠረፍ ላይ የተገኘ አገር ሲሆን ከ24 ሚሊዮን ኗሪዎች በላይ አሉት። የጋና ስራ ቋንቋ እንግሊዝኛ ሲሆን፣ ሌሎች ኗሪ ቋንቋዎች በተለይም ትዊኛ (አካንኛ) በሰፊ ይነገራሉ። የ«ጋና» ስያሜ በታሪክ የድሮ «ጋና መንግሥት» ወይም «ዋጋዱጉ መንግሥት» ለማክበር በ1949 ዓም ተመረጠ። እንዲያውም ያው መንግሥት እስከ 1068 ዓም ድረስ ከጋና ወደ ስሜን-ምዕራብ በአሁኑ ማሊ ይገኝ ነበር እንጂ የዛሬውን ጋና መቸም አልገዛም። «ጋና» በትክክል የዋጋዱጉ መንግሥት አለቆች ማዕረግ ሆኖ ነበር። ዋጋዱጉ መንግሥት በ1068 ዓም ግድም ከወደቀ ቀጥሎ፣ የአካን ብሔሮች ከዚያው ፈልሰው በዛሬው ጋና ሠፈሩና መጀመርያ ግዛቶችን መሠረቱ። ከ1662 እስከ 1949 ዓም ድረስ የአሻንቲ መንግሥት ባካባቢው ቆየ፤ በ1894 ዓም ይህ የብሪታንያ አሻንቲ ጥብቅ ግዛት ሆነ። ከ1949 ዓም አስቀድሞ የዩናይትድ ኪንግደም ጥገኛ ግዛት ሲሆን በወርቅ ሀብቱ ምክንያት «የወርቅ ጠረፍ ጥገኛ ግዛት» (ጎልድ ኮስት ፕሮቴክቶሬት) በመባል ይታወቅ ነበር። ከ1984 ዓም ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ እና ፓርላሜንታዊ መንግሥት ኖሮታል። አብዛኞቹ ኗሪዎች (70%) በተለይ በደቡቡ ክርስቲያን ሲሆኑ፣ በተለይ በስሜኑ 16% የእስልምና ተከታዮች ናቸው። የተረፉትም የኗሪ አረመኔነትን እምነቶች ይከተላሉ። የጋና ዋና ምርቶች ካካዎ፣ ዘይት፣ አልማዝ ናቸው። በአለሙ ከሁሉ ትልቅ የሆነው ሠው ሰራሽ ሐይቅ፣ ቮልታ ሐይቅ፣ በጋና ይገኛል። እግር ኳስ ከሁሉ የተወደደው እስፖርት ነው። የጋና አበሳሰል በተለይ በኮቤ፣ ጐርጠብ፣ የስኳር ድንች፣ ባቄላ፣ በቆሎ፣ ኦቾሎኒ፣ ባሚያና ሩዝ ይሠራል። \n \nጥያቄ: በጋና የሙስሊሞች ብዛት በመቶኛ ምን ያህል ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 16% ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጮቄ አስደሳቹ ስፊውና ማራኪው ጮቄ በቢቡኝ ወረዳ ውስጥ ከሚገኙ የተፈጥሮ የቱሪስት መስህብ ሃብቶች መካከል አንዱና ዋነኛው ሲሆን ወረዳዋ በስፋት የምትታወቅበት አስደናቂና ከፍተኛ የሆነ ተራራማ ቦታ ነው። ጮቄ ከወረዳዋ ድጓ ፅዮን ከተማ 10 ኪ/ሜ ፣ ከዞን ዋና ከተማ ከደ/ማርቆስ 61 ኪ.ሜ፣ ከክልል ዋና ከተማ ከባህር ዳር 325 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። ጮቄ በእፅዋት ብዝሀነት የታደለና ከ85 በላይ አገር በቀል እፅዋት የሚበቅልበት ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ዋና ዋናዎቹ፡- ጅባራ፣ ጓሳ፣ አስታ፣ ቅርቅሃ፣ አምጃ፣ አሸንግድየ፣ ዝግባ/ግምይ/ ተጠቃሽ ናቸው። አባይን ያረገዘ ጮቄ አካባቢው የአባይ ወንዝ የውሃ ምንጭ ሲሆን የአባይ ተፋሰስ የውሃ ማማ እንደሆናና ከአባይ 9.5% ተፋሰስ ድርሻ ያለው ተራራማ የውሃ ስፍራ ነው። እንደ አጠቃላይ ሲታይ የምስራቅ አፍሪካ የውሃ ማማ (East Africa water Tower) የሆነው ጮቄ የአባይ ገባር የሆኑ 273 ትናንሽ የውሃ ጅረትና ከ23 በላይ የሚሆኑ ታላላቅ ወንዞች መፍለቂያ ነው። ከታላላቅ ወንዞች መካከል እናት ሙጋ፣ ግልገል ሙጋ፣ ተምጫ፣ ዝምብል፣ ትልቁ አብያ፣ ትንሹ አብያ፣ ጨሞጋ፣ ጌደብ፣ ጥጃን፣ ጠፍ፣ ጦመ፣አዝዋሪ፣ ተጠቃሽ ሲሆኑ ከነዚህም ቢቡኝ ወረዳ ውስጥ የሚገኙት፡- ዝምብል፣ ትልቁ አብያና ትንሹ አብያ ናቸው። የጮቄ ተራራ ከባህር ወለል በላይ 4088 ሜትር አካባቢ ከፍታ ያለው በመሆኑ የጎጃም ጣራ ( The roof of Gojjam) በመባል ይታወቃል። የጮቄ ተራሮች በምስራቅ ጎጃምና በምዕራብ ጎጃም ዞኖች ዘጠኝ ወረዳዎች ክልል ውስጥ የሚገኝ ሲሆን ጠቅላላ ስፋቱም 53558 ሄክታር በላይ እንደሚደርስ ጥናቶች ያመለክታሉ። ጮቄ በጣም ሰፊ ከመሆኑም የተነሳ ገና ብዙ ያልታወቁ ዋሻዎች፣ ጥንታዊ መኖሪያዎችና ያልተዳሰሱ አስደሳች የተፈጥሮ መስህቦች አሉት ፡፡ የጮቄ አካባቢ፡- በስተ ምስራቅ እነማይና እናርጅ እናውጋ፣ በስተ ሰሜን ምስራቅ 2 እጁ እነሴ በስተ ሰሜን ቢቡኝ በምዕራብ ማቻከል፣ በስተ ደቡብ ስናን እንዲሁም በስተ ደቡብ ምስራቅ ደባይ ጥላት ግን ወረዳዎች ያዋስናል። ይህ ተራራ በዋናነት በቢቡኝ ወረዳ ውስጥ የሚገኙ አምስት ቀበሌዎችን ያቀፈ ነው፡፡ እነሱም፡- አሩሲ መሰሳቢያ ደድ ደብረ ፅዮን ደብረ ጊዮርጊስና ወንበር ቅዱስ ዮሐንስ ቀበሌዎች በዋናነት ይገኛሉ፡፡ \n \nጥያቄ: የጮቄ ተራራ ስሙ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የጎጃም ጣራ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበደቡብ ሱዳን መከላከያ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጀኔራል ጆንሰን ጁማ ኡኮት የተመራ ልዑክ አዲስ አበባ ገብቷል፡፡ ልዑኩ አዲስ አበባ ሲገባ በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጀኔራል ብርሀኑ ጁላ እና በሌሎች ከፍተኛ የመከላከያ አዛዦች አቀባበል ተደርጎለታል፡፡ በቆይታቸውም በሁለቱ ሀገራት የመከላከያ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚመክሩ ከመከላከያ ሰራዊት ገጽ የተገኘው መረጃ አመላክቷል፡፡ \n \nጥያቄ: ጄነራል ብርሃኑ ጁላ በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ውስጥ ኃላፊነታቸው ምንድን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዓለማየሁ ቴዎድሮስ ልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ የዳግማዊ ዓፄ ቴዎድሮስ እና የወይዘሮ ጥሩወርቅ ውቤ ልጅ ነበር። በ1860 ዓ.ም አፄ ቴዎድሮስ ከእንግሊዞች ጋር ባደረጉት ጦርነት ልጃቸው ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ ወደ እንግሊዝ ሀገር ተወስዶ ነበር፡፡ ልዑል አለማየሁ ሚያዚያ 5 ቀን 1853 ዓ.ም በደብረ ታቦር ከተማ ነበር ውልደቱ፡፡ በልዑሉ ውልደት የተደሰቱት አፄ ቴዎድሮስም በእለቱ መድፍ ያስተኮሱ ሲሆን 500 ያህል እስረኞችንም ፈትተዋል፡፡ ልዑል አለማየሁ እንግሊዞች እጅ ከገባ በኋላ ከእድሜው ለጋነት የተነሳ የሚጠብቀው እና የሚንከባከበው ሰው ሊኖር ግድ ነበር፡፡ ይህንን የተረዳው ጀነራል ናፔር ካፕቴን ስፒዲ የተባለን ሰው የአለማየሁ ጠባቂ እንዲሆን መደበው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ካፕቴኑ የአማርኛ ቋንቋን አቀላጥፎ መናገሩ ነበር፡፡ በተጨማሪም አለቃ ዝርዓት እና አቶ ገብረመድህን የተባሉ ሁለት ኢትዮጵዊያን ሞዚቶች እና አጫዋቾች ተመረጡለት፡፡ አለማየሁ ከጠባቂው ስፒዲ ጋር ፌሬዝ በተባለችው መርከብ ተሳፍሮ በ1860 ዓ.ም. ወደ እንግሊዝ አቀና፡፡ በመርከቢቱ ላይ በነበራቸውም ቆይታ ስፒዲ እና አለማሁ እጅግ የጠበቀ ወዳጅነትን መስርተው ነበር፡፡ ስፒዲ በሄደበት ቦታ ሁሉ አለማየሁን ማስከተል ያዘወትር ነበር፡፡ ይህንን የሁለቱን ፍቅር ያየው ጀነራል ናፒየርም ኢትዮጵያውያን ሞግዚቶቹ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ይልቁንም የአለማየሁን ሀላፊነት ሙሉ በሙሉ ካፕቴን ስፒዲ እንዲረከብ ስለወሰነ ሁለቱ ሞግዚቶች ጉዞው ተጠናቆ እንግሊዝ ሀገር ሳይደርሱ ከስዊዝ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ተደረገ፡፡ ከሶስት ወራት የመርከብ ላይ ጉዞ በኃላ አለማየሁ እንግሊዝ ሀገር ደረሰ፡፡ \n \nጥያቄ: የዳግማዊ ቴዎድሮስና የወይዘሮ ጥሩወርቅ ውቤ ልጅ ማን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአቡነ ጴጥሮስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ቤተክርስቲያን በአደራነት የሰጠቻቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ሕዝበ ክርስቲያኑን በጸሎታቸው እየደገፉ በትምህርታቸው እያበረቱ በማስተዳደር ላይ እንዳሉ በ፲፱፳፰ ዓ.ም. አረመኔው የኢጣልያ ፋሺስት በግፍ ሀገራችንን ለመውረር ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት በማለት ባሕርን አቋርጦ መጣ፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሀገር በመጣ ወራሪ ቀጥተኛ ተጠቂናትና ሊቃውንቷ፣ ገዳማትና አድባራቷ እንዲሁም ንዋያተ ቅድሳቷ በወራሪው የኢጣልያ ኃይል ይጨፈጨፉና ይቃጠሉ ገቡ ፡፡ ይህ ግፍ በዕውቀት ኮትኩታ ባሳደገቻቸው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ሲፈጸም ያዩት ብፁዕነታቸው ወራሪውን ኃይል ከኢትዮጵያውያኑ አርበኞች ጋር በመሆን በጸሎት ሊዋጉት ወሰኑ፡፡ ይሁን እንጂ ጠላት በመላ ከተማዋ ባሰማራቸው በርካታ ባንዳዎች መካከል ብፁዕነታቸው እንዳሰቡት ሊንቀሳቀሱ አልቻሉም፡፡ በመጨረሻ እዚሁ ከተማ ተሰውሬ መኖር አልፈልግም፤ ወደ ገጠር ፊቴን አልመልስም በማለት ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም በወቅቱ የኢጣሊያ እንደራሴ ለነበሩት ራስ ኃይሉ እጃቸውን ሰጡ፡፡ እራስ ኃይሉም ወዲያውኑ ለግራዚያኒ አሳልፈው ሰጧቸው፡፡ ሐምሌ 22 ቀን 1928 አቡነ ጴጥሮስ ተይዘው ወደ ግራዚያኒ ቀረቡ ፡፡ ጠላት ድል ተደርጎ ሀገራችን ነፃነቷን ከተቀዳጀት በኋላ የብፁዕነታቸውን አኩሪ ታሪክ ትውልድ ሲያዘክርላቸው እንዲኖር መታሰቢያ ይሆናቸው ዘንድ በግርማዊ ቀዳማዊ ንጉሠ ነገሥት አሳሳቢነት ሐምሌ 16 ቀን 1938 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ እምብርት ሐውልት ቆሞላቸዋል፡፡ ከድል በኋላ የብፁዕነታቸ ሐውልት ተመርቆ የቤተ መንግሥቱም ሆኑ የቤተ ክህነቱ ባለሥልጣናት አበባ ጉንጉን ከሐውልቱ ሥር ሲያስቀምጡ ከቤተ ክህነት ካስቀመጡት አባቶች አንዱ በ1921 ዓ.ም አብረዋቸው የተሾሙት ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ ነበሩ፡፡ ትውልድ ሁሉ ለሀገር ክብርና ለነጻነት በተከፈለው፡፡ የብዕፁነታቸው ሕይወት እንዲማርበትና ሕያው ምስክር ሆኖ እንዲኖር የቆመላቸውን ሐውልት ኢትዮጵያዊያን ሁሉ በክብር ይጠብቁታል ፡፡ የእኝህን ታላቅና ቅዱስ ሰማዕት አባት ክብርና ተጋድሎ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ከአምስት ዓመት በፊት ቅዱስ /ሰማዕት/ ብሎ በማጽደቅ በስማቸው በቅድስና ማዕረግን ሰጥቶ በስማቸው ታቦት ተቀርጾ ቤተክርስቲያን እንዲሰራላቸው ወስኗል ፡፡ ይህም በተወለዱበት በሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሃገረሰብከት በፍቼ ከተማ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ተግባራዊ ሆኗል፡፡ ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ፣ አርበኛ፣ ጀግና፣ ጳጳስ፣ ሰማዕት ቅዱስም የሆኑ አባት ናቸው ፡፡ \n \nጥያቄ: አቡነ ጴጥሮስ መቼ ለግራዚያኒ ቀረቡ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሐምሌ 22 ቀን 1928 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nማርክ ትዌይን ሳሙኤል ላንግሆርን ክሌመንስ ወይም በብእር ስሙ ማርክ ትዌይን አሜሪካ ካፈራቻቸው ድንቅ ጸሃፍት መካካል የሚመደብ ደራሲ ነው። ትዌይን በኖቬምበር 1835 ዓ.ም. ሚዙሪ በተባለችው የአሜሪካ ግዛት ተወለደ። 18 ዓመት እስኪሞላው ድረስ ከቤተሰቦቹ ጋር የኖረው ሃኒባል በተባለች እና ሚሲሲፒ ላይ በተቆረቆረች ትንሽ ከተማ-አከል ቦታ ነው። አባቱ በ1847 ሲሞት ትዌይን ትምህርቱን በማቋረጥ በማተሚያ ቤት ውስጥ በሰልጣኝነት ተቀጠረ። ይህን ስራውን በ1857 በመተው የእንፋሎት ጀልባ ነጂ በመሆን መስራት ጀመረ። በዚሁ ስራ በቆየባቸው አመታት ነው ኋላ ላይ አድናቆትን ላተረፉለት የስነ-ጽሁፍ ስራዎቹ የሚሆኑትን እውቀቶች ለማሰባሰብ የበቃው። እሱ ራሱም እንዳለው በዚሁ ስራ ላይ ነው \"ማንኛውንም በልብ-ወለድ፣ በግለ-ታሪክም ሆነ በታሪክ ላይ ሊገኙ የሚችሉ የሰው ባህርያትን\" ሊያጠና የበቃው። በ1861 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የእርስ-በርስ ጦርነት በመቀስቀሱ ምክንያት ማንኛውም አይነት የመርከብ ላይ ጉዞ ሲስተጓጎል ትዌይንም ስራውን ለመልቀቅ ተገዷል። ከዚህ በኋላም በውትድርና ወዶ-ገብነት፣ በወርቅ ማእድን ፈላጊነት፣ በጋዜጠኝነት ወዘተ ስረቷል። በ1869 ዓ.ም የመጀመሪያ ዋነኛ ስራው የሆነውን \"The Innocents Abroad\" ለማሳተም በቃ። ይኽ ድርሰት ክሌመንስ ራሱ በአውሮፓ እና በእየሩሳሌም ባካሄዳቸው ጉብኝቶች ላይ የተመሰረተ ነው። በ1870 ዓ.ም ኦሊቭያ ላንግዶንን በማግባት ኑሮውን ኮኔቲከት በተባለችው ግዛት አድርጓ በዛው ለ17 ዓመታት ኖሯል። በነዚህ 17 ዓመታት ነው አድናቆት ያተረፉለት ስራዎቹን ማለትም \"Roughing It\"፣ \"The Adventures of Tom Sawyer\"፣ Life on the Mississippi\"፣ እና ከሁኡ የላቀ የተባለለት ድርሰቱን \"The Adventures of Huckleberry Finn\"ን ያሳተመው። ትዌይን በ1910 ዓ.ም አርፎ ሬዲንግ፣ ኮኔቲከት ውስጥ በድኑ አርፏል። \n \nጥያቄ: ማርክ ትዌይን ሳሙኤል ላንግሆርን ክሌመንስ የመጀመሪያ ስራው የሆነው የመጽሐፍ ርዕሱ ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ The Innocents Abroad ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nፍቅር እስከ መቃብር ፍቅር እስከ መቃብር በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. በደራሲ ሀዲስ አለማየሁ የቀረበ ልብ ወለድ ሲሆን ሰብለ ወንጌል እና በዛብህ የሚባሉ የሁለት ገፀ ባህሪያትን ፍቅር ይተርካል። ይህ ድርሰት ከሌሎች ልብወለድ ሥራዎች ለየት የሚያደርገው ደራሲው ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ በፊደል አጠቃቀም ላይ ለውጥ አድርገው በማቅረባቸው ነው። ይኸውም ለምሳሌ ያህል ሦስት «ሀ»ዎች፣ ሁለት «ሰ»ዎች፣ ሁለት «ኣ»ዎች የመሳሰሉትን እንደ አንድ ወይም የመጀመሪያውን ብቻ በመያዝ ነው። በተጨማሪም ጠብቀው በሚነገሩ ቃላት ላይ ከላይ አንድ ነጥብ በማስቀመጥ ይታወቃሉ።ሀዲስ ኣለማየሁ በኢትዮጵያ ስነ-ፅሑፍ የራሳቸው ትልቅ አሻራ አኑረው ያለፉ አንጋፋ ደራሲ ናቸው። የታሪኩ ማጠቃለያ በዛብህ‌ ‌ጎጃም‌ ‌ማንኩሳ‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከእናቱ‌ ‌ከውድነሽ‌ ‌በጣሙና‌ ‌ከአባቱን‌ ‌ከቦጋለ‌ ‌መብራት‌ ‌ይወለዳል።‌ ‌በሽታ‌ ‌ይበዛበትና‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይባላል።‌ ‌እናቱ‌ ‌ከበሽታው‌ ‌እንዲድን‌ ‌ስእለት‌ ‌ይሳላሉ።‌ ‌ዕድል‌ ‌ሆኖ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይተርፋል፤‌ ‌አድጎ‌ ‌ጎበዝ‌ ‌ልጅ‌ ‌ይሆናል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌በሽታ፣‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ዕውቀትና‌ ‌ፍቅር‌ ‌(የሰው‌ ‌መውደድ)‌ ‌ይበዛበታል።‌ ‌በወጣትነቱ‌ ‌ይቀድስና‌ ‌ለቤተሰቡ‌ ‌ገንዘብ‌ ‌ማምጣት‌ ‌ይጀምራል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌የስእለት‌ ‌ልጅ‌ ‌መባልን‌ ‌አይጠላም‌ ‌ነበር።‌ ‌ሲያድግ‌ ‌ግን‌ ‌ትርጉሙን‌ ‌በመረዳቱ‌ ‌ነጻነቱን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌ዲማን‌ ‌ጥሎ‌ ‌ወደደብረ‌ ‌ወርቅ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌እዚያም‌ ‌ከእመት‌ ‌ጠጂቱ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይጠጋል።‌ ‌ትንሽ‌ ‌ዜማና‌ ‌ቅኔም‌ ‌ይማራል።‌ ‌ደብተራ‌ ‌በየነ‌ ‌መጥቶ‌ ‌የወላጆቹን‌ ‌ሞት‌ ‌ሲያረዳው‌ ‌ወደዲማ‌ ‌ይወርዳል።‌ ‌በተክለ‌ ‌አልፍአው‌ ‌በዓል‌ ‌በመልካም‌ ‌ድምጹ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻንና‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትን‌ ‌ያወድሳል።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻም‌ ‌የሰብለ‌ ‌መምህር‌ ‌አድርገው‌ ‌ይቀጥሩታል።‌ ‌ሰብለና‌ ‌በዛብህ‌ ‌የሕይወት‌ ‌ገጠመኞቻቸው‌ ‌በመጠኑ‌ ‌ስለሚመሳሰል‌ ‌ይግባባሉ።‌ ‌በመሃል‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌አሰጋኸኝ‌ ‌ሰብለን‌ ‌በፈት‌ ‌ወግ‌ ‌አገባለሁ‌ ‌በማለቱ‌ ‌በርሱና‌ ‌በፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌መካከል‌ ‌ጥል‌ ‌ተፈጠረ፤‌ ‌ሆኖም‌ ‌በሃይማኖት‌ ‌ጣልቃገብነት‌ ‌ሳይዋጉ‌ ‌ቀሩ።‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከባላገሮች‌ ‌ጋራ‌ ‌በግብር‌ ‌ጉዳይ‌ ‌ተጣሉ።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ተማርከው‌ ‌ሳለ‌ ‌የበዛብህንና‌ ‌የሰብለወንጌልን‌ ‌የፍቅር‌ ‌ዜና‌ ‌ይሰማሉ።‌ ‌ወዲያውም‌ ‌መጥተው‌ ‌ሰብለን‌ ‌በሌሊት‌ ‌ያስሯታል።‌ ‌የሰብለ‌‌አጎት‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ሁለቱን‌ ‌ለማስመለጥ‌ ‌ወጣ፣‌ ‌ወረደ።‌ ‌የዕጣ‌ ‌ነገር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ግን‌ ‌ሳይሳካ‌ ‌ቀረ።‌ ‌በዛብህ‌ ‌ግን‌ ‌በግራጌታ‌ ‌ቀለመወርቅና‌ ‌በጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጥረት‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌በራጉኤል‌ ‌ቤተክርስቲያንም‌ ‌የቅኔ‌ ‌መምህር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ይቀጠራል።‌ ‌ባደረጉላቸው‌ ‌ውለታ‌ ‌ምክንያት‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌ሰብለን‌ ‌ለፊታውራሪ‌ ‌ታፈሰ‌ ‌ሊድሯት‌ ‌ይሞክራሉ።‌ ‌የሰብለን‌ ‌አቋም‌ ‌አውቀው‌ ‌አባ‌ ‌ተክለሃይማኖት‌ ‌በተባሉ‌ ‌መነኩሴ‌ ‌ያስጠብቋቷል።‌ ‌መነኩሴው‌ ‌ግን‌ ‌ሰክረው‌ ‌ሰብለ‌ ‌ታመልጣለች።‌ ‌ፍለጋ‌ ‌ሲሄዱ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከፈረስ‌ ‌ላይ‌ ‌ተወርውረው፣‌ ‌ተንኮታክተው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትም‌ ‌ቤተክርስቲያን‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከደረጃ‌ ‌ላይ‌ ‌ተንሸራትተው‌ ‌ወድቀው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ሰብለ‌ ‌ደግሞ‌ ‌በዛብህን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌መነኩሴ‌ ‌መስላ‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ትሄዳለች።‌ ‌ደርሳም‌ ‌በዛብህ‌ ‌አለመኖሩን‌ ‌ትሰማና‌ ‌ጎሃጽዮን‌ ‌ትወርዳለች።‌ ‌በዚያም‌ ‌በዛብህ‌ ‌ተደብድቦ፣‌ ‌ነፍስ‌ ‌ውጪ‌ ነፍስ‌ ‌ግቢ‌ ‌አይነት‌ ‌ሁኔታ‌ ‌ላይ‌ ‌ሳለ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌እንደምንም‌ ‌ብለው‌ ‌ሥጋ‌ ‌ወደሙን‌ ‌ይቀበላሉ።‌ ‌ጥቂት‌ ‌ቆይቶ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይሞታል።‌ ‌ሰብለም‌ ‌መንኩሳ፣‌ ‌የበዛብህን‌ ‌አስከሬን‌ ‌ባጠገቧ‌ ‌አድርጋ‌ ‌ስትኖር‌ ‌ከጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጋራ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌ጉዱ‌ ‌የተሰኘው‌ ‌ካሳ‌ ‌ዳምጤም‌ ‌እርሷ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይቀመጣል።‌ ‌አስራ‌ ‌አምስት‌ ‌ቀናት‌ ‌አንድ‌ ‌ላይ‌ ‌ይኖሩና‌ ‌ሰብለ‌ ‌የልብ‌ ‌በሽታዋ‌ ‌ተነሥቶባት‌ ‌ትሞታለች፣‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ከበዛብህ‌ ‌አጠገብ‌ ‌ያስተኛታል።‌ ‌በሦስተኛው‌ ‌አመት‌ ‌ጉዱም‌ ‌አረፍተ‌ ‌ዘመን‌ ‌ይገታዋል።‌ \n \nጥያቄ: ፍቅር እስከ መቃብር ደራሲ ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዳምጠው አየለ ዳምጠው አየለ (23.11. 1944 አ/ም – 27.10. 2006 አ/ም) ባህላዊ የኢትዮጵያ ዘፋኝ ነበር። በሃምሌ 23 1944 አ/ም ከእናቱ ወይዘሮ ሸዋየ ተካና ከአባቱ አየለ ካሰኝ በመራቤቴ ሰሜን ሸዋ ተወለደ። ልጅነቱን በእረኝነት፥ በግብርና እንዲሁም በቆሎ ተማሪነት እንዳሳለፈ ይናገራል። እድሜውም ለትምህርት ሲደርስ ባቅራቢያው በሚገኘው መራኛ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገብቶ ተምሯል። ዳምጠው ህይወቱ እስካለፈችበት ጊዜ ድረስ ለረዥም ጊዜ አብሯት የኖረው ባለቤቱ አልማዝ ይመር ትባላለች። ከአልማዝ ይመር አብዩ ዳምጠውና ቤቴልሄም ዳምጠው የሚባሉ ሁለት ልጆችን አፍርቷል። ዳምጠው መራቤቴ እያለ በየባእላቱ መዝፈን፣ ማቅራራት እንዲሁም መሸለል ይወድ እንደነበር ተናግሯል። በተለይም ጥምቀትን በማድመቅ ይታወቅ ነበር። የ 6ኛ ክፍል ተማሪ እያለ ክፍሌ ሞገስ የሚባል መምህሩ ወደ አዲስ አበባ ይዞት እንደመጣ ይናገራል። ባጋጣሚም የምድር ጦር ማስታወቂያ አውጥቶ ስለነበር ይፈተንና ያልፋል። የምድር ጦር ካምፕ ውስጥም እንዲኖር ይደረጋል። የዘፋኝነት ሙያው በዚህ አጋጣሚ ነበር የጀመረው። ዳምጠው ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማዉና መነሻ የሆነው አበበ ተሰማ እንደሆነ ይናገራል። ዳምጠው አየለ በምድር ጦር ከ 30 አመት በላይ አገልግሏል። የኢትዮዽያ ምድር ጦር በ1927 አ/ም ተመስርቶ በ1983 አ/ም የፈረሰ የሙዚቃ ቡድን ነበር። ዳምጠው በመንግስት ለውጥ ምክንያት እስከፈረሰበት ጊዜ ድረስ አብሮ እንደነበር ይናገራል። ምድር ጦርም እያለ ከነታምራት ሞላ፣ ሲራክ ታደሰ፣ ተክሌ ደስታ ፣ ጥላየ ጨዋቃ፣ ክፍሌ አቦቸር እንዲሁም ሌሎች የጦሩ አባላት ጋር ሰርቷል። ከሌሎች የሙዚቃ ቡድንም ጋር አብሮ ሰርቷል። ለምሳሌ ያክል ከነ ክቡር ጥላሁን ገሰሰ፣ ሙሃሙድ አህመድ፣ ብዙነሽ በቀለ ፣ ሙሉቀን መለስ፣ ፀሃየ ዮሃንስ፣ ቴድሮስ ታደሰ፣ቴድሮስ ካሳሁን እንዲሁም ሌሎችም ጋር ሰርቷል። የዳምጠው አየለ የመጀመሪያ የህትመት ስራው በ1963 አ/ም ሲሆን ወፌ ላላ የሚለው የሸክላ ስራ ነበር። ዳምጠው አየለ ባጠቃላይ 13 ሲዲዎችን ሰርቷል። ዳምጠው አየለ ኖርዌይ ሃገር በስደት ለ 8 አመት ያክል ኖሯል። ኢትዮጵያም ከገባ በኋላ አዲስ አበባ በሚገኘው በቅ/ገብራኤል ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በተወለደ በ 62 አመቱ ሰኔ 27 2006 አ/ም ቀን ህይወቱ አልፏል። የቀብር ስነስርአቱም ወዳጅ፣ ዘመድ እንዲሁም አድናቂዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ዳምጠው አየለ ከኢትዮጵያ ውጭ የት አገር ኖሯል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ኖርዌይ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሄርበርት ሁቨር (1866 - 1957 ዓ.ም.) ከ1921 እስከ 1925 ዓ.ም. ድረስ 31ኛ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ነበሩ። የሁቨር ቤተሠብ ከስዊስና ጀርመን ትውልድ ሲሆን ሃይማኖቱ የክዌከር ('የሚንቀጠቀጡ' ማለት ነው) ቤተ ክርስቲያን ነበረ። ወላጆቹ በልጅነቱ ጊዜ ካረፉ አንስቶ ድሃ አደግ ሆነና ከአጎቱ ጋር አደገ። በስታንፎርድ ዩኒቨርሲቴ መጀመርያ ክፍል በመሆኑ ትምህርቱ በነጻ ተቀበለ። ከዚያ በላይ የዩኒቬርሲቴው የቤስባልና የፉትቦል ቡድኖች አለቃ ሆነ። በ1887 ዓ.ም. የጂዮሎጂ ዲግሪ ይዘው ተመረቁ። ለ20 ዓመት የማዕደን ሊቅ ሲሆኑ እንኳን በአውስትራልያና በእንግሊዝ በማዕደን ዘርፍ የሠሩት ሥራ ስመ ጥሩ ሆነ። መጀመርያው ታላቅ አለማዊ ጦርነት በ1906 ዓ.ም. በጀመረበት ወቅት ሁቨር ከራሳቸው ኪስ ለጋሥነት አውጥተው 120,000 አሜሪካውያን ቱሪስቶችና ሠራተኞችን ከአውሮፓ ወደ አገራቸው አስመለሷቸው። ከዚያ በጀርመኖች በተወረረው በቤልጅግ ውስጥ የኖሩት ረሃብተኞች ምግብ እንዲደርሳቸው ብዙ አደረጉ። በዚህ አይነት ሥራ በጦርነት ጊዜ የሁቨር ስም ጀግና እንዳለው ሁኔታ በመገኘት ላይ ሄዶ ነበር። ጦርነቱም ከተጨረሰ በኋላ ለምሥራቅ አውሮጳ ድሃ ሕዝብ እስከ ሩስያም ድረስ በረሃብ ላሉት ሰዎች ምግብ አደረሷቸው። \n \nጥያቄ: ሄርበርት ሁቨር ወላጆች ከሞቱ በኃላ ማን ነው ያሳደገው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከአጎቱ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \n67ኛው ግጥም በጃዝ ምሽት የፊታችን ረቡዕ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በራስ ሆቴል ይካሄዳል፡፡ አንጋፎቹ ገጣሚያን ነቢይ መኮንን፣ ተፈሪ አለሙ፣ ዶ/ር ሙሉአለም ተገኝወርቅ፣ መርድ ተስፋዬና ቤዛ ትዕዛዙ የግጥም ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን አርቲስት ሽመልስ አበራና እታፈራሁ መብራቱ አጭር ተውኔት ያቀርባሉ ተብሏል፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ምሁር የሆኑት አቶ አበባው አያሌው ዲስኩር እንደሚያቀርቡ ታውቋል፡፡ \n \nጥያቄ: አቶ አበባው አያሌው በየት ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህርነት ይሰራሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nናሚቢያ ናሚቢያ በደቡብ-ምዕራብ አፍሪቃ የምትገኝ ሀገር ናት። በምዕራብ በአትላንቲክ ውቅያኖስ፣ በስሜን በአንጎላና በዛምቢያ፣ በምስራቅ በቦትስዋና፣ በደቡብም በደቡብ አፍሪቃ ትካለላለች። በ1982 አመተ ምኅረት ነጻነትዋን ከደቡብ አፍሪቃ ስላገኘች በጣም አዲስ አገር ነች። ዋና ከተማዋ ዊንድሁክ ነው። የናሚቢያ በረኅ አውራጃ ከጥንት ጀምሮ በሳን (ቡሽማን)፣ በዳማራና በናማቋ ሕዝቦች ተሰፈረ። በ14ኛው መቶ ዘመን፣ የባንቱ ወገኖች ባስፋፉ ጊዜ አገሩን ሠፈሩ። ክልሉ ግን ከ19ኛው መቶ ዘመን በፊት በአውሮጳውያን አልተዘለቀም። በዚያን ጊዜ ጀርመን ደቡብ-ምዕራብ አፍሪቃ ተብላ አገሪቱ የጀርመን ቅኝ ግዛት ሆነች። ዳሩ ግን ዋልቪስ በይ የተባለው ትንሽ ወደብ ብቻ የእንግሊዝ ግዛት ነበር። \n \nጥያቄ: ናሚቢያ ከደቡብ አፍሪካ ነጻነቷን ያገኘችው መቼ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ1982 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየ2014 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ የ2014 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ ፳ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሲሆን ከሰኔ ፭ እስከ ሐምሌ ፮ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. በብራዚል ይካሄዳል። ብራዚል ይህን ውድድር ስታዘጋጅ ይሄ ሁለተኛ ጊዜዋ ነው። ፊፋ የ2014 እ.ኤ.አ. ውድድር በደቡብ አሜሪካ እንደሚካሄድ በ2007 እ.ኤ.አ. ካወጀ በኋላ ብራዚል ያለማንም ተቀናቃኝ አዘጋጅ አገር ሆና ተመርጣለች። የ፴፩ አገራት ብሔራዊ ቡድኖች ከጁን 2011 እ.ኤ.አ. ጀምሮ የተካሄዱ የማጣሪያ ውድድሮችን በማለፍ ከብራዚል ጋር በመጨረሻው ውድድር ላይ ለመሳተፍ በቅተዋል። በጠቅላላው ፷፬ ጨዋታዎች በ፲፪ ከተማዎች ውስጥ በሚገኙ አዲስ የተገነቡ ወይም የተሻሻሉ ስታዲየሞች ይከናወናሉ። በዓለም ዋንጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የጎል ላይን ቴክኖሎጂ በጥቅም ላይ ውሏል። በ1930 እ.ኤ.አ. ከተካሄደው የመጀመሪያው የዓለም ዋንጫ ጀምሮ ሁሉም የዓለም ዋንጫ ሻምፕዮን አገራት (ብራዚል፣ አርጀንቲና፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሣይ፣ ጀርመን፣ ኢጣልያ፣ እስፓንያ እና ኡራጓይ) በዚህ ውድድር ውስጥ ተሳታፊ ናቸው። ከዚህ በፊት በደቡብ አሜሪካ የተዘጋጁትን ዋንጫዎች እንዳለ የወሰዱት የደቡብ አሜሪካ ቡድኖች ናቸው። ፊፋ ለውድድሩ ያቀረበው ጠቅላላ የሽልማት ገንዘብ $576 ሚሊዮን ነው። ይህም ከ2010 እ.ኤ.አ. ውድድር ሽልማት ገንዘብ የ፴፯ ከመቶ ዕድገት አለው። ከዚህ ውስጥ $70 ሚሊዮን የሚሆነው ተጫዋቾቹ ለሚጫወቱበት ክለቦች ተጫዋቾቹ ለሚደርስባቸው ጉዳት መካካሻ እንዲሆን ተሰጥቷል። ከውድድሩ በፊት እያንዳንዱ ቡድን ለዝግጅት ወጪው $1.5 ሚሊዮን የተረከበ ሲሆን ቀሪው ገንዘብ እንደሚመለከተው ተከፋፍሏል፦ $8 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በምድብ ደረጃ የወደቀ ቡድን (፲፮ ቡድኖች) $9 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በየ፲፮ ዙር የወደቀ ቡድን (፰ ቡድኖች) $14 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በሩብ ፍፃሜ የወደቀ ቡድን (፬ ቡድኖች) $20 ሚሊዮን - በአራተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $22 ሚሊዮን - በሶስተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $25 ሚሊዮን - በሁለተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $35 ሚሊዮን - ለአሸናፊው ቡድን በአስራ ሁለት ከተማዎች የሚገኙ አስራ ሁለት ስታዲየሞች ለውድድሩ ተዘጋጅተዋል። ሰባቱ አዲስ የተገነቡ ሲሆን አምስቱ ደግሞ የተሻሻሉ ስታዲየሞች ናቸው። \n \nጥያቄ: በብራዚል በተካሄደው በ2014ቱ ፳ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ በአጠቃላይ ስንት ጨዋታዎች ይደረጋሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ፷፬ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nብሪታኒያ የቻይናው ሁዋዌ 5ኛ ትውልድ (5G) ኔትወርክ በተወሰነ ገደብ በሀገሯ ስራውን እንዲቀጥል ውሳኔ አሳለፈች፡፡ ውሳኔው የተላለፈው ብሪታኒያ ኩባንያውን እንድታግደው አሜሪካ ጫና እየፈጠረች ባለችበት ወቅት፡፡ ብሪታኒያ ውሣኔውን ያሳለፈችው በተወሰኑ ጉዳዮች ላይ ገደብ በመጣል ነው ተብሏል፡፡ በዚህም ኩባንያው ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚፈልገው ወሳኝ ክፍል (ኮር) ተብሎ የሚጠራውን አካል እንዳያቀርብ እገዳ ተጥሎበታል፡፡ ሁዋዌ ኩባንያ በብሪታኒያ 35 በመቶ በሚሆነው 5ኛ ትውልድ ኔትወርክ ዝርጋት እንዲሰማራ እንደተፈቀደለት ተነግሯል፡፡ በተጨማሪም ከወታደራዊ ማዕከላት እና ከኒውክሌር ጣቢያዎች አቅራቢያ እቀባ እንደተጣለበት ነው የተገለጸው፡፡ ቤጂንግ ኩባንያው ከታገደ በብሪታኒያ ሌሎች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ ከፍተኛ እርምጃ እንደምትወስድ አስጠንቅቃ ነበር፡ ኩባንያው በበኩሉ ይህ መፈቀዱ ብሪታኒያ የዓለም-መሪ ቴክኖሎጂን ማግኘት እንድትችል እና ተወዳዳሪ የሆነ ገበያ እንዲኖራት ያደርጋል ብለዋል፡፡ አያይዘውም የ5G ልቀትን ለማስቀጠል ከደንበኞቻችን ጋር አብረን መሥራታችን እንደምንቀጥል ለብሪታኒያ መንግስት እናረጋግጣለን ማለታቸው ነው የተነገረው፡፡ ምንጭ፡-ቢ.ቢ.ሲ \n \nጥያቄ: የቻይናው ሁዋዌ 5ኛ ትውልድ (5G) ኔትወርክ በተወሰነ ገደብ በሀገሯ ስራውን እንዲቀጥል ውሳኔ ያሥተላለፈችው አውሮፓዊት ሀገር ማናት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ብሪታኒያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nመስከረም 24 ቀን 2012 የደቡብ ክልልን ሁለንተናዊ መረጃ የያዘ አትላስ እና የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ሥርአት ተመርቀው ለአገልግለት ተዘጋጁ፡፡ በደቡብ ክልል ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ አማካይነት በአዲስ መልክ ተዘጋጅቶ ትናንት የተመረቀው አትላስ የክልሉን ኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ ፣ ዲሞግራፊያዊና መልክአ-ምድራዊ መረጃዎችን አካቶ መያዙ ተገልጿል። የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ስርአቱም (የመረጃ ቋቱ) ላለፉት 10 ተከታታይ ዓመታት የነበሩ ሁለንተናዊ መረጃዎችን በድህረ-ገጽ አማካይነት ለማሰራጨት የሚያስችል ነው፡፡ በምርቃ ሥነ-ሥርዐቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የደቡብ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ሄለን ደበበ የስታቲስቲክስና መልክዐ-ምድር መረጃ ሥርዐት አስተዳደር የክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ከያዛቸው የትኩረት አቅጣጫዎች አንዱ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የደቡብ ክልል ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ታምራት ዲላ ከዚህ በፊት የነበረው የክልሉን አኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ ፣ ዲሞግራፊያዊና መልክዐ ምድራዊ መረጃዎችን የያዘ አትላስ ላለፉት 15 ዓመታት ማገልግሉንና በአሁኑ ወቅት ያለውን ሁለንተናዊ የክልሉን እድገት ያካተተ እንዳልሆነ ተናግረዋል። ዛሬ ይፋ የተደረገው አትላስ አስከ 2009 ዓ.ም ያለውን ክልላዊ መረጃ የያዘ እንደሆነ ገልጸው አጠቃላይ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፍ የተመዘገቡትን ውጤቶች፣ የመሰረተልማት ስርጭቶችን፣ ዴሞግራፊያዊ፣ መልክዐ-ምድራዊና ሌሎች መረጃዎችን ማካተቱን ተናግረዋል ፡፡ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ በበኩላቸው ከዚህ በፊት ለዕቅድ መነሻ የሚሆኑ መረጃዎች ታች ካሉ መዋቅሮች ብቻ እንደሚሰበሰቡ ገልፀው ይህም ተአማኒ መረጃ ለማግኘት የሚስቸግር አሰራር እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ ይፋ የተደረጉት አትላስና የመረጃ ቋት ይህንን የመረጃ ክፍተት የሚሸፍኑና በቀላሉም ተደራሽ የሚሆኑ በመሆናቸው በፍትሀዊነት ላይ የተመሰረቱ ዕቅዶችን ለማዘጋጀት ትልቅ እገዛ ያደርጋሉ ብለዋል ፡፡ በምረቃ ሥነ-ሥርዐቱ ላይ የደቡብ ክልል፣ የዞኖችና የልዩ ወረዳዎች አመራሮች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲ አስተዳደር አካላት ተገኝተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ የምን ዞን ዋና አስተዳዳሪ ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የሀዲያ ዞን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nነሐሴ ፳፰ ነሐሴ ፳፰ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፰ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፰ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፯ ዕለታት ይቀራሉ። 1862 - የፕሩሲያ (ጀርመን) ሠራዊት 3ኛ ናፖሊዎንን ከ100,000 ጭፍሮች ጋር በሰዳን ውግያ አሸነፈ። 1890 - በኦምዱርማን ውግያ ሱዳንን የእንግሊዝ ሠራዊት ድል በማድረግ ቅኝ አገር አደረጉት። 1935 - በ2ኛ አለማዊ ጦርነት ኢጣልያ በጓደኞቿ ሃያላት (በጀርመን ኃይል) ተወረረች። 1946 - የቻይና ኃያላት የደቡብ ኮርያ ደሴቶችን በቦምብ ደበደቡ። ፲፱፻፸፱ ዓ/ም በቡሩንዲ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ሻለቃ ፒዬር ቡዮያ የአገሪቱን ፕሬዚደንት ዣን ባፕቲስት ባጋዛን ከሥልጣን አስወረዱ። \n \nጥያቄ: በቡሩንዲ በ፲፱፻፸፱ ዓ/ም ሻለቃ ፒዬር ቡዮያ በመፈንቅለ መንግሥት ስልጣን የያዘው ማንን ሽሮ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፕሬዚደንት ዣን ባፕቲስት ባጋዛን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኬንያ የኬንያ ሪፐብሊክ በምስራቅ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በሰሜን ከኢትዮጵያ፣ በሰሜን-ምስራቅ ከሶማሊያ፣ በደቡብ ከታንዛኒያ፣ በምስራቅ ከዩጋንዳ፣ በስሜን-ምዕራብ ከደቡብ ሱዳን፣ በደቡብ-ምስራቅ ከሕንድ ውቅያኖስ ጋር ድንበር ትጋራለች። አውሮፓውያን አካባቢውን ማሰስ የጀመሩት ከ፲፱ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ሲሆን የብሪታንያ መንግሥት የምሥራቅ አፍሪካ ፕሮቴክቶሬትን በ1895 እ.ኤ.አ. አቋቁሟል። ይህ ፕሮቴክቶሬት በ1920 እ.ኤ.አ. የኬንያ ግዛት ተብሎ ተሰይሟል። ነፃ የኬንያ ሪፐብሊክ በዲሴምበር 1963 እ.ኤ.አ. ታወጀ። የኬንያ ስም የመጣው በአፍሪካ በከፍታ ሁለተኛ ከሆነው ከደብረ ኬንያ ተራራ ነው። በዚሁ ተራራ ዙሪያ የሚኖሩት ነገዶች ስሙን «ኪኛ» (በካምባኛ)፣ «ኪሪማራ» (በአመሩኛ)፣ «ኪሬኛ» (በኤምቡኛ)፣ «ኪሪኛጋ» (በኪኩዩ)፣ ወይም «ኬሪ» (በመዓሳይኛ) ይሉታል። የነዚህ ስሞች ሁሉ ትርጉሞች «ቡራቡሬ» ሲሆኑ ይህም ደግሞ «ሰጎን» ማለት ነው፤ አመዳይ ያለበት የተራራው ጫፍ ለተመልካች ቡራቡሬ ወንድ ሰጎንን ያሳስባልና። በኦገስት 2010 እ.ኤ.አ. በተካሄደ ውሳኔ ሕዝብ መሠረት ከብሪታንያ የተወረሰው ሕገ መንግሥት በአዲስ ሕገ መንግሥት ተለውጧል። በአሁኑ ጊዜ ኬንያ በ፵፯ ካውንቲዎች (የአስተዳደር ክፍሎች) ተዋቅራለች። እነዚህ ካውንቲዎች በሕዝብ በተመረጡ ሰዎች የሚስተዳደሩ ሲሆን በናይሮቢ ከሚገኘው ማዕከላዊ መንግሥት በነፃነት ይንቀሳቀሳሉ። የኬንያ ዋና ከተማ እና ትልቋ ከተማ ናይሮቢ ናት። የኬንያ ኢኮኖሚ በምሥራቅና መካከለኛው አፍሪቃ በጂ.ዲ.ፒ. ትልቁ ነው። ግብርና በአገሪቱ ትልቅ የሥራ ዘርፍ ሲሆን ከኤክስፖርቶች መካከል ሻይ፣ ቡና እና ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ አበባዎች ይገኛሉ። እንዲሁም ቱሪስምና ፔትሮሊየም አቢይ ዘርፎች ናቸው። \n \nጥያቄ: የኬንያ ሕገ መንግሥት በሕዝበ ውሳኔ የተሻሻለው መቼ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በኦገስት 2010 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበውሃ ላይ የሚሰራ የኤሌክትሪክ ብስክሌት በገበያ ላይ መዋሉ ተነገረ። ማንታ 5 የተባለው የኒውዝላንድ ኩባንያ ኤክስ ኢ 1 የተሰኘችውን እና በውሃ ላይ የምትሰራውን የኤሌክትሪክ ብስክሌት በላስ ቬጋስ አስተዋውቋል። ብስክሌቱ በፔዳል የሚሰራ ሲሆን፥ አንድ ጊዜ ባትሪ ከተሞላ በኋላ ለአንድ ሰዓት ያክል መጠቀም ይቻላል። በሰዓትም እስከ 20 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር ድረስ መጓዝ ይችላልም ነው የተባለው። አዲሱ ብስክሌት የ6 ሺህ ፓውንድ ዋጋ ተቆርጦለታል። ብስክሌቱን ለዕይታ ለማብቃት እስከ 10 አመት ጊዜ እንደፈጀ ኩባንያው ምርቱን ባስተዋወቀበት ወቅት ገልጿል። አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 29፣ 2012 (ኤፍቢሲ) \n \nጥያቄ: በውሃ ላይ የሚሄድ የኤሌክትሪክ ብስክሌቱ የሚሰራው በምንድን ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በፔዳል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nደቡብ አፍሪካ በደቡብ አፍሪቃ ሕገ መንግሥት መሠረት 11 ልሳናት በእኩልነት ይፋዊ ኹኔታ አላቸው። ከነዚህ መካከል ኳዙሉ ከሁሉ ብዙዎች ተናጋሪዎቹ በአገሩ ውስጥ አሉት፤ ቆሣ በቁጥር ብዛት 2ኛው ነው። ከነዚያ በኋላ በተናጋሪዎች ብዛት አፍሪካንስ 3ኛው፣ ስሜን ሶጦ 4ኛው፣ እንግሊዝኛም 5ኛው፣ ጿና 6ኛው፣ ደቡብ ሶጦ 7ኛው፣ ጾንጋ 8ኛው፣ ሷቲ 9ኛው፣ ቬንዳ 10ኛው፣ ንዴቤሌም 11ኛው ነው። ብዙ ሰዎች እስከ 6 ቋንቋዎች ድረስ የመናገር ዕውቀት አላቸው፤ ከነጭም ዜጋዎች አብዛኛው አፍሪካንስና እንግሊዝኛ ሁለቱን ይችላሉ። ትልቁ ከተማ ጆሃንስበርግ ሲሆን ዋና ከተሞቹ ሦስት ናቸው፤ እነርሱም ኬፕ ታውን፣ ብሉምፎንቴንና ፕሪቶሪያ ናቸው። ይህ ፓርላሜንቱ በኬፕ ታውን፣ ላዕላይ ችሎቱ በብሉምፎንቴን፣ ቤተ መንግሥቱ በፕሪቶሪያ ስለ ሆነ ነው። ስመ ጥሩ የሆኑት የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች ሂው ማሴኬላ እና ሌዲስሚስ ብላክ ማምባዞ ናቸው። የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች አሁን የራሳቸውን ዘመናዊ ሙዚቃ ዓይነት «ኳይቶ» አላቸው። የአገሩ አበሳሰል የተለያየ ነው። ብዙ ኗሪዎች የተቀመመ በሬ ቋሊማ ጥብስ (ቡረቮርስ)፣ የበቆሎ አጥሚት (ኡምጝቁሾ)፣ የተቀመመ ዶሮ፣ እና የተቀመመ ወጥ (ካሪ) ይወድዳሉ። የተወደዱ እስፖርቶች እግር ኳስ፣ ክሪኬት እና ራግቢ ናቸው። \n \nጥያቄ: በደቡብ አፍሪካ በተናጋሪ ብዛት የመጨረሻውን ደረጃ የያዘው ቋንቋ የቱ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ንዴቤሌም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \n‹‹አለቃ ኪዳነ ወልድ ብርሃንና ሰላምን ሲጎበኙ ደስታ ተክለ ወልድ የግእዙን መጽሐፍ ከፍ ባለ ድምፅ ሲያነብቡና ሲያናብቡ ሰምተው ‘ከኔ ጋር ሥራ’ ብለው ጠይቀዋቸው ነው ይባላል፡፡ ከዚህም የተነሣ በድሬዳዋ አልአዛር ማተሚያ ቤት 16 ዓመት ያህል ሠርተዋል፡፡ እንደገና ከድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በብርሃንና ሰላምና በአርቲስቲክ ማተሚያ ቤቶች አገልግለዋል፡፡ ‹‹አስተማሪዬ መምህር ክፍለ ጊዮርጊስ የጀመሩትን ግእዝ አማርኛ ግስ እንድጨርስ አዘውኝ ነበር፡፡ እነሆ እስከ ዛሬ ደክሜበታለሁ፤ አልተጠናቀቀልኝምና አንተ ተረክበኸኝ ሥራውን ቀጥል፡፡ ዘርሁን፤ ዘር ይውጣልህ›› ብለው አለቃ ኪዳነ ወልድ ለአለቃ ደስታ አደራ ሰጥተው ነበር፡፡ አለቃም አደራውን ጠብቀው በ1948 ዓ.ም. ከመደበኛ ሥራቸው ውጭ ሌት ከቀን በመሥራት ‹‹መጽሐፍ ሰዋሰው ወግስ፤ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ›› የተባለውን የመጀመሪያ ታላቅ መዝገበ ቃላት አሳትመዋል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር የነበሩት የታሪክ ምሁሩ ነፍስ ኄር ዶ/ር ብርሃኑ አበበ ስለ አለቃ ክፍሌና ስለ አለቃ ኪዳነ ወልድ ለ‹‹ምን እየሠሩ ነው?›› አዘጋጅ ሲገልጹ እንዲህ ብለዋል፤ ‹‹አለቃ ክፍሌ በወቅቱ የአገሪቱ የቀለም ሰዎች ከተባሉት አንዱ ነበሩ፡፡ ዘመኑም የአፄ ዮሐንስ ነበር፡፡ የሃይማኖት ክርክሩ ቦሩ ሜዳ ላይ ተነሥቶ አለቃ ክፍሌ በኋላቀር ካህናት ከሃዲ መስለው በመታየታቸውና በአፄ ዮሐንስ ዘንድ እጅግ ፊት በማጣታቸው የሸዋ ንጉሥ የነበሩት ምኒልክ አገር ጥለው እንዲሰደዱ ይመክሩዋቸዋል፡፡ ከዚያም በምድረ ሱዳን አድርገው ግብፅ ቀጥለውም ወደ ኢጣልያ ይሻገራሉ፡፡ እነ አግናጥዮስ ጒይዲንና ሌሎችንም ግእዝ ካማርኛ ያስተምራሉ፡፡ ቀጥሎም እርጅና ሲመጣባቸው ወደ ኢየሩሳሌም ጉዞ ያደርጋሉ፡፡ ከዚያም አለቃ ኪዳነ ወልድን ያገኛሉ፡፡ ያላቸውን ዕውቀት ከውድ መጻሕፍታቸው ጋር ለኪዳነ ወልድ ያስረክባሉ፡፡ በተለይም የግእዝና የአማርኛ መዝገበ ቃላት በውል ተሰናድቶ እንዲታተም ለኪዳነ ወልድ አደራ ይሰጣሉ፡፡ በአገሪቱ ዘመናዊ ማተሚያ ሲቋቋም አለቃ ኪዳነ ወልድ ለመጻሕፍት ትርጓሜ ሥራ ወደ አገራቸው ይጠራሉ፡፡ እሳቸው ከአለቃ ክፍሌ የተቀበሉትን አደራ ለአለቃ ደስታ ተክለ ወልድ ያስረክባሉ፡፡ የዚህ ዐቢይ መዝገበ ቃላት ሥራ መነሻው ይህ ነው፤›› በማለት ስለሦስቱም ሊቃውንት ያላቸው ግምት ከፍተኛ መሆኑን አንፀባርቀዋል፡፡ ዶ/ር ብርሃኑ የሦስቱንም የቀለም ሰዎች ታሪክ በፈረንሣይኛ ቋንቋ አዘጋጅተው ‹‹ሃይማኖተ አበው ቀደምት ወዘደኃርት›› ከተባለው የአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መጽሐፍ ጋር አዳብለው በ1978 ዓ.ም. በጀርመን ማሳተማቸው ይታወቃል፡፡ አለቃ ደስታ ለኢትዮጵያ ባህል፣ ቋንቋና ታሪክ ካበረከቷቸው ሥነ ጽሑፋዊ ትሩፋቶች መካከል የግእዝ መማርያ ‹‹ርባሐ ስም ወአንቀጽ›› (1946 ዓ.ም.) እና ‹‹ገበታ ሐዋርያት›› (1928 ዓ.ም.) ይገኙበታል፡፡ ‹‹አንባቢ ሆይ ያማርኛ ቋንቋ ይህ ብቻ እንዳይመስልህ ከዚህ የቀረውን የእንስሳትንና የአራዊትን የአዕዋፍን፣ የዓሣትን፣ የዕፅዋትን፣ ያገርንና የሰውን ስም አምልተን፣ አስፍተን፣ ከነትርጓሜው ለማሳየት ሐሳብ አለን፤ ለዚሁም ያምላካችን ፈቃዱ ይሁን፤›› ብለው በመዝገበ ቃላቱ ላይ ጽፈው ነበር፡፡ ያልታተሙትን ሥራዎቻቸውን ሁለተኛውን እትም ያሳተሙት ልጆቻቸውና ወራሾቻቸው ለንባብ እንደሚያበቁት ይጠበቃል፡፡ \n \nጥያቄ: አለቃ ደስታ ተክለወልድ በድሬደዋ በየትኛው ማተሚያ ቤት ሰሩ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አልአዛር ማተሚያ ቤት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዓረብኛ ዓረብኛ የሴማዊ ቋንቋዎች ቤተሠብ አባል ሆኖ የዕብራይስጥ የአረማያ እንዲሁም የአማርኛ ቅርብ ዘመድ ነው። ፪፻፶ (250) ሚሊዮን የሚያሕሉ ሰዎች እንደ እናት ቋንቋ ይናገሩታል። ከዚህም በላይ በጣም ብዙ ሰዎች እንደ ፪ኛ ቋንቋ ተምረውታል። የሚጻፈው በዓረብኛ ፊደል ነው። በዓረብ አለም ውስጥ አያሌ ቀበሌኞች ይገኛሉ። ቋንቋው በእስልምና ታላቅ ሚና አጫውቷል። እስላሞች አላህ ለሙሐማድ ቁርዓንን ሲገልጽ በዓረብኛ እንደ ሆነ ስለሚያምኑ እንደ ቅዱስ ቋንቋ ይቆጥሩታል። አብዛኛው ዓረብኛ ተናጋሪዎች ሙስሊሞች ናቸው። ዛሬ በምዕራብ ዓለም ደግሞ ብዙ ሰዎች አረብኛ እያጠኑ ነው። በታሪክ ከፍተኛ ሚና በማጫወቱ መጠን ፤ ብዙ የዓረብኛ ቃላት ወደ ሌሎች ቋንቋዎች ገብተዋል። \n \nጥያቄ: አብዛኛው ዓረብኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች የትኛውን እምነት ተከታዮች ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሙስሊሞች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ታኅሣሥ ፳፫ ቀን ፲፱፻፲፯ ዓ/ም በአንዲት “ብርሃንና ሰላም” በተሰኘች አነስተኛ ጋዜጣ ሕትመት ሥራውን ጀመረ። በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው መጻሕፍት ፣ ጋዜጦች ፣ መጽሔቶችና የምስጢራዊ ሕትመት ሥራዎች በተለያዩ ቋንቋዎች እያተመ ይገኛል። ማተሚያ ቤቱ በርካታ የመንግሥት እና የግል ጋዜጦችን የሚያትም ሲሆን ፥ በተጨማሪም በየዓመቱ በርካታ የፈተና ሥራዎችን በማተም ይታወቃል። ጥንታዊ ኢትዮጰያውያን ሊቃውንት የሚጽፏቸው መጻሕፍት ለሕዝብ የሚቀርቡት ብራና ተፍቆ ፣ ቀለም ተቀምሞ በእጅ ተፅፎ ነበር። በዳግማዊ ምኒልክ ዘመነ-መንግሥት የተጀመረው የዘመናዊ ሕትመት ሥራ በሀገሪቱ ቁጥራቸውና መጠናቸው በርከት ያሉ ጋዜጦች፣ መፅሔቶች፣ መጻሕፍት፣ እንዲሁም ሌሎች የሕትመት ውጤቶች መታተም በመጀመራቸው የትምህርትና የሥልጣኔ መሰፋፋት ላይ የበኩሉን ሚና መጫወት ጀመረ። የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤትም ምሥረታ ዋና ዓላማ የአገሪቱን መንፈሳዊ መጻሕፍት በብዛት እና በዘመናዊ መልክ ከእጅ ጽሑፍ ወደ ሕትመት ለማሸጋገር ሲሆን፤ ምሑሩ ተክለጻድቅ መኩሪያ (፲፱፻፷፩ ዓ/ም)፣ ማተሚያ ቤቱ መስከረም ፫ ቀን ፲፱፻፲፬ ዓ/ም መቋቋሙን እና ብዙ ሥጋዊና የመንፈሳዊ መጻሕፍት እንዲሁም ምክርና ተግሣጽ፣ የለት ወሬ፣ የሹም-ሽር አዋጆችን ያትም እንደነበር ዘግበዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ረዳት መምህር መኩሪያ መካሻ፤ “የፕሬስ ታሪክ” በተሰኘ ጽሑፋቸው ላይ ደግሞ የኢትዮጵያ መንግሥት አልጋ ወራሽና ባለሙሉ ሥልጣን እንደራሴ፣ ራስ ተፈሪ መኮንን በ፲፱፻፲፫ ዓ/ም የማተሚያ መሣሪያ አስመጥተው “ትንሹ ግቢ” (በኋላ ገነተ ልዑል — አሁን አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ) ይባል በነበረው መኖሪያቸው ውስጥ አስተክለው የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት የተባለውን እንደመሠረቱ ዘግበዋል። ከሁለት ዓመት በኋላ በ፲፱፻፲፭ ዓ/ም አራት ተጨማሪ ማተሚያዎች ተገዝተው ከተተከሉ ከአንድ ዓመት በኋላ ሣምንታዊው ‘ብርሃንና ሰላም’ የተሰኘው ጋዜጣ እየታተመ፣ አስቀድሞ በዳግማዊ ምኒልክ ዘመን ከተጀመረችው ‘አዕምሮ’ ጋዜጣ ጋር እስከ ጠላት ወረራ ዘመን ድረስ በአዲስ አበባ ከተማ ይሠራጩ ነበር። የወቅቱ ማተሚያ መሣሪያዎች በእግር እየተረገጡ የሚንቀሳቀሱ መሣሪያዎች ሲሆኑ የሠራተኞቹ ቁጥር ከሰባት እስከ አሥራ-ሁለት እንደነበር ተዘግቧል። ራስ ተፈሪም አልፎ-አልፎ በብርሃን እና ሰላም ጋዜጣ ላይ በአዘጋጅነት ይረዱ እንደነበረና ጽሑፎቻቸውንም ለሕትመት ያበቁ እንደነበር ተምዝግቧል። \n \nጥያቄ: የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤትም የምሥረታው ዋና ዓላማ ምንድ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የአገሪቱን መንፈሳዊ መጻሕፍት በብዛት እና በዘመናዊ መልክ ከእጅ ጽሑፍ ወደ ሕትመት ለማሸጋገር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nፌስቡክ የሰዎችን ምስል ለማጣራት እና ለመለየት የሚጠቀምበት መሳሪያ ጋር ተያይዞ ለረጅም ጊዜ የዘለቀውን የህግ ክርክር እልባት መስጠቱ ተገልጿል። ፌስቡክ በፈረንጆቹ 2010 የሰዎችን የፊት ገጽታ መለያዎች መሣሪያን መጠቀም በፈረንጆቹ 2010 ላይ የጀመረ ሲሆን፥ መሣሪያው የተጠቃሚውን ፊት ገጽታ በመቃኘት ስለ ደንበኛው ማንነት ሃሳቦችን የሚያቀርብ መሆኑ ተገልጿል። ምንም እንኳን ተጠቃሚዎች እሱን የማጥፋት አማራጭ ቢኖራቸውም፣ በወቅቱ ቴክኖሎጂው አወዛጋቢ ሆኖ መገኘቱ ተጠቁሟል። ተቃዋሚዎቹ የፊት ገጽታ መለያ መሣሪያው በኢሊኖስ ግዛትከወጣው የግላዊነት ህጎችን ይጥሳል ብለው የተከራከሩ ሲሆን ÷በግዛቱ ለሚገኙ ቡድኖችም 550 ሚሊየን ዶላር ይከፍላልም ተብሏል። ጉዳዩ በፈረንጆቹ ከ2015 ጀምሮ ሲካሄድ የቆየ ሲሆን ፥ስምምነቱም በየሩብ ዓመቱ ከሚገኝ ገቢ መሆኑም ተመላክቷል። ይህ የፊት ገጽታ እውቅናው በፖሊስ እና በአደባባይ ቦታዎችጥቅም ላይ ሲውል በጥልቀት ክትትል እንደሚደረግበትም ተገልጿል። በፈረንጆቹ ታህሳስ ወር 2017ተጠቃሚዎች ይበልጥ በቀላሉ ማብራት ወይም ማጥፋት ይችላሉ እንዲችሉ ተደርጎ የተሰራ ሲሆን ÷በ 2019 ፌስቡክ ይበልጥ በግላዊነት ላይ ያተኮረ እንዲሆን አድርጎ አዲሱ የመቆጣጠሪያ አካል አድርጎ መስራቱም ነው የተገለጸው። የማህበራዊ አውታር መረቡ ይህንን ጉዳይ ለማህበረሰባችን እና ለባለአክሲዮኖቻችን ጥቅም ስንል ለመፍታት ወስነናል ሲል አስታውቋል፡፡ ይህ ማስተካከያ የሰዎችን መረጃ እና ግላዊነትን ለመጠበቅ በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ሁለተኛውን ትልቁ መሆኑን የኢንቨስትመንት ባንክ ጃንስትር የሆኑት ክርስቶፎር ሮዝባች ተናግረዋል። ምንጭ፡-ቢ.ቢ.ሲ \n \nጥያቄ: ፌስቡክ የሰዎችን የፊት ገጽታ መለያ መሣሪያ በመጠቀም ምን ዓይነት ጥቅም አግኝቷል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ስለ ደንበኛው ማንነት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሪት ፍሬህይወት ታምሩን ጨምሮ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በገበታ ለአገር የሚለማውን የወንጪ ፕሮጀክት እየጎበኙ ነው። የስራ ሃላፊዎቹ ጉብኝት በዋናነት ቴሌኮሙ በፕሮጀክቱ የሚያከናውነውን ስራ በተመለከተ የመስክ ምልከታ ለማድረግ ነው። ኢትዮ-ቴሌኮም በፕሮጀክቱ ከሚያከናውነው ስራ በተጨማሪ ለገበታ ለአገር ፕሮጀክቶች 500 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉን ከተቋሙ የተገኘው መረጃ ያሳያል። \n \nጥያቄ: ኢትዮ ቴሌኮም የ500 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ለምን አደረገ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ለገበታ ለአገር ፕሮጀክቶች ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየመደመር መንገድ መጽሐፍ ሁለት ዓላማ ያነገበ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ፡፡ ይህም በአንድ በኩል ሐሳብ ማስተላለፍ በሌላ በኩል በገቢው ትምህርት ቤቶችን ማስፋፋት መሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል፡፡ የመጽሐፉ የነጠላ መሸጫ ዋጋ 350 ብር ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ አንባቢዎች ሊዳረስ የሚችል በቂ ቅጅ ስላለ ከዚህ በላይ ከሚሸጡት እንዳይገዙም አሳስበዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የመደመር መጽሀፍ ዋጋ ስንት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 350 ብር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቦሌ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ በአዲስ አበባ ከተማ በደቡብ-ምሥራቅ አቅጣጫ ከአራዳ በስምንት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ የአገሪቱ ዋና አድማሳዊ የንግድና የግንኙነት በር ነው። አውሮፕላን ወደ ኢትዮጵያ መግባት የጀመሩት በንግሥት ዘውዲቱ ዘመን ሲሆን በአዲስ አበባ ዙሪያ በጃን ሜዳ እና አቃቂ ያርፉ እንደነበር በታሪክ ተዘግቧል። የመጀመሪያው ቋሚ የአውሮፕላን ጣቢያ ግን የተሠራው በአምሥቱ የፋሺስት ዘመናት ሲሆን የካቲት ፳፬ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ/ም አክሱም አካባቢ ላይ ከነጥያራው ተከስክሶ በሞተው አብራሪያቸው፣ “ኢቮ ኦሊቬቲ” ስም ሠይመውት የነበረው የልደታ የጥያራ ጣቢያ ነው። በዚሁ በፋሺስት ወረራ ዘመን ‘አላ ሊቶሪያ’ የተሰኘው ኩባንያ በአገር ውስጥ ከአዲስ አበባ ተነስቶ ነገሌን፤ ሞቃዲሾን፤ ድሬ ዳዋን፤ ጎራኄን፤ ጂቡቲን፤ አሰብን፤ ጂማን፣ ጋምቤላን ደምቢ ዶሎን፤ ጎንደርን አስመራን፤ ደሴን፤ ለቀምትን እና አሶሳን የሚያገለግሉ የበረራ መሥመሮች ሲኖረው ከአድማስ ባሻገር ደግሞ ከተማዋን በካርቱም፣ ዋዲ ሃይፋ፤ ካይሮ፣ ቤንጋዚ እና ሲራኩሳ አድርጎ ከሮማ ጋር የሚያገናኝ የበረራ መሥመርም ነበረው። ከድል ወዲህ ልደታ አውሮፕላን ጣቢያ፤ የብሪታኒያ ጦር ኃይሎች ሲገለገሉበት ከቆየ በኋላ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ታኅሣሥ ፳፩ ቀን ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ሲመሠረት ዋና ጣቢያው እዚያው ነበር። ዳሩ ግን የአየር መንገዱ አገልግሎት እየተስፋፋ ሲመጣና ትላልቅ ጄት አውሮፕላኖች እንደሚያስፈልጉት ግልጽ ሲሆን፣ የልደታ አየር ጣቢያ ብቃት እንደሌለው እና ለጄት አየር ዠበቦችም ማሳረፊያ የማይስማማ መሆኑ ታምኖበት የአማራጭ ሥፍራ ፍለጋ ተጀመረ። የአዲሱንም አየር ጣቢያ ዝርዝር ጥናት እንዲያዘጋጅ ውሉ ለአሜሪካዊው ‘አማን እና ዊትኒ’ ኩባንያ ተሰጥቶ፤ ጥናቱ በ፲፱፻፶ ዓ/ም ተገባዶ አማራጩ ሥፍራ ቦሌ እንዲሆን ተወሰነ። የአየር ጣቢያውን የግንባታ ወጪ ከአሜሪካዊው ‘ኤክስፖርት-ኢምፖርት’ ባንክ በተገኘ ብድር ተሸፍኖ ሥራው ተጀመረ። ጠቅላላ ግንባታው ተጠናቆ ሲያልቅ ኅዳር ፲፩ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ/ም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተብሎ፣ በንጉሠ ነገሥቱ ተመርቆ ተከፈተ። \n \nጥያቄ: አውሮፕላን ወደ ኢትዮጵያ መግባት የጀመሩት በማን ዘመን ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በንግሥት ዘውዲቱ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nካሣ አያሌው ገና የአራት ዓመት ህፃን ልጅ ሳለ በወቅቱ የትምህርት ገበታን መቋደስ የሚጀመርበት የቄስ ትምህርት ቤት ተልኮ ፊደል መቁጠር ጀምሯል። በዚህ ቆይታው ከፊደል ቆጠራ እስከ ዳዊት ንባብ በአግባቡ ለመማር በቅቷል። በኋላም በጊዜው እንጦጦ አምባ አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተብሎ ይጠራ የነበረው ት/ቤት በመዝለቅ ዘመናዊ ትምህርቱን አንድ ብሎ ጀምሯል። ካሣ በዚህ ት/ቤት ሳለ ነበር ውስጡ ከነበረው የህይወት መክሊቱ ጋር የተገናኘው። የሦስተኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ በት/ቤታችን የሚገኘውን ሚኒ ሚዲያ የምቀላቀልበት ዕድል ተፈጠረ። ይህ ዕድል የተገኘው በክፍሌ ውስጥ ተማሪዎች ፊት ቆሜ ጋዜጣ ሳነብ ድንገት ክፍላችን በተገኙት የት/ቤታችን ም/ርዕሰ መምህር አማካኝነት ነው። ስማቸው መምህር ግርማ ይገዙ ይባላል። አነባበቤን አይተው ስለወደዱት እርሳቸው ይመሩት የነበረውን የሚኒ ሚዲያ ክበብ እንድቀላቀል አደረጉ። በዚህ ክበብ ውስጥ ሆኜ በትምህርት ቤቱ እንቅስቃሴ ላይ ያተኮሩ ዜናዎችን እየዘገብኩ ዘወትር ማለዳ የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር እየተዘመረ ሰንደቅ ዓላማ በሚሰቀልበት የተማሪዎች ሰልፍ ላይ ማንበብ ጀመርኩ» በማለት ካሣ የጋዜጠኝነት ህይወት መስመሩ አንድ ብሎ የተጀመረበትን ሁኔታ ያስታውሳል። ካሣ አያሌው ካሣ የዘጠነኛ ክፍል ትምህርቱን በእንጦጦ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት /ቲ ኤም ኤስ/ ከጀመረ አንስቶ ሙሉ ትኩረቱን የቀለም ትምህርቱ ላይ አድርጎ ቆይቷል። በዚህ ቆይታው ከማህበራዊ ሳይንስ ይልቅ የተፈጥሮ ሳይንስን ምርጫው አድርጎ ትምህርቱን ተከታትሏል። የአስራ ሁለተኛ ክፍል መልቀቂያ አገር ዓቀፍ ፈተና ሲወስድም እንደ ተለመደው ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ወደ ከፍተኛ ትምህርት የሚሸጋገርበት ዕድል አግኝቷል። በወቅቱ የከፍተኛ ትምህርት ምደባ የሚሰጠው በዕጣ ስለነበር ካሣ በዚህ አመዳደብ መሰረት የኢንጂነሪንግ ትምህርት እንዲማር የአዳማ ቴክኒክ ኮሌጅን እንዲቀላቀል ምደባ ወጥቶለታል። ምደባውን ተከትሎ ወደ አዳማ በማቅናት የቴክኖሎጂ ትምህርቱን መከታተል ቢጀምርም ቅሉ ሁኔታው ምቾት እንዳሳጣውና እንዳሎደደው ካሣ ይናገራል። ካሣ በ2005ዓ.ም ላይ ከፍቅረኛው ሊና ኑር አሕመድ ጋር በጋብቻ የተሳሰረ ሲሆን ቀዳማዊትና ለዕልና የተባሉ ሁለት ሴት ልጆችን ወልዷል። በትዳር ህይወቱ እጅግ የተሳካለት እንደሆነ በቅርበት የሚያውቁት ጓደኞቹ ይመሰክራሉ። ከስራ ውጪ ያለ ሰዓቱን ሁሉ ከቤተሰቦቹ ጋር ማሳለፍ እንደሚያስደስተው ሁሉም ይመሰክሩለታል። \n \nጥያቄ: ካሳ በትምህርት ቤቱ ሚኒ ሚዲያ ክለብ ውስጥ አንቢገባ ያደረጉት ማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ መምህር ግርማ ይገዙ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበኢትዮጵያ የሚገኙ በርካታ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች መንግሥት ተገቢውን ክትትል እያደረገ ባለመሆኑና ኩባንያዎች በክህሎት የበቁ ኢትዮጵያዊያን በሥልጠና ዕገዛ ባለማድረጋቸው ምክንያት፣ አብዛኛዎቹ በሲሚንቶ ፋብሪካዎች ተቀጥረው የሚሠሩት ሠራተኞች የውጭ ዜጎች መሆናቸው ተገለጸ፡፡ በኢትዮጵያ ምርት በማምረትና በግንባታ ላይ የሚገኙትን ጨምሮ 17 የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የሚገኙ ሲሆን፣ 12ቱ በተለያየ የማምረት መጠን ላይ ይገኛሉ፡፡ ይሁን እንጂ በበርካታ ፋብሪካዎች በተለይም ግዙፍ በሚባሉት ዳንጎት፣ ሙገርና ደርባ ኩባንያዎች ውስጥ የውጭ ዜጎች የማኔጅመንቱንና ቴክኒካል ሥራውን በበላይነት እንደሚይዙ የኬሚካልና ኮንስትራክሽን ግብዓቶች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ ስምረት ግርማ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ በዚህም በሥራ ላይ በሚገኙት የሲሚንቶ ፋብሪካዎች በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ የውጭ ዜጎች እንዳሉ የገለጹት ምክትል ዳይሬክተሯ፣ ኢትዮጵያውያን እየሠሩባቸው ያሉ ዘርፎችም ቢሆን በዝቅተኛ ዕርከንና በጉልበት ሥራ ላይ የሚገኙ ስለመሆኑ ተናግረዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ወ/ሮ ስምረት ግርማ ያላቸው ኃላፊነት ምንድን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የኬሚካልና ኮንስትራክሽን ግብዓቶች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየንግዱን ዘርፍ በማዘመን ሸማችን ከአምራች ጋር በቀጥታ የሚያገናኝ የኤሌክትሮኒክስ ግብይት (ኢ-ኮሜርስ) ይፋ ሆነ:: በአሸዋ ቴክኖሎጂ ሶሉሽን አ.ማ የበለፀገው የኢ-ኮሜርስ ቴክኖሎጂ የኢንተርኔት አገልግሎት በሚገኝበት አካባቢ አምራችን በቀላል እንዲሁም ቀጥተኛ በሆነ መንገድ የሚያገናኝ ቴክኖሎጂ መሆኑ ተገልጿል:: ቴክኖሎጂው የንግድ ሰንሰለትን በማሳጠር የዋጋ ንረትን በማስቀረት ረገድ አስተዋጽኦው የጎላ መሆኑ ተመላክቷል:: ዘመኑን የዋጀ የግብይት ሥርአትን መፍጠር የንግድ ዘርፉን በማነቃቃት ረገድ አበርክቶው የላቀ በመሆኑ የኢ-ኮሜርስም የሀገርን ምጣኔ ሀብት የማሳደግ አቅም እንዳለው ከግምት ውስጥ በማስገባት የንግዱ አለም ተዋናዮች ተግባራዊ ሊያደርጉት ይገባል ተብሏል:: \n \nጥያቄ: ኢ-ኮሜርስ ምን ዓይነት የንግድ መንገድ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሸማችን ከአምራች ጋር በቀጥታ የሚያገናኝ የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበኢትዮጵያ አየር ኃይል ውስጥ ለ25 ዓመታት ያገለገሉት ብርጋዴር ጄነራል መአሾ ሀጎስ ስዩም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የደቡብ ሱዳን ሰላም ማስከበር ተልእኮ አዛዥ ሆነው ተሰየሙ። ብርጋዴየር ጄነራል መአሾ በተመድ የላይቤሪያ እንዲሁም ዳርፉር ሰላም አስከባሪ ኃይል ውስጥ ማገልገላቸውም ታውቋል። አዲሱን ሹመት ከጥር 04 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ እንደተሰጣቸውም በተመድ መረጃ ላይ ተገልጿል። \n \nጥያቄ: ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የደቡብ ሱዳን ሰላም ማስከበር ማን ተሾመ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ብርጋዴር ጄነራል መአሾ ሀጎስ ስዩም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዓለማየሁ ቴዎድሮስ ልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ የዳግማዊ ዓፄ ቴዎድሮስ እና የወይዘሮ ጥሩወርቅ ውቤ ልጅ ነበር። በ1860 ዓ.ም አፄ ቴዎድሮስ ከእንግሊዞች ጋር ባደረጉት ጦርነት ልጃቸው ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ ወደ እንግሊዝ ሀገር ተወስዶ ነበር፡፡ ልዑል አለማየሁ ሚያዚያ 5 ቀን 1853 ዓ.ም በደብረ ታቦር ከተማ ነበር ውልደቱ፡፡ በልዑሉ ውልደት የተደሰቱት አፄ ቴዎድሮስም በእለቱ መድፍ ያስተኮሱ ሲሆን 500 ያህል እስረኞችንም ፈትተዋል፡፡ ልዑል አለማየሁ እንግሊዞች እጅ ከገባ በኋላ ከእድሜው ለጋነት የተነሳ የሚጠብቀው እና የሚንከባከበው ሰው ሊኖር ግድ ነበር፡፡ ይህንን የተረዳው ጀነራል ናፔር ካፕቴን ስፒዲ የተባለን ሰው የአለማየሁ ጠባቂ እንዲሆን መደበው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ካፕቴኑ የአማርኛ ቋንቋን አቀላጥፎ መናገሩ ነበር፡፡ በተጨማሪም አለቃ ዝርዓት እና አቶ ገብረመድህን የተባሉ ሁለት ኢትዮጵዊያን ሞዚቶች እና አጫዋቾች ተመረጡለት፡፡ አለማየሁ ከጠባቂው ስፒዲ ጋር ፌሬዝ በተባለችው መርከብ ተሳፍሮ በ1860 ዓ.ም. ወደ እንግሊዝ አቀና፡፡ በመርከቢቱ ላይ በነበራቸውም ቆይታ ስፒዲ እና አለማሁ እጅግ የጠበቀ ወዳጅነትን መስርተው ነበር፡፡ ስፒዲ በሄደበት ቦታ ሁሉ አለማየሁን ማስከተል ያዘወትር ነበር፡፡ ይህንን የሁለቱን ፍቅር ያየው ጀነራል ናፒየርም ኢትዮጵያውያን ሞግዚቶቹ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ይልቁንም የአለማየሁን ሀላፊነት ሙሉ በሙሉ ካፕቴን ስፒዲ እንዲረከብ ስለወሰነ ሁለቱ ሞግዚቶች ጉዞው ተጠናቆ እንግሊዝ ሀገር ሳይደርሱ ከስዊዝ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ተደረገ፡፡ ከሶስት ወራት የመርከብ ላይ ጉዞ በኃላ አለማየሁ እንግሊዝ ሀገር ደረሰ፡፡ \n \nጥያቄ: ልዑል አለማየሁ አባቱ አጼ ቴዎድሮስ ከሞቱ በኋላ ወዴት ተወሰደ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ወደ እንግሊዝ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየኮምፒዩተር አውታር የኮምፒዩተር አውታር (ኔትወርክ) ማለት ሁለት ወይም ከሁለት በላይ የሆኑ ኮምፒዩተሮችን ማገናኘት ነው። እነዚህ ኮምፒዩተሮች ሲገናኙ መረጃ መለዋወጥ ይቻላል። አውታሩ ውስጥ ያሉት ኮምፒዩተሮች በአንደ ክፍል ውስጥ ወይም በጣም በተራራቁ ሕንጻዎች ውስጥ ሊገኙ ይችላሉ። ኮምፒዩተሮቹ በኤሌትሪክ ገመድ ፣ በገመድ የለሽ ግንኙነት ወይም በሞደም ሊገናኙ ይችላሉ። አውታሩ ላይ ሌሎች የኮምፒዩተር መሣሪያዎችንም መግጠም ይቻላል። ለምሳሌ አንድ ፕሪንተር አውታር ውስጥ አገናኝቶ አውታሩ ውስጥ ከሚገኝ ማንኘውም ኮምፒዩተር ወደዛ ፕሪንተር ማተም ይቻላል። የአውታሩን ኮምፒዩተሮች ሁሉንም እኩል ሥልጣን መስጠት ይቻላል ወይም ለአንዳንድ ኮምፒዩተሮች የተለዩ ሥራዎች መሥራት እንዲችሉ ማድረግ ይቻላል። ሁለተኛው ዘዴ ክላየንት-ሰርቨር ይባላል። አብዛኛው ጊዜ ሰርቨሮቹ ሀይለኛና ትልቅ ሲሆኑ ክላየንቶቹ ደግሞ አነስተኛ ናቸው። \n \nጥያቄ: ሁለትና ከዛ በላይ የሆኑ ኮምፒዩተሮችን እርስ በእርስ በማገናኘት የሚፈጠር ትስስር ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የኮምፒዩተር አውታር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nይምርሃነ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በዓፄ ይምርሃነ ክርስቶስ አነሳሽነት በ12ኛው ክፍለ ዘመን በአቡነ ዮሴፍ ተራራ ውስጥ በሚገኝ ዋሻ ውስጥ የተሰራ ቤተክርስቲያንና በዚያው ዋሻ ውስጥ ከቤተርክስቲያኑ ፊትለፊት ያለ ቤተ መንግስት ህንጻ በአንድነት የሚጠሩበት ስም ነው። ዋሻው ከላሊበላ የ6 ሰዓት የእግር ጉዞ ርቀት ላይ ይሚገኝ ሲሆን 45ሜትር ርዝመት በ6 ሜትር ቁመትና 50ሜትር ጉድጉደት አለው። በዋሻው ውስጥና ውጭ ለጸበል የሚያገለግሉ ምንጮች ይፈልቁበታል። ዓፄ ይምርሃነ ክርስቶስ ከሮሃ ሆኖ አገሩን ያስተዳድር እንጂ ይሄው ቤተክርስቲያንና ቤተመንግስት ሲታነጽ መኖሪያውን ወድዚህ ዋሻ እንዳዛወረ በ17ኛው ክፍለ ዘመን የተጻፈ የህይወት ታሪኩ ይገልጻል። የቤተክርስቲያኑ ህንጻ 3 መግቢያዎች ሲኖሩት በሰሜን(ለወንዶች)፣ ደቡብ(ለሴቶች) እና ምሥራቅ (ለካህናት) ይገኛሉ። በግድግዳው ላይ የሚገኙ፣ ነገር ግን በአቧራ የተሸፉኑት ምስሎች ከዚሁ ዘመን የሚመነጩ ሲሆኑ በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ የግድግዳ ምስላት ቀደምት ናቸው። ፍራንሲስኮ አልቫሬዝ ይህን ቤተክርቲያን በ16ኛው ክፍለዘመን መግቢያ ላይ የጎበኘው ሲሆን፣ እንደርሱ ዘገባ በዚህ ወቅት ቤተክርስቲያኑ 200 ደብተራዎች የነበሩት ሲሆን አጠቃላይ ቤቱ በሊቀ ካህናት ይመራ እንደነበር ሲጠቅስ፤ በወቅቱ መነኮሳት እንደማይኖሩበትም ዘግቧል። ከይምርሃነ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ጀርባ 3 መቃብሮች ሲኖሩ፣ የራሳቸው የዓፄ ይምርሃነ፣ የሴት ልጃቸው እና ከእስክንድርያ ንጉሱን ሊጠይቁ የመጡ ፓትሪያርክ እንደሆኑ ይጠቀሳል። ወደዋሻው ውስጥ በጣም ርቆ ደግሞ የብዙ ምዕመናን አጽም የሚታይበት ሰፊና ጨለማ ክፍል አለ። \n \nጥያቄ: ዓፄ ይምርሃነ ክርስቶስ ከየት ሆኖ ነበር አገሩን ያስተዳድር የነበረው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከሮሃ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአማራ (ክልል) አማራ (ክልል 3) ከዘጠኙ የኢትዮጵያ ክልሎች አንዱ ሲሆን ከ 1994 በፊት አራት የሀገሪቱን ዋና ወና ክፍለ ሀገራት የ ካትት ነበር እነሱም በጌምድር ጐጃም ወሎና ሸዋ ነበሩ ።የአማራ ብሔራዊ ክልል ጅኦግራፊያዊ አቀማመጥ በ8° 45 እስከ 13° 45 ሰሜን የኬንትሮስ እና በ35° 46 እስከ 40° 25 ምስራቅ የኬንትሮስ መስመር ውስጥ ይገኛል። በምስራቅ የአፋርና የኦሮሚያ ክልሎች፣ በምዕራብ ሱዳን እና ቤንሻንጉል-ጉምዝ ክልል፣ በሰሜን የትግራይ ክልልና በደቡብ የኦሮሚያ ክልል ያዋስኑታል። የቆዳ ስፋቱ ፻፶፯ሺ፸፮ ካሬ ሜትር ሲሆን ከአገሪቱ አሥራ አምስት በመቶ ድርሻ ይይዛል። የክልሉ ሕዝብ ብዛት ደግሞ በ፳፻፪ ዓ/ም 20,875,456 እንደነበር የተገመተ ሲሆን ከአገሪቱ ጠቅላላ ሕዝብ 33.9% አካባቢ ድርሻ ይይዛል ተብሎ ይገመታል። ክልሉ በ፲ ዞኖችና በ፻፷፮ የገጠርና የከተማ ወረዳ አስተዳደሮች የተከፋፈለ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ፴፰ የሚሆኑት የከተማ አስተዳደሮች ናቸው። የአማራ፣ የአገው፣ የኦሮሞና የሌሎች ብሔረሰቦች በጋራ የሚኖሩበት ክልል ነው። እንዲሁም የአማራ ክልል አሁን ላይ የክልል ከተማው ባህር ዳር ነው። በክልሉ አልፎ አልፎ ከሚታዩ የመንግሥትና የማኅበራት ደኖች፣ በደሴቶች፣ በአብያተ ክርስቲያናት፣ በወንዞች ዳርቻና ሰው ሊደርስባቸው በማይችሉ ገደላማና ተራራማ ስፍራዎች ከሚገኙ ጥቂት ደኖች በስተቀር ሊጠቀስ የሚችል ከፍተኛ የደን ሀብት ጋር በቅርብ የተያያዘ ነው። በዚህ ረገድ በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የሚገኙ እንደ ቀይ ቀበሮ፣ ዋልያ፣ ጭላዳ ዝንጀሮ እንዲሁም በምዕራባዊው የክልሉ አካባቢ ዝሆን አንበሳና ነብር፣ ሰጐንና የተለያዩ አዕዋፋት በስተቀር ከፍተኛ የዱር እንስሳት ክምችት ካለመኖሩም በላይ በተለያዩ አካባቢዎች ባሉ ጥቂት የደን ቅሪቶችና ዋሻዎች የነበሩት አነስተኛ ቁጥር ያላቸው አራዊቶችም ለዘመናት በደረሰው የደን መጨፍጨፍና መራቆት ምክንያት ከክልሉ ወደ ሌላ አካባቢ እንደተሰደዱ ይታወቃል። ክልሉን የማዕድን ሀብት አስመልክቶ በሚገባ የተጠናከረ ጥናት ባይኖርም ከክልሉ ስነ-ምድራዊ ሁኔታዎችና ከተካሄዱ አንዳንድ ጠቋሚ ጥናቶች መረዳት እንደሚቻለው በክልሉ ውስጥ የተለያዩ ማዕድናት እንደአሉ ይገመታል። በዚህም መሠረት በሰሜን ሸዋ የኦፓል ማዕድን፣ በሰሜን ጐንደር፣ በጭልጋና በደቡብ ወሎ በአምባሰል ወረዳ የድንጋይ ከሰል ክምችት እንዳሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ከዚህም በተጨማሪ ለግንባታ ሥራ የሚውል በቂ የድንጋይ፣ የኖራ ድንጋይ፣የሸክላ አፈር፣ ጅኘሲየም፣ የጌጣጌጥ ማዕድናት እንዲሁም በዓባይ ሸለቆ የዕብነ በረድ ሐብቶች እንዳሉ ጥናቶች ይጠቁማሉ። ይሁን እንጅ በውል የሚታወቀው ሐብትም ቢሆን በበቂ ሁኔታ አልለማም። \n \nጥያቄ: የአማራ ክልል ዋና ከተማ ማን ናት?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ባህር ዳር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሚያዝያ ፴ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፵ ኛው ዕለትና የወርኅ ፀደይ (በልግ) ፴፭ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ ሉቃስ ፻፳፮ ቀናት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመን ማርቆስ ደግሞ ፻፳፭ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፰፻፸፬ ዓ/ም - እምባቦ በሚባል ሥፍራ የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ ሠራዊት እና የጎጃም ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ሠራዊት ውጊያ ገጥሞ ድሉ የንጉሥ ምኒልክ ሲሆን፣ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ተማረኩ። ፲፰፻፺ ዓ/ም - በጣልያ አበጋዙ ባቫ-በካሪስ ብዙ መቶ ሰልፈኞች በመድፍ ገደላቸው። ፲፱፻፳፭ ዓ/ም - የሕንድ አባት በሚል ቅጽል ስም የሚታወቀው ሞሃንድራስ ካራምቻንድ ጋንዲበአገሩ የእንግሊዝን አስተዳደር በመቃወም የሃያ አንድ ቀን የ'ረሀብ አድማ' ጀመረ። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - በአውሮፓ የሁለተኛው የዓለም ጦርነትን ማክተም ምክንያት በማድረግ 'ሴቲፍ' በተባለች የአልጄሪያ ከተማ በተካሄደ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ፻፫ አውሮፓውያን በመሞታቸው፣ የገዢው የፈረንሳይ መንግሥት ፖሊሶች እና ወታደሮች ባካሄዱት ጨካኝ በቀላ እስከ ስድስት ሺ አልጄሪያውያን ተጨፍጭፈዋል። የዚህ አረመኔያዊ ድርጊት ሳቢያ በመላው የሰሜን አፍሪቃ የፈረንሳይን ቅኝ ገዢነት ማክተሚያ አብሳሪ እንደሆነ ታሪካውያን ይዘግባሉ። ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - በሩሲያኖች የተገነባው የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ዶክቶር ምናሴ ኃይሌ እራሳቸውን ከሥልጣናቸው አስወገዱ። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - አቶ ለገሰ ዜናዊ አስረስ፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር አድዋ ላይ ተወለዱ። \n \nጥያቄ: የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ ሠራዊት እና የጎጃም ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ሠራዊት ውጊያ የገጠሙበት ቦታ ምን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ እምባቦ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nማርክ ትዌይን ሳሙኤል ላንግሆርን ክሌመንስ ወይም በብእር ስሙ ማርክ ትዌይን አሜሪካ ካፈራቻቸው ድንቅ ጸሃፍት መካካል የሚመደብ ደራሲ ነው። ትዌይን በኖቬምበር 1835 ዓ.ም. ሚዙሪ በተባለችው የአሜሪካ ግዛት ተወለደ። 18 ዓመት እስኪሞላው ድረስ ከቤተሰቦቹ ጋር የኖረው ሃኒባል በተባለች እና ሚሲሲፒ ላይ በተቆረቆረች ትንሽ ከተማ-አከል ቦታ ነው። አባቱ በ1847 ሲሞት ትዌይን ትምህርቱን በማቋረጥ በማተሚያ ቤት ውስጥ በሰልጣኝነት ተቀጠረ። ይህን ስራውን በ1857 በመተው የእንፋሎት ጀልባ ነጂ በመሆን መስራት ጀመረ። በዚሁ ስራ በቆየባቸው አመታት ነው ኋላ ላይ አድናቆትን ላተረፉለት የስነ-ጽሁፍ ስራዎቹ የሚሆኑትን እውቀቶች ለማሰባሰብ የበቃው። እሱ ራሱም እንዳለው በዚሁ ስራ ላይ ነው \"ማንኛውንም በልብ-ወለድ፣ በግለ-ታሪክም ሆነ በታሪክ ላይ ሊገኙ የሚችሉ የሰው ባህርያትን\" ሊያጠና የበቃው። በ1861 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የእርስ-በርስ ጦርነት በመቀስቀሱ ምክንያት ማንኛውም አይነት የመርከብ ላይ ጉዞ ሲስተጓጎል ትዌይንም ስራውን ለመልቀቅ ተገዷል። ከዚህ በኋላም በውትድርና ወዶ-ገብነት፣ በወርቅ ማእድን ፈላጊነት፣ በጋዜጠኝነት ወዘተ ስረቷል። በ1869 ዓ.ም የመጀመሪያ ዋነኛ ስራው የሆነውን \"The Innocents Abroad\" ለማሳተም በቃ። ይኽ ድርሰት ክሌመንስ ራሱ በአውሮፓ እና በእየሩሳሌም ባካሄዳቸው ጉብኝቶች ላይ የተመሰረተ ነው። በ1870 ዓ.ም ኦሊቭያ ላንግዶንን በማግባት ኑሮውን ኮኔቲከት በተባለችው ግዛት አድርጓ በዛው ለ17 ዓመታት ኖሯል። በነዚህ 17 ዓመታት ነው አድናቆት ያተረፉለት ስራዎቹን ማለትም \"Roughing It\"፣ \"The Adventures of Tom Sawyer\"፣ Life on the Mississippi\"፣ እና ከሁኡ የላቀ የተባለለት ድርሰቱን \"The Adventures of Huckleberry Finn\"ን ያሳተመው። ትዌይን በ1910 ዓ.ም አርፎ ሬዲንግ፣ ኮኔቲከት ውስጥ በድኑ አርፏል። \n \nጥያቄ: የአሜሪካ የእርስ-በርስ ጦርነት የተቀሰቀሰው በስንት ዓመተ ምህረት ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ1861 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአሸናፊ ከበደ ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ አዲስ አበባ ግንቦት ፰ ቀን ፲፱፻፴ ዓ/ም ተወለዱ። አባታቸው ግራዝማች ከበደ አድነው ሲሆኑ ክልጅነታቸው ጀምሮ የሙዚቃ ስሜትንና ፍቅር ያሳደሩባቸው እናታቸው ወይዘሮ ፋንታዬ ነከሬ ነበሩ። አያታቸው ሊቀመኳስ አድነው ጎሹ ደግሞ የአድዋ አርበኛ እናየንግሥት ዘውዲቱም ታማኝ አማካሪ እንደነበሩ ይነገራል። የሙዚቃ ፍቅርን ገና በልጅነታቸው ያሳደሩባቸው እናታቸው ሲሆኑ ታዳጊው አሸናፊ ገና የዘጠኝ ዓመት ልጅ ሳሉ እኒህ የሚያፈቅሯቸውና ዕድሜ ልካቸውን በኀዘን የሚስታውሷቸው እናታቸው ሞተውባቸዋል። መሠረታዊ ትምህርታቸውን በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት እና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ኮከበ ጽባሕ) ካጠናቀቁ በኋላ በሐረር የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ በኒው ዮርክ ክፍለ-ሀገር ከሚገኘው የሮቼስተር ዩኒቨርሲቲ፣ “ኢስትማን የሙዚቃ ትምህርት ቤት” በ፲፱፻፶፬ ዓ/ም በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመረቁ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው፤ የያሬድ ሙዚቃ ትምሕርት ቤትን መሠረቱ። የዚሁ ትምህርት ቤትም የመጀመሪያው ዳይሬክቶር ከመሆናቸውም ባሻገር በአዲስ አበባው የወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማኅበር (ወ.ወ.ክ.ማ Y.M.C.A.)፤ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የበጎ አድራጎት ድርጅት መርሓ-ዕውራን ትምህርት ቤት እና በመሳሰሉ የወጣቶች ማኅበራት እየተገኙ የሙዚቃ ትምህርት ይሰጡ ነበር። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በስንት ዓመተ ምህረት ተመረቁ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ፲፱፻፶፬ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአዶልፍ ሂትለር አዶልፍ ሂትለር (ጀርመንኛ Adolf Hitler አዶልፍ ሂትለ) እ.አ.አ. ከ1933 ጀምሮ የጀርመን ቻንስለር እንዲሁም ከ1934 ጀምሮ ደግሞ የጀርመን መሪም (Führer) ጭምር የነበረ ሰው ነው። ሂትለር በሚያዝያ 13 ቀን 1881 ዓ.ም. (20 አፕሪይል 1889 እ.ኤ.አ.) በዛሬይቷ ኦስትሪያ ተወለደ። በሚያዝያ 22 ቀን 1937 ዓ.ም. (30 አፕሪይል 1945 እ.ኤ.አ.) በርሊን ውስጥ ከአንድ ቀን በፊት ካገባት ሚስቱ ኤቫ ብራውን ጋር የራሱን ህይወት አጠፋ። በ1925 ዓ.ም. መጀመርያ የሂትለር ናዚ ወገን ከጓደኞቹ ወገን ጋር በራይክስታግ ምክር ቤት ትብብር መንግሥት ለመሥራት በቂ መንበሮች አልነበራቸውም። ተቃራኒዎቻቸው የኰሙኒስት ወገን 17% መንበሮች ስለ ነበራቸው የሂትለር ወገኖች የድምጽ ብዛት ሊያገኙ አልተቻላቸውም ነበር። በዚያው ዓመት ግን ከምርጫው ትንሽ በፊት የራይክስታግ ሕንጻ በእሳት ተቃጠለ። ይህ የኰሙኒስቶች ሥራ ነው ብለው የሂትለር ወገን ኰሙኒስት ፓርቲ ቶሎ እንዲከለከል አደረጉ። ስለዚህ ከምርጫው በኋላ የኰሙኒስትን መንበሮች ስለ አጡ የሂትለርም ወገኖች አሁን ከ50% መንበሮች በላይ ስላገኙ፣ የትብብር መንግሥት ሠሩና ወዲያው በድንጋጌ አቶ ሂትለር ባለሙሉ ሥልጣን አደረጉት። ሂትለር የጻፈው የርዮተ አለሙ ጽሑፍ «የኔ ትግል» (Mein Kampf) ሟርት ብቻ ነው። ለመጥቀስ ያህል፦ «ትኩረቴ ወደ አይሁዶች ስለ ተሳበ፣ ቪየናን ከበፊት በሌላ ብርሃን ለማየት ጀመርኩ። በሄድኩበት ሁሉ አይሁዶችን አየሁዋቸው፤ በብዛትም እያየኋቸው፣ ከሌሎች ሰዎች ፈጽሞ እንድለያቸው ጀመርኩ።»... «የግዛቱ (ኦስትሪያ-ሀንጋሪ) ዋና ከተማ የከሠተውን የዘሮች ውሑድ ጠላሁት፤ የዚህን ሁሉ የቼኮች፣ ፖሎች፣ ሀንጋርዮች፣ ሩጤኖች፣ ሰርቦች፣ ክሮዋቶች ወዘተ. የዘሮች ድብልቀት፤ በሁላቸውም መካከል፣ እንደ ሰው ልጅ መከፋፈል ሻገቶ፣ አይሁዶችና ተጨማሪ አይሁዶች።» በነበረው ዘረኛ አስተዳደሩ 6 ሚሊዮን የአውሮፓ አይሁዶችን እና 5 ሚሊዮን ሌሎች የተለያዩ ሀገራት ህዝቦችን (በተለይም ስላቮችን) በገፍ (በሆሎኮስት) አስጨርሷል። በሂትለር ሥር የናዚዎች ፍልስፍና በሂንዱኢዝም እንደሚገኘው በዘር የተከፋፈለ ካስት ሲስተም መመሥረት አይነተኛ ነበር። «አርያኖች» የተባሉት ዘሮች በተለይም የጀርመናውያን ብሔሮች ከሁሉ ላዕላይነት እንዲገኙ አሠቡ። ይህ ዝብረት የተነሣ በርግ ቬዳ ዘንድ በ1500 ዓክልበ. ያህል ወደ ሕንድ የወረሩት ነገዶች «አርያን» ስለ ተባሉ ነው፤ በጥንትም «አሪያና» የአፍጋኒስታን አካባቢ ስም የዘመናዊው ኢራንም ሞክሼ ነበር። በናዚዎቹ እንደ ተዛበው ግን ታሪካዊ ባይሆንም የ«አርያኖች» ትርጓሜ ጀርመናውያን ብቻ ነበሩ፤ ስላቮች (በተለይ የሩስያና የፖሎኝ ሕዝቦች) ግን አርያኖች ሳይሆኑ እንደ ዝቅተኞች ተቆጠሩ። የሂትለር እብደት እየተራመደ በ1926 ዓም የሀንጋሪ ሕዝብ ደግሞ «አርያኖች» ተደረጉ፣ በ1928 ዓም የጃፓን ሕዝብ እንኳን በይፋ «አርያኖች» ተደረጉ፤ በ1934 ዓም የፊንላንድ ሕዝብ ወደ «አርያኖች» በሂትለር ዐዋጅ ተጨመሩ። በሙሶሊኒ ሥር የፋሺስት ጣልያኖች እኛም አርያኖች ነን ቢሉም ጣልያኖች አርያን መሆናቸው በናዚዎች ዘንድ መቸም አልተቀበለም ነበር። \n \nጥያቄ: አዶልፍ ሂትለር መቼ ተወለደ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በሚያዝያ 13 ቀን 1881 ዓ.ም. (20 አፕሪይል 1889 እ.ኤ.አ.) ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቴሌቪዥን ቴሌቪዥን የስዕል እና ድምጽ ምልክቶችን ከማሰራጫ የሚቀበል የመገናኛ ዘዴ ነው። «ቴሌ-» የሚለው ክፍል በግሪክ «ሩቅ» ማለት ቢሆን «-ቪዥን» ደግሞ ከሮማይስጥ visio /ዊዚዮ/ «ማየት» («ትርዒት») ተወስዷል። በአጠቃላይ ቴሌቪዥን ማለት ተንቀሳቃሽ ምስልን (ብዙ ጊዜ ከድምፅ ጋር) ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለማስተላለፍ የሚረዳ የመልዕክት ማስራጫ መንገድ ነው። ይህ ከሆነ ዘንዳ ቴሌቪዥን ምስል መቅጃውንም ሆነ ምስል መቀበያውን መሳሪያ ሁሉ ያጠቃልላል ግን በተለምዶ ቴሌቪዥን የምንለው ምስል መቀበያውን ብቻ ነው። በ1873 እ.ኤ.አ. (1865 ዓም) የእንግላንድ ኤንጅኔር ውሎቢ ስሚስ ባደረገው ጥረት ጥንተ ንጥሩ ሴሌኒይም ብርሃን-አስተላልፎሽ መሆኑን ገለጸ። በ1884 እ.ኤ.አ. ፓውል ጎትሊብ ኒፕኮው የተባለ ጀርመናዊ ክብ የሆነ ዲስክን በስፓይራል በምብሳት ይህ ዲስክ በተሽከረከረ ቁጥር ከፊትለፊቱ የሚመጣውን ብርሃን በቀዳዶቹ በማሾለክ ከሴሌኒይም በተሰራ የካሜራ ግድግዳ ላይ እንዲያርፍ አደረገ። ግድግዳው ብርሃን ሲነካው ያንን ብርሃን ወደ ኮሬንቲ ሃይል በመቀየር ምስልን በኮሬንቲ መልክ በሽቦ ለመላክ ቻለ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ አምፕሊፋየር ስላልነበር የሚላከው ምስል እምብዛም አመርቂ አልነበረም። ከ27 አመታት በኋላ በ1911 እ.ኤ.አ. የራሻው ቦሪስ ሮዚንግ ለመጀመሪያ ጊዜ የሲርቲን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፣ አሁንም ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል ቻለ። ነገር ግን የሚንቀሳቀሱት ምስሎች የጂዎሜትሪ ቅርጽ ነበራቸው ማለትም ሶስት ማዕዘን፣ አራት ማእዘን ወዘተ... ከ7 አመታት በኋላ በ1925 እ.ኤ.አ. ጆን ሎጂ ቤርድ የተሰኘው የስኮትላንድ ተመራማሪ 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለመላክ ቻለ ከዚያም በ1926 እ.ኤ.አ. ጥቁርና ነጭ የሆኑ ምስሎችን ለማስተላለፍ በቃ። በዚህ ጊዜ የሚላኩት ምስል ጥራት 30 መስመር በአንድ ጊዜ ነበር፣ በዚህም ምክንያት የሰውን ፊት ለመለየት አስቸጋሪ ቢሆንም ግን ይቻል ነበር። አቶ ቤርድ በ 1918 ዓ.ም. (26 January 1926 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የቴሌቪዥን መግለጫ ሰጠ። በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ የተሰኘው የቤል ላብራቷር ተቀጣሪ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ መላክ ቻለ። ቀጠል አድርጎም በራዲዮ ወደ ዊፓኒ ኒው ጀርሲ ለመላክ በቃ። በዚያው አመት ፊሎ ፍራንስዎርዝ የመጀመሪያውን የተሟላና በኤሌክትሪክ ስካኒንግ ብቻ የሚስራውን የቴሌቭዥን ስርዓት በተግባር አዋለ።.በጥር 1928 እ.ኤ.አ. (1920 ዓም) መጀመርያው የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያ በስከነክተዲ፣ ኒው ዮርክ ተከፈተ፤ እስከ ዛሬም ድረስ ያሰራጫል። \n \nጥያቄ: በ1926 እ.ኤ.አ. በቴሌቪዥን ጥቁርና ነጭ ምስሎችን ለመጀመሪያ ጊዜ ማስተላለፍ የቻለው ሰው ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ጆን ሎጂ ቤርድ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nመለጋሲ መለጋሲ (Malagasy) ከአውስትሮኔዚያን የቋንቋ ቤተሠብ ቋንቋዎች ሁሉ ምእራበኛው ሲሆን የማዳጋስካር መደበኛ ቋንቋ ነው። 1500-2000 አመታት ከዛሬ በፊት ከእንዶኔዚያ የመጡ የማዳጋስካር ኗሪዎች ቋንቋ በመሆኑ፣ ከቃላቱ መዝገብ 90% ከመቶ በቦርኔዮ እንዶኔዚያ ከተገኘው ቋንቋ ከማአንያን ጋራ ተመሳሳይ ነው። የቀሩትም 10% ቃላት በተለይ ከአፍሪቃ ቋንቋዎች (ከባንቱ) እና ከአረብኛ ተበድረዋል። በአረፍተ ነገር ውስጥ ግሡ ከሁሉ ይቀድማል። ይህ ተራ እንደ ዕብራይስጥ ይመስላል እንጂ ለብዙዎች ቋንቋዎች የተለመደ አይደለም። በየቃሉ ውስጥ ከመጨረሻው ክፍለ-ቃል በፊት የሆነው ክፍለ-ቃል አናባቢ ይጠበቃል፤ ሌሎቹ አናባቢዎችም ይነበነባሉ (በሙሉ አይስሙም)፤ ስለዚህ \"Malagasy\" እንደ ፈረንሳይኛ አጻጻፉ \"Malgache\" (መልጋሽ) ይመስላል። \n \nጥያቄ: በመለጋሲኛ ቋንቋ የሚናገሩ የማዳጋስካር ነዋሪዎች ከየት አካባቢ የመጡ ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከእንዶኔዚያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአሸናፊ ከበደ ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ አዲስ አበባ ግንቦት ፰ ቀን ፲፱፻፴ ዓ/ም ተወለዱ። አባታቸው ግራዝማች ከበደ አድነው ሲሆኑ ክልጅነታቸው ጀምሮ የሙዚቃ ስሜትንና ፍቅር ያሳደሩባቸው እናታቸው ወይዘሮ ፋንታዬ ነከሬ ነበሩ። አያታቸው ሊቀመኳስ አድነው ጎሹ ደግሞ የአድዋ አርበኛ እናየንግሥት ዘውዲቱም ታማኝ አማካሪ እንደነበሩ ይነገራል። የሙዚቃ ፍቅርን ገና በልጅነታቸው ያሳደሩባቸው እናታቸው ሲሆኑ ታዳጊው አሸናፊ ገና የዘጠኝ ዓመት ልጅ ሳሉ እኒህ የሚያፈቅሯቸውና ዕድሜ ልካቸውን በኀዘን የሚስታውሷቸው እናታቸው ሞተውባቸዋል። መሠረታዊ ትምህርታቸውን በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት እና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ኮከበ ጽባሕ) ካጠናቀቁ በኋላ በሐረር የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ በኒው ዮርክ ክፍለ-ሀገር ከሚገኘው የሮቼስተር ዩኒቨርሲቲ፣ “ኢስትማን የሙዚቃ ትምህርት ቤት” በ፲፱፻፶፬ ዓ/ም በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመረቁ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው፤ የያሬድ ሙዚቃ ትምሕርት ቤትን መሠረቱ። የዚሁ ትምህርት ቤትም የመጀመሪያው ዳይሬክቶር ከመሆናቸውም ባሻገር በአዲስ አበባው የወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማኅበር (ወ.ወ.ክ.ማ Y.M.C.A.)፤ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የበጎ አድራጎት ድርጅት መርሓ-ዕውራን ትምህርት ቤት እና በመሳሰሉ የወጣቶች ማኅበራት እየተገኙ የሙዚቃ ትምህርት ይሰጡ ነበር። \n \nጥያቄ: የፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ አያት ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሊቀመኳስ አድነው ጎሹ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበ ፰፻ (800) ዓመተ-ዓለም አካባቢ ደአማት የሚባል መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያና ኤርትራ ተቋቋመ። በሰሜን ኢትዮጵያ የምትገኘው የሀ የደአማት ዋና ከተማ ነበረች። በየመን የሚኖሩት ሳባውያን በደአማት ላይ ተፅዕኖ እንደነበራቸው የሚታመን ሲሆን ይህ ተፅዕኖ ምን ያህል እንደሆነ ግን በእርግጥ አይታወቅም። ወደ ፬፻ (400) ዓመተ-ዓለም አካባቢ የደአማት መንግስት ከስልጣን ሲወድቅ በትናንሽ መንግስቶች ተተካ። ከነዚህ ትናንሽ መንግስቶች አንዱ አክሱም ሲሆን አካባቢውን እንደገና በአንድነት ለመግዛት ችሎ ነበር። የአክሱማውያን ስፈን በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥታዊ ማኅበረሰብ ነበር። በፋርስ ፣ ሮማ እና ቻይና ይገኙ ከነበሩ ታላላቅ መንግሥታት በወደረኛነት የሚቆጠር ትልቅ ኅይል ነበር። በ4ኛው ምእተ-ዓመት አክሱም ወደ ክርስትና ተለወጠ። በ፮ኛው ምእት ዓመት የአክሱማውያን ግዛታዊ ቁጥጥር የዛሬዋን የመን ግዛት ይጨምር ነበር። ግን በ፮ኛው እና በ ፰ኛው አምኣት የአክሱም ሥልጣኔ በእስልምና መነሣት እና መስፋፋት ተዳክሞ ለውድቀት በቃ ። ተከታዩ የዛጔ ሥርወ-መንግሥት ልክ በድንገት እንደተነሳ በድንገት ሲያበቃ ፣ ይኵኖ አምላክ ሥልጣን በ ፲፪፻፷፪ (1262) ዓ. ም. ጨበጡ ፤ እንዲያም ሲል የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥትን መለሱ። ከዚያም ለብዙ ዘመናት የሰለሞናዊው መንግስት ከጠለ። \n \nጥያቄ: የደአማት መናገሻ ከተማ በኢትዮጵያ በየትኛው ክፍል ትገኝ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በሰሜን ኢትዮጵያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአዲስ አበባ መስከረም 23/2012 ዕውቁና አንጋፋው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ በውጭ አገራት የሚሰሩ ኢትዮጵያዊያን ሳይንቲስቶች ወጣቶችን በሳይንስ በማነጽ ተግባር እንዲሰማሩ፤ መንግስትም ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጥሪ አቀረቡ። ፕሮፌሰር ጥላሁን በቻይና ከሚገኙ የምርምር ተቋማት ጋር በመተባበር ኢትዮጵያ ውስጥ የአፍሪካ ሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል ሊያቋቁሙ መሆኑን ይፋ አድርገዋል። የአሜሪካው ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ትምህርት ቤት ዕውቁ ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ በሚዘጋጀው ወርኃዊ የሳይንስ ገለጻ መድረክ ወጣቱን ትውልድ ማስተማርና ማነጽ ለኢትዮጵያ ተስፋ፤ የቻይና ተምሳሌትነት በሚል ትናንት ምሽት ገለጻ አድርገዋል። በአውሮጳዊያኑ ዘመን አቆጣጠር 1943 በኢትዮጵያ የተወለዱት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በናዝሬት፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጅማ የግብርና ቴክኒካል ትምህርት ቤቶች አጠናቀው በቀድሞው የአለማያ እርሻ ኮሌጅ ለሁለት ዓመት ተከታትለዋል። ከዛሬ 55 ዓመታት በፊት በኮሌጅ ቆይታቸው ባሳዩት የላቀ ውጤትም አሜሪካን አገር በሚገኘው የካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምና ትምህር ቤት ተልከው ትምህርታቸውን በማጥናት ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው በቢሾፍቱ የእንስሳት ህክምና ትምህርት ቤት አስተምረዋል። ከሁለት ዓመታት በኋላም ወደ ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ በመመለስ የ3ኛ ዲግሪያቸውን በደቂቀ ሥነ ሕይወት መስክ በማጥናት በአውሮጳዊያኑ አቆጣጠር ከ1980-2006 በተማሩበት ካሊፎርኒያ በዋሽንግተን ስቴት ዩኒቨርሲቲ ከረዳት እስከ ሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አስተምረዋል፤ ተመራምረዋል። እ.አ.አ ከ2017 ጀምሮ ደግሞ የዲስቲንጉሽድ ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ማዕረግ ያገኙ ሲሆን እ.አ.አ ከ1990 ጀምሮ እስካሁን ድረስ ዓለም አቀፍ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል በማቋቋም በዳይሬክተርነት እየመሩ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ በተማሩበት ካሊፎርኒያ ዋሽንግተን ስቴት ዩኒቨርሲቲ በአውሮፓውያን አቆጣጠር ከመቼ እስከ መቼ ቆዩ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከ1980-2006 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአዲስ አበባ አዲስ አበባ ተብላ የተሠየመችው እቴጌ ጣይቱ ኅዳር ፲፬ ቀን ፲፰፻፸፱ (1879) ዓ.ም. ፍልውሃ ፊን-ፊን ወደሚልበት መስክ ወርደው ሳሉ ከዚህ በፊት አይተዋት የማያውቋት አንዲት ልዩ አበባ አይተ ስለማረከቻቸው ቦታውን ‹‹አዲስ አበባ!›› አሉ ይባላል። አዲስ አበባ (ኣዲስ ኣበባ) ኢትዮጵያ ዋና ከተማ ስትሆን በተጨማሪ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ እንዲሁም የብዙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቅርንጫፎችና ሌሎችም የዓለም የዲፕሎማቲክ (የሰላማዊ ግንኙነት) ልዑካን መሰብሰቢያ ከተማ ናት። ራስ-ገዝ አስተዳደር ስላላት የከተማና የክልል ማዕረግ ይዛ ትገኛለች። አብዛኞቹን የሀገሩ ቋንቋዎች የሚናገሩ ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞች የሚኖሩባት ከተማ ናት። ከባሕር ጠለል በ2500 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኘው ከተማ በግምት 2,757,729 በላይ ሕዝብ የሚኖርባት በመሆኗ የሀገሪቱ አንደኛ ትልቅ ከተማ ናት። ከተማዋ እቴጌ ጣይቱ በመረጡት ቦታ ማለትም በፍል ውሐ አካባቢ ላይ በባላቸው በዳግማዊ ምኒልክ በ፲፰፻፸፰ (1878) ዓ.ም. ተቆረቆረች። የሕዝቧ ብዛት በያመቱ 8% (ስምንት በመቶ) እየጨመረ አሁን አምስት ሚሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከእንጦጦ ጋራ ግርጌ ያለችው መዲና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መገኛ ሆናለች። ይህም በመስራቹ የቀድሞው ንጉሠ-ነገሥት ስም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ይባል ነበር። \n \nጥያቄ: አዲስ አበባ የተመሰረተችው በማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በዳግማዊ ምኒልክ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኤስፔራንቶ ኤስፔራንቶ (Esperanto) ከሁሉም አለማቀፋዊ ሠው ሰራሽ ቋንቋዎች እጅጉን የተስፋፋ ቋንቋ ነው። በ1859 እ.ኤ.አ. በዛሬይቷ ፖሎኝ የተወለደውና በሞያው የአይን ሀኪም የሆነው ሉድዊክ ሌይዛር ዛመንሆፍ በ1887 እ.ኤ.አ. ቋንቋውን ለህዝብ አሳወቀ። አላማው ኤስፔራንቶን በቀላሉ ሊማሩት የሚቻል፣ የጋራ የሆነና ለአለማቀፋዊ መግባባት የሚረዳ ግን ያሉትን ቋንቋዎች የማይተካ ቋንቋ ማድረግ ነበር። ኤስፔራንቶ ከ1,600,000 በላይ ተናጋሪዎች ቢኖሩትም የቋንቋው ደጋፊ ያልሆኑ እንግሊዝኛን ከመስፋፋቱ አንፃር ለአለማቀፋዊ ቋንቋነት በተሻለ ይመርጡታል። \n \nጥያቄ: ሉድዊክ ሌይዛር ዛመንሆፍ ኤስፔራንቶ የተሰኘውን ዓለም አቀፋዊ ቋንቋ ያስተዋወቀው መቼ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ1887 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሆ ቺ ሚን ሆ ቺ ሚን ከ1890-1969 እ.ኤ.አ. የኖረ የቬትናም ኮሚኒስት ፓርቲ መሥራችና መሪ ነበር። ሆ ቺ ሚን ከወጣትነት ጊዜው ጀምሮ ለአብዮታዊ ተግባራት የቆመ ነበር። ሆ ቺ ሚን በሥራ ምክንያት ፈረንሳይ ውስጥ በነበረበት ወቅት የካፒታሊስት ሥርዓት ምን ያህል ሠርቶአድሩን ሕዝብ ለሥቃይና ለመከራ እንደዳረገውና የዓለም ወዛደሮች በቀለም በቋንቋና በባህል ቢለያዩም ብሶታቸው አንድ መሆኑን በቅርብ ተገነዘበ። በአፍሪካና በእስያ የኢምፔሪያሊስቶች መምጣት ምን ያህል ሥቃይና ውርደት በእነዚህ ሕዝቦች ላይ እንዳደረሰ ተረዳ። በዚህም ምክንያት ሆ ቺ ሚን የቬትናም ሕዝብ ጠላት የፈረንሳይ ኢምፔሪያሊዝም እንጂ የፈረንሳይ መላው ሕዝብ አለመሆኑን ደጋግሞ ገልጿል። ሆ ቺ ሚን በ1917 እ.ኤ.አ. በፈረንሳይ ወዝአደሮች ትግል ውስጥ በቀጥታ ተሳታፊ በመሆን የፈረንሳይ ሶሻሊስት ፓርቲ አባል ሆነ። ከዚህም በላይ በፈረንሳይ የቬትናም አርበኞችን ማኅበር በማቋቋም በፈረንሳይ ይኖሩ የነበሩትን ቬትናማውያን በማንቃትና በማስተማር ለሀገራቸው ነፃነትና ክብር እንዲታገሉ ያነሣሣ ነበር። የጥቅምቱ የሩሲያ አብዮት ለአያሌ ዓመታት በዓለም ሰፍኖ የነበረውን የኢምፔሪያሊዝም ብቸኛ የበላይነት ሰባብሮ አዲስ ዘመን በማብሰሩ ሆ ቺ ሚን የጀመረውን ትግል ከግብ ለማድረስ የቦልሼቪኮችን ፈለግ መከተል እንዳለበት አመነ። በሆ ቺ ሚን አስተሳሰብ የቬትናም ብቻ ሳይሆን የሌሎች ቅኝ ተገዥ የሆኑ ሀገሮች ነፃነት የሚገኘው የወዝአደሩን የአብዮት ጎዳና በመከተል ብቻ እንደሆነ አጥብቆ ያምን ነበር። የነዚህ ሀገሮች ብሔራዊ ነፃነት ከማኅበራዊ ነፃነት ጋር መያያዙንና ይህም ነፃነት ከሶሻሊዝምና ከኮሚኒዝም ጋር በጥብቅ የተሳሰረ መሆኑን አስገንዝቧል። ሆ ቺ ሚን ከ1924 እስከ 1930 እ.ኤ.አ. በቻይናና በቬትናም በመዘዋወር ለዚህ ውስብስብ ትግል ግንባር ቀደም አመራር ሊሰጥ የሚችለውን ማርክሳዊ ሌኒናዊ ፓርቲ ለማቋቋም ከፍተኛ ትግል አደረገ። በመጀመሪያም የቬትናም አብዮታዊ ወጣቶች ማኅበር የተባለውን በማቋቋም «ወጣት» በተባለው ጋዜጣ ወጣቱን ለትግል ቀሰቀሰ። በዚህ ዓይነት ከብዙ ጥረትና ትግል በኋላም በ1930 እ.ኤ.አ. የኢንዶቻይና ኮሚኒስት ፓርቲን (ኋላ የቬትናም ሠራተኞች ፓርቲ፤ ዛሬ ደግሞ የቬትናም ኮሚኒስት ፓርቲ) መሠረተ። በ1935 እ.ኤ.አ. ሞስኮ ውስጥ የተካሄደው የኮሚኒስቶች ስብሰባ አንድ ሰፊ ፀረ ኢምፔሪያሊስት የሆነ ዲሞክራሲያዊ ግንባር እንዲቋቋም በወሰነው መሠረት ሆ ቺ ሚን ቬትሚን የተሰኘውን ሰፊ ፀረ ኢምፔሪያሊስት ግንባር በማቋቋም መላውን ሕዝብ በትግሉ ለማሳተፍ ችሏል። ዲየን ቢየን ፉ በተባለው ታሪካዊ ስፍራ የቬትናም አርበኞች የፈረንሳይን ጦር በማሸነፋቸው ፈረንሳይ በጀኔቩ ስምምነት መሠረት የቬትናምን አንድነት በማወቅ የሰላም ውል ፈረመች። ነገር ግን ከ1955 እ.ኤ.አ. ጀምሮ የአሜሪካ ኢምፔሪያሊዝም በፈረንሳይ እግር በመተካት የደቡቡን ክፍል ለመቁረስ የጦር ሰፈር በመሥራትና በውስጥ አርበኞች በመጠቀም ጦርነት ከፈተ። ነገር ግን አሜሪካ ከግማሽ ሚሊዮን ወታደሮች በላይና በብዙ ቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ቢያፈስም ቬትናምን ሊያሸንፍ አልቻለም። \n \nጥያቄ: ሆ ቺ ሚን የኢንዶቻይና ኮሚኒስት ፓርቲን መቼ መሰረተ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ1930 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዝናሽ ማሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ በእሁድ ጠዋት ፕሮግራም ከ1979 ጀምሮ በመስራት ትታወቃለች፡፡ በኢትዮጵያ ሬድዮ ለ 16 አመት ያገለገለችው ዝናሽ ከእነ ታደሰ ሙሉነህ ፤ ታምራት አሰፋ ጋር በትጋት የሰራች ሲሆን ከ20 አመት በፊት ከእነ ቤተሰቦችዋ ወደ ምድረ አሜሪካ አቅንታለች፡፡ እምብዛም ልደት መከበር ባልተለመደበት በዚያን ዘመን ከተወለደች ከአንድ አመቷ ጀምሮ እስከ 16 አመቷ ድረስ ቤተሰቦቿ የልደት በዐልዋን እያከበሩላት ያደገችው ዝናሽ ማሞ አብዲበአዲስ አበባ ከተማ ግንቦት 21 ቀን 1954 አ.ም መወለድዋን ለማስታወስ አልተቸገረችም:: ትውልዷም እድገቷም ጠብመንጃ ያዥ ወይም በቅሎ ቤትበሚባለው አካባቢ ነበርእናትና አባቷ ወ/ሮ ሽብሬ ወ/ሃናና አቶ ማሞ አብዲ ይባላሉ:: ዝናሽ ማሞ መጀመሪያ በቄስ ትምህርት ቤት ከፊደል እስከ መልእክተ ዮሀንስ ተምራ ፊደላትን ከለየች በኋላ በበቅሎ ቤት አካባቢ በነበረው አስቀድሞ ኤስ አይ ኤም የልጃገረዶች ክርስቲያን አካዳሚ ተብሎ ይታወቅ በነበረው ጂሲኤ የልጃገረዶች ት/ቤት ከ አንደኛ እስከ ስድስተኛቀጥሎም ይኸው ት/ቤት የፀጋ ክርስቲያን አካዳሚ በመባል ስሙ ተቀይሮ ወንዶችም አብረው መማር በጀመሩበት ት/ቤት ከሰባተኛ እስከ አስረኛበመጨረሻም በጊዜው የነበረው የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግስት ት/ቤቱን ወደ መንግስት ንብረትነት በማዘዋወር የአብዬት ቅርስ ተብሎ ከሰየመው በኋላ አስራ አንደኛና አስራ ሁለተኛ ክፍልን እዚያው ተምራለች:: \n \nጥያቄ: የዝናሽ ማሞ እድገቱዋ የት ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ጠብመንጃ ያዥ ወይም በቅሎ ቤትበሚባለው አካባቢ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበ1240 አካባቢ በግብጽ አገር ቅብጡ አቡል ፋዳዒል እብን አል-አሣል ፍትሐ ነገሥት በአረብኛ ጻፉ። እብን አል-አሣል ሕጎቹን የወሰዱት በከፊል ከሃዋርያት ጽህፈቶችና ከሕገ ሙሴ፤ በከፊልም ከድሮ ቢዛንታይን ነገስታት ሕጎች ነበር። መጽሐፉ በግዕዝ ተተርጉሞ ወደ ኢትዮጵያ የገባበት ወቅት በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን በ1450 አከባቢ እንደነበር የሚል ታሪካዊ መዝገብ አለ። ቢሆንም መጀመርያ እንደ ሕገ ምንግሥት መጠቀሙን የተመዘገበው በዓፄ ሠርፀ ድንግል ዘመን (ከ1555 ጀምሮ) ነው። ፍትሐ ነገስት እስከ 1923 ዓ.ም. የብሄሩን ዋና ሕግ ሆኖ ቆየ። በ1904 ዓ.ም. ዐጼ 2 ምኒልክ የዘመናዊ ሕገ መንግሥት ፅንሰ ሀሳብ ተረድተው በጸሀፊው መምሬ ብስራት አንድ ሕገ መንግሥት የሚመስል ሰነድ ታተመ፤ ይህ ግን በውነት ሕገ መንግሥት አይባልም። «በምኒሊክ ስለተቋቋሙት ሚኒስቴሮች በምሳሌ የቀረበ ጽሑፍ» በምሳሌና በትርጓሜ የእያንዳንዱን ሚኒስቴር ሥራ እንደ ሰውነት አካላት አስመሰለ። ለምሳሌ፦ ኢትዮጵያ መጀመርያ ዘመናዊ ሕገ መንግሥት የተቀበለችው በ1923 አመተ ምኅረት በአጼ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የታወጀ ሲሆን የሕግ አማካሪ ቤቶች በሁለት ያስከፈለ ነው። ይህ የመንግሥታቸው ዋና መሠረት ሆኖ እስከ 1948 አ.ም. አገለገለ፤ በዚያ አመት ተሻሽሎ በወጣ ሕገ መንግሥት ሕዝቦች በመንግሥት ሥራ የሚጫወቱት ሚና እንደገና ተስፋፋ። ይህ ብቻ የአገሪቱ ሕገ መንግሥት ሆኖ እስከ 1967 አ.ም. ቆየ፤ የዛኔ በደርግ (በሕገ መንግስት እራሱ ባልሆነ ሂደት) ተሰረዘ። \n \nጥያቄ: ፍትሐ ነገሥት ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ በሕገ መንግሥትነት ጥቅም ላይ የዋለው መች ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ1555 ጀምሮ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: በማሊ በእርሻና በዓሣ ማጥመድ የሚተዳደረው በመቶኛ ምን ያህል ሕዝብ ይሆናል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 80 ከመቶ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየእስክንድርያ ማስተማርያ ቤት የእስክንድርያ ማስተማርያ ቤት በእስክንድርያ፣ ግብጽ በጥንት (54-373 ዓም ያህል) የተገኘ የክርስትና ሥነ መለኮት ትምህርት ተቋም ነበረ። ተቋሙን የመሠረተው የኢየሱስ ሐዋርያ እና መጀመርያው የእስክንድርያ ጳጳስ፣ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ በ54 ዓም እንደ ሆነ ተጽፏል። የተቋሙ መጀመርያው መሪ በኋላ የእስክንድያ ፮ኛው ጳጳስ የሆነው ዩስቱስ እንደ ተሾመ ይታመናል። ተቋሙ ያስተማረው ከሥነ መለኮት፣ መጽሐፍ ቅዱስና ክርስትናን ጭምር፣ የግሪክኛና የሮማይስጥ ስነ ጽሁፍ፣ ሥነ ጥበብ፣ ስነ አመክንዮ፣ ሥነ ቁጥርና ስነ-ተፈጥሮ ጥናቶች ነበሩ። ለዕውሮችም ማስተማርያ አገልግሎት አቀረቡ። በፓንታይኖስ መሪነት (173-182 ዓም) ተቋሙ ስለ ትምህርቱ ዝነኛ ሆነ። ፓንታይኖስ በክርስትና ከመጠመቁ በፊት፣ የግሪኮች «ስቶዊሲሲም» ፍልስፍና ተከታይ ሆኖ ነበር። ፓንታይኖስ የግሪክ ፍልስፍና ከክርስትና ርዕዮተ አለም ጋር እንዳዋሐደ ይታስባል። ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ ከ182-194 ዓም በተቋሙ መሪነት ተከተለው። ብዙ አረመኔዎች በዚያን ጊዜ ለትምህርት ስለመጡ ከፍልስፍና መሠረት ጀምሮ የክርስትናን ትምህርት ያሳውቃቸው ነበር። በ194 ዓም የሮሜ መንግሥት ቄሣር በክርስቲያኖች ላይ ስላዘረጋው ማሳደድ፣ ቀሌምንጦስ ለጊዜው ከእስክንድርያ ሸሸ። እሱም የጻፋቻው ትልቅ መጻሕፍት ተርፈውልናል። የቀሌምንጦስ ተከታይ ኦሪገኔስ በመከራ ጊዜ ቢሆንም ተቋሙን በ195 ዓም ዳግመኛ አቆመ። ኦሪገኔስ ደግሞ ብሉይ ኪዳን በስድስት ትይዩ ዕብራይስጥና ግሪክኛ ትርጉሞች (ሄክሳፕላ) ያሳተመው እና ብዙ አንድምታ የጻፈው ዝነኛ መምህር ነው። በ373 ዓም በተካሄደው በቁስጥንጥንያ ጉባኤ፣ የጵጵሳት ቅድምንትነት ለሮሜ ፓፓ፣ ከርሱም ቀጥሎ ለአንጾኪያ ጳጳስ እንዲሰጥ የሚል ብያኔ ወረደ። ስለሆነም፣ የእስክንድርያ ጳጳስ የቀድሞ ቀድምትነቱን በማጣቱ፣ በእስክንድርያ ከተማ ውስጥ ትልቅ ሁከት ደረሰ። በዚያም ጊዜ በተደረገው ጉዳት የማስተማርያ ተቋሙ ጠፋ። \n \nጥያቄ: ፓንታይኖስ ከመጠመቁ በፊት የምን ፍልስፍና ተከታይ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የግሪኮች «ስቶዊሲሲም» ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሰቆጣ ሰቆጣ ከ1956 ጀምሮ የዋግ አውራጃ ማዕከል እና የሰቆጣ ወረዳ ዋና ከተማ ነው። ከሰቆጣ 6 ኪሎ ሜትር ወጣ ብሎ የውቅሮ መስቀል ክርስቶስ አለት ውቅር ቤ.ክ. ይገኛል። በዚሁ ቤተ ክርስቲያን ላስታን ከሰቆጣ ሆነው ያስተዳደሩ ዋግሹሞች ደረቅ ቅሪቶች ይገኛሉ። ከአክሱም መዳከም በኋላ በአረብ ጸሐፊዎች ዘንድ እንደ የኢትዮጵያ ዋና ከተማነት ብዙ ጊዜ የሚጠቀሰውኩባር የተሰኘው የጥንቱ የኢትዮጵያ ገናና ማዕከል ሰቆጣ እንደነበር በታሪክ ግንዛቤ አለ። ስለሆነም ይመስላል፣ ላስታን በዋግ ሹም ማዕረግ ያስተዳደሩ ገዢዎች መቀመጫቸው ሰቆጣ ነበር። ከጥፋት በተረፉ መዝገቦች ዘንድ ሰቆጣ ለመጀመሪያ ጊዜ ተጠቅሶ የምናገኘው በ1738ዓ.ም. ሲሆን፣ ዳግማዊ ዓፄ ኢያሱ ወደ ላስታ ባደረጉት ዘመቻ ሰቆጣ ውስጥ በዋግ ሹም ነዓኩቶ ለአብ (የዋግ ሹም ቴዎድሮስ አባት) ቤት ለ5ቀን እንዳረፉ ዜና መዋዕላቸው በማተቱ ነው ። ከዚያም በ19ኛው ክፍለ ዘመን ብዙ የአውሮጳ ተጓዦች ሰቆጣን ሲጎበኙ፣ ዋልተር ፕላውዴን ለምሳሌ በኢትዮጵያ ከሚገኙ 5 ብቻ ነጋድራሶች አንዱ በሰቆጣ ይገኝ እንደነበር መዝግቧል። ከዚያም በ1800ዎቹ መጨረሻ ሰቆጣን የጎበኘው ኤ.ቢ.ዋይልድ ሰቆጣን የላስታ ዋና ከተማ አድርጎ ሲጠቅስ፣ የሰቆጣ ቤተ መንግስት ባለ ሶስት ፎቅና በ1650ዎቹ የተገነባ እንደነበር ያትታል። ቤተ መንግስቱን የሰሩት የፋሲል ግቢን አናጺዎ እደሆኑም መላምት ያቀርባል። ይሄው የአውሮጳ ተጓዝ፣ በ1880ዎቹ የሰቆጣ ገበያ ከአካባቢው ካሉት ሁሉ ግዙፉ እንደነበር ፣ የዝሆን ጥርስ እና በቅሎ ገበያው የደራ እንደነበር፣ እንዲሁም 21፣000 በሬዎች፣ 2፣900 ላሞች፣ 10ሺህ ፍየሎች፣ 1፣500 በጎች በየአመቱ ለግብይት ይቀርቡበት እንደነበር ሳይጠቅስ አላለፈም። ጥር 2፣ 1929 ጣሊያኖች በሰቆጣ ላይ የመርዝ ጋዝ ቦምብ እንደጣሉ በታሪክ ተመዝግቦ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ከ1956 ጀምሮ የዋግ አውራጃ ማዕከል እና የሰቆጣ ወረዳ ዋና ከተማ ማን ናት?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሰቆጣ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሩሲያ ለአለም አቀፍ በይነመረብ አማራጭ የሚሆን አር ዩ ኔት የተሰኘ ኢንተርኔት በተሳካ ሁኔታ መሞከሯን የሀገሪቱ መንግስት አስታውቋል ፡፡ ይሁን እንጂ የተከናወነውን ሙከራ በተመለከተ ዝርዝር መረጃ አለመሰጠቱ በዘገባው ተመላክቷል። እንደ ሀገሪቱ ኮሙኒኬሽን ሚኒስቴር መረጃ ፥ማንኛውም ተጠቃሚ በተደረገው ሙከራ ወቅት ምንም አይነት ለውጥ ማስተዋል አለመቻሉን አስታውቋል፡፡ የሙከራ ውጤቱም ለሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ይቀርባል ነው የተባለው ፡፡ ምሁራኖችበ አንዳንድ ሀገሮች በበይነ መረብ የሚደርስ ጥፋትን እንዳለ ይጠቅሳሉ። በጥናቱ ዩኒቨርሲቲ የኮምፒተር ሳይንቲስት የሆኑት ፕሮፌሰር አላን ውድዋርድ እንዳሉት፥ በሚያሳዝን ሁኔታ የበይነመረብ ሰርጎ ገቦች መበራከት የሩሲያ የጉዞ አቅጣጫ ሌላ ደረጃ እያደረሰ ነው። ቁጥራቸው እየጨመረ ያሉ ሃያላን መንግስታት ዜጎች የሚያዩትን መቆጣጠር የሚፈልጉ ስለመሆናቸው ከኢራን እና ከቻይና መመልከት ይቻላል። ይህ ማለት ሰዎች ሀገራቸው ውስጥ ስለሚሆነው ነገር የመነጋገር እድል አይኖራቸውም፡፡ የተገኘው ውጤት እንደሚያሳየው ባለስልጣኖች እና የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ውጤታማ ምላሽ በመስጠት አደጋዎች እና ስጋቶችን ማስወገድ እንዲሁም በሁለቱም በይነመረብ እና ቴሌኮሙዩኒኬሽን አውታር መረብ ውስጥ የተስተካከለ አሠራር በሩሲያ ፌዴሬሽን እንዲኖር ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸው ተነግሯል። \n \nጥያቄ: ሀገራት የራሳቸውን የበይነ መረብ መተግበሪያ መስራታቸው ችግሩ ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሰዎች ሀገራቸው ውስጥ ስለሚሆነው ነገር የመነጋገር እድል አይኖራቸውም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nግሥላ ግሥላ በእስያ፣ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በመካከለኛው ምሥራቅ የሚገኝ አጥቢ አውሬ ነው። በእስያ የተገኘው ነብር የግስላ ቅርብ ዘመድ ሆኖ፣ በአነጋገር «ግስላ»ና «ነብር» የሚሉ ስሞች ሊለዋወጡ ይችላሉ። የአንድ ጎልማሳ ግሥላ ክብደት ከ35 እስከ 80 ኪ.ግ ሲደርስ በርዝመት ከ90 ሴ.ሜ እስከ 1,60 ሜ.ና በአፍሪካ የሚገኘው ዘር እስከ 1,90 ሜ ይደርሳል ። ከመሬት እስከ ሆዱ ከ50 እስከ 70 ሴ.ሜ ቁመት ሲኖረው ጭራው ደግሞ እስከ 100 ሴ.ሜ ርዝማኔ ያሳያል ። ሴቲቱ ከወንዱ አነስ ትላለች ። በዱር ሲኖር እስከ 10 አመት እንደሚኖር ሲታወቅ በሰው ተይዘው ሲኖሩ እስከ 20 አመት እድሜ ያስመዘገቡ ግሥሎች አሉ። \n \nጥያቄ: ግሥላ አጥቢ አውሬ ሲሆን የሚገኘው የት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በእስያ፣ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በመካከለኛው ምሥራቅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዶናልድ ጆን ትራምፕ ዶናልድ ጆን ትራምፕ (ጁን 14 ቀን 1946 እ.ኤ.አ. ተወለደ) አሜሪካዊ ነጋዴ ፣ ፖለቲከኛ ፣ በቴሌቪዥን ፕሮግራሞቹ ታዋቂ እና 45ኛው የዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ ፕሬዚደንት ነው። ሥልጣኑንም እ.ኤ.አ. በጃኑዌሪ 20 ቀን 2017 ተረክቧል። በክዊንስ ኒው ዮርክ ከተማ የተወለደው አቶ ትራምፕ በሪል እስቴት ሥራ ላይ ተሰማርቶ የነበረው የፍሬድ ትራምፕ ልጅ ነው። በኮሌጅ እያለም ኤሊዛቤት ትራምፕ ኤንድ ሰንስ በተባለው ድርጅት ይሠራ ነበር። በእ.ኤ.አ. 1968 ከኮሌጅ ከተመረቀ በኋላ ያንን ድርጅት ተቀላቀለ። በእ.ኤ.አ. 1971 ደግሞ ሙሉ ሥልጣን ከተሠጠው በኋላ የድርጅቱን ስም ወደ \"ዘ ትራምፕ ኦርጋናይዜሽን\" ለወጠው። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ካሲኖዎችን ፣ የጎልፍ ሜዳዎችን ፣ ሆቴሎችን እና ሌሎች በእርሱ ስም የሚጠሩ ንብረቶችን አፍርቷል። እ.ኤ.አ. ከ2005 እስከ 2015 ድረስ ዘ አፕሬንቲስ የተባለ ፕሮግራምን በኤን ቢ ሲ ላይ ያቀርብ ነበር። እ.ኤ.አ. በ2000 ላይ፣ ትራምፕ ለመጀመሪያ ጊዜ ለዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንትነት ተወዳድሮ ሁለት የሪፎርም ፓርቲ እጩነትን አሸንፎ ነበር። በእ.ኤ.አ. ጁን 16 2015 ላይ ደግሞ ለፕሬዚደንትነት እንደሚወዳደር አሳወቀ። ይህን ጊዜ ግን የሪፐብሊካን ፓርቲን በመወከል ነው። በስደት፣ በነፃ ገበያ እና በጦር ጣልቃ ገብነት ላይ ባለው ተቃውሞ ምክንያት ታዋቂ ሆኗል። በእነኚህ አነጋጋሪ አስተያየቶቹ በመላው ዩናይትድ ስቴትስ የተቃውሞ እና የድጋፍ ሰልፎች እንዲካሄዱ ምክንያት ሆኗል። በእ.ኤ.አ. ሜይ 2016 ከሪፐብሊካን የፕሬዚደንታዊ እጩነት ውድድሮች ውስጥ 28ቱን ውድድሮች ካሸነፈ በኋላ እና የተቀሩት ተቀናቃኞቹ እነ ቴድ ክሩዝ እና ጆን ካሲች ከውድድሩ ራሳቸውን ስላገለሉ፥ ትራምፕ ለሪፐብሊካን ፓርቲ እጩ መሆኑ የተረጋገጠ ሆኗል። በእ.ኤ.አ. ከጁላይ 18 እስከ 21 በተካሄደው የ2016ቱ የሪፐብሊካኖች አገር አቀፍ ስብሰባ ላይ እጩ መሆኑ በይፋ ታወጀ። በእ.ኤ.አ. ኖቬምበር 8 ቀን 2016 ላይ የፕሬዚደንትነት ምርጫውን አሸነፈ። ማሸነፉንም ተከትሎ ብዙ የተቃውሞ ሠልፎች በተለያዩ የአሜሪካ ከተሞች ውስጥ ተካሂዶ ነበር። በ70 ዓመቱም ሥልጣን ላይ በመውጣቱ ከእርሱ በፊት ከነበሩት ፕሬዚደንቶች ሁሉ በዕድሜ ትልቁ ያደርገዋል። \n \nጥያቄ: ዘኦፕሬንተስ የተባለው ፕሮግራም በኤን ቢ ሲ ላይ መቼ ቀረበ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በእ.ኤ.አ. 1971 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቀጭኔ ከዝሆን በስተቀር ማንኛውም ሌላ እንስሳ ሊደርስ በማይችልበት ከፍታ ላይ የሚገኙ ረዣዥም ቀንበጠቦችን ለመብላት የሚያስችል አስደናቂ አፈጣጠር አላት። ልዩ የሆነ የመቆንጠጥ ችሎታ ያለው የላይኛው ከንፈሯና እንደተፈገለው የሚተጣጠፍ ችሎታ ያለው ምላሷ ሹል በሆኑ እሾሆች የታጠሩ ቅጠሎችን ለመቀንጠብ ያስችሏታል። ቀጭኔዎች በቀን እስከ 34 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕፅዋት መመገብ ይችላሉ። የተለያዩ ዕፅዋትን የሚበሉ ቢሆኑም ይበልጥ የሚመርጡት በአፍሪካ ሜዳዎች የሚገኙትን እሾሃማ ግራሮች ነው። አንድ ወንድ ቀጭኔ ምግብ ለመፈለግ ምላሱን እስከ 42 ሳንቲ ሜትር መዘርጋት ይችላል። የቀጭኔ አንገት በጣም አስደናቂ የሆነ የመተጣጠፍ ችሎታ አለው። ይህም ላይኛዎቹን የዛፍ ቅርንጫፎች ለመቀንጠብ በምታደርገው እንቅስቃሴ ረዥሙን ራሷን እንደ ልቧ ለማዘንበልና ለማዟዟር ያስችላታል። ለቀጭኔ ወደ ላይ መንጠራራት በጣም ቀላል ነገር ሲሆን ተጎንብሶ ውኃ መጠጣት ግን ይከብዳታል። ወደ ውኃ ጉድጓድ በምትቀርብበት ጊዜ የፊት እግሮቿን ቀስ በቀስ ከፍታ ካራራቀቻቸው በኋላ ወደ ውኃው ለመድረስ እንድትችል ሁለት ጉልበቶቿን አጠፍ ታደርጋለች። ቀጭኔዋ እንዲህ ባለው አመቺ ባልሆነ ሁኔታ እያለች ረዥም አንገቷን እስከ መጨረሻ ትዘረጋለች። ደግነቱ ግን ከምትመገባቸው ቅጠላ ቅጠሎች በቂ እርጥበት ስለምታገኝ ቶሎ ቶሎ መጠጣት አያስፈልጋትም። የቀጭኔ አንገትና ትከሻ የቅጠል ቅርፅ ባላቸውና ቀጫጭን በሆኑ ነጭ መስመሮች ያጌጠ ነው። ቀለማቸው የተለያየ ሲሆን ከወርቃማ ዳለቻ አንስቶ እስከ ቡናማ እንዲያውም ጠቆር እስካለ ቀለም ይደርሳል። የቀጭኔ ዕድሜ እየገፋ በሄደ መጠን ቀለሟም እየጠቆረ ይሄዳል። ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው። አንዲት ነፍሰ ጡር ቀጭኔ ልጅዋን ከ420 እስከ 468 ለሚደርሱ እርግዝና ቀናት ከተሸከመች በኋላ ሁለት ሜትር ቁመት ያለው ግልገል ትወልዳለች። ግልገሏ በምትወለድበት ጊዜ ራስዋን ታስቀድምና ከሁለት ሜትር ከፍታ ላይ ወደ መሬት ትወረወራለች። ይሁን እንጂ በ15 ደቂቃ ውስጥ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባት እየተውተረተረች ትነሳና ጡት ለመጥባት ዝግጁ ትሆናለች። ከሁለት ወይም ከሦስት ሳምንት በኋላ በደመ ነፍስ ተመርታ የግራር ቀንበጦችን መለቃቀም ስለምትጀምር ብዙም ሳትቆይ ረዥም እርምጃ ያላትን እናትዋን ተከትላ ለመሄድ የሚያስችል ጉልበት ታገኛለች። አንዲት የቀጭኔ ግልገል በጣም ውብ መልክ ሲኖራት የወላጆችዋ አነስተኛ ግልባጭ ነች። ቁመቷ ከቀጭኔ ርዝመት ጋር ሲወዳደር አጭር ብትሆንም ከብዙ ሰዎች ቁመት ግን ትበልጣለች። በእናቷ ጥንቃቄ የተሞላበት ጥበቃ ተማምና አላንዳች መሸበር አካባቢዋን የምትማትረው ግልገል ላያት ሁሉ ልዩ መስህብ አላት። ግልገል ቀጭኔዎች በተወለዱበት ወራት በግልገል መዋያ ተሰባስበው ሙሉውን ቀን ዕረፍት በማድረግ፣ በመጫወትና በአካባቢያቸው የሚሆነውን ነገር በመመልከት ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ። የቀጭኔ ግልገል ለማመን በሚያዳግት ፍጥነት ያድ⁠ጋል። በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ አንድ ሜትር የሚያክል ቁመት ሲጨምር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በእጥፍ ያድጋል። በአንድ ሳምንት ብቻ 23 ሳንቲ ሜትር ያህል ሊያድግ ይችላል! እናትዬው ለልጅዋ ከፍተኛ ጥበቃ የምታደርግ ሲሆን ልጅዋ የተወሰነ ርቀት እንድትዘዋወር ብትፈቅድላትም ሩቅ የማየት ችሎታ ስላላት በዓይኗ ትከታተላታለች። ቀጭኔ ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ስላላት ከአንበሳ በቀር የሚያጠቃት ጠላት የለም። ቢሆንም ይህችን የምታምር ፍጥረት የሰውን ያህል በብዛት አድኖ የገደለ የለም። ቀጭኔ በሚያምር ቆዳዋ፣ በሚጣፍጥ ሥጋዋና አንዳንዶች ምትሐታዊ ኃይል አለው በሚሉት ረዥምና ጥቁር ጭራዋ ምክንያት እጅግ ተፈላጊ ስለሆነች በአሁኑ ጊዜ የዚህች ሰላማዊ ፍጡር የወደፊት ሕልውና ስጋት ላይ ወድቋል። በአንድ ወቅት በብዙ የአፍሪካ አካባቢዎች እንደ ልብ ትታይ የነበረችው ቀጭኔ በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው በቂ ጥበቃ በሚደረግላት ፓርኮች ብቻ ሆኗል። የቀጭኔ አካላዊ ቅርጽና ግዝፈት ችግሮች ማስከተሉ አይቀርም ብሎ የሚያስብ ይኖር ይሆናል። በጣም ትልቅ ቁመትና ረዥም አንገት ስላላት የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖራትና ወደ ሁሉም የአካሏ ክፍሎች ደም እንዲደርስ ማድረግ የማይቻል ነገር ሊመስል ይችላል። ለምሳሌ ያህል ቀጭኔ አንገቷን ወደ መሬት ስታጎነብስ በስበት ኃይል ምክንያት ብዙ ደም ወደ ጭንቅላቷ ፈስሶ አንጎሏን ማጥለቅለቅ ነበረበት። ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ደሟ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ልቧ ተመልሶ ራሷን እስከ መሳት ሊያደርሳት ይገባ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ነገር አይደርስም። ለምን? የቀጭኔ የደም ዝውውር ሥርዓት በዓይነቱ ልዩ ለሆነው ለዚህች እንስሳ ቅርጽና መጠን እንዲያገለግል ሆኖ በታላቅ ጥበብ የተሠራ ነው። ልቧ ራሱ በጣም ትልቅ ሲሆን ደሙን ሦስት ሜትር ተኩል ገደማ ርቆ እስከሚገኘው እስከ አንጎላ ለመግፋት የሚያስችል አቅም አለው። በደቂቃ እስከ 170 ጊዜ የሚመታውና 7 ሳንቲ ሜትር ያህል ውፍረት ባለው ጡንቻ የተገነባው የቀጭኔ ልብ ከሰው የደም ግፊት በሦስት እጥፍ የሚበልጥ ግፊት ያመነጫል። ወደ አንጎል የሚሄደውን ደም የሚሸከመው ካሮቲድ የተባለው የደም ቧንቧና ከአንጎል ወደ ልብ የሚመለሰውን ደም የሚሸከመው ጀጉላር የተባለው የደም ቧንቧ እንዲህ ያለውን ከፍተኛ ግፊት መቋቋም የሚያስችል መጠን ሊኖራቸው ይገባል። በእርግጥም እነዚህ የደም ቧንቧዎች ከ2.5 ሳንቲ ሜትር በላይ ስፋት ያላቸው ከመሆኑም በላይ ጠንካራና የመለጠጥ ችሎታ ባላቸው ሕዋሳት የተገነቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥንካሬና የመለመጥ ችሎታ አላቸው። ቀጭኔ ከጭንቅላቷ ጎንበስ በምትልበት ጊዜ ወደ አንጎሏ የሚሄደውን የደም ፍሰት የሚቆጣጠሩ ልዩ መቆጣጠሪያዎች አሏት። አንጎልና አንገት በሚገናኙበት ቦታ ላይ ትልቁ ካሮቲድ የደም ቧንቧ ሬቴ ሚራቢሌ ተብሎ ከሚጠራ አስደናቂ የሆነ መረብ መሰል አካል ይገናኛል። በከፍተኛ ኃይል ተገፍትሮ የመጣው ደም እዚህ ጋር ሲደርስ በጣም በርካታ ወደሆኑ ትናንሽ የደም ሥሮች እንዲገባ ስለሚደረግ የደሙ ግፊት ተስተካክሎ በአንጎል ላይ ጉዳት የማያስከትል ይሆናል። ቀጭኔዋ ራስዋን ጎንበስ በምታደርግበት ጊዜ ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው መረብ ይለጠጣል፤ ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ይኮማተራል። ይህም የስበት ኃይል የሚያሳድረው ተጽዕኖ ሚዛኑን የጠበቀ እንዲሆን ማድረግና የደም ግፊቷ በእጅጉ ቀንሶ ራሷን የምትስትበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ለመከላከል ይረዳታል። የሳይንስ ሊቃውንት በጣም አስደናቂ ርዝመት ያለው የቀጭኔ አንገት ያሉት አከርካሪዎች ቁጥር ከአይጥ ወይም ከብዙዎቹ አጥቢ እንስሳ ጋር እኩል መሆኑን ሲያውቁ በጣም ተደንቀዋል! ይሁን እንጂ የቀጭኔ አከርካሪዎች በጣም ረዣዥሞችና እርስ በርሳቸው ልዩ በሆነ ሁኔታ የተሰካኩ በመሆናቸው እንደ ልብ ሊተጣጠፉ ይችላሉ። ቀጭኔ አንገቷን መጠምዘዝና ማጠፍ ስለምትችል ሁሉንም የአካሏን ክፍሎች ለመላስም ሆነ ረዣዥም የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ለመድረስ ትችላለች። \n \nጥያቄ: በደቂቃ እስከ 170 ጊዜ የሚመታው የቀጭኔ ልብ ምን ያህል ውፍረት አለው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 7 ሳንቲ ሜትር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nተክለጻድቅ መኩርያ ተክለጻድቅ መኩርያ በ፲፱፻፮ ዓ.ም. በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ አሳግርት ልዩ ስሙ ሳር አምባ በተባለ ሥፍራ ተወለዱ። ዕድሜያቸው ለትምሕርት ሲደርስ መጀመሪያ ከአባታቸውና ቀጥሎም በአጥቢያቸው ባህላዊውን ትምሕርት እስከቅኔ ያለውን ቀስመዋል። ከዚያም አዲስ አበባ መጥተው አሊያንስ ፍራንሴዝና ተፈሪ መኮንን ትምሕርት ቤት ገብተው የጊዜውን የትምሕርት ደረጃ አጠናቀዋል። ኢጣልያ አገራችንን የወረረች ጊዜም በየካቲት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ.ም. ፍጅት ተይዘው ወደ ሶማሌ ደናኔ ተግዘው ለሦስት ዓመታት ታስረዋል። ከነጻነትም መልስ አገራቸውን በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች አገልግለዋል። መጀመሪያ ተቀጥረው ያገለገሉት በትምሕርትና ሥነጥበብ ሚኒስቴር ነበር። እዚያም ሳሉ በአገራችን ሰው የተጻፈ የአገራችን ታሪክ አንድም ባለመኖሩ በቁጭትና በመቆርቆር ነበር ‘መጻፍ አለብኝ’ ብለው በደንብ ከሚታወቀው ከቅርቡ ጊዜ በቅጡ ወደማይታወቀው የሩቁ ዘመን መጻፍ የጀመሩት። የመጀመሪያውን መጽሐፍ “የኢትዮጵያ ታሪክ ከዓፄ ቴዎድሮስ እስከ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ” የሚለውን በ ፲፱፻፴፰ ዓ.ም. አሳተሙ። ከጫፍ እስከ ጫፍ ጽፈው የመጨረቻውን መጽሐፍ፣ የታሪካችን መጀመሪያ የሚሆነውን “የኢትዮጵያ ታሪክ ኑብያ-አክሱም-ዛጉዬ እስከ ዓፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት” የሚለውን በ፲፱፻፶፩ ዓ.ም. አቅርበዋል። እኒህኑ መጻሕፍት ትምሕርት ሚኒስቴር ታሪክ ለማስተማሪያ በትምሕርት ቤት ተጠቅሞባቸዋል። ተክለጻድቅ ከታሪክ ውጭ የጻፏቸው “የሰው ጠባይና አብሮ የመኖር ዘዴ” እና በሚዮቶሎዢያ (አፈ ታሪክ) ላይ ያተኮረ “ከጣዖት አምልኮ እስከ ክርስትና” የሚሉም መጽሐፎች አሏቸው። ተክለጻድቅ በምድር ባቡር በዋና ጸሐፊነት፥ በቤተ መጻሕፍት ወመዘክር ዋና ሥራ አስኪያጅነት፥ እንዲሁም በፈረንሳይ፥ በእስራኤል፥ በዩጎዝላቪያ በዲፕሎማሲ ሥራ በመጨረሻም የትምሕርትና የባህል ሚኒስቴር ሆነው አግልግለዋል። በፈቃዳቸው ጡረታም ከወጡ በኋላ በምርምር የታገዙ ሦስት ታላላቅ የታሪክ ሥራዎችን አቅርበዋል። ተክለጻድቅ ከረጅም የአገልግሎት ዘመን በኋላ በተወለዱ በ ሰማንያ ስድስት ዓመታቸው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፱፻፺፪ ዓ.ም. አርፈዋል። \n \nጥያቄ: ተክለጻድቅ መኩርያ በስንት ዓመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለዩ ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ ሰማንያ ስድስት ዓመታቸው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኢትዮ ሬይን ሜከርስ ኢትዮ ሬይን ሜከርስ (Ethio Rain Maker) በኢትዮጵያ ውስጥ ዛፎች በመትከል ረሃብን ለመከልከል የተቋቋመ ቡድን ነው። አሁን ወደ ምድረ በዳ መጥተው በወንድማማችነት ገነት ይሠራሉ። በድርቅ አፈር ውስጥ የሚተክሉት ዘር ታላቅ ደን ይሆናል፤ ምድሪቱ እንደገና በሙሉ እስክትሸፈን ድረስ ረጀም ዛፎች በዝተው አረንጓዴ ክንፎቻቸውን ይዘረጋሉ። ሀገራችን ኢትዮጵያ በአለም መገናኛ ብዙሃን በረሃብ ስትጠራ፣ ህዝቦችዋ በጠኔ ሲሰቃዩ ዘመናት ተቆጥረዋል። የወገኖቻችን ስቃይ፣ የሀገራችን ኋላ ቀርነት በኢትዮጲያዊነታችን እያንዳንዳችንን ይመለከተናል። ላለፉት ሰላሳ አመታት በጎ አድራጊ ድርጅቶች በአይነትም ሆነ በጥሬ ገንዘብ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እንደረዱን መረጃ አውጥተዋል። የኛ ስቃይ ግን አላበቃም። መከር ሲመጣ ሰብል ከማጨድና ምርት ከመሰብሰብ ይልቅ ለልመና እጁን የሚዘረጋ ኢትዮጲያዊ ቁጥር በሶስት እጥፍ ጨመረ። ይህ ሂደት መቆም አለበት። እንዴት? አበው “ነገርን ከስሩ …” እንደሚሉት የሁሉም ችግር መፍትሔው ያለው ከመነሻው ላይ ነው። የኛ ረሐብ መንስዔው ምንድነው? በአጭሩ ለመግለጽ ያህል ለረሐባችን መንስዔ የዝናብ አለመኖር (ድርቅ) መሆኑን ከረሐባችን ታሪክም ሆነ ጥናቱን ካካሄዱት ምሁራን መረዳት ይቻላል። ዛሬም ቢሆን ገበሬው ዝናብ በማጣቱ ሰብሉ መበላሸቱን ከአንደበቱ እየሰማን ነው። ጦርነትን ለማቆም የጦርነት መነሻ ሃሳቦችን ማስወገድ እንጂ ጦርነትን ከጦር ሜዳ ማስቆም እንደማይቻል ሁሉ የሃገራችንንም ረሃብ ከመንስዔው እንንቀለው። ኢትዮ ሬይን ሜከርስ፣ ኢትዮጵያ ዉስጥ ደን ማደነን (አፎረስቴሽን) ችግራችንን ከመቅረፊያ መንገዶች አንዱ እንደሆነ በማመን የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም ችግኞችን መትከል ጀምሯል። በ1995 ዓ.ም. ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለ አደራ ጋር በመተባበር በእንጦጦ የተፈጥሮ መናፈሻ አስር ሺህ ችግኞችን ተክሎ ሰባ ሁለት ከመቶው (7167) ፀድቋል። በ1996 ክረምት ደግሞ ሀምሳ ሺህ ችግኞችን ለመትከል አቅዶ ሀያ ከመቶው ተጠናቋል። በአሰላ፣ በመቀሌና በባህር ዳር አንድ ሺህ ዛፎችን የሚይዙ የተፈጥሮ መናፈሻዎችንን በመስራት ላይ ነን። በ1997 ለሀገራችን የሺህ አመት ስጦታ እንስጥ በሚል መነሻ ሀሳብ እያንዳንዱ ኢትዮጲያዊ አንድ ዛፍ ተክሎ የሚንከባከብበትን እቅድ አውጥተናል። ከነዚህም አንዱ አንድ ዛፍ ለአንድ ተማሪ ነው። የሃገራችን የዘመናት ችግር በአንድ አመትና በጥቂት ሰዎች ጥረት አይፈታም። ለዚህ አላማ መሳካት የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥረትና እገዛ ያስፈልጋልና ሃገራችንን ከረሐብ ለመታደግ አብረን ዛፍ እንትከል። እንንከባከብም። \n \nጥያቄ: ኢትዮ ሬይን ሜከርስ በ1995ዓ.ም. ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለደራ ጋር በመሆን በእንጦጦ ከተከሉት አስር ሺህ ችግኝ ምን ያህሉ ጸደቀ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሰባ ሁለት ከመቶው (7167) ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአብርሀም ሊንከን (የካቲት ፮ ቀን ፲፰፻፩ ዓ.ም. - ሚያዝያ ፰ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም.) ድረስ የኖሩ ከ፲፰፻፶፫ ዓ.ም. እስከ ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ድረስ ፲፮ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ከአሜሪካ የእርስ በርስ ጦርነት ፍጻሜ በኋላ ጆን ዊልክስ ቡዝ በተባለ ነፍሰ ገዳይ እጅ በጥይት ተመትተው ተገደሉ። የአብርሀም አባት ማሀይም ገበሬ ቢሆንም፣ አብርሀም ከልጅነት ጀምሮ እራሱን በትጋት ያስተምር ነበር። በ፲፰፻፳፮ ዓ.ም. ለኢሊኖይ ክፍለ ሀገር ምክር ቤት መቀመጫ ተመረጡ። የሕግ ትምህርት በጠንካራ ትጉነት አጥንቶ የሕግ ባለሙያ ሆነ። ከ፲፰፻፳፱ ዓ.ም. ጀምሮ የባርነት ተቃዋሚ ሆነ። ከአፍሪካ የተወሰዱት ጥቁር ሕዝቦች በግብርና መሥራት እንዲገደዱ ትክክለኛ ወይም ጥሩ ሀሣብ አይደለም ብለው አመኑ። ዳሩ ግን በ1834 ብዙ ባርያዎች ባገለገሉበት ቤተሠብ ውስጥ ያደገችውን ሚስታቸውን ሜሪ ቶድን አገቡ። ሜሪ ያለ ባርያዎች ከባልዋ ጋር መኖር ትንሽ የተቸገሩ ቢሆነም ከጊዜ ብዛት ግን ለምደዉ 4 ወንድ ልጆችን በተከተሉት አመታት ወለዱ። በ፲፰፻፵፮ ዓ.ም. የባርነት ተቃዋሚዎች ወገን ሪፐብሊካን ፓርቲ መሥርተው አብርሀም ከፍተኛ ሚና ተጫወቱ። በ፲፰፻፶፪ ዓ.ም. የፕሬዚዳንትነት ምርጫ ዘመቻ፣ እሳቸው የሪፐብሊካን ዕጩ ሆኑ። ምርጫው በተደረገበት ቀን በጥቅምት ፳፰ ቀን ፲፰፻፶፫ ዓ.ም.፣ ሊንከን አሸነፉ። በጦርነቱ የስሜን ሠራዊት ከብዛታቸው የተነሣ በአራት ዓመት ውስጥ አሸነፉ። በዚህ ጊዜ ላይ ሊንከን ለአመጸኖቹ ባርዮች ነጻነት አዋጁ። ያላመጹ ዜጎች ባርያዎች ግን በዚያን ጊዜ ነጻ አልወጡም። በ፲፰፻፶፮ዓ.ም.ምርጫ ሊንከን በቀላል ለሁለተኛ ጊዜ ለፕሬዚዳንትነት ተመረጡ። በሚያዝያ ፪ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. የኮንፌደራት ሠራዊት እጁን ሰጠ። ነገር ግን ሚያዝያ ፯ ቀን የመድረክ ትርዒት ሲያዩ በነፍሰ ገዳዩ በጆን ዊልክስ ቡዝ እጅ በጥይት ተመትተው በማግሥቱ ሞቱ። ከዚህም ትንሽ በኋላ ባርነት በሕግ በሙሉ ተክለክሎ የተረፉት ባርያዎች ነጻነት አገኙ። \n \nጥያቄ: አብርሃም ሊንከን ባርነትን መቃወም የጀመሩት መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከ፲፰፻፳፱ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአሪዞና አሪዞና (Arizona) በምዕራባዊ ዩናይትድ ስቴትስ የሚገኝ ክፍላገር ነው። ኒው ሜክሲኮ ፣ ዩታህ ፣ ኔቫዳ ፣ ካሊፎርኒያ እና ኮሎራዶ ያዋስኑታል። የአሪዞና ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ የ30 ሰው ሴኔት እና የ60 ሰው ምክር-ቤት አለው። የሪፑብሊካን ፓርቲ በስቴቱ ዋነኛው ፓርቲ ነው። በ2002 እ.ኤ.አ. የአሪዞና ስቴት ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ በጀት 14.3 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በጀት ደግሞ 13.8 ቢሊዮን ዶላር ነው። የስቴቱ ሴኔተሮች እና ምክር-ቤት ተወካዮች ለሁለት-ዓመት ጊዜ ላልተወሰነ ብዛት ይመረጣሉ። ከ4 ጊዜ በላይ በተካካይ መመረጥ ግን አይችሉም። የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በአስተዳዳሪ የሚመራ ሲሆን ለ4 ዓመት ሥልጣን ላይ ይቆያል። ያልተወሰነ ጊዜ መወዳደር ሲቻል ከሁለት ጊዜ በላይ ግን በተካካይ መመረጥ አይፈቀድም። \n \nጥያቄ: የአሪዞና ሕግ አውጪ የ30 ሴኔት አባላትና የስንት ምክር ቤት አባላት ውቅር ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የ60 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nመስከረም 23/12 ዓ ም ሽሬ ኢዜአ የተለያዩ የፈጠራ ውጤቶችን ለተጠቃሚዎች በማቅረብ ይሁንታ ያገኘው የ35 ዓመት ወጣት ሔሊኮፕተር ሰርቶ ለሙከራ እየተዘጋጀ መሆኑን አስታወቀ ። ወጣት ዕበ ለገሰ ይባላል ። በመደበኛ ትምህርት ብዙ ገፍቶ ባይሔድም በፈጣራ ብቃቱ ግን በርካታ ስራዎች ለህዝብ እንዲያደርስ አድርጎታል ። የ10ኛ ክፍል ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ በኤሌክትሪክ ሃይል የሚሰራ ምጣድ ጥገና ሥራ የጀመረው ወጣት አሁን ላይ ትልቅ ራእይ አንግቦ የራሱ የሆኑ የፈጠራ ስራዎችን በማቅረብ ውጤታማነቱን በተጠቃሚዎች ዘንድ እየተመሰከረለት መጥቷል ። የምጣድ ጥገና ስራው ለታናሽ ወንድሙ በመልቀቅ የወርቅ መአድን መፈለጊያ መሳሪያ ወደ ማሻሻል መሸጋገሩን ይገልፃል ። በራሱ ፈጠራ ያሻሻለው የወርቅ መፈለጊያ መሳሪያ በባህላዊ መንገድ ወርቅ ለሚያመርቱ ሰዎች በሽያጭ በማቅረብ የፍለጋ ሥራቸውን እንዲቃለል እንዳስቻላቸው ተጠቃሚዎቹ ይናገራሉ ። ቀደም ሲል የነበረው ‘’ጂ አር ዜድ’’ የተባለው የወርቅ መፈለጊያ መሳሪያ ከ70 እስከ 80 ሳንቲ ሜትር ጥልቀት ባለው መሬት ውስጥ የሚገኝ የደለል ወርቅ የሚጠቁም ነበር ። ወጣቱ ያሻሸለው ግን በአንድ ሜትር ጥልቀት የሚገኘውን የደለል ወርቅ በቀላሉ መለየት የሚያስችል መሳርያ ሆኖ ተገኝቷል ። እንዲሁም ከድንጋይ ጋር ተደባልቆ የሚገኝ ወርቅ በቀላሉ መለየት የሚያስችል የድንጋይ ወፍጮ በመፍጠር ለተጠቃሚዎቹ በማቅረብ ላይ እንደሚገኝም ወጣት ለገሰ ይናገራል ። ባለፉት አምስት ዓመታት አምስት የድንጋይ ወፍጮዎችን በመስራት ለተጣቀሚዎቹ በተመጣጣኝ ዋጋ አቅርቧል ። በተጠናቀቀው ዓመት በራሱ ፈጠራ ሶስት ሰዎች የማሳፈር አቅም ያለት ሔሊኮፕተር ሰርቶ በሙከራ ደረጃ ለህዝብ እይታ አቅርቦ የነበረው ወጣቱ ዘንድሮ ለማብረር እየተዘጋጀ መሆኑንም ተናግሯል ። የፈጠራ ሥራዬ ስኬትና ሚስጥር “ይቻላል” የሚል ጽኑ እምነት ስላለኝ ነው የሚለው ወጣቱ ከኢንተርኔት የሚያገኛቸው የፈጠራ ሥራዎችም እገዛ እንዳደረጉለት ጠቁሟል። ሥራ ፈጣሪ ወጣቱ ወደ ገበያ በሚያቀርባቸው የፈጠራ ውጤቱ ጥሩ ገቢ ከማግኘቱም ባሻገር ለሌሎች 10 ወጣቶች የስራ እድል መፍጠሩን ተናግሯል። የወጣቱ የፈጠራ ወጤት ተጠቃሚ ከሆኑትና በባህላዊ መንገድ በደለል ወርቅ ምርት ፍለጋ ከተሰማሩ ማህበራት መካከል የ“ስምረት” ማህበር አንዱ ነው። የማህበሩ አባል የሆነው ወጣት በላይ ተክለሃይማኖት በሰጠው አስተያየት ” ከወጣቱ የገዛነው የደለል ወርቅ ጠቋሚ መሳርያ ሥራችንን ከማቃለል በተጨማሪ በወርቅ ፍለጋው ስኬታማ እንድንሆን አግዞናል” ብሏል። ሌላው የማህበሩ አባል ወጣት ተስፋይ በላይ በበኩሉ ” ከድንጋይ ጋር ተደባልቆ የሚገኝ ወርቅ ለመለየት እጅግ አድካሚ የነበረው ሥራ ወጣቱ ባቀረበልን አነስተኛ የድንጋይ ወፍጮ በመጠቀም የድካማችንን ዋጋ ማግኘት አስችሎናል ” በማለት አድናቆቱን ገልፆለታል ። የሽሬ እንዳስላሴ ከተማ የወጣቶችና ስፖርት ጉዳይ ጽህፈት ቤት ምክትል ሃላፊ አቶ ጎይቶኦም ይሰማ እንዳሉትም ደግሞ የወጣቱን የፈጠራ ክህሎት እንዲሰፋና ሄሊኮፕተሯ ለህዝብ እይታ እንድትበቃ አስፈላጊውን ድጋፍ ይደረግለታል ። የሽሬ እንደስላሴ ፖሊ ቴክኒክና ኮሌጅ ዲን አቶ ፀጋይ ገብረሚካኤል በበኩላቸው የፈጠራ ባለቤት የሆነው ወጣት እበ ለገሰ የፈጠራ ስራዎች የሚያተኩሩት በአካባቢው ህብረተሰብ ላይ በሚታዩ መሰረታዊ ችግሮች ዙሪያ በመሆናቸው ተቀባይነታቸው የጎላ ነው ብለዋል ። ወጣቱ የሚያሳየው ትጋት የተሞላበት የፈጠራ ስራ ለሌሎች ወጣቶችም አርአያ በመሆን መነቃቃት መፍጠሩን የኮሌጁ ዲን መስክረውለታል ። \n \nጥያቄ: በሽሬ ከተማ ለሙከራ ሔሊኮፕተር ሰርቶ ያቀረበው ወጣት ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ወጣት ዕበ ለገሰ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበ ፰፻ (800) ዓመተ-ዓለም አካባቢ ደአማት የሚባል መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያና ኤርትራ ተቋቋመ። በሰሜን ኢትዮጵያ የምትገኘው የሀ የደአማት ዋና ከተማ ነበረች። በየመን የሚኖሩት ሳባውያን በደአማት ላይ ተፅዕኖ እንደነበራቸው የሚታመን ሲሆን ይህ ተፅዕኖ ምን ያህል እንደሆነ ግን በእርግጥ አይታወቅም። ወደ ፬፻ (400) ዓመተ-ዓለም አካባቢ የደአማት መንግስት ከስልጣን ሲወድቅ በትናንሽ መንግስቶች ተተካ። ከነዚህ ትናንሽ መንግስቶች አንዱ አክሱም ሲሆን አካባቢውን እንደገና በአንድነት ለመግዛት ችሎ ነበር። የአክሱማውያን ስፈን በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥታዊ ማኅበረሰብ ነበር። በፋርስ ፣ ሮማ እና ቻይና ይገኙ ከነበሩ ታላላቅ መንግሥታት በወደረኛነት የሚቆጠር ትልቅ ኅይል ነበር። በ4ኛው ምእተ-ዓመት አክሱም ወደ ክርስትና ተለወጠ። በ፮ኛው ምእት ዓመት የአክሱማውያን ግዛታዊ ቁጥጥር የዛሬዋን የመን ግዛት ይጨምር ነበር። ግን በ፮ኛው እና በ ፰ኛው አምኣት የአክሱም ሥልጣኔ በእስልምና መነሣት እና መስፋፋት ተዳክሞ ለውድቀት በቃ ። ተከታዩ የዛጔ ሥርወ-መንግሥት ልክ በድንገት እንደተነሳ በድንገት ሲያበቃ ፣ ይኵኖ አምላክ ሥልጣን በ ፲፪፻፷፪ (1262) ዓ. ም. ጨበጡ ፤ እንዲያም ሲል የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥትን መለሱ። ከዚያም ለብዙ ዘመናት የሰለሞናዊው መንግስት ከጠለ። \n \nጥያቄ: በሰሜን ኢትዮጵያና ኤርትራ በ800 ዓመተ-ዓለም የተቋቋመው መንግስት ምን ይባል ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ደአማት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nግንቦት ፳፮ ቀን፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፷፮ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት ፷፩ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፺፱ ቀናት ይቀራሉ። ፲፱፻፶፬ ዓ/ም - የኤር ፍራንስ ቦይንግ ፯፻፯ አየር ዠበብ ከፓሪስ ኦርሊ ማረፊያ ተነስቶ ወደ አትላንታ ለመብረር ሲነሳ በደረሰበት አደጋ ፻፴ መንገደኞችና የዓየር መንገዱ ባልደረቦች ሞተዋል። ፲፱፻፶፭ ዓ/ም - የአሜሪካው ‘ኖርዝ ዌስት ኤየርላይንስ’ ዲ-ሲ-፯ አየር ዠበብ በረራ በሰላማዊ ውቅያኖስ ላይ ውድቆ ሲሰምጥ ፻፩ ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኮንኮርድ አየር ዠበብ አምሳል የተሠራው የሶቪዬት ቱፖሌቭ ቲ-ዩ-፻፵፬ ፈረንሳይ ላይ በደረሰበት የበረራ አደጋ ሲከሰከስ ፲፬ ሰዎች ሞተዋል። ፲፱፻፺፰ ዓ/ም - የቀድሞዋ ዩጎዝላቪያ አካላት የነበሩት ሰርቢያ እና ሞንቴኔግሮ የውሕደት ስምምነታቸውን በሞንቴኔግሮ የሉዐላዊነት አዋጅ ምክንያት ሰረዙ። ፲፯፻፷፭ ዓ/ም - የዓፄ በካፋ ሚስት የነበሩት እቴጌ ምንትዋብ በዚህ ዕለት አርፈው በቁስቋም ደብረ ጸሐይ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። \n \nጥያቄ: የኤር ፍራንስ ቦይንግ ፯፻፯ አየር ዠበብ ከፓሪስ ኦርሊ ማረፊያ ተነስቶ ወደ አትላንታ ለመብረር ሲነሳ በደረሰበት አደጋየደረሰበት መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፲፱፻፶፬ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቱርክ በዊኪፒዲያ ላይ ላለፉት ሶስት ዓመታት ጥላው የነበረውን እገዳ በማንሳት ተጠቃሚዎች ድረ ገፁን ማግኘት እንዲችሉ ፈቀደች። የሀገሪቱ ህገ መንግስታዊ ፍርድ ቤት እገዳው የመናገር መብትን ይጥሳል ሲል እግዱ እንዲነሳ ውሳኔ አሳልፏል። ዊኪፒዲያ በፈረንጆቹ ሚያዚያ ወር 2017 የቱርክን መንግስት የሚተች ፅሁፍ ለማንሳት ፈቃደኛ አለመሆኑን ተከትሎ የቱርክ መንግስት እገዳ ማሳላፉ ይታወሳል። በወቅቱ በዊኪፒዲያ ላይ የሰፈረው ፅሁፍ የቱርክ መንግስት ከአይ ኤስ እና አል ቃይዳ ጋር ትብብር አለው የሚል መሆኑን ዘገባው አመልክቷል። ይህንን ተከትሎም እገዳው ላለፉት 991 ቀናት ተግባራዊ ሆኖ መቆየቱን የኢንተርኔት ክትትል ተቋም የሆነው ኔትብሎክስ አስታውቋል። እገዳው በሂደት ቀስ በቀስ የሚነሳ በመሆኑ እና የተወሰኑ የኢንተርኔት አገልግሎት አቅራቢዎች ዊኪፒዲያን ለመመለስ እየሰሩ በመሆኑ በቱርክ የሚገኙ ሁሉም ተጠቃሚዎች ድረ ገፁን ማግኘት አይችሉም ተብሏል፡፡ ዊኪፒዲያ በበርካታ የዓለም ሀገራት ሳንሱር የሚደረግ ሲሆን በቻይና አሁንም ታግዶ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ቱርክ በዊኪፒዲያ ላይ ላለፉት ሶስት ዓመታት በምን ምክንያት እገዳ ጥላ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የቱርክን መንግስት የሚተች ፅሁፍ ለማንሳት ፈቃደኛ አለመሆኑን ተከትሎ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nመዓዛ ብሩ በእሁድ የሬዲዮ ፕሮግራም ታቀርባቸው የነበሩት ሥራዎች ይዘት ማህበራዊ ሕይወት እንዲሠምር በመጣር ላይ ያተኮሩ ሆነው ግልጽ፣ ቀላልና ለዛ ያልተለያቸው ስለነበሩ ከሶስት አሥርት ዓመታት በኋላም ትውስታቸው ከአድማጭ ህሊና አልጠፉም፡፡ በዚሁ ፕሮግራም ላይ መዓዛ ካበረከተቻቸው የፈጠራ ሥራዎቿ ውስጥ ጎልቶ የሚታወሰው “የአዲሱ ቤተሰብ” የተሰኘ ባለ ሰማንያ ስድስት ክፍል ድራማ ሲሆን በዘመኑ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ሁሉም የሚያደምጠው ተወዳጅ የቤተሰብ ድራማ ነበር፡፡ መዓዛ በ “መርሀ ስፖርት” እና በሬዲዮ መካከል ሆና ከአራት ዓመት በላይ ከቆየች በኋላ በ1979 ዓ.ም የባህል ሚኒስቴርን ለቃ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተቀጠረች፡፡ አዲሱን መስሪያ ቤቷን ከተቀላቀለችበት ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ከሬዲዮ እየራቀች መጣች፡፡ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ውስጥ የቆየችው ለሶስት ዓመታት ያህል ሲሆን ከዚያ በኋላ የግሏን የማስታወቂያ ሥራ ድርጅት መሥርታ የራስዋ ተቀጣሪ ሆናለች፡፡ ከ1979 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 1992 ዓ.ም ባሉት የአስራ ሶስት ዓመታት ጊዜ ግን መዓዛና ሬዲዮ ተራራቁ፡፡ መዓዛና ሬዲዮ ዳግም የተዋደዱት ከላይ እንደተገለጸው በ1992 ዓ.ም ሳምንታዊውን የ “ጨዋታ” ፕሮግራም በኤፍ ኤም 97.1 ከተፈሪ ዓለሙ ጋር በጋራ ማቅረብ ሲጀምሩ ነበር፡፡ የ “ጨዋታ” ፕሮግራም እስከ 1999 ዓ.ም ድረስ በአድማጮቹ እንደተወደደ በኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ላይ ሲቀርብ ቆይቷል፡፡ መንግሥት ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለት የኤፍ ኤም ሬዲዮ ፈቃዶችን ለግሉ ዘርፍ ለመስጠት ሲዘጋጅ፣ ዝርዝር የሥራ እቅድ አቅርባ ባመለከተችው መሠረት፤ ከረጅም ጊዜ ቆይታ በኋላ ከአስር አመልካቾች መካከል አንዷ ሆና የመጀመሪያ የግል የኤፍ ኤም ሬዲዮ ባለቤት ያደረጋትን ፈቃድ ተቀበለች፡፡ መዓዛ የሬዲዮ ማሰራጫ መሳሪያዎችን ውድነት፣ የማሰራጫ ቦታ እና የባለሙያ እጦትን ተቋቁማ ሸገር 102.1 ኤፍ ኤም ሬዲዮን በታህሳስ 1999 ዓ.ም አበረከተችልን፡፡ ባለትዳርና የሶስት ልጆች እናት የሆነችው መዓዛ እንደ ባለቤት፣ ሥራ አስኪያጅና ጋዜጠኛ በመሆን በኢትዮጵያ ተወዳጁንና የመጀመሪያውን የግል የኤፍ ኤም ሬዲዮ ጣቢያ ትመራለች፡ “ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!”እያለች:: \n \nጥያቄ: መዓዛ ብሩ ምን ያህል ጊዜ ከሬድዮ ጋር ተራራቀች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አስራ ሶስት ዓመታት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአሸናፊ ከበደ ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ አዲስ አበባ ግንቦት ፰ ቀን ፲፱፻፴ ዓ/ም ተወለዱ። አባታቸው ግራዝማች ከበደ አድነው ሲሆኑ ክልጅነታቸው ጀምሮ የሙዚቃ ስሜትንና ፍቅር ያሳደሩባቸው እናታቸው ወይዘሮ ፋንታዬ ነከሬ ነበሩ። አያታቸው ሊቀመኳስ አድነው ጎሹ ደግሞ የአድዋ አርበኛ እናየንግሥት ዘውዲቱም ታማኝ አማካሪ እንደነበሩ ይነገራል። የሙዚቃ ፍቅርን ገና በልጅነታቸው ያሳደሩባቸው እናታቸው ሲሆኑ ታዳጊው አሸናፊ ገና የዘጠኝ ዓመት ልጅ ሳሉ እኒህ የሚያፈቅሯቸውና ዕድሜ ልካቸውን በኀዘን የሚስታውሷቸው እናታቸው ሞተውባቸዋል። መሠረታዊ ትምህርታቸውን በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት እና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ኮከበ ጽባሕ) ካጠናቀቁ በኋላ በሐረር የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ በኒው ዮርክ ክፍለ-ሀገር ከሚገኘው የሮቼስተር ዩኒቨርሲቲ፣ “ኢስትማን የሙዚቃ ትምህርት ቤት” በ፲፱፻፶፬ ዓ/ም በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመረቁ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው፤ የያሬድ ሙዚቃ ትምሕርት ቤትን መሠረቱ። የዚሁ ትምህርት ቤትም የመጀመሪያው ዳይሬክቶር ከመሆናቸውም ባሻገር በአዲስ አበባው የወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማኅበር (ወ.ወ.ክ.ማ Y.M.C.A.)፤ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የበጎ አድራጎት ድርጅት መርሓ-ዕውራን ትምህርት ቤት እና በመሳሰሉ የወጣቶች ማኅበራት እየተገኙ የሙዚቃ ትምህርት ይሰጡ ነበር። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ የሙዚቃ ትምህርታቸውን የተማሩት በሮችስተር ዩኒቨርሲቲ ማን በሚባል ትምህርት ቤት ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ኢስትማን የሙዚቃ ትምህርት ቤት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአሪዞና አሪዞና (Arizona) በምዕራባዊ ዩናይትድ ስቴትስ የሚገኝ ክፍላገር ነው። ኒው ሜክሲኮ ፣ ዩታህ ፣ ኔቫዳ ፣ ካሊፎርኒያ እና ኮሎራዶ ያዋስኑታል። የአሪዞና ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ የ30 ሰው ሴኔት እና የ60 ሰው ምክር-ቤት አለው። የሪፑብሊካን ፓርቲ በስቴቱ ዋነኛው ፓርቲ ነው። በ2002 እ.ኤ.አ. የአሪዞና ስቴት ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ በጀት 14.3 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በጀት ደግሞ 13.8 ቢሊዮን ዶላር ነው። የስቴቱ ሴኔተሮች እና ምክር-ቤት ተወካዮች ለሁለት-ዓመት ጊዜ ላልተወሰነ ብዛት ይመረጣሉ። ከ4 ጊዜ በላይ በተካካይ መመረጥ ግን አይችሉም። የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በአስተዳዳሪ የሚመራ ሲሆን ለ4 ዓመት ሥልጣን ላይ ይቆያል። ያልተወሰነ ጊዜ መወዳደር ሲቻል ከሁለት ጊዜ በላይ ግን በተካካይ መመረጥ አይፈቀድም። \n \nጥያቄ: የአሪዞና ሕግ አውጪ የ60 ምክር ቤት አባላትና የስንት ሴኔት አባላት ውቅር ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የ30 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nመጠነ እንቅፋት የኤሌክትሪክ መጠነ እንቅፋት (ሬዚስታንስ) የሚባለው አንድ ኤሌክትሪክ አባል በውስጡ ሊያልፍ የሚሞክር የኤሌክትሪክ ጅረትን የሚያደናቅፍበት መጠን ልኬት ነው። የኤሌክትሪክ መጠነ እንቅፋት ከሰበቃ ጋር ተመሳሳይ ባህርይ አለው። የኤሌክትሪክ መጠነ እንቅፋት የተደረሰበት በ1819 ዓ፣ም በጆርጅ ኦም ሲሆን፤ በዚህ ሰው ጥናት መሰረት የአንድ ነገር ኤሌክትሪካዊ መጠነ እንቅፋት በዚያ ነገር ላይ ያለ የቮልቴጅ ለ በውስጡ የሚያልፍ ጅረት ሲካፈል ጋር እኩል ነው። በሒሳብ ቋንቋ፡ ለብዙ ቁሶችና ሁኔታዎች፣ የኤሌክትሪክ መጠነ እንቅፋት R ጸንቶ የሚቆይ ቋሚ ቁጥር ነው። ማለት በኤሌክትሪክ ጅረትና በቮልቴጅ መጠን አይቀየርም። እነዚህ ነገሮች ኦማዊ ቁሶች ይባላሉ። የአንድ ሽቦ መጠነ እንቅፋት መጠን በርዝመቱና በስፋቱ ይወሰናል። የሽቦው ርዝመት በጨመረ ቁጥር እንቅፋቱ እየጨመረ ይሄዳል፣ በአንጻሩ ስፋቱ ሲጨምር እንቅፋቱ ይቀንሳል። ልክ ውሃ በሰፊ ቱቦ ውስጥ በቶሎ ሊሄድ እንደሚችልና፣ በረጅም ቱቦ ውስጥ ብዙ ሰበቃ ስለሚገጥመው በቀስታ እንደሚጓዝ ሁሉ። ከዚህ በተጨማሪ የሽቦው መጠነ እንቅፋት ሽቦው ከተሰራበት ዕቃ ተፈጥሮ ጋር ይዛመዳል። ስለሆነም የአንድ ሽቦን መጠነ እንቅፋት በሒሳብ ለማስላት የሚከተለው ቀመር ይጠቅማል፡ ሽቦው የተሰራበት ቁስ ልዩ መጠነ እንቅፋት ሲሆን የሚለካውም በ ኦም-ሜትር ነው። \n \nጥያቄ: የኤሌክትሪክ መጠነ እንቅፋት የደረሰበት ሰው ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ጆርጅ ኦም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nደስታ ተክለወልድ አለቃ ደስታ ተክለወልድ የኢትዮጵያ ዕውቅ የቤተክርስቲያን ሊቅ፣ የመዝገበ ቃላት አዘጋጅና ደራሲ ነበሩ። ሐምሌ 19 ቀን 1893 ዓ.ም. በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ ላይ ወግዳ ጎሽ ውኃ ቀበሌ የተወለዱት አለቃ ደስታ፣ ያረፉት ጳጉሜን 2 ቀን 1977 ዓ.ም. ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ትምህርትን ከአጥቢያቸው ጀምሮ እስከ ደብረ ሊባኖስ የቅኔና የዜማ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል፡፡ ቀለምን ፈጥኖ በመቀበልና በማስተዋል ችሎታቸው የተመሰከረላቸው አለቃ ደስታ የመጻሕፍት አንድምታ ትርጓሜን አደላድለዋል፡፡ በብርሃንና ሰላም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ማተሚያ ቤት ቅዱሳት መጻሕፍትን በማረምና በማስተካከል ከ1916 እስከ 1920 ዓ.ም. ድረስ የሠሩ ሲሆን፣ በእርሳቸው አረጋጋጭነት በርካታ መጸሕፍት ለሕትመት በቅተዋል፡፡ በሀገረ ጀርመን በታተመው ኢንሳይክሎፔዲያ ኢትዮፒካ እንደተዘገበው፣ ወደ ድሬዳዋ በመሄድ በአልዓዛር ማተሚያ ቤት ሥራቸውን የቀጠሉበት አጋጣሚ የተፈጠረው ከሊቁ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መተዋወቃቸው ነበር፡፡ ከ30 ዓመት በፊት በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ምን እየሠሩ ዐምድ አጋጣሚውን እንዲህ ያስታውሰዋል፡፡ \n \nጥያቄ: አለቃ ደስታ ተክለወልድ በብርሃንና ሰላም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ማተሚያ ቤት ከመቼ እስከ መቼ ሰሩ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከ1916 እስከ 1920 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአፈወርቅ ተክሌ የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር የተከበሩ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በዓለም የታወቁና የተከበሩት ኢትዮጵያዊ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በሰሜን ሸዋ በምትገኘው የሸዋ ነገሥታት ከተማ አንኮበር ላይ ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም ከአባታቸው አቶ ተክሌ ማሞ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ፈለቀች የማታወርቅ ተወለዱ። ገና በጨቅላ ዕድሜያቸው ፋሺስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በግፍ ሲወራት፣ የልጅነት ትዝታቸውም ይሄው የግፍ ወረራ እና ጦርነት የሚያስከትለው የሰው፣ የንብረት እና የባህል ጥፋት ፤ ከነጻነትም በኋላ ዐቢዩ ሥራ በወረራ የተበላሸችውን ሀገራቸውን እንደገና መገንባት እንደሆነ ነው። ለዚህም የሀገር ግንባታ አስፈላጊውን እውቀት መሸመት የፈለጉት በ ማዕድን ምሕንድስና ዘርፍ ነበር። ወላጆቻቸውና ዘመድ አዝማዶች ግን የኪነ ጥበብ ስጦታቸውን በቤታቸውና በከተማው ዙሪያ በሚስሏቸው ስዕሎች ተገንዝበውት ነበር። ገና በአሥራ አምስት ዓመታቸው በ፲፱፻፵ ዓ/ም ለከፍተኛ ትምህርት ተመርጠው የምሕንድስና ትምህርታቸውን ለመከታተል ወደ እንግሊዝ አገር ይላካሉ። አፈወርቅ ተክሌ በእንግሊዝ አገር የአዳሪ ተማሪ ቤትን ኑሮ ሲያስታውሱ የባዕድ ባህላት፣ የአየር ለውጥ እና የተለመደው የተማሪ ቤት ዝንጠላ እንዳስቸገራቸው ያወሳሉ። ቢሆንም ትምሕርታቸውን በትጋት ሲከታተሉ ቆዩ። በተለይም በሒሣብ፣ በኬሚስትሪ እና በታሪክ ትምሕርቶች ጥሩ ውጤት በማምጣት ሰለጠኑ። ነገር ግን አስተማሪዎቻቸው የተፈጥሮ ስጦታቸው ኪነ ጥበብ እንደሆነ ለመገንዘብ ብዙ ጊዜም አልወሰደባቸውም። በነሱም አበረታችነት በእዚህ ስጦታቸው ላይ የበለጠ ለማተኮር ወስነው በሎንዶን የኪነ ጥበብ ማእከላዊ ትምሕርት ቤት ተመዝግበው ገቡ እዚህ ትምህርት ቤት ጥምሕርታቸውን ሲያጠናቅቁ ለከፍተኛ ጥናት በስመ ጥሩው የሎንዶን ዩኒቨርሲቲ የስሌድ ኪነ ጥበብ ማዕከል የመጀመሪያው አፍሪቃዊ ተማሪ (ከተከተሏቸው አፍሪቃውያን አንዱ የሱዳን ተወላጁ ኢብራሂም ኤል ሳላሂ ናቸው) በመሆን ገቡ። እዚህ በስዕል፣ ቅርጽ እና በአርክቴክቸር ጥናቶች ላይ አተኩረው ተመረቁ። ትምሕርታቸውን አጠናቀው ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ፣ በየጥቅላይ ግዛቶቹ እየተዘዋወሩ፣ በየቦታው እስከ ሦስት ወራት በመቀመጥ የኢትዮጵያን ታሪክ እና የብሔረሰቦቿን ባህልና ወግ በሚገባ አጥንተዋል። \n \nጥያቄ: አፈወርቅ ተክሌ ፲፱፻፵ ዓ.ም ለከፍተኛ ት/ት ተመርጠው ወደ እንግሊዝ ሀገር የተላኩት ምን ትምህርት እንዲያጠኑ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የምሕንድስና ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየእስክንድርያ ማስተማርያ ቤት የእስክንድርያ ማስተማርያ ቤት በእስክንድርያ፣ ግብጽ በጥንት (54-373 ዓም ያህል) የተገኘ የክርስትና ሥነ መለኮት ትምህርት ተቋም ነበረ። ተቋሙን የመሠረተው የኢየሱስ ሐዋርያ እና መጀመርያው የእስክንድርያ ጳጳስ፣ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ በ54 ዓም እንደ ሆነ ተጽፏል። የተቋሙ መጀመርያው መሪ በኋላ የእስክንድያ ፮ኛው ጳጳስ የሆነው ዩስቱስ እንደ ተሾመ ይታመናል። ተቋሙ ያስተማረው ከሥነ መለኮት፣ መጽሐፍ ቅዱስና ክርስትናን ጭምር፣ የግሪክኛና የሮማይስጥ ስነ ጽሁፍ፣ ሥነ ጥበብ፣ ስነ አመክንዮ፣ ሥነ ቁጥርና ስነ-ተፈጥሮ ጥናቶች ነበሩ። ለዕውሮችም ማስተማርያ አገልግሎት አቀረቡ። በፓንታይኖስ መሪነት (173-182 ዓም) ተቋሙ ስለ ትምህርቱ ዝነኛ ሆነ። ፓንታይኖስ በክርስትና ከመጠመቁ በፊት፣ የግሪኮች «ስቶዊሲሲም» ፍልስፍና ተከታይ ሆኖ ነበር። ፓንታይኖስ የግሪክ ፍልስፍና ከክርስትና ርዕዮተ አለም ጋር እንዳዋሐደ ይታስባል። ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ ከ182-194 ዓም በተቋሙ መሪነት ተከተለው። ብዙ አረመኔዎች በዚያን ጊዜ ለትምህርት ስለመጡ ከፍልስፍና መሠረት ጀምሮ የክርስትናን ትምህርት ያሳውቃቸው ነበር። በ194 ዓም የሮሜ መንግሥት ቄሣር በክርስቲያኖች ላይ ስላዘረጋው ማሳደድ፣ ቀሌምንጦስ ለጊዜው ከእስክንድርያ ሸሸ። እሱም የጻፋቻው ትልቅ መጻሕፍት ተርፈውልናል። የቀሌምንጦስ ተከታይ ኦሪገኔስ በመከራ ጊዜ ቢሆንም ተቋሙን በ195 ዓም ዳግመኛ አቆመ። ኦሪገኔስ ደግሞ ብሉይ ኪዳን በስድስት ትይዩ ዕብራይስጥና ግሪክኛ ትርጉሞች (ሄክሳፕላ) ያሳተመው እና ብዙ አንድምታ የጻፈው ዝነኛ መምህር ነው። በ373 ዓም በተካሄደው በቁስጥንጥንያ ጉባኤ፣ የጵጵሳት ቅድምንትነት ለሮሜ ፓፓ፣ ከርሱም ቀጥሎ ለአንጾኪያ ጳጳስ እንዲሰጥ የሚል ብያኔ ወረደ። ስለሆነም፣ የእስክንድርያ ጳጳስ የቀድሞ ቀድምትነቱን በማጣቱ፣ በእስክንድርያ ከተማ ውስጥ ትልቅ ሁከት ደረሰ። በዚያም ጊዜ በተደረገው ጉዳት የማስተማርያ ተቋሙ ጠፋ። \n \nጥያቄ: የእስክንድርያ ሥነ መለኮት ትምህርት ቤት መቼ ተመሰረተ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ54 ዓም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nከ1881 እስከ 1905 ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ በአፍሪካ ይዞታቸውን እያሰፉ የነበሩትን የአውሮፖ ሀይሎችን ጥቃት በመከላከል ኢትዮጵያን በስርዓት አስተዳድረዋል፡፡ በዚያን ጊዜ ጣልያን ኤርትራን በከፊል ቅኝ ገዝታ የነበረችበትና በ1880ዎቹ አጋማሽ ላይ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ቅኝ ገዝታት የነበረችበት ጊዜ ስለነበር ከሌሎች አውሮፖ አገራት በበለጠ ለኢትዮጵያ አስጊ ነበረች፡፡ በ1880 ግን እስከዛሬ ድረስ ዝነኛ በሆነው የአድዋ ጦርነት ኢትዮጵያ ጣልያንን ድል በማድረግ በአፍሪካ የባእዳን ገዥ ሀይሎችን ያሸነፈች ብቸኛዋ ሀገር ሆናለች፡፡ ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ የቅኝ ገዥዎችን ወረራና መስፋፋት በመመከትና ድልን በመቀዳጀት ለኢትዮጵያዉያን ብቻ ሳይሆን በባርነት ቀንበር ተጠምደዉ ለሚማቅቁ የመላዉ ዓለም ህዝቦች ከፍተኛ ክብርና ተስፋን አጎናጥፈዋል በ1908 የዳግማዊ ሚኒሊክ ልጅ የሆኑትን እቴጌ ዘውዲቱ ስልጣን ያዙ ፡፡ የሳቸው የቅርብ የስጋ ዘመድ የነበሩት ራስ ተፈሪ መኮንንም ሞግዚት አስተዳደርና ወራሽ ሆነው ተሹመዋል፡፡ እቴጌ ዘውዲቱ በ1922 ሲሞቱ ተተኪያቸው ዐጼ ሀይለስላሴ ስልጣን ያዙ ፡፡ ነገር ግን በ1928 ዓ.ም የጣልያን ሀይሎች ኢትዮጵያን ለአጭር ጊዜ ወረው ሲቆጣጠሩ ግዛታቸው ተቋርጦ ነበር፡፡ \n \nጥያቄ: ዳግማዊ ሚኒሊክ ኢትዮጵያን በሚያስተዳድሩበት ወቅት ከሰሩት አንዱ ተግባር ምን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የአውሮፖ ሀይሎችን ጥቃት በመከላከል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሱዳን ሱዳን በይፋ የሱዳን ሪፑብሊክ (አረብኛ السودان) ከአፍሪካ በስፋት ሦስተኛ ስትሆን በአህጉሪቱ ሰሜናዊ ምስራቅ ክልል ትገኛለች። ዋና ከተማዋ ካርቱም ነው። ከግብፅ ፣ ከቀይ ባሕር ፣ ከኤርትራ ፣ ከኢትዮጵያ ፣ ከደቡብ ሱዳን፣ ከመካከለኛው የአፍሪካ ሪፑብሊክ ፣ ከቻድ ፣ እና ከሊቢያ ጋር ድንበር ትካለላለች። የአባይ ወንዝ (ናይል) ሀገሪቱዋን ወደ ምሥራቅና ምዕራብ ይከፍላል። የአረብ ባህል ደንበኛ ሲሆን አብዛኛው ሕብዝ የእስልምና ዕምነት ተከታይ ነው። ሱዳን ከግብፅ የተጣመረ ረዥም ታሪክ አላት። የመጀመሪያው የሱዳን እርስ በርስ ጦርነት ከ1955 እስከ 1972 እ.ኤ.አ. ከዚያም ሁለተኛው የሱዳን እርስ በርስ ጦርነት ከ1983 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. ተከስቷል። በ1989 እ.ኤ.አ. በሰላማዊ መፈንቅለ መንግሥት ኦማር ሀሳን አህመድ አል-በሽር ሥልጣን ላይ የወጡ ሲሆን እራሳቸውን የሱዳን ፕሬዝዳንት ብለው ሾመዋል። የእርስ በርስ ጦርነቱ በሰላም ውል የቆመ ሲሆን ይህ ውል ያኔ የሀገሪቱዋ ደቡባዊ ክፍል ለነበረው ቦታ ራስን የመምራት መብት ሰጥቷል። በጃኑዋሪ 2011 እ.ኤ.አ. በተካሄደው ውሳኔ ሕዝብ (referendum) መሠረት በሱዳን ፈቃድ ደቡብ ሱዳን ሐምሌ ፪ ቀን ፳፻፫ ዓ.ም. ሉዓላዊ ሀገር ሆነች። ዋና ከተማዋ ካርቱም የሱዳን የፖለቲካ፣ ባህል እና ንግድ ማዕከል ናት። የሀገሪቱዋ መንግሥት በይፋ ፌዴራላዊ ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ቢሆንም ስልጣን ላይ ያለው ብሔራዊ ኮንግረስ ፓርቲ (National Congress Party) በሁሉም የመንግሥት አካላት ላይ ባለው ጥብቅ ቁጥጥር ምክንያት በብዙ የዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ ዘንድ መንግሥቱ አምባገነናዊ ተብሎ ይቆጠራል። \n \nጥያቄ: ሱዳን በአፍሪካ በየትኛው አቅጣጫ ትገኛለች?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሰሜናዊ ምስራቅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኤስፔራንቶ ኤስፔራንቶ (Esperanto) ከሁሉም አለማቀፋዊ ሠው ሰራሽ ቋንቋዎች እጅጉን የተስፋፋ ቋንቋ ነው። በ1859 እ.ኤ.አ. በዛሬይቷ ፖሎኝ የተወለደውና በሞያው የአይን ሀኪም የሆነው ሉድዊክ ሌይዛር ዛመንሆፍ በ1887 እ.ኤ.አ. ቋንቋውን ለህዝብ አሳወቀ። አላማው ኤስፔራንቶን በቀላሉ ሊማሩት የሚቻል፣ የጋራ የሆነና ለአለማቀፋዊ መግባባት የሚረዳ ግን ያሉትን ቋንቋዎች የማይተካ ቋንቋ ማድረግ ነበር። ኤስፔራንቶ ከ1,600,000 በላይ ተናጋሪዎች ቢኖሩትም የቋንቋው ደጋፊ ያልሆኑ እንግሊዝኛን ከመስፋፋቱ አንፃር ለአለማቀፋዊ ቋንቋነት በተሻለ ይመርጡታል። \n \nጥያቄ: ኤስፔራንቶ የተሰኘውን ሰው ሰራሽ ቋንቋ ለህዝብ ያስተዋወቀው ማን ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሉድዊክ ሌይዛር ዛመንሆፍ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአፋር (ክልል) አፋር ክልል (ክልል 2) በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙት ዘጠኝ ክልሎች አንዱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ዋና ከተማው ሰመራ ሲሆን የቀድሞዋ ከተማ ግን አሳይታ ነበረች። 96,707 ካሬ ኪ.ሜ. ሲሸፍን በ1999 እ.ኤ.አ. የሕዝብ ብዛቱ 1,188,000 ነው። የድንቅ ነሽ ወይም ሉሲ አጽም በአፋር ክልል ውስጥ በ, 1967 (Nov. 24, 1974 እ.ኤ.አ.) ነው የተገኘው። በማርች 5, 2005 ደግሞ ሌላ 3.8 ሚሊዮን ዓመት የሚገመት አጽምም በዚሁ ክልል ተገኝቷል። \n \nጥያቄ: በአፋር ክልል ከሉሲ በተጨማሪ አዲስ የተገኘችው የሰው ቅሪተ አካል መቼ ተገኘች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በማርች 5, 2005 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ እንግሊዝ ሀገር አንደደረሰም የወቅቱ የእንግሊዝ ንግስት ከነበረችው ንግስት ቪክቶሪያ ጋር ተገናኘ፡፡ ንግስቲቱም ልዑሉ የፈለገው እና ያሻው ይደረግለት ዘንድ ቀጭን ትዕዛዝ አስተላለፈች፡፡ ልዑሉ በመቅደላ የነበረውን እልቂት በመጠኑም ቢሆን በማየቱ እና የአባቱ እና የእናቱ ተከታታይ ሞትም በልጅ አዕምሮው ሊቀበለው ከሚችለው በላይ ስለነበር እጅግ ታውኮ እንደነበር በተደጋጋሚ ተፅፎ እናገኛለን፡፡ በ1861 ዓ.ም ስፒዲ ህንድ ሀገር በምትገኝ አንዲት ከተማ አዛዥ ሆኖ ስለተሾመ የ8 ዓመቱን አለማየሁን እና ሚስቱን ይዞ ወደዛው አቀና፡፡ በሄዱበት ሀገርም አለማየሁ ትምህርቱን መከታተሉን ቀጥሎ የነበረ ሲሆን ከመደበኛው ትምህርት በዘለለም ፈረስ ግልቢያ እና ሌሎች ስፖርቶችንም ያዘወትር ነበር፡፡ 1867 ዓ.ም አለማየሁ ወደ ራግቢ ትምህርት ቤት ተዛወረ፡፡ በዚህም ከቄስ ብሌክ ቤት ወጥቶ ወደ ሊው ዋርነር ቤት እንዲገባ ተደረገ፡፡ በዚህ ግን ደስተኛ ስላልነበር በቀጣዩ አመት ሚስተር ድራፐር ቤት እንዲኖር ተደረገ፡፡ ቄስ ብሌክም ካዩት የልዑሉ ባህሪ በመነሳት ልዑሉ ወታደርነት ላይ ቢያተኩር የበለጠ ውጤታማ እንደሚሆን ተናገሩ፡፡ በዚህም ንግግር መሰረት የወታደር ትምህርት ቤት እንዲገባ ተደረገ፡፡ በአንድ ወቅት አለማየሁ ወደ ሊድስ በመሄድ በሰር ራምሰን ቤት ተቀምጦ በነበረበት ወቅት በመርዝ ተመረዘ። መርዙ ህዳር 5 ቀን 1872 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3 ሰዓት ከሩብ በተወለደ በ19 ዓመቱ ከዚህ አለም እንዲሰናበት አደረገው፡፡ አስከሬኑም ዊንድሶር ባለው የነገስታት መቀበርያ በክብር አረፈ፡፡ በመቃብሩም ላይ “የሀበሻው ልዑል አለማየሁ” የሚል ፅሁፍ ሰፍሮበት እስካሁን በእንግሊዝ ሀገር ይገኛል፡፡ \n \nጥያቄ: በልዑል አለማየሁ መቃብር ላይ ምን ተብሎ ነው ፅኁፍ የተፃፈለት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ “የሀበሻው ልዑል አለማየሁ” ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዳምጠው አየለ ዳምጠው አየለ (23.11. 1944 አ/ም – 27.10. 2006 አ/ም) ባህላዊ የኢትዮጵያ ዘፋኝ ነበር። በሃምሌ 23 1944 አ/ም ከእናቱ ወይዘሮ ሸዋየ ተካና ከአባቱ አየለ ካሰኝ በመራቤቴ ሰሜን ሸዋ ተወለደ። ልጅነቱን በእረኝነት፥ በግብርና እንዲሁም በቆሎ ተማሪነት እንዳሳለፈ ይናገራል። እድሜውም ለትምህርት ሲደርስ ባቅራቢያው በሚገኘው መራኛ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገብቶ ተምሯል። ዳምጠው ህይወቱ እስካለፈችበት ጊዜ ድረስ ለረዥም ጊዜ አብሯት የኖረው ባለቤቱ አልማዝ ይመር ትባላለች። ከአልማዝ ይመር አብዩ ዳምጠውና ቤቴልሄም ዳምጠው የሚባሉ ሁለት ልጆችን አፍርቷል። ዳምጠው መራቤቴ እያለ በየባእላቱ መዝፈን፣ ማቅራራት እንዲሁም መሸለል ይወድ እንደነበር ተናግሯል። በተለይም ጥምቀትን በማድመቅ ይታወቅ ነበር። የ 6ኛ ክፍል ተማሪ እያለ ክፍሌ ሞገስ የሚባል መምህሩ ወደ አዲስ አበባ ይዞት እንደመጣ ይናገራል። ባጋጣሚም የምድር ጦር ማስታወቂያ አውጥቶ ስለነበር ይፈተንና ያልፋል። የምድር ጦር ካምፕ ውስጥም እንዲኖር ይደረጋል። የዘፋኝነት ሙያው በዚህ አጋጣሚ ነበር የጀመረው። ዳምጠው ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማዉና መነሻ የሆነው አበበ ተሰማ እንደሆነ ይናገራል። ዳምጠው አየለ በምድር ጦር ከ 30 አመት በላይ አገልግሏል። የኢትዮዽያ ምድር ጦር በ1927 አ/ም ተመስርቶ በ1983 አ/ም የፈረሰ የሙዚቃ ቡድን ነበር። ዳምጠው በመንግስት ለውጥ ምክንያት እስከፈረሰበት ጊዜ ድረስ አብሮ እንደነበር ይናገራል። ምድር ጦርም እያለ ከነታምራት ሞላ፣ ሲራክ ታደሰ፣ ተክሌ ደስታ ፣ ጥላየ ጨዋቃ፣ ክፍሌ አቦቸር እንዲሁም ሌሎች የጦሩ አባላት ጋር ሰርቷል። ከሌሎች የሙዚቃ ቡድንም ጋር አብሮ ሰርቷል። ለምሳሌ ያክል ከነ ክቡር ጥላሁን ገሰሰ፣ ሙሃሙድ አህመድ፣ ብዙነሽ በቀለ ፣ ሙሉቀን መለስ፣ ፀሃየ ዮሃንስ፣ ቴድሮስ ታደሰ፣ቴድሮስ ካሳሁን እንዲሁም ሌሎችም ጋር ሰርቷል። የዳምጠው አየለ የመጀመሪያ የህትመት ስራው በ1963 አ/ም ሲሆን ወፌ ላላ የሚለው የሸክላ ስራ ነበር። ዳምጠው አየለ ባጠቃላይ 13 ሲዲዎችን ሰርቷል። ዳምጠው አየለ ኖርዌይ ሃገር በስደት ለ 8 አመት ያክል ኖሯል። ኢትዮጵያም ከገባ በኋላ አዲስ አበባ በሚገኘው በቅ/ገብራኤል ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በተወለደ በ 62 አመቱ ሰኔ 27 2006 አ/ም ቀን ህይወቱ አልፏል። የቀብር ስነስርአቱም ወዳጅ፣ ዘመድ እንዲሁም አድናቂዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ዳምጠው አየለ ትምህርቱን በየት ትምህርት ቤት ተከታተለ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ መራኛ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ በጥሩ ጎናቸው ከሚነሱ የቅርብ ጊዜያት ተጫዋቾች መካከል አዳነ ግርማ ይገኝበታል።ተጫዋቹ በበርካታ የስፖርቱ ቤተሰቦች ልብ ውስጥ ትልቅ ቦታንም ይዟል።አዳነ ግርማ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን መነቃቃት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ተጫዋቹ በብሄራዊ ቡድኑ ውስጥ ለ10 ዓመታት በመጫወትም አንጋፋ ለመሆን በቅቷል። አዳነ ግርማን ስናስብ ሁለት ጨዋታዎች ሁሌም ከፊታችን ድቅን ይላሉ።ደቡብ አፍሪካ ላስተናገደ ችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በአዲስ አበባ ስታዲየም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡደን ከሱዳን አቻው ጋር ሲጫወት በግንባሩ ገጭቶ ያስቆጠራት ግብ መቼም ቢሆን አዳነ እንዲታወስ ያደረገችም የምታደርግ ናት።ኢትዮጵያ ለደቡብ አፍሪካው የአፍሪካ ዋንጫ እንድታልፍ ያረገችው ወሳኝ ግብም ሆናለች። በአፍሪካ ዋንጫው ከ 39 ዓመታት በኋላ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዛምቢያ ላይ ያስቆጠራት ግብም አዳነን ሁሌም እንድናስበው ያረገች ሌላዋ ግቡ ናት። ተጫዋቹ ከዋልያዎቹ ጋር ለአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጉዞ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳደረገና የቡድኑ ምሰሶ እንደነበርም ይታወቃል።በአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ዘመን አዳነ ቡድኑን በአምበልነት መርቷል። የአትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ከሰውነት ቢሻው የተረከቡት አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ ቡድኑን እንደ አዲስ ሲያዋቅሩ አዳነ ግርማን መቀነሳቸው ሲሰማ በስፖርቱ ቤተሰብ ዘንድ ቅሬታ ቢፈጠርም፣ ተጫዋቹ ግን ውሳኔውን አሜን ብሎ ነው የተቀበለው። በወቅቱም አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ማብራሪያ ለተጫዋቹ መቀነስ ምክንያታቸው ያደረጉት የተጫዋቹ «ብቃትና አቅም ወርዷል» የሚል ነው። ተጫዋቹ ግን በወቅቱ ለአንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን ያረጋገጠው ምንም አይነት የአቋም መዋዠቅም እንደሌለበት ነው። የብቃት መውረድ እንዳላሳየም ገልጿል። የመቀነሱ ሚስጥር ለሱም እንቆቅልሽ እንደሆነበት ነበር ያስታወቀው። ይህን ተከትሎ ራሱን ከብሄራዊ ቡድን ያገለለው አዳነ በአዲሱ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ሰሞኑን ጥሪ ተደርጎለት ነበር:: የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከአልጄሪያ ጋር ላለበት ወሳኝ ጨዋታ በአጥቂ እጥረት ላይ ቢገኝም አዳነ ግርማ ከቤተሰቦቼ ጋር ተመካክሬ የወሰንክይት ውሳኔ ነው በሚል ለብሔራዊ ቡድኑ እንደማይጫወት አስታውቋል:: በ2017 የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በምድብ ሁለት የተደለደለውና በአሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ የሚሰለጥነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከአልጀሪያ አቻው ጋር ላለበት የምድቡ ሶስተኛ እና አራተኛ ጨዋታ 24 ተጫዋቾችን መጥራቱ ይታወሳል። አሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ ሁለት ተጫዋቾችን ከአገር ውጭ ቀሪዎቹን 22 ደግሞ ከአገር ውስጥ ሊጎች የመረጡ ቢሆንም የአዳማ ከነማው አጥቂ ታፈሰ ተስፋዬ ባጋጠመው ጉዳት ከቡድኑ ውጭ ሆኗል። እርሱን ለመተካት ሳልሃዲንና አዳነን ቢጠሩም እምቢ ተብለዋል:: ሆኖም ግን አሰልጣኙ ከቅዱስ ጊዮርጊስ የመረጧቸውን አምስት ተጫዋቾችና ከአገር ውጭ ከሚጫወቱት ሕመልስ በቀለና ጌታነህ ከበደ በስተቀር 15 ተጫዋቾችን ይዘው ልምምዳቸውን ዛሬ ጀምረዋል። \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ በ29ኛው የእግር ኳስ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው ከስንት ጌዜ በኋላ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከ 39 ዓመታት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nከ 60 ዓመት በኋላ ወባን ለማከም የሚረዳ ኪኒን በአሜሪካ ባለስልጣናት ፈቃድ አገኘ። መድሃኒቱ በየአመቱ 8 ሚሊየን ሰዎች ላይ የሚያገረሸውን የወባ አይነት ለማከም የሚረዳ ነው። ይህ አይነት የወባ በሽታ በጉበት ውስጥ ለረጅም ዓመት ተደብቆ የመቆየት ባህሪ አለው። ተመራማሪዎች ይህንን \"ድንቅ ስኬት ሲሉ አሞካሽተውታል\"። ደጋግሞ የሚያገረሽ የወባ በሽታ ፕላስሞዲየም ቪቫክስ በሚሰኝ ጥገኛ ተዋህሲያን የሚከሰት ሲሆን በአፍሪካ በዋናነት ከሚጠቀሱ የበሽታ አይነቶች መካከል አንዱ ነው። አሁን የአሜሪካው የምግብና የመድሃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን ታፌኖኪውይን ለተሰኘው መድሃኒት እውቅና ሰጥቷል። መድሃኒቱ በሽታዋ ከተደበቀበችበት ጉበት አውጥቶ በመግደል ሰዎች በህመሙ ዳግመኛ እንዳይሰቃዩ ያደርጋል። በአሁን ሰዓት ጉበት ውስጥ የተደበቀች ወባን ለማከም የሚረዳ ፕሪማኪውን የተሰኘ መድሃኒት አለ። ነገር ግን አንድ ታፌንኪውንን ወስዶ ከሚገኘው ፈውስ ጋር ሲነፃፀር ፕሪማኪውንን ለ 14 ቀን መውሰድ ይጠይቃል። \n \nጥያቄ: ወባን ለማከም የሚጠቅመው መድሃኒት በአሜሪካ ፈቃድ ያገኘው ከስንት ዓመት በኋላ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከ 60 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nተክለጻድቅ መኩርያ ተክለጻድቅ መኩርያ በ፲፱፻፮ ዓ.ም. በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ አሳግርት ልዩ ስሙ ሳር አምባ በተባለ ሥፍራ ተወለዱ። ዕድሜያቸው ለትምሕርት ሲደርስ መጀመሪያ ከአባታቸውና ቀጥሎም በአጥቢያቸው ባህላዊውን ትምሕርት እስከቅኔ ያለውን ቀስመዋል። ከዚያም አዲስ አበባ መጥተው አሊያንስ ፍራንሴዝና ተፈሪ መኮንን ትምሕርት ቤት ገብተው የጊዜውን የትምሕርት ደረጃ አጠናቀዋል። ኢጣልያ አገራችንን የወረረች ጊዜም በየካቲት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ.ም. ፍጅት ተይዘው ወደ ሶማሌ ደናኔ ተግዘው ለሦስት ዓመታት ታስረዋል። ከነጻነትም መልስ አገራቸውን በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች አገልግለዋል። መጀመሪያ ተቀጥረው ያገለገሉት በትምሕርትና ሥነጥበብ ሚኒስቴር ነበር። እዚያም ሳሉ በአገራችን ሰው የተጻፈ የአገራችን ታሪክ አንድም ባለመኖሩ በቁጭትና በመቆርቆር ነበር ‘መጻፍ አለብኝ’ ብለው በደንብ ከሚታወቀው ከቅርቡ ጊዜ በቅጡ ወደማይታወቀው የሩቁ ዘመን መጻፍ የጀመሩት። የመጀመሪያውን መጽሐፍ “የኢትዮጵያ ታሪክ ከዓፄ ቴዎድሮስ እስከ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ” የሚለውን በ ፲፱፻፴፰ ዓ.ም. አሳተሙ። ከጫፍ እስከ ጫፍ ጽፈው የመጨረቻውን መጽሐፍ፣ የታሪካችን መጀመሪያ የሚሆነውን “የኢትዮጵያ ታሪክ ኑብያ-አክሱም-ዛጉዬ እስከ ዓፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት” የሚለውን በ፲፱፻፶፩ ዓ.ም. አቅርበዋል። እኒህኑ መጻሕፍት ትምሕርት ሚኒስቴር ታሪክ ለማስተማሪያ በትምሕርት ቤት ተጠቅሞባቸዋል። ተክለጻድቅ ከታሪክ ውጭ የጻፏቸው “የሰው ጠባይና አብሮ የመኖር ዘዴ” እና በሚዮቶሎዢያ (አፈ ታሪክ) ላይ ያተኮረ “ከጣዖት አምልኮ እስከ ክርስትና” የሚሉም መጽሐፎች አሏቸው። ተክለጻድቅ በምድር ባቡር በዋና ጸሐፊነት፥ በቤተ መጻሕፍት ወመዘክር ዋና ሥራ አስኪያጅነት፥ እንዲሁም በፈረንሳይ፥ በእስራኤል፥ በዩጎዝላቪያ በዲፕሎማሲ ሥራ በመጨረሻም የትምሕርትና የባህል ሚኒስቴር ሆነው አግልግለዋል። በፈቃዳቸው ጡረታም ከወጡ በኋላ በምርምር የታገዙ ሦስት ታላላቅ የታሪክ ሥራዎችን አቅርበዋል። ተክለጻድቅ ከረጅም የአገልግሎት ዘመን በኋላ በተወለዱ በ ሰማንያ ስድስት ዓመታቸው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፱፻፺፪ ዓ.ም. አርፈዋል። \n \nጥያቄ: የተክለጻድቅ መኩርያ የመጨረሻው መጽሐፍ መቼ ለአንባቢ ቀረበ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ፲፱፻፶፩ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአሪዞና አሪዞና (Arizona) በምዕራባዊ ዩናይትድ ስቴትስ የሚገኝ ክፍላገር ነው። ኒው ሜክሲኮ ፣ ዩታህ ፣ ኔቫዳ ፣ ካሊፎርኒያ እና ኮሎራዶ ያዋስኑታል። የአሪዞና ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ የ30 ሰው ሴኔት እና የ60 ሰው ምክር-ቤት አለው። የሪፑብሊካን ፓርቲ በስቴቱ ዋነኛው ፓርቲ ነው። በ2002 እ.ኤ.አ. የአሪዞና ስቴት ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ በጀት 14.3 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በጀት ደግሞ 13.8 ቢሊዮን ዶላር ነው። የስቴቱ ሴኔተሮች እና ምክር-ቤት ተወካዮች ለሁለት-ዓመት ጊዜ ላልተወሰነ ብዛት ይመረጣሉ። ከ4 ጊዜ በላይ በተካካይ መመረጥ ግን አይችሉም። የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በአስተዳዳሪ የሚመራ ሲሆን ለ4 ዓመት ሥልጣን ላይ ይቆያል። ያልተወሰነ ጊዜ መወዳደር ሲቻል ከሁለት ጊዜ በላይ ግን በተካካይ መመረጥ አይፈቀድም። \n \nጥያቄ: አሪዞና ስቴት የት ሀገር ይገኛል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ዩናይትድ ስቴትስ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ታኅሣሥ ፳፫ ቀን ፲፱፻፲፯ ዓ/ም በአንዲት “ብርሃንና ሰላም” በተሰኘች አነስተኛ ጋዜጣ ሕትመት ሥራውን ጀመረ። በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው መጻሕፍት ፣ ጋዜጦች ፣ መጽሔቶችና የምስጢራዊ ሕትመት ሥራዎች በተለያዩ ቋንቋዎች እያተመ ይገኛል። ማተሚያ ቤቱ በርካታ የመንግሥት እና የግል ጋዜጦችን የሚያትም ሲሆን ፥ በተጨማሪም በየዓመቱ በርካታ የፈተና ሥራዎችን በማተም ይታወቃል። ጥንታዊ ኢትዮጰያውያን ሊቃውንት የሚጽፏቸው መጻሕፍት ለሕዝብ የሚቀርቡት ብራና ተፍቆ ፣ ቀለም ተቀምሞ በእጅ ተፅፎ ነበር። በዳግማዊ ምኒልክ ዘመነ-መንግሥት የተጀመረው የዘመናዊ ሕትመት ሥራ በሀገሪቱ ቁጥራቸውና መጠናቸው በርከት ያሉ ጋዜጦች፣ መፅሔቶች፣ መጻሕፍት፣ እንዲሁም ሌሎች የሕትመት ውጤቶች መታተም በመጀመራቸው የትምህርትና የሥልጣኔ መሰፋፋት ላይ የበኩሉን ሚና መጫወት ጀመረ። የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤትም ምሥረታ ዋና ዓላማ የአገሪቱን መንፈሳዊ መጻሕፍት በብዛት እና በዘመናዊ መልክ ከእጅ ጽሑፍ ወደ ሕትመት ለማሸጋገር ሲሆን፤ ምሑሩ ተክለጻድቅ መኩሪያ (፲፱፻፷፩ ዓ/ም)፣ ማተሚያ ቤቱ መስከረም ፫ ቀን ፲፱፻፲፬ ዓ/ም መቋቋሙን እና ብዙ ሥጋዊና የመንፈሳዊ መጻሕፍት እንዲሁም ምክርና ተግሣጽ፣ የለት ወሬ፣ የሹም-ሽር አዋጆችን ያትም እንደነበር ዘግበዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ረዳት መምህር መኩሪያ መካሻ፤ “የፕሬስ ታሪክ” በተሰኘ ጽሑፋቸው ላይ ደግሞ የኢትዮጵያ መንግሥት አልጋ ወራሽና ባለሙሉ ሥልጣን እንደራሴ፣ ራስ ተፈሪ መኮንን በ፲፱፻፲፫ ዓ/ም የማተሚያ መሣሪያ አስመጥተው “ትንሹ ግቢ” (በኋላ ገነተ ልዑል — አሁን አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ) ይባል በነበረው መኖሪያቸው ውስጥ አስተክለው የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት የተባለውን እንደመሠረቱ ዘግበዋል። ከሁለት ዓመት በኋላ በ፲፱፻፲፭ ዓ/ም አራት ተጨማሪ ማተሚያዎች ተገዝተው ከተተከሉ ከአንድ ዓመት በኋላ ሣምንታዊው ‘ብርሃንና ሰላም’ የተሰኘው ጋዜጣ እየታተመ፣ አስቀድሞ በዳግማዊ ምኒልክ ዘመን ከተጀመረችው ‘አዕምሮ’ ጋዜጣ ጋር እስከ ጠላት ወረራ ዘመን ድረስ በአዲስ አበባ ከተማ ይሠራጩ ነበር። የወቅቱ ማተሚያ መሣሪያዎች በእግር እየተረገጡ የሚንቀሳቀሱ መሣሪያዎች ሲሆኑ የሠራተኞቹ ቁጥር ከሰባት እስከ አሥራ-ሁለት እንደነበር ተዘግቧል። ራስ ተፈሪም አልፎ-አልፎ በብርሃን እና ሰላም ጋዜጣ ላይ በአዘጋጅነት ይረዱ እንደነበረና ጽሑፎቻቸውንም ለሕትመት ያበቁ እንደነበር ተምዝግቧል። \n \nጥያቄ: ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት መቼ ስራ ጀመረ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ታኅሣሥ ፳፫ ቀን ፲፱፻፲፯ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየ2014 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ የ2014 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ ፳ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሲሆን ከሰኔ ፭ እስከ ሐምሌ ፮ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. በብራዚል ይካሄዳል። ብራዚል ይህን ውድድር ስታዘጋጅ ይሄ ሁለተኛ ጊዜዋ ነው። ፊፋ የ2014 እ.ኤ.አ. ውድድር በደቡብ አሜሪካ እንደሚካሄድ በ2007 እ.ኤ.አ. ካወጀ በኋላ ብራዚል ያለማንም ተቀናቃኝ አዘጋጅ አገር ሆና ተመርጣለች። የ፴፩ አገራት ብሔራዊ ቡድኖች ከጁን 2011 እ.ኤ.አ. ጀምሮ የተካሄዱ የማጣሪያ ውድድሮችን በማለፍ ከብራዚል ጋር በመጨረሻው ውድድር ላይ ለመሳተፍ በቅተዋል። በጠቅላላው ፷፬ ጨዋታዎች በ፲፪ ከተማዎች ውስጥ በሚገኙ አዲስ የተገነቡ ወይም የተሻሻሉ ስታዲየሞች ይከናወናሉ። በዓለም ዋንጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የጎል ላይን ቴክኖሎጂ በጥቅም ላይ ውሏል። በ1930 እ.ኤ.አ. ከተካሄደው የመጀመሪያው የዓለም ዋንጫ ጀምሮ ሁሉም የዓለም ዋንጫ ሻምፕዮን አገራት (ብራዚል፣ አርጀንቲና፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሣይ፣ ጀርመን፣ ኢጣልያ፣ እስፓንያ እና ኡራጓይ) በዚህ ውድድር ውስጥ ተሳታፊ ናቸው። ከዚህ በፊት በደቡብ አሜሪካ የተዘጋጁትን ዋንጫዎች እንዳለ የወሰዱት የደቡብ አሜሪካ ቡድኖች ናቸው። ፊፋ ለውድድሩ ያቀረበው ጠቅላላ የሽልማት ገንዘብ $576 ሚሊዮን ነው። ይህም ከ2010 እ.ኤ.አ. ውድድር ሽልማት ገንዘብ የ፴፯ ከመቶ ዕድገት አለው። ከዚህ ውስጥ $70 ሚሊዮን የሚሆነው ተጫዋቾቹ ለሚጫወቱበት ክለቦች ተጫዋቾቹ ለሚደርስባቸው ጉዳት መካካሻ እንዲሆን ተሰጥቷል። ከውድድሩ በፊት እያንዳንዱ ቡድን ለዝግጅት ወጪው $1.5 ሚሊዮን የተረከበ ሲሆን ቀሪው ገንዘብ እንደሚመለከተው ተከፋፍሏል፦ $8 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በምድብ ደረጃ የወደቀ ቡድን (፲፮ ቡድኖች) $9 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በየ፲፮ ዙር የወደቀ ቡድን (፰ ቡድኖች) $14 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በሩብ ፍፃሜ የወደቀ ቡድን (፬ ቡድኖች) $20 ሚሊዮን - በአራተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $22 ሚሊዮን - በሶስተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $25 ሚሊዮን - በሁለተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $35 ሚሊዮን - ለአሸናፊው ቡድን በአስራ ሁለት ከተማዎች የሚገኙ አስራ ሁለት ስታዲየሞች ለውድድሩ ተዘጋጅተዋል። ሰባቱ አዲስ የተገነቡ ሲሆን አምስቱ ደግሞ የተሻሻሉ ስታዲየሞች ናቸው። \n \nጥያቄ: የ2014 እ.ኤ.አ. የፊፋ የዓለም ዋንጫ ስንተኛው ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ፳ኛው ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nክዋሜ ንክሩማህ የተወለዱት በ1909 እ.ኤ.አ. ደቡባዊ ምዕራብ ጋና (ቀደም ሲል ጎልድ ኮስት) ንክሮፉል በምትባል ከተማ ነው። ንክሩማህ በካቶሊክ ሚሽነሪ ትምህርት ቤት ይማሩበት በነበረ ወቅት ብሩህ አዕምሮ እንደነበራቸው የተመሰከረላቸው ሲሆን ገና በአሥራዎቹ እድሜ ውስጥ እያሉ ነው በአቅራቢያቸው በሚገኝ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት አስተማሪ የሆኑት። ይሁንና ያለሥልጠና የጀመሩትን ትምህርት በ1926 እ.ኤ.አ. የአክራውን አቺሞታ ኮሌጅ ተቃለቅለው የመምህርነት ምሥክር ወረቀት በማግኘት በተለያዩ የካቶሊክ ትምህርት ቤቶች አስተምረዋል። በ1935 እ.ኤ.አ. ወደ አሜሪካ በማቅናትም የፔንሴልቬኒያውን ሊንከን ዩኒቨርሲቲ ተቀላቅለው በኢኮኖሚክስና ሶሲዮሎጂ የመጀመሪያ ድግሪያቸውን በ1939 የተቀበሉ ሲሆን በ1942ም በሥነ-መለኮት ሌላ ድግሪ ከዚሁ ዪኒቨርሰቲ አግኝተዋል። በ1942 እና በ1943ም የማስተርስ ድግሪያቸውን ከፔንሴልቬኒያ ዩኒቨርሲቲ በሥነ-ትምህርትና በፍልስፍና ሠርተዋል። በአሜሪካ ቆይታቸውም በግራ ዘመም አሰተሳሰቦች በመማረከቸው የተነሳ በወቅቱ በሥርነቀል ለውጥ ፈላጊነታቸው ከሚታወቁ ምሁራን ጋር ቅርብ ግንኙነት መሥርተው ነበር። አፍሪካውያንን ያሰባሰበ የተማሪዎች እንቅስቃሴ መሥራችና ግንባር ቀደም ተናጋሪ እንዲሁም የአፍሪካ አገራት ነፃ እንዲወጡና የአውሮፓ ቅኝ ግዛት እንዲያበቃ ቁርጠኛ አቋም ነበራቸው። ከዚሁ ጎን ለጎንም የተባበረች አፍሪካ አስፈላጊነትን በማመን አፍሪካውያንና የአፍሪካ ዝርያ ያላቸው ሕዝቦች በአንድነት እንዲቆሙ የሚሰብከው ፓንአፍሪካኒዝም አቀንቃኝ ነበሩ። በ1945 ወደ ለንደን ሕግና ኢኮኖሚክስ ለማጥናት ባመሩበት ወቅትም በማንችስተር እንግሊዝ የተካሄደውን 5ኛው የፓን አፍሪካን ጉባዔ እንዲካሄድ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የአፍሪካን ከቅኝ ግዛት የመውጣት እንቅስቃሴ ለማስተባበርና ቅኝ አገዛዝን ለመቃውም የተደራጀው ጉባዔ ንክሩማህ ታዋቂ የጥቁር መብት ታጋዮችና የፀረ-ቅኝ ግዛት ንቅናቄ መሪዎች ጋር እንዲገናኙ ዕድል የሰጣቸው ሲሆን በ1946ም ጥናታቸውን ትተው በ5ኛው ጉባኤ የተቋቋመው የምዕራብ አፍሪካ ብሔራዊ ጽ/ቤት ዋና ጸኃፊና የምዕራብ አፍሪካ ተማሪዎች ማኅበር ምክትል ፕሬዝዳንት በመሆን አገልግለዋል። \n \nጥያቄ: ንክሩማህ የመምህርነት ምስክር ወረቀት መቼ አገኘ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ1926 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nመዓዛ ብሩ መዓዛ የተወለደችው እዚህ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሲሆን ዘመኑም 1951 ዓ.ም ነበር፡፡ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ክፍል በሐረርጌ ክፍለ ሀገር በሒርና ከተማ ተምራ፣ ከአራተኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን ትምህርቷን ደግሞ በቅድስት ማርያም ትምህርት ቤት ተከታትላ ፈጽማለች፡፡ መዓዛ በትምህርት ቤቷ በክፍል ውስጥ አጫጭር ታሪኮችን ለተማሪዎች በማንበብ ከመታወቋም ሌላ ከፍ ያለ የሥነ - ጽሑፍ ዝንባሌ እንደነበራት የሚያስታውሱት መምህራኗ “አንድ ቀን ታላቅ የጥበብ ሰው እንደሚወጣት እናውቅ ነበር” ይላሉ፡፡ መዓዛ በ1971 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሥነ - ቋንቋ ጥናት ተቋም ውስጥ በሥነ-ልሣን ትምህርት ክፍል ተመደበች፡፡ ሥነ-ልሣን መዓዛ የምትፈልገው ጥናት ባለመሆኑ በምደባው ቅር ብትሰኝም፤ በንዑስ ትምህርት ደረጃ የምትወስደው የውጭ ቋንቋና ሥነ - ጽሑፍ በመሆኑ ለነበራት ቅሬታ እንደማካካሻ ሆኖላታል፡፡ በዚህ ዩኒቨርሲቲ የሶስተኛ ዓመት ተማሪ ሳለች የተፈጠረ አንድ አጋጣሚ ደግሞ መዓዛንና ሬዲዮንን የሚያስተሳስር ይሆናል፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ ሬዲዮ የፕሮግራሞች ኃላፊ የነበረው አቶ ታደሰ ሙሉነህ ለሚያዘጋጀው የእሁድ የሬዲዮ ፕሮግራም ድራማ የሚጫወቱ ሸጋ ድምጽ ያላቸው ወጣቶችን ሲያፈላልግ ከመዓዛ ጋር ይተዋወቃል፡፡ ድራማው አስታጥቃቸው ይሁን ያሰናዳው ሲሆን የመዓዛ ድምጽ ለሙከራ በስቱዲዮ ተቀርጾ ሲሰማው፣ ታደሰ ሙሉነህ የሚፈልገውና የሚወደው ድምጽ ሆኖ ስላገኘው ይደሰታል፡፡ ከዚህ በኋላም ለእሁድ ፕሮግራም የሚሆኑ ጽሑፎችን በየሳምንቱ እንድታነብለት ያግባባትና የመዓዛና የሬዲዮ ፍቅር በኢትዮጵያ ሬዲዮ ይወለዳል፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የመዓዛ ድምጽ በእሁድ የሬዲዮ ፕሮግራም አድማጮች ዘንድ የተለመደና የተወደደ ሆነ፡፡ መዓዛም የሌሎችን ጽሑፎች በማንበብ ብቻ ሳትወሰን የራሷን ጽሁፎች እያዘጋጀች የምታቀርብ ንቁ ተሳታፊ በመሆን ከሬዲዮ ፕሮግራሙ ቤተሰቦች እንደ አንዱ ሆነች፡፡ በ1974 ዓ.ም ከዩኒቨርሲቲ ተመርቃ ትምህርቷ ፍጻሜውን እስካገኘ ድረስም መዓዛ ሬዲዮና ትምህርትን ጎን ለጎን ስታስኬድ ቆይታለች፡፡ የመዓዛ የሥራ ዓለም የተጀመረው ግን በምትወደውና በምትፈልገው በኢትዮጵያ ሬዲዮ ውስጥ ሳይሆን መንግስት በመደባት በባህል ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ውስጥ ነበር፡፡ ስራዋም ባህልና ስፖርት የተባለው የመስሪያ ቤቱ መምሪያ በሚያሳትመው “መርሐ ስፖርት” የተሰኘ ወርሃዊ የስፖርት መጽሔት (በኋላ ጋዜጣ) ላይ ሆነ፡፡ ምንም እንኳ አዲሱ ስራዋ ከራዲዮ የሚያርቃት ቢሆንም መዓዛ ግን ሳትሸነፍ ሬዲዮን በትርፍ ጊዜ ሥራነት ተያያዘችው፡፡ ሬዲዮ ጣቢያው የሚሠጣትን አነስተኛ ክፍያ እየተቀበለችም ልዩ ልዩ ጭውውቶችን እና መጣጥፎችን በግልና በጋራ በማቅረብ ተወዳጅ ሥራዎቿን ለሕዝብ አበርክታለች፡፡ \n \nጥያቄ: መዓዛ ብሩ በስንት ዓመተ ምህረት ተወለደች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 1951 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበሊትር እስከ 40 ኪሎ ሜትር መጓዝ የምትችል ተሸከርካሪ በኢትዮጵያዊ ወጣት መሰራቱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ በወላይታ ዞን አረካ ከተማ ነዋሪ የሆነው ታዳጊ አጃዬ ማጆር ተሸከርካሪዋን ከወዳደቁ ብረቶች እንደሰራት ተነግሯል፡፡ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ባደረገለት ድጋፍ የተሰራችው የባለ ሁለት እግር ተሸከርካሪ ሞተርን በመጠቀም የተሰራች ሲሆን ወደ ኋላ መሄድ እንድትችል ተደርጋ ተሻሽላ ተሰርታለች፡፡ አራት ኩንታል ክብደት ያላት ተሽከርካሪዋ እስከ 4 ሰዎች የመጫን አቅም ያላት ሲሆን በአንድ ሊትር እስከ 40 ኪሎ ሜትር መጓዝ ትችላለች ተብሏል፡፡ ታዳጊው የ11ኛ ክፍል ተማሪ ሲሆን ከዚህ በፊትም ተመሳሳይ መኪና መስራቱ ተገልጿል፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለታዳጊው የተለያዩ ድጋፎችን እንደሚያደርግ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ \n \nጥያቄ: አጃዬ ማጆር በትምህርት ደረጃው ስንተኛ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የ11ኛ ክፍል ተማሪ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዓጼ ኃይለ ሥላሴ ዘውድ እንደጫኑ የአገሪቱን የመጀመሪያ ሕገ-መንግሥት እንዲዘጋጅ አዝዘው በዘውዱ አንደኛ ዓመት በዓል ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፬ ዓ.ም. በአዲሱ ምክር ቤት (ፓርላማ) ለሕዝብ ቀረበ። ከዚህም በላይ ብዙ የቴክኖዎሎጂ ስራዎችና መሻሻያዎች ወደ ኢትዮጵያ ከውጭ አገር አስገቡ። በ፲፱፻፳፰ ዓ.ም. የሙሶሊኒ ፋሺስት ሠራዊት ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ጃንሆይ ሕዝባቸውን ወራሪውን በሙሉ ለመቃወም እንዳስነሡና የከተት ዐዋጆቻቸው በታሪክ ገጾች ይዘገባሉ። በዐዋጅ መሠረት የዘመቻው ጊዜ እስቲያልቅ ድረስ ለሚታግሉ ነጋዶች ከቀረጥ አስተስርየት ሰጣቸው። እራሳቸው በቆራጥነት ከታገሉ በኋላ የጠላቱ ጦር ኅይል ግን በመጨረሻ ወደ እንግሊዝ አገር ለጊዜው አሰደዳቸው። ወደ ጄኔቭ ስዊስ ወደ ዓለም መንግሥታት ማኅበር ሄደው ስለ ጣልያኖች የዓለምን እርዳታ በመጠየቅ ተናገሩ። የዓለም መንግሥታት ግን ብዙ አላደረጉም። በ፲፱፻፴፪ ዓ.ም. ግን አውሮፓ ሁሉ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ተያዘ። የእንግሊዝ ሠራዊቶች ለኢትዮጵያ አርበኞች እርዳታ በመስጠት ጣልያኖች ተሸንፈው በ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. ኢትዮጵያን ተዉ። ዓፄ ኃይለ ሥላሴ አዲስ አበባን እንደገና የገቡበት ቀን ከወጡበት ቀን በልኩ ዕለት አምስት ዓመት በኋላ ነበረ። ከዚህ በኋላ በ1948 ዓ.ም. ተሻሽሎ የወጣ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት የሕዝቦችን መብቶችና ተከፋይነት በመንግሥት አስፋፍቶ ሁለቱ ምክር ቤቶች እንደመረጡ አደረገ። በ፲፱፻፶፭ ዓ.ም. ግርማዊነታቸው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በአዲስ አበባ እንዲመሠረት ብዙ ድጋፍ ሰጡ። በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. ወደ ካሪቢያን ጉብኝት አድርገው የጃማይካ ራስታዎች ተገኛኙ። በ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. በማርክሲስት አብዮት ደርግ ሥልጣን ያዙና እሳቸው በእሥር ቤት ታሰሩ። በሚከተለው ዓመት ከተፈጥሮ ጠንቅ እንደ አረፉ አሉ ፤ ሆኖም ለምን እንደ ሞቱ ስለሚለው ጥያቄ ትንሽ ክርክር አለ። ብዙ ራስታዎች ደግሞ አሁን እንደሚኖሩ ይላሉ። የዓፄ ኃይለ ሥላሴ የትውልድ ስም ልጅ ተፈሪ መኮንን ነው። ስመ-መንግሥታቸው ግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ነበር። ሞዓ አንበሣ ዘእምነገደ ይሁዳ ሥዩመ እግዚአብሔር ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ የሚለው የሰሎሞናዊ ሥረወ-መንግሥት ነገሥታት መጠሪያም በንጉሠ-ነገሥቱ አርማ እና ሌሎች ይፋዊ ጽሑፎች ላይ ከመደበኛው ማዕረግ ጋር ይጠቀስ ነበር። ጃንሆይ ፣ ታላቁ መሪ እና አባ ጠቅል በመባልም ይታወቁ ነበር። \n \nጥያቄ: የአጼ ኃይለ ሥላሴ የመንግስት ስማቸው ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበምዕራቡ ዓለም ውስጥ ስለ ፀሓይ ሳይንሳዊ መግለጫ ለመስጠት ከቻሉ ቀዳሚ ሰዎች አንዱ ግሪካዊው ፈላስፋ አናክሳጎራስ ነበር። ፀሓይ በእሳታዊ ነበልባል የምትንቀለቀል እጅግ ግዙፍ የብረት ኳስ እንጂ የሄሊዮስ ሰረገላ እንዳልነበረች በምክንያት የተደገፈ ትንተና አቀረበ። ይህንን እንደ ኑፋቄ የተቈጠረ ሐተታ በማስተማሩም ታሰረ፤ በሞት እንዲቀጣም ተፈርዶበት ነበር፤ በፔሪክልስ አማላጅነት እንዲፈታ ተፈቀደለት እንጂ። የባለሥልጣናት መዓት የወደቀበት ሌላው የሳይንስ ሊቅ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነበር። በ16ኛው ምእት ውስጥ የኖረው ቆጰርኒቆስ ምድር ፀሓይን በቀለበትማ ምሕዋር ትዞራለች እንጂ፣ ፀሓይ ምድርን አትዞርም የሚል ኀልዮ አቅርቦ ነበር። በ17ኛው ምእት ጋሊሌዮ በቴሌስኮፕ ለታገዘ የፀሓይ ጥናት ፈር-ቀዳጅ ሊቅ ኾነ። አይዛክ ኒውተን ደግሞ በፕሪዝም አማካይነት የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ አሳየ። 19ኛው ምእት ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የኾነበት፣ በስፔክትሮስኮፕ ስለ ፀሓይ የሚደረገው ጥናትም እጅግ የመጠቀበት ምእት ኾነ። ዛሬ በብዙ አገሮች ልማድ ፀሓይ እንደ ባህላዊ ምልክት ትታያለች። ለምሳሌ በሜክሲኮ ኪነ ጥበብ አበክራ የምትታይ ሞቲፍ በመባል ትታወቃለች። በኛ ሥርዐተ-ፀሓይ ዋናዋ ትልቅ አካል ራሷ ፀሓይ ናት። በመላው ሥርዐተ-ፀሓይ ውስጥ ከሚገኘው ክብደት 99.86% የፀሓይ ነው። ለምሳሌ ከታላቁ ፈለክ ከጁፒተር ሲነጻጸር የፀሐይ ክብደት 1000 ዕጥፍ ይበልጣል። የፀሓይ ክብደት ከምድር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ ይበልጣል። በጣም ግዙፍ እና ከባድ የኾነችው ኮከብ ከምድር ያለችበት ርቀት በጣም የሚያስደንቅ ነው። በምድር እና በፀሓይ መካከል ያለው ርቀት የምድርን ዳያሜትር በ12,000 ጊዜ ይበልጣል። ብርሃን ይህን ርቀት ለመጓዝ 8.5 ደቂቃ ይፈጅበታል። \n \nጥያቄ: ስለፀሓይ በስፔክትሮስኮፕ እጅግ ብዙ ጥናት የተጀመረበት ክፍለ ዘመን መች ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 19ኛው ምእት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዳምጠው አየለ ዳምጠው አየለ (23.11. 1944 አ/ም – 27.10. 2006 አ/ም) ባህላዊ የኢትዮጵያ ዘፋኝ ነበር። በሃምሌ 23 1944 አ/ም ከእናቱ ወይዘሮ ሸዋየ ተካና ከአባቱ አየለ ካሰኝ በመራቤቴ ሰሜን ሸዋ ተወለደ። ልጅነቱን በእረኝነት፥ በግብርና እንዲሁም በቆሎ ተማሪነት እንዳሳለፈ ይናገራል። እድሜውም ለትምህርት ሲደርስ ባቅራቢያው በሚገኘው መራኛ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገብቶ ተምሯል። ዳምጠው ህይወቱ እስካለፈችበት ጊዜ ድረስ ለረዥም ጊዜ አብሯት የኖረው ባለቤቱ አልማዝ ይመር ትባላለች። ከአልማዝ ይመር አብዩ ዳምጠውና ቤቴልሄም ዳምጠው የሚባሉ ሁለት ልጆችን አፍርቷል። ዳምጠው መራቤቴ እያለ በየባእላቱ መዝፈን፣ ማቅራራት እንዲሁም መሸለል ይወድ እንደነበር ተናግሯል። በተለይም ጥምቀትን በማድመቅ ይታወቅ ነበር። የ 6ኛ ክፍል ተማሪ እያለ ክፍሌ ሞገስ የሚባል መምህሩ ወደ አዲስ አበባ ይዞት እንደመጣ ይናገራል። ባጋጣሚም የምድር ጦር ማስታወቂያ አውጥቶ ስለነበር ይፈተንና ያልፋል። የምድር ጦር ካምፕ ውስጥም እንዲኖር ይደረጋል። የዘፋኝነት ሙያው በዚህ አጋጣሚ ነበር የጀመረው። ዳምጠው ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማዉና መነሻ የሆነው አበበ ተሰማ እንደሆነ ይናገራል። ዳምጠው አየለ በምድር ጦር ከ 30 አመት በላይ አገልግሏል። የኢትዮዽያ ምድር ጦር በ1927 አ/ም ተመስርቶ በ1983 አ/ም የፈረሰ የሙዚቃ ቡድን ነበር። ዳምጠው በመንግስት ለውጥ ምክንያት እስከፈረሰበት ጊዜ ድረስ አብሮ እንደነበር ይናገራል። ምድር ጦርም እያለ ከነታምራት ሞላ፣ ሲራክ ታደሰ፣ ተክሌ ደስታ ፣ ጥላየ ጨዋቃ፣ ክፍሌ አቦቸር እንዲሁም ሌሎች የጦሩ አባላት ጋር ሰርቷል። ከሌሎች የሙዚቃ ቡድንም ጋር አብሮ ሰርቷል። ለምሳሌ ያክል ከነ ክቡር ጥላሁን ገሰሰ፣ ሙሃሙድ አህመድ፣ ብዙነሽ በቀለ ፣ ሙሉቀን መለስ፣ ፀሃየ ዮሃንስ፣ ቴድሮስ ታደሰ፣ቴድሮስ ካሳሁን እንዲሁም ሌሎችም ጋር ሰርቷል። የዳምጠው አየለ የመጀመሪያ የህትመት ስራው በ1963 አ/ም ሲሆን ወፌ ላላ የሚለው የሸክላ ስራ ነበር። ዳምጠው አየለ ባጠቃላይ 13 ሲዲዎችን ሰርቷል። ዳምጠው አየለ ኖርዌይ ሃገር በስደት ለ 8 አመት ያክል ኖሯል። ኢትዮጵያም ከገባ በኋላ አዲስ አበባ በሚገኘው በቅ/ገብራኤል ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በተወለደ በ 62 አመቱ ሰኔ 27 2006 አ/ም ቀን ህይወቱ አልፏል። የቀብር ስነስርአቱም ወዳጅ፣ ዘመድ እንዲሁም አድናቂዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: የዳምጠው አየለ ሁለቱ ልጆች ማን ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አብዩ ዳምጠውና ቤቴልሄም ዳምጠው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: በ1887 ዓ.ም. የብሪታንያ ደቡብ አፍሪካ ድርጅት የዛምቤዚያን ስም ምን ብሎ ቀየረው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሳምሰንግ ኩባንያ በተጠናቀቀው የፈረንጆች ዓመት 6 ነጥብ 7 ሚሊየን አምስተኛ ትውልድ (5ጂ) ኢንተርኔት የሚጠቀሙ ዘመናዊ ስልኮችን ለደንበኞቹ ሸጧል። ኩባንያው በዓመቱ 4 ሚሊየን 5ጂ ስማርት ስልኮችን ለመሸጥ አቅዶ 6 ነጥብ 7 ሚሊየን ስልኮችን በተሳካ ሁኔታ መሸጡን አስታውቋል። ይህን ተከትሎም ኩባንያው 5ጂ ኢንተርኔት የሚጠቀሙ ስልኮችን በደንበኞች እጅ በማድረስ ከተቀናቃኞቹ የተሻለው ሆኗል። በዓመቱ ለገበያ ከቀረቡ ዘመናዊ ስልኮች ውስጥ ሳምሰንግ ኤስ ኤስ ኤን አል ኤፍ የተሰኘው ሞዴል ብባዛት መሸጡ ተመላክቷል። እንዲሁም ሳምሰንግ ጋላክሲ ኖት 10ጂ፣ 10+5ጂ፣ ኤ90 5ጂ እና የመተጣጠፍ ችሎታ ያለው ጋላክሲ 5ጂ በዓመቱ ለገበያ የቀረቡ ሞዴሎች ናቸው። ሳምሰንግ በአዲሱ የፈረንጆች ዓመትም ለኩባንያው የመጀመሪያ የሆነውን ኤስ6 የተሰኘ 5ጂ ኢንተርኔት የሚጠቀም ታብሌት ለገበያ እንደሚያቀርብ ገልጿል።   ምንጭ፦ ሲ ኤን ኤን \n \nጥያቄ: ሳምሰንግ በዓመቱ ሊሸጣቸው ገበያ ላይ ከዋሉት ስማርት ስልኮች ውስጥ በብዛት የተሸጠው ሞዴል ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሳምሰንግ ኤስ ኤስ ኤን አል ኤፍ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኤርትራ ኤርትራ በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ አገሮች አንዷ ስትሆን በስሜን-ምዕራብ ከሱዳን፣ በሰሜን-ምስራቅ ከቀይ ባህር፣ በደቡብ ከኢትዮጵያ፣ በደቡብ-ምስራቅ ጅቡቲ ጋር ድንበር ትካለላለች። ኤርትራ የሚለው ስም ከላቲን የተወሰደ እና ስረ-መሰረቱ የግሪክ ሐረግ ሲሆን ትርጉሙም ቀይ ማለት ነው። ይህን ስም ለአካባቢው የሰጡት ጣሊያኖች በጥር ፲፰፻፺ ቅኝ ግዛታቸውን ሲያውጁ ነበር (ተመሳሳይ ስም በጀርመኖች 1870 እና ግብጾች ፲፰፻፷ወቹ በጥቅም ላይ ውለዋል፣ ነገር ግን የትኛውን ክፍል ስሙ እንደሚመለከት ግልጽ አልነበረም)። ኤርትራ፣ እንደ ሐገር፣ በጣሊያኖች ከተመሰረተች በኋላ በ5 ልዩ ሂደቶች ውስጥ በማለፍ ነው ያሁኑን ቁመናዋን የያዘችው። ከ1890 በፊት የነበረው የአካባቢው ታሪክ በ«ኤርትራ» ስር የሚጠና ባህይሆንም ስለአዲሱ ኤርትራ ግንዛቤ ስለሚያስጨብጥ ታሪክ ተመራማሪዎች ከ፲፰፻፺ በፊት ያለውንም ታሪክ ማጥናት ተገቢ እንደሆነ ይስማማሉ። በ1860ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ፣ የግብጹ መሪ ኢስማኤል ከዴቭ ፓሻ በናይል ተፋሰስ ላይ ሰፊ የግብጽ ቅኝ ግዛት ለማበጀት ተነሳ። ለዚህ አዲሱ ግዛቱ ካርቱምን ዋና ከተማው በማድረግ የሱዳን ግዛቱን አጸና። ቀጥሎም የቀይ ባህርን ጠረፎች በ1865 ከተቆጣጠረ በኋላ በ1870ዎቹ መጀመሪያ ሐረርንና ተሻግሮ ሕንድ ውቅያኖስ ውስጥ ግዛቶችን አበጀ። እንግዲህ በኒህ ግዛቶቹና በሱዳን መካከል የነበረው ብቸኛ መገናኛ መንገድ ካርቱም-ከሰላ- ከረን -ምፅዋ ብሎ የሚዘልቅ ነበር። ስለሆነም በ1872 ይህን ስልታዊ መንገድ የክዴቭ ፓሻ ሰራዊቶች ተቆጣጠሩ። መቆጣጠር ብቻ አይደለም በየመንገዱ ምሽግ እየሰሩና የአውሮጳ ምስዮናውያንን እርሻ ቦታ እየሰጡ ቅኝ ግዛት አበጁ። በዚህ ሳይቆጠቡ፣ የመንገዱን ደህንነት ዋስትና ለማስጠበቅ ሲሉ የአካባቢውን ደጋማ ክፍል መያዝ ግድ አላቸው። ደጋማው ክፍል በዚህ ወቅት በአጼ ዮሐንስ ግዛት ስር ነበር። \n \nጥያቄ: ኤርትራ በየት የምትገኝ ሀገር ናት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በምስራቅ አፍሪካ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበርግጥም የመጀመሪያው በሰፊው ተግባራዊ የሆነ የቴሌቭዥን ስርዓት ስራ ላይ የዋለው በጀርመን አገር ሲሆን ይኸውም በ1929 እ.ኤ.አ. ነው። በ1936 እ.ኤ.አ. (1928 ዓም) ጀርመን ሃገር ተደርጎ የነበረውን የኦሎምፒክ ውድድር በቴሌቭዥን ሊሰራጭ ቻለ፣ ህዝቡም ውድድሩን እቤቱ ሆኖ ቀጥታ ሲካሄድ ለማየት ቻለ። ከዚያ መጀመርያው ጥቁርና-ነጭ ፕሮግራሚንግ በዩናይትድ ኪንግደም 1928 ዓም፤ በአሜሪካ 1933 ዓም ተደረገ። በአፍሪካ መጀመርያው ጣቢያዎች በ1952 ዓም በናይጄሪያና ደቡብ ሮዴዝያ (አሁን ዚምባብዌ) ተሰራጩ፣ በኢትዮጵያ የቴሌቪዥን ስርጭት አገልግሎት (ኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን) የጀመረው በ1956 ዓም ሆነ። ሁለት አገራት - እነርሱም ቱቫሉና ኪሪባስ - ምንም የራሳቸውን ቴሌቪዥን አሁን አያሰራጩም፤ ሆኖም የሌላ አገር ስርጭት እዚያ ሊታይ ይችላል። ከዚያ ቤርድ በግንቦት 26 ቀን 1920 (ጁላይ 3, 1928 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የከለር ቴሌቪዥን ስርጨት ሙከራ አደረገ። ነገር ግን ከለር ቴሌቪዥን ቢፈጠረም ለሚከተሉት ብዙ ዓመታት ስርጭት ባብዛኛው ጥቁርና ነጭ ብቻ ሆኖ ቀረ። ይሄው ቴክኖዎሎጂው በጣም ውድ፣ በጣም ከባድና በትክክል ያልተስተካከለ ስለ ሆነ ነው። በየጥቂቱ ከ1946 ዓም (1954 እ.ኤ.አ.) ጀምሮ አገራት ወደ ከለር ስርጭትና ከለሩን ማሳየት የሚችል ቴሌቪዥን ወደ መሸጥ ይዛወሩ ጀመር። በጥር ወር 1946 ዓም NBC የተባለው አሜሪካዊ ስርጭት ጣቢያ በከፊሉ ወደ ከለር ተሸጋገረ፤ ብዙ ሰዎች ግን ያንጊዜ ከለር ማሳያ ቴሌቪዥን ለመግዛት ገና አልቻሉም ነበር። ከ1955 እስከ 1959 ዓም ድረስ ሌሎቹ ትልልቅ አሜሪካዊ ጣቢያዎች ABC እና CBS ደግሞ ወደ ከለር ተዛወሩ፣ የከለርም ተቀባዮች ዋጋ እየተቀነሰ የሚይዩት ሕዝብ ቁጥር ደግሞ ከዚህ በኋላ እየተጨመረ ሄደ፤ ከረጅሙ ጥቁርና-ነጭ ዘመን ቀጥሎ ከለርም በኅብረተሠብ ያመጣው ለውጥ ለግዙፍነቱ በኋላ ኢንተርኔት እንደ ሆነ ያሕል ነው። ጃፓን በ1952 ዓም፣ ሜክሲኮ በ1955፤ ካናዳ በ1958፣ የአውሮፓ ኅብረትና የሶቪዬት ሕብረት በ1959፣ ኮት ዲቯር በ1962፣ አውስትራሊያ በ1967 ከለር ስርጭትን ጀመሩ። በኢትዮጵያም ከለር ስርጭት ከ1976 ዓም ጀምሮ ተገኝቷል። በ1977 ዓም ሮማኒያ ከጥቁርና-ነጭ ስርጭት ወደ ከለር ማሰራጨት የለወጠ በዓለም መጨረሻው ሃገር ሆነ። \n \nጥያቄ: በጃፓን የቀለም ቴሌቭዥን ስርጭት የተጀመረው ከመቼ ጀምሮ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ1952 ዓም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኒኑስ ኒኑስ በጥንታዊ የግሪክ ታሪክ ጸሃፊዎች ዘንድ የነነዌ መስራችና የአሦር ንጉስ ነበረ። ለዘመናዊ ሥነ ቅርስ የታወቀ አንድ ግለሰብ አይመስልም፤ ዳሩ ግን የአያሌ ታሪካዊ ወይም አፈ ታሪካዊ ግለሰቦች ትዝታ በአንድ ስም በግሪኮች በኋለኛ ዘመን እንደ ተዘከረ አሁን ይታስባል። የንጉሥ ኒኑስና ሚስቱ ንግሥት ሴሚራሚስ ስሞች በጽሁፍ መጀመርያ የተገኘው ክቴስያስ ዘክኒዱስ (400 ዓክልበ. ገዳማ) በጻፈው በፋርስ አገር ታሪክ ነው። ክቴስያስ ለ2 አርጤክስስ (2 አርታሕሻጽታ) የመንግሥት ሀኪም ሆኖ የፋርስ ነገሥታት ታሪካዊ መዝገቦች አንብቤያለሁ ብሎ አሳመነ። ከዚህ በኋላ የግሪክ ታሪክ ጸሐፊ ዲዮዶሮስ ሲኩሉስ የክቴስያስን ወሬ አስፋፋ። የአለም ታሪክ ሊቃውንት እስከ 1880ዎቹ ድረስ የኒኑስ ታሪክ ዕውነት መሆኑን ይቈጠሩት ነበር። በዚያን ጊዜ የኩኔይፎርም ጽሕፈት ፍች ስለ ተፈታ፣ በሜስፖጦምያና በነነዌ ብዙ ቅርሶችም በመገኘታቸው፣ የአሦር ትክክለኛ ታሪክ ዕውቀት ተጨመረልን። ኒኑስ የቤሉስ ወይም ቤል ልጅ ተባለ፤ ይህም ምናልባት በሴማዊ ቋንቋ ሥር «ባል» (ጌታ) የመሰለ ማዕረግ ሊሆን ይችላል። በካስቶር ዘሮድስ ዘንድ ኒኑስ ለ52 ዓመታት ነገሰ፤ ክቴስያስም እንዳለው መጀመርያው ዓመተ መንግሥቱ 2198 ዓክልበ. ነበረ። በ17 አመታት ውስጥ ኒኑስ በአረቢያ ንጉስ አርያዎስ እርዳታ ምዕራብ እስያን በሙሉ እንዳሸነፈ ተብሏል። ከዚህ ቀጥሎ የአርመን ንጉስ ባርዛኔስን (ይቅርታ የሰጠውን) እና የሜዶን ንጉስ ፋርኖስን (በስቅለት ይሙት በቃ የሰጠውን) ድል በማድረግ የአለም መጀመርያ ንጉሠ ነገስት እንደ ሆነ ተብሏል። \n \nጥያቄ: ኑኒስ ለ52 አመት የነገሰው በየትኞቹ ወገን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በካስቶር ዘሮድስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nለአጽዋማትና በዓላት ማውጫ ወሳኝ የሆነው ነጥብ መባጃ ሐመር ነው፡፡ መባጃ ሐመር መባጊያ ሐመር እየተባለም ይጠራል፡፡ መባጊያ ሐመር ሲሆን የበጋ መመላለሻ የሚል ትርጉም ይሰጣል፡፡ በሌላ በኩል መባጃ በራሱ ማቆያ፣ ማክረሚያ ተብሎ ይተረጎማል፡፡ ሐመር መርከብ፣ መጓጓዣ የሚለውን ትርጉም ያስገኛል፡፡ መባጃ ሐመር የመጥቅዕና የዕለታት ተውሳክ ድምር ሆኖ አጽዋማትና በዓላት የሚውሉበትን ቀን ያመለክታል፡፡ በሐመር የተመሰለውም አጽዋማትና በዓላት ወደ ላይና ወደታች የሚመላለሱበት ሥርዓት /መርከብ/ ስለሆነ ነው፡፡ በአጠቃላይ መባጃ ሐመር ማለት የአጽዋማትንና የበዓላትን መዋያ ወይም መግቢያ ቀን ለማወቅ የሚያገለግል ልዩ ቁጥር ማለት ነው፡፡ ከሰባቱ አጽዋማት መካከል አራቱ በመባጃ ሐመር መሠረት በየዓመቱ እየተቀያየሩ ወይም ቀመር እየተሠራላቸው የሚወጡ ሲሆን፣ ሦስቱ ግን ያለ መባጃ ሐመር በየዓመቱ በተመሳሳይ ወቅት ይባጃሉ፡፡ በመባጃ ሐመር የሚባጁት አራት አጽዋማት ዐቢይ ጾም፣ ጾመ ድኅነት፣ ጾመ ነነዌና ጾመ ሐዋርያት ሲሆኑ፣ ያለ ማባጃ ሐመር በየዓመቱ ቋሚ ጊዜ ይዘው የሚብቱት ሦስቱ አጽዋማት ደግሞ ጾመ ነቢያት፣ ጾመ ገሃድና ጾመ ማርያም /ፍልሰታ/ ናቸው፡፡ ከላይ በተመለከትነው መሠረት መባጃ ሐመር የአጽዋማትና የበዓላት ማስገኛ ልዩ ቁጥር ነው ካልን ቁጥሩ እንዴት እንደሚገኝ ማወቅ ያስፈልገናል፡፡ መባጃ ሐመርን ለማግኘት መጥቅዕንና በዓለ መጥቅዕ የዋለበትን ዕለት ተውሳክ እንደምራለን፡፡ \n \nጥያቄ: መባጃ ሐመር ሳያስፈልጋቸው ቋሚ ጊዜ ጠብቀው የሚጀምሩ አጽዋማት የትኞቹ ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ጾመ ነቢያት፣ ጾመ ገሃድና ጾመ ማርያም /ፍልሰታ/ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nክልሉ የትልልቅ ወንዞች ባለቤት ሲሆን በአጠቃላይ በሦስት ዋና ዋና ተፋሰሶች ተከፋፍሎ ሊታይ የሚችል ነው። እነርሱም የዓባይ፣ የተከዜ እና የአዋሽ ተፋሰስ ናቸው። ወደነዚህ ተፋሰሶች የሚገቡና ዓመቱን በሙሉ የማይደርቁ ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ ትልልቅ ወንዞች ያሉ ሲሆን በክልሉ በጥቅም ላይ ያልዋለ ሰፊ የውሐ ሀብት መኖሩን ያመለክታሉ። ከነዚህ በተጨማሪ እንደ ጣናና አርዲቦ የመሳሰሉ ሐይቆችም በክልሉ ውስጥ ይገኛሉ። በአጠቃላይ በክልሉ ውስጥ ባሉ ትልልቅ ወንዞችና መጋቢ ወንዞች የመስኖ ልማት ለማካሄድ የሚያስችል ከፍተኛ የውሐ ሐብት ክምችት እንዳለ መገንዘብ ይቻላል። ይሁን እንጅ እስከ አሁን ጥቅም ላይ የዋለው በጣም አነስተኛ ነው። በአመዛኙ አብዛኛው የክልሉ ምጣኔ ሀብት በግብርና እና ከብት እርባታ ላይ የተመሠረተ ነው። በአጠቃላይ ክልሉ ከፍተኛ የሆነ የሕዝብ ቁጥር፣ ለእርሻና ለእንስሳት እርባታ ተስማሚ የሆነ መሬት፣ የአየር ንብረት እና የውሐ ሀብቶች ያሉት በመሆኑ በተለይም የሰብል እና የእንስሳት ሀብት ልማት ለማካሄድ የማይናቅ አቅም አለው። በዝናብም ሆነ የመስኖ እርሻ ልማት በማስፋፋት በክልሉ በገበያ የሚውሉ የተለያዩ የአገዳ፣ የጥራጥሬ፣ የቅባት፣የአትክልትና ፍራፍሬ ሰብሎችን ማምረት ይቻላል። ጤፍ፣ ገብስ፣በቆሎ፣ ማሽላ፣ዳጉሣ፣ ስንዴ፣አተር፣ ባቄላ፣ ሽምብራ፣ ጓያ፣ምስር፣ሰሊጥ፣ ጥጥ፣ ተልባ፣ ወዘተ የመሳሰሉት በክልሉ ውስጥ ከሚመረቱ ሰብሎች መካከል ዋና ዋናዎቹ ናቸው። በእንስሳት ሀብት ረገድም በወተት ምርታማነታቸው የታወቁ የፎገራ ዝርያዎችና በፀጉር ምርት የታወቁት የመንዝ በግ ዝርያዎች በክልሉ ይገኛሉ። በቱሪዝም የሥራ መስክ ሊበለጽጉ ፣በሰፊው አገልግሎት ሊሰጡ የሚችሉ እና በዓለም የቅርስ መዝገብ የሰፈሩት የጐንደር ቤተ መንስግት ህንፃዎች፣ የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት፣ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ እንዲሁም ልዩ ልዩ የቱሪዝም መስሕቦች አሉት፣ ይሁን እንጅ ክልሉ ሰፊ የሆነ የቱሪዝም እምቅ ሀብት ያለው ቢሆንም በሚፈለገው መጠን በጥቅም ላይ ውሏል ማለት አያስደፍርም። በዚህ ረገድ፤አካባቢዉ የብዙ ታሪካዊ ገዳማትና የታሪካዊ ቅርሶችም ባለሀብት ነው። \n \nጥያቄ: በአማራ ክልል ውስጥ ተጠቃሽ ከሆኑት ሐይቆች እነማን ይገኛሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ጣናና አርዲቦ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአዲስ አበባ አዲስ አበባ ተብላ የተሠየመችው እቴጌ ጣይቱ ኅዳር ፲፬ ቀን ፲፰፻፸፱ (1879) ዓ.ም. ፍልውሃ ፊን-ፊን ወደሚልበት መስክ ወርደው ሳሉ ከዚህ በፊት አይተዋት የማያውቋት አንዲት ልዩ አበባ አይተ ስለማረከቻቸው ቦታውን ‹‹አዲስ አበባ!›› አሉ ይባላል። አዲስ አበባ (ኣዲስ ኣበባ) ኢትዮጵያ ዋና ከተማ ስትሆን በተጨማሪ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ እንዲሁም የብዙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቅርንጫፎችና ሌሎችም የዓለም የዲፕሎማቲክ (የሰላማዊ ግንኙነት) ልዑካን መሰብሰቢያ ከተማ ናት። ራስ-ገዝ አስተዳደር ስላላት የከተማና የክልል ማዕረግ ይዛ ትገኛለች። አብዛኞቹን የሀገሩ ቋንቋዎች የሚናገሩ ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞች የሚኖሩባት ከተማ ናት። ከባሕር ጠለል በ2500 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኘው ከተማ በግምት 2,757,729 በላይ ሕዝብ የሚኖርባት በመሆኗ የሀገሪቱ አንደኛ ትልቅ ከተማ ናት። ከተማዋ እቴጌ ጣይቱ በመረጡት ቦታ ማለትም በፍል ውሐ አካባቢ ላይ በባላቸው በዳግማዊ ምኒልክ በ፲፰፻፸፰ (1878) ዓ.ም. ተቆረቆረች። የሕዝቧ ብዛት በያመቱ 8% (ስምንት በመቶ) እየጨመረ አሁን አምስት ሚሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከእንጦጦ ጋራ ግርጌ ያለችው መዲና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መገኛ ሆናለች። ይህም በመስራቹ የቀድሞው ንጉሠ-ነገሥት ስም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ይባል ነበር። \n \nጥያቄ: በዳግማዊ ምኒልክ በ፲፰፻፸፰ (1878) ዓ.ም. እቴጌ ጣይቱ በመረጡት ቦታ የተቆረቆረችው ከተማ ማን ትባላለች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ አዲስ አበባ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቶማስ ጄፈርሰን ቶማስ ጄፈርሰን (ሚያዝያ 7 ቀን 1735 ~ ሰኔ 28 ቀን 1818 ዓ.ም.) ከየካቲት 26 ቀን 1793 እስከ የካቲት 25 ቀን 1801 ዓ.ም. ድረስ የአሜሪካ 3ኛ ፕሬዝዳንት ነበሩ። ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቨርጂኚያን ያቋቋሙት ጄፈርሰንም ነበሩ። ቶማስ ጄፈርሰን ከአባቱ ከፒተር ጄፈርስን እና ከእናቱ ጄን ራንዶልፍ ተወለዱ። ቶማስ በአሜሪካ አብዮት ጊዜ በ1768 ዓ.ም. ከእንግሊዝ ንጉሥ የአሜሪካ ነጻነት ዐዋጅ ጻፉ። በኋላ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ የመርከብ ሃያላት ወደ አልጀርስ ላኩ፣ ከናፖሌዎን ደግሞ ሰፊ መሬት በሚሲሲፒ ወንዝ አቅራቢያ (የሉዊዚያና አቅራቢያ የተባለው) ገዝተው ነበር። ይህ ድርጊት የአሜሪካ ስፋት በሁለት እጅ አስፋፋ። \n \nጥያቄ: ቶማስ ጄፈርሰን ከእንግሊዝ ንጉሥ የአሜሪካንን ነጻነት አዋጅ ያወጁት መች ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ1768 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nማርክሲስም-ሌኒኒስም ማርክሲስም-ሌኒኒስም በተለይ በካርል ማርክስና በቭላዲሚር ሌኒን ትምህርት የተመሠረተ ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለም ነው። ማርክሲስም-ሌኒኒስም የአንዳንድ መንግሥት ፍልስፍና በመሆኑ፣ በሃይማኖት ፈንታ እንደ የመንግሥት ሃይማኖት ያህል ያለ ሚና አጫውቷል። በአሁኑ ሰዓት በይፋ የማርክሲስት-ሌኒኒስት መንግሥት ያላቸው አገራት የሚከተሉ ናቸው፦ ቬትናም - ከ1937 ዓም ጀምሮ ማርክሲስት ሲሆን፣ ከ1982 ዓም ይፋዊው ርዕዮተ ዓለም «የሆ ቺ ሚን ሃሣብ» ተብሏል። የቻይና ሕዝባዊ ሪፐብሊክ - ከ1941 ዓም ጀምሮ ማርክሲስት ሲሆን፣ ከ1970 ዓም ይፋዊው ርዕዮተ ዓለም «ሶሻሊስም ከቻይናዊ ጸባይ ጋራ» ተብሏል። ኩባ - ከ1951 ዓም ጀምሮ ርዕዮተ ዓለሙ ማርክሲስት-ሌኒኒስት ሆኗል። ላዎስ - ከ1967 ዓም ጀምሮ ርዕዮተ ዓለሙ ማርክሲስት-ሌኒኒስት ሆኗል። ስሜን ኮርያ - ከ1937 እስከ 1983 ዓም ድረስ በይፋ ማርክሲስት ሲሆን፣ ከ1964 ዓም ጀምሮ ከማርክሲስም የተደረጀው ርዕዮተ ዓለም «ጁቼ» ኰሙኒስም ተብሏል። በ1983 ዓም ደግሞ «ማርክሲስም» በይፋ ተተወ። ርስት ሁሉ የመንግሥት መሆኑ እንጂ የግል ርስት አለመኖሩ የሚገኝበት ሁናቴ የጀርመን ፋላስፋ የካርል ማርክስ ፍልስፍና ውጤት ነው። በተጨማሪ ማርክስ የሃይማኖት ወዳጅ ባለመሆኑ መጠን፣ ባለፈው ጊዜ በማርክሲስም-ሌኒኒስም በተገዙት አያሌ አገራት ውስጥ የሃይማኖት ወይም የኅሊና ነጻነት አልተገኘም። \n \nጥያቄ: ማርክሲስም-ሌኒኒስም በተለይ በካርል ማርክስና በቭላዲሚር ሌኒን ትምህርት የተመሠረተ ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለም ምን ይባላል ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ማርክሲስም-ሌኒኒስም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየእብድ ውሻ በሽታ የእብድ ውሻ በሽታ የየቫይረስ በሽታ ሆኖ ከፍተኛ የየአንጎል መጉረብረብን በሰዎች እና በሌሎች ደመ-ሞቃት እንስሳት ላይ የሚያስከትል ነው። ቅድሚያ ምልክቶቹ ትኩሳት እና በተነከሱበት ቦታ ማሳከክ/ማቃጠልን ያካትታል። እነዚህ ምልክቶች ከሚከተሉት አንድ ወይም የበለጡ ምልክቶች አስከትለው ይመጣሉ- ሃይል የታከለባቸው የሰውነት እንቅስቃሴዎች፣ ከቁጥጥር ወጭ የሆ መሸበር፣ የውሀ ፍራቻ, የሰውነት ክፍለን ለማንቀሳቀስ አለመቻል፣ ግራ መጋባት፣ እና ህሊናን መሳት። ምልክቶቹ ከታዩ በኋላ፣ የእብድ ውሻ በሽታ በአብላጫው ሁልጊዜ ሞትን ያስከትላል። በበሽታው በመያዘዎ እና ምልክቶቹ መታየት የሚጀምሩበት የጊዜ ገደብ በአብዛኛውን ጊዜ ከአንድ እሰከ ሶስት ወራት ባሉት ጊዜ ውስጥ ነው። ሆኖም ግን፣ ይህ የጊዜ ገደብ ከሳምንት ባነሰ እና ከአመት በበለጠ ጊዜ ሊለያይ ይችላል። የጊዜ ገደቡ የሚወስነው የበሽታ አምጭው ረቂቅ ህዋስ ወደ የማዕከላዊ የነርብ ስርዓትለመድረስ በሚፈጅበት እርቀት ነው። የእብድ ውሻ በሽታ በአለም ዙሪያ በአመት ከ26,000 እሰከ 55,000 ሞቶች ምክንያት ነው። ከ95% በላይ እነዚህ ሞቶች የተከሰቱት በኢሲያ እና አፍሪቃነው። የእብድ ውሻ በሽታ ከ150 ሀገራት በላይ እና ከአንታርቲካ በቀር በሁሉም አሀጉራት ይገኛል። ከ3 ቢሊዮን ሰዎች በላይ የእብድ ወሻ በሽታ በሚከሰትበት የአለማችን ከፍሎች ውስጥ ይኖራሉ። እጅግ በአብዛኛው አውሮፓ እና አውስትራሊያ፣ የእብድ ወሻ በሽታ የሚገኘው በሌሊት ወፎች ላይ ነው። \n \nጥያቄ: የእብድ ውሻ በሽታው ምልክት በምን ያህል ጊዜ ይታያል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በአብዛኛውን ጊዜ ከአንድ እሰከ ሶስት ወራት ባሉት ጊዜ ውስጥ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየአባ ጊዮርጊስ ትምህርታቸው የአባ ጊዮርጊስ አባት ሕዝበ ጽዮን በቤተ መንግሥት በንጉሡ ስዕል ቤት ከሚያገለግሉት ካህናት ጋር ይሠሩ ስለነበር ልጃቸው በመልካም አስተዳደግና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት በማስተማር በዕውቀት አሳድገዋቸዋል። በድቁናም አሹመዋቸዋል። ከዚያም በኋላ በንጉሥ ዳዊት ዘመን (፲፫፻፸፮ ፥ ፲፬፻፭) በደብረ ሐይቅ ባሕር ወደምትገኘው የቅዱስ እስጢፋኖስ አባ እየሱስ ሞዐ ገዳምና ታዋቂ ትምህርት ቤት ወስደው ከታላቁ ዓቃቤ ሰዓት አባ ሠረቀ ብርሃን ጉባዔ ተቀላቅለው እንዲማሩ አድርገዋል ። ይሁን እንጂ አባ ጊዮርጊስ በትምህርት ቤቱ የሚሰጡትን የቀለም ትምህርቶች ቶሎ ለማጥናት አልቻሉም ። ወደ ኋላ የመቅረታቸው ዋናው ምክኒያትም አባ ጊዮርጊስ ከመማሩ ይልቅ የማረካቸው በሥራ እየደከሙ የገዳሙን አባቶች መርዳትና የብትህውናው ሕይወት መሆኑ ነው ። ጉዋደኞቻቸው በትምህርት ሲቀድሙአቸው ባዩ ጊዜ እጅግ አዘኑ ። በጾምና ጸሎትም ወደ እግዚአብሔር ጮሁ በፍፁም ልባቸውም አምነው ብርቱ ልመናን ከእመቤታችን ሥዕል ፊት ቁሞ በጠለቀ ተመስጦልቦና እንባን በማፍሰስ ወደ እግዚአብሔር \" የአባቶቻችን አምላክ የምህረት ጌታ ሁሉን በቃልህ የፈጠርክ ሰውንም በረቂቅ ጥበብህ የፈጠርክ አቤቱ አንተ ከልዑል ጌትነትህ ጥበብን ስጠኝ በእውነትም አትናቀኝ እኔ ባሪያህ ነኝ የባሪያህም ልጅ ነኝና \" በማለት ለመኑ ። ከዚህም በኋላ የዓለም ንግሥት የአምላክ እናት ተገለጸችላቸው ። በነሐሴ ፳፩ ቀንም ወደርሳቸው መጣች ፣ በዕውቀትና በትምህርት የሚተጉበትን ኃይል ሰጠቻቸው ። ከዚያም የዜማ የቅኔና የመጽሐፍትን ትርጉዋሜ ትምህርታቸውን በሚገባ አጠናቀቁ ብዙ መጽሐፍትንም ደረሱ ። በዚህም በቀሰሙት ዕውቀታቸው በዜማ በኩል ከቅዱስ ያሬድ ቀጥለው የሚጠሩ አባ ጊዮርጊስ ናቸው። በቤተመቅደስም ዘማሪ ማኅሌታይ ተብለው ይጠራሉ። በዚያም ዘመን ለነገሥት ፣ ለካህናት ፣ ለመኳንንት ፣ ለንቡራነእድ ፣ ለመሳፍንት ፣ ለሁሉም የቤተመንግሥት ሠራተኞች አስተማሪ ሆኑ ። በአንድ ወቅት ግብፃዊው ጳጳስ አቡነ በርተሎሜዎስ “ሥላሴን አንድ ገጽ” ብለው ያምናሉ ተብለው በተከሰሱ ጊዜነገሩን እንዲያጣሩ ከተመረጡት ከቄስ ሐፄ ተከሥተ ብርሃንና ከሐይቁ መምህር ከዐቃቤ ሰዓት ዮሴፍ ጋር አብሮ ተልኮ ነበር፡፡ እነዚህ ሦስት አበውጳጳሱን ካነጋገሩ በኋላ ክሱ ውሸት መሆኑን በማረጋገጥ ስለ ምሥጢረ ሥላሴ የሚገልጠውን የጳጳሱን እምነት በጽሑፍ ይዘው መጡ፡፡ ሊቅነታቸውን የተረዱት ዓፄ ዳዊት አባ ጊዮርጊስን ወደ ቤተመንግሥታቸው በማስገባት የስምንቱም ልጆቻቸው መምህር አድርገዋቸው ነበር ። ከእነርሱም ውስጥ ቅዱስ የተባለው ንጉሥ ቴዎድሮስ እንዲሁም በተለያዩ ጊዜ የነገሡት ንጉሥ እንድርያስ ፣ ዓፄ ይስሐቅ ፣ ንግሥት እሌኒ እና ዓፄ ዘርአ ያዕቆብ ይገኙበታል። ዐፄ ዳዊት በጋብቻ እንዲዛመዱዋቸው ጥረው ነበር ነገር ግን አባ ጊዮርጊስ ራሳቸውን የመንግሥተ ሰማያት ጃንደረባ ማድረግን ስለመረጡ በማስተማሩና በብሕትናው ጸንተው የአመክሮ ጊዜያቸውን ሲጨርሱ አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ገብተው መንኩሰዋል። \n \nጥያቄ: አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጭ በየት ተማሩ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በደብረ ሐይቅ ባሕር ወደምትገኘው የቅዱስ እስጢፋኖስ አባ እየሱስ ሞዐ ገዳምና ታዋቂ ትምህርት ቤት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበደቡብ ሱዳን መከላከያ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጀኔራል ጆንሰን ጁማ ኡኮት የተመራ ልዑክ አዲስ አበባ ገብቷል፡፡ ልዑኩ አዲስ አበባ ሲገባ በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጀኔራል ብርሀኑ ጁላ እና በሌሎች ከፍተኛ የመከላከያ አዛዦች አቀባበል ተደርጎለታል፡፡ በቆይታቸውም በሁለቱ ሀገራት የመከላከያ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚመክሩ ከመከላከያ ሰራዊት ገጽ የተገኘው መረጃ አመላክቷል፡፡ \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ማናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ጀኔራል ብርሀኑ ጁላ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nነሐሴ ፳፰ ነሐሴ ፳፰ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፰ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፰ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፯ ዕለታት ይቀራሉ። 1862 - የፕሩሲያ (ጀርመን) ሠራዊት 3ኛ ናፖሊዎንን ከ100,000 ጭፍሮች ጋር በሰዳን ውግያ አሸነፈ። 1890 - በኦምዱርማን ውግያ ሱዳንን የእንግሊዝ ሠራዊት ድል በማድረግ ቅኝ አገር አደረጉት። 1935 - በ2ኛ አለማዊ ጦርነት ኢጣልያ በጓደኞቿ ሃያላት (በጀርመን ኃይል) ተወረረች። 1946 - የቻይና ኃያላት የደቡብ ኮርያ ደሴቶችን በቦምብ ደበደቡ። ፲፱፻፸፱ ዓ/ም በቡሩንዲ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ሻለቃ ፒዬር ቡዮያ የአገሪቱን ፕሬዚደንት ዣን ባፕቲስት ባጋዛን ከሥልጣን አስወረዱ። \n \nጥያቄ: በ1890 በተደረገው የኦምዱርማን ውግያ የእንግሊዝ ሠራዊት ድል ያደረገው ማንን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሱዳንን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nናሚቢያ ናሚቢያ በደቡብ-ምዕራብ አፍሪቃ የምትገኝ ሀገር ናት። በምዕራብ በአትላንቲክ ውቅያኖስ፣ በስሜን በአንጎላና በዛምቢያ፣ በምስራቅ በቦትስዋና፣ በደቡብም በደቡብ አፍሪቃ ትካለላለች። በ1982 አመተ ምኅረት ነጻነትዋን ከደቡብ አፍሪቃ ስላገኘች በጣም አዲስ አገር ነች። ዋና ከተማዋ ዊንድሁክ ነው። የናሚቢያ በረኅ አውራጃ ከጥንት ጀምሮ በሳን (ቡሽማን)፣ በዳማራና በናማቋ ሕዝቦች ተሰፈረ። በ14ኛው መቶ ዘመን፣ የባንቱ ወገኖች ባስፋፉ ጊዜ አገሩን ሠፈሩ። ክልሉ ግን ከ19ኛው መቶ ዘመን በፊት በአውሮጳውያን አልተዘለቀም። በዚያን ጊዜ ጀርመን ደቡብ-ምዕራብ አፍሪቃ ተብላ አገሪቱ የጀርመን ቅኝ ግዛት ሆነች። ዳሩ ግን ዋልቪስ በይ የተባለው ትንሽ ወደብ ብቻ የእንግሊዝ ግዛት ነበር። \n \nጥያቄ: ናሚቢያ ዋና ከተማዋ ማነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ዊንድሁክ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nግንቦት ፳፮ ቀን፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፷፮ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት ፷፩ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፺፱ ቀናት ይቀራሉ። ፲፱፻፶፬ ዓ/ም - የኤር ፍራንስ ቦይንግ ፯፻፯ አየር ዠበብ ከፓሪስ ኦርሊ ማረፊያ ተነስቶ ወደ አትላንታ ለመብረር ሲነሳ በደረሰበት አደጋ ፻፴ መንገደኞችና የዓየር መንገዱ ባልደረቦች ሞተዋል። ፲፱፻፶፭ ዓ/ም - የአሜሪካው ‘ኖርዝ ዌስት ኤየርላይንስ’ ዲ-ሲ-፯ አየር ዠበብ በረራ በሰላማዊ ውቅያኖስ ላይ ውድቆ ሲሰምጥ ፻፩ ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኮንኮርድ አየር ዠበብ አምሳል የተሠራው የሶቪዬት ቱፖሌቭ ቲ-ዩ-፻፵፬ ፈረንሳይ ላይ በደረሰበት የበረራ አደጋ ሲከሰከስ ፲፬ ሰዎች ሞተዋል። ፲፱፻፺፰ ዓ/ም - የቀድሞዋ ዩጎዝላቪያ አካላት የነበሩት ሰርቢያ እና ሞንቴኔግሮ የውሕደት ስምምነታቸውን በሞንቴኔግሮ የሉዐላዊነት አዋጅ ምክንያት ሰረዙ። ፲፯፻፷፭ ዓ/ም - የዓፄ በካፋ ሚስት የነበሩት እቴጌ ምንትዋብ በዚህ ዕለት አርፈው በቁስቋም ደብረ ጸሐይ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። \n \nጥያቄ: በሰላማዊ ውቅያኖስ ላይ የወደቀው የአሜሪካው ‘ኖርዝ ዌስት ኤየርላይንስ’ አውሮፕላን ስሙ ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ዲ-ሲ-፯ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአዲስ አበባ መስከረም 23/2012 ዕውቁና አንጋፋው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ በውጭ አገራት የሚሰሩ ኢትዮጵያዊያን ሳይንቲስቶች ወጣቶችን በሳይንስ በማነጽ ተግባር እንዲሰማሩ፤ መንግስትም ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጥሪ አቀረቡ። ፕሮፌሰር ጥላሁን በቻይና ከሚገኙ የምርምር ተቋማት ጋር በመተባበር ኢትዮጵያ ውስጥ የአፍሪካ ሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል ሊያቋቁሙ መሆኑን ይፋ አድርገዋል። የአሜሪካው ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ትምህርት ቤት ዕውቁ ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ በሚዘጋጀው ወርኃዊ የሳይንስ ገለጻ መድረክ ወጣቱን ትውልድ ማስተማርና ማነጽ ለኢትዮጵያ ተስፋ፤ የቻይና ተምሳሌትነት በሚል ትናንት ምሽት ገለጻ አድርገዋል። በአውሮጳዊያኑ ዘመን አቆጣጠር 1943 በኢትዮጵያ የተወለዱት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በናዝሬት፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጅማ የግብርና ቴክኒካል ትምህርት ቤቶች አጠናቀው በቀድሞው የአለማያ እርሻ ኮሌጅ ለሁለት ዓመት ተከታትለዋል። ከዛሬ 55 ዓመታት በፊት በኮሌጅ ቆይታቸው ባሳዩት የላቀ ውጤትም አሜሪካን አገር በሚገኘው የካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምና ትምህር ቤት ተልከው ትምህርታቸውን በማጥናት ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው በቢሾፍቱ የእንስሳት ህክምና ትምህርት ቤት አስተምረዋል። ከሁለት ዓመታት በኋላም ወደ ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ በመመለስ የ3ኛ ዲግሪያቸውን በደቂቀ ሥነ ሕይወት መስክ በማጥናት በአውሮጳዊያኑ አቆጣጠር ከ1980-2006 በተማሩበት ካሊፎርኒያ በዋሽንግተን ስቴት ዩኒቨርሲቲ ከረዳት እስከ ሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አስተምረዋል፤ ተመራምረዋል። እ.አ.አ ከ2017 ጀምሮ ደግሞ የዲስቲንጉሽድ ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ማዕረግ ያገኙ ሲሆን እ.አ.አ ከ1990 ጀምሮ እስካሁን ድረስ ዓለም አቀፍ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል በማቋቋም በዳይሬክተርነት እየመሩ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ በየት ሀገር ተወለዱ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በኢትዮጵያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሊቢያ ኦይል ከኢትዮጵያ የተሰናበተውን ሼል ኢትዮጵያ ሊሚትድ በመግዛት የኢትዮጵያን የነዳጅ ገበያ የተቀላቀለው በ2000 ዓ.ም. ነበር፡፡ ኩባንያው ኢትዮጵያ ውስጥ 143 የነዳጅ ማደያዎች ሲኖሩት፣ 24 በመቶ የገበያ ድርሻ አለው፡፡ ኩባንያው በየዓመቱ ዘጠኝ ማደያዎች በመክፈት እ.ኤ.አ. በ2020 የነዳጅ ማደያዎቹን ቁጥር 185 ለማድረስ፣ የገበያ ድርሻውን ወደ 30 በመቶ ለማሳደግ አቅዷል፡፡ በአሁኑ ወቅት የኩባንያው ዓመታዊ ሽያጭ 13 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተገልጿል፡፡ ሊቢያ ኦይል 50 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ የአቪዬሽን ነዳጅ ዲፖ ማስፋፊያና በአዲስ አበባ ጎተራ አካባቢ በሚገኘው የነዳጅ ዲፖ የኤታኖል ማደባለቂያ ገንብቷል፡፡ ኩባንያው እስከዛሬ እንደ አዲስ የገነባቸው ስምንት የነዳጅ ኩባንያዎችን ብቻ ነው፡፡ ይህ ሊሆን የቻለው ለግንባታ የሚሆን ቦታ የማግኘት ችግር በመኖሩ መሆኑን የሚናገሩት አቶ ዘካሪያስ፣ ከሼል ኩባንያ ግዢ ጋር የተፈጠረው የታክስ ክርክር የኩባንያውን ዕድገት እንደጎተተው ያስረዳሉ፡፡ የታክስ ክርክሩ እልባት ያገኘ በመሆኑ ኩባንያው በኢትዮጵያ ያለውን ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት ቆርጦ መነሳቱን አስታውቋል፡፡ ሊቢያ ኦይል ባለፈው ሐሙስ ነሐሴ 28 ቀን 2007 ዓ.ም. በሸራተን አዲስ አዳዲስ የሞተር ዘይትና ቅባቶችን አስተዋውቋል፡፡ የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ የሊቢያ ኦይል የነዳጅ ማደያ ባለቤቶች፣ የሊቢያ ኦይል ምርቶች አከፋፋዮችና የትራንስፖርት ኩባንያዎች የሊቢያ ኦይል ዋና ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ሙስባሕ ኤልቤሽቲ ሽልማቶች አበርክተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: በእቅዱ መሰረት ሊቢያ ኦይል በ2020 ኢትዮጵያ ውስጥ ስንት ማደያዎች ይኖሩታል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 185 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በቆዳ ስፋቷ ሁለተኛ የሆነችው ሀገር ማናት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ማሊ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሊንጋላ ሊንጋላ (Lingala) ከባንቱ ቋንቋዎች ቤተሠብ አንድ ነው። የሚናገርበት በተለይ በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ ስሜን-ምዕራብ ክፍል፣ በኮንጎ ሪፑብሊክም፣ እንዲሁም በአንጎላና በመካከለኛው አፍሪካ ሪፑብሊክ ነው። ተናጋሪዎቹ 10 ሚልዮን ናቸው። የሊንጋላ መነሻ ቦባንጊ በተባለ ቋንቋ ነበር። ከኮንጎ ነጻ መንግሥት አስቀድሞ ቦባንጊ የአከባቢው መደበኛ ቋንቋ ይሆን ነበር። የቤልጅክ ንጉስ አገሩን ከያዙ በኋላ የቀኝ አገሩ መንግሥት ለማስተዳደርና ለመሰበክ ቋንቋውን ጠቃሚ ሆኖ አገኙት። ካለፈው ቦባንጊ እንዲለይ የአዲሱን ቋንቋ ስም ባንጋላ ብለው ጠሩት። ሚስዮናዊዎቹ ወዲያ (1900 አ.ም.) ባንጋላን ዳግመኛ ሲያሻሽሉ \"ሊንጋላ\" እንዲህ ተፈጠረ። ሊንጋላ ከፈረንሳይኛ ብዙ ቃሎች ተበድሮ ደግሞ ከፖርቱጊዝ ተጽእኖ አለ (ለምሳሌ \"ማንቴካ\" = ቅቤ፤ \"ሜሳ\" = ጠረጴዛ፤ \"ሳፓቱ\" = ጫማ) ከእንግሊዝኛም ተጽእኖ አለ (\"ሚሊኪ\" = ወተት፤ \"ቡኩ\" = መጽሐፍ)። \n \nጥያቄ: ሊንጋላ ቋንቋ ከየትኘው ቋንቋ ቤተሰብ ይመደባል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከባንቱ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nተክለጻድቅ መኩርያ ተክለጻድቅ መኩርያ በ፲፱፻፮ ዓ.ም. በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ አሳግርት ልዩ ስሙ ሳር አምባ በተባለ ሥፍራ ተወለዱ። ዕድሜያቸው ለትምሕርት ሲደርስ መጀመሪያ ከአባታቸውና ቀጥሎም በአጥቢያቸው ባህላዊውን ትምሕርት እስከቅኔ ያለውን ቀስመዋል። ከዚያም አዲስ አበባ መጥተው አሊያንስ ፍራንሴዝና ተፈሪ መኮንን ትምሕርት ቤት ገብተው የጊዜውን የትምሕርት ደረጃ አጠናቀዋል። ኢጣልያ አገራችንን የወረረች ጊዜም በየካቲት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ.ም. ፍጅት ተይዘው ወደ ሶማሌ ደናኔ ተግዘው ለሦስት ዓመታት ታስረዋል። ከነጻነትም መልስ አገራቸውን በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች አገልግለዋል። መጀመሪያ ተቀጥረው ያገለገሉት በትምሕርትና ሥነጥበብ ሚኒስቴር ነበር። እዚያም ሳሉ በአገራችን ሰው የተጻፈ የአገራችን ታሪክ አንድም ባለመኖሩ በቁጭትና በመቆርቆር ነበር ‘መጻፍ አለብኝ’ ብለው በደንብ ከሚታወቀው ከቅርቡ ጊዜ በቅጡ ወደማይታወቀው የሩቁ ዘመን መጻፍ የጀመሩት። የመጀመሪያውን መጽሐፍ “የኢትዮጵያ ታሪክ ከዓፄ ቴዎድሮስ እስከ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ” የሚለውን በ ፲፱፻፴፰ ዓ.ም. አሳተሙ። ከጫፍ እስከ ጫፍ ጽፈው የመጨረቻውን መጽሐፍ፣ የታሪካችን መጀመሪያ የሚሆነውን “የኢትዮጵያ ታሪክ ኑብያ-አክሱም-ዛጉዬ እስከ ዓፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት” የሚለውን በ፲፱፻፶፩ ዓ.ም. አቅርበዋል። እኒህኑ መጻሕፍት ትምሕርት ሚኒስቴር ታሪክ ለማስተማሪያ በትምሕርት ቤት ተጠቅሞባቸዋል። ተክለጻድቅ ከታሪክ ውጭ የጻፏቸው “የሰው ጠባይና አብሮ የመኖር ዘዴ” እና በሚዮቶሎዢያ (አፈ ታሪክ) ላይ ያተኮረ “ከጣዖት አምልኮ እስከ ክርስትና” የሚሉም መጽሐፎች አሏቸው። ተክለጻድቅ በምድር ባቡር በዋና ጸሐፊነት፥ በቤተ መጻሕፍት ወመዘክር ዋና ሥራ አስኪያጅነት፥ እንዲሁም በፈረንሳይ፥ በእስራኤል፥ በዩጎዝላቪያ በዲፕሎማሲ ሥራ በመጨረሻም የትምሕርትና የባህል ሚኒስቴር ሆነው አግልግለዋል። በፈቃዳቸው ጡረታም ከወጡ በኋላ በምርምር የታገዙ ሦስት ታላላቅ የታሪክ ሥራዎችን አቅርበዋል። ተክለጻድቅ ከረጅም የአገልግሎት ዘመን በኋላ በተወለዱ በ ሰማንያ ስድስት ዓመታቸው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፱፻፺፪ ዓ.ም. አርፈዋል። \n \nጥያቄ: ተክለጻድቅ መኩርያ የመጀመሪያውን መጽሐፋቸውን መቼ አሳተሙ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ ፲፱፻፴፰ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሩሲያ ለአለም አቀፍ በይነመረብ አማራጭ የሚሆን አር ዩ ኔት የተሰኘ ኢንተርኔት በተሳካ ሁኔታ መሞከሯን የሀገሪቱ መንግስት አስታውቋል ፡፡ ይሁን እንጂ የተከናወነውን ሙከራ በተመለከተ ዝርዝር መረጃ አለመሰጠቱ በዘገባው ተመላክቷል። እንደ ሀገሪቱ ኮሙኒኬሽን ሚኒስቴር መረጃ ፥ማንኛውም ተጠቃሚ በተደረገው ሙከራ ወቅት ምንም አይነት ለውጥ ማስተዋል አለመቻሉን አስታውቋል፡፡ የሙከራ ውጤቱም ለሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ይቀርባል ነው የተባለው ፡፡ ምሁራኖችበ አንዳንድ ሀገሮች በበይነ መረብ የሚደርስ ጥፋትን እንዳለ ይጠቅሳሉ። በጥናቱ ዩኒቨርሲቲ የኮምፒተር ሳይንቲስት የሆኑት ፕሮፌሰር አላን ውድዋርድ እንዳሉት፥ በሚያሳዝን ሁኔታ የበይነመረብ ሰርጎ ገቦች መበራከት የሩሲያ የጉዞ አቅጣጫ ሌላ ደረጃ እያደረሰ ነው። ቁጥራቸው እየጨመረ ያሉ ሃያላን መንግስታት ዜጎች የሚያዩትን መቆጣጠር የሚፈልጉ ስለመሆናቸው ከኢራን እና ከቻይና መመልከት ይቻላል። ይህ ማለት ሰዎች ሀገራቸው ውስጥ ስለሚሆነው ነገር የመነጋገር እድል አይኖራቸውም፡፡ የተገኘው ውጤት እንደሚያሳየው ባለስልጣኖች እና የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ውጤታማ ምላሽ በመስጠት አደጋዎች እና ስጋቶችን ማስወገድ እንዲሁም በሁለቱም በይነመረብ እና ቴሌኮሙዩኒኬሽን አውታር መረብ ውስጥ የተስተካከለ አሠራር በሩሲያ ፌዴሬሽን እንዲኖር ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸው ተነግሯል። \n \nጥያቄ: አር ዩ ኔት የተሰኘ ዓለም አቀፍ የበይነ መረብ አማራጭ በኢንተርኔት በተሳካ ሁኔታ የሞከረችው ሀገር ማናት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሩሲያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nታኅሣሥ ፳፫ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፻፲፫ተኛው እና የመፀው ወቅት ፹፰ተኛው ቀን ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየወሩ ፳፫ኛ ቀን የሰማዕታትን ዓለቃ ቅዱስ ጊዮርጊስንን ታስታውሳለች። ፲፯፻፷፰ ዓ/ም - የእንግሊዝ ሠራዊት የክዌቤክ ከተማን ከአሜሪካ አስመለሰ። ፲፯፻፺፮ ዓ/ም - በሀይቲ ደሴት የፈረንሳይ ሉዐላዊነት ሲያከትም ደሴቷ በሰሜን አሜሪካ አኅጉር ከአሜሪካ ኅብረት ተከትላ ሁለተኛዋ ነፃ ሪፑብሊክ ሆነች። ፲፰፻ ዓ/ም - በባርነት የተገዙ ሰዎች ወደ አሜሪካ ኅብረት እንዳይገቡ የሚከለክል ሕግ ተደነገገ። ፲፱፻፲፯ ዓ/ም - ብርሃንና ሰላም ጋዜጣ ተመሰረተ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የ፩ሚሊዮን ፱መቶ ሺ ኪሎ የመዳብ ሽያጭ ወደጃፓን ላከች። መዳቡ በኤርትራ ውስጥ ከሚገኘው የድባሮ መዳብ ማዕድን ቁፋሮ የተገኘ ነው። ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ የጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት ባንኮችንና የኢንሹራንስ ኩባንያዎችን የብሔራዊ ንብረት አድርጎ ወረሰ። ፲፱፻፹፱ ዓ/ም - ጋናዊው ዲፕሎማት ኮፊ አናን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ፯ተኛው ዋና ጸሐፊ ሆነው ተሾሙ። \n \nጥያቄ: ብርሃንና ሰላም ጋዜጣ የተመሰረተው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ፲፱፻፲፯ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nላሊበላ ላሊበላ በኢትዮጵያ፣ በአማራ ክልል በቀድሞው የወሎ ክፍለ ሃገር የምትገኝ ከተማ ነች። በ ላይ የምትገኘው የላሊበላ ከተማ ከባህር ጠለል በላይ 2,500 ሜትር ከፍታ ያላት ስትሆን የህዝቡም ብዛት ወደ 11,152 ነው። 1 ላሊበላ ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት ቅዱሳን ከተማዎች መካከል ከአክሱም ቀጥላ በሁለተኛነት ደረጃ የምትገኝ ከተማ ስትሆን፣ ለአብዛኞቹ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንደ ዋና የእምነት ማእከል በመሆን ታገለግላለች። የላሊበላ ነዋሪዎች በአብዛኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች ናቸው። የላሊበላን ከተማ በዋነኛነት ታዋቂ ያረጉዋት ከክ.ል. በኋላ በ13ኛው መቶ ክፍለዘመን እንደ ተሰሩ የሚነገርላቸው 11 አብያተ-ክርስቲያናት ናቸው። በኢትዮጵያ ትውፊት መሰረት እነዚህ አብያተ-ክርስቲያናት በንጉሥ ላሊበላ ዘመን በቅዱሳን መላዕክት እረዳትነት እንደተሰሩ የሚታመን ሲሆን ግርሃም ሃንኮክ የተባለው እንግሊዛዊ ፀሃፊ ግን እኤአ በ1993 ዓ.ም ባሳተመውና The Sign and the Seal በተባለው መጽሃፉ አብያተ-ክርስቲያናቱን በማነፁ ሥራ ላይ ቴምፕላርስ የሚባሉት የመስቀል ጦረኞች ተካፍለዋል ሲል አትቷል ነገር ግን ማረጋገጫ አልነበረውም። እነዚሀ አብያተ-ክርስቲያናት ውስጥ አርባ ትንንሽ ቤተክርስቲያኖች አሉ። \n \nጥያቄ: ላሊበላ በኢትዮጵያ በየትኛው ክልል ይገኛል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በአማራ ክልል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nፍሪዩልያን ፍሪዩልያን (Furlan) በስሜን-ምሥራቅ እጣልያ በ600,000 ሰዎች የሚናገር ቋንቋ ነው። ከነዚህ ተናጋሪውዎች አብዛኞቹ ደግሞ ጣልኛ የሚችሉ ናቸው። የቋንቋ ስም በጣልኛ ፍሪዩልያኖ ሲሆን በራሱ ግን ፉርላን ወይም ማሪለንጌ ይባላል። ላዲን ለሚባለው ቋንቋ ቅርብ ዝምድና ስላለው አንዳንዴ \"ምስራቅ ላዲን\" ይሰየማል። ከዚያ በላይ በስዊስ አገር ለሚናገረው ለሮማንሽ ቅርብ ዘመድ ነው። ዛሬ በጣልያ መንግሥት በኩል ፍሪዩልያን ይፋዊ ሁኔታ አለውና በብዙ ትምህርት ቤቶች ይማራል። ጥቂት ሥነ ጽሑፍ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም፣ ዘፈኖችና አንዳንድ የመንገድ ምልክት፣ ደግሞ የድረ-ገጽ ጋዜጣ በፍሪዩልያን አለ። ባለፈው አመት ውስጥ የቢራ ማስታወቂያ ቢሆንም በፍሪዩልያን በጣልያ ቴሌቪዥን ታይቷል። ስለዚህ ዱሮ ቋንቋው በጣም ትንሽ ከሆነ አሁን ግን በጉልበት እየተመለሠ ነው። \n \nጥያቄ: ፍሪዩልያን ቋንቋ በጣልያን የት አካባቢ ይነገራል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በስሜን-ምሥራቅ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሮማንሽ ሮማንሽ ወይም ሩማንች (Rumantsch) ከስዊስ አገር 4 ብሔራዊ ቋንቋዎች 1ዱ ሆኖ ሌሎቹ 3 ጀርመንኛ ጣልኛና ፈረንሳይኛ ናቸው። ከሮማይስጥ የታደገ ቋንቋ በመሆኑ የሮማንስ ቋንቋ ቤተሠብ አባል ነውና በተለይ የሚመስለው ፈረንሳይኛ ወይም እጣልኛ ነው። የሚናገረው በግራውብውንደን (ግሪዞን) ካንቶን ስዊስ በሚኖሩ 60,000 ሰዎች ነው። ይህ ከስዊስ አገር ሕዝብ ብዛት 1% ብቻ ሲሆን ከስዊስ አገር ብሔራዊ ቋንቋዎች ሁሉ ትንሹ ነው። እንኳን በስዊስ አገር ከሚኖሩት ስርቦ-ክሮዌሽኛ ተናጋሪዎች ቁጥር ብዛት (111,000) በግማሽ ያንሳል። በስሜን እጣልያ አገር ዛሬ ለሚናገሩ ቋንቋዎች ለፍሪዩልያንና ለላዲን ቅርብ ዘመድ ነው። \n \nጥያቄ: በስዊስ ሀገር የሮማንሽ ቋንቋ ተናጋሪዎች በመቶኛ ምን ያህል ይሆናሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 1% ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ለወጣት ለአዛውንት የሚመቹ ደግ እናት፡፡ በኢትዮጵያ የሚድያ ታሪክ ስም ያተረፉ፡፡ ለምርምር የማይደክሙ፡፡ ተወዳጅ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን እነሆ ታሪካቸውን አቀረበ፡፡ ጋዜጠኛዋ በ79 አመታቸው ሀምሌ 14 2013 ህይወታቸው አልፏል፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ በ1934 አመተ ምህረት ከአባታቸው ከአቶ መኩሪያ ወልደስላሴ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ሶስና ወርቅነህ ተወለዱ፡፡ እናታቸው ወይዘሮ ሶስና ወርቅነህ የሀኪም ወርቅነህ እሸቴ ልጅ ናቸው፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ የአንደኛ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በሳንፎርድ ተማሪ ቤት ነበር የተከታተሉት፡፡ ወይዘሮ እሌኒ ያደጉት ካዛንቺስ አካባቢ ሲሆን የልጅነት ዘመናቸው በደስታ የተሞላ ነበር፡፡ በተለይ በሳንፎርድ ተማሪ ቤት ጥሩ የእንግሊዝኛ ችሎታቸውን ከማዳበራቸው በላይ ደስ የሚል የመዝናኛ ጊዜን አሳለፈው ነበር፡፡ ቴኒስ መጫወት ፤ ዋና መዋኘት ፣ ቴአትር ማየት እና መተወን ደስ ይላቸው ነበር፡፡ እንዲያውም ለልኡል መኮንን ሆስፒታል ማሰሪያ የገቢ ማሰባሰቢያ ላይ ቴአትር መስራታቸውን ወይዘሮ እሌኒ በህይወት በነበሩ ጊዜ ተናግረዋል፡፡ በተለይ አያታቸው ክቡር ሀኪም ወርቅነህ እሸቴ ዳንስ ያለማምዷቸው እንደነበር አይዘነጉትም፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ፣ ማህበራዊ ሳይንስ የማጥናት ግብ ቢኖራቸውም ቤሩት የነጻ የትምህርት እድል አግኝተው ወደዚያ በ1951 ግድም ያቀናሉ፡፡ ነገር ግን የነርስነትን ትምህርት ቢጀምሩም አቋርጠው ወደ እናት ሀገራቸው ይመለሳሉ፡፡ በመቀጠልም ወደ ብስራተ ወንጌል ሬድዮ በማቅናት በእንግሊዝኛው ክፍል ተቀጠሩ፡፡ ያኔ በሬድዮ ከወይዘሮ እሌኒ ጋር ይሰሩ ከነበሩት ባለሙያዎች መካከልም ጋዜጠኛ ልኡልሰገድ ኩምሳ ይጠቀሳል፡፡ ወይዘሮ እሌኒና ጋዜጠኛ ልኡልሰገድ ዜና ሲያቀርቡ ያለበት ቪድዮ ከዚህ ጽሁፍ አዘጋጅ ዘንድ ይገኛል፡፡ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ቻርተር በግንቦት 18 1955 ሲፈረም ጋዜጠኛ ከነበሩት መካከል ወይዘሮ እሌኒ ይጠቀሳሉ፡፡ በወቅቱ ገና የ21 አመት ወጣት የነበሩት ወይዘሮ እሌኒ መሪዎች ሲመጡ የተደረገውን ታሪካዊ አቀባበል በፍጹም አይዘነጉትም፡፡ \n \nጥያቄ: የወ/ሮ እሌኒ አያት ማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ክቡር ሀኪም ወርቅነህ እሸቴ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቴሌቪዥን ቴሌቪዥን የስዕል እና ድምጽ ምልክቶችን ከማሰራጫ የሚቀበል የመገናኛ ዘዴ ነው። «ቴሌ-» የሚለው ክፍል በግሪክ «ሩቅ» ማለት ቢሆን «-ቪዥን» ደግሞ ከሮማይስጥ visio /ዊዚዮ/ «ማየት» («ትርዒት») ተወስዷል። በአጠቃላይ ቴሌቪዥን ማለት ተንቀሳቃሽ ምስልን (ብዙ ጊዜ ከድምፅ ጋር) ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለማስተላለፍ የሚረዳ የመልዕክት ማስራጫ መንገድ ነው። ይህ ከሆነ ዘንዳ ቴሌቪዥን ምስል መቅጃውንም ሆነ ምስል መቀበያውን መሳሪያ ሁሉ ያጠቃልላል ግን በተለምዶ ቴሌቪዥን የምንለው ምስል መቀበያውን ብቻ ነው። በ1873 እ.ኤ.አ. (1865 ዓም) የእንግላንድ ኤንጅኔር ውሎቢ ስሚስ ባደረገው ጥረት ጥንተ ንጥሩ ሴሌኒይም ብርሃን-አስተላልፎሽ መሆኑን ገለጸ። በ1884 እ.ኤ.አ. ፓውል ጎትሊብ ኒፕኮው የተባለ ጀርመናዊ ክብ የሆነ ዲስክን በስፓይራል በምብሳት ይህ ዲስክ በተሽከረከረ ቁጥር ከፊትለፊቱ የሚመጣውን ብርሃን በቀዳዶቹ በማሾለክ ከሴሌኒይም በተሰራ የካሜራ ግድግዳ ላይ እንዲያርፍ አደረገ። ግድግዳው ብርሃን ሲነካው ያንን ብርሃን ወደ ኮሬንቲ ሃይል በመቀየር ምስልን በኮሬንቲ መልክ በሽቦ ለመላክ ቻለ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ አምፕሊፋየር ስላልነበር የሚላከው ምስል እምብዛም አመርቂ አልነበረም። ከ27 አመታት በኋላ በ1911 እ.ኤ.አ. የራሻው ቦሪስ ሮዚንግ ለመጀመሪያ ጊዜ የሲርቲን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፣ አሁንም ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል ቻለ። ነገር ግን የሚንቀሳቀሱት ምስሎች የጂዎሜትሪ ቅርጽ ነበራቸው ማለትም ሶስት ማዕዘን፣ አራት ማእዘን ወዘተ... ከ7 አመታት በኋላ በ1925 እ.ኤ.አ. ጆን ሎጂ ቤርድ የተሰኘው የስኮትላንድ ተመራማሪ 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለመላክ ቻለ ከዚያም በ1926 እ.ኤ.አ. ጥቁርና ነጭ የሆኑ ምስሎችን ለማስተላለፍ በቃ። በዚህ ጊዜ የሚላኩት ምስል ጥራት 30 መስመር በአንድ ጊዜ ነበር፣ በዚህም ምክንያት የሰውን ፊት ለመለየት አስቸጋሪ ቢሆንም ግን ይቻል ነበር። አቶ ቤርድ በ 1918 ዓ.ም. (26 January 1926 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የቴሌቪዥን መግለጫ ሰጠ። በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ የተሰኘው የቤል ላብራቷር ተቀጣሪ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ መላክ ቻለ። ቀጠል አድርጎም በራዲዮ ወደ ዊፓኒ ኒው ጀርሲ ለመላክ በቃ። በዚያው አመት ፊሎ ፍራንስዎርዝ የመጀመሪያውን የተሟላና በኤሌክትሪክ ስካኒንግ ብቻ የሚስራውን የቴሌቭዥን ስርዓት በተግባር አዋለ።.በጥር 1928 እ.ኤ.አ. (1920 ዓም) መጀመርያው የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያ በስከነክተዲ፣ ኒው ዮርክ ተከፈተ፤ እስከ ዛሬም ድረስ ያሰራጫል። \n \nጥያቄ: በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ በሽቦ የላከው ከየት ወደ የት ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየጥምቀት በዓል በክርስትና ኃይማኖት ተከታዮች በተለይም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ ኢየሱስ ክርስቶስ በ፴ ዓ/ም በፈለገ ዮርዳኖስ በመጥምቁ ዮሐንስ እጅ በዮርዳኖስ ባሕር የተጠመቀበትን ዕለት የሚያስታውሰው፣ ኤጲፋንያ በመባልም የሚታወቀው ደማቅ በዓል ነው። መገለጥ፣ መታየት ማለት ነው። በአገራችን፣ ጥር ፲ ቀን፣ በከተራ፣ በገጠር ወራጅ ውሃ የሚከተርበት፣ ታቦታት ከየአቢያተ ክርስቲያናቱ በዓሉ ወደሚከበርበት ቦታ በምዕመናን ታጅበው እየዘመሩ ይሄዳሉ። እዚያም በየተዘጋጀው ድንኳን እንዲያርፉ ተደርጎ ሌሊቱን እዛው ያሳልፋሉ።በከተሞች ግን ሰው ሰራሽ ግድብ ይሰራል። ጥር ፲፩ ቀን የጥምቀት ዕለት፤ በገጠር፣ ጎኅ ሲቀድ ምእመናን እዚያው በድንኳኑ ዙሪያ አስቀድሰው ሲጨርሱ በካህናት መሪነት ሁሉም ወደከተራው ያመራና ውሃውም ተባርኮ ሕዝቡ ይረጫል። «ተጠምቀ ሰማያዊ በእደ መሬታዊ፤ ሰማያዊው በመሬታዊው እጅ ተጠመቀ» የሚለው የዕለቱ ቀለም በሊቃውንቱ አንደበት በያሬዳዊ ዜማ ጎልቶ ይሰማል። ከዚህ ሥነ ሥርዓት በኋላ በመቋሚያ፣ በከበሮና በጽናፅል በሚታጀብ ኃይማኖታዊ ዝማሬ፣ ወንዱ በሆታ፤ ሴቱ በእልልታ፤ ካህኑ በሃሌታ ታቦተ ሕጉን አጅበው፣ እንደያመጣጣቸው ወደየ ቤተክርሲያናቸው ይመለሳሉ። በየዓመቱ በመላ ኢትዮጵያ የሚከበረው የጥምቀት በዓል፣ ታቦታት ከመንበራቸው ወጥተው፣ በየጥምቀተ ባሕሩ የሚከበሩ በመኾናቸው፣ ሀገሬውን ብቻ ሳይሆን ዓለም አቀፋዊ መስህብ በመፍጠሩ፣ ቱሪስቶችን መሳቡ አልቀረም። ጥቁርና ነጭ፣ ቀይና ብጫ ያለም ዘር፣ ከአዲስ አበባ እስከ ላሊበላ፣ ከአክሱም እስከ ጎንደር በሁሉም ሥፍራዎች በዚሁ ዓይነት ደምቆ ይከበራል። የምእመናኑም ሆነ የካህናትና ዲያቆናት አለባበስ ፍፁም በሚማርክ ባህላዊ አልባሳት የተዋበ በመሆኑ ከውጭም ሆነ ከአገር ውስጥ ለሚመጡ ጎብኚዎች ሁል ጊዜ አዲስ ነው። ሊቃውንቱ እንደሚናገሩት፣ ዘመነ አስተርእዮ የሚባለው፣ ከጥር ፲፩ ቀን ጀምሮ እስከ ጾመ ነነዌ ያለው ጊዜ ነው። በዚህ ጊዜ ውስጥ አምላክ ሰው ሆኖ በሥጋ መገለጡ፣ በዮርዳኖስ በተጠመቀ ጊዜ የአንድነትና የሦስትነት ምሥጢር መታወቁ፣ በቃና ዘገሊላ በተደረገው ሠርግ ላይ የመጀመሪያው ተዐምር በመፈጸሙ፣ አምላካዊ ኃይሉ መገለጡ፣ እየታሰበ ምስጋና ይቀርባል። ይህ ሁነት ኢትዮጵያ ብሂልን ከባህል ጋር አዛምዳ ከሌላው የክርስቲያን ዓለም በተለየ አከባበር በዓሉን ማክበሯ፣ አያሌ ቱሪስቶችን ለመሳብ አስችሏታል። \n \nጥያቄ: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በስንት ዓመተ ምህረት ተጠመቀ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ፴ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nለሚያንኮራፉ ሰዎች መፍትሄ ይሆናል የተባለው አዲሱ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ይፋ ተደርጓል። ሚሊዮኖች የሚሰቃዩበት ማንኮራፋት ከጤና መቃወስ ጋር በተያያዘ በቂ የሆነ እንቅልፍ ከመከልከሉ በተጨማሪ በአካባቢው የሚገኙትን ሰዎች በመረበሽ ማህበራዊ ኑሯችንን ያውካል፡፡ መንስኤዎቹ የመተንፈሻ አካላት የተፈጥሮ ሁኔታና ህመም ሲሆኑ ከ60 እሰከ 80 በመቶ ከ50 አመት በላይ በሆኑ ወንዶች ላይ አንደሚከሰት ጥናቱ ያመላክታል፡፡ አዲሱ ፈጠራም የመተንፈሻ አካላትን የአተነፋፈስ ስረዓት በማሻሻል እና በማገዝ ማንኮራፋትን የሚያስወግድ ነው ተብሏል፡፡ ቴክኖሎጂው በአፍንጫ የሚቀመጥ ሲሆን ነርቮችን በማነቃቃት የአተነፋፈስ ስርዓትን በማስተካከል አየር በአግባቡ እንዲዘዋወርና ማንኮራፋትን በማስወገድ ጥሩ እንቅልፍ መተኛት ያስችላል ተብሏል፡፡ \n \nጥያቄ: ለሚያንኮራፉ ሰዎች መፍትሄ ይሆናል የተባለው አዲሱ ቴክኖሎጂ በሰውነታችን የትኛው አካል ላይ ይደረጋል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በአፍንጫ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nመንግስቱ ለማ መንግሥቱ ለማ (1924-1988) በጣሊያን ወረራ ዋዜማ በሀረር ሀደሬ ጢቆ መካነ ሥላሴ ተወልዶ ከቆሎ ተማሪነት ተነስቶ የለንደን ስኩል ኦፍ ኢኮኖሚክስ ደቀመዝሙርነት እስከመሆን በቅቶ የቅኔ ቤት ሊቅነት ሳይበቃው የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ቀደምቶች መሃከል ለመደብለቅ የበቃ ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ድንቅ ገጣምያን/ፀሃፌ ተውኔቶች አንዱ ነው። አባቱ አለቃ ለማ ኃይሉ ወልደ-ታሪክ (ታሪክ የእናታቸው ስም ነው - ምናልባት በኢትዮጵያ ታሪክ የእናታቸውን ስም ከስማቸው አስተባብረው በመጻፍ የመጀመሪያው ሳይሆኑ አይቀሩም) ታዋቂ የቤተክርስቲያን ሊቅ የነበሩ ሲሆን በመጀመሪያ ላይ የመንግስቱን የአስኳላ (በወቅቱ ዘመናዊ ትምህርት የሚጠራው እንዲህ ነበር) ትምህርት ባይወዱለትም ጣሊያኖቹ ልጁን የማያስተምር ሰው ሁሉ ይቀጡ ስለነበር ለማስተማር ተገደዋል። ሁዋላ ላይ ግን እሳቸው አዲስ አበባ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ትእዛዝ ተቀይረው መጥተው እሱ የኮተቤ ተማሪ ከሆነና የትምህርት ውጤቱም እስደሳች ሲሆን የቀድሞ ቅዋሜያቸውን ሳያላሉት አልቀሩም። መንግስቱ በእንግሊዝ አገር ወደ ስድስት አመት ቢቆይም ትምህርቱን ሳያጠናቅቅ ነው በ1956 ዓ.ም ወደ አገሩ ለመመለስ የበቃው። ይሁን እና በቆይታው ከብዙ የእንግሊዝ ደራስያን ጋር ለመተዋወቅ በቅቷል። በተለይም ከጆርጅ በርናርድ ሾው ጋር ወዳጆች እንደነበሩ ይነገራል። መንግሥቱ ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በሁዋላ የተሰማራው ወደ መንግስት ሥራ ሲሆን በህንድ አገር ዲፕሎማት ሆኖ ከሄደ በሁዋላ ምናልባትም በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን ዘመናዊ ኮሜድ ተውኔት «ጠልፎ በኪሴ\"ን ደርሷል ከዚያ በሁዋላ የደረሳቸው እነ «ያላቻ ጋብቻ»፣ «ጸረ-ኮሎኒያሊስት»፣ «ባለካባና ባለዳባ» የመንግስቱን ስም በኢትዮጵያ የስነ-ጽሁፍ ታሪክ ውስጥ ቀዳሚ ተጠቃሽ ካደረጉት ስራዎቹ መካከል ናቸው። በተጨማሪም «The bear» የተሰኘውን እና የታዋቂው የሩሲያ ደራሲ አንቷን ቼኾቭ ተውኔት የሆነውን «ዳንዴዎ ጨቡዴ» በሚል የተረጎመ ሲሆን የጄ.ቢ. ፕሪስትሊን «The Inspector Calls»ን ተርጉሞ ለመድረክ አብቅቷል። መንግስቱ ከተውኔቱ በተጨማሪም በስነ-ግጥም የተዋጣለት እንደነበር ስራዎቹ ይመሰክራሉ። «የግጥም ጉባኤ» የተሰኘው ስብስብ መንግስቱ የግጥም መክሊት የተቸረው ደራሲ እንደነበር ይመሰክራል። መንግሥቱ ደራሲም ብቻ አልነበረም፤ በተማሪዎቹ የተወደደ መምህር በሳል ተመራማሪ ለባህሉ እና ለቋንቋው ሙት የነበረ ከኢትዮጵያ ብርቅዬዎች አንዱ ነው። \n \nጥያቄ: መንግስቱ ለማን በኢትዮጵያ የስነ-ጽሁፍ ታሪክ ውስጥ ቀዳሚ ተጠቃሽ ካደረጉት ስራዎቹ የሚጠቀሱት የትኞቹ ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ «ያላቻ ጋብቻ»፣ «ጸረ-ኮሎኒያሊስት»፣ «ባለካባና ባለዳባ» ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nክልሉ የትልልቅ ወንዞች ባለቤት ሲሆን በአጠቃላይ በሦስት ዋና ዋና ተፋሰሶች ተከፋፍሎ ሊታይ የሚችል ነው። እነርሱም የዓባይ፣ የተከዜ እና የአዋሽ ተፋሰስ ናቸው። ወደነዚህ ተፋሰሶች የሚገቡና ዓመቱን በሙሉ የማይደርቁ ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ ትልልቅ ወንዞች ያሉ ሲሆን በክልሉ በጥቅም ላይ ያልዋለ ሰፊ የውሐ ሀብት መኖሩን ያመለክታሉ። ከነዚህ በተጨማሪ እንደ ጣናና አርዲቦ የመሳሰሉ ሐይቆችም በክልሉ ውስጥ ይገኛሉ። በአጠቃላይ በክልሉ ውስጥ ባሉ ትልልቅ ወንዞችና መጋቢ ወንዞች የመስኖ ልማት ለማካሄድ የሚያስችል ከፍተኛ የውሐ ሐብት ክምችት እንዳለ መገንዘብ ይቻላል። ይሁን እንጅ እስከ አሁን ጥቅም ላይ የዋለው በጣም አነስተኛ ነው። በአመዛኙ አብዛኛው የክልሉ ምጣኔ ሀብት በግብርና እና ከብት እርባታ ላይ የተመሠረተ ነው። በአጠቃላይ ክልሉ ከፍተኛ የሆነ የሕዝብ ቁጥር፣ ለእርሻና ለእንስሳት እርባታ ተስማሚ የሆነ መሬት፣ የአየር ንብረት እና የውሐ ሀብቶች ያሉት በመሆኑ በተለይም የሰብል እና የእንስሳት ሀብት ልማት ለማካሄድ የማይናቅ አቅም አለው። በዝናብም ሆነ የመስኖ እርሻ ልማት በማስፋፋት በክልሉ በገበያ የሚውሉ የተለያዩ የአገዳ፣ የጥራጥሬ፣ የቅባት፣የአትክልትና ፍራፍሬ ሰብሎችን ማምረት ይቻላል። ጤፍ፣ ገብስ፣በቆሎ፣ ማሽላ፣ዳጉሣ፣ ስንዴ፣አተር፣ ባቄላ፣ ሽምብራ፣ ጓያ፣ምስር፣ሰሊጥ፣ ጥጥ፣ ተልባ፣ ወዘተ የመሳሰሉት በክልሉ ውስጥ ከሚመረቱ ሰብሎች መካከል ዋና ዋናዎቹ ናቸው። በእንስሳት ሀብት ረገድም በወተት ምርታማነታቸው የታወቁ የፎገራ ዝርያዎችና በፀጉር ምርት የታወቁት የመንዝ በግ ዝርያዎች በክልሉ ይገኛሉ። በቱሪዝም የሥራ መስክ ሊበለጽጉ ፣በሰፊው አገልግሎት ሊሰጡ የሚችሉ እና በዓለም የቅርስ መዝገብ የሰፈሩት የጐንደር ቤተ መንስግት ህንፃዎች፣ የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት፣ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ እንዲሁም ልዩ ልዩ የቱሪዝም መስሕቦች አሉት፣ ይሁን እንጅ ክልሉ ሰፊ የሆነ የቱሪዝም እምቅ ሀብት ያለው ቢሆንም በሚፈለገው መጠን በጥቅም ላይ ውሏል ማለት አያስደፍርም። በዚህ ረገድ፤አካባቢዉ የብዙ ታሪካዊ ገዳማትና የታሪካዊ ቅርሶችም ባለሀብት ነው። \n \nጥያቄ: በአማራ ክልል ውስጥ ጥሩ የጸጉር ምርት ያላቸው የየት አካባቢ በጎች ዝርያዎች ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የመንዝ በግ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nማርክ ትዌይን ሳሙኤል ላንግሆርን ክሌመንስ ወይም በብእር ስሙ ማርክ ትዌይን አሜሪካ ካፈራቻቸው ድንቅ ጸሃፍት መካካል የሚመደብ ደራሲ ነው። ትዌይን በኖቬምበር 1835 ዓ.ም. ሚዙሪ በተባለችው የአሜሪካ ግዛት ተወለደ። 18 ዓመት እስኪሞላው ድረስ ከቤተሰቦቹ ጋር የኖረው ሃኒባል በተባለች እና ሚሲሲፒ ላይ በተቆረቆረች ትንሽ ከተማ-አከል ቦታ ነው። አባቱ በ1847 ሲሞት ትዌይን ትምህርቱን በማቋረጥ በማተሚያ ቤት ውስጥ በሰልጣኝነት ተቀጠረ። ይህን ስራውን በ1857 በመተው የእንፋሎት ጀልባ ነጂ በመሆን መስራት ጀመረ። በዚሁ ስራ በቆየባቸው አመታት ነው ኋላ ላይ አድናቆትን ላተረፉለት የስነ-ጽሁፍ ስራዎቹ የሚሆኑትን እውቀቶች ለማሰባሰብ የበቃው። እሱ ራሱም እንዳለው በዚሁ ስራ ላይ ነው \"ማንኛውንም በልብ-ወለድ፣ በግለ-ታሪክም ሆነ በታሪክ ላይ ሊገኙ የሚችሉ የሰው ባህርያትን\" ሊያጠና የበቃው። በ1861 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የእርስ-በርስ ጦርነት በመቀስቀሱ ምክንያት ማንኛውም አይነት የመርከብ ላይ ጉዞ ሲስተጓጎል ትዌይንም ስራውን ለመልቀቅ ተገዷል። ከዚህ በኋላም በውትድርና ወዶ-ገብነት፣ በወርቅ ማእድን ፈላጊነት፣ በጋዜጠኝነት ወዘተ ስረቷል። በ1869 ዓ.ም የመጀመሪያ ዋነኛ ስራው የሆነውን \"The Innocents Abroad\" ለማሳተም በቃ። ይኽ ድርሰት ክሌመንስ ራሱ በአውሮፓ እና በእየሩሳሌም ባካሄዳቸው ጉብኝቶች ላይ የተመሰረተ ነው። በ1870 ዓ.ም ኦሊቭያ ላንግዶንን በማግባት ኑሮውን ኮኔቲከት በተባለችው ግዛት አድርጓ በዛው ለ17 ዓመታት ኖሯል። በነዚህ 17 ዓመታት ነው አድናቆት ያተረፉለት ስራዎቹን ማለትም \"Roughing It\"፣ \"The Adventures of Tom Sawyer\"፣ Life on the Mississippi\"፣ እና ከሁኡ የላቀ የተባለለት ድርሰቱን \"The Adventures of Huckleberry Finn\"ን ያሳተመው። ትዌይን በ1910 ዓ.ም አርፎ ሬዲንግ፣ ኮኔቲከት ውስጥ በድኑ አርፏል። \n \nጥያቄ: ማርክ ትዌይን የማተሚያ ቤት ስራውን ትቶ በ1857 የተሰማራው በምን ስራ ላይ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የእንፋሎት ጀልባ ነጂ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nመስከረም 23/12 ዓ ም ሽሬ ኢዜአ የተለያዩ የፈጠራ ውጤቶችን ለተጠቃሚዎች በማቅረብ ይሁንታ ያገኘው የ35 ዓመት ወጣት ሔሊኮፕተር ሰርቶ ለሙከራ እየተዘጋጀ መሆኑን አስታወቀ ። ወጣት ዕበ ለገሰ ይባላል ። በመደበኛ ትምህርት ብዙ ገፍቶ ባይሔድም በፈጣራ ብቃቱ ግን በርካታ ስራዎች ለህዝብ እንዲያደርስ አድርጎታል ። የ10ኛ ክፍል ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ በኤሌክትሪክ ሃይል የሚሰራ ምጣድ ጥገና ሥራ የጀመረው ወጣት አሁን ላይ ትልቅ ራእይ አንግቦ የራሱ የሆኑ የፈጠራ ስራዎችን በማቅረብ ውጤታማነቱን በተጠቃሚዎች ዘንድ እየተመሰከረለት መጥቷል ። የምጣድ ጥገና ስራው ለታናሽ ወንድሙ በመልቀቅ የወርቅ መአድን መፈለጊያ መሳሪያ ወደ ማሻሻል መሸጋገሩን ይገልፃል ። በራሱ ፈጠራ ያሻሻለው የወርቅ መፈለጊያ መሳሪያ በባህላዊ መንገድ ወርቅ ለሚያመርቱ ሰዎች በሽያጭ በማቅረብ የፍለጋ ሥራቸውን እንዲቃለል እንዳስቻላቸው ተጠቃሚዎቹ ይናገራሉ ። ቀደም ሲል የነበረው ‘’ጂ አር ዜድ’’ የተባለው የወርቅ መፈለጊያ መሳሪያ ከ70 እስከ 80 ሳንቲ ሜትር ጥልቀት ባለው መሬት ውስጥ የሚገኝ የደለል ወርቅ የሚጠቁም ነበር ። ወጣቱ ያሻሸለው ግን በአንድ ሜትር ጥልቀት የሚገኘውን የደለል ወርቅ በቀላሉ መለየት የሚያስችል መሳርያ ሆኖ ተገኝቷል ። እንዲሁም ከድንጋይ ጋር ተደባልቆ የሚገኝ ወርቅ በቀላሉ መለየት የሚያስችል የድንጋይ ወፍጮ በመፍጠር ለተጠቃሚዎቹ በማቅረብ ላይ እንደሚገኝም ወጣት ለገሰ ይናገራል ። ባለፉት አምስት ዓመታት አምስት የድንጋይ ወፍጮዎችን በመስራት ለተጣቀሚዎቹ በተመጣጣኝ ዋጋ አቅርቧል ። በተጠናቀቀው ዓመት በራሱ ፈጠራ ሶስት ሰዎች የማሳፈር አቅም ያለት ሔሊኮፕተር ሰርቶ በሙከራ ደረጃ ለህዝብ እይታ አቅርቦ የነበረው ወጣቱ ዘንድሮ ለማብረር እየተዘጋጀ መሆኑንም ተናግሯል ። የፈጠራ ሥራዬ ስኬትና ሚስጥር “ይቻላል” የሚል ጽኑ እምነት ስላለኝ ነው የሚለው ወጣቱ ከኢንተርኔት የሚያገኛቸው የፈጠራ ሥራዎችም እገዛ እንዳደረጉለት ጠቁሟል። ሥራ ፈጣሪ ወጣቱ ወደ ገበያ በሚያቀርባቸው የፈጠራ ውጤቱ ጥሩ ገቢ ከማግኘቱም ባሻገር ለሌሎች 10 ወጣቶች የስራ እድል መፍጠሩን ተናግሯል። የወጣቱ የፈጠራ ወጤት ተጠቃሚ ከሆኑትና በባህላዊ መንገድ በደለል ወርቅ ምርት ፍለጋ ከተሰማሩ ማህበራት መካከል የ“ስምረት” ማህበር አንዱ ነው። የማህበሩ አባል የሆነው ወጣት በላይ ተክለሃይማኖት በሰጠው አስተያየት ” ከወጣቱ የገዛነው የደለል ወርቅ ጠቋሚ መሳርያ ሥራችንን ከማቃለል በተጨማሪ በወርቅ ፍለጋው ስኬታማ እንድንሆን አግዞናል” ብሏል። ሌላው የማህበሩ አባል ወጣት ተስፋይ በላይ በበኩሉ ” ከድንጋይ ጋር ተደባልቆ የሚገኝ ወርቅ ለመለየት እጅግ አድካሚ የነበረው ሥራ ወጣቱ ባቀረበልን አነስተኛ የድንጋይ ወፍጮ በመጠቀም የድካማችንን ዋጋ ማግኘት አስችሎናል ” በማለት አድናቆቱን ገልፆለታል ። የሽሬ እንዳስላሴ ከተማ የወጣቶችና ስፖርት ጉዳይ ጽህፈት ቤት ምክትል ሃላፊ አቶ ጎይቶኦም ይሰማ እንዳሉትም ደግሞ የወጣቱን የፈጠራ ክህሎት እንዲሰፋና ሄሊኮፕተሯ ለህዝብ እይታ እንድትበቃ አስፈላጊውን ድጋፍ ይደረግለታል ። የሽሬ እንደስላሴ ፖሊ ቴክኒክና ኮሌጅ ዲን አቶ ፀጋይ ገብረሚካኤል በበኩላቸው የፈጠራ ባለቤት የሆነው ወጣት እበ ለገሰ የፈጠራ ስራዎች የሚያተኩሩት በአካባቢው ህብረተሰብ ላይ በሚታዩ መሰረታዊ ችግሮች ዙሪያ በመሆናቸው ተቀባይነታቸው የጎላ ነው ብለዋል ። ወጣቱ የሚያሳየው ትጋት የተሞላበት የፈጠራ ስራ ለሌሎች ወጣቶችም አርአያ በመሆን መነቃቃት መፍጠሩን የኮሌጁ ዲን መስክረውለታል ። \n \nጥያቄ: ቀድሞ ይጠቀሙበት የነበረው የወርቅ መፈለጊያ ማሽን ምን ያህል ጥልቀት ይፈልጋል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከ70 እስከ 80 ሳንቲ ሜትር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nጋና ጋና በአፍሪካ አትላንቲክ ጠረፍ ላይ የተገኘ አገር ሲሆን ከ24 ሚሊዮን ኗሪዎች በላይ አሉት። የጋና ስራ ቋንቋ እንግሊዝኛ ሲሆን፣ ሌሎች ኗሪ ቋንቋዎች በተለይም ትዊኛ (አካንኛ) በሰፊ ይነገራሉ። የ«ጋና» ስያሜ በታሪክ የድሮ «ጋና መንግሥት» ወይም «ዋጋዱጉ መንግሥት» ለማክበር በ1949 ዓም ተመረጠ። እንዲያውም ያው መንግሥት እስከ 1068 ዓም ድረስ ከጋና ወደ ስሜን-ምዕራብ በአሁኑ ማሊ ይገኝ ነበር እንጂ የዛሬውን ጋና መቸም አልገዛም። «ጋና» በትክክል የዋጋዱጉ መንግሥት አለቆች ማዕረግ ሆኖ ነበር። ዋጋዱጉ መንግሥት በ1068 ዓም ግድም ከወደቀ ቀጥሎ፣ የአካን ብሔሮች ከዚያው ፈልሰው በዛሬው ጋና ሠፈሩና መጀመርያ ግዛቶችን መሠረቱ። ከ1662 እስከ 1949 ዓም ድረስ የአሻንቲ መንግሥት ባካባቢው ቆየ፤ በ1894 ዓም ይህ የብሪታንያ አሻንቲ ጥብቅ ግዛት ሆነ። ከ1949 ዓም አስቀድሞ የዩናይትድ ኪንግደም ጥገኛ ግዛት ሲሆን በወርቅ ሀብቱ ምክንያት «የወርቅ ጠረፍ ጥገኛ ግዛት» (ጎልድ ኮስት ፕሮቴክቶሬት) በመባል ይታወቅ ነበር። ከ1984 ዓም ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ እና ፓርላሜንታዊ መንግሥት ኖሮታል። አብዛኞቹ ኗሪዎች (70%) በተለይ በደቡቡ ክርስቲያን ሲሆኑ፣ በተለይ በስሜኑ 16% የእስልምና ተከታዮች ናቸው። የተረፉትም የኗሪ አረመኔነትን እምነቶች ይከተላሉ። የጋና ዋና ምርቶች ካካዎ፣ ዘይት፣ አልማዝ ናቸው። በአለሙ ከሁሉ ትልቅ የሆነው ሠው ሰራሽ ሐይቅ፣ ቮልታ ሐይቅ፣ በጋና ይገኛል። እግር ኳስ ከሁሉ የተወደደው እስፖርት ነው። የጋና አበሳሰል በተለይ በኮቤ፣ ጐርጠብ፣ የስኳር ድንች፣ ባቄላ፣ በቆሎ፣ ኦቾሎኒ፣ ባሚያና ሩዝ ይሠራል። \n \nጥያቄ: በአፍሪካ ካሉ ሀገራት ጋና በየትኛው ውቅያኖስ ጠረፍ ላይ ይገኛል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አትላንቲክ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሴኔጋል ከ፹ በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሏት። ፓርላማዋ ሁለት ምክር ቤቶች አሉት። አንዱ ፻፳ መቀመጫዎች ያሉት የብሔራዊ ስብሰባ (እንግሊዝኛ፦ National Assembly) ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ፻ መቀመጫዎች ያሉት ሴኔት ነው። ሴኔጋል ራሱን የቻለ ህግ ተርጓሚ አካል አላት። ዳኛዎቹ የሚሾሙት በፕሬዝዳንቱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ሴኔጋል የዴሞክራሲ ሂደት ስኬታማ ነው ከሚባሉት የቀድሞ ቅኝ ተገዢ ሀገራት መካከል የምትጠቀስ ናት። የአካባቢ አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። ማራባውት የሚባሉ የእስልምና ሃይማኖት መሪዎችም በሴኔጋል ጠንካራ የፖለቲካ ተፅእኖ አላቸው፡ ከ፪ ሚሊዮን ነዋሪዎች ያሉበት የሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር የሀገሩ ትልቁ ከተማ ነው። ሁለተኛው ፭፻ ሺህ ሰዎች የሚኖሩበት ቱባ ከተማ ነው። ሴኔጋል ከ12.5 ሚልዮን በላይ የሚሆን ሕዝብ አላት። ከዚህ ውስጥም ወደ ፵፪ ከመቶ በገጠር ነው የሚኖረው። የአሜሪካ የስደተኖች ኮሚቴ ባቀረበው የ2008 እ.ኤ.አ. የዓለም ስደተኞች አጠቃላይ ቅኝት መሠረት ሴኔጋል በ2007 እ.ኤ.አ. ወደ 23,800 የሚገመቱ ስደተኞች ይኖሩባታል። ከዚህ አብዛኛዎቹ የመጡት ከሞሪታኒያ ነው። ስደተኞቹ በንድዮም፣ ዶዴል እና በሴኔጋል ወንዝ አቅራቢያ በሚገኙ ሠፈሮች ይኖራሉ። የአገር ይፋዊ ብሔራዊ ቋንቋ ፈረንሳይኛ ሲሆን ከብዙ ኗሪ ቋንቋዎች 11ዱ በተለይም ዎሎፍኛ አገራዊ ዕውቅና አላቸው። ሌሎቹ ባላንታኛ፣ ማንዲንክኛ፣ ፑላርኛ (ፉላኒኛ)፣ ሰረርኛ፣ ሶኒንክኛ፣ ኖንኛ፣ ማንካኛኛ፣ ማንጃክኛ፣ ጆላኛ እና ሀሣኒያ አረብኛ ናቸው። ፖርቱጊዝኛም በትምህርት ቤት ይማራል፣ የካቦ ቨርዴ እና የጊኔ-ቢሳው ኅብረተሠቦችም ፖርቱጊዝኛ ክሬዮል ይናገራሉ። ከሴኔጋል ሕዝብ 94% የእስልምና አማኞች፣ 5% ክርስትና (ባብዛኛው ካቶሊክ)፣ 1% የኗሪ አርመኔነት ተከታዮች ናቸው። የመንግሥት ሃይማኖት የለውም። በሴኔጋል ልማዳዊ ባሕል ግሪዮት የተባሉ ሽማግሎች ታሪኮቻቸውን በአፍ ቃል ይደግማሉ። ሴኔጋል ለሙዚቃዊ ስልቶቹ ይታወቃል፤ በተለይ የሚወድደው ዘመናዊው ስልት ምባላክስ ተብሏል። በሴኔጋል አበሳሰል በተለይ አሣ፣ ዶሮ፣ በግ፣ አተር፣ ዕንቁላል፣ በሬ ይጠቀማሉ፤ እስላም አገር እንደ ሆነው መጠን ግን አሳማ አይበላም። ኩስኩስ፣ ሩዝ፣ ስኳር ድንች፣ ምስር፣ ጥቁር-ዐይን አተር ደግሞ በሴኔጋል አበሳሰል በሰፊ ይገኛሉ። በእስፖርት በኩል፣ ከሁሉ የሚወደደው ባህላዊው የሴኔጋል ትግል ግጥሚያ ሲሆን፣ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ ደግሞ እጅግ ይወደዳሉ። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር ምን ያህል ነዋሪዎች አሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፪ ሚሊዮን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየ2010 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ የ2010 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ ፲፱ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የነበረ ሲሆን ከሰኔ ፬ እስከ ሐምሌ ፬ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. በደቡብ አፍሪካ ተካሄዷል። ውድድሩን ለማቅረብ የተካሄደው ዕጣ ውስጥ የአፍሪካ ሀገሮች ብቻ እንዲሳተፉ ነበር የተፈቀደው። ደቡብ አፍሪካ ግብፅና ሞሮኮን በማሸነፍ የመጀመሪያው የዓለም ዋንጫን ያቀረበች አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ፊፋ ለውድድሩ ያቀረበው ጠቅላላ የሽልማት ገንዘብ $420 ሚሊዮን ነው። ይህም ከ2006 እ.ኤ.አ. ውድድር ሽልማት ገንዘብ የስልሳ ከመቶ ዕድገት አለው። ከዚህ ውስጥ $40 ሚሊዮን የሚሆነው ተጫዋቾቹ ለሚጫወቱበት ክለቦች ተጫዋቾቹ ለሚደርስባቸው ጉዳት መካካሻ እንዲሆን ተሰጥቷል። ከውድድሩ በፊት እያንዳንዱ ቡድን ለዝግጅት ወጪው $1 ሚሊዮን ተረከበ። ግጥሚያዎቹ በዘጠኝ ከተማዎች ውስጥ በሚገኙ አስር ስታዲየሞች ውስጥ ነው የተካሄዱት። የዋንጫ ጨዋታው በጆሃንስበርግ ከተማ በሚገኘው ሶከር ሲቲ ስታዲየም ነው የተከናወነው። የምድብ ድልድል ሥነ ስርዓቱ በኬፕ ታውን፣ ደቡብ አፍሪካ በሚገኘው ኬፕ ታውን ዓለም አቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል በኅዳር ፳፭ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. ተከናወነ። ሥነ ስርዓቱ የቀረበው በደቡብ አፍሪካዊቷ ተዋናይ ሻርሊዝ ቴሮን እና የፊፋ ዋና ጸሐፊ ዠሮም ቫልክ ነው። የዕጣ ኳሶቹን ያወጡት ዴቪድ ቤክሃም፣ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ፣ ጆን ስሚት፣ መካያ ንቲኒ፣ ማቲው ቡዝ እና ሲምፊዌ ድሉድሉ ናቸው። የፊፋ ዳኛዎች ኮሚቴ ፳፱ ዳኛዎችን ለዓለም ዋንጫ መርጧል። እነዚህም ከኤ.ኤፍ.ሲ. አራት፣ ከካፍ አስር፣ ከኮንሜቦል ስድስት፣ ከኮንካካፍ አራት፣ ከኦ.ኤፍ.ሲ. ሁለት እና ከዩኤፋ አስር ዳኛዎችን ያጠቃልላል። እንግሊዛዊው ዳኛ ሀዋርድ ዌብ የዋንጫ ጨዋታውን እንዲዳኝ ተመርጧል። \n \nጥያቄ: ደቡብ አፍሪካ የትኞቹን የአፍሪካ ሀገሮች በመብለጥ ነው የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ የአለም ዋንጫ አዘጋጅ ለመሆን የበቃችው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ግብፅና ሞሮኮን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: በማሊ በተደረገው ዲሞክራሲያዊ ምርጫ በማሸነፍ አልፋ ዑመር ኮናሬ ወደ ስልጣን የመጡት መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ1992 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቦትስዋና ቦትስዋና ወይም በይፋ የቦትስዋና ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ Republic of Botswana ሰጿና፡ Lefatshe la Botswana) በደቡባዊ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ አገር ናት። ቦትስዋና የቀድሞ የብሪታንያ ቅኝ ግዛት ስትሆን ነፃነቷን በመስከረም ፳ ቀን ፲፱፻፶፱ ዓ.ም. ከተቀዳጀች በኋላ መሪዎቿ በነፃ ዴሞክራሲያዊ ምርጫዎች ተመርጠዋል። ቦትስዋና ሜዳማ ስትሆን ከሰባ ከመቶ በላይ በካለሃሪ በርሃ የተሸፈነች ናት። በደቡብና ደቡብ ምሥራቅ ከደቡብ አፍሪካ፣ በምዕራብና ሰሜን ከናሚቢያ እና በሰሜን ምሥራቅ ከዚምባብዌ ጋር ትዋሰናለች። ከዛምቢያም ጋር በደንብ ያልተወሰነ ቢበዛ በመቶ ሜትር የሚቆጠር ወሰን አላት። \n \nጥያቄ: ቦትስዋና ሰባ በመቶ ያህል የተሸፈነችው በየትኛው በረሃ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በካለሃሪ በርሃ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ (ቀ.ኃ.ሥ.) ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ተፈሪ መኰንን ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ። በ፲፰፻፺፱ የሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ፲፱፻፫ ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቀሳውስት ስለዚህ ኢያሱን አልወደዱዋቸውም ነበር። ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ። በመስከረም ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. የንጉሥነት ማዕረግ ተጨመረላችው። በ፲፱፻፳፪ ዓ.ም ንግሥት ዘውዲቱ አርፈው ንጉሠ ነገሥት ሆኑና ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. ብዙ የውጭ ልዑካን በተገኙበት ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ቅብዓ ቅዱስ ተቀብተው እሳቸውና ሚስታቸው እቴጌ መነን ዘውድ ጫኑ። በንግሥ በዓሉ ዋዜማ ጥቅምት ፳፪ ቀን የትልቁ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለዘውድ በዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት ፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ። ለንግሥ ስርዐቱ ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገር ልኡካን ከየአገራቸው ጋዜጠኞች ጋር ከጥቅምት ፰ ቀን ጀምሮ በየተራ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ስለነበር ሥርዓቱ በዓለም ዜና ማሰራጫ በየአገሩ ታይቶ ነበር። በተለይም በብሪታንያ ቅኝ ግዛት በጃማይካ አንዳንድ ድሀ ጥቁር ሕዝቦች ስለ ማዕረጋቸው ተረድተው የተመለሰ መሢህ ነው ብለው ይሰብኩ ጀመር። እንደዚህ የሚሉት ሰዎች እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ፊተኛው ስማቸው «ራስ ተፈሪ» ትዝታ ራሳቸውን «ራስታፋራይ» (ራሰተፈሪያውያን) ብለዋል። \n \nጥያቄ: የአጼ ኃይለ ሥላሴ ባለቤት ማን ይባሉ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ እቴጌ መነን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበምዕራቡ ዓለም ውስጥ ስለ ፀሓይ ሳይንሳዊ መግለጫ ለመስጠት ከቻሉ ቀዳሚ ሰዎች አንዱ ግሪካዊው ፈላስፋ አናክሳጎራስ ነበር። ፀሓይ በእሳታዊ ነበልባል የምትንቀለቀል እጅግ ግዙፍ የብረት ኳስ እንጂ የሄሊዮስ ሰረገላ እንዳልነበረች በምክንያት የተደገፈ ትንተና አቀረበ። ይህንን እንደ ኑፋቄ የተቈጠረ ሐተታ በማስተማሩም ታሰረ፤ በሞት እንዲቀጣም ተፈርዶበት ነበር፤ በፔሪክልስ አማላጅነት እንዲፈታ ተፈቀደለት እንጂ። የባለሥልጣናት መዓት የወደቀበት ሌላው የሳይንስ ሊቅ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነበር። በ16ኛው ምእት ውስጥ የኖረው ቆጰርኒቆስ ምድር ፀሓይን በቀለበትማ ምሕዋር ትዞራለች እንጂ፣ ፀሓይ ምድርን አትዞርም የሚል ኀልዮ አቅርቦ ነበር። በ17ኛው ምእት ጋሊሌዮ በቴሌስኮፕ ለታገዘ የፀሓይ ጥናት ፈር-ቀዳጅ ሊቅ ኾነ። አይዛክ ኒውተን ደግሞ በፕሪዝም አማካይነት የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ አሳየ። 19ኛው ምእት ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የኾነበት፣ በስፔክትሮስኮፕ ስለ ፀሓይ የሚደረገው ጥናትም እጅግ የመጠቀበት ምእት ኾነ። ዛሬ በብዙ አገሮች ልማድ ፀሓይ እንደ ባህላዊ ምልክት ትታያለች። ለምሳሌ በሜክሲኮ ኪነ ጥበብ አበክራ የምትታይ ሞቲፍ በመባል ትታወቃለች። በኛ ሥርዐተ-ፀሓይ ዋናዋ ትልቅ አካል ራሷ ፀሓይ ናት። በመላው ሥርዐተ-ፀሓይ ውስጥ ከሚገኘው ክብደት 99.86% የፀሓይ ነው። ለምሳሌ ከታላቁ ፈለክ ከጁፒተር ሲነጻጸር የፀሐይ ክብደት 1000 ዕጥፍ ይበልጣል። የፀሓይ ክብደት ከምድር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ ይበልጣል። በጣም ግዙፍ እና ከባድ የኾነችው ኮከብ ከምድር ያለችበት ርቀት በጣም የሚያስደንቅ ነው። በምድር እና በፀሓይ መካከል ያለው ርቀት የምድርን ዳያሜትር በ12,000 ጊዜ ይበልጣል። ብርሃን ይህን ርቀት ለመጓዝ 8.5 ደቂቃ ይፈጅበታል። \n \nጥያቄ: የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት ማን ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ዊሊያም ኸርሽል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nስዋሂሊ ስዋሂሊ ፡ (ወይም ፡ ኪሷሂሊ Kiswahili) ፡ በምሥራቅ ፡ አፍሪቃ ፡ የሚናገር ፡ የባንቱ ፡ ቋንቋዎች ፡ ቤተሠብ ፡ ቋንቋ ፡ ነው። የስዋሂሊ ፡ ሕዝብ (፭ ፡ ሚሊዮን ፡ ተናጋሪዎች) ፡ ልደት ፡ ቋንቋ ፡ ከመሆኑ ፡ በላይ ፡ ለ ፴ ፡ እስከ ፡ ፶ ፡ ሚሊዮን ፡ ሌሎች ፡ ሰዎች ፡ ሁለተኛ ፡ ቋንቋ ፡ ሆኗል። የስዋሂሊ ፡ ስም ፡ መነሻ ፡ ከዓረብኛ ፡ ቃል ፡ «ሰዋሂል» ፡ ነበር ፤ ይህም ፡ የ«ሳኸል» ፡ (ማለት ፡ ዳር) ፡ ብዙ ፡ ቁጥር ፡ ነው። ስለዚህ ፡ የ«ስዋሂሊ» ፡ ትርጉም ፡ የ(ባሕር) ፡ ዳረኞች ፡ ቋንቋ ፡ ሊሆን ፡ ይችላል። የቋንቋው ፡ ቤተሰብ ፡ ባንቱ ፡ ሲሆን ፡ ተናጋሪዎቹ ፡ መርከበኞችና ፡ ነጋዴዎች ፡ በመሆናቸው ፡ መጠን ፡ ከዓረብኛ ፣ ከፋርስ ፣ ከህንዲ ፣ እና ፡ ከቻይንኛ ፡ ቢሆንም ፡ ብዙ ፡ ቃሎች ፡ ተበድረዋል። \n \nጥያቄ: ስዋሂሊ ሁለተኛ ቋንቋቸው የሆኑ ምን ያህል ሕዝቦች አሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ፴ ፡ እስከ ፡ ፶ ፡ ሚሊዮን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየብረት ማዕድኖች የብረት ማዕድናት በሁለት ይከፈላሉ። እነሱም ፕሪሽየስ ሜታል መደብ እና ቤዝ ሜታል መደብ ናቸው። ወርቅ እንደ ሌሎቹ የብረታ ብረት ማዕድኖች የይዘቱ ሚዛን የሚለካው በትሮይ አውንስ መጠን ነው። አንድ ትሮይ አውንስ ፤ ሠላሳ አንድ ነጥብ አስር ግራም ነው። ትሮይ የሚባለውን ስም ያገኘው ከግሪክ አገር ሳይሆን ፤ በፈረንሳይ አገር ከሚገኘው ከዘመናት በፊት የወርቅና የብር እንዲሁም የተለያዩ የከበሩ ማዕድናት ይሸጥበት ከነበረው ትሮይስ ከተማ ነው። የወርቅ ጌጥ ማድረግ ለሚወዱ ሰዎች ደግሞ ፤ የንፁህ ወርቅ መጠን በካራት ይለካል። በጣም ንፁህ የሆነው ሃያ አራት ካራት ሲሆን ከዚያ ዝቅ ያለ መጠን ያለው ደግሞ ከሌላ ብረት ማዕድን ጋር የተደባለቀው ነው። የዋጋውም ዓይነት በዚሁ መጠን በወርቅ ሰሪ ቤቶች ሱቅ ውስጥ ይለያያል። ብር የተባለው ማዕድን ደግሞ ተፈላጊነቱ በድሮ ጊዜ ለመገበያያነት ቀጥሎም ለተለያዩ የንብረት እቃዎችና የፋብሪካ ውጤቶች አገልግሎቱን የሚሰጥ የማዕድን ብረት ነው። ንፁህ ብር የሚባለው ብዙውን ጊዜ ዘጠና ሁለት ነጥብ አምስት ያክሉን ሲልቨር የሚይዘው ነው። የተቀረው ሰባት ነጥብ አምስት ከመዳብ (ኮፕር) - ወይንም ከሌላ የብረት ማዕድን ጋር የሚደባለቀው ነው። የአጠቃላይ ስሙም እስተርሊንግ ሲልቨር ይባላል። መደባለቁ የሚጠቅመው የብር ይዘቱን ለማጠንከር ወይንም በቀላሉ ከውስጡ ያሉትን ንጥረ ማዕድኖች በሙቀት ጊዜ ወይንም በቅዝቃዜ መጠናቸው እንዳይለወጥ ነው። \n \nጥያቄ: አንድ ትሮይ ስንት ግራም ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሠላሳ አንድ ነጥብ አስር ግራም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአል የተባለ ሰው ሰራሽ መሳሪያ የጡት ካንሰር መመርመሪያ መሳሪያን በማንበብ ረገድ ከሐኪሞች በተሻለ ትክክለኛ መሆኑን አንድ ጥናት አመለከተ። ሰው ሰራሹ መሳሪያ የጡት ካንሰር መመርመሪያ መሳሪያን በማንበብ ረገድ ሁለት ሐኪሞች በጋራ ከሚሰሩት በተሻለ መልኩ ትክክለኛ መሆኑን ባለሙያዎቹ አረጋግጠናል ብለዋል። ከተለያዩ ተቋማት የተውጣጣው ቡድን አል የተባለው ሰው ሰራሽ መሳሪያን ይዘው በ29 ሺህ ሴቶች ላይ ሙከራ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። በዚህም መሳሪያው የጡት ካንሰርን በመለየት ረገድ የስድስት ራዲዮሎጂ ባለሙያዎችን ያክል ውጤታማ መሆኑንም ገልጸዋል። ይህም ሁለት የዘርፉ ሐኪሞች (ዶክተሮች) ከሚሰሩት ስራ ጋር እኩል ውጤት ያለው ስለመሆኑም በጥናት ውጤታችን አረጋግጠናል ነው ያሉት። ከዚህ ባለፈም መሳሪያው እንደ ሐኪሞቹና ራዲዮሎጂስቶቹ የግለሰቧን የቀደመ የጤና ሁኔታ የሚገልጽ መረጃ ሳይኖረው የጡት ካንሰሩን መለየት መቻሉም የተሻለ ስለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል። ባለው አሰራር ሁለት የራዲዮሎጂ ባለሙያዎች ችግሩን ለመለየት የጡት ካንሰር መለያ መሳሪያውን የሚያነቡ ሲሆን፥ ባልተስማሙባቸው ጉዳዮች ላይ ሦስተኛ ሐኪም ተጨምሮ ምስሎቹን እንዲገመግም ይደረጋል። አዲሱ መሳሪያ ራሱን ችሎ ከማንበቡም በላይ ችግሩን ለይቶ በመረዳት በኩል ውጤታማ ስለመሆኑ በባለሙያዎቹ ተመስክሮለታል። መሳሪያው የጡት ካንሰር ምርመራ ውጤት ላይ ከባለሙያዎቹ የተሻለ ውጤት ማስመዝገቡም ተገልጿል፤ በዚህም ለታካሚዋ የጡት ካንሰር አለብሽ በሚል በባለሙያ የሚነገራትን ሃሰተኛ የምርመራ ውጤት በ1 ነጥብ 2 በመቶ ቀንሷል። ከዚህ ባለፈም በምርመራ ወቅት የጡት ካንሰር የለም በሚል የሚነገር የተሳሳተ ውጤት ደግሞ ከባለሙያ አንጻር መሳሪያው በ2 ነጥብ 7 በመቶ መቀነሱን ባለሙያዎቹ ገልጸዋል። ምንጭ፦ ቢቢሲ \n \nጥያቄ: አል የተባለው ሰው ሰራሽ መሳሪያ ምንን ለመመርመር ነው ስራ ላይ የዋለው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የጡት ካንሰር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nእንደ ፕላቶ ዘገባ፣ የሶቅራጠስ እናት ፌናርት የተሰኘች አዋላጅ ነበረች። ሶቅራጠስ እናቱ ሴቶች ልጅ እንዲወልዱ እንደምትረዳ ሁሉ እርሱ ደግሞ ሰዎች አዳዲስ አሳቦችን እንዲወልዱ ለመርዳት እንደሚሞክር መናገሩ ይጠቀሳል። የሶቅራጠስ አባት ድንጋይ አናጢ የነበረው ሶፍሮኒስከስ እንደነበር ይጠቀሳል። ሶቅራጠስ በዘመኑ ድሃ የነበረ ሲሆን ለዚህ ምክንያቱ ከገንዘብ ይልቅ እውቀት ይበልጣል ብሎ ስለሚያምን ነበር። ሶቅራጠስ ስራ እንደማይሰራና በፍልስፍና ሃሳብና ክርክር ጊዜውን እንደሚያሳልፍ ፕላቶ ዘግቦት ይገኛል። ዛንቲፕ የተሰኘች ከርሱ በዕድሜ በጣም የምታንስ ሴትን አግብቶ ሶስት ልጆች እንደነበሩት ፕላቶ ጽፏል። ሶቅራጠስ 70 ዓመት በሞላው ጊዜ የአቴና መንግስት እንዲያዝና ለፍርድ እንዲቀርብ አደረገ። በወቅቱ ሁለት ክሶች ሲቀርቡበት አንደኛው \"በትምህርትህ ወጣቱን አበላሽተሃል\" የሚል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ \"ለግሪክ ጣዖታት አልተገዛህም\" የሚል ነበር። እንደ ፕላቶ ዘገባ ግን ሶቅራጠስ የግሪክ ጣኦታት አምላኪ ነበር። በአንድ አንድ ተመራማርወች ዘንድ የአቴንስ መንግስት ያቀረባቸው ክሶች በውሸት ላይ የተመሰረቱ ናቸው። የሆኖ ሆኖ፣ ክሪቶ የተሰኘው የፈላስፋው ጓደኛ ለጠባቂወቹ ጉቦ በመስጠት እንዲያመልጥ ሁኔታውን አመቻችቶ ነበር። ሶቅራጠስ ግን እምቢ በማለት ቀረ እንጂ አላመለጠም። ሶቅራጠስ ለፍርድ በቀረበ ጊዜ ሰፊ የሆነ የመከላከያ ክርክር በማቅረብ የአቴናን መንግስት ክስ ውድቅ ለማደርግ ሞክሯል። ከዚህ በኋላ ዳኞቹ ምን አይነት ቅጣት እንዲበይኑበት እንደሚፈልግ ሲጠይቁት፣ ለአቴና ህብረተሰብ ካበረከተው ጥሩ ተግባራቱ አንጻር በቀሪው ዘመኑ ሁሉ ነጻ እራት እንዲያመጡለት ተናገረ። ነገር ግን ፍርድ ቤቱ ወይ በቅጣት እንዲለቀቅ ወይንም ደግሞ እንዲገደል የእጅ ምርጫ አደረገ። ውጤቱም ሶቅራጠስ እንዲገደል የሚል ሆነ። ይሁንና ሶቅራጠስ ሞትን አይፈራም ነበር። ሞቱን ለማስቀረት ይቅርታም ሆነ ሌላ ማባበያ አላቀረበም። በርሱ ሥነ ምግባር መሰረት ላመነበት ነገር እስከመጨረሻ መቆሙ ሰናይ ድርጊት ነበር። ስለሆነም ሄምሎክ የተሰኘ መርዝ ጠጥቶ እንዲሞት ስለታዘዘ፣ መርዙን በመጠጣት አለፈ። \n \nጥያቄ: ሶቅራጥስ ጊዜውን የሚያሳልፈው ምን በማድረግ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በፍልስፍና ሃሳብና ክርክር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል ከቅኝ ግዛት ነጻነት በኋላ የመጀመሪያ ፕሬዘዳንት የሆነው ሊዎፖልድ ሴንግሆርም ስልጣን የያዘው መቼ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአፍሪካ አፍሪካ (አፍሪቃ) ከዓለም ሁለተኛ ትልቅ አህጉር ነች። ከ869 ሚሊዮን በላይ ህዝብ በዚች አህጉር የሚኖር ሲሆን በጠቅላላ 54 ሀገሮች ይገኛሉ። ከእነዚህም ሀገሮች መሀል ናይጄሪያ በህዝብ ብዛት (127 ሚሊዮን) የመጀመሪያውን ደረጃ ስትይዝ፤ ግብፅና ኢትዮጵያ በ73 ሚሊዮን እና በ72 ሚሊዮን ህዝብ በሁለተኛና በሶስተኛ ደረጃ ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት የህዝብ ብዛት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር ከሌሎች የፖለቲካና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች ጋር በመደማመር ድህነትን በማባባስ ደረጃ ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡ ጂዎግራፊና ሕዝብ ከስድስቱ ዓለማት አንዱ አፍሪካ ነው። አፍሪካ ሰፊ ነው። የዓለምም አራተኛ ክፍል ይሆናል። ከኤውሮጳ የሚለየው በሜዴቲራኒያን ባሕር ነው። ከአሜሪካም በአትላንቲክ ውቅያኖስ ይለያል። ከኒው ዮርክም ቢሆን ወይም ከቦስቶን ከአሜሪካ የሚቀርበው ክፍል ሦስት ሺህ ማይል ይሆናል። ነገር ግን በጊብሮልታር (ጂብራልታር) በኩል የሆነ እንደ ሆነ ለኤውሮጳ በጣም ቅርብ ነው። ከእስያ በኤርትራ ባሕር ይለያያል። የሆነ ሆኖ እስያ ባንድ ወገን ሱዝ ካናል በሚባለው በኩል ከአፍሪካ ጋር ተጋጥሞአል። ሙሴ ሌስፖስ መርከብ እንዲተላለፍ ብሎ አስቆፍሮ ያስከፈተው በዚህ በኩል ነው። \n \nጥያቄ: በአፍሪካና በእስያ አሕጉር መካከል ያለው መተላለፊያ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሱዝ ካናል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበ628 ዓክልበ.፣ ድራኮ የሚባል ጸሃፊ የአቴና ከተማ ሕግጋት ጻፈ፤ ይህም ሕግ እጅግ ጨካኝ ሆኖ ይሙት በቃ ለማንኛውም ጥፋት ወሰነ። በ600 ዓክልበ.፣ የአቴና አለቃ ሶሎን አዲስ ሕገ መንግሥት ፈጠረ። የሰራተኞች ሸክም አቀለለ፣ ነገር ግን ባላባትነት በልደት ሳይሆን በንብረት ብዛት እንዲቈጠር አስደረገ። ክሊስቴኔስ እንደገና በ516 ዓክልበ. በዴሞክራሲያዊ መሠረት የተሻሸለ ለአቴና ሕገ መንግሥት አወጣ። የግሪክ ፈላስፋ አሪስጣጣሊስ በ350 ዓክልበ. ግድም የሕገ መንግሥት ሀሣብ ለይቶ ዐወቀ። በጽሑፎቹ የአቴና፣ የስፓርታና የካርታግና ሕገ መንግሥቶች ያነጻጽራል። በመደምደሚያው የተሻለው ሕገ መንግሥት ከንጉሣዊ፣ ከመኳንንታዊና ከሕዝባዊ ወገኖች የተደባለቀ መሆኑን ገመተ። በሀሣቡ በመንግሥት የሚከፋፈሉ ዜጎች ከማይከፋፈሉ ከባርዮችና ዜጎች ካልሆኑ ሰዎች ልዩነት አደረገ። ሮማውያን መጀመርያ «12ቱ ሰንተረዦች» የተባለውን ሕገ መንግሥት ያወጡ በ457 ዓክልበ. ነበር። ከዚያ በኋላ አንዳንዴ የተለያዩ ሕጎችና ትእዛዛት ይጨምሩበት ነበር እንጂ እስከ መጽሐፈ ቴዎዶስዮስ ድረስ (430 ዓ.ም.) ሌላ ክምቹ ሕገ መንግሥት አልኖረም ነበር። በኋላም በምሥራቁ መንግሥት (ቢዛንታይን) በኩል መጽሐፈ ዩስጢኒያኖስ (526 ዓ.ም.) ለአውሮፓ ከፍ ያለ ተጽእኖ ነበረው። ይህም በምስራቁ ነገሥታት 3ኛ ሌዎን ኢሳውራዊ «ኤክሎጋ» (732 ዓ.ም.) እና በ1ኛ ባሲሌዎስ «ባሲሊካ» (870 ዓ.ም.) በተባሉት ሕገ ፍትሐን ተከተለ። \n \nጥያቄ: በ457 ዓክልበ. ሮማውያን ለመጀመሪያ ጊዜ ያወጡት ሕግ ምን በመባል ይጠራ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 12ቱ ሰንተረዦች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአዲስ አበባ፣ ታህሳስ 15፣ 2012(ኤፍቢሲ) ኡበር የተሰኘው የታክሲ አገልግሎት ሰጭ ድርጅት ተባባሪ መስራች ትራቪስ ካላኒክ በዓመቱ መጨረሻ ከቦርድ አባልነታቸው ሊለቁ መሆኑን አስታውቀዋል ፡፡ ይሁን እንጂ የ43 ዓመቱ ትራቪስ በድርጅቱ ውስጥ ካሉ ዘጠኙ ዳይሬክተሮች ውስጥ አንዱ ሆነው የሚቀጥሉ መሆኑን ነው የተናገሩት። ትራቪስ ካላኒክ እንደ አውሮፓውያ ኑ አቆጣጠር 2017 ላይ በድርጅቱ በተስተዋሉ የተለያዩ የሙስና ቅሌቶች ምክንያት ስራ ለማቆም ጫፍ ደርሰው ነበር ። ይህን ተከትሎም በኡበር ድርጅት ውስጥ ያላቸውን አብዛኛውን የአክሲዮን ድርሻ መሸጣቸው ነው የተነገረው። ትራቪስ ካላኒክ በአስር ዓመቱ መገባደጃ ኩባንያው ያለው የሕዝብ ግንኙነት እና በጎ አድራጎት ላይ ለማተኮር ለእኔ ትክክለኛ ጊዜ ይመስለኛል፤ በዚህም ደስተኛ ነኝ ተናግረዋል ፡፡ ካናኒክ በጣም ዝነኛ የሆነው የታክሲ አገልግሎት ሰጭ ድርጅት በመመስረት በዓለም ዙሪያ የትራንስፖርት ችግርን ለመቅረፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክተዋል። ምንጭ፣ ቢቢሲ \n \nጥያቄ: በኡበር የታክሲ አገልግሎት ውስጥ ለረጅም ጊዜ በቦርድ አባልነት ያገለገሉት ትራቪስ ካላኒክ መቼ በተስተዋለው የሙስና ችግር ምክንያት ነው ከኃላፊነታቸው ለመልቀቅ ያሰቡት?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 2017 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቱርክመንኛ ቱርክመንኛ (Türkmen) የቱርክምኒስታን ብሔራዊ ቋንቋ ነው። በቱርክመኒስታን 3,430,000 ተናጋሪዎች ሲኖሩ ከቱርክመኒስታን ውጭ ደግሞ 3 ሚሊዮን የሚያሕሉ ተናጋሪዎች በተለይም በኢራን (2 ሚሊዮን) በአፍጋኒስታን (500,000) እና በቱርክ (1000) አሉ። ቱርክመንኛ በቱርኪክ ቋንቋ ቤተሰብ ውስጥ ይከተታል። ይህም አንዳንዴ በትልቁ አልታይ ቋንቋ ቤተሰብ ውስጥ ይደመራል። ቀድሞ የተጻፈበት ወይም በቂርሎስ ወይም በ አረብ ፊደሎች ነበር፤ አሁን ግን የቱርክመኒስታን መሪ ሳፓርሙራት ኒያዞቭ በላቲን ፊደል እንዲጻፍ አዋጀ። በ1994 አ.ም. ደግሞ የሳምንት ቀኖችና የወር ስሞች ሁሉ እንደ አቶ ኒያዞቭ \"ሩህናማ\" የሚባል ይፋዊ መጽሐፍ ፍልስፍና በአዋጅ ተቀየሩ። \n \nጥያቄ: በአፍጋኒስታን ምን ያህል የቱርክመንኛ ቋንቋ ተናጋሪ አለ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 500,000 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዩጋንዳ ዩጋንዳ ሪፐብሊክ (ወይም ዑጋንዳ) በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። በኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ ይዋሰናል። የዩጋንዳ ሰም የመጣው ከቡጋንዳ መንግሥት ነው። ከአረቦችና አውሮፓውያን በ1800ቹ ከመድረሳቸው በፊት ብዙ የሚታወቅ ነገር አልነበረም። በ15ተኛ መቶ ክፍለ-ዘመን ችዌዚ የተባለውን መንግስት በአፈ ታሪክ ይገኛል። አረቦችና አውሮፓውያን በ19ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሲደርሱ ብዙ መንግሥቶች በቦታው ነበሩ። እነዚህም በንዮሮ ፣ ቡሶጋ ፣ ቡጋንዳ ፣ ቶሮ እና አንኮልን ያጠቃልላሉ። ከ1894 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በታላቁ ብሪታን ስትመራ ነበር። የተለያዩ ቦታዎች ከተዋሃዱ በኋላ ዩጋንዳ በ1914 እ.ኤ.አ. ቅርጿን ያዘች። በ1966 እ.ኤ.አ. ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ ሕገ-መንግሥቱን አፍርሰው እራሳቸውን ፕሬዝዳንት አደረጉ። በ1971 እ.ኤ.አ. ኢዲ አሚን ሀገሩን መምራት ጀመሩ። የኢዲ አሚን አመራር 300,000 የሚገመቱ ዩጋንዳውያንን አስጨርሷል። በ1979 እ.ኤ.አ. የታንዛንያ ኃይሎች ኢዲ አሚንን ከሥልጣን ያስወግዳሉ። ሚልተን ኦቦቴ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ግን በ1985 እ.ኤ.አ. እንደገና ይወርዳሉ። ያሁኑ ፕሬዝዳንት ዮወሪ ሙሴቪኒ ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ናቸው። ፕሬዝዳነንቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይመርጣሉ። ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሎ ሲባምቢ ናቸው። ዩጋንዳ በመሬት የተቆለፈች ብትሆንም ታላላቅ የውሃ አካላት አሉ። ከነዚህ ውስጥም ቪክቶሪያ ሐይቅ፣ አልበርት ሐይቅ፣ ክዮጋ ሐይቅ እና ኤድዋርድ ሐይቅ ይዘረዘራሉ። ታላላቅ ከተማዎች በቪክቶሪያ ሐይቅ አቅራቢያ ይገኛሉ። እነዚህም ካምፓላንና እንትቤን ያጠቃልላል። ዩጋንዳ በ70 ወረዳዎች የተከፋፈለች ስትሆን እነዚህም በአራት አመራር ክልሎች ውስጥ ናቸው። አራቱ አመራር ክልሎች ሰሜናዊ ፣ ምሥራቃዊ ፣ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ይባላሉ። ወረዳዎቹ በዋና ከተማዎቻቸው ነው የሚሰየሙት። በዩጋንዳ ውስጥ የመዳብ እና ነጭ ብረት ክምችቶት አሉ። ግብርና ዋናው የኤኮኖሚ ሴክተር ነው። ከ80 በመቶ በላዩ የስራ ኃይል በግብርና ነው የተሰማራው። ቡና ዋናው የኤክስፖርት ትርፍ ምንጭ ነው። ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግሥቱ ከሌሎች ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን በኢዲ አሚን ጊዜ የወደቀውን ኤኮኖሚ ለማንሳት ተጣጥሯል። ዩጋንዳ ለብዙ ብሔረሰቦች ቤት ነው። ከነዚህ ውስጥ ግን አንድ ትልቁን ሕዝብ ብዛት የሚወክል የለም። 40 አካባቢ የሚሆኑ ቋንቋዎች ባሁኑ ጊዜ ይነገራሉ። ከነጻነት በኋላ እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተደርጓል። ብዙ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ ሉጋንዳ ሲሆን የአቴሶ ቋንቋ በሁለተኛነት ይከተላል። ኪስዋሂሊ ዋናው የንግድ ቋንቋ ነው። የዩጋንዳ የትምህርት ስርዐት የሰባት ዓመት መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፣ ስድስት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና ከ3 እስከ 5 ዓመት ከሁለተኛ ደረጃ በኃላ ትምህርት ያጠቃልላል። \n \nጥያቄ: ኢዲአሚን በዩጋንዳ ሥልጣን የያዘው መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ1971 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nብሪታኒያ የቻይናው ሁዋዌ 5ኛ ትውልድ (5G) ኔትወርክ በተወሰነ ገደብ በሀገሯ ስራውን እንዲቀጥል ውሳኔ አሳለፈች፡፡ ውሳኔው የተላለፈው ብሪታኒያ ኩባንያውን እንድታግደው አሜሪካ ጫና እየፈጠረች ባለችበት ወቅት፡፡ ብሪታኒያ ውሣኔውን ያሳለፈችው በተወሰኑ ጉዳዮች ላይ ገደብ በመጣል ነው ተብሏል፡፡ በዚህም ኩባንያው ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚፈልገው ወሳኝ ክፍል (ኮር) ተብሎ የሚጠራውን አካል እንዳያቀርብ እገዳ ተጥሎበታል፡፡ ሁዋዌ ኩባንያ በብሪታኒያ 35 በመቶ በሚሆነው 5ኛ ትውልድ ኔትወርክ ዝርጋት እንዲሰማራ እንደተፈቀደለት ተነግሯል፡፡ በተጨማሪም ከወታደራዊ ማዕከላት እና ከኒውክሌር ጣቢያዎች አቅራቢያ እቀባ እንደተጣለበት ነው የተገለጸው፡፡ ቤጂንግ ኩባንያው ከታገደ በብሪታኒያ ሌሎች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ ከፍተኛ እርምጃ እንደምትወስድ አስጠንቅቃ ነበር፡ ኩባንያው በበኩሉ ይህ መፈቀዱ ብሪታኒያ የዓለም-መሪ ቴክኖሎጂን ማግኘት እንድትችል እና ተወዳዳሪ የሆነ ገበያ እንዲኖራት ያደርጋል ብለዋል፡፡ አያይዘውም የ5G ልቀትን ለማስቀጠል ከደንበኞቻችን ጋር አብረን መሥራታችን እንደምንቀጥል ለብሪታኒያ መንግስት እናረጋግጣለን ማለታቸው ነው የተነገረው፡፡ ምንጭ፡-ቢ.ቢ.ሲ \n \nጥያቄ: ሁዋዌ የየትኛው እስያዊ ሀገር ድረጅት ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የቻይናው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአዳም ረታ አዳም ረታ ልቦለድና ግጥም በአማርኛ የሚጽፍ ኢትዮጵያዊ ደራሲ ነው። አዳም ረታ በ1950 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ተወለደ። በትምህርት አለም - በጂኦግራፊ የመጀመሪያ ዲግሪውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተቀብሏል። ሁለተኛ (የማስተርስ) ዲግሪውን ደግሞ በውጭ ሀገር አግኝቷል። የሚፅፈው በአብዛኛው ልቦለዶችን ቢሆንም ግጥሞችንም ይፅፋል። በተለያዩ ጊዜያት ግጥሞቹ በተለያዩ መፅሔቶች ላይ ታትመዋል። ያልታተሙ ግጥሞችም አሉት። ከተደራሲው ጋር የተዋወቀበት እና በኢትዮጵያ ስነ ጽሑፍ ተከታታዮችና አንባቢዎች ልብ ውስጥ የመሠረት ድንጋይ ያስቀመጠበት “አባ ደፋር እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች” በኩራዝ አሳታሚ ድርጅት የታተመው በ1977 ዓ.ም ነው። (በዚህ መድብል ውስጥ አራት ስራዎችን አዋጥቷል፡ “ድብድብ”፣ “ዕብዱ ሺበሺ”፣ “ሲሮኮ” እና “ሲፊንክስ”) ሜጋ አሳታሚ ድርጅት በ1990 ዓ.ም ባሳተመው “ጭጋግና ጠል” የአጭር ታሪኮች ስብስብ “ዘላን” የተባለው ልቦለዱ ታትሟል። እነዚህ ሁለቱ ከሌሎች ደራሲዎች ስራዎች ጋር የታተሙለት ስለሆነ እንደ ወጥ ሳይቆጠሩ ነው ከላይ የሰፈረው የተባለው። በ1981 ዓ.ም በኩራዝ አሳታሚ የታተመው “ማህሌት” የደራሲው የመጀመሪያ ወጥ የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ መፅሀፍ ነው። በሻማ ቡክስ በ1997 ዓ.ም የታተመው “ግራጫ ቃጭሎች” እንደ ብሉይ (classic) ሥራ ሊታይ የሚችልና የደራሲው ልዩ ብቃት የታየበት ወጥ ረጅም ልብወለድ ነው። በ2001 ዓ.ም ሁለት ልዩ ስራዎች ይዞ የቀረበው አዳም፡ የአጫጭር ልብወለዶች ስብስብ የሆነው “አለንጋና ምስር” እና እርስ በርሳቸው በቀጭን የታሪክ ክር የሚገናኙ ልብወለዶች (ኖቬላዎች) ያካተተው “እቴሜቴ ሎሚ ሽታ” ለአንባቢያን አበርክቷል። ይህ የአጻጻፍ ስልቱ ሕጽናዊነት የሚባል ሲሆን ደራሲው በሌሎቹ መጻሕፍቱም ውስጥ በስፋት ተጠቅሞበታል፡፡ በቀጠሉት ሦስት ዓመታት በየዓመቱ አንዳንድ መፅሐፍ ለአንባቢያ ያደረሰ ሲሆን በ2002 ዓ.ም “ከሰማይ የወረደ ፍርፍር”፣ በ2003 ዓ.ም “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ” እና በ2004 ዓ.ም “ሕማማት እና በገና” ታትመው ለንባብ በቅተዋል። “ከሰማይ የወረደ ፍርፍር” በተሰኘው መፅሀፉ ድንቅ የፋንታሲ (“ፈንጠዚያ”) ሥራዎች የተካተቱ ሲሆን በ”ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ” ለመጀመሪያ ጊዜ መቼቱን ከሀገር ውጭ በማድረግ የውጭውን ሕይወት በስሱ የዳሰሰ ሲሆን ከሌሎቹ ስራዎቹ በተለየ መልኩ ስለሀገራችን ፖለቲካ ወጣ-ገባ መንገድ በታዛቢ አይን ምልከታው፣ ትውስታውን … አስፍሯል፡፡ ሕማማትና በገና የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ ሲሆን ለየት ያለ ቅርፅ ያላቸው አንዳንድ ልቦለዶች ተካተውበታል። ፍልስፍናውና ስልቱ ሕፅናዊነት በሚል ስያሜው ይፋ ሆኗል። \n \nጥያቄ: “እቴሜቴ ሎሚ ሽታ” በተሰኘው መፅሀፍ ላይ ምን አይነት ያጻጻፍ ስልት ተጠቅሟል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሕጽናዊነት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየጥንቶቹ ሰወች እቃን በቃ በመለዋወጥ መገበያየት ቻሉ። ይህም በማይተዋወቁ ሰወች ዘንድ ነበር። በሚተዋወቁ ግን የስጦታ ልውውጥ ይደረግ ነበር። ቀስ ብሎ የተለያዩ ባህሎች ኮሞዲቲ ገንዘብ መጠቀም ጀመሩ። ከሁሉ አስቀድሞ ከብትና እህል (ገብስ) መደበኛ ነበሩ። በተለይ ዛጎል በብዙ ህብረተሶቦች ዘንድ እንደ መገበባያ ገንዘብ ይጠቅም ነበር። መዳብ፣ ብረት፣ ብርና ወርቅ በክብደት ለመግዣ ቢጠቀሙም፣ ሰዎች ውዱን ብረታብረት ከርካሹ ጋራ ስላቀላቀሉት በአማካኝ ጥረቱ እየቀነሰ ሄደ። በ660 ዓክልበ. ያሕል ጥረቱን እንዲመረምሩ የፈተና ደንጊያ ዕውቀት ስላገኙ ለመጀመሪያ ጊዜ የወርቅ ሳንቲም እና የብር ሳንቲም መጠቀም የጀመሩት ልድያውያን ነበር።. በኢትዮጵያም በአክሱም ነገሥታት የታተሙ የወርቅ ሳንቲሞች ስራ ላይ ውለዋል። ከዚህ ቀጥሎ የተነሳው ተወካይ ገንዘብ የሚባለው ገንዘብ አመጣጡ እንዲህ ነው። ወርቅና ብር ነጋዴወች ለደንበኞቻቸው ደረሰኝ በመጻፍ፣ ያንን ደረሰኝ ደምበኞች በማምጣት በፈለጉት ሰዓት ወርቁንና ብሩን ማግኘት ቻሉ። ቀስ በቀስ ደረሰኙ በወርቁና በብሩ ቦታ ተተክቶ እንደ ሙሉ ገንዘብ መስራት ጀመረ። የወረቀት ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በሶንግ ስርወ መንግስት (970 ዓ.ም. - 1276 ዓ.ም.) ዘመን በቻይና አገር ነበር፣ ብሮቹም ያወዚ ይባሉ ነበር፣ አመጣጣቸውም ከላይ እንደተገለጸው የደረሰኝ ጽሁፈትን ተከትሎ ነው። አውሮጳ ውስጥ የወረቀት ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በ1661፣ ስዊድን አገር ነበር። በዚህ ወቅት እያንዳንዱ ጥሬ የወረቀት ብር ወደ ተወሰነ የወርቅ ክብደት የሚቀየርበት ስሌት ነበረው። ሆኖም ስዊድን የወረቀት ብር ያወጣው ምክንያት ጦርነት ለማድረግ ፈልጎ በቂ ወርቅ ወይም ሌላ ገንዘብ በአገሩ ስላልነበረው ነው። አሁን ወዲያው የስዊድን መንግሥት ፈቃዱን እንዲፈጽሙ ሥራተኖች መክፈል ቻለ። በጥቂት ዓመት ውስት የስዎድን ወረቀት ገንዘብ ወደቀ። ነገር ግን ከትንሽ በኋላ የእንግላንድ መንግሥት በፈረንሣይ ላይ በጦርነት ተይዞ ለጦርነትም ያህል በቂ ሀብት ባለመኖሩ እንዲህ አይነት መፍትሄ መረጡ፤ የኢንግላንድ ፓውንድ ድፍን ጀመሩ። ስለዚህ ከዚህ በኋላ አገራት ፈቃዳቸውን ለመፈጽም አዲስ የወርቅ ወይም የብር ማዕድን ማግነት አስፈላጊ አልነበረም። በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ይህ በወርቅ የተደገፈ የተሰኘው የገንዘብ ስርዓት በይፋ በመላው ዓለም ተንሰራፋ። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በብሬቶን ውድስ ስብሰባ፣ አብዛኞቹ የአለማችን አገሮች ፊያት ገንዘብን በማጽደቅ ገንዘባቸውን በቀጥታ በወርቅ ከመደገፍ ይልቅ ከአሜሪካን ዶላር አንጻር እንዲተረጎም አደረጉ። የአሜሪካን ዶላር በተራው በወርቅ የተደገፈ ነበር። በ1971 የአሜሪካን መንግስት ዶላሩን በወርቅ መደገፍ/መተርጎም አቆመ። ከዚህ በኋላ ሌሎቹም አገሮች የየራሳቸውን ገንዘብ ከአሜሪካን ዶላር አንጻር መተርጎም አቆሙ። በአሁኑ ወቅት አብዛኛው የአለማችን ገንዘቦች በወርቅም ሆነ በሌላ ቋሚ ነገር የሚደገፉ ሳይሆን በየአገሩ ባሉ መንግስታት እንደ ህጋዊ መገበባያ በወጡ አዋጆች ምክንያት ነው። \n \nጥያቄ: አውሮጳ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የወረቀት ገንዘብ ጥቅም ላይ የዋለው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ1661 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኬንያ የኬንያ ሪፐብሊክ በምስራቅ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በሰሜን ከኢትዮጵያ፣ በሰሜን-ምስራቅ ከሶማሊያ፣ በደቡብ ከታንዛኒያ፣ በምስራቅ ከዩጋንዳ፣ በስሜን-ምዕራብ ከደቡብ ሱዳን፣ በደቡብ-ምስራቅ ከሕንድ ውቅያኖስ ጋር ድንበር ትጋራለች። አውሮፓውያን አካባቢውን ማሰስ የጀመሩት ከ፲፱ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ሲሆን የብሪታንያ መንግሥት የምሥራቅ አፍሪካ ፕሮቴክቶሬትን በ1895 እ.ኤ.አ. አቋቁሟል። ይህ ፕሮቴክቶሬት በ1920 እ.ኤ.አ. የኬንያ ግዛት ተብሎ ተሰይሟል። ነፃ የኬንያ ሪፐብሊክ በዲሴምበር 1963 እ.ኤ.አ. ታወጀ። የኬንያ ስም የመጣው በአፍሪካ በከፍታ ሁለተኛ ከሆነው ከደብረ ኬንያ ተራራ ነው። በዚሁ ተራራ ዙሪያ የሚኖሩት ነገዶች ስሙን «ኪኛ» (በካምባኛ)፣ «ኪሪማራ» (በአመሩኛ)፣ «ኪሬኛ» (በኤምቡኛ)፣ «ኪሪኛጋ» (በኪኩዩ)፣ ወይም «ኬሪ» (በመዓሳይኛ) ይሉታል። የነዚህ ስሞች ሁሉ ትርጉሞች «ቡራቡሬ» ሲሆኑ ይህም ደግሞ «ሰጎን» ማለት ነው፤ አመዳይ ያለበት የተራራው ጫፍ ለተመልካች ቡራቡሬ ወንድ ሰጎንን ያሳስባልና። በኦገስት 2010 እ.ኤ.አ. በተካሄደ ውሳኔ ሕዝብ መሠረት ከብሪታንያ የተወረሰው ሕገ መንግሥት በአዲስ ሕገ መንግሥት ተለውጧል። በአሁኑ ጊዜ ኬንያ በ፵፯ ካውንቲዎች (የአስተዳደር ክፍሎች) ተዋቅራለች። እነዚህ ካውንቲዎች በሕዝብ በተመረጡ ሰዎች የሚስተዳደሩ ሲሆን በናይሮቢ ከሚገኘው ማዕከላዊ መንግሥት በነፃነት ይንቀሳቀሳሉ። የኬንያ ዋና ከተማ እና ትልቋ ከተማ ናይሮቢ ናት። የኬንያ ኢኮኖሚ በምሥራቅና መካከለኛው አፍሪቃ በጂ.ዲ.ፒ. ትልቁ ነው። ግብርና በአገሪቱ ትልቅ የሥራ ዘርፍ ሲሆን ከኤክስፖርቶች መካከል ሻይ፣ ቡና እና ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ አበባዎች ይገኛሉ። እንዲሁም ቱሪስምና ፔትሮሊየም አቢይ ዘርፎች ናቸው። \n \nጥያቄ: ኬንያ ስንት የአስተዳደር ክልሎች አሏት?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ፵፯ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየካናዳ ጥንታዊ ኗሪዎች የካናዳ ጥንታዊ ኗሪዎች በካናዳ አገር 1974 ዓ.ም. ሕገ መንግስት ሥር ኢንዲያን (መጀመሪያ አገሮች የተባሉ)፤ ሜቲ (ክልሶች)፤ እና እኑዊት (ወይም ኤስኪሞ) ናቸው። እነዚህ 3 ክፍሎች አንድ ላይ ደግሞ መጀመርያ ሕዝቦች ይባላሉ። በካናዳ በተደረገው 1993 ቆጠራ ዘንድ፣ የጥንታዊ ኗሪዎች ብዛት ከ900,000 በለጠ። በዚህ ቁጥር ውስጥ 600,000 ከመጀመርያ አገሮች ዘር፤ 290,000 ሜቲ፣ እና 45,000 እኑዊት ይከተታሉ። የጥንታዊ ኗሪዎች ማህበራዊ ወኪሎች በካናዳ እንዲህ ናቸው፤ የመጀመርያ አገሮች ስብሰባ ለመጀመርያ አገሮች፤ እኑዊት ታፒሪት ካናታሚ ለእኑዊት፤ የሜቲ ብሔራዊ ጉባኤ ለሜቲ ናቸው። ባለፈው ዐሥር አመት የካናዳ መንግሥት የዘውድ ጉባኤ ስለ ጥንታዊ ኗሪዎች ሰበሰበ። ይህ ጉባኤ ያለፉትን መንግስት ዐቅዶች ስለ ጥንታዊ ኗሪዎች ለምሳሌ የሚሲዮን ተማሪ ቤቶች አመዛዝኖ ብዙ የአቅዋም ምክሮች ለካናዳ መንግስት አቀረበ። ብዙ መጀመርያ አገሮች የሚኖሩት በተከለለ ቦታ ሲሆን፣ ብዙ ኗሪዎች ደግሞ ከቦታዎቹ ውጭ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: በካናዳ በተደረገው የ1993 ዓ.ም ሕዝብ ቆጠራ የካናዳ ጥንታዊ ነዋሪዎች ብዛታቸው ስንት ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 900,000 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nባሕር-ዳር ባሕር-ዳር በድሮ ስሙ ባሕር ዳር ጊዮርጊስ በሰሜን-ምዕራብ ኢትዮጵያ የምትገኝ ከተማ ስትሆን የአማራ ክልል ዋና ከተማ ናት። ከተማዋ በቀድሞው ጎጃም ክፍለ ሓገር ውስጥ ከጣና ሐይቅ ደቡባዊ ጫፍ ላይ ተቀምጣ ስትገኝ ባህር ዳር እንደ መቀሌና ደሴ የወረዳ ደረጃ ያላት ስፔሻል(ልዩ) ዞን ናት። በማዕከላዊ ስታትስቲክ ትመና የ167,261 ህዝብ ከነሱም መሃከል የ86,355 ወንዶችና የ80,906 ሴቶች መኖሪያ ከተማ ናት። 1700 ሜትር ከባሕር ወለል በላይ ትገኛለች። ባሕር-ዳር ከአዲስ አበባ 565 ኪ.ሜ ወደ ሰሜን-ሰሜን ምዕራብ ትገኛለች። ባህር ዳር ከጢስ አባይ በ30 ኪሎሜትር ስለምትርቅ ለጎብኚዎች አመቺ ቦታ ላይ ናት። ባህር ዳር የአንድ የአስፋልት ንጣፍ ያለው ኤርፖርት የሰፊ ገበያና የተለያዩ የመዝናኛ ቦታዎች እና ታሪካዊ እና ጥንታዊ ግዳማት መግኛ ቦታ ናት። ባሕርዳር ከተማ የምትገኘዉ በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍል፣ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት፣ በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ከአዲስ አበባ በ 565 ኪሜ ርቀት ላይ ነው፡፡ አስትሮኖሚያዊ መገኛ ቦታዋ በ 11º 38’ በሰሜን ላቲቲውድ እና በ37º15’ ምስራቅ ሎንግቲውድ ነው፡፡ በአፈ ታሪክ እንደሚነገረው የባሕር-ዳር ስያሜን ያወጡት አፄ ሠርጸ ድንግል ሲሆኑ እሳቸውም ይሕን ታቦት የት እናስቀምጥ ተብለው በተጠየቁ ጊዜ \"ከባሕሩ-ዳር\" አድርጉ የተባሉ ሰወች ለመንደሩ ባሕር-ዳር ብለው ስያሜ አወጡለት ይባላል። ባሕር-ዳር ከተማ የተቆረቆረችው በ1915 ዓ.ም ነው ፡፡ ባሕር-ዳር በክልሉ ከሚገኙ የሪፎርም ከተሞች አንድዋ ስትሆን፤ የከተማ አስተዳደር፣ 3 ሜትሮፖሊታን ክ/ከተማዎች፣ የከተማ አገልግሎት ጽ/ቤት፣ 9 የከተማ ቀበሌዎችና 4 የገጠር ቀበሌዎች አሏት፡፡ ከተማዋ በ1998 ዓ.ም የተቀናጀ ልማት ፕላን አላት፡፡ የተቆረቆረችበትን ዓመት፣ የቆረቆሩትን ቀደምት ሠዎች፣ የሠፈሮችን ስሞች፣ ለባሕር-ዳር የተገጠሙትና የተዘፈኑ ታሪካዊ ግጥሞችና ስነ ቃሎች፣ ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከጎጆ ቤት ወደ አሁኑ ይዞታው አመጣጥ (ባሕር-ዳርን ስናስብ ጊዮርጊስን ሚካኤልን እና ገበያውን ከገበያው አካባቢ የነበረውን ፍርድ ቤት ነጣጥሎ ማየት አይቻልም የሚል አስተያየት ስላለ ነው)፣ ባሕር-ዳር እንደባሕር ዳርነቱ ከመቆርቆሩ በፊት በሚካኤል እና በሽመምብጥ ሠፈር አካባቢ ስለነበረው አሰፋፈር፣ ስለማዘጋጃቤቱ፣ ስለ አውቶቡስ ተራው፣ ስለ ድባነቄ ተራራ፣ እና ስለ መሳሉት፣ ስለፖሊቴክኒክ፣ ስለዓባይ ወንዝና ድልድዩ፣ ስለዓባይ ወንዝና ስለጣና ሐይቅ መገናኛ እና ስለሌሎችም ቁልፍ ነገሮችን ማቅረብ የሚችሉ አፈታሪኮች አሉ። \n \nጥያቄ: ባሕር ዳር ከተማ ከአዲስ አበባ በምን ያህል ርቀት ላይ ትገኛለች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 565 ኪ.ሜ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nመለጋሲ መለጋሲ (Malagasy) ከአውስትሮኔዚያን የቋንቋ ቤተሠብ ቋንቋዎች ሁሉ ምእራበኛው ሲሆን የማዳጋስካር መደበኛ ቋንቋ ነው። 1500-2000 አመታት ከዛሬ በፊት ከእንዶኔዚያ የመጡ የማዳጋስካር ኗሪዎች ቋንቋ በመሆኑ፣ ከቃላቱ መዝገብ 90% ከመቶ በቦርኔዮ እንዶኔዚያ ከተገኘው ቋንቋ ከማአንያን ጋራ ተመሳሳይ ነው። የቀሩትም 10% ቃላት በተለይ ከአፍሪቃ ቋንቋዎች (ከባንቱ) እና ከአረብኛ ተበድረዋል። በአረፍተ ነገር ውስጥ ግሡ ከሁሉ ይቀድማል። ይህ ተራ እንደ ዕብራይስጥ ይመስላል እንጂ ለብዙዎች ቋንቋዎች የተለመደ አይደለም። በየቃሉ ውስጥ ከመጨረሻው ክፍለ-ቃል በፊት የሆነው ክፍለ-ቃል አናባቢ ይጠበቃል፤ ሌሎቹ አናባቢዎችም ይነበነባሉ (በሙሉ አይስሙም)፤ ስለዚህ \"Malagasy\" እንደ ፈረንሳይኛ አጻጻፉ \"Malgache\" (መልጋሽ) ይመስላል። \n \nጥያቄ: የመለጋሲ ቋንቋ 90% የሚሆኑት ቃላት ከየትኛው ቋንቋ ጋር ይመሳሰላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከማአንያን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየትነበርሽ ንጉሴ የትነበርሽ ንጉሴ በኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ እና የአካል ጉዳተኛ መብትቶች ተሟጋች ናት ፡ እ.ኤ.አ በ 2017 \"የአካል ጉዳተኞችን መብቶችን እና ማካተቶችን በማስተዋወቅ እንዲሁም በማኅበረሰቡ ውስጥ ያሉየአእምሮ ውቅርን መለወጥ የሚያበረታታ ሥራዋ\" ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድን ተሸልማለች። የትነበርሽ ንጉሴ የአይን ብርሃኗን ያጣችው በ 5 ዓመቷ ነበር ። ይህ አጋጣሚ በተወለድችበት በአማራ ክልል በስፋት ይተገበር ከነበረው ያለ አድሜ ጋብቻ አንድታመልጥ እድሉን እንደፈጠረላት ትናገራለች። ፡፡የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቷን በሻሸመኔ ካቶሊክ የዓይነ ስውራን ት/ቤት ተከታትላ ወደ ዳግማዊ ምኒልክ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (አካታች ትምህርት ቤት) ገብታ እስከ 12 ኛ ክፍል እዚያ ተማረች። በትምህርት ቤቱ ካላት አካዳሚክ ተሳትፎ በተጨማሪ የተማሪዎችን አማካሪ ጨምሮ ከ 6 በላይ የክለቦችን ክበባት መርታለች ፡፡ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን በመቀላቀል የመጀመሪያ ዲግሪ በሕግ ሁለተኛ ዲግሪ በማኅበራዊ ሥራ አግኝ ታለች፡፡ ከመደበኛ ትምህርት ውጭ በልዩ ልዩ እንቅስቃሴዎች ውስጥ በተከታታይ ትሳተፋለች በዚህም የመኢአድ የፀረ ኤድስ እንቅስቃሴን ከ2004 - 05 በመምራት በ 2006 የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ (አአዩ) ሴት ተማሪዎች ማህበርን በመመስረት እንዲሁም የማህበሩ የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት በመሆን አገልግላለች ፡፡ \n \nጥያቄ: የትነበርሽ ንጉሴ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቷን የት ተከታተለች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በሻሸመኔ ካቶሊክ የዓይነ ስውራን ት/ቤት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ በጥሩ ጎናቸው ከሚነሱ የቅርብ ጊዜያት ተጫዋቾች መካከል አዳነ ግርማ ይገኝበታል።ተጫዋቹ በበርካታ የስፖርቱ ቤተሰቦች ልብ ውስጥ ትልቅ ቦታንም ይዟል።አዳነ ግርማ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን መነቃቃት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ተጫዋቹ በብሄራዊ ቡድኑ ውስጥ ለ10 ዓመታት በመጫወትም አንጋፋ ለመሆን በቅቷል። አዳነ ግርማን ስናስብ ሁለት ጨዋታዎች ሁሌም ከፊታችን ድቅን ይላሉ።ደቡብ አፍሪካ ላስተናገደ ችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በአዲስ አበባ ስታዲየም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡደን ከሱዳን አቻው ጋር ሲጫወት በግንባሩ ገጭቶ ያስቆጠራት ግብ መቼም ቢሆን አዳነ እንዲታወስ ያደረገችም የምታደርግ ናት።ኢትዮጵያ ለደቡብ አፍሪካው የአፍሪካ ዋንጫ እንድታልፍ ያረገችው ወሳኝ ግብም ሆናለች። በአፍሪካ ዋንጫው ከ 39 ዓመታት በኋላ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዛምቢያ ላይ ያስቆጠራት ግብም አዳነን ሁሌም እንድናስበው ያረገች ሌላዋ ግቡ ናት። ተጫዋቹ ከዋልያዎቹ ጋር ለአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጉዞ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳደረገና የቡድኑ ምሰሶ እንደነበርም ይታወቃል።በአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ዘመን አዳነ ቡድኑን በአምበልነት መርቷል። የአትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ከሰውነት ቢሻው የተረከቡት አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ ቡድኑን እንደ አዲስ ሲያዋቅሩ አዳነ ግርማን መቀነሳቸው ሲሰማ በስፖርቱ ቤተሰብ ዘንድ ቅሬታ ቢፈጠርም፣ ተጫዋቹ ግን ውሳኔውን አሜን ብሎ ነው የተቀበለው። በወቅቱም አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ማብራሪያ ለተጫዋቹ መቀነስ ምክንያታቸው ያደረጉት የተጫዋቹ «ብቃትና አቅም ወርዷል» የሚል ነው። ተጫዋቹ ግን በወቅቱ ለአንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን ያረጋገጠው ምንም አይነት የአቋም መዋዠቅም እንደሌለበት ነው። የብቃት መውረድ እንዳላሳየም ገልጿል። የመቀነሱ ሚስጥር ለሱም እንቆቅልሽ እንደሆነበት ነበር ያስታወቀው። ይህን ተከትሎ ራሱን ከብሄራዊ ቡድን ያገለለው አዳነ በአዲሱ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ሰሞኑን ጥሪ ተደርጎለት ነበር:: የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከአልጄሪያ ጋር ላለበት ወሳኝ ጨዋታ በአጥቂ እጥረት ላይ ቢገኝም አዳነ ግርማ ከቤተሰቦቼ ጋር ተመካክሬ የወሰንክይት ውሳኔ ነው በሚል ለብሔራዊ ቡድኑ እንደማይጫወት አስታውቋል:: በ2017 የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በምድብ ሁለት የተደለደለውና በአሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ የሚሰለጥነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከአልጀሪያ አቻው ጋር ላለበት የምድቡ ሶስተኛ እና አራተኛ ጨዋታ 24 ተጫዋቾችን መጥራቱ ይታወሳል። አሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ ሁለት ተጫዋቾችን ከአገር ውጭ ቀሪዎቹን 22 ደግሞ ከአገር ውስጥ ሊጎች የመረጡ ቢሆንም የአዳማ ከነማው አጥቂ ታፈሰ ተስፋዬ ባጋጠመው ጉዳት ከቡድኑ ውጭ ሆኗል። እርሱን ለመተካት ሳልሃዲንና አዳነን ቢጠሩም እምቢ ተብለዋል:: ሆኖም ግን አሰልጣኙ ከቅዱስ ጊዮርጊስ የመረጧቸውን አምስት ተጫዋቾችና ከአገር ውጭ ከሚጫወቱት ሕመልስ በቀለና ጌታነህ ከበደ በስተቀር 15 ተጫዋቾችን ይዘው ልምምዳቸውን ዛሬ ጀምረዋል። \n \nጥያቄ: ለ29ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የኢትዮጵያ የእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ከሱዳን አቻው ጋር የት ባደረገው ጨዋታ ነው አዳነ ግርማ በግንባሩ ገጭቶ ጎል ያስቆጠረው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በአዲስ አበባ ስታዲየም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየአባ ጊዮርጊስ ትምህርታቸው የአባ ጊዮርጊስ አባት ሕዝበ ጽዮን በቤተ መንግሥት በንጉሡ ስዕል ቤት ከሚያገለግሉት ካህናት ጋር ይሠሩ ስለነበር ልጃቸው በመልካም አስተዳደግና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት በማስተማር በዕውቀት አሳድገዋቸዋል። በድቁናም አሹመዋቸዋል። ከዚያም በኋላ በንጉሥ ዳዊት ዘመን (፲፫፻፸፮ ፥ ፲፬፻፭) በደብረ ሐይቅ ባሕር ወደምትገኘው የቅዱስ እስጢፋኖስ አባ እየሱስ ሞዐ ገዳምና ታዋቂ ትምህርት ቤት ወስደው ከታላቁ ዓቃቤ ሰዓት አባ ሠረቀ ብርሃን ጉባዔ ተቀላቅለው እንዲማሩ አድርገዋል ። ይሁን እንጂ አባ ጊዮርጊስ በትምህርት ቤቱ የሚሰጡትን የቀለም ትምህርቶች ቶሎ ለማጥናት አልቻሉም ። ወደ ኋላ የመቅረታቸው ዋናው ምክኒያትም አባ ጊዮርጊስ ከመማሩ ይልቅ የማረካቸው በሥራ እየደከሙ የገዳሙን አባቶች መርዳትና የብትህውናው ሕይወት መሆኑ ነው ። ጉዋደኞቻቸው በትምህርት ሲቀድሙአቸው ባዩ ጊዜ እጅግ አዘኑ ። በጾምና ጸሎትም ወደ እግዚአብሔር ጮሁ በፍፁም ልባቸውም አምነው ብርቱ ልመናን ከእመቤታችን ሥዕል ፊት ቁሞ በጠለቀ ተመስጦልቦና እንባን በማፍሰስ ወደ እግዚአብሔር \" የአባቶቻችን አምላክ የምህረት ጌታ ሁሉን በቃልህ የፈጠርክ ሰውንም በረቂቅ ጥበብህ የፈጠርክ አቤቱ አንተ ከልዑል ጌትነትህ ጥበብን ስጠኝ በእውነትም አትናቀኝ እኔ ባሪያህ ነኝ የባሪያህም ልጅ ነኝና \" በማለት ለመኑ ። ከዚህም በኋላ የዓለም ንግሥት የአምላክ እናት ተገለጸችላቸው ። በነሐሴ ፳፩ ቀንም ወደርሳቸው መጣች ፣ በዕውቀትና በትምህርት የሚተጉበትን ኃይል ሰጠቻቸው ። ከዚያም የዜማ የቅኔና የመጽሐፍትን ትርጉዋሜ ትምህርታቸውን በሚገባ አጠናቀቁ ብዙ መጽሐፍትንም ደረሱ ። በዚህም በቀሰሙት ዕውቀታቸው በዜማ በኩል ከቅዱስ ያሬድ ቀጥለው የሚጠሩ አባ ጊዮርጊስ ናቸው። በቤተመቅደስም ዘማሪ ማኅሌታይ ተብለው ይጠራሉ። በዚያም ዘመን ለነገሥት ፣ ለካህናት ፣ ለመኳንንት ፣ ለንቡራነእድ ፣ ለመሳፍንት ፣ ለሁሉም የቤተመንግሥት ሠራተኞች አስተማሪ ሆኑ ። በአንድ ወቅት ግብፃዊው ጳጳስ አቡነ በርተሎሜዎስ “ሥላሴን አንድ ገጽ” ብለው ያምናሉ ተብለው በተከሰሱ ጊዜነገሩን እንዲያጣሩ ከተመረጡት ከቄስ ሐፄ ተከሥተ ብርሃንና ከሐይቁ መምህር ከዐቃቤ ሰዓት ዮሴፍ ጋር አብሮ ተልኮ ነበር፡፡ እነዚህ ሦስት አበውጳጳሱን ካነጋገሩ በኋላ ክሱ ውሸት መሆኑን በማረጋገጥ ስለ ምሥጢረ ሥላሴ የሚገልጠውን የጳጳሱን እምነት በጽሑፍ ይዘው መጡ፡፡ ሊቅነታቸውን የተረዱት ዓፄ ዳዊት አባ ጊዮርጊስን ወደ ቤተመንግሥታቸው በማስገባት የስምንቱም ልጆቻቸው መምህር አድርገዋቸው ነበር ። ከእነርሱም ውስጥ ቅዱስ የተባለው ንጉሥ ቴዎድሮስ እንዲሁም በተለያዩ ጊዜ የነገሡት ንጉሥ እንድርያስ ፣ ዓፄ ይስሐቅ ፣ ንግሥት እሌኒ እና ዓፄ ዘርአ ያዕቆብ ይገኙበታል። ዐፄ ዳዊት በጋብቻ እንዲዛመዱዋቸው ጥረው ነበር ነገር ግን አባ ጊዮርጊስ ራሳቸውን የመንግሥተ ሰማያት ጃንደረባ ማድረግን ስለመረጡ በማስተማሩና በብሕትናው ጸንተው የአመክሮ ጊዜያቸውን ሲጨርሱ አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ገብተው መንኩሰዋል። \n \nጥያቄ: አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጭ በየት መነኮሱ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዋዝንቢት ዋዝንቢት የሦስት አጽቄ አይነት ነው። የፌንጣና የአንበጣ ዘመድ ነው። ሁለንተናው ትንሽ ለጥ ይላል፤ ረጃጅም አንቴኖችም አሉት። ዋዝንቢት የሚታወቀው በሚያሰማው ድምጽ ነው። ድምጽ ማውጣትና ማሰማት የሚችለው አውራው ዋዝንቢት ብቻ ነው። የተባዕቱ ዋዝንቢት ክንፍ እንደ \"ሚዶና ሞረድ\" የሚመስል ፍርግርግ ነው። ክንፎቹን በማፋተግ ድምጽ ይፈጥራል፤ የድምጹ ቅላፄ እንደየ ዋዝንቢቱ ወገን ይለያያል። ሁለት ዓይነት የዋዝንቢት ዘፈኖች አሉ፤ የጥሪ ዘፈንና የመርቢያ ዘፈን ናቸው። የጥሪ ዘፈን ዓላማ አንስት ዋዝንቢ ለመሳብ ሲሆን ረጅምና ከፍተኛ ድምፅ ነው። ለመራባት ሲባል የሚዘፈነው ድምፅ አንስቲቱ እንስቲቱን ለማቅረብ ስለሆነ ቀስ ያለና ለስላሳ ነው። አንስት ዋዝንቢት መርፌ የሚመስል ረጅም የዕንቁላል መጣያ አላት። በምድር ላይ 900 የሚያሕሉ የዋዝንቢት ዝርያዎች ይገኛሉ። አንዳንድ ዝርያ ሣርና ተክል ብቻ ሲበላ፣ ሌሎች ዝርዮች ደግሞ ነፍሳት ያድናሉ። ዋዝንቢት ሌሊት የሚነቃ ፍጥረት ነው። ብዙ ጊዜ ከፌንጣ ጋር ይመሳሰላል፣ በተለይ የመዝለያ እግሮቹ ከፊንጣ እግሮች አይለዩም። በ1963 ዓ.ም. ዶ/ር ዊሊያም ከይድ ምርመራ አድርጎ አንዲት ተባይ ዝንብ ደግሞ በተባዕቱ ዘፈን እንደምትሳብ፤ ዕጯንም እንድታስቀምጥበት ቦታውን ለማወቅ እንደሚጠቅማት አገኘ። የመርባትን ድምጽ በመጠቀም የአስተናጋጇን ቦታ ለምታገኝ የተፈጥሮ ጠላት ይህች መጀመርያ ምሳሌ ሆነች። ከዚያ በኋላ ብዙ የዋዝንቢት ወገኖች ይህችን ተባይ ዝንብ ሲሸክሙ በምድር ላይ ተገኝተዋል። በእስያ በተላይም በቻይና ዋዝንቢት ዝነኛ ለማዳ እንስሳ ሆኖ መያዙ እንደ መልካም እድል ይቈጠራል። የተያዘ ዋዝንቢት ሁሉ ማናቸውም አትክልት ወይም ሥጋ ቢሰጥ ይበላል። በአንዳንድ ባሕል ደግሞ ዋዝንቢት እንደ ምግብ ሊበላ ይችላል። \n \nጥያቄ: ዋዝንቢት የሚንቀሳቀሰው በየትኛው ክፍለ ቀን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሌሊት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nነሐሴ ፳፯ ነሐሴ ፳፯ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፯ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፱ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፰ ዕለታት ይቀራሉ። ፲፮፻፶፰ ዓ/ም ለሦስት ቀናት የጋየውና አስር ሺህ ሕንጻዎችን ያወደመው የሎንዶን ትልቁ እሳት ተነሳ። ፲፯፻፵፬ ዓ/ም የምዕራብ አውሮፓ አገራት ዘመን አቆጣጠራቸውን በለወጡ በሁለት መቶ ዓመታቸው፣ ብሪታንያ የጎርጎራዊ ዘመን አቆጣጠርን ተቀበለች። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በጠላት ወረራ ዘመን የሸዋ አርበኞች ቡልጋ ላይ ተሰባስበው የልጅ ኢያሱን ልጅ መልአከ-ፀሐይ ኢያሱን አነገሡ። አዲሱ 'ንጉሥ' ወዲያው የአርበኞች መሪ ለነበሩት ባላምባራስ አበበ አረጋይ የራስነት ማዕርግ ሰጠ። መልአከ-ፀሐይ ኢያሱ መስከረም ፳፬ ቀን ፲፱፻፴፩ ዓ/ም አረፎ አንኮበር አካባቢ በሚገኘው ዞማ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተቀብሯል። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ጃፓን በተሸናፊነቷ እጇን ሰጠች። ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ነጻነትን አስከትሎ በጃዋሃርላል ኔህሩ ምክትል ፕሬዚደንትነት የሚመራ የሕንድ ጊዜያዊ መንግሥት ተመሠረተ። ፲፱፻፺ ዓ/ም የርዋንዳን ፍጅት አስከትሎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያቋቋመው የወንጀለኛ ፍርድ ቤት ጃን ፖል አካዬሱ የተባለውን የቀድሞ ከንቲባ ላይ ፍርዱን የወንጀለኛነት ፍርድ ፈረደበት። \n \nጥያቄ: ለሦስት ቀናት የጋየውና አስር ሺህ ሕንጻዎችን ያወደመው የሎንዶን ትልቁ እሳት የተከሰተው በስንት ዓመተ ምህረት ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ፲፮፻፶፰ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nፍሬምናጦስ የተወለዱት ታይር በምትባል ቦታ በምሥራቃዊ የሮማ ነገሥት በ፬ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያዎቹ ሲሆን ማንም መርምሮ ሊደርስበት በማይችለው በእግዚአብሔር ሀሳብ ወደ ኢትዮጵያ መተው ክርስትናን ከመሠረቱት ዋነኛው አባት ሆኖ በመቆጠር ፣ አገራችንን ከሌሎች ክርስቲያን አገሮች ጋር ያስተዋወቁ ፣ ያስተካከሉ ፣ በአክሱም ዘመነ መንግሥትና መንግሥት የተወደዱና የተከበሩ ፣ በመላው ኢትዮጵያ የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች የተከበሩ ታላቅ አባት ናቸው ። አባታችን ፍሬምናጦስ የ፲፪ ዓመት ልጅ እያለ ሜሮጵዮስ የተባለ ነጋዴ ፈላስፋም የነበረ መርከበኛ ይዞት ወደ አገራችን መጣ ። ከእርሱም ጋር ወንድሙ ኤድስዮስ የተባለም አብሮት እንደነበረ ይታወቃል ። እነዚህን ሁለት ወጣቶች አስከትሎ የመጣው ሜሮጵዮስ በቀይ ባሕር አካባቢ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች በጣሉለት አደጋ በዚሁ እንደ ሞተ ታሪክ ይነግረናል ። ይህም በንጉሥ ዒዛና ዘመነ መንግሥት ሆነ ። ፍሬምናጦስና ኤድስዮስ ግን በወቅቱ የአክሱም ንጉሥ የነበረው ንጉሥ ታዜር ጋር አድገዋል ። ንጉሡ በአእምሮ መብሰላቸውን ተመልክቶ ፍሬምናጦስ በጅሮንድ ኤድስዮስም ጋሻ ጃግሬው አድርጎ ሾማቸው ። ከዚያ በኋላ ንጉሥ ታዜር ሲያርፍ ወደ ፈለጉበት እንድሄዱ ነፃ ስለተለቀቁ ኤድስዮስ ወደ አገሩ ተመልሶ ሄዷል ። አባታችን አቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ግን ወንድሙን ሸኝቶ \"በጨለማ የሚኖረውን ሕዝብ ትቼ ወደ አገሬ አልመለስም\" በማለት የኢትዮጵያን ሕዝብ በማፍቀር እንደቀረ ታሪክ ያስረዳናል ። የቅዱሳን ፍቅራቸው እውነትም ልብ ይነካል ። በዚያን ዘመን በአገራችን ኢትዮጵያ ክርስትና ነገሥታቱ የታወቀ ቢሆንምኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ስርዓተ ንስሐ ፣ ስርዓተ ጥምቀት ፣ ስርዓተ ቅዳሴ ፣ ስርዓተ ቅዱስ ቁርባን የሚያከናውን ጳጳስ ስላልነበረ ይህን የተመለከቱ ነገስታት ኢዛናና ሳይዛና ጵጵስና እንዲያመጣ አባታችን አቡነ ሰላማን ወደ ግብጽ ላኩት ። አባታችንም ወደ ግብጽ በመሄድ ስርዓቶቹን በመማር በቅዱስ አትናትዮስ አንብሮተ እድ \"ኤጲስ ቆጶስ ዘአክሱም ወዘኩላ ኢትዮጵያ\" ተብሎ ጵጵስና ተቀበለ። \n \nጥያቄ: አባ ፍሬምናጦስ ወንድም ማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ኤድስዮስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nፍልስፍና ፍልስፍና የሚለው ቃል ከግሪኩ ፊሎስ ማለትም ፍቅር እና፣ ሶፎስ (ጥበብ) የተገኘ ውሁድ ነው። በቀጥታው የጥበብ ፍቅር ወይም ፍቅረ ጥበብ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል። በመሆኑም ፍልስፍና እውቀትን፣ እውነትን፣ ጥበብን መውደድ፣ መሻት፣ መመርመር ተብሎ ሊተረጎም ይችላል። ባንድ በኩል ወደ ጥበብ የተሳበ፣ ጥበብን የወደደ እንደዚሁም የጥበብ ባለሟልን የሚያመለክት ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ጥበብን ወዶ ሌላውም እንዲወድ ምክንያት የሚሆን ለማለት ይውላል። ይህ የጥናት ክፍል በዋናነት ነገሮችን በመላምታዊ መንገድ ለመመርመር ይሞክራል። ፍልስፍና የሚመረምራችው አምስት ዋነኛ ቁምነገሮች ህላዌ፣ ግብረገብ፣ እውቀት፣ እውነት፣ እና ውበት ናቸው። ፈላስፋዎችን ለብዙ ዘመናት ሲያስጨንቁ ከቆዩ ጥያቄዎች ውስጥ እውነት ምንድር ነው? አንድን አስተያየት ለምንና እንዴት እውነት ወይም ሃሰት መሆኑን እናውቃለን? ጥበብስ ምንድር ናት? አዋቂነት የሚቻል ነገር ነውን? ማወቃችንን እንዴት እናውቃለን? አዋቂነት የሚቻል ነገር ከሆነ የታወቀ እና ያልታወቀ ማለት ምንድር ነው? ከታወቀው ያልታወቀውን እንዴት መሻት እንችላለን? ግብረገብ በሆነው እና ባልሆነው መካከል ልዩነት አለን? ካለስ ልዩነቱ ምንድር ነው? የትኞቹ ድርጊቶቻችን ናቸው ልክ? ልክ ያልሆኑትስ የትኞቹ ናቸው? ሥነምግባራዊ መስፈርቶች ቋሚ ናቸው ወይስ ተነፃፃሪ? እንዴትስ መኖን አለብኝ? ገሃድ የሆነው ምንድር ነው? የገሃድ ነገሮች ተፈጥሮአቸው እንዴት ያለ ነው? እውን አንዳንድ ነገሮች ከኛ ግንዛቤ ውጭ መኖር ይቻላቸዋልን? ውበት ምንድር ነው? ውብ የሆኑ ነገሮች ከሌሎቹ በምን ይለያሉ? ሥነጥበብ ምንድር ነች? ሃቀኛ ውበት የገኛልን? የሚሉት ናቸው። እነዚህ ከላይ በደፈናው የተጠቀሱ ጥያቄዎች እንደ ቅደም ተከተላቸው አመክንዮአዊ፣ ሥነ-እውቀታዊ፣ ሥነ-ምግባራዊ፣ ሥነ-ኃልዮአዊ፣ እና ሥነ-ውበትአዊ በመባል ይታወቃሉ። ምንም እንኳን እነዚህ ዋነኞቹ ጥያቄዎች ይሁኑ እንጂ ብቸኞቹ አይደሉም። በተጨማሪም በመካከላቸው አንዳንድ መደራረብ ይታያል። ታዋቂው የግሪክ ፈላስፋ አሪስጣጣሊስ ሥነ-መንግሥት፣ ሥነ-ተፈጥሮ፣ ሥነ-ምድር፣ ሥነ፡ሕይወት፣ ሥነ-አየር እና ሥነ ፈለክ የፍልስፍና ክፍሎች ናቸው ብሎ ያምን ነበር። \n \nጥያቄ: ፍልስፍና የሚመረምረው ስንት ዋነኛ ነገሮችን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አምስት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኮንታ የኮንታ ብሔረሰብ የአፍ መፍቻ ቋንቋ ኮንቲኛ ሲሆን፣ ከ1990 ዓ.ም ጀምሮ ከንግግር ቋንቋነት ባሻገር የትምህርትና የሥራ ቋንቋ በመሆን አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። አብዛኛው የብሔረሰቡ አባላት ከአፍ መፍቻ ቋንቋቸው በተጨማሪ ዳውሮኛ፣ ጋሞኛ፣ ወላይትኛና አማርኛ ይናገራሉ። የኮንታ ብሔረሰብ ባህላዊ አስተዳደር መዋቅር ተዋረዳዊ ኃላፊነትና ተግባር ባላቸው የተለያዩ ክፍሎች የተደራጀ ነው፡፡ በእዚህ መዋቅር የሁሉም የበላይ ካዎ ወይም ንጉስ በመባል የሚታወቅ ሲሆን ከማላ ጎሳ ይመረጣል፡፡ በኮንታ ብሔረሰብ ስድስት ባህላዊ የጋብቻ ዓይነቶች ያሉ ሲሆን፣ እነዚህም በቤተሰብ ስምምነት የሚፈጸም ጋብቻ (ቦሣ) የለፋ ጋብቻ (ላታ) በተጋቢዎች ስምምነት የሚፈጸም ጋብቻ (ማቆ) የቃል ጋብቻ (ያኤኤኩዎ) እና ሚሽቶ (የምትክ ጋብቻ) በመባል ይታወቃሉ፡፡ ከእነዚህ የጋብቻ ዓይነቶች በብዛት ሲከናወን የሚስተዋለው በቤተሰብ ስምምነት የሚፈጸመው የቦሣ ጋብቻ ነው፡፡ ከብሔረሰቡ ባህላዊ የሙዚቃ መሣሪያዎች ፂፄ፣ ጫቻ፣ ዛይ፣ዲንኬ እና ኡልዱዶ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ እነዚህ የትንፋሽና የምት የሙዚቃ መሣሪያዎች ለለቅሶና ለደስታ ጊዜ ያገለግላሉ፡፡ በተለይ ኡላዱዶ የተሰኘው የትንፋሽ መሣሪያ ከድኩላ ቀንድ ተበስቶ የሚሠራ ሲሆን ከብቶቻቸው ሆራ (ጨውነት ያለው ውሃ) ሊያጠጡ የሚወስዱ እረኞች ይነፉታል፡፡ የኮንታ ባህላዊ የቤት አሠራር ከፍልጥ እንጨት፣ ከቀርከሀ ከሰንበሌጥና ከሣር የሚዘጋጅ ሲሆን በደጋውና በቆላው አካባቢ ልዩነት አለው፡፡ ሱልሶ፣ ሲሊሶ፣ ኡስታ፣ ጨዲያ፣ ኩበዋ፣ ቦሩዋ (ዱቢያ) እና ባጨራ የኮንታ ብሔረሰብ ዋነኛ ባህላዊ ምግቦች ናቸው፡፡ ሲልሶ ለአብነት ከምን እንደሚሠራ እንይ፡፡ ሲልሶ ከጥሬ ሥጋ፣ ከቅቤ፣ ከደም፣ ከሀሞት እና ከተለያዩ የማጣፈጫ ቅመሞች ከተዘጋጀ በኋላ ከተለበለበና በክብ በተቆረጠ የእንሰት ቅጠል ላይ ለቤተሰቡ አባላት ይቀርብና በቡላ ወይም በቆጮ ይበላል፡፡ በብሔረሰቡ ወንዶች ከአቡጀዲ በእጅ የተሰፋ እጀ ጠባብ ሸሚዝና ሱሪ እንዲሁም ሀሲያ የተባለ በእጅ የተፈተለ ልብስ ሲለብሱ ሴቶች በኋላ በኩል ባለወጥ ጥለት የሆነውን ማዳ የተባለ የእጅ ፈትል ይለብሳሉ፡፡ \n \nጥያቄ: የኮንታ ብሔረሰብ የሙዚቃ መሣሪያዎች ለምን አገልግሎት ይውላሉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ለለቅሶና ለደስታ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \n67ኛው ግጥም በጃዝ ምሽት የፊታችን ረቡዕ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በራስ ሆቴል ይካሄዳል፡፡ አንጋፎቹ ገጣሚያን ነቢይ መኮንን፣ ተፈሪ አለሙ፣ ዶ/ር ሙሉአለም ተገኝወርቅ፣ መርድ ተስፋዬና ቤዛ ትዕዛዙ የግጥም ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን አርቲስት ሽመልስ አበራና እታፈራሁ መብራቱ አጭር ተውኔት ያቀርባሉ ተብሏል፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ምሁር የሆኑት አቶ አበባው አያሌው ዲስኩር እንደሚያቀርቡ ታውቋል፡፡ \n \nጥያቄ: አቶ አበባው አያሌው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የምን መምህር ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የታሪክ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nመስከረም 23/12 ዓ ም ሽሬ ኢዜአ የተለያዩ የፈጠራ ውጤቶችን ለተጠቃሚዎች በማቅረብ ይሁንታ ያገኘው የ35 ዓመት ወጣት ሔሊኮፕተር ሰርቶ ለሙከራ እየተዘጋጀ መሆኑን አስታወቀ ። ወጣት ዕበ ለገሰ ይባላል ። በመደበኛ ትምህርት ብዙ ገፍቶ ባይሔድም በፈጣራ ብቃቱ ግን በርካታ ስራዎች ለህዝብ እንዲያደርስ አድርጎታል ። የ10ኛ ክፍል ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ በኤሌክትሪክ ሃይል የሚሰራ ምጣድ ጥገና ሥራ የጀመረው ወጣት አሁን ላይ ትልቅ ራእይ አንግቦ የራሱ የሆኑ የፈጠራ ስራዎችን በማቅረብ ውጤታማነቱን በተጠቃሚዎች ዘንድ እየተመሰከረለት መጥቷል ። የምጣድ ጥገና ስራው ለታናሽ ወንድሙ በመልቀቅ የወርቅ መአድን መፈለጊያ መሳሪያ ወደ ማሻሻል መሸጋገሩን ይገልፃል ። በራሱ ፈጠራ ያሻሻለው የወርቅ መፈለጊያ መሳሪያ በባህላዊ መንገድ ወርቅ ለሚያመርቱ ሰዎች በሽያጭ በማቅረብ የፍለጋ ሥራቸውን እንዲቃለል እንዳስቻላቸው ተጠቃሚዎቹ ይናገራሉ ። ቀደም ሲል የነበረው ‘’ጂ አር ዜድ’’ የተባለው የወርቅ መፈለጊያ መሳሪያ ከ70 እስከ 80 ሳንቲ ሜትር ጥልቀት ባለው መሬት ውስጥ የሚገኝ የደለል ወርቅ የሚጠቁም ነበር ። ወጣቱ ያሻሸለው ግን በአንድ ሜትር ጥልቀት የሚገኘውን የደለል ወርቅ በቀላሉ መለየት የሚያስችል መሳርያ ሆኖ ተገኝቷል ። እንዲሁም ከድንጋይ ጋር ተደባልቆ የሚገኝ ወርቅ በቀላሉ መለየት የሚያስችል የድንጋይ ወፍጮ በመፍጠር ለተጠቃሚዎቹ በማቅረብ ላይ እንደሚገኝም ወጣት ለገሰ ይናገራል ። ባለፉት አምስት ዓመታት አምስት የድንጋይ ወፍጮዎችን በመስራት ለተጣቀሚዎቹ በተመጣጣኝ ዋጋ አቅርቧል ። በተጠናቀቀው ዓመት በራሱ ፈጠራ ሶስት ሰዎች የማሳፈር አቅም ያለት ሔሊኮፕተር ሰርቶ በሙከራ ደረጃ ለህዝብ እይታ አቅርቦ የነበረው ወጣቱ ዘንድሮ ለማብረር እየተዘጋጀ መሆኑንም ተናግሯል ። የፈጠራ ሥራዬ ስኬትና ሚስጥር “ይቻላል” የሚል ጽኑ እምነት ስላለኝ ነው የሚለው ወጣቱ ከኢንተርኔት የሚያገኛቸው የፈጠራ ሥራዎችም እገዛ እንዳደረጉለት ጠቁሟል። ሥራ ፈጣሪ ወጣቱ ወደ ገበያ በሚያቀርባቸው የፈጠራ ውጤቱ ጥሩ ገቢ ከማግኘቱም ባሻገር ለሌሎች 10 ወጣቶች የስራ እድል መፍጠሩን ተናግሯል። የወጣቱ የፈጠራ ወጤት ተጠቃሚ ከሆኑትና በባህላዊ መንገድ በደለል ወርቅ ምርት ፍለጋ ከተሰማሩ ማህበራት መካከል የ“ስምረት” ማህበር አንዱ ነው። የማህበሩ አባል የሆነው ወጣት በላይ ተክለሃይማኖት በሰጠው አስተያየት ” ከወጣቱ የገዛነው የደለል ወርቅ ጠቋሚ መሳርያ ሥራችንን ከማቃለል በተጨማሪ በወርቅ ፍለጋው ስኬታማ እንድንሆን አግዞናል” ብሏል። ሌላው የማህበሩ አባል ወጣት ተስፋይ በላይ በበኩሉ ” ከድንጋይ ጋር ተደባልቆ የሚገኝ ወርቅ ለመለየት እጅግ አድካሚ የነበረው ሥራ ወጣቱ ባቀረበልን አነስተኛ የድንጋይ ወፍጮ በመጠቀም የድካማችንን ዋጋ ማግኘት አስችሎናል ” በማለት አድናቆቱን ገልፆለታል ። የሽሬ እንዳስላሴ ከተማ የወጣቶችና ስፖርት ጉዳይ ጽህፈት ቤት ምክትል ሃላፊ አቶ ጎይቶኦም ይሰማ እንዳሉትም ደግሞ የወጣቱን የፈጠራ ክህሎት እንዲሰፋና ሄሊኮፕተሯ ለህዝብ እይታ እንድትበቃ አስፈላጊውን ድጋፍ ይደረግለታል ። የሽሬ እንደስላሴ ፖሊ ቴክኒክና ኮሌጅ ዲን አቶ ፀጋይ ገብረሚካኤል በበኩላቸው የፈጠራ ባለቤት የሆነው ወጣት እበ ለገሰ የፈጠራ ስራዎች የሚያተኩሩት በአካባቢው ህብረተሰብ ላይ በሚታዩ መሰረታዊ ችግሮች ዙሪያ በመሆናቸው ተቀባይነታቸው የጎላ ነው ብለዋል ። ወጣቱ የሚያሳየው ትጋት የተሞላበት የፈጠራ ስራ ለሌሎች ወጣቶችም አርአያ በመሆን መነቃቃት መፍጠሩን የኮሌጁ ዲን መስክረውለታል ። \n \nጥያቄ: የሽሬ እንደስላሴ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጉዳይ ጽ/ቤት ም/ኃላፊ ማን ይባላሉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ አቶ ጎይቶኦም ይሰማ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሴኔጋል ሴኔጋል ወይም የሴኔጋል ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። ሴኔጋል ከምዕራብ በሴኔጋል ወንዝ፣ ከሰሜን በሞሪታንያ፣ ክምሥራቅ በማሊ እና ክደቡብ በጊኒና ጊኒ-ቢሳው ይዋሰናል። የጋምቢያ ግዛት እንዳለ በሴኔጋል ውስጥ ነው የሚገኘው። የሴኔጋል የቆዳ ስፋት 197,000 ካሬ ኪ.ሜ. የሚጠጋ ሲሆን የሕዝብ ብዛቱ ደግሞ ወደ 14 ሚሊዮን እንደሆነ ይገመታል። የሴኔጋል የአየር ሁኔታ የየምድር ወገብ ሲሆን ደረቅና ዝናባማ ወራት ተብሎ ወደ ሁለት ይከፈላል። የሴኔጋል ርዕሰ ከተማ ዳካር በሀገሩ የምዕራብ ጫፍ በካፕ-ቨርት ልሳነ ምድር ላይ ይገኛል። ከባህር ጠረፍ ወደ ፭፻ ኪ.ሜ. ገደማ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የኬፕ ቨርድ ደሴቶች ይገኛሉ። በ፲፯ኛው ና ፲፰ኛው ክፍለ ዘመናት በቅኝ ገዢ መንግሥታት የተሠሩ የንግድ ተቋማት ከባህር ዳር ይገኛሉ። በአካባቢው ያሉ ግኝቶች ሴኔጋል ከጥንት ጀምሮ የሚኖርበት እንደነበረ ያሳያሉ። እስልምና የአካባቢው ዋና ሀይማኖት ሲሆን ወደ ሴኔጋል የተዋወቀውም በ11ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን እንደሆነ ይታመናል። በ13ኛውና 14ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን የማንዲንጎ ግዛት በአካባቢው ላይ ተጽኖ ያደርግ ነበር። በዚሁም ጊዜ ነው የጆሎፍ ግዛት የተመሠረተው። በ15ኛው ክፍለ-ዘመን ፖርቱጋል፣ ኔዘርላንድስ እና ኢንግላንድ በአካባቢው ለመነገድ ይወዳደሩ ነበር። በ1677 እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ጎሪ የሚባለውን ዋና የባሪያ ንግድ ደሴት ተቆጣጠረች። ከዛም በ1850ዎቹ እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ቁጥጥሩዋን ወደ መላው ሴኔጋል ማስፋፋት ጀመረች። \n \nጥያቄ: ሴኔጋል በምስራቅ አቅጣጫ በማን ትዋሰናለች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በማሊ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቢል ክሊንተን ያደጉት በሆት ስፕሪንግስ፣ አርካንሳው ነው። የቢል ክሊንተን አባት ዊሊያም ጄፈርሰን ብላይዝ ጁኚየር፣ ቢል ክሊንተን ከመወለዱ ሶስት ወር በፊት በመኪና አደጋ ሞተዋል። የቢል ክሊንተን እናት ቨርጂኒያ ክሊንተን ኬሊ፣ በ1950 እ.ኤ.ኣ. ሮጀር ክሊንተን የሚባል ሰዉ አገባች። 14 ዓመቱ ሲሆን ቢል ክሊንተን የመጨረሻ ስሙን ወደ ክሊንተን ለወጠ። ክሊንተን በጆርጅታውን ዩኒቨርሲቲ፥ ዋሽንግተን ዲ.ሲ.፣ ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ፥ ኢንግላንድ፣ እና ዬል ዩኒቨርሲቲ፥ ኮነቲኬት ተምረዋል። በ1975 እ.ኤ.ኣ. ሂለሪ ሮድሃምን አገቡና በሊትል ሮክ፥ አርካንሳው መኖር ጀመሩ። ከዚያም በዩኒቨርሲቴ ኦፍ አርካንሳው የሕግ ፐሮፌሰር ሆነው አገልግለዋል። ቢል ክሊንተን የአርካንሳው አስተዳዳሪ ሆኖ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመረጡት በ1978 እ.ኤ.ኣ. ነው። በዛ ጊዜ ከአሜሪካ በዕድሜ ትንሹ አስተዳዳሪ ነበሩ። በ1980 እ.ኤ.ኣ. በፍራንክ ዲ ዋይት ከተሸነፉ በኋላ በ1982 እ.ኤ.ኣ. እንደገና ተመረጡ። ከዛ ጀምሮ እስከ 1992 እ.ኤ.ኣ. ድረስ ለአራት ጊዜ አስተዳዳሪ ሆነው መርተዋል። በ1984 እ.ኤ.ኣ. የአስተዳዳሪ የስልጣን ዕድሜ ከ2 ዓመት ወደ 4 ዓመት አራዝመዋል። በ1992 እ.ኤ.ኣ. ለፕሬዝዳንትነት ተወዳድርው አሸንፈዋል። በ1996 እንደገና ተወዳድረው አሸንፈዋል። \n \nጥያቄ: ቢል ክሊንተን ለአርካንሳው አስተዳዳሪነት በ1982 እ.ኤ.አ. ድጋሚ ካሸነፉ በኋላ በአስተዳዳሪነት እስከ መቼ ቆዩ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 1992 እ.ኤ.ኣ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nጾመ ነቢያት በአራቱም ዘመናት ምን ጊዜም ኅዳር ዐሥራ አምስት እንዲጾም ተወስኗል፡፡ ጾመ ገሀድ የምትክ ጾም ነው፡፡ ይህ ጾም ዓርብንና ሮብን የሚያሽር በዓል በዓርብና በሮብ ሲውል በምትኩ በዋዜማው የሚጾም ጾም ነው፡፡ ለምሳሌ ጥምቀት ዓርብ ቢውል ሐሙስ ጾመ ገሀድ ይሆናል፡፡ ነገር ግን አበው ለጾም ማድላት አለብን በማለት ጾመ ገሀድ ምንጊዜም ጥምቀት በጾም ቀን ዋለም አልዋለም በዋዜማው እንዲጾም ወስነዋል፡፡ ጾመ ፍልሰታ ሐዋርያት የእመቤታችንን ትንሣኤ ለማየት ይበቁ ዘንድ ሱባኤ ገብተው የጾሙት ጾም ሲሆን ምንጊዜም ነሐሴ አንድ ቀን ገብቶ ከሁለት ሱባኤ በኋላ የእመቤታችን ዕርገት ይፈጸማል፡፡ \n \nጥያቄ: ጾመ ፍልሰታ ከምን ያህል ጊዜ በኋላ ይፈታል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከሁለት ሱባኤ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአዶልፍ ሂትለር አዶልፍ ሂትለር (ጀርመንኛ Adolf Hitler አዶልፍ ሂትለ) እ.አ.አ. ከ1933 ጀምሮ የጀርመን ቻንስለር እንዲሁም ከ1934 ጀምሮ ደግሞ የጀርመን መሪም (Führer) ጭምር የነበረ ሰው ነው። ሂትለር በሚያዝያ 13 ቀን 1881 ዓ.ም. (20 አፕሪይል 1889 እ.ኤ.አ.) በዛሬይቷ ኦስትሪያ ተወለደ። በሚያዝያ 22 ቀን 1937 ዓ.ም. (30 አፕሪይል 1945 እ.ኤ.አ.) በርሊን ውስጥ ከአንድ ቀን በፊት ካገባት ሚስቱ ኤቫ ብራውን ጋር የራሱን ህይወት አጠፋ። በ1925 ዓ.ም. መጀመርያ የሂትለር ናዚ ወገን ከጓደኞቹ ወገን ጋር በራይክስታግ ምክር ቤት ትብብር መንግሥት ለመሥራት በቂ መንበሮች አልነበራቸውም። ተቃራኒዎቻቸው የኰሙኒስት ወገን 17% መንበሮች ስለ ነበራቸው የሂትለር ወገኖች የድምጽ ብዛት ሊያገኙ አልተቻላቸውም ነበር። በዚያው ዓመት ግን ከምርጫው ትንሽ በፊት የራይክስታግ ሕንጻ በእሳት ተቃጠለ። ይህ የኰሙኒስቶች ሥራ ነው ብለው የሂትለር ወገን ኰሙኒስት ፓርቲ ቶሎ እንዲከለከል አደረጉ። ስለዚህ ከምርጫው በኋላ የኰሙኒስትን መንበሮች ስለ አጡ የሂትለርም ወገኖች አሁን ከ50% መንበሮች በላይ ስላገኙ፣ የትብብር መንግሥት ሠሩና ወዲያው በድንጋጌ አቶ ሂትለር ባለሙሉ ሥልጣን አደረጉት። ሂትለር የጻፈው የርዮተ አለሙ ጽሑፍ «የኔ ትግል» (Mein Kampf) ሟርት ብቻ ነው። ለመጥቀስ ያህል፦ «ትኩረቴ ወደ አይሁዶች ስለ ተሳበ፣ ቪየናን ከበፊት በሌላ ብርሃን ለማየት ጀመርኩ። በሄድኩበት ሁሉ አይሁዶችን አየሁዋቸው፤ በብዛትም እያየኋቸው፣ ከሌሎች ሰዎች ፈጽሞ እንድለያቸው ጀመርኩ።»... «የግዛቱ (ኦስትሪያ-ሀንጋሪ) ዋና ከተማ የከሠተውን የዘሮች ውሑድ ጠላሁት፤ የዚህን ሁሉ የቼኮች፣ ፖሎች፣ ሀንጋርዮች፣ ሩጤኖች፣ ሰርቦች፣ ክሮዋቶች ወዘተ. የዘሮች ድብልቀት፤ በሁላቸውም መካከል፣ እንደ ሰው ልጅ መከፋፈል ሻገቶ፣ አይሁዶችና ተጨማሪ አይሁዶች።» በነበረው ዘረኛ አስተዳደሩ 6 ሚሊዮን የአውሮፓ አይሁዶችን እና 5 ሚሊዮን ሌሎች የተለያዩ ሀገራት ህዝቦችን (በተለይም ስላቮችን) በገፍ (በሆሎኮስት) አስጨርሷል። በሂትለር ሥር የናዚዎች ፍልስፍና በሂንዱኢዝም እንደሚገኘው በዘር የተከፋፈለ ካስት ሲስተም መመሥረት አይነተኛ ነበር። «አርያኖች» የተባሉት ዘሮች በተለይም የጀርመናውያን ብሔሮች ከሁሉ ላዕላይነት እንዲገኙ አሠቡ። ይህ ዝብረት የተነሣ በርግ ቬዳ ዘንድ በ1500 ዓክልበ. ያህል ወደ ሕንድ የወረሩት ነገዶች «አርያን» ስለ ተባሉ ነው፤ በጥንትም «አሪያና» የአፍጋኒስታን አካባቢ ስም የዘመናዊው ኢራንም ሞክሼ ነበር። በናዚዎቹ እንደ ተዛበው ግን ታሪካዊ ባይሆንም የ«አርያኖች» ትርጓሜ ጀርመናውያን ብቻ ነበሩ፤ ስላቮች (በተለይ የሩስያና የፖሎኝ ሕዝቦች) ግን አርያኖች ሳይሆኑ እንደ ዝቅተኞች ተቆጠሩ። የሂትለር እብደት እየተራመደ በ1926 ዓም የሀንጋሪ ሕዝብ ደግሞ «አርያኖች» ተደረጉ፣ በ1928 ዓም የጃፓን ሕዝብ እንኳን በይፋ «አርያኖች» ተደረጉ፤ በ1934 ዓም የፊንላንድ ሕዝብ ወደ «አርያኖች» በሂትለር ዐዋጅ ተጨመሩ። በሙሶሊኒ ሥር የፋሺስት ጣልያኖች እኛም አርያኖች ነን ቢሉም ጣልያኖች አርያን መሆናቸው በናዚዎች ዘንድ መቸም አልተቀበለም ነበር። \n \nጥያቄ: አዶልፍ ሂትለር የራሱንና የመጨረሻ ባለቤቱን ሕይወት ያጠፋው የት ከተማ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በርሊን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየማይዳሰሱ (ኢንታንጀብል) ባህላዊ ቅርሶችን የሚመለከተው የዩኔስኮ አካል በይነ መንግሥታዊው ኮሚቴ 10ኛ ስብሰባውን ከኅዳር 20 እስከ ኅዳር 24 ቀን 2008 ዓ.ም. በናሚቢያ መዲና ዊንድሆክ በተደረገው 10ኛ የዩኔስኮ ጉባዔ ለውሳኔ ከቀረቡት 35 (ሠላሳ አምስት) ባሕላዊ ቅርሶች መካከል የሲዳማ ብሔር የአዲስ ዓመት ዘመን መለወጫ የሆነው ፍቼ ጫምባላላ በዓል በሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ የ2003 የኢንታጀብል ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃ ዓለም አቀፍ ስምምነት መስፈርቶችን አሟልቶ በመገኘቱ አባል አገሮች ውይይት ካደረጉበት በኋላ ፍቼ ጫምባላላ ተመዝግቧል፡፡ ይህም ከመስቀል በዓል ቀጥሎ የኢትዮጵያ ሁለተኛው የማይዳሰስ ዓለም አቀፍ የሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ሆኖ ሕዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም በአገሩ ሰዓት አቆጣጠር 9፡40 በፋይል ቁጥር (01054) በውሳኔ ቁጥር 10.com.10.b.16 ተመዝግቧል፡፡ በ2004 በጀት ዓመት የመስቀል በዓል አከባበርን በዩኔስኮ ማስመዝገብ የሚያስችል የጥናት ሰነድ ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ የተላከ ሲሆን በአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ ከህዳር 23-28 ቀን 2006 ዓ.ም በተካሄደው 8ኛው የዩኔስኮ የኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃ የኢንተርገቨርንመንታል ኮሚቴ መደበኛ ጉባዔ ውሳኔ መሰረት የመስቀል በዓል አከባበር በዩኔስኮ የሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ተካቷል፡፡ በ2006 የበጀት ዓመት የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው ፊቼ ጫምበላላን በሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ለማስመዝገብ የሚያስችል የጥናት ሰነድ (ኖሚኔሽን ፋይል) ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ የተላከውና ህዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም የተመዘገበው የተደረገው ፊቼ ጫምበላላ ሰነዶች በሚከተለው የዩኔስኮ ድረ ገጽ ላይ ለመላው ዓለም ተለቀው ይገኛል፡፡ በተመሳሳይም በ2007 የበጀት ዓመት ኦሮሞ ህዝብ የማንነት መገለጫ የሆነው የገዳ ስርዓትን በሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ለማካተት የሚያስችል የኖሚኔሽን ሰነድ ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ መጋቢት 2007 ዓ.ም ተልኳል፡፡ \n \nጥያቄ: የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው ፍቼ ጨምበላላ ለማስመዝገብ የተሰራው ጥንታዊ ሰነድ መቼ ወደ ዩኔስኮ ተላከ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ህዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዓጼ ኃይለ ሥላሴ ዘውድ እንደጫኑ የአገሪቱን የመጀመሪያ ሕገ-መንግሥት እንዲዘጋጅ አዝዘው በዘውዱ አንደኛ ዓመት በዓል ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፬ ዓ.ም. በአዲሱ ምክር ቤት (ፓርላማ) ለሕዝብ ቀረበ። ከዚህም በላይ ብዙ የቴክኖዎሎጂ ስራዎችና መሻሻያዎች ወደ ኢትዮጵያ ከውጭ አገር አስገቡ። በ፲፱፻፳፰ ዓ.ም. የሙሶሊኒ ፋሺስት ሠራዊት ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ጃንሆይ ሕዝባቸውን ወራሪውን በሙሉ ለመቃወም እንዳስነሡና የከተት ዐዋጆቻቸው በታሪክ ገጾች ይዘገባሉ። በዐዋጅ መሠረት የዘመቻው ጊዜ እስቲያልቅ ድረስ ለሚታግሉ ነጋዶች ከቀረጥ አስተስርየት ሰጣቸው። እራሳቸው በቆራጥነት ከታገሉ በኋላ የጠላቱ ጦር ኅይል ግን በመጨረሻ ወደ እንግሊዝ አገር ለጊዜው አሰደዳቸው። ወደ ጄኔቭ ስዊስ ወደ ዓለም መንግሥታት ማኅበር ሄደው ስለ ጣልያኖች የዓለምን እርዳታ በመጠየቅ ተናገሩ። የዓለም መንግሥታት ግን ብዙ አላደረጉም። በ፲፱፻፴፪ ዓ.ም. ግን አውሮፓ ሁሉ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ተያዘ። የእንግሊዝ ሠራዊቶች ለኢትዮጵያ አርበኞች እርዳታ በመስጠት ጣልያኖች ተሸንፈው በ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. ኢትዮጵያን ተዉ። ዓፄ ኃይለ ሥላሴ አዲስ አበባን እንደገና የገቡበት ቀን ከወጡበት ቀን በልኩ ዕለት አምስት ዓመት በኋላ ነበረ። ከዚህ በኋላ በ1948 ዓ.ም. ተሻሽሎ የወጣ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት የሕዝቦችን መብቶችና ተከፋይነት በመንግሥት አስፋፍቶ ሁለቱ ምክር ቤቶች እንደመረጡ አደረገ። በ፲፱፻፶፭ ዓ.ም. ግርማዊነታቸው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በአዲስ አበባ እንዲመሠረት ብዙ ድጋፍ ሰጡ። በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. ወደ ካሪቢያን ጉብኝት አድርገው የጃማይካ ራስታዎች ተገኛኙ። በ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. በማርክሲስት አብዮት ደርግ ሥልጣን ያዙና እሳቸው በእሥር ቤት ታሰሩ። በሚከተለው ዓመት ከተፈጥሮ ጠንቅ እንደ አረፉ አሉ ፤ ሆኖም ለምን እንደ ሞቱ ስለሚለው ጥያቄ ትንሽ ክርክር አለ። ብዙ ራስታዎች ደግሞ አሁን እንደሚኖሩ ይላሉ። የዓፄ ኃይለ ሥላሴ የትውልድ ስም ልጅ ተፈሪ መኮንን ነው። ስመ-መንግሥታቸው ግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ነበር። ሞዓ አንበሣ ዘእምነገደ ይሁዳ ሥዩመ እግዚአብሔር ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ የሚለው የሰሎሞናዊ ሥረወ-መንግሥት ነገሥታት መጠሪያም በንጉሠ-ነገሥቱ አርማ እና ሌሎች ይፋዊ ጽሑፎች ላይ ከመደበኛው ማዕረግ ጋር ይጠቀስ ነበር። ጃንሆይ ፣ ታላቁ መሪ እና አባ ጠቅል በመባልም ይታወቁ ነበር። \n \nጥያቄ: የጣልያን ፋሺስት ጦር ኢትዮጵያን በ፲፱፻፳፰ ሲወር ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ለተባበሩት መንግሥታት አባል ሀገራት አቤቱታ ያቀረቡት የት ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ጄኔቭ ስዊስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኮንግ-ፉጸ ኮንግ-ፉጸ ወይም ኮንፉክዩስ 558-487 ዓክልበ. የኖረ ቻይናዊ ፋላስፋ ነበረ። ፍልስፍናውና ትምህርቱ «የኮንግፉጸ ትምህርት» በተለይ በቻይና፣ በኮርያ፣ በጃፓንና በቬትናም አገር ባህሎች ላይ ጥልቅ ያለ ተጽእኖ አሳድሮዋል። በእርሱ ፍልስፍና፣ የግለሰብና የመንግሥት ግብረገብ፣ የኅብረተሠባዊ ግንኙነቶች ትክከለኛነት፣ የወላጆች ክብር፣ ፍርድና ቅንነት ልዩ ትኩረት አገኙ። ኮንግ-ፉጸ በሉ ክፍላገር የተወለደ ሲሆን፣ በክፍላገሩ ውስጥ የፖለቲካ ሰው ነበር። በ509 ዓክልበ. የአንድ ከተማ ከንቲባ ከመሆኑ በኋላ፤ የክፍላገሩ ወንጀል ሚኒስትር ሆነ። ነገር ግን በፖለቲካ ረገድ በሙሉ ስኬታማ አልነበረም። ከክፍላገሩ ሦስት ታላላቅ ኃይለኛ ቤተሠቦች ወገኖች፣ ሁለቱ አምባዎቻቸው እንዲፈርሱ በመጨረሻ ተስማሙ፣ እንጂ ሦስተኛው እምቢ ብሎ ለኮንግ-ፉጸ እቅድ አልተከናወነለትም። ስለዚህ በ505 ዓክልበ. ኮንግ-ፉጸ ከሉ ክፍላገር ሸሽቶ ለጊዜው በስደት ኖረ። ከዚያ እስከ 491 ዓክልበ. ድረስ ወደየክፍላገሩ ቤተ መንግሥት ጎብኝቶ የፖለቲካ ፍልስፍናውን ያስተምር ነበር፤ ሆኖም ሁላቸው ምክሩን ስላላስገቡ ይህ ደግሞ በጣም ስኬታም አልነበረም። በ491 ዓክልበ. ወደ ሉ በክብር ተመልሶ ከዚያ እስከ ዕረፍቱ ድረስ ወይም ለ4 ዓመታት ዕውቀቱን ለ77 ደቃ መዛሙርት (ተማሪዎች) ያስተምር ነበር። ከኮንግፉጸ ሕይወት በኋላ ትምህርቶቹ ተከታይነት አገኙ፤ በ148 ዓክልበ. የሃን ሥርወ መንግሥት የኮንግ-ፉጸ ትምህርት ይፋዊ አደረጉት። ወደ ማዕረግ ለመሾም ዕጩዎቹ በዚህ እምነት መጻሕፍት ይፈተኑ ነበር። ከ212 እስከ 1360 ዓም ድረስ ግን ልዩ ልዩ የቻይና ግዛቶች ዳዊስም ወይም ቡዲስም የመንግሥት ሃይማኖት አድርገው ነበር። እንደገና 1360-1903 ዓም ዘመናዊው የኮንግፉጸ ትምሕርት በቻይና ይፋዊ ሆነ። በዳዊስም ሃይማኖት ዘንድ፣ የእምነቱ መሥራች ላው ድዙ በ539 ዓክልበ. ያሕል ዳው ዴ ቺንግ እንደ ጻፈ፣ እንዲሁም አንዴ ከኮንግ-ፉጸ ጋራ እንደ ተገናኙ ይታመናል። በዘመናዊ ዳዊስም በኩል፣ ላው ድዙና ኮንግ-ፉጸ ሁለቱ እንደ አማልክት ይከብራሉ። በተለይ በፓኪስታን የሚታወቅ ከእስልምና የወጣ ክፍልፋይ አሕማዲያ እስልምና እንዳለው፣ ኮንግ-ፉጸ እና ላው ድዙ ሁለቱ የአላህ ነቢዮች ነበሩ። \n \nጥያቄ: ኮንግ-ፋጸ በየትኛዎቹ አገራት እና ባህሎች ላይ ተጽእኖ አድርጋል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በቻይና፣ በኮርያ፣ በጃፓንና በቬትናም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nለአጽዋማትና በዓላት ማውጫ ወሳኝ የሆነው ነጥብ መባጃ ሐመር ነው፡፡ መባጃ ሐመር መባጊያ ሐመር እየተባለም ይጠራል፡፡ መባጊያ ሐመር ሲሆን የበጋ መመላለሻ የሚል ትርጉም ይሰጣል፡፡ በሌላ በኩል መባጃ በራሱ ማቆያ፣ ማክረሚያ ተብሎ ይተረጎማል፡፡ ሐመር መርከብ፣ መጓጓዣ የሚለውን ትርጉም ያስገኛል፡፡ መባጃ ሐመር የመጥቅዕና የዕለታት ተውሳክ ድምር ሆኖ አጽዋማትና በዓላት የሚውሉበትን ቀን ያመለክታል፡፡ በሐመር የተመሰለውም አጽዋማትና በዓላት ወደ ላይና ወደታች የሚመላለሱበት ሥርዓት /መርከብ/ ስለሆነ ነው፡፡ በአጠቃላይ መባጃ ሐመር ማለት የአጽዋማትንና የበዓላትን መዋያ ወይም መግቢያ ቀን ለማወቅ የሚያገለግል ልዩ ቁጥር ማለት ነው፡፡ ከሰባቱ አጽዋማት መካከል አራቱ በመባጃ ሐመር መሠረት በየዓመቱ እየተቀያየሩ ወይም ቀመር እየተሠራላቸው የሚወጡ ሲሆን፣ ሦስቱ ግን ያለ መባጃ ሐመር በየዓመቱ በተመሳሳይ ወቅት ይባጃሉ፡፡ በመባጃ ሐመር የሚባጁት አራት አጽዋማት ዐቢይ ጾም፣ ጾመ ድኅነት፣ ጾመ ነነዌና ጾመ ሐዋርያት ሲሆኑ፣ ያለ ማባጃ ሐመር በየዓመቱ ቋሚ ጊዜ ይዘው የሚብቱት ሦስቱ አጽዋማት ደግሞ ጾመ ነቢያት፣ ጾመ ገሃድና ጾመ ማርያም /ፍልሰታ/ ናቸው፡፡ ከላይ በተመለከትነው መሠረት መባጃ ሐመር የአጽዋማትና የበዓላት ማስገኛ ልዩ ቁጥር ነው ካልን ቁጥሩ እንዴት እንደሚገኝ ማወቅ ያስፈልገናል፡፡ መባጃ ሐመርን ለማግኘት መጥቅዕንና በዓለ መጥቅዕ የዋለበትን ዕለት ተውሳክ እንደምራለን፡፡ \n \nጥያቄ: መባጃ ሐመር ማለት ምን ማለት ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የአጽዋማትንና የበዓላትን መዋያ ወይም መግቢያ ቀን ለማወቅ የሚያገለግል ልዩ ቁጥር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጋና ጋና በአፍሪካ አትላንቲክ ጠረፍ ላይ የተገኘ አገር ሲሆን ከ24 ሚሊዮን ኗሪዎች በላይ አሉት። የጋና ስራ ቋንቋ እንግሊዝኛ ሲሆን፣ ሌሎች ኗሪ ቋንቋዎች በተለይም ትዊኛ (አካንኛ) በሰፊ ይነገራሉ። የ«ጋና» ስያሜ በታሪክ የድሮ «ጋና መንግሥት» ወይም «ዋጋዱጉ መንግሥት» ለማክበር በ1949 ዓም ተመረጠ። እንዲያውም ያው መንግሥት እስከ 1068 ዓም ድረስ ከጋና ወደ ስሜን-ምዕራብ በአሁኑ ማሊ ይገኝ ነበር እንጂ የዛሬውን ጋና መቸም አልገዛም። «ጋና» በትክክል የዋጋዱጉ መንግሥት አለቆች ማዕረግ ሆኖ ነበር። ዋጋዱጉ መንግሥት በ1068 ዓም ግድም ከወደቀ ቀጥሎ፣ የአካን ብሔሮች ከዚያው ፈልሰው በዛሬው ጋና ሠፈሩና መጀመርያ ግዛቶችን መሠረቱ። ከ1662 እስከ 1949 ዓም ድረስ የአሻንቲ መንግሥት ባካባቢው ቆየ፤ በ1894 ዓም ይህ የብሪታንያ አሻንቲ ጥብቅ ግዛት ሆነ። ከ1949 ዓም አስቀድሞ የዩናይትድ ኪንግደም ጥገኛ ግዛት ሲሆን በወርቅ ሀብቱ ምክንያት «የወርቅ ጠረፍ ጥገኛ ግዛት» (ጎልድ ኮስት ፕሮቴክቶሬት) በመባል ይታወቅ ነበር። ከ1984 ዓም ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ እና ፓርላሜንታዊ መንግሥት ኖሮታል። አብዛኞቹ ኗሪዎች (70%) በተለይ በደቡቡ ክርስቲያን ሲሆኑ፣ በተለይ በስሜኑ 16% የእስልምና ተከታዮች ናቸው። የተረፉትም የኗሪ አረመኔነትን እምነቶች ይከተላሉ። የጋና ዋና ምርቶች ካካዎ፣ ዘይት፣ አልማዝ ናቸው። በአለሙ ከሁሉ ትልቅ የሆነው ሠው ሰራሽ ሐይቅ፣ ቮልታ ሐይቅ፣ በጋና ይገኛል። እግር ኳስ ከሁሉ የተወደደው እስፖርት ነው። የጋና አበሳሰል በተለይ በኮቤ፣ ጐርጠብ፣ የስኳር ድንች፣ ባቄላ፣ በቆሎ፣ ኦቾሎኒ፣ ባሚያና ሩዝ ይሠራል። \n \nጥያቄ: ቮልታ ሐይቅ የት ይገኛል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በጋና ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአዶልፍ ሂትለር አዶልፍ ሂትለር (ጀርመንኛ Adolf Hitler አዶልፍ ሂትለ) እ.አ.አ. ከ1933 ጀምሮ የጀርመን ቻንስለር እንዲሁም ከ1934 ጀምሮ ደግሞ የጀርመን መሪም (Führer) ጭምር የነበረ ሰው ነው። ሂትለር በሚያዝያ 13 ቀን 1881 ዓ.ም. (20 አፕሪይል 1889 እ.ኤ.አ.) በዛሬይቷ ኦስትሪያ ተወለደ። በሚያዝያ 22 ቀን 1937 ዓ.ም. (30 አፕሪይል 1945 እ.ኤ.አ.) በርሊን ውስጥ ከአንድ ቀን በፊት ካገባት ሚስቱ ኤቫ ብራውን ጋር የራሱን ህይወት አጠፋ። በ1925 ዓ.ም. መጀመርያ የሂትለር ናዚ ወገን ከጓደኞቹ ወገን ጋር በራይክስታግ ምክር ቤት ትብብር መንግሥት ለመሥራት በቂ መንበሮች አልነበራቸውም። ተቃራኒዎቻቸው የኰሙኒስት ወገን 17% መንበሮች ስለ ነበራቸው የሂትለር ወገኖች የድምጽ ብዛት ሊያገኙ አልተቻላቸውም ነበር። በዚያው ዓመት ግን ከምርጫው ትንሽ በፊት የራይክስታግ ሕንጻ በእሳት ተቃጠለ። ይህ የኰሙኒስቶች ሥራ ነው ብለው የሂትለር ወገን ኰሙኒስት ፓርቲ ቶሎ እንዲከለከል አደረጉ። ስለዚህ ከምርጫው በኋላ የኰሙኒስትን መንበሮች ስለ አጡ የሂትለርም ወገኖች አሁን ከ50% መንበሮች በላይ ስላገኙ፣ የትብብር መንግሥት ሠሩና ወዲያው በድንጋጌ አቶ ሂትለር ባለሙሉ ሥልጣን አደረጉት። ሂትለር የጻፈው የርዮተ አለሙ ጽሑፍ «የኔ ትግል» (Mein Kampf) ሟርት ብቻ ነው። ለመጥቀስ ያህል፦ «ትኩረቴ ወደ አይሁዶች ስለ ተሳበ፣ ቪየናን ከበፊት በሌላ ብርሃን ለማየት ጀመርኩ። በሄድኩበት ሁሉ አይሁዶችን አየሁዋቸው፤ በብዛትም እያየኋቸው፣ ከሌሎች ሰዎች ፈጽሞ እንድለያቸው ጀመርኩ።»... «የግዛቱ (ኦስትሪያ-ሀንጋሪ) ዋና ከተማ የከሠተውን የዘሮች ውሑድ ጠላሁት፤ የዚህን ሁሉ የቼኮች፣ ፖሎች፣ ሀንጋርዮች፣ ሩጤኖች፣ ሰርቦች፣ ክሮዋቶች ወዘተ. የዘሮች ድብልቀት፤ በሁላቸውም መካከል፣ እንደ ሰው ልጅ መከፋፈል ሻገቶ፣ አይሁዶችና ተጨማሪ አይሁዶች።» በነበረው ዘረኛ አስተዳደሩ 6 ሚሊዮን የአውሮፓ አይሁዶችን እና 5 ሚሊዮን ሌሎች የተለያዩ ሀገራት ህዝቦችን (በተለይም ስላቮችን) በገፍ (በሆሎኮስት) አስጨርሷል። በሂትለር ሥር የናዚዎች ፍልስፍና በሂንዱኢዝም እንደሚገኘው በዘር የተከፋፈለ ካስት ሲስተም መመሥረት አይነተኛ ነበር። «አርያኖች» የተባሉት ዘሮች በተለይም የጀርመናውያን ብሔሮች ከሁሉ ላዕላይነት እንዲገኙ አሠቡ። ይህ ዝብረት የተነሣ በርግ ቬዳ ዘንድ በ1500 ዓክልበ. ያህል ወደ ሕንድ የወረሩት ነገዶች «አርያን» ስለ ተባሉ ነው፤ በጥንትም «አሪያና» የአፍጋኒስታን አካባቢ ስም የዘመናዊው ኢራንም ሞክሼ ነበር። በናዚዎቹ እንደ ተዛበው ግን ታሪካዊ ባይሆንም የ«አርያኖች» ትርጓሜ ጀርመናውያን ብቻ ነበሩ፤ ስላቮች (በተለይ የሩስያና የፖሎኝ ሕዝቦች) ግን አርያኖች ሳይሆኑ እንደ ዝቅተኞች ተቆጠሩ። የሂትለር እብደት እየተራመደ በ1926 ዓም የሀንጋሪ ሕዝብ ደግሞ «አርያኖች» ተደረጉ፣ በ1928 ዓም የጃፓን ሕዝብ እንኳን በይፋ «አርያኖች» ተደረጉ፤ በ1934 ዓም የፊንላንድ ሕዝብ ወደ «አርያኖች» በሂትለር ዐዋጅ ተጨመሩ። በሙሶሊኒ ሥር የፋሺስት ጣልያኖች እኛም አርያኖች ነን ቢሉም ጣልያኖች አርያን መሆናቸው በናዚዎች ዘንድ መቸም አልተቀበለም ነበር። \n \nጥያቄ: በአዶልፍ ሂትለር መንግሥት በ1928 ዓም የማን ሕዝቦች ናቸው የአርያኖች ዘር የተደረጉት?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የጃፓን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዓጼ ኃይለ ሥላሴ ዘውድ እንደጫኑ የአገሪቱን የመጀመሪያ ሕገ-መንግሥት እንዲዘጋጅ አዝዘው በዘውዱ አንደኛ ዓመት በዓል ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፬ ዓ.ም. በአዲሱ ምክር ቤት (ፓርላማ) ለሕዝብ ቀረበ። ከዚህም በላይ ብዙ የቴክኖዎሎጂ ስራዎችና መሻሻያዎች ወደ ኢትዮጵያ ከውጭ አገር አስገቡ። በ፲፱፻፳፰ ዓ.ም. የሙሶሊኒ ፋሺስት ሠራዊት ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ጃንሆይ ሕዝባቸውን ወራሪውን በሙሉ ለመቃወም እንዳስነሡና የከተት ዐዋጆቻቸው በታሪክ ገጾች ይዘገባሉ። በዐዋጅ መሠረት የዘመቻው ጊዜ እስቲያልቅ ድረስ ለሚታግሉ ነጋዶች ከቀረጥ አስተስርየት ሰጣቸው። እራሳቸው በቆራጥነት ከታገሉ በኋላ የጠላቱ ጦር ኅይል ግን በመጨረሻ ወደ እንግሊዝ አገር ለጊዜው አሰደዳቸው። ወደ ጄኔቭ ስዊስ ወደ ዓለም መንግሥታት ማኅበር ሄደው ስለ ጣልያኖች የዓለምን እርዳታ በመጠየቅ ተናገሩ። የዓለም መንግሥታት ግን ብዙ አላደረጉም። በ፲፱፻፴፪ ዓ.ም. ግን አውሮፓ ሁሉ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ተያዘ። የእንግሊዝ ሠራዊቶች ለኢትዮጵያ አርበኞች እርዳታ በመስጠት ጣልያኖች ተሸንፈው በ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. ኢትዮጵያን ተዉ። ዓፄ ኃይለ ሥላሴ አዲስ አበባን እንደገና የገቡበት ቀን ከወጡበት ቀን በልኩ ዕለት አምስት ዓመት በኋላ ነበረ። ከዚህ በኋላ በ1948 ዓ.ም. ተሻሽሎ የወጣ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት የሕዝቦችን መብቶችና ተከፋይነት በመንግሥት አስፋፍቶ ሁለቱ ምክር ቤቶች እንደመረጡ አደረገ። በ፲፱፻፶፭ ዓ.ም. ግርማዊነታቸው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በአዲስ አበባ እንዲመሠረት ብዙ ድጋፍ ሰጡ። በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. ወደ ካሪቢያን ጉብኝት አድርገው የጃማይካ ራስታዎች ተገኛኙ። በ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. በማርክሲስት አብዮት ደርግ ሥልጣን ያዙና እሳቸው በእሥር ቤት ታሰሩ። በሚከተለው ዓመት ከተፈጥሮ ጠንቅ እንደ አረፉ አሉ ፤ ሆኖም ለምን እንደ ሞቱ ስለሚለው ጥያቄ ትንሽ ክርክር አለ። ብዙ ራስታዎች ደግሞ አሁን እንደሚኖሩ ይላሉ። የዓፄ ኃይለ ሥላሴ የትውልድ ስም ልጅ ተፈሪ መኮንን ነው። ስመ-መንግሥታቸው ግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ነበር። ሞዓ አንበሣ ዘእምነገደ ይሁዳ ሥዩመ እግዚአብሔር ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ የሚለው የሰሎሞናዊ ሥረወ-መንግሥት ነገሥታት መጠሪያም በንጉሠ-ነገሥቱ አርማ እና ሌሎች ይፋዊ ጽሑፎች ላይ ከመደበኛው ማዕረግ ጋር ይጠቀስ ነበር። ጃንሆይ ፣ ታላቁ መሪ እና አባ ጠቅል በመባልም ይታወቁ ነበር። \n \nጥያቄ: የጃንሆይ ኃይለ ሥላሴ የትውልድ መጠሪያ ስም ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ልጅ ተፈሪ መኮንን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኒሺ ፍሬደሪክ ዊልሄልም ኒትሸ (ኦክቶበር 15, 1844 - ኦገስት 25, 1900) ጀርመናዊ ጻህፊና ፈላስፋ ሲሆን አለምን ይቀይራሉ ብሎ ያመነባቸውን ብዙ መጻህፍት በመድረስ ይታወቃል። እርግጥ ኒሺ፣ በነበረበትም ሆነ በኋላ ዘመኑ ብዙ ተቃዋሚወች ቢነሱበትም በዚያው ልክ ብዙ ሰወች ስራወቹን እንደ ታላቅ የፍልስፍና እና ስነ ጽሁፍ ስራ ይወስዷቸዋል። ኒትሸ አብዛኛው ጽሁፉ የሚያተኩረው ሰወች እንዴት ሊኖሩ ይገባቸዋል? በሚለው ጥያቄ ነው። በዚህ ምክንያት እሱ ይኖርበት የነበረውን ዘመን የጀርመን ሥነ ምግባር (ኤቲክስ) በመንቀፍ ብዙ ጽፎአል። ሠናይ እና እኩይ (ጥሩና መጥፎ) ተብለው ተለይተው ይሰራባቸው የነበሩትን የጊዜውን ሥነ ምግባር ዋጋወች በመተቸት ሰወች አዲስ ሥነ ምግባር ፈጥረው ለሁሉም ምግባር አዲስ የሠናይነትና እኩይነት (ጥሩ እና መጥፎ) ዋጋ እንዲሰጡ በጽሑፎቹ ብዙ ሞክሯል።በዚህ መሰረት፣ ለምሳሌ፣ በክርስቲያኖች ዘንድ የሚሰራበትን ለደካሞች ማዘንን ሠናይነት ተቃውሟል። በሱ አስተያየት ደካሞች ሲታዘንላቸው የበለጠ ይዳከማሉ የሚል ነው ምክንያቱም በሱ አስተያየት ደካሞቹ በጠንካሮቹ ላይ የበለጠ ጥገኛ በመሆን መላው ህብረተሰብ ይዳከማል የሚል ነው። በተጨማሪም፣ የሰው ልጅ የሚኖርበትን ተጨባጩን አለም መገንዘብ እና ክሁሉ በላይ ስለዚሁ ዓለም ማተኮር አለበት ብሏል። ሰማይና ሌሎች አለማትን በማጣጣል፣ የሰው ልጅ እነዚህን አይነት አለሞች የሚፈጥረው አሁን ያለበትን ተጨባጩ የውኑ አለም ችግሮች መፍታት ሲያቅተው ለመፈርጠጥ ነው በማለት የሰው ልጅ ስለዚህ ምድር ብቻ እንዲያስብ ይወተውታል። ኒሽ የሰው ልጅ እራሱን በራሱ ማሸነፍ እንዲችል አጥብቆ ያምናል። በኒሺ ፍልስፍና፣ አንድ እራሱን ያሽነፈ ሰው በጣም የተለወጠ እና የተሻለ ስለሚሆን \"ሱፐር ማን\" ወይም \"የበላይ ሰው\" እንዲባል ሰይሟል። የበላይ ሰው እንግዴህ ጠንካራና በሌሎች ሰወች \"ሠናይ\" እና \"እኩይ\" ወይም ደግሞ \"ጥሩ\" ና \"መጥፎ\" ዋጋወች የማይመራ፣ ይልቁኑ የራሱን ሥነ ምግባር የሚፈጥር ነው። \n \nጥያቄ: ፍሬደሪክ ዊልሄልም ኒትሸ ከመቼ እስከ መቼ ኖረ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ኦክቶበር 15, 1844 - ኦገስት 25, 1900 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጎንደር ከተማ ፋሲለደስ የጎንደር ከተማን በ1636 የኢትዮጵያም ዋና ከተማ አድርጎ እንደቆረቆራት ይታመናል። ከሱ በፊት በአካባቢው ከተማ እንደነበር ወይም እንዳልነበር በታሪክ የተገኘ ማስርጃ እስካሁን የለም። አከታትሎም የፋሲል ግቢንና 44ቱ ታቦታት ተብለው የሚታወቁትን የጎንደር ከተማ አብያተ ክርስቲያናት መሰረት ጣለ። በአፄ ፋሲል ከተመሰረቱት ታዋቂወቹ 44 አብያተ ክርስቲያናት፣ ታዋቂወቹ አደባባይ እየሱስ፣ አደባባይ ተክለ ሃይማኖት፣ አጣጣሚ ሚካኤል፣ ግምጃቤት ማራያም፣ ፊት ሚካኤል፣ እና ፊት አቦ ይገኙበታል። ያለመታከትም 7 የድንጋይ ድልድዮችን በማሰራት እስካሁን ድረስ ስሙ ሲጠራ ይኖራል። አልፎም በግራኝ አህመድ ዘመን በእሳት ጋይቶ የነበረችውን አክሱም ፂዮን በአዲስ መሰረት እንደገና ማሰራት ችሎአል። ፋሲለደስ በዘመኑ እጅግ ተወዳጅ ንጉስ ቢሆንም አመጽ መነሳቱ አልቀረም። በላስታ ለምሳሌ በ1637 መልክዓ ክርስቶስ በተባለ ሰው መሪነት ጦርነት ተነስቶ አፄ ፋሲልን ስጋት ላይ ቢጥልም በሚቀጥለው አመት በተደረገው ጦርነት አመፁ ሊገታ ችሎአል። ፋሲለደስ ፖርቱጋሎችን ቢያባርርም ከውጭው አለም ጋር ብዙ ግንኙነት ያደርግ ነበር። ለምሳሌ በ1664-5 የህንድ ንጉስ አውራንግዘብ ሲነግስ መልካም ምኞትን በመልክተኞቹ ለሙግሃሉ መሪ ልኮ ነበር። በ1666 ልጁ ዳዊት ሲያምጽ፣ ወህኒ ተብሎ ወደሚታወቀው አገር በግዞት ልኮት ነበር። ይህም ከጥንቶቹ የኢትዮጵያውን ነገሥት ተፎካካሪያቸውን ወደ አምባ ግሽን በግዞት እንደሚልኩት ስርዓት ነበር። \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ ነገስታት ተፎካካሪያቸውን ወደ የትኛው ግዞት ቤት እንዲሄዱ ነበር የሚያደርጉት?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ወደ አምባ ግሽን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nራስ መኮንን ልዑል ራስ መኮንን ወልደሚካኤል የሸዋ ንጉሥ የነበሩት የሣህለ ሥላሴ ልጅ የልዕልት ተናኘወርቅ እና የደጃዝማች ወልደሚካኤል ልጅ ናቸው። ግንቦት ፩ ቀን ፲፰፻፵፬ ዓ.ም ጎላ ወረዳ ደረፎ ማርያም በሚባል ሥፍራ ተወልደው፤ እስከ ፲፬ ዓመት ዕድሜያቸው ከአባታቸው ጋር ከኖሩ በኋላ ያጐታቸው የንጉሥ ኃይለ መለኮት ልጅ ዳግማዊ ምኒልክ ገና የሸዋ ንጉሥ እንደነበሩ፡ ወደርሳቸው ቤተ መንግሥት መጥተው፡ ባለሟል ሆኑ። በ፲፰፻፷፰ ዓ.ም ዕድሜያቸው ሀያ አራት ዓመት ሲሆን ከወይዘሮ የሺ እመቤት ጋር ተጋብተው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም የወደፊቱን ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ወለዱ። \n \nጥያቄ: የልዕልት ተናኘወርቅ አባታቸው የየት ክፍለ ሀገር ንጉሥ ነበሩ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የሸዋ ንጉሥ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኢትዮጵያ ET-Smart-RSS የተባለች ሳተላይት ማምጠቋን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ETRSS-1 የተባለች የመጀመሪያዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት ታኅሣሥ ወር 2012 ዓ.ም ማምጠቋ ይታወሳል። ባለፈው አመት የመጠቀችው “ETRSS-1” የሚል ስያሜ የተሰጣት ምድርን እየቃኘች ፎቶ እየመዘገበች መረጃ የምትሰበስበው ሳተላይት በሀገራችን የዕድገት ጉዞ ላይ ቁልፍ ሚና እንደሚኖራት መነገሩ አይዘነጋም። መረጃ መላክ የጀመረችው ይች ሳተላይት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቆጣጠር፣ ከግብርና ጋር የተያያዙ ጥናት እና ምርምሮችን ለመሥራት እና ሌሎች ዘርፈ ብዙ የመሠረተ ልማት ተግባራትን በማከናወን ላይ ትገኛለች። ኢትዮጵያ አሁን ደግሞ ET-Smart-RSS የተባለች ሳተላይት ማምጠቋን ነው ኢንስቲትዩቱ ያስታወቀው። \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ የመጀመሪያው የመሬት ምልክታ ሳተላይቷን መቼ አመጠቀች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ታኅሣሥ ወር 2012 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአልጄሪያ አልጄሪያ (አረብኛ፦ الجزائر‎ አል ጃዝኤር; በርበርኛ፦ ድዜየር) በይፋ የአልጄሪያ ሕዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በሰሜን አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። ከቆሳ ስፋት አኳያ በሜዲቴራንያን ባህር ዙሪያ ትልቋ ስትሆን፣ ከአፍሪካ ደግሞ ከሱዳን በኋላ ሁለተኛ ናት። አልጄሪያ ከሰሜን ምሥራቅ በቱኒዚያ፣ ከምሥራቅ በሊቢያ፣ ከምዕራብ በሞሮኮ፣ ከደቡብ ምዕራብ በምዕራባዊ ሣህራ፣ ሞሪታኒያና ማሊ፣ ከደቡብ ምሥራቅ በኒጄር፣ ከሰሜን በሜዲቴራንያን ባህር ትዋሰናለች። ዋና ከተማዋ አልጂርዝ ሲሆን የ፳፻፫ ዓ.ም. ሕዝብ ብዛቷ ወደ 35.7 ሚሊዮን ይገመታል። አልጄሪያ የተባበሩት መንግሥታት፣ የአፍሪካ ሕብረት፣ ኦፔክ እና ሌሎችም ዓለም አቀፍ ድርጅቶች አባል ሀገር ናት። የሀገሯ ስም የመጣው ከአልጂርዝ ከተማ ሲሆን በድሮ ጊዜ ከዛሬዎቹ ምዕራብ ቱኒዚያና ምሥራቅ ሞርኮ አብራ ኑሚዲያ ትባል ነበር። በጥንት ጊዜ አልጄሪያ የኑሚዲያ መንግሥት ትባል የነበረ ሲሆን ነዋሪዎቿ ደግሞ ኑሚዲያውያን ይባሉ ነበር። የኑሚዲያ መንግሥት ከካርታጎ፣ ሮማና ጥንታዊ ግሪክ ጋር ግንኙነት ነበራት። አካባቢው ለምለም እንደነበረ ሲነገር ኑሚዲያውያን ደግሞ ለኃይለኛ ፈረሰኛ ጦራቸው ይታወቁ ነበር። \n \nጥያቄ: አልጄርያ በአፍሪካ በየትኛው አቅጣጫ ትገኛለች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በሰሜን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nላይቤሪያ ላይቤሪያ (እንግሊዝኛ፦ Liberia)፣ በይፋ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ፦ Republic of Liberia)፣ በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በጊኒ፣ ኮት ዲቯር፣ ሴራሊዮን እና በአትላንቲክ ውቅያኖስ ትዋሰናለች። ላይቤሪያ የቅኝ ግዛት ሆና በ1822 እ.ኤ.አ. ከአሜሪካ በመጡ ነጻ የወጡ ባሪያዎች የተመሠረተች ሲሆን በአካባቢው ግን የተለያዩ ብሔሮች ለብዙ ምእተ አመታት ኖረዋል። መሥራቾቹ ዋና ከተማቸውን ሞንሮቪያ ብለው ለአሜሪካን ፕሬዝዳንት ጄምስ ሞንሮው ሰይመውታል። ሐምሌ ፳ ቀን ፲፰፻፴፱ ዓ/ም ነጻነት አወጁና ግዛቷ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ሆነች። በ1980 እ.ኤ.አ. በወታደራዊ መፈንቅለ-መንግስት የላይቤሪያ አመራር ከወረደ በኋላ ከ1989 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. ድረስ ሀገሩዋ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ያፈናቀሉና የሀገሩዋን ኢኮኖሚ ያቃወሱ ሁለት የእርስ-በርስ ጦርነቶችን አይታለች። የአንትሮፖሎጂ ምርምር እንደሚያሳየው ከሆነ፣ በላይቤሪያ ላይ ከ12ኛው ክፍለ-ዘመን ወይም ከዛ በፊት ጀምሮ ሰው ሠፍሯል። መንዴ (Mende) የሚባል ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ ምዕራብ ሲስፋፉ፣ ሌሎች ታናናሽ ብሄረሰቦችን ወደ ደቡብ ወደ አትላንቲክ ውቅያኖስ ገፍተዋቸዋል። ዴዪ፣ ባሳ፣ ክሩ፣ ጎላ እና ኪሲ የሚባሉ ጎሳዎች በአካባቢው ከመጀመሪያ ጀምሮ እንደነበሩ በማስረጃ ይታወቃል። ይህ ፍልሰት የጨመረው የማሊ ግዛት በ1375 እ.ኤ.አ. እና የሶንጋይ ግዛት በ1591 እ.ኤ.አ. ሲዳከሙ ነው። በተጨማሪም ወደ ውስጥ ያለው ሥፍራ ወደ በርሃነት እየተለወጠ ስለመጣ፣ ነዋሪዎቹ ወደ እርጥቡ ፔፐር ጠረፍ (Pepper Coast) እንዲሄዱ ተገደዱ። ከማሊና ሶንጋይ ግዛቶች የመጡ አዳዲስ ነዋሪዎች ጥጥ ማሽከርከር፣ ልብስ መስፋት፣ ብረት ማቅለጥ እና ሩዝና ማሽላ ማብቀልን የመሳሰሉ ጥበቦች ለቦታው አስተዋወቁ። መኔ ሰዎች (ከመንዴ ወታደሮች የመጡ) አካባቢውን ከተቆጣጠሩ በኋላ ቫይ የሚባል የማሊ ግዛት ከፈረሰ በኋላ ለመሰደድ የተገደደ ብሔር ወደ ግራንድ ኬፕ ማውንት (Grand Cape Mount) የሚባለው ሥፍራ ፈለሱ። የክሩ ብሔር የቫይን ፍልሰት ተቃወሙ። ከመኔ ብሔር ጋር አንድ ላይ በመሆንም የቫይ ብሔርን ከግራንድ ኬፕ ማውንት አልፈው እንዳይስፋፉ አገዱ። በጠረፍ ላይ የሚኖሩት ሰዎች ታንኳ ሰርተው ከካፕ-ቨርት እስከ የወርቅ ጠረፍ (Gold Coast) ድረስ ካሉት ሌሎች ምዕራብ አፍሪካውያን ጋር ይገበያዩ ነበር። የክሩ ጎሳ በመጀመሪያ ለአውሮፓውያን ሰው ያልሆኑ ነገሮችን ይሸጡ ነበር። ግን በኋላ በየአፍሪካ ባሪያ ንግድ ውስጥ መሳተፍ ጀመሩ። የክሩ ሠራተኞች ቦታቸውን ትተው በትልቅ እርሻዎችና የግንባታ ሥራዎች ላይ ተሳትፈዋል። አንዳንዶቹም የስዊዝና ፓናማ መስኖዎች ለመገንባት ረድተዋል። ሌላ ግሌቦ የሚባሉ ሰዎች የመኔ ጎሳ አካባቢያቸውን ሲወር፣ በኋላ የላይቤሪያ ወደ ሚሆነው ጠረፍ አመሩ። በ1461 እ.ኤ.አ. እና 17ኛው ክፍለ-ዘመን መጨረሻ መካከል ፖርቱጋላዊ፣ ሆላንዳዊና ብራታንያዊ ነጋዴዎች በላይቤሪያ የንግድ ቦታ አቋቁመው ነበር። በተጨማሪም የአንድ የሚጥሚጣ አይነት ፍሬ በመብዛቱ ፖርቱጋላዊያን አካባቢውን Costa da Pimenta (ኮስታ ዳ ፒሜንታ) ማለትም የፍሬ ጠረፍ ብለው ሰይመውት ነበር። በ1822 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የቅኝ መግዛት ማህበር ላይቤሪያን ባሪያ የነበሩ ጥቁር ሰዎች የሚላኩበት ቦታ አድርጎ አቋቋመ። ከሌሎች ባሪያ ያልነበሩ ጥቁር አሜሪካውያንም ወደ ላይቤሪያ ለመሄድ የመረጡ ነበሩ። ወደ እዛ የሄዱት አሜሪካዊ ላቤሪያዊያን በመባል ይታወቃሉ። በሐምሌ 20 ቀን 1839 ዓ.ም. እነዚህ ሰፋሪዎች የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ነፃነትን አወጁ። አርባ ከመቶ የሚሆነው የሀገሩ ሕዝብ ክርስቲያን ነው። ሌላ ሀያ ከመቶ የሚሆን ሕዝብ የራሱ የአገሬው ሀይማኖት አለው። የቀረው አርባ ከመቶ ሕዝብ የእስልምና እምነት ተከታይ ነው። የላይቤሪያ ዩኒቨርሲቲ በሞንሮቪያ ይገኛል። በ1862 እ.ኤ.አ. የተከፈተ ሲሆን ከአፍሪካ ቀደምት የከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አንዱ ነው። በእርስ-በርስ ጦርነት ጊዜ በጣም የተጎዳ ሲሆን አሁን እንደገና እየተገነባ ነው። ከቲንግተን ዩኒቨርሲቲ በየአሜሪካ ኢጲስ ቆጶስ ቤተክርስቲያን በ1889 እ.ኤ.አ. ተመሥርቷል። ግቢው በሱዋኮኮ፣ ቦንግ የአገዛዝ ክፍል ይገኛል። \n \nጥያቄ: ላይቤሪያ ነጻነቷን መች አገኘች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሐምሌ ፳ ቀን ፲፰፻፴፱ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጉጃራቲ ጉጃራቲ (ગુજરાતી) በህንዳዊ-አውሮፓዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ የሚገኝ ቋንቋ ነው። በዓለሙ ውስጥ በ46 ሚልዮን ሰዎች ይናገራል፤ ከነዚህም 45.5 ሚልዮን በህንደኬ፣ 250,000 በታንዛኒያ፣ 150,000 በዩጋንዳ፣ 100,000 በፓኪስታንና 50,000 በኬንያ አሉ። በሕዝብ ብዛት የዓለሙ 23ኛ ቋንቋ ነው። በምእራብ ህንደኬ ያለው የጉጃራት ክፍላገር ይፋዊ ቋንቋ ነው። የጉጃር ሕዝብ ወደ ህንደኬ የደረሱ በ5ኛው መቶ ዘመን ሲሆን በ6ኛው መቶ ዘመን ዛሬ ጉጃራት በሚባለው አገር ሰፈሩ። የራሳቸውን ቋንቋ ቶሎ ትተው እንደ አገሩ ሰዎች ሳንስክሪት ለመናገር ጀመሩ። በ12ኛው ክፍለ ዘመን ግን ሳንስክሪት ተለውጦ ብዙ አዲስ ቋንቋዎች ተወለዱ። ከነዚሁም አንድ ጉጃራቲ ነበር። አብዛኛው ተናጋሪዎቹ የህንድ ሃይማኖት ተከታዮች ቢሆኑም ለረጅም ዘመን የእስላም ገዢዎች ስለነበሩባቸው ብዙ ቃላት የተወሰዱ ከፋርስ ሆኗል። ከዚያ በላይ በንግድ ምክንያት ብዙ ቃሎች ከፖርቱጊዝ ወይም ከእንግሊዝኛ ተበደሩ። የሚጻፍበት በራሱ ጉጃራቲ ፊደል ነው፤ ይህም ከላይኛ መስመር በማጣቱ በስተቀር የህንዲ ደቫናጋሪ ፊደል ይመስላል። \n \nጥያቄ: የጉጃር ሕዝብ ወደ ህንደኬ የመጡት በስንተኛው ክፍለ ዘመን ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ5ኛው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየቻይናው ግዙፉ የቴሌኮም ኩባንያ ሁዋዌ በፈረንጆቹ 2019 240 ሚሊየን ስልኮችን ለገበያ ማቅረቡን አስታውቋል፡፡ ይህን ተከትሎም ኩባንያው የሽያጭ ገቢው 850 ቢሊየን ዩዋን ወይም 122 ቢሊየን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል ተገምቷል ፡፡ ሽያጩ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ 18 በመቶ ብልጫ ያለው ሲሆን፥ የተጠበቀውን ያክል ገቢ አለመገኘቱም ተመላክቷል ፡፡ የኩባንያው መሳሪያዎቹን በመጠቀም ስለላ ሊያካሂድ ይችላል በሚል በአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነት ባለሥልጣናት ላይ ስጋትን በመጫሩ ከአሜሪካ የግንኙነት መረቦች በፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዛዝ መታገዱ ይታወሳል ፡፡ ይህም ለሁዋዌ አስቸጋሪ ሁኔታን ፈጥሮ ቆይቷል፡፡ ኩባንያው በ2020ም የተፈጠረውን ችግር በመቋቋም ገበያው ላይ መቆየት ተቀዳሚ አላማው መሆኑን የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ ተናግረዋል። ምንጭ፡-www.cnet.com/ \n \nጥያቄ: የቻይናው ግዙፉ የቴሌኮም ኩባንያ ሁዋዌ በፈረንጆቹ 2019 240 ሚሊየን ስልኮችን ለገበያ በማቅረቡ ምን ያሀል ገቢ ለማግኘት ቻለ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 850 ቢሊየን ዩዋን ወይም 122 ቢሊየን ዶላር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ አ.ማ ኢንደስትሪያል ኮምፕሌክስ የመሰረት ድንጋይ የማኖር ስነስርአት ተካሄደ። የፋብሪካው ግንባታ በ2 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር የሚከናወን ሲሆን በሀገሪቱ ያለውን የሲሚንቶ እጥረት ሊቀርፍ እንደሚችል ተጠቁሟል፡፡ \n \nጥያቄ: በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ የፋብሪካው ግንባታ በምን ያህል ወጪ ነው የሚገነባው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ2 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጋሊልዮ ጋሊልዮ ጋሊሊ ታህሳስ 15, 1564 – ጥር 8, 1642 የነበረ የጣሊያን ሥነ-ፈለክ አጥኝና ተመራማሪ ነበር። ጋሊልዩ በዘመኑ የራሱን አጉሊ መነጽር በመስራት ጨረቃ ተራራ እንዳላት፣ ጁፒተር የተባለው ፈለክ ልክ እንደ መሬት የራሱ የሆኑ 4 ጨረቃወች እንዳሉት፣ ረጨቶች ከከዋክብት ስብስብ እንደተሰሩ፣ ፀሐይ ጥቁር ነጠብጣቦች እንዳሏት፣ ቬነስ ልክ እንደ ጨረቃ የተለያየ ቅርጽ በጥልቁ እንደምትይዝ የመሰከረና በኋላም መጽሃፍ ጽፎ ያሳተመ ሳይንቲስት ነው። ከዚህ በተጨማሪ ጋሊልዮ የተፈጥሮ ህጎችን/ጉልበቶችን አጥንቷል። በትውፊት እንደሚነገር ጣልያን ውስጥ ባለው የተንጋደደው የፒሳ ግንብ ላይ በመውጣት፣ የተለያዩ ክብደት ያላቸውን የብረት ኳሶች ወደመሬት በመልቀቅ፣ ሁሉም በዕኩል ሰዓት መሬትን እንደሚመቱ አረጋግጧል። ከዚህ በመነሳት እስከሱ ዘመን ይሰራበት የነበረውን የአሪስቶትል አስተሳሰብ (ከባድ ነገሮች ከቀላል ነገሮች በበለጠ ፍጥነት ወደመሬት ይወድቃሉ) ፉርሽ አድርጓል። ሆኖም ግን በጊዜው የአሪስቶትል አስተሳሰብ በህብረተሰቡ ህሊና ውስጥ በጥብቅ ስለሰረጸ ቆይቶ ኢሳቅ ኒውተን የጋሊልዮን አስተሳሰብ ልክ መሆኑን በግስበት ጥናቱ እስካረጋገጠበት ድረስ የአሪስቶትል አስተሳሰብ ተቀባይነት ነበረው። ጋሊልዩ ከሱ ቀድሞ የተነሳውን የኮፐርኒከስን ሃሳብ (መሬት ሳትሆን ፀሓይ የአለም መካከለኛ ናት) በመደገፉ በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ለእስር ተዳርጎ ነበር። ይህም በዚያ ዘመን የነበሩ የቤ/ክርስቲያኒቱ አዋቂወች ያምኑት እንደነበረው መሬት ቆማ ሌላው አለም ሁሉ በመሬት ዙሪያ ይሽከረከራሉ የሚለውን ስለተቃወመ ነበር። ከዚህ በኋላ እስከ አረፈበት 1642 ድረስ የቤት እስረኛ ሆኖ ዘልቋል። በቅርቡ በ20ኛው ክፍለ ዘመን የሮማው ፓፓ ጆን ፓውል 2ኛ ጋሊልዮን \"የተፈጥሮ ህግጋት ጥናት] አባት\" በማለት የካቶሊክ ቤ/ክርስቲያ ከ400 አመት በፊት በጋሊልዮ ላይ ለፈጸመችው ግፍ ይቅርታ ጠይቀዋል። \n \nጥያቄ: የሮማው ፓፓ ጆን ፓውል 2ኛ የጋሊልዮ ጥናት ትክክለኛ እንደነበር በማመን የካቶሊክ ቤተክርስቲያንን ወክለው ስለደረሰበት ግፍ ይቅርታ የጠየቁት ከስንት ዓመት በኋላ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከ400 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nረጅሙ የቦይንግ አውሮፕላን የመጀመሪያ በረራውን በስኬት አጠናቋል። ቦይንግ 777- 9 ኤክስ የተሰኘው ይህ አውሮፕላን ባለ ሁለት ሞተር እና 76 ሜትር ርዝመት እንዳለው ተገልጿል። አዲሱ አውሮፕላን በኩባንያው ምርቶች ላይ በሚፈጠሩ እክሎች ምክንያት የሚደርሱ አደጋዎችን ለመቀነስ ያስችላል ነው የተባለው። የአውሮፕላኑ የተሳካ የበረራ ሙከራ ሲያትል ከተማ አካባቢ የተከናወነ ሲሆን፥ ይህ ሙከራ ከመካሄዱ በፊት በአየር ፀባይ ችግር ምክንያት ሊካሄዱ የነበሩ ሁለት የሙከራ በረራዎች እንዲቋረጡ ተደርጓል። ኩባንያው እስካሁን 309 የሚሆኑ 777 ኤክስ አውሮፕላኖችን የሸጠ ሲሆን፥ የአንዱ ዋጋም 442 ሚሊየን ዶላር ነው ተብሏል። ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖቹ ላይ በተፈጠረ የቴክኒክ ችግር ምክንያት ንብረትነታቸው የኢትዮጵያ እና ኢንዶኔዢያ የሆኑ ሁለት አውሮፕላኖች ተከስክሰው የ346 ሰዎች ህይወት ማለፉ ይታወሳል። ይህን ተከትሎም ኩባንያው የሚያመርታቸው አውሮፕላኖች ደህንነት አስተማማኝ አይደለም በሚል በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እና በባለሙያዎች ከፍተኛ ወቀሳ ሲቀርብበት ቆይቷል። ምንጭ፦ ሲ ኤን ኤን   \n \nጥያቄ: ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖቹ ላይ በተፈጠረ የቴክኒክ ችግር ምክንያት የየት ሀገር ንብረት የሆኑ አውሮፕላን ናቸው የተከሰከሱት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የኢትዮጵያ እና ኢንዶኔዢያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቢል ክሊንተን ያደጉት በሆት ስፕሪንግስ፣ አርካንሳው ነው። የቢል ክሊንተን አባት ዊሊያም ጄፈርሰን ብላይዝ ጁኚየር፣ ቢል ክሊንተን ከመወለዱ ሶስት ወር በፊት በመኪና አደጋ ሞተዋል። የቢል ክሊንተን እናት ቨርጂኒያ ክሊንተን ኬሊ፣ በ1950 እ.ኤ.ኣ. ሮጀር ክሊንተን የሚባል ሰዉ አገባች። 14 ዓመቱ ሲሆን ቢል ክሊንተን የመጨረሻ ስሙን ወደ ክሊንተን ለወጠ። ክሊንተን በጆርጅታውን ዩኒቨርሲቲ፥ ዋሽንግተን ዲ.ሲ.፣ ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ፥ ኢንግላንድ፣ እና ዬል ዩኒቨርሲቲ፥ ኮነቲኬት ተምረዋል። በ1975 እ.ኤ.ኣ. ሂለሪ ሮድሃምን አገቡና በሊትል ሮክ፥ አርካንሳው መኖር ጀመሩ። ከዚያም በዩኒቨርሲቴ ኦፍ አርካንሳው የሕግ ፐሮፌሰር ሆነው አገልግለዋል። ቢል ክሊንተን የአርካንሳው አስተዳዳሪ ሆኖ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመረጡት በ1978 እ.ኤ.ኣ. ነው። በዛ ጊዜ ከአሜሪካ በዕድሜ ትንሹ አስተዳዳሪ ነበሩ። በ1980 እ.ኤ.ኣ. በፍራንክ ዲ ዋይት ከተሸነፉ በኋላ በ1982 እ.ኤ.ኣ. እንደገና ተመረጡ። ከዛ ጀምሮ እስከ 1992 እ.ኤ.ኣ. ድረስ ለአራት ጊዜ አስተዳዳሪ ሆነው መርተዋል። በ1984 እ.ኤ.ኣ. የአስተዳዳሪ የስልጣን ዕድሜ ከ2 ዓመት ወደ 4 ዓመት አራዝመዋል። በ1992 እ.ኤ.ኣ. ለፕሬዝዳንትነት ተወዳድርው አሸንፈዋል። በ1996 እንደገና ተወዳድረው አሸንፈዋል። \n \nጥያቄ: የቢል ክሊንተን አባት በምን ምክንያት ሞቱ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በመኪና አደጋ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአብዱልራዛቅ እ.ኤ.አ. በ1994 ላይ ያሳተሙት ‹ፓራዳይዝ› የተሰኘው ልብ ወለድ ታንዛኒያ ውስጥ በ20ኛው ምዕት ዓመት የልጅ አስተዳደግ ምን እንደሚመስል ፍንትው አድርገው ያሳዩበት ነው። በዚህ ልብ ወለድም ዓለም አቀፉን የ‹ቡከር› ሽልማት ለማግኘት መቻላቸውን ቢቢሲ ዘግቦታል፡፡ እንደ የኖቤል ኮሚቴ የሥነ ጽሑፍ ክፍል አገላለጽም፣ ‹‹[የእሳቸው] ገጸ ባህርያት ሁሌም ቢሆን በባህልና አኅጉራት መካከል የሚሽከረከሩ፣ በአሁን ሕይወትና በመጪው ሕይወት መካከል የሚመላለሱ ናቸው። በቀላሉ ሊያልፉት የማይችሉት ከባድ እውነታ ውስጥ ናቸው፡፡›› እ.ኤ.አ. በ1948 በዛንዚባር የተወለዱት አብዱልራዛቅ፣ እ.ኤ.አ. በ1960ዎቹ መገባደጃ አገረ እንግሊዝ የገቡት ስደተኛ ሆነው ነው። በቅርቡ ጡረታ እስከወጡበት ዕለት ድረስ በካንተርበሪው የኬንት ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዝኛና የድኅረ ቅኝ ግዛት ሥነ ጽሑፎች ፕሮፌሰር ነበሩ። ሽልማቱ፣ ደራሲው ያለፉበትን የስደተኞች ቀውስንና ቅኝ አገዛዝን በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ውይይት እንዲደረግባቸው ያስችላል ብለዋል፡፡ ‹‹እነዚህ በየዕለቱ ከእኛ ዘንድ ያሉ ነገሮች ናቸው። ሰዎች እየሞቱ ነው፣ ሰዎች በዓለም ዙርያ አሁንም እየተጎዱ ነው፡፡ በእነዚህን ጉዳዮች ላይ በፍፁም ቀናነትና አስተውሎት መንገድ መነጋገር መላ መምታት አለብን፤›› ብለዋል የኖቤል ተሸላሚው አብዱልራዛቅ። ዓምና በሥነ ጽሑፍ ያሸነፉት አሜሪካዊው ገጣሚ ሊዊስ ግሉክ መሆናቸው ይታወሳል። የስዊድኑ አካዴሚ በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት ከሸለማቸው ታላላቅ ደራስያን መካከል ከአፍሪካ አኅጉር ስድስት ደራስያን ይገኙበታል፡፡ እነርሱም ዎሌ ሾንካ (ናይጀሪያ)፣ ነጂብ ማኅፉዝ (ግብፅ)፣ ናዲን ጎርዲመር (ደቡብ አፍሪካ)፣ ጄ.ኤም ኮትዚ (ደቡብ አፍሪካ)፣ እና ዶሪስ ሌሲንግ (ዚምባቡዌ -እንግሊዝ) ይገኙበታል፡፡ \n \nጥያቄ: ደራሲ አብዱልራዛቅ ወዴት ተሰደዱ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ እንግሊዝ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየኒያ ፋውንዴሽን እና የጆይ ኦውቲዝም ማዕከል መሥራች ወይዘሮ ዘሚ የኑስ በኮሮና ቫይረስ ፅኑ ህክምና ማዕከል ውስጥ በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ህይወታቸው ማለፉ ተነገረ። ዘሚ የኑስ በአሁኑ ሰአት ከ200 በላይ ለሚሆኑ የአእምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸውን ልጆች እንክብካቤ እያደረጉ እንደሚገኙ ከቅርብ ቤተሰቦቻቸው ያገኘውን መረጃ ጠቅሶ ኢዜአ ዘግቧል። \n \nጥያቄ: ወይዘሮ ዘሚ የኑስ ምን ያህል የአእምሮ እድገት ውስንነት ላለባቸው ልጆች ይንከባከቡ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ200 በላይ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሴኔጋል ሴኔጋል ወይም የሴኔጋል ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። ሴኔጋል ከምዕራብ በሴኔጋል ወንዝ፣ ከሰሜን በሞሪታንያ፣ ክምሥራቅ በማሊ እና ክደቡብ በጊኒና ጊኒ-ቢሳው ይዋሰናል። የጋምቢያ ግዛት እንዳለ በሴኔጋል ውስጥ ነው የሚገኘው። የሴኔጋል የቆዳ ስፋት 197,000 ካሬ ኪ.ሜ. የሚጠጋ ሲሆን የሕዝብ ብዛቱ ደግሞ ወደ 14 ሚሊዮን እንደሆነ ይገመታል። የሴኔጋል የአየር ሁኔታ የየምድር ወገብ ሲሆን ደረቅና ዝናባማ ወራት ተብሎ ወደ ሁለት ይከፈላል። የሴኔጋል ርዕሰ ከተማ ዳካር በሀገሩ የምዕራብ ጫፍ በካፕ-ቨርት ልሳነ ምድር ላይ ይገኛል። ከባህር ጠረፍ ወደ ፭፻ ኪ.ሜ. ገደማ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የኬፕ ቨርድ ደሴቶች ይገኛሉ። በ፲፯ኛው ና ፲፰ኛው ክፍለ ዘመናት በቅኝ ገዢ መንግሥታት የተሠሩ የንግድ ተቋማት ከባህር ዳር ይገኛሉ። በአካባቢው ያሉ ግኝቶች ሴኔጋል ከጥንት ጀምሮ የሚኖርበት እንደነበረ ያሳያሉ። እስልምና የአካባቢው ዋና ሀይማኖት ሲሆን ወደ ሴኔጋል የተዋወቀውም በ11ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን እንደሆነ ይታመናል። በ13ኛውና 14ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን የማንዲንጎ ግዛት በአካባቢው ላይ ተጽኖ ያደርግ ነበር። በዚሁም ጊዜ ነው የጆሎፍ ግዛት የተመሠረተው። በ15ኛው ክፍለ-ዘመን ፖርቱጋል፣ ኔዘርላንድስ እና ኢንግላንድ በአካባቢው ለመነገድ ይወዳደሩ ነበር። በ1677 እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ጎሪ የሚባለውን ዋና የባሪያ ንግድ ደሴት ተቆጣጠረች። ከዛም በ1850ዎቹ እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ቁጥጥሩዋን ወደ መላው ሴኔጋል ማስፋፋት ጀመረች። \n \nጥያቄ: የኬፕ ቨርድ ደሴቶች በየትኛው ውቅያኖስ ይገኛሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በአትላንቲክ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበውሃ ላይ የሚሰራ የኤሌክትሪክ ብስክሌት በገበያ ላይ መዋሉ ተነገረ። ማንታ 5 የተባለው የኒውዝላንድ ኩባንያ ኤክስ ኢ 1 የተሰኘችውን እና በውሃ ላይ የምትሰራውን የኤሌክትሪክ ብስክሌት በላስ ቬጋስ አስተዋውቋል። ብስክሌቱ በፔዳል የሚሰራ ሲሆን፥ አንድ ጊዜ ባትሪ ከተሞላ በኋላ ለአንድ ሰዓት ያክል መጠቀም ይቻላል። በሰዓትም እስከ 20 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር ድረስ መጓዝ ይችላልም ነው የተባለው። አዲሱ ብስክሌት የ6 ሺህ ፓውንድ ዋጋ ተቆርጦለታል። ብስክሌቱን ለዕይታ ለማብቃት እስከ 10 አመት ጊዜ እንደፈጀ ኩባንያው ምርቱን ባስተዋወቀበት ወቅት ገልጿል። አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 29፣ 2012 (ኤፍቢሲ) \n \nጥያቄ: ማንታ 5 ያስተዋወቀው በውሃ ላይ የምትሰራው የኤሌክትሪክ ብስክሌት ምን ትባላለች?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ኤክስ ኢ 1 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየማይዳሰሱ (ኢንታንጀብል) ባህላዊ ቅርሶችን የሚመለከተው የዩኔስኮ አካል በይነ መንግሥታዊው ኮሚቴ 10ኛ ስብሰባውን ከኅዳር 20 እስከ ኅዳር 24 ቀን 2008 ዓ.ም. በናሚቢያ መዲና ዊንድሆክ በተደረገው 10ኛ የዩኔስኮ ጉባዔ ለውሳኔ ከቀረቡት 35 (ሠላሳ አምስት) ባሕላዊ ቅርሶች መካከል የሲዳማ ብሔር የአዲስ ዓመት ዘመን መለወጫ የሆነው ፍቼ ጫምባላላ በዓል በሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ የ2003 የኢንታጀብል ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃ ዓለም አቀፍ ስምምነት መስፈርቶችን አሟልቶ በመገኘቱ አባል አገሮች ውይይት ካደረጉበት በኋላ ፍቼ ጫምባላላ ተመዝግቧል፡፡ ይህም ከመስቀል በዓል ቀጥሎ የኢትዮጵያ ሁለተኛው የማይዳሰስ ዓለም አቀፍ የሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ሆኖ ሕዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም በአገሩ ሰዓት አቆጣጠር 9፡40 በፋይል ቁጥር (01054) በውሳኔ ቁጥር 10.com.10.b.16 ተመዝግቧል፡፡ በ2004 በጀት ዓመት የመስቀል በዓል አከባበርን በዩኔስኮ ማስመዝገብ የሚያስችል የጥናት ሰነድ ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ የተላከ ሲሆን በአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ ከህዳር 23-28 ቀን 2006 ዓ.ም በተካሄደው 8ኛው የዩኔስኮ የኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃ የኢንተርገቨርንመንታል ኮሚቴ መደበኛ ጉባዔ ውሳኔ መሰረት የመስቀል በዓል አከባበር በዩኔስኮ የሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ተካቷል፡፡ በ2006 የበጀት ዓመት የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው ፊቼ ጫምበላላን በሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ለማስመዝገብ የሚያስችል የጥናት ሰነድ (ኖሚኔሽን ፋይል) ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ የተላከውና ህዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም የተመዘገበው የተደረገው ፊቼ ጫምበላላ ሰነዶች በሚከተለው የዩኔስኮ ድረ ገጽ ላይ ለመላው ዓለም ተለቀው ይገኛል፡፡ በተመሳሳይም በ2007 የበጀት ዓመት ኦሮሞ ህዝብ የማንነት መገለጫ የሆነው የገዳ ስርዓትን በሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ለማካተት የሚያስችል የኖሚኔሽን ሰነድ ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ መጋቢት 2007 ዓ.ም ተልኳል፡፡ \n \nጥያቄ: የዩኔስኮ አካል በይነ መንግስታዊ ኮሚቴ 10ኛ ስብሰባውን በየት ተደረገ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በናሚቢያ መዲና ዊንድሆክ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኤስፔራንቶ ኤስፔራንቶ (Esperanto) ከሁሉም አለማቀፋዊ ሠው ሰራሽ ቋንቋዎች እጅጉን የተስፋፋ ቋንቋ ነው። በ1859 እ.ኤ.አ. በዛሬይቷ ፖሎኝ የተወለደውና በሞያው የአይን ሀኪም የሆነው ሉድዊክ ሌይዛር ዛመንሆፍ በ1887 እ.ኤ.አ. ቋንቋውን ለህዝብ አሳወቀ። አላማው ኤስፔራንቶን በቀላሉ ሊማሩት የሚቻል፣ የጋራ የሆነና ለአለማቀፋዊ መግባባት የሚረዳ ግን ያሉትን ቋንቋዎች የማይተካ ቋንቋ ማድረግ ነበር። ኤስፔራንቶ ከ1,600,000 በላይ ተናጋሪዎች ቢኖሩትም የቋንቋው ደጋፊ ያልሆኑ እንግሊዝኛን ከመስፋፋቱ አንፃር ለአለማቀፋዊ ቋንቋነት በተሻለ ይመርጡታል። \n \nጥያቄ: ኤስፔራንቶ የተሰኘውን ዓለም አቀፋዊ ቋንቋ ያስተዋወቀው ሉድዊክ ሌይዛር ዛመንሆፍ የተወለደው መቼ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ1859 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nፍቅር እስከ መቃብር ፍቅር እስከ መቃብር በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. በደራሲ ሀዲስ አለማየሁ የቀረበ ልብ ወለድ ሲሆን ሰብለ ወንጌል እና በዛብህ የሚባሉ የሁለት ገፀ ባህሪያትን ፍቅር ይተርካል። ይህ ድርሰት ከሌሎች ልብወለድ ሥራዎች ለየት የሚያደርገው ደራሲው ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ በፊደል አጠቃቀም ላይ ለውጥ አድርገው በማቅረባቸው ነው። ይኸውም ለምሳሌ ያህል ሦስት «ሀ»ዎች፣ ሁለት «ሰ»ዎች፣ ሁለት «ኣ»ዎች የመሳሰሉትን እንደ አንድ ወይም የመጀመሪያውን ብቻ በመያዝ ነው። በተጨማሪም ጠብቀው በሚነገሩ ቃላት ላይ ከላይ አንድ ነጥብ በማስቀመጥ ይታወቃሉ።ሀዲስ ኣለማየሁ በኢትዮጵያ ስነ-ፅሑፍ የራሳቸው ትልቅ አሻራ አኑረው ያለፉ አንጋፋ ደራሲ ናቸው። የታሪኩ ማጠቃለያ በዛብህ‌ ‌ጎጃም‌ ‌ማንኩሳ‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከእናቱ‌ ‌ከውድነሽ‌ ‌በጣሙና‌ ‌ከአባቱን‌ ‌ከቦጋለ‌ ‌መብራት‌ ‌ይወለዳል።‌ ‌በሽታ‌ ‌ይበዛበትና‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይባላል።‌ ‌እናቱ‌ ‌ከበሽታው‌ ‌እንዲድን‌ ‌ስእለት‌ ‌ይሳላሉ።‌ ‌ዕድል‌ ‌ሆኖ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይተርፋል፤‌ ‌አድጎ‌ ‌ጎበዝ‌ ‌ልጅ‌ ‌ይሆናል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌በሽታ፣‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ዕውቀትና‌ ‌ፍቅር‌ ‌(የሰው‌ ‌መውደድ)‌ ‌ይበዛበታል።‌ ‌በወጣትነቱ‌ ‌ይቀድስና‌ ‌ለቤተሰቡ‌ ‌ገንዘብ‌ ‌ማምጣት‌ ‌ይጀምራል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌የስእለት‌ ‌ልጅ‌ ‌መባልን‌ ‌አይጠላም‌ ‌ነበር።‌ ‌ሲያድግ‌ ‌ግን‌ ‌ትርጉሙን‌ ‌በመረዳቱ‌ ‌ነጻነቱን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌ዲማን‌ ‌ጥሎ‌ ‌ወደደብረ‌ ‌ወርቅ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌እዚያም‌ ‌ከእመት‌ ‌ጠጂቱ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይጠጋል።‌ ‌ትንሽ‌ ‌ዜማና‌ ‌ቅኔም‌ ‌ይማራል።‌ ‌ደብተራ‌ ‌በየነ‌ ‌መጥቶ‌ ‌የወላጆቹን‌ ‌ሞት‌ ‌ሲያረዳው‌ ‌ወደዲማ‌ ‌ይወርዳል።‌ ‌በተክለ‌ ‌አልፍአው‌ ‌በዓል‌ ‌በመልካም‌ ‌ድምጹ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻንና‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትን‌ ‌ያወድሳል።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻም‌ ‌የሰብለ‌ ‌መምህር‌ ‌አድርገው‌ ‌ይቀጥሩታል።‌ ‌ሰብለና‌ ‌በዛብህ‌ ‌የሕይወት‌ ‌ገጠመኞቻቸው‌ ‌በመጠኑ‌ ‌ስለሚመሳሰል‌ ‌ይግባባሉ።‌ ‌በመሃል‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌አሰጋኸኝ‌ ‌ሰብለን‌ ‌በፈት‌ ‌ወግ‌ ‌አገባለሁ‌ ‌በማለቱ‌ ‌በርሱና‌ ‌በፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌መካከል‌ ‌ጥል‌ ‌ተፈጠረ፤‌ ‌ሆኖም‌ ‌በሃይማኖት‌ ‌ጣልቃገብነት‌ ‌ሳይዋጉ‌ ‌ቀሩ።‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከባላገሮች‌ ‌ጋራ‌ ‌በግብር‌ ‌ጉዳይ‌ ‌ተጣሉ።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ተማርከው‌ ‌ሳለ‌ ‌የበዛብህንና‌ ‌የሰብለወንጌልን‌ ‌የፍቅር‌ ‌ዜና‌ ‌ይሰማሉ።‌ ‌ወዲያውም‌ ‌መጥተው‌ ‌ሰብለን‌ ‌በሌሊት‌ ‌ያስሯታል።‌ ‌የሰብለ‌‌አጎት‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ሁለቱን‌ ‌ለማስመለጥ‌ ‌ወጣ፣‌ ‌ወረደ።‌ ‌የዕጣ‌ ‌ነገር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ግን‌ ‌ሳይሳካ‌ ‌ቀረ።‌ ‌በዛብህ‌ ‌ግን‌ ‌በግራጌታ‌ ‌ቀለመወርቅና‌ ‌በጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጥረት‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌በራጉኤል‌ ‌ቤተክርስቲያንም‌ ‌የቅኔ‌ ‌መምህር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ይቀጠራል።‌ ‌ባደረጉላቸው‌ ‌ውለታ‌ ‌ምክንያት‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌ሰብለን‌ ‌ለፊታውራሪ‌ ‌ታፈሰ‌ ‌ሊድሯት‌ ‌ይሞክራሉ።‌ ‌የሰብለን‌ ‌አቋም‌ ‌አውቀው‌ ‌አባ‌ ‌ተክለሃይማኖት‌ ‌በተባሉ‌ ‌መነኩሴ‌ ‌ያስጠብቋቷል።‌ ‌መነኩሴው‌ ‌ግን‌ ‌ሰክረው‌ ‌ሰብለ‌ ‌ታመልጣለች።‌ ‌ፍለጋ‌ ‌ሲሄዱ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከፈረስ‌ ‌ላይ‌ ‌ተወርውረው፣‌ ‌ተንኮታክተው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትም‌ ‌ቤተክርስቲያን‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከደረጃ‌ ‌ላይ‌ ‌ተንሸራትተው‌ ‌ወድቀው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ሰብለ‌ ‌ደግሞ‌ ‌በዛብህን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌መነኩሴ‌ ‌መስላ‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ትሄዳለች።‌ ‌ደርሳም‌ ‌በዛብህ‌ ‌አለመኖሩን‌ ‌ትሰማና‌ ‌ጎሃጽዮን‌ ‌ትወርዳለች።‌ ‌በዚያም‌ ‌በዛብህ‌ ‌ተደብድቦ፣‌ ‌ነፍስ‌ ‌ውጪ‌ ነፍስ‌ ‌ግቢ‌ ‌አይነት‌ ‌ሁኔታ‌ ‌ላይ‌ ‌ሳለ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌እንደምንም‌ ‌ብለው‌ ‌ሥጋ‌ ‌ወደሙን‌ ‌ይቀበላሉ።‌ ‌ጥቂት‌ ‌ቆይቶ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይሞታል።‌ ‌ሰብለም‌ ‌መንኩሳ፣‌ ‌የበዛብህን‌ ‌አስከሬን‌ ‌ባጠገቧ‌ ‌አድርጋ‌ ‌ስትኖር‌ ‌ከጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጋራ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌ጉዱ‌ ‌የተሰኘው‌ ‌ካሳ‌ ‌ዳምጤም‌ ‌እርሷ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይቀመጣል።‌ ‌አስራ‌ ‌አምስት‌ ‌ቀናት‌ ‌አንድ‌ ‌ላይ‌ ‌ይኖሩና‌ ‌ሰብለ‌ ‌የልብ‌ ‌በሽታዋ‌ ‌ተነሥቶባት‌ ‌ትሞታለች፣‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ከበዛብህ‌ ‌አጠገብ‌ ‌ያስተኛታል።‌ ‌በሦስተኛው‌ ‌አመት‌ ‌ጉዱም‌ ‌አረፍተ‌ ‌ዘመን‌ ‌ይገታዋል።‌ \n \nጥያቄ: ሰብለን ለሞት ያደረሳት በሽታ ምን ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የልብ‌ ‌በሽታዋ‌ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nታንዛኒያዊው ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ የ2021 የኖቤል የሥነ ጽሑፍ አሸናፊ መሆናቸውን የስዊድን አካዴሚ መስከረም 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1986 ዎሌ ሾይንካ በሥነ ጽሑፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑ ከ35 ዓመታት በኋላ አብዱልራዛቅ ጉራህ ሁለተኛው ጥቁር አፍሪካዊ ያሰኛቸውን ክብር ተቀዳጅተዋል፡፡ በመላው አፍሪካ ደረጃ ስድስተኛ ተሸላሚ ናቸው፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው፣ አብዱልራዛቅ ለአሸናፊነታቸው ከስዊድኑ የኖቤል ሽልማት ድርጀት 10 ሚሊዮን ክራውን ወይም 1.14 ሚሊዮን ዶላር ያገኛሉ፡፡ የ73 ዓመቱ አዛውንት ጉራህ ጎልተው የሚታወቁትን ‹‹ፓራዳይዝ›› (Paradise) እና ‹‹ዲዘርሽን›› (Desertion) ጨምሮ የ10 ልብ ወለዶች ደራሲ ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: አብዱልራዛቅ ጉራህ በአፍሪካ በኖቤል የሥነ ጽሑፍ ተሸላሚ ሲሆኑ ስንተኛው ሰው ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሁለተኛው ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበቁርጥራጭ ብረትና ያገለገሉ ማሽኖች ንግድ የተሰማራው ሳርፌ ቢዝነስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር፣ የግንባታ ብረታ ብረቶች ማምረቻ ፋብሪካ በዱከም ከተማ ለመገንባት በዝግጅት ላይ እንደሆነ አስታወቀ፡፡ የሳርፌ ቢዝነስ መሥራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ክብርይስፋ ተክሌ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ኩባንያው እስካሁን ቁርጥራጭ ብረቶች ከውጭ በማስመጣትና ከአገር ውስጥ በመግዛት ለብረት አቅላጮች ሲያቀርብ ቆይቷል፡፡ የብረት ማቅለጫው ማሽኖች ከህንድ ተገዝተው የሚመጡ ሲሆን፣ የብረት መዋቅሩ ደግሞ ከቻይና ይገዛል፡፡ የፋብሪካው ጠቅላላ የኢንቨስትመንት ወጪ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚገመት የተናገሩት አቶ ክብርይስፋ፣ ፋብሪካው ለ300 ኢትዮጵያውያን የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡ ሳርፌ ቢዝነስ ለብረት ፋብሪካው ግንባታ የሚሆን 30,000 ካሬ ሜትር ቦታ በሊዝ ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከዱከም ከተማ አስተዳደር በቅርቡ መረከቡን ገልጸው፣ ኩባንያቸው ተገቢውን የአዋጭነት ጥናት ማሠራቱን አስረድተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ሳርፌ ቢዝነስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ዋና ኃላፊው ማን ይባላሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አቶ ክብርይስፋ ተክሌ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዓለማየሁ ቴዎድሮስ ልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ የዳግማዊ ዓፄ ቴዎድሮስ እና የወይዘሮ ጥሩወርቅ ውቤ ልጅ ነበር። በ1860 ዓ.ም አፄ ቴዎድሮስ ከእንግሊዞች ጋር ባደረጉት ጦርነት ልጃቸው ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ ወደ እንግሊዝ ሀገር ተወስዶ ነበር፡፡ ልዑል አለማየሁ ሚያዚያ 5 ቀን 1853 ዓ.ም በደብረ ታቦር ከተማ ነበር ውልደቱ፡፡ በልዑሉ ውልደት የተደሰቱት አፄ ቴዎድሮስም በእለቱ መድፍ ያስተኮሱ ሲሆን 500 ያህል እስረኞችንም ፈትተዋል፡፡ ልዑል አለማየሁ እንግሊዞች እጅ ከገባ በኋላ ከእድሜው ለጋነት የተነሳ የሚጠብቀው እና የሚንከባከበው ሰው ሊኖር ግድ ነበር፡፡ ይህንን የተረዳው ጀነራል ናፔር ካፕቴን ስፒዲ የተባለን ሰው የአለማየሁ ጠባቂ እንዲሆን መደበው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ካፕቴኑ የአማርኛ ቋንቋን አቀላጥፎ መናገሩ ነበር፡፡ በተጨማሪም አለቃ ዝርዓት እና አቶ ገብረመድህን የተባሉ ሁለት ኢትዮጵዊያን ሞዚቶች እና አጫዋቾች ተመረጡለት፡፡ አለማየሁ ከጠባቂው ስፒዲ ጋር ፌሬዝ በተባለችው መርከብ ተሳፍሮ በ1860 ዓ.ም. ወደ እንግሊዝ አቀና፡፡ በመርከቢቱ ላይ በነበራቸውም ቆይታ ስፒዲ እና አለማሁ እጅግ የጠበቀ ወዳጅነትን መስርተው ነበር፡፡ ስፒዲ በሄደበት ቦታ ሁሉ አለማየሁን ማስከተል ያዘወትር ነበር፡፡ ይህንን የሁለቱን ፍቅር ያየው ጀነራል ናፒየርም ኢትዮጵያውያን ሞግዚቶቹ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ይልቁንም የአለማየሁን ሀላፊነት ሙሉ በሙሉ ካፕቴን ስፒዲ እንዲረከብ ስለወሰነ ሁለቱ ሞግዚቶች ጉዞው ተጠናቆ እንግሊዝ ሀገር ሳይደርሱ ከስዊዝ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ተደረገ፡፡ ከሶስት ወራት የመርከብ ላይ ጉዞ በኃላ አለማየሁ እንግሊዝ ሀገር ደረሰ፡፡ \n \nጥያቄ: በስንት ዓ.ም ነው እንግሊዞች ልዑል አለማየሁን የወሰዱት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ1860 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nፈረንሳይ የዜጎቿን የማህበራዊ ሚዲያ ገፅ በመፈተሽ ግብር ሰዋሪዎችን ልትለይ እንደሆነ ተገለፀ፡፡ ይህም ባለፈው ሳምንት ከግብር ክፍያ ጋር በተያያዘ የወጣው ሕግ አካል ሲሆን የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች በገፃቸው ላይ የሚለጥፉትን የግል መረጃ ዝርዝር በማየት ነው ግብር የከፈለ እና ያልከፈለ የሚለየው፡፡ እርምጃው የዜጎች ራስን በነፃነት የመግለጽ እና የግላዊነት መብት ላይ ጫና ሊያሳድር ቢችልም ድንጋጌው የሚተገበርበት ቅድመ ሁኔታዎች አሉ ተብሏል። ከቅድመ ሁኔታዎቹ አንዱ በሚስጥራዊ ይለፍ ቃል የተቆለፉ ገጾችን ሰብሮ አለመግባት ነው፡፡ ከዚህ ባለፈ ግን ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ለሕዝብ ይፋ የተደረጉ መረጃዎችን መጠቀም እንደሚችል ነው የተነገረው። የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የፈረንሳይ የመረጃ ደህንነት ክፍል ሕጉ እንደሚያሰጋቸው ተናግረዋል። የበጀት ሚንስትሩ ጄራልድ ዳርማኒን በበኩላቸው አጭበርባሪዎችን የምንገታበት አንድ መንገድ ነው ብለዋል፡፡ ምንጭ፡-ቢቢሲ በፌቨን ቢሻው \n \nጥያቄ: የዜጎቿን የማህበራዊ ሚዲያ ገፅ በመፈተሽ የግብር ስወራን ለማስቀረት ያሰበችው ሀገር ማን ናት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፈረንሳይ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአዳኝ አንበሶች በጣም ቀልጣፋና ፈጣን ቢሆኑም እንኳ በአደን ጊዜ የሚሳካላቸው 30 በመቶ ብቻ ነው። በመሆኑም አንበሶች ከተደቀኑባቸው ትልልቅ አደጋዎች አንዱ ረኃብ ነው። ለአካለ መጠን የደረሰ አንድ አንበሳ ያለው ጥንካሬ እጅግ የሚያስገርም ነው። በቤተሰብ ደረጃ የሚያድኑ እንደ መሆናቸው መጠን ከ1,300 ኪሎ ግራም በላይ ክብደት ያላቸውን እንስሳት የመጣልና የመግደል አቅም እንዳላቸው ይነገራል። አንበሶች በመጀመሪያ ላይ በሰዓት እስከ 59 ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሮጡ ይችላሉ፤ ሆኖም ይህ ፍጥነታቸው እስከ መጨረሻ አይዘልቅም። በዚህ ምክንያት ቀለባቸውን ለማግኘት አድብቶ የመያዝ ዘዴ ይጠቀማሉ። የማደኑን ተግባር 90 በመቶ የሚያከናውኑት ሴቶቹ አንበሶች ቢሆኑም በሚበሉበት ጊዜ ትልቁን ድርሻ የሚያገኙት ትልልቆቹ ወንድ አንበሶች ናቸው። አደን በሚጠፋበት ጊዜ አንዳንዴ አንበሶች በጣም ስለሚርባቸው ያገኙትን መብል ለራሳቸው ግልገሎች እንኳ ለማካፈል ፈቃደኛ አይሆኑም። ታዳኝ ከብዙ ዓመታት በፊት ባለ ግርማ ሞገሱ አንበሳ በመላው የአፍሪካ አህጉር እንዲሁም በእስያ፣ በአውሮፓ፣ በህንድና በፍልስጤም አንዳንድ ቦታዎች ይገኝ ነበር። አዳኝ እንደመሆኑ መጠን ሰውን እየተቀናቀነ የሚኖር እንስሳ ነው። በከብቶች ላይ አደጋ የሚጥልና በሰዎች ላይ ጉዳት የሚያደርስ በመሆኑ አንበሳ ገና እንደታየ በጥይት የሚገደል ፍጡር ሆነ። የሕዝብ ቁጥር ፍንዳታ የአንበሳን መኖሪያ በእጅጉ አመናምኖታል። ዛሬ ከአፍሪካ ውጪ ባለው የዓለም ክፍል በዱር የሚኖሩት አንበሶች በጥቂት መቶዎች ብቻ የሚቆጠሩ ሆነዋል። በአሁኑ ጊዜ አንበሶች ሰው ከሚያደርስባቸው ጥቃት ሙሉ በሙሉ ተጠብቀው መኖር የሚችሉት ጥበቃ በሚደረግባቸው ክልሎች ውስጥና በዱር አራዊት መጠበቂያ ቦታዎች ብቻ ሆኗል። አንበሳ ሲያገሣ አንበሶች በሚያገሡበት ጊዜ በብዙ ኪሎ ሜትር ርቀት ሊሰማ የሚችል ከፍተኛ ድምፅ የማውጣት ልዩ ችሎታ አላቸው። አንበሳ ሲያገሣ የሚያሰማው ድምፅ “እጅግ ማራኪ ከሆኑት የተፈጥሮ ድምፆች” አንዱ እንደሆነ ይነገራል። ብዙውን ጊዜ አንበሶች በጨለማ ሰዓትና ንጋት ላይ ያገሣሉ። ወንዶቹም ሆኑ ሴቶቹ አንበሶች የሚያገሡ ሲሆን አንዳንዴም የመንጋው አባላት በአንድነት ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ያገሣሉ። በአንበሶች ላይ ጥናት የሚያካሂዱ ሳይንቲስቶች አንበሶች የሚያገሡባቸው የተወሰኑ ምክንያቶች እንዳሉ ይናገራሉ። ወንዶቹ አንበሶች የሚኖሩበትን ክልል ድንበር ለማሳወቅ እንዲሁም ሌሎች ወንድ አንበሶች ወደ ክልላቸው እንዳይገቡ ለማስጠንቀቅ ሲሉ ያገሣሉ። በርቀት ወይም በጨለማ ተነጣጥለው ያሉ የአንድ መንጋ አባላት ያሉበትን ቦታ ለመጠቆም ያገሣሉ። በተጨማሪም አንድ እንስሳ ከገደሉ በኋላ ለሌሎቹ የቤተሰቡ አባላት ምግቡ ያለበትን ቦታ ለማሳወቅ ያገሣሉ። አንበሶች በሚያድኑበት ጊዜ የሚያድኗቸውን እንስሳት ለማስደንበር ብለው አያገሡም። ሪቻርድ ኤስቲዝ ዘ ቢሄቭየር ጋይድ ቱ አፍሪካን ማማልስ በተባለው መጽሐፋቸው ላይ “አንበሶች የሚያድኑትን እንስሳ ለማጥመድ ሲሉ ሆን ብለው እንደሚያገሡ የሚጠቁም ምንም ነገር የለም (በተሞክሮዬ እንዳየሁት በአንበሳ የሚታደኑ እንስሳት አንበሳ ለሚያሰማው የግሣት ድምፅ ብዙም ትኩረት አይሰጡም)። \n \nጥያቄ: አዳኝ አንበሶች በጣም ቀልጣፋና ፈጣን ቢሆኑም እንኳ አደን ጊዜ የሚሳካላቸው ስንት በመቶ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 30 በመቶ ብቻ ነው ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኮንታ የኮንታ ብሔረሰብ የአፍ መፍቻ ቋንቋ ኮንቲኛ ሲሆን፣ ከ1990 ዓ.ም ጀምሮ ከንግግር ቋንቋነት ባሻገር የትምህርትና የሥራ ቋንቋ በመሆን አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። አብዛኛው የብሔረሰቡ አባላት ከአፍ መፍቻ ቋንቋቸው በተጨማሪ ዳውሮኛ፣ ጋሞኛ፣ ወላይትኛና አማርኛ ይናገራሉ። የኮንታ ብሔረሰብ ባህላዊ አስተዳደር መዋቅር ተዋረዳዊ ኃላፊነትና ተግባር ባላቸው የተለያዩ ክፍሎች የተደራጀ ነው፡፡ በእዚህ መዋቅር የሁሉም የበላይ ካዎ ወይም ንጉስ በመባል የሚታወቅ ሲሆን ከማላ ጎሳ ይመረጣል፡፡ በኮንታ ብሔረሰብ ስድስት ባህላዊ የጋብቻ ዓይነቶች ያሉ ሲሆን፣ እነዚህም በቤተሰብ ስምምነት የሚፈጸም ጋብቻ (ቦሣ) የለፋ ጋብቻ (ላታ) በተጋቢዎች ስምምነት የሚፈጸም ጋብቻ (ማቆ) የቃል ጋብቻ (ያኤኤኩዎ) እና ሚሽቶ (የምትክ ጋብቻ) በመባል ይታወቃሉ፡፡ ከእነዚህ የጋብቻ ዓይነቶች በብዛት ሲከናወን የሚስተዋለው በቤተሰብ ስምምነት የሚፈጸመው የቦሣ ጋብቻ ነው፡፡ ከብሔረሰቡ ባህላዊ የሙዚቃ መሣሪያዎች ፂፄ፣ ጫቻ፣ ዛይ፣ዲንኬ እና ኡልዱዶ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ እነዚህ የትንፋሽና የምት የሙዚቃ መሣሪያዎች ለለቅሶና ለደስታ ጊዜ ያገለግላሉ፡፡ በተለይ ኡላዱዶ የተሰኘው የትንፋሽ መሣሪያ ከድኩላ ቀንድ ተበስቶ የሚሠራ ሲሆን ከብቶቻቸው ሆራ (ጨውነት ያለው ውሃ) ሊያጠጡ የሚወስዱ እረኞች ይነፉታል፡፡ የኮንታ ባህላዊ የቤት አሠራር ከፍልጥ እንጨት፣ ከቀርከሀ ከሰንበሌጥና ከሣር የሚዘጋጅ ሲሆን በደጋውና በቆላው አካባቢ ልዩነት አለው፡፡ ሱልሶ፣ ሲሊሶ፣ ኡስታ፣ ጨዲያ፣ ኩበዋ፣ ቦሩዋ (ዱቢያ) እና ባጨራ የኮንታ ብሔረሰብ ዋነኛ ባህላዊ ምግቦች ናቸው፡፡ ሲልሶ ለአብነት ከምን እንደሚሠራ እንይ፡፡ ሲልሶ ከጥሬ ሥጋ፣ ከቅቤ፣ ከደም፣ ከሀሞት እና ከተለያዩ የማጣፈጫ ቅመሞች ከተዘጋጀ በኋላ ከተለበለበና በክብ በተቆረጠ የእንሰት ቅጠል ላይ ለቤተሰቡ አባላት ይቀርብና በቡላ ወይም በቆጮ ይበላል፡፡ በብሔረሰቡ ወንዶች ከአቡጀዲ በእጅ የተሰፋ እጀ ጠባብ ሸሚዝና ሱሪ እንዲሁም ሀሲያ የተባለ በእጅ የተፈተለ ልብስ ሲለብሱ ሴቶች በኋላ በኩል ባለወጥ ጥለት የሆነውን ማዳ የተባለ የእጅ ፈትል ይለብሳሉ፡፡ \n \nጥያቄ: የኮንታ ብሔረሰብ ባህላዊ ምግብ ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሱልሶ፣ ሲሊሶ፣ ኡስታ፣ ጨዲያ፣ ኩበዋ፣ ቦሩዋ (ዱቢያ) እና ባጨራ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nመስከረም ፩ መስከረም ፩ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ የመጀመሪያው ዕለት ነው። በመሆኑም ቀኑ የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት በዓል ወይም ዕንቁጣጣሽ በመባል ይታወቃል። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ ሉቃስ ፫፻፷፭ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ዮሐንስ፤ ማቴዎስ፤ እና ማርቆስ ደግሞ ፫፻፷፬ ቀናት ይቀራሉ። ==ታሪካዊ ማስታወሻዎች== ፲፭፻፯ ዓ/ም - የፖሎኝ ሠራዊት በኦርሻ ውግያ በሩስያ ላይ አሸነፈ። ፲፮፻፺፮ ዓ/ም - በጎንደር ትልቅ አውሎ ነፋስ ተነስቶ ብዙ የሕዝብ እና የንጉሥ ቤቶችን ሲያወድም፣ የሸዋው ታላቅ መኮንን አቤቶ ወልደ ብርሃን እና ፵ ሰዎች ሞተዋል። ፲፰፻፮ ዓ/ም - የአሜሪካ መርከቦች በኤሪ ሐይቅ በእንግሊዝ አሸነፉ። ፲፰፻፺ ዓ/ም - በላቲመር ፔንሲልቬኒያ ፖሊሶች 19 የማዕደን ሰራተኞች በእልቂት ገደሉ። ፲፱፻፲፭ዓ/ም - የእንግሊዝ አስተዳደር በፍልስጤም ጀመረ። ፲፱፻፴፮ ዓ/ም - የጀርመን ሃያላት ሙሶሊኒን ከእስር በት እንዲያመልጥ ነጻ አወጡት። ፲፱፻፹፪ ዓ/ም - የብረት መጋረጃ በኰሙኒስት ሃንጋሪና በኦስትሪያ መሃል ተከፍቶ ወዲያው ብዙ ሺህ የቀድሞው የምሥራቅ ጀርመን ዜጋዎች ወደ ምዕራብ ፈለሱ። ፲፱፻፺፬ ዓ/ም - አራት አውሮፕላኖች በአረብ ተዋጊዎች ተሰርቀው በአለም ንግድ ሕንጻና በፔንታጎን ተጋጭተው 3000 ያህል ሰዎች ተገደሉ። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የመጀመሪያው ቀን መች ይጀምራል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ መስከረም ፩ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nስብሐት ገብረ እግዚአብሔር ስብሐት (ስብሐት ለአብ) ገብረ እግዚአብሔር (ሚያዝያ 27 [1928]ዓ.ም. - ሰኞ፣ ቀን ትግራይ ጠቅላይ ግዛት፣ አድዋ አውራጃ፣ እርባ ገረድ በተባለች መንደር ከአባቱ ከቄስ ገብረ እግዚአብሔር ዮሐንስ እና ከወይዘሮ መአዛ ወልደ መድኅን ተወለደ። ትምህርቱን በስዊድን ሚሲዮን፣ እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተከታትሎ በትምህርት አስተዳደር የመጀመሪያ ዲግሪውን ተቀብሏል። በአስፋ ወሰን ትምህርት ቤት በእንግሊዝኛ መምህርነት ለ2 ዓመት አገልግሏል። በመቀጠልም ከየተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፤ ሳየንስ እና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ባገኘው የትምህርት እድል አማካይነት ወደ ፈረንሳይ (ኤክስ አን ፕሮቫንስ) በመሄድ ከ1962-1964 ቆይቷል። የሄደበትን ትምህርት አጠናቆ ምስክር ወረቀት ባይቀበልም ቆይታው ከአውሮፓ ባህል እና ስነ-ጽሁፍ እንዲተዋወቅ በጣም እንደረዳው ይናገራል። ወደ ፈረንሳይኛ «Les Nuits d'Addis-Abeba» ተብሎ በፍራንሲስ ፋልሴቶ የተተረጎመውን የልብ-ወለድ ድርስቱን «ሌቱም አይነጋልኝ»ን ብዙውን ለመጻፍ የበቃው እዚያው በፈረንሳይ እንደሆነም ይናገራል። ይኸው ድርሰቱም ወደ ፈረንሳይኛ ቋንቋ የተተረጎመ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ልብ-ወለድ ነው። ስብሐት ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በኋላ በመነን መጽሄት የዝግጅት ክፍል ውስጥ ሰርቷል። በ1966 ዓ.ም. ወታደራዊው ደርግ ስልጣን ከያዘ በኋላ ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ሲቋቋም በአርታኢነት ተቀጥሮ ሰርቷል። በመንግሥት ትእዛዝም ከሌሎች ሰዎች ጋር በመሆን የካርል ማርክስ ሥራ የሆነውን ካፒታልን ከእንግሊዝኛ ወደ አማርኛ በመመለስ ሥራ ላይ ተሳትፏል። ብዙዎቹ የስብሐት ሥራዎች በተጻፉበት ጊዜ ለመታተም ባይታደሉም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን የህትመትን ብርሃን ለማየት በቅተዋል። ጽሁፎቹ ረዘም ላለ ጊዜ ሳይታተሙ ለመቆየታቸው ዋነኛው ምክንያቱ ስብሐት በመጽሐፉ የሚጠቀማቸው ቃላት ብዙዎቹ በኢትዮጵያ ባህል ያደገ አንባቢን አይን የሚያስፈጥጡ፣ ጆሮ የሚያስይዙ በመሆናቸው ነው። በገበያ ላይ በቅርብ የወጡት ድርሰቶቹ ከመጀመሪያ ቅጂያቸው ብዙ ለውጥ እና የአርትኦት ሥራ የተደረገባቸው እንደሆኑ ይነገራል። ስለዚሁ ጉዳይ ለአዲስ ላይቭ በሰጠው ቃለመጠይቅ ላይ ሲናገር «በጨለማ ያልተደረገውን ነገር አንድም የጻፍኩት የለም... ያለውን እንዳለ ነው የምጽፈው» ብሏል። ይህንኑም ከኤሚል ዞላ የአጻጻፍ ዘይቤ የወሰደው እንደሆነ ይናገራል። ስብሐት ገብረእግዚአብሔር ደራሲ፣ አርታኢ፣ ጋዜጠኛ ብቻ አይደለም - የልብ-ወለድ ድርሰት ገጸባህርይም ነው። ደራሲው የተሰኘው የበአሉ ግርማ ልብ-ወለድ በስብሐት ህይወት ላይ ተመስርቶ የተጻፈ ነው። ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር የ2 ወንዶች እና የ3 ሴቶች አባት ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ ነው። \n \nጥያቄ: ከየተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፤ ሳየንስ እና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ያገኘው የትምህርት እድል በየት ሀገር ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ፈረንሳይ (ኤክስ አን ፕሮቫንስ) ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nንጉሡ «አፄ ምኒልክ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ» የሚለውን ስም በተቀዳጁ በማግሥቱ ጥቅምት ፳፯ ቀን ፲፰፻፹፪ ዓ.ም. ወይዘሮ ጣይቱ ብጡል እቴጌ ተብለው ተሰየሙ። እቴጌ ጣይቱም ጳጳሱ አቡነ ማቴዎስ ከንጉሠ ነገሥቱ እጅ የተቀበሉትን ዘውድ ደፉላቸው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በታወቁበት «እቴጌ ጣይቱ ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ» በሚል የክብር ስም ማኅተም ተቀረፀላቸው። እቴጌ ጣይቱ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ተሳትፏቸው የገነነውና በአገር አስተዳደርም ውስጥ ከፍተኛ ሚና መጫወት የጀመሩት ኢትዮጵያ ሚያዝያ ፳፭ ቀን ፲፰፻፹፩ ዓ/ም በውጫሌ ላይ ከኢጣሊያ ጋር በተፈራረመችው ውል ውስጥ በጣልያንኛው ትርጉም ሀገሪቷን ነፃነት እንደሌላት ጥገኛ በማስመሰል ዓላማ ላይ የተመረኮዘ ውንብድና መኖሩ ከታወቀ ወዲህ ነው። ይህ ለአድዋ ጦርነት መነሳት ምክንያትና ዋነኛ መንስዔ የሆነው ጉዳይ ሊታወቅ የቻለው እቴጌ ጣይቱ የውጫሌው ውል አንቀፅ ፲፯ ላይ ዓለቃ ዓፅመ ጊዮርጊስ የተባሉት ቋንቋ አዋቂ ዓፄ ምኒልክ በሰጧቸው ትዕዛዝ መሠረት የውሉን ሰነድ በመመርመር የውሉ አስራ ሰባተኛው አንቀፅ የያዘውን የትርጉም መዛባት በመግለፅ ጉዳዮ ኢትዮጵያ የምትጐዳበት ስለመለሆኑ ጭምር በማስረዳት በሰጡት ቃል ሲሆን እቴጌ በዚህ ወቅት ነገሮችን በጥንቃቄ የሚከታተሉ ስለነበር ዓፄ ምኒልክ በመጀመሪያ ሳይረዱ ዓለቃ ዓፅመ ጊዮርጊስ እንዲታሰሩ ቢያደርጉም እቴጌ ጣይቱ ግን እኒህ ሰው ትክክለኛ የኢትዮጵያ ወዳጅ መሆናቸውን ለዓፄ ምኒልክ በማስረዳት ከሦስት ዓመታት እስራት በኋላ ማስፈታቸው ይታወቃል። እቴጌ እንደተናገሩትም «ዓፅመ ጊዮርጊስ ቢታሰር ቢፈታም ለሀገሩ የሚገባውን ሠርቶ ነው። ኧረ ለመሆኑ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚለው ዮሴፍ፣ ጣሊያኖች በተንኮል ገብተው በማታለል ይህን የመሰለ ሥራ ሲሠሩ አነጋጋሪ ሆኖ ሳለ እንዴት ሳይስጠነቅቅዎ ቀረ?» በማለት የእቴጌ ጣይቱ የቁጣ መዓት ወደ ዮሴፍ ዞረ። \n \nጥያቄ: የውጫሌ ስምምነት ኢትዮጵያ ከማን ጋር ያደረገችው ስምምነት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከኢጣሊያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበ628 ዓክልበ.፣ ድራኮ የሚባል ጸሃፊ የአቴና ከተማ ሕግጋት ጻፈ፤ ይህም ሕግ እጅግ ጨካኝ ሆኖ ይሙት በቃ ለማንኛውም ጥፋት ወሰነ። በ600 ዓክልበ.፣ የአቴና አለቃ ሶሎን አዲስ ሕገ መንግሥት ፈጠረ። የሰራተኞች ሸክም አቀለለ፣ ነገር ግን ባላባትነት በልደት ሳይሆን በንብረት ብዛት እንዲቈጠር አስደረገ። ክሊስቴኔስ እንደገና በ516 ዓክልበ. በዴሞክራሲያዊ መሠረት የተሻሸለ ለአቴና ሕገ መንግሥት አወጣ። የግሪክ ፈላስፋ አሪስጣጣሊስ በ350 ዓክልበ. ግድም የሕገ መንግሥት ሀሣብ ለይቶ ዐወቀ። በጽሑፎቹ የአቴና፣ የስፓርታና የካርታግና ሕገ መንግሥቶች ያነጻጽራል። በመደምደሚያው የተሻለው ሕገ መንግሥት ከንጉሣዊ፣ ከመኳንንታዊና ከሕዝባዊ ወገኖች የተደባለቀ መሆኑን ገመተ። በሀሣቡ በመንግሥት የሚከፋፈሉ ዜጎች ከማይከፋፈሉ ከባርዮችና ዜጎች ካልሆኑ ሰዎች ልዩነት አደረገ። ሮማውያን መጀመርያ «12ቱ ሰንተረዦች» የተባለውን ሕገ መንግሥት ያወጡ በ457 ዓክልበ. ነበር። ከዚያ በኋላ አንዳንዴ የተለያዩ ሕጎችና ትእዛዛት ይጨምሩበት ነበር እንጂ እስከ መጽሐፈ ቴዎዶስዮስ ድረስ (430 ዓ.ም.) ሌላ ክምቹ ሕገ መንግሥት አልኖረም ነበር። በኋላም በምሥራቁ መንግሥት (ቢዛንታይን) በኩል መጽሐፈ ዩስጢኒያኖስ (526 ዓ.ም.) ለአውሮፓ ከፍ ያለ ተጽእኖ ነበረው። ይህም በምስራቁ ነገሥታት 3ኛ ሌዎን ኢሳውራዊ «ኤክሎጋ» (732 ዓ.ም.) እና በ1ኛ ባሲሌዎስ «ባሲሊካ» (870 ዓ.ም.) በተባሉት ሕገ ፍትሐን ተከተለ። \n \nጥያቄ: ክሊስቴኔስ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተሻሸለ ለአቴና ሕገ መንግሥት ያወጣው መች ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ516 ዓክልበ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአዲስ አበባ አዲስ አበባ ተብላ የተሠየመችው እቴጌ ጣይቱ ኅዳር ፲፬ ቀን ፲፰፻፸፱ (1879) ዓ.ም. ፍልውሃ ፊን-ፊን ወደሚልበት መስክ ወርደው ሳሉ ከዚህ በፊት አይተዋት የማያውቋት አንዲት ልዩ አበባ አይተ ስለማረከቻቸው ቦታውን ‹‹አዲስ አበባ!›› አሉ ይባላል። አዲስ አበባ (ኣዲስ ኣበባ) ኢትዮጵያ ዋና ከተማ ስትሆን በተጨማሪ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ እንዲሁም የብዙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቅርንጫፎችና ሌሎችም የዓለም የዲፕሎማቲክ (የሰላማዊ ግንኙነት) ልዑካን መሰብሰቢያ ከተማ ናት። ራስ-ገዝ አስተዳደር ስላላት የከተማና የክልል ማዕረግ ይዛ ትገኛለች። አብዛኞቹን የሀገሩ ቋንቋዎች የሚናገሩ ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞች የሚኖሩባት ከተማ ናት። ከባሕር ጠለል በ2500 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኘው ከተማ በግምት 2,757,729 በላይ ሕዝብ የሚኖርባት በመሆኗ የሀገሪቱ አንደኛ ትልቅ ከተማ ናት። ከተማዋ እቴጌ ጣይቱ በመረጡት ቦታ ማለትም በፍል ውሐ አካባቢ ላይ በባላቸው በዳግማዊ ምኒልክ በ፲፰፻፸፰ (1878) ዓ.ም. ተቆረቆረች። የሕዝቧ ብዛት በያመቱ 8% (ስምንት በመቶ) እየጨመረ አሁን አምስት ሚሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከእንጦጦ ጋራ ግርጌ ያለችው መዲና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መገኛ ሆናለች። ይህም በመስራቹ የቀድሞው ንጉሠ-ነገሥት ስም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ይባል ነበር። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ከባህር ጠለል 2500 ሜትር ከፍታ የምትገኝ እንዲሁም በሀገሪቱ ትልቋ ከተማ ማን ትባላለች?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አዲስ አበባ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nብርቱካን በዓለሙ ውስጥ ሙቅ አየር በሚገኝበት በሰፊ ይበቅላል፤ የብርቱካንም ጣዕም ከጣፋጭ እስከ ኮምጣጣ ድረስ ይለያል። ፍሬው በተለመደ ይላጣል ጥሬም ሆኖ ይበላል፤ አለዚያ ለጭማቂው ይጨመቃል። ወፍራምና መራራ ልጣጩ በተለመደ ወደ ቆሻሻ ይጣላል፤ ነገር ግን በክብደትና በሙቀት አማካኝነት ውሃውን በማስወግድ፣ ለመኖ ሊጠቅም ይችላል። ባንዳንድ የምግብ አሠራር ዘዴ ደግሞ፣ እንደ ጣዕም ወይም እንደ መከሸን ይጨመራል። የልጣጩ አፍአዊው ቆዳ በልዩ መሣርያ በቀጭን ይፋቃልና ይሄ ጣዕሙ ለወጥ የሚወደድ ቅመም ያስገኛል። ከልጣጩ በታች ያለው ነጭና ሥሥ ሽፋን ስለማይረባ ይጣላል። ደግሞ የብርቱካን ዘይት አስታጋሽ መዓዛ ስላለው በሕክምና ይጠቅማል። \n \nጥያቄ: የብርቱካን ልጣጭ ለምን ይጠቅማል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ለመኖ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሳህሌ ደጋጎ ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ከእናታቸው ከወይዘሮ ደጊቱ ፈይሣ እና ከባላንባራስ ደጋጎ አለቤ አብራክ በ1923 ዓ/ም በምዕራብ ወለጋ ልዩ ስሙ ነጆ ከተባለው ሥፍራ ተወለዱ። እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በነቀምት አንደኛ ደረጃ እና በአዲስ አበባ ተፈሪ መኮንን ት/ቤት ዘመናዊ ትምህርቱን ከተከታተለ በኋላ በነበረው ልዩ የውትድርና ፍቅር በቀድሞ 1ኛ ክፍለ ጦር በኋላም ማዕከላዊ ዕዝ ተብሎ በተጠራው የክ/ዘበኛ የጦር ክፍል ውስጥ በ1942 ዓ/ም ተቀጥሯል። በነበረው ሙያዊ ብቃትና ወታደራዊ ሥነ ሥርዓት አክባሪነት ከተራ ወታደርነት በአንድ ጊዜ የሃምሳ አለቅነት ማዕረግ ማግኘት የቻለው ሣህሌ፤ በሂደት እስከ ኮሎኔል ደረጃ ደርሷል። ወደ ሙዚቃ ቀማሪነት፣ ዜማና ግጥም ደራሲነት እንደዚሁም ወደ የማዕከላዊ ዕዝ የሙዚቃ ባንድ ኃላፊነት ከመሸጋገሩ በፊት በእግረኛ ባንድ ውስጥ “ክላርኔት” የተሰኘው የሙዚቃ መሣሪያ ተጫዎች የነበረው ሣህሌ ደጋጎ፣ የሙዚቃን ትምህርት የቀሰመው ከፈረንሣዊው መምህሩ ሙሴ ኒኮ መሆኑን የሕይወት ታሪኩ ላይ ተጠቅሷል። ከክላርኔት በተጨማሪ “አኮርዲዮን፣ አልቶ-ሳክስ፣ ፒያኖ” የተሰኙትን የሙዚቃ መሣሪያዎችንም በብቃት ይጫወት ነበር። በጠቅል ራዲዮ ጣቢያ (በተቋቋመ ጊዜ ) በአኮርዲዮን ጥዑም ዜማ ለጣቢያው አድማጮች ሲያንቆረቁር ከነበሩት የሙዚቃ ሰዎች መካከል ሣህሌ ደጋጎ የመጀመሪያው ነበር። ከእነ ሻለቃ ግርማ ይህደጎ፣ ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ እና ከሻለቃ ባሻ ገብረዓብ ተፈሪ ጋር በመሆን የክቡር ዘበኛ ኦርኬስትራን ስም እፁብ ድንቅ በማድረጉ በኩል የበኩሉን ሚና ተጫውቷል። ግጥምና ዜማ ደራሲ ከመሆኑም ባሻገር የአጫጭር እና ረዣዥም ድራማዎች ፀሐፊ የነበረው ሣህሌ፣ «ሁለገብ የታሪክ ማኅደር» ያሰኘውን ተግባር በሕይወት ዘመኑ አከናውኗል። \n \nጥያቄ: ኮሎኔር ሣህሌ ደጋጎ በእግር ባንድ የትኛውን የሙዚቃ መሳሪያ ይጫወቱ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ክላርኔት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሜሪላንድ ሜሪላንድ (እንግሊዝኛ፦ Maryland) በአሜሪካ የምትገኝ ስቴት ስትሆን ምዕጻረ ቃሏ MD ወይም Md. ነው። ሜሪላንድ ከአሜሪካ አስራሶስት ጥንታዊ ስቴቶች አንዷ ናት። ከሜሪላንድ ጋር የሚገናኙ ስቴቶች ፔንስልቫኚያ ፣ ቨርጂኚያ ፣ ዌስት ቨርጂኚያ ፣ እና ዴላዌር እያሉ፤ ደግሞ በኮለምቢያ ክልል (ዋሽንግተን ዲ.ሲ.)ና በአትላንቲክ ውቂያኖስ ትወሰናለች። የቼሳፒክ ወሽመጥ ስቴቱን መሃል ለመሃል ይከፍለዋል። የሜሪላንድ ከፍተኛ ቦታ የባክቦን ተራራ ጫፍ ነው። የሜሪላንድ አየር ሁኔታ ከቦታ ቦታ ይለያያል። የምስራቅ ክፍሉ ሞቃታማ በጋና መካከለኛ ክረምት የአየር ሁኔታ ሲኖረው የምዕራብ ክፍሉ ደግሞ መካከለኛ በጋ እና በጣም ቀዝቃዛ ክረምት አለው። የሜሪላንድ ጠቅላላ ምርቶች በ2003 እ.ኤ.ኣ. ወደ 212 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ነው። በዚሁ ዓመት የአንድ ሰው የዓመታዊ ገቢ በኣማካይ 37,446 የአሜሪካን ዶላር ነበር ፣ ከአገሩ 5ኛ። ከፍተኛ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ፣ ወታደራዊ ካምፖች እና የሳይንስና የሕክምና ተቋማት በዚሁ ክፍላገር ይገኛሉ። የስቴቱ ዋና ያውሮፕላን ማረፊያ ባልቲሞር-ዋሽንግተን ዓለም አቀፍ ያውሮፕላን ማረፊያ (BWI) ነው። በ1996 የሜሪላንድ ጠቅላላ የህዝብ ብዛት 5,558,058 ነው ተብሎ ይገመታል። ከዚሁ ውስጥም 583,900ቹ ወይም 10.6 በመቶ ሌላ ስቴት ወይም አገር የተወለዱ ነዋሪዎች ናቸው። አብዛኛው ህዝብ የስቴቱ መዓከላዊ ክፍል ውስጥ ይኖራል። \n \nጥያቄ: በ2003 እ.ኤ.ኣ. የሜሪላንድ ስቴት ነዋሪዎች ባላቸው አማካኝ የነፍስ ወከፍ ዓመታዊ ገቢ መጠን ከአሜሪካ ስንተኛ ደረጃ ይዞ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 5ኛ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሁዋዌ የተሰኘው ግዙፍ የቻይና ቴሌኮም ኩባንያ በብሪታኒያ የ5ጂ ኢንተርኔት አገልግሎት ሊሰጥ መሆኑ ተሰምቷል። የብሪታኒያው ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ሀገራቸው ከሁዋዌ ቴክኖሎጂ ኩባንያ ጋር በቅንጅት ለመስራት ፍላጎት ያላት መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ መሰረትም ኩባንያው በቀጣይ በብሪታኒያ የ5ጂ ኢንተርኔት አገልግሎት መስጠት በሚችልበት ሁኔታ ላይ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ነው የገለጹት። ሁዋዌ ቻይና ከአሜሪካ ጋር የንግድ ጦርነት ውስጥ መግባቷን ተከትሎ በዩናይትድ ስቴትስ አገልግሎት እንዳይሰጥ ክልከላ የተደረገበት መሆኑ ይታወቃል። ከዚህ ባለፈም ኩባንያው አገልግሎት በሚሰጥባቸው ሀገራት በፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ጣልቃ ይገባል በሚል ካናዳ እና አውስትራሊያን ጨምሮ ከበርካታ ሀገራት ጋር ያለው ግንኙነት መሻከሩ ይታወቃል። ብሪታኒያ ከኩባንያው ጋር በቅንጀት ለመስራት እና አገልግሎቱን ለመጠቀም መፈለጓም ከአሜሪካ ጋር ያላትን ግንኙነት ሊያሻክረው እንደሚችል ተሰግቷል። ምንጭ፦ሲ ጂ ቲኤ ን \n \nጥያቄ: የብሪታንያ ጠቅላይ ሚንስትር ማነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ቦሪስ ጆንሰን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሰርጌይ ብሪን ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን ኦገስት 21, 1973 እ.ኤ.አ. ተወለደ ሩሲያዊ-አሜሪካዊ ሲሆን ጉግልን በመፍጠሩ ይታወቃል። በሩሲያ የተወለደ ሲሆን፥ ብሪን ከላሪ ፔጅ ጋር ጉግልን ከመጀመሩ በፊት ኮምፒዩተር ሳይንስና ሒሳብ አጥንቷል። ብሪን ባሁኑ ጊዜ የጉግል ቴክኖሎጂ ፕሬዝዳንት በመሆኑ ወደ 14.1 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ገንዘብ አለው። ይህም ከዓለም 26ኛ እና ከአሜሪካ 12ኛው ሀብታም ሰው ያደርገዋል። ሰርጌይ በሞስኮ፣ ሩሲያ ለየይሁዳ ቤተሰብ ተወለደ። 6 ዓመቱ ሲሆን ሰርጌይና ቤተሰቡ ወደ አሜሪካ መጡ። አባቱ ሚካኤል በሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ ማቲማቲሻን ሆኖ እስክ ዛሬ ድረስ ያስተምራል። የስርጂ እናት ዩጂኒያ ብሪን ማቲማቲሻንና ሲቭል ኢንጅነር ሆና ለናሳ ትሰራለች። ሳሙኤል የሚባል ታናሽ ወንድምም አለው። ሰርጌይ በኮምፒዩተር ዕድገት ጊዜ በማደጉ የኮምፒዩተር ፍላጎቱ ከልጅነቱ ነው የጀመረው። መጀመሪያው ያገኘው ኮምፒዩተር አንድ ኮሞዶር 64 ሲሆን ይህንንም ከአባቱ ዘጠነኛው ልደት በዓሉ ላይ ነው ያገኘው። በሒሳብና ኮምፒዩተር ያለውን ተስዕጦም ገና ትንሸ እያለ ነው ያሳየው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በፔንት ብራንች ሞንቴሶሪ ትምህርት ቤት የወሰደ ሲሆን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ በኤላኖር ሩዝቬልት ትምህርት ቤት አጠናቋል። ቤተስቡም የሒሳብ ዕውቀቱንና ሩሲያኛው በማዳበር ረድተውቷል። በሴፕቴምብር 1990 እ.ኤ.አ.፣ ሰርጌይ ሒሳብና ኮምፒዩተር ሳይንስ ለማጥናት ሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ፣ ኮሌጅ ፓርክ ገባ። በሜይ 1993 እ.ኤ.አ. የባችለር ሳይንስ ካማግኘቱ በኅላ በስኮላርሺፕ ኮምፒዩተር ሳይንስን ለማጥናት ወደ ስታንፎርድ ዩኒቨርስቲ ሄደ። ከዛም ከታሰበው ጊዜ በፊት በኦገስት 1995 እ.ኤ.አ. የማስተርስ ዲግሪውን ተቀበለ። ባሁኑ ጊዜ ግን የፒ.ኤች.ዲ. ጥናቱን ላልተወስነ ጊዜ አቋርጦ ጉግል ውስጥ እየሰራ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን የተማረው የት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በኤላኖር ሩዝቬልት ትምህርት ቤት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየአሜሪካ ታላቅ ማኅተም የአሜሪካ ብሔራዊ ምልክት የአሜሪካ ታላቅ ማኅተም ይባላል። መጀመርያው የተገለጸው በ1774 ዓ.ም. ነበር። እንዲያውም በይፋ 'አርማ' ሳይሆን 'ማኅተም' ነው። ነገር ግን ይፋዊ አርማ ስለማይኖር በዘልማድ ይህ ማኅተም እንደ አርማ ይጠቀማል። በአሜሪካ ዶላር ላይ (ከ1927 ዓ.ም. ጀምሮ) እንዲሁም በአሜሪካ ፓስፖርት ላይ ይታያል። በማኅተሙ ፊት ላይ ክንፎቹን የሚዘረጋ የመላጣ ንሥር ስዕል እሱም የአሜሪካ ምልክት ይታያል። በግራው ጥፍሩ (ከንሥሩ አንጻር) ውስጥ አሥራ ሦስት ፍላጻ ይዟል። እነርሱም ከእንግሊዝ ያመጹ የመጀመርያ 13 ክፍላገሮች ያመልክታሉ። በቀኙም ጥፍር የወይራ ቅርንጫፍ ይይዛል። ይህ 13 ቅጠልና 13 ፍሬዎች አሉበት። ፍላጻ የጦር ምልክትና ወይራ የሰላም ምልክት በመሆኑ የንሥሩ ራስ ወደሱ ቀኝ ሲዞር ስላምን ይመርጣል እንደ ማለት ነው። በመንቁራው ውስጥ ደግሞ E PLURIBUS UNUM የሚለውን መፈክር ይይዛል። ይህም በሮማይስጥ ማለት 'አንድ ከብዙ' ነው። ከራሱ በላይ 13 ከዋክብት በሰማያዊ በስተኋላ መደብ አለ። እኚህ ከዋክብት የዳዊት ኮከብ ይሠራሉ። በፍርምባው ላይ የሚሸክመው ጋሻ እንደ አሜሪካ ሰንደቅ አለማ ዝንጉርጉር ነው። በማኅተሙ ጀርባ ላይ ያልተጨረሰ ሀረም (ፒራሚድ) ይታያል። ይህ 13 ደረጃዎች ሲኖሩት በመሠረቱ ላይ MDCCLXXVI ይላል። ይህ በሮማይስጥ ቁጥሮች ማለት '፼፯፻፸፮' ወይም 1776 ሲሆን በአውሮጳውያን አቆጣጠር የአሜሪካ ነጻነት አዋጅ የተፈረመበት አመት (1768 ዓ.ም.) ለማመልከት ነው። በሀረሙ ጫፍ ፈንታ 'የእግዚአብሔር ጥበቃ ዓይን' የሚባል ምልክት ይታያል። በዚሁ ዙሪያ «ANNUIT CŒPTIS» የሚለው መፈክር አለ፤ ይህም በሮማይስጥ 'የተጀመረው ተስማምቶታል' ለማለት ነው። በግርጌው ደግሞ «NOVUS ORDO SECLORUM» የሚል መፈክር እያለ ይህ ትርጉም 'የዘመናት አዲስ ሥርዓት' ነው። \n \nጥያቄ: የአሜሪካ ብሔራዊ ምልክት ከራሱ በላይ ያሉት 13 ከዋክብት በሰማያዊ በስተኋላ መደብ ላይ ያሉት ምን ይሰራሉ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የዳዊት ኮከብ ይሠራሉ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nፀሐይ ፀሓይ በምድር ሥርዐተ-ፈለክ መኻል ያለች ኮከብ ናት። ምድር ሞላላ ቀለበት በሚመስል የዑደት ምሕዋር እየተጓዘች ፀሓይን ትዞራታለች። ሌሎች ሰማያዊ አካላትም፣ ፈለኮች፣ ፈለክ-አስተኔዎች፣ ጅራታም ከዋክብት እና ኅዋዊ ብናኞች በፀሓይ ዙሪያ ይዞራሉ። ምድር በፀሓይ ዙሪያ የምታደርገውን አንድ ዙር ጉዞ ለመጨረስ አንድ ዓመት ይፈጅባታል፤ ይህን ጉዞ ስታደርግም በገዛ ራሷ ዘንጎ ወይም ምሽዋር ዙሪያ እየሾረች ነው። ምድር በፀሓይ ዙሪያ የምታደርገው ዙረት ወቅቶች በዓመታዊ ዑደት እንዲለዋወጡ ከሚያደርጉት ምክንያቶች አንዱ ሲኾን፣ በራሷ ዘንጎ ዙሪያ የምታደርገው ሹረት ደግሞ በዕለታዊ ዑደት መዓልት (ቀን) እና ሌሊት ለሚያደርጉት መፈራረቅ ምክንያት ነው። ፀሓይ ለሥርዐተ-ፈለካችን በጣም ብሩህ የኾነ ብርሃን ትሰጣለች። ያለ ፀሓይ ብርሃን ሙቀትም ኾነ ሕይወት በምድር አይኖርም ነበር። ለምሳሌ አረንጓዴ ዕፅዋት ያለ ፀሓይ ብርሃን ሊኖሩ አይችሉም፤ ለህልውናቸው የሚያስፈልጓቸውን ካርቦን ዳይኦክሳይድ እና አልሚ ምግቦች ለማስተጻመር የሚችሉት በፀሓይ ብርሃን ብቻ ነውና። ከምድር ይልቅ ለፀሓይ ይበልጥ ቅርብ የኾኑ ፈለኮች ለከፍተኛ ጨረር እና ግለት የተጋለጡ በመኾናቸው በምድር ላይ ላለው ዐይነት ሕይወት ተስማሚ አይደሉም። ከምድር ጋር ሲነጻጸር ከፀሓይ በጣም ርቀው ያሉ ፈለኮችም ለሕይወት መኖር ምቹ ኹኔታዎች የሏቸውም፤ በቂ ብርሃን እና ሙቀት ካለማግኘታቸው የተነሣ። \n \nጥያቄ: መሬት በራሱ ዙሪያ የምታደርገው ሹረት ውጤቱ ምንድን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ መዓልት (ቀን) እና ሌሊት ለሚያደርጉት መፈራረቅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ለወጣት ለአዛውንት የሚመቹ ደግ እናት፡፡ በኢትዮጵያ የሚድያ ታሪክ ስም ያተረፉ፡፡ ለምርምር የማይደክሙ፡፡ ተወዳጅ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን እነሆ ታሪካቸውን አቀረበ፡፡ ጋዜጠኛዋ በ79 አመታቸው ሀምሌ 14 2013 ህይወታቸው አልፏል፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ በ1934 አመተ ምህረት ከአባታቸው ከአቶ መኩሪያ ወልደስላሴ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ሶስና ወርቅነህ ተወለዱ፡፡ እናታቸው ወይዘሮ ሶስና ወርቅነህ የሀኪም ወርቅነህ እሸቴ ልጅ ናቸው፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ የአንደኛ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በሳንፎርድ ተማሪ ቤት ነበር የተከታተሉት፡፡ ወይዘሮ እሌኒ ያደጉት ካዛንቺስ አካባቢ ሲሆን የልጅነት ዘመናቸው በደስታ የተሞላ ነበር፡፡ በተለይ በሳንፎርድ ተማሪ ቤት ጥሩ የእንግሊዝኛ ችሎታቸውን ከማዳበራቸው በላይ ደስ የሚል የመዝናኛ ጊዜን አሳለፈው ነበር፡፡ ቴኒስ መጫወት ፤ ዋና መዋኘት ፣ ቴአትር ማየት እና መተወን ደስ ይላቸው ነበር፡፡ እንዲያውም ለልኡል መኮንን ሆስፒታል ማሰሪያ የገቢ ማሰባሰቢያ ላይ ቴአትር መስራታቸውን ወይዘሮ እሌኒ በህይወት በነበሩ ጊዜ ተናግረዋል፡፡ በተለይ አያታቸው ክቡር ሀኪም ወርቅነህ እሸቴ ዳንስ ያለማምዷቸው እንደነበር አይዘነጉትም፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ፣ ማህበራዊ ሳይንስ የማጥናት ግብ ቢኖራቸውም ቤሩት የነጻ የትምህርት እድል አግኝተው ወደዚያ በ1951 ግድም ያቀናሉ፡፡ ነገር ግን የነርስነትን ትምህርት ቢጀምሩም አቋርጠው ወደ እናት ሀገራቸው ይመለሳሉ፡፡ በመቀጠልም ወደ ብስራተ ወንጌል ሬድዮ በማቅናት በእንግሊዝኛው ክፍል ተቀጠሩ፡፡ ያኔ በሬድዮ ከወይዘሮ እሌኒ ጋር ይሰሩ ከነበሩት ባለሙያዎች መካከልም ጋዜጠኛ ልኡልሰገድ ኩምሳ ይጠቀሳል፡፡ ወይዘሮ እሌኒና ጋዜጠኛ ልኡልሰገድ ዜና ሲያቀርቡ ያለበት ቪድዮ ከዚህ ጽሁፍ አዘጋጅ ዘንድ ይገኛል፡፡ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ቻርተር በግንቦት 18 1955 ሲፈረም ጋዜጠኛ ከነበሩት መካከል ወይዘሮ እሌኒ ይጠቀሳሉ፡፡ በወቅቱ ገና የ21 አመት ወጣት የነበሩት ወይዘሮ እሌኒ መሪዎች ሲመጡ የተደረገውን ታሪካዊ አቀባበል በፍጹም አይዘነጉትም፡፡ \n \nጥያቄ: ወ/ሮ እሌኒ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በየት ተከታተሉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በሳንፎርድ ተማሪ ቤት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየኩላሊት ጠጠር የኩላሊት ጠጠር የሚባለው በኩላሊት ውስጥ የጠጣር ነገሮች መጋገር ወይም መሰብሰብ ሲሆን የጠጣር ነገሮቹም ምንጭ በሽንት ውስጥ የሚገኙ የምግብ ንጥረ ነገሮች ናቸው። ፹ በመቶ (80%) ወንዶች በአብዛኛው የኩላሊት ጠጠር ህመም ከ ፴(30)-፵(40) ባለው እድሜአቸው ሲጀምራቸው ሴቶች ላይ ግን ዘግይቶ ይከሰታል። የኩላሊት ጠጠሮች በአመዛኙ ምንም የህመም ስሜትና ጉዳት ሳያስከትሉ በሽንት መስመር ውስጥ አልፈው ከሰውነት ይወገዳሉ ነገር ግን ጠጠሮቹ በመጠን ከጨመሩ (፫(3) ሚሜ አካባቢ ከደረሱ) የሽንት ትቦ ሊዘጉ ይችላሉ የሽንት ትቦ በጠጠር መዘጋት ሽንት በቀላሉ እንዳይተላለፍ (ፓስቴርናል አዞቶሚያ) ብሎም ሽንት ወደ ሁዋላ በመመለስና በኩላሊት ውስጥ በመከማቸት ሃይድሮኔፕሮሊስ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል:: ይሄ ችግር (ሃይድሮኔፕሮሊስ) ከታችኛው የጎድን አጥንት አንስቶ እስከ የዳሌ አጥንት ድረስ ባለው ቦታ በብሽሽትና በታችኛው የምግብ መፍጫ ክፍሎች አካባቢ ለህመም ስሜት (ሬናል ኮሊክ) ይዳርጋል። የኩላሊት ጠጠር ከማቅለሽለሽና የማስታወክ ስሜቶች ትኩሳት በሽንት ውስጥ ደም መኖር በሽንት ውስጥ መግል የሚመስል ፈሰሽ እና በሽንት ጊዜ ከከፍተኛ የህመም ስሜት ጋር ሊያያዝ ይችላል። የኩላሊት ጠጠር መኖር በሰውነት አቁዋም ምርመራዎች (ፊዚካል ኤግዛሚኔሽን) በሽንት ምርመራ በራጅ ምርመራ እንዲሁም በበሽተኛው የበፊት የጤና ምርመራ ውጤቶች ድጋፍ ይታወቃል። የአልትራሳውንድ እና የደም ምርመራዎችም የኩላሊት ጠጠር በሽታ መኖሩን ለማወቅ አጋዥ ይሆናሉ። ለኩላሊት ጠጠር መፈጠር ምክንያት ሊሆኑ ከሚችሉ የአመጋገብ ልምዶች መካከል፤ ውሃ በበቂ አለመጠጣት፣ ከፍተኛ የሆነ የእንሥሳት ሥጋ (ፕሮቲን) መመገብ፣ ጨው (ሶዲየም)፣ የተጣሩ ስኳሮች፣ የፍራፍሬ ስኳር (ፍሩክቶስ)፣ ኦክሳሌት የያዙ ምግቦች (ኦክሳሌት በብዙ ዕፅዋት ውሥጥ የሚገኝ ንጥረ ነገር ሲሆን በተለይም በሰባ ዶሮ፣ በጥቀር አዝሙድ፣ ፐርስሊ፣ ስፒናች፣ ካካዎ፣ ቸኮላት፣ ኦቾሎኒ፣ አብዛኛዎቹ እንጆሬዎች ውስጥ ይገኛል)፣ የአፕል ጭማቂ እና የኮላ መጠጦች ናቸው። \n \nጥያቄ: አንድ ሰው የኩላሊት ህመምተኛ ነው የሚባለው የጠጠሩ መጠን ስንት ሲሆን ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ፫(3) ሚሜ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኋንግ ዲ ኋንግ ዲ (ቢጫው ንጉሥ) በቻይና ልማዳዊ አፈ ታሪክ ዘንድ የቻይና ሕዝብ አባትና ንጉሥ ነበረ። የቤተሠቡ ስም «ጎንግሱን» የተሰጠው ስም «ሽወንዩወን» ነበር ይባላል። አባቱ ሻውድየን ተባለ። የተወለደው ሾው ጪው በተባለ ሥፍራ በጩፉ ሲሆን በኋላ ነገዱን ወደ ዥዎሉ ወሰደው፤ በዚያ ገበሬ ሆኖ ድብ፣ ነብርና ባለክንፍ አንበሣ የመሰለ ፍጡር አንዳስለመደ የሚል ትውፊት አለ። ያንጊዜ የኋንግ ዲ ወገን እና የያንዲ (ዩዋንግ) ወገን ለቢጫው ወንዝ ሸለቆ ተወዳዳሪዎች ነበሩ። ሦስተኛ ወገን - የሊ ሕዝብና ንጉሣቸው ቺ ዮው - ደግሞ ጠላቶቻቸው ሆኑ። ሦስት ውግያዎች ተከተሉ። በመጀመርያው የቺ ዮው ሥራዊት ያንዲውን አሸነፈው። ከዚያ ያንዲው ተሸንፎ ወደ ኋንግ ዲ ሸሸ። በሁለተኛው የዥዎሉ ውግያ ኋንግ ዲ እና ቺ ዮው ተጋጠሙ። በዚህ ውግያ ቺ ዮው ጉምን በጥንቆላ ፈጥሮ ኋንግ ዲ እንደገና በተነው፣ ብዙም ሌሎች ጉድ ሥራዎች እንደ ተከሠቱ የሚል ትውፊት አለ። ቺ ዮው በዚህ ውግያ ቢሸነፍም፣ የኮርያ ሕዝብና የህሞንግ ሕዝብ ዛሬውንም እንደ ቅድማያታቸው ይቆጥሩታል። በሦስተኛው የባንጯን ውግያ፣ ኋንግ ዲ በያንዲው ላይ ድል አደረገ። ከዚያ በኋላ ወገኖቻቸው ተባብረው የኋሥያ ብሔር (የቻይና ሕዝብ ቅድማያቶች) ፈጠሩ። ኋንግ ዲ በይፋ የቻይና ንጉሥነት ማዕረግ ወሰደ፤ የዘውድና ቤተ መንግሥት ሥርዓት ጀመረ። ከዚህ በተረፈ ኋንግ ዲ ጋሪና መርከብ እንደ ፈጠረ ይጻፋል። ደግሞ ምኒስትሩ ጻንግችየ መጀመርያ የቻይና ጽሕፈት ፈጠረ፤ የኋንግ ዲ ሚስት ሌዙም ልብስ ከሃር ትል እንዴት እንደሚሠራ አሳየች። የህክምና መጽሓፍ ኋንግዲ ኔጂንግ ሌሎችንም መጻሕፍት እንደ ጻፈ ይታመናል። ከዚህ በላይ የቻይና ስነ ፈለክና የቻይና ዘመን አቆጣጠር ፈጠረ። ስለ ኋንግ ዲ ብዙ ሌሎች ትውፊቶች አሉ። መጀመርያ ሚስቱ ሌዙ ተከታዩን ሻውሃውን ወለደች። 3 ሌሎች ሚስቶች እነርሱም ፋንግሌ፣ ቶንግዩ እና ሞሙ ነበሩት። በተለመደው ታሪክ ዘንድ ለ99 አመት ነገሠ። ታላቅ መቃብሩ በያንአን ከተማ ሲገኝ እስከ ዛሬ ድረስ በየአመቱ በሥነ ስርአት ይከብራል። \n \nጥያቄ: ኋንግ ዲ በይፋ የቻይና ንጉስነት ማዕረግ የወሰደው ስንት ውጊያዎችን ካሸነፈ በኋላ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሦስት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአዲስ አበባ አዲስ አበባ ተብላ የተሠየመችው እቴጌ ጣይቱ ኅዳር ፲፬ ቀን ፲፰፻፸፱ (1879) ዓ.ም. ፍልውሃ ፊን-ፊን ወደሚልበት መስክ ወርደው ሳሉ ከዚህ በፊት አይተዋት የማያውቋት አንዲት ልዩ አበባ አይተ ስለማረከቻቸው ቦታውን ‹‹አዲስ አበባ!›› አሉ ይባላል። አዲስ አበባ (ኣዲስ ኣበባ) ኢትዮጵያ ዋና ከተማ ስትሆን በተጨማሪ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ እንዲሁም የብዙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቅርንጫፎችና ሌሎችም የዓለም የዲፕሎማቲክ (የሰላማዊ ግንኙነት) ልዑካን መሰብሰቢያ ከተማ ናት። ራስ-ገዝ አስተዳደር ስላላት የከተማና የክልል ማዕረግ ይዛ ትገኛለች። አብዛኞቹን የሀገሩ ቋንቋዎች የሚናገሩ ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞች የሚኖሩባት ከተማ ናት። ከባሕር ጠለል በ2500 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኘው ከተማ በግምት 2,757,729 በላይ ሕዝብ የሚኖርባት በመሆኗ የሀገሪቱ አንደኛ ትልቅ ከተማ ናት። ከተማዋ እቴጌ ጣይቱ በመረጡት ቦታ ማለትም በፍል ውሐ አካባቢ ላይ በባላቸው በዳግማዊ ምኒልክ በ፲፰፻፸፰ (1878) ዓ.ም. ተቆረቆረች። የሕዝቧ ብዛት በያመቱ 8% (ስምንት በመቶ) እየጨመረ አሁን አምስት ሚሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከእንጦጦ ጋራ ግርጌ ያለችው መዲና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መገኛ ሆናለች። ይህም በመስራቹ የቀድሞው ንጉሠ-ነገሥት ስም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ይባል ነበር። \n \nጥያቄ: አዲስ አበባ የተመሰረተችው መች ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ፲፰፻፸፰ (1878) ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበ628 ዓክልበ.፣ ድራኮ የሚባል ጸሃፊ የአቴና ከተማ ሕግጋት ጻፈ፤ ይህም ሕግ እጅግ ጨካኝ ሆኖ ይሙት በቃ ለማንኛውም ጥፋት ወሰነ። በ600 ዓክልበ.፣ የአቴና አለቃ ሶሎን አዲስ ሕገ መንግሥት ፈጠረ። የሰራተኞች ሸክም አቀለለ፣ ነገር ግን ባላባትነት በልደት ሳይሆን በንብረት ብዛት እንዲቈጠር አስደረገ። ክሊስቴኔስ እንደገና በ516 ዓክልበ. በዴሞክራሲያዊ መሠረት የተሻሸለ ለአቴና ሕገ መንግሥት አወጣ። የግሪክ ፈላስፋ አሪስጣጣሊስ በ350 ዓክልበ. ግድም የሕገ መንግሥት ሀሣብ ለይቶ ዐወቀ። በጽሑፎቹ የአቴና፣ የስፓርታና የካርታግና ሕገ መንግሥቶች ያነጻጽራል። በመደምደሚያው የተሻለው ሕገ መንግሥት ከንጉሣዊ፣ ከመኳንንታዊና ከሕዝባዊ ወገኖች የተደባለቀ መሆኑን ገመተ። በሀሣቡ በመንግሥት የሚከፋፈሉ ዜጎች ከማይከፋፈሉ ከባርዮችና ዜጎች ካልሆኑ ሰዎች ልዩነት አደረገ። ሮማውያን መጀመርያ «12ቱ ሰንተረዦች» የተባለውን ሕገ መንግሥት ያወጡ በ457 ዓክልበ. ነበር። ከዚያ በኋላ አንዳንዴ የተለያዩ ሕጎችና ትእዛዛት ይጨምሩበት ነበር እንጂ እስከ መጽሐፈ ቴዎዶስዮስ ድረስ (430 ዓ.ም.) ሌላ ክምቹ ሕገ መንግሥት አልኖረም ነበር። በኋላም በምሥራቁ መንግሥት (ቢዛንታይን) በኩል መጽሐፈ ዩስጢኒያኖስ (526 ዓ.ም.) ለአውሮፓ ከፍ ያለ ተጽእኖ ነበረው። ይህም በምስራቁ ነገሥታት 3ኛ ሌዎን ኢሳውራዊ «ኤክሎጋ» (732 ዓ.ም.) እና በ1ኛ ባሲሌዎስ «ባሲሊካ» (870 ዓ.ም.) በተባሉት ሕገ ፍትሐን ተከተለ። \n \nጥያቄ: ከመጀመሪያው ሕግ ቀጥሎ የአቴናው አለቃ ሶሎን አዲሱን ሕገ መንግሥት መች ፈጠረ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ600 ዓክልበ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአሪዞና አሪዞና (Arizona) በምዕራባዊ ዩናይትድ ስቴትስ የሚገኝ ክፍላገር ነው። ኒው ሜክሲኮ ፣ ዩታህ ፣ ኔቫዳ ፣ ካሊፎርኒያ እና ኮሎራዶ ያዋስኑታል። የአሪዞና ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ የ30 ሰው ሴኔት እና የ60 ሰው ምክር-ቤት አለው። የሪፑብሊካን ፓርቲ በስቴቱ ዋነኛው ፓርቲ ነው። በ2002 እ.ኤ.አ. የአሪዞና ስቴት ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ በጀት 14.3 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በጀት ደግሞ 13.8 ቢሊዮን ዶላር ነው። የስቴቱ ሴኔተሮች እና ምክር-ቤት ተወካዮች ለሁለት-ዓመት ጊዜ ላልተወሰነ ብዛት ይመረጣሉ። ከ4 ጊዜ በላይ በተካካይ መመረጥ ግን አይችሉም። የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በአስተዳዳሪ የሚመራ ሲሆን ለ4 ዓመት ሥልጣን ላይ ይቆያል። ያልተወሰነ ጊዜ መወዳደር ሲቻል ከሁለት ጊዜ በላይ ግን በተካካይ መመረጥ አይፈቀድም። \n \nጥያቄ: በአሪዞና ዋነኛው ፓርቲ ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የሪፑብሊካን ፓርቲ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሰርጌይ ብሪን ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን ኦገስት 21, 1973 እ.ኤ.አ. ተወለደ ሩሲያዊ-አሜሪካዊ ሲሆን ጉግልን በመፍጠሩ ይታወቃል። በሩሲያ የተወለደ ሲሆን፥ ብሪን ከላሪ ፔጅ ጋር ጉግልን ከመጀመሩ በፊት ኮምፒዩተር ሳይንስና ሒሳብ አጥንቷል። ብሪን ባሁኑ ጊዜ የጉግል ቴክኖሎጂ ፕሬዝዳንት በመሆኑ ወደ 14.1 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ገንዘብ አለው። ይህም ከዓለም 26ኛ እና ከአሜሪካ 12ኛው ሀብታም ሰው ያደርገዋል። ሰርጌይ በሞስኮ፣ ሩሲያ ለየይሁዳ ቤተሰብ ተወለደ። 6 ዓመቱ ሲሆን ሰርጌይና ቤተሰቡ ወደ አሜሪካ መጡ። አባቱ ሚካኤል በሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ ማቲማቲሻን ሆኖ እስክ ዛሬ ድረስ ያስተምራል። የስርጂ እናት ዩጂኒያ ብሪን ማቲማቲሻንና ሲቭል ኢንጅነር ሆና ለናሳ ትሰራለች። ሳሙኤል የሚባል ታናሽ ወንድምም አለው። ሰርጌይ በኮምፒዩተር ዕድገት ጊዜ በማደጉ የኮምፒዩተር ፍላጎቱ ከልጅነቱ ነው የጀመረው። መጀመሪያው ያገኘው ኮምፒዩተር አንድ ኮሞዶር 64 ሲሆን ይህንንም ከአባቱ ዘጠነኛው ልደት በዓሉ ላይ ነው ያገኘው። በሒሳብና ኮምፒዩተር ያለውን ተስዕጦም ገና ትንሸ እያለ ነው ያሳየው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በፔንት ብራንች ሞንቴሶሪ ትምህርት ቤት የወሰደ ሲሆን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ በኤላኖር ሩዝቬልት ትምህርት ቤት አጠናቋል። ቤተስቡም የሒሳብ ዕውቀቱንና ሩሲያኛው በማዳበር ረድተውቷል። በሴፕቴምብር 1990 እ.ኤ.አ.፣ ሰርጌይ ሒሳብና ኮምፒዩተር ሳይንስ ለማጥናት ሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ፣ ኮሌጅ ፓርክ ገባ። በሜይ 1993 እ.ኤ.አ. የባችለር ሳይንስ ካማግኘቱ በኅላ በስኮላርሺፕ ኮምፒዩተር ሳይንስን ለማጥናት ወደ ስታንፎርድ ዩኒቨርስቲ ሄደ። ከዛም ከታሰበው ጊዜ በፊት በኦገስት 1995 እ.ኤ.አ. የማስተርስ ዲግሪውን ተቀበለ። ባሁኑ ጊዜ ግን የፒ.ኤች.ዲ. ጥናቱን ላልተወስነ ጊዜ አቋርጦ ጉግል ውስጥ እየሰራ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን ጉግልን ከመጀመሩ በፊት ያጠናቸው የትምህርት ዘርፎች ምን ምን ነበሩ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ኮምፒዩተር ሳይንስና ሒሳብ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: በ1981 ዓ.ም. ንጉሥ ሌቤንጉላ የማዕድን ማውጣት ፈቃድ ለሴሲል ሮድስ መስጠቱ ቦታው በማን ቅኝ እንዲገዛ አደረገ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በብሪታኒያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nናጊብ ማህፉዝ ናጊብ ማህፉዝ በ1988 እ.ኤ.አ. በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን የተቀዳጀ ግብጻዊ ደራሲ ነው። ማህፉዝ ካይሮ ውስጥ ገማልያ በተባለው ሰፈር ዲሴምበር 11፣ 1911 እ.ኤ.አ. ተወለድ። የመጠሪያ ስሙን የወረሰው ሲወለድ አዋላጅ ሃኪም ከነበሩት ከፕሮፌሰር ናጊብ ማህፉዝ ፓሻ ነው። ማህፉዝ ለረጅም ዘመን በመንግስት መስሪያቤቶች ውስጥ ያገለገል ሲሆን በስነ-ጽሁፉም ዘርፍ 34 ወጥ ልብ-ወለዶች፣ ከ350 የሚዘሉ አጫጭር ታሪኮች፣ ከደርዘን በላይ የሲኒማ ድርሰቶች፣ እና አምስት ተውኔቶችን አበርክቷል። በ1971 ያሳተመው «ጭውውት በአባይ ወንዝ ላይ» የተሰኘው ድርሰቱ ተወዳጅነትን ካተረፉለት ስራዎቹ መካከል ሲሆን የገማል አብድል ናስር አገዛዝ በግብጽ ማህበረሰብ ላይ ያደረሰውን ዝቅጠት የሚተች ነው። የገብላዊ ልጆች የተሰኘው ሌላው ልብ-ወለዱ ተምሳሌታዊ በሆነ መልክ እግዚአብሄርን እና የታላላቆቹን እምነቶች መስራቾች (ሙሴን፣ እየሱስን እና መሃመድን) በገጸባህርይነት የቀረጸበት በመሆኑ አምላክን በመገዳደር አስወንጅሎት መጽሃፉም በግብጽ ውስጥ እንዳይሰራጭ ለረጅም ጊዜ ታግዶ ቆይቷል። በ1989 ሳልማን ሩሽዲ ሰይጣናዊ ጥቅሶች (Satanic Verses) የተሰኘ መጽሃፉን በማሳተሙ የኢራኑ መሪ አያቶላህ ሮላህ ኾሚኒ የግድያ ትእዛዝ ካስተላለፉበት በኋላ ግብጻዊው የስነ-መለኮት መርማሪ ኦማር አብዱል ራህማን ለጋዜጠኞች በሰጠው ቃለ-መጠይቅ ላይ «ማህፉዝ 'የገብላዊ ልጆች'ን ሲያሳትም ተገቢው ቅጣት ተሰጥቶት ቢሆን ኖሮ ሩሽዲ 'ሰይጣናዊ ጥቅሶች'ን ለማሳተም ባልደፈረ ነበር» በማለቱ ይህንኑ ቃሉን እንደ ግድያ ትእዛዝ የወሰዱ ጽንፈኞች በ1994 ዓ.ም ማህፉዝን በስለት አንገቱ ላይ በመውጋት ጉዳት አድርሰውበታል። አጥቂዎቹ አላማቸው ማህፉዝን መግደል ነበር ቢባልም እሱ ግን በህይወት ለመትረፍ ችሏል። ይኽ መጽሃፍ ከ2006 መጀመሪያ ወሮች አንስቶ እንደ አዲስ ግብጽ ውስጥ ታትሞ መሰራጨት ጀምሯል። ማህፉዝ የአንዋር ሳዳት መንግስት ደጋፊነቱ የታወቀ ሲሆን ግብጽ ከእስራኤል መንግስት ጋር በካምፕ ዴቪድ ያደረገችው የሰላም ስምምነት ደጋፊም ስለነበር ድርሰቶቹ ለብዙ ዓመታት በአረብ አገራት ታግደው ቆይተው እገዳው የተነሳላቸው የኖቤል ሽልማትን እንዳሸነፈ ከተሰማ በኋላ ነው። ማህፉዝ የኖቤልን ሽልማት ለመቀበል ለግብጽም ሆነ ለአረቡ ዓለም የመጀመሪያው ሲሆን በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑት ሰዎች ሁሉ የረጅም እድሜ ባለቤት በመሆን ሶስተኛ ደረጃን የያዘ ሰው ነው። ማህፉዝ ኦገስት 30 ቀን፣ 2006 አርፎ ቀብሩ በኦገስት 31 ቀን ካይሮ ውስጥ በሚገኘው የአል ረሽዳን መስጊድ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ናጊብ ማህፉዝ የመግደል ሙከራ ተደርጎበት በስለት አንገቱ ላይ በመውጋት ጉዳት ያደረሱበት በስንት ዓመተ ምህረት ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ1994 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዩጋንዳ ዩጋንዳ ሪፐብሊክ (ወይም ዑጋንዳ) በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። በኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ ይዋሰናል። የዩጋንዳ ሰም የመጣው ከቡጋንዳ መንግሥት ነው። ከአረቦችና አውሮፓውያን በ1800ቹ ከመድረሳቸው በፊት ብዙ የሚታወቅ ነገር አልነበረም። በ15ተኛ መቶ ክፍለ-ዘመን ችዌዚ የተባለውን መንግስት በአፈ ታሪክ ይገኛል። አረቦችና አውሮፓውያን በ19ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሲደርሱ ብዙ መንግሥቶች በቦታው ነበሩ። እነዚህም በንዮሮ ፣ ቡሶጋ ፣ ቡጋንዳ ፣ ቶሮ እና አንኮልን ያጠቃልላሉ። ከ1894 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በታላቁ ብሪታን ስትመራ ነበር። የተለያዩ ቦታዎች ከተዋሃዱ በኋላ ዩጋንዳ በ1914 እ.ኤ.አ. ቅርጿን ያዘች። በ1966 እ.ኤ.አ. ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ ሕገ-መንግሥቱን አፍርሰው እራሳቸውን ፕሬዝዳንት አደረጉ። በ1971 እ.ኤ.አ. ኢዲ አሚን ሀገሩን መምራት ጀመሩ። የኢዲ አሚን አመራር 300,000 የሚገመቱ ዩጋንዳውያንን አስጨርሷል። በ1979 እ.ኤ.አ. የታንዛንያ ኃይሎች ኢዲ አሚንን ከሥልጣን ያስወግዳሉ። ሚልተን ኦቦቴ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ግን በ1985 እ.ኤ.አ. እንደገና ይወርዳሉ። ያሁኑ ፕሬዝዳንት ዮወሪ ሙሴቪኒ ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ናቸው። ፕሬዝዳነንቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይመርጣሉ። ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሎ ሲባምቢ ናቸው። ዩጋንዳ በመሬት የተቆለፈች ብትሆንም ታላላቅ የውሃ አካላት አሉ። ከነዚህ ውስጥም ቪክቶሪያ ሐይቅ፣ አልበርት ሐይቅ፣ ክዮጋ ሐይቅ እና ኤድዋርድ ሐይቅ ይዘረዘራሉ። ታላላቅ ከተማዎች በቪክቶሪያ ሐይቅ አቅራቢያ ይገኛሉ። እነዚህም ካምፓላንና እንትቤን ያጠቃልላል። ዩጋንዳ በ70 ወረዳዎች የተከፋፈለች ስትሆን እነዚህም በአራት አመራር ክልሎች ውስጥ ናቸው። አራቱ አመራር ክልሎች ሰሜናዊ ፣ ምሥራቃዊ ፣ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ይባላሉ። ወረዳዎቹ በዋና ከተማዎቻቸው ነው የሚሰየሙት። በዩጋንዳ ውስጥ የመዳብ እና ነጭ ብረት ክምችቶት አሉ። ግብርና ዋናው የኤኮኖሚ ሴክተር ነው። ከ80 በመቶ በላዩ የስራ ኃይል በግብርና ነው የተሰማራው። ቡና ዋናው የኤክስፖርት ትርፍ ምንጭ ነው። ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግሥቱ ከሌሎች ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን በኢዲ አሚን ጊዜ የወደቀውን ኤኮኖሚ ለማንሳት ተጣጥሯል። ዩጋንዳ ለብዙ ብሔረሰቦች ቤት ነው። ከነዚህ ውስጥ ግን አንድ ትልቁን ሕዝብ ብዛት የሚወክል የለም። 40 አካባቢ የሚሆኑ ቋንቋዎች ባሁኑ ጊዜ ይነገራሉ። ከነጻነት በኋላ እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተደርጓል። ብዙ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ ሉጋንዳ ሲሆን የአቴሶ ቋንቋ በሁለተኛነት ይከተላል። ኪስዋሂሊ ዋናው የንግድ ቋንቋ ነው። የዩጋንዳ የትምህርት ስርዐት የሰባት ዓመት መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፣ ስድስት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና ከ3 እስከ 5 ዓመት ከሁለተኛ ደረጃ በኃላ ትምህርት ያጠቃልላል። \n \nጥያቄ: በዩጋንዳ የአቴሶ ቋንቋ በተናጋሪዎች ብዛት በስንተኛነት ይገኛል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በሁለተኛነት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየአባ ጊዮርጊስ ትምህርታቸው የአባ ጊዮርጊስ አባት ሕዝበ ጽዮን በቤተ መንግሥት በንጉሡ ስዕል ቤት ከሚያገለግሉት ካህናት ጋር ይሠሩ ስለነበር ልጃቸው በመልካም አስተዳደግና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት በማስተማር በዕውቀት አሳድገዋቸዋል። በድቁናም አሹመዋቸዋል። ከዚያም በኋላ በንጉሥ ዳዊት ዘመን (፲፫፻፸፮ ፥ ፲፬፻፭) በደብረ ሐይቅ ባሕር ወደምትገኘው የቅዱስ እስጢፋኖስ አባ እየሱስ ሞዐ ገዳምና ታዋቂ ትምህርት ቤት ወስደው ከታላቁ ዓቃቤ ሰዓት አባ ሠረቀ ብርሃን ጉባዔ ተቀላቅለው እንዲማሩ አድርገዋል ። ይሁን እንጂ አባ ጊዮርጊስ በትምህርት ቤቱ የሚሰጡትን የቀለም ትምህርቶች ቶሎ ለማጥናት አልቻሉም ። ወደ ኋላ የመቅረታቸው ዋናው ምክኒያትም አባ ጊዮርጊስ ከመማሩ ይልቅ የማረካቸው በሥራ እየደከሙ የገዳሙን አባቶች መርዳትና የብትህውናው ሕይወት መሆኑ ነው ። ጉዋደኞቻቸው በትምህርት ሲቀድሙአቸው ባዩ ጊዜ እጅግ አዘኑ ። በጾምና ጸሎትም ወደ እግዚአብሔር ጮሁ በፍፁም ልባቸውም አምነው ብርቱ ልመናን ከእመቤታችን ሥዕል ፊት ቁሞ በጠለቀ ተመስጦልቦና እንባን በማፍሰስ ወደ እግዚአብሔር \" የአባቶቻችን አምላክ የምህረት ጌታ ሁሉን በቃልህ የፈጠርክ ሰውንም በረቂቅ ጥበብህ የፈጠርክ አቤቱ አንተ ከልዑል ጌትነትህ ጥበብን ስጠኝ በእውነትም አትናቀኝ እኔ ባሪያህ ነኝ የባሪያህም ልጅ ነኝና \" በማለት ለመኑ ። ከዚህም በኋላ የዓለም ንግሥት የአምላክ እናት ተገለጸችላቸው ። በነሐሴ ፳፩ ቀንም ወደርሳቸው መጣች ፣ በዕውቀትና በትምህርት የሚተጉበትን ኃይል ሰጠቻቸው ። ከዚያም የዜማ የቅኔና የመጽሐፍትን ትርጉዋሜ ትምህርታቸውን በሚገባ አጠናቀቁ ብዙ መጽሐፍትንም ደረሱ ። በዚህም በቀሰሙት ዕውቀታቸው በዜማ በኩል ከቅዱስ ያሬድ ቀጥለው የሚጠሩ አባ ጊዮርጊስ ናቸው። በቤተመቅደስም ዘማሪ ማኅሌታይ ተብለው ይጠራሉ። በዚያም ዘመን ለነገሥት ፣ ለካህናት ፣ ለመኳንንት ፣ ለንቡራነእድ ፣ ለመሳፍንት ፣ ለሁሉም የቤተመንግሥት ሠራተኞች አስተማሪ ሆኑ ። በአንድ ወቅት ግብፃዊው ጳጳስ አቡነ በርተሎሜዎስ “ሥላሴን አንድ ገጽ” ብለው ያምናሉ ተብለው በተከሰሱ ጊዜነገሩን እንዲያጣሩ ከተመረጡት ከቄስ ሐፄ ተከሥተ ብርሃንና ከሐይቁ መምህር ከዐቃቤ ሰዓት ዮሴፍ ጋር አብሮ ተልኮ ነበር፡፡ እነዚህ ሦስት አበውጳጳሱን ካነጋገሩ በኋላ ክሱ ውሸት መሆኑን በማረጋገጥ ስለ ምሥጢረ ሥላሴ የሚገልጠውን የጳጳሱን እምነት በጽሑፍ ይዘው መጡ፡፡ ሊቅነታቸውን የተረዱት ዓፄ ዳዊት አባ ጊዮርጊስን ወደ ቤተመንግሥታቸው በማስገባት የስምንቱም ልጆቻቸው መምህር አድርገዋቸው ነበር ። ከእነርሱም ውስጥ ቅዱስ የተባለው ንጉሥ ቴዎድሮስ እንዲሁም በተለያዩ ጊዜ የነገሡት ንጉሥ እንድርያስ ፣ ዓፄ ይስሐቅ ፣ ንግሥት እሌኒ እና ዓፄ ዘርአ ያዕቆብ ይገኙበታል። ዐፄ ዳዊት በጋብቻ እንዲዛመዱዋቸው ጥረው ነበር ነገር ግን አባ ጊዮርጊስ ራሳቸውን የመንግሥተ ሰማያት ጃንደረባ ማድረግን ስለመረጡ በማስተማሩና በብሕትናው ጸንተው የአመክሮ ጊዜያቸውን ሲጨርሱ አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ገብተው መንኩሰዋል። \n \nጥያቄ: አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጭ የስንቱ የዓፄ ዳዊት ልጆችን መምህር ነበሩ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የስምንቱም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሃሙራቢ ሃሙራቢ (አካድኛ፤ ከአሞርኛ አሙራፒ) ከ1705 እስከ 1662 ዓክልበ. ድረስ ('ኡልትራ አጭር አቆጣጠር') የባቢሎን ንጉሥ ነበረ። አባቱ ሲን-ሙባሊት ማዕረጉን ከተወ በኋላ ወራሹ ሃሙራቢ የባቢሎንን መንግሥት ግዛት በሜስፖጦምያ በጦርነት አስፋፋ። ሃሙራቢ በተለይ የሃሙራቢ ሕገ ፍትሕ ስለሚባለው የ1704 ዓክልበ. ሕገ ፍትሕ ይታወቃል። ሕግጋቱ የተቀረጹ ቁመቱ 2.4 ሜትር በሆነ ድንጋይ ሲሆን በ1893 ዓ.ም. ለሥነ ቅርስ ተገኝቷል። ሃሙራቢ እንደ ሕግ-ሰጪ ንጉሥ ዝነኛ ስለሚሆን፣ ምስሉ በአሜሪካ መንግስት ቤቶች ዛሬው ሊታይ ይችላል። ዋሺንግተን ዲሲ በአሜሪካ ምክር ቤት ውስጥ በእብነ በረድ ተቀርጸው ከ23 ታሪካዊ ሕግ-ሰጪዎች ምስሎች መካከል የሃሙራቢ ምስል አንዱ ነው። በአሜሪካ ላይኛ ችሎት ቤት ውስጥ በደቡብ ግድግዳ ላይ ሃሙራቢ ከታሪካዊ ሕግ-ሰጪዎች ጋራ የሚያሳይ ትርዒት አለ። \n \nጥያቄ: ሃሙራቢ እንደ ሕግ ሰጪ ንጉስ ዝነኛ ስለሚሆን ምስሉ በየት ሀገር መንግስት ቤቶች እስከ ዛሬ ይታያል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ዋሺንግተን ዲሲ በአሜሪካ ምክር ቤት ውስጥ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቢል ክሊንተን ያደጉት በሆት ስፕሪንግስ፣ አርካንሳው ነው። የቢል ክሊንተን አባት ዊሊያም ጄፈርሰን ብላይዝ ጁኚየር፣ ቢል ክሊንተን ከመወለዱ ሶስት ወር በፊት በመኪና አደጋ ሞተዋል። የቢል ክሊንተን እናት ቨርጂኒያ ክሊንተን ኬሊ፣ በ1950 እ.ኤ.ኣ. ሮጀር ክሊንተን የሚባል ሰዉ አገባች። 14 ዓመቱ ሲሆን ቢል ክሊንተን የመጨረሻ ስሙን ወደ ክሊንተን ለወጠ። ክሊንተን በጆርጅታውን ዩኒቨርሲቲ፥ ዋሽንግተን ዲ.ሲ.፣ ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ፥ ኢንግላንድ፣ እና ዬል ዩኒቨርሲቲ፥ ኮነቲኬት ተምረዋል። በ1975 እ.ኤ.ኣ. ሂለሪ ሮድሃምን አገቡና በሊትል ሮክ፥ አርካንሳው መኖር ጀመሩ። ከዚያም በዩኒቨርሲቴ ኦፍ አርካንሳው የሕግ ፐሮፌሰር ሆነው አገልግለዋል። ቢል ክሊንተን የአርካንሳው አስተዳዳሪ ሆኖ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመረጡት በ1978 እ.ኤ.ኣ. ነው። በዛ ጊዜ ከአሜሪካ በዕድሜ ትንሹ አስተዳዳሪ ነበሩ። በ1980 እ.ኤ.ኣ. በፍራንክ ዲ ዋይት ከተሸነፉ በኋላ በ1982 እ.ኤ.ኣ. እንደገና ተመረጡ። ከዛ ጀምሮ እስከ 1992 እ.ኤ.ኣ. ድረስ ለአራት ጊዜ አስተዳዳሪ ሆነው መርተዋል። በ1984 እ.ኤ.ኣ. የአስተዳዳሪ የስልጣን ዕድሜ ከ2 ዓመት ወደ 4 ዓመት አራዝመዋል። በ1992 እ.ኤ.ኣ. ለፕሬዝዳንትነት ተወዳድርው አሸንፈዋል። በ1996 እንደገና ተወዳድረው አሸንፈዋል። \n \nጥያቄ: ቢል ክሊንተን በሕግ ፕሮፌሰርነት የሠሩት የት ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በዩኒቨርሲቴ ኦፍ አርካንሳው ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዳምጠው አየለ ዳምጠው አየለ (23.11. 1944 አ/ም – 27.10. 2006 አ/ም) ባህላዊ የኢትዮጵያ ዘፋኝ ነበር። በሃምሌ 23 1944 አ/ም ከእናቱ ወይዘሮ ሸዋየ ተካና ከአባቱ አየለ ካሰኝ በመራቤቴ ሰሜን ሸዋ ተወለደ። ልጅነቱን በእረኝነት፥ በግብርና እንዲሁም በቆሎ ተማሪነት እንዳሳለፈ ይናገራል። እድሜውም ለትምህርት ሲደርስ ባቅራቢያው በሚገኘው መራኛ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገብቶ ተምሯል። ዳምጠው ህይወቱ እስካለፈችበት ጊዜ ድረስ ለረዥም ጊዜ አብሯት የኖረው ባለቤቱ አልማዝ ይመር ትባላለች። ከአልማዝ ይመር አብዩ ዳምጠውና ቤቴልሄም ዳምጠው የሚባሉ ሁለት ልጆችን አፍርቷል። ዳምጠው መራቤቴ እያለ በየባእላቱ መዝፈን፣ ማቅራራት እንዲሁም መሸለል ይወድ እንደነበር ተናግሯል። በተለይም ጥምቀትን በማድመቅ ይታወቅ ነበር። የ 6ኛ ክፍል ተማሪ እያለ ክፍሌ ሞገስ የሚባል መምህሩ ወደ አዲስ አበባ ይዞት እንደመጣ ይናገራል። ባጋጣሚም የምድር ጦር ማስታወቂያ አውጥቶ ስለነበር ይፈተንና ያልፋል። የምድር ጦር ካምፕ ውስጥም እንዲኖር ይደረጋል። የዘፋኝነት ሙያው በዚህ አጋጣሚ ነበር የጀመረው። ዳምጠው ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማዉና መነሻ የሆነው አበበ ተሰማ እንደሆነ ይናገራል። ዳምጠው አየለ በምድር ጦር ከ 30 አመት በላይ አገልግሏል። የኢትዮዽያ ምድር ጦር በ1927 አ/ም ተመስርቶ በ1983 አ/ም የፈረሰ የሙዚቃ ቡድን ነበር። ዳምጠው በመንግስት ለውጥ ምክንያት እስከፈረሰበት ጊዜ ድረስ አብሮ እንደነበር ይናገራል። ምድር ጦርም እያለ ከነታምራት ሞላ፣ ሲራክ ታደሰ፣ ተክሌ ደስታ ፣ ጥላየ ጨዋቃ፣ ክፍሌ አቦቸር እንዲሁም ሌሎች የጦሩ አባላት ጋር ሰርቷል። ከሌሎች የሙዚቃ ቡድንም ጋር አብሮ ሰርቷል። ለምሳሌ ያክል ከነ ክቡር ጥላሁን ገሰሰ፣ ሙሃሙድ አህመድ፣ ብዙነሽ በቀለ ፣ ሙሉቀን መለስ፣ ፀሃየ ዮሃንስ፣ ቴድሮስ ታደሰ፣ቴድሮስ ካሳሁን እንዲሁም ሌሎችም ጋር ሰርቷል። የዳምጠው አየለ የመጀመሪያ የህትመት ስራው በ1963 አ/ም ሲሆን ወፌ ላላ የሚለው የሸክላ ስራ ነበር። ዳምጠው አየለ ባጠቃላይ 13 ሲዲዎችን ሰርቷል። ዳምጠው አየለ ኖርዌይ ሃገር በስደት ለ 8 አመት ያክል ኖሯል። ኢትዮጵያም ከገባ በኋላ አዲስ አበባ በሚገኘው በቅ/ገብራኤል ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በተወለደ በ 62 አመቱ ሰኔ 27 2006 አ/ም ቀን ህይወቱ አልፏል። የቀብር ስነስርአቱም ወዳጅ፣ ዘመድ እንዲሁም አድናቂዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ዳምጠው አየለ ወደ አዲስ አበባ ይዞት የመጣው ማነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ክፍሌ ሞገስ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጁፒተር እና ሳተርን ጁፒተር እና ሳተርን ከ4 መቶ አመት በሆላ ትላንት ምሽት በአንድ ላይ ገጥመው አንድ ፕላኔት መስለው ታይተዋል፡፡ ፕላኔቶቹ ከቀን ቀን እየተቀራረቡ መጥተው ትላንት ምሽት በአንድ ላይ በመግጠም ደማቅ ብርሃን ፈንጥቀዋል፡፡ የሁለቱ ግዙፍ ፕላኔቶች ምህዋር በየ20 ዓመቱ የሚገናኙ ሲሆን ክስተቱ በብዛት በቀን ውስጥ ስለሚሆን በዓይን ለማየት ከባድ መሆኑ ተገልጿል፡፡ ‘ዘ ስታር ኦፍ ቤቴልሄም’ ወይም የቤቴልሄም ኮከብ ተብሎ በሚጠራው በዚህ ክስተት ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ሰማይ ላይ እጅግ ደማቅ ብርሃን ታይቶ እንደነበር ሳይንቲስቶች መናገራቸውን ዘ ጋርዲያን አስነብቧል፡፡ \n \nጥያቄ: የቤተልሄም ኮከብ ተብሎ የሚጠራው ክስተት ከስንት አመታት በፊት ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከ2 ሺህ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኬንያ የኬንያ ሪፐብሊክ በምስራቅ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በሰሜን ከኢትዮጵያ፣ በሰሜን-ምስራቅ ከሶማሊያ፣ በደቡብ ከታንዛኒያ፣ በምስራቅ ከዩጋንዳ፣ በስሜን-ምዕራብ ከደቡብ ሱዳን፣ በደቡብ-ምስራቅ ከሕንድ ውቅያኖስ ጋር ድንበር ትጋራለች። አውሮፓውያን አካባቢውን ማሰስ የጀመሩት ከ፲፱ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ሲሆን የብሪታንያ መንግሥት የምሥራቅ አፍሪካ ፕሮቴክቶሬትን በ1895 እ.ኤ.አ. አቋቁሟል። ይህ ፕሮቴክቶሬት በ1920 እ.ኤ.አ. የኬንያ ግዛት ተብሎ ተሰይሟል። ነፃ የኬንያ ሪፐብሊክ በዲሴምበር 1963 እ.ኤ.አ. ታወጀ። የኬንያ ስም የመጣው በአፍሪካ በከፍታ ሁለተኛ ከሆነው ከደብረ ኬንያ ተራራ ነው። በዚሁ ተራራ ዙሪያ የሚኖሩት ነገዶች ስሙን «ኪኛ» (በካምባኛ)፣ «ኪሪማራ» (በአመሩኛ)፣ «ኪሬኛ» (በኤምቡኛ)፣ «ኪሪኛጋ» (በኪኩዩ)፣ ወይም «ኬሪ» (በመዓሳይኛ) ይሉታል። የነዚህ ስሞች ሁሉ ትርጉሞች «ቡራቡሬ» ሲሆኑ ይህም ደግሞ «ሰጎን» ማለት ነው፤ አመዳይ ያለበት የተራራው ጫፍ ለተመልካች ቡራቡሬ ወንድ ሰጎንን ያሳስባልና። በኦገስት 2010 እ.ኤ.አ. በተካሄደ ውሳኔ ሕዝብ መሠረት ከብሪታንያ የተወረሰው ሕገ መንግሥት በአዲስ ሕገ መንግሥት ተለውጧል። በአሁኑ ጊዜ ኬንያ በ፵፯ ካውንቲዎች (የአስተዳደር ክፍሎች) ተዋቅራለች። እነዚህ ካውንቲዎች በሕዝብ በተመረጡ ሰዎች የሚስተዳደሩ ሲሆን በናይሮቢ ከሚገኘው ማዕከላዊ መንግሥት በነፃነት ይንቀሳቀሳሉ። የኬንያ ዋና ከተማ እና ትልቋ ከተማ ናይሮቢ ናት። የኬንያ ኢኮኖሚ በምሥራቅና መካከለኛው አፍሪቃ በጂ.ዲ.ፒ. ትልቁ ነው። ግብርና በአገሪቱ ትልቅ የሥራ ዘርፍ ሲሆን ከኤክስፖርቶች መካከል ሻይ፣ ቡና እና ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ አበባዎች ይገኛሉ። እንዲሁም ቱሪስምና ፔትሮሊየም አቢይ ዘርፎች ናቸው። \n \nጥያቄ: ኬንያን ቅኝ የገዛቻት ሀገር ማናት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ብሪታንያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nመጠነ እንቅፋት የኤሌክትሪክ መጠነ እንቅፋት (ሬዚስታንስ) የሚባለው አንድ ኤሌክትሪክ አባል በውስጡ ሊያልፍ የሚሞክር የኤሌክትሪክ ጅረትን የሚያደናቅፍበት መጠን ልኬት ነው። የኤሌክትሪክ መጠነ እንቅፋት ከሰበቃ ጋር ተመሳሳይ ባህርይ አለው። የኤሌክትሪክ መጠነ እንቅፋት የተደረሰበት በ1819 ዓ፣ም በጆርጅ ኦም ሲሆን፤ በዚህ ሰው ጥናት መሰረት የአንድ ነገር ኤሌክትሪካዊ መጠነ እንቅፋት በዚያ ነገር ላይ ያለ የቮልቴጅ ለ በውስጡ የሚያልፍ ጅረት ሲካፈል ጋር እኩል ነው። በሒሳብ ቋንቋ፡ ለብዙ ቁሶችና ሁኔታዎች፣ የኤሌክትሪክ መጠነ እንቅፋት R ጸንቶ የሚቆይ ቋሚ ቁጥር ነው። ማለት በኤሌክትሪክ ጅረትና በቮልቴጅ መጠን አይቀየርም። እነዚህ ነገሮች ኦማዊ ቁሶች ይባላሉ። የአንድ ሽቦ መጠነ እንቅፋት መጠን በርዝመቱና በስፋቱ ይወሰናል። የሽቦው ርዝመት በጨመረ ቁጥር እንቅፋቱ እየጨመረ ይሄዳል፣ በአንጻሩ ስፋቱ ሲጨምር እንቅፋቱ ይቀንሳል። ልክ ውሃ በሰፊ ቱቦ ውስጥ በቶሎ ሊሄድ እንደሚችልና፣ በረጅም ቱቦ ውስጥ ብዙ ሰበቃ ስለሚገጥመው በቀስታ እንደሚጓዝ ሁሉ። ከዚህ በተጨማሪ የሽቦው መጠነ እንቅፋት ሽቦው ከተሰራበት ዕቃ ተፈጥሮ ጋር ይዛመዳል። ስለሆነም የአንድ ሽቦን መጠነ እንቅፋት በሒሳብ ለማስላት የሚከተለው ቀመር ይጠቅማል፡ ሽቦው የተሰራበት ቁስ ልዩ መጠነ እንቅፋት ሲሆን የሚለካውም በ ኦም-ሜትር ነው። \n \nጥያቄ: ለብዙ ቁሶችና ሁኔታዎች ጸንቶ የሚቆየው ቋሚ ቁጥር ምንድን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የኤሌክትሪክ መጠነ እንቅፋት R ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nናይጄሪያ ናይጄሪያ በይፋ የናይጄሪያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪቃ የምትገኝ አገር ናት። በሕዝብ ብዛትም ከአፍሪቃ አንደኛ ናት። ከቤኒን ፣ ቻድ ፣ ካሜሩን ፣ ኒጄር ፣ እና ከጊኒ ባሕረ ሰላጤ ጋር ድንበር ትካለላለች። በናይጄሪያ ውስጥ ትልቁ ብሔሮች ሀውዛ ፣ ኢግቦ እና ዮሩባ ናቸው። ግማሹ ሕዝብ እስላም ሲሆን ሌላው ግማሽ ደግሞ የክርስትና እምነት ይከተላል። ትንሽ የሕዝቡ ክፍልም ባህላዊ ሃይማኖቶችን ይከተላል። የሳይንስ ጥናት እንደሚያሳየው ናይጄሪያ ከ፱ሺህ ዓመታት ከክርስቶስ ልደት በፊት ጀምሮ ነዋሪዎች እንደነበሩባት ያሳያል። በቤንዌ እና ክሮስ ወንዞች አካባቢ ያለው ሥፍራ የባንቱ ፍልሰቶች መነሻ እንደ ነበረ ይታመናል። የናይጄሪያ ስም ከኒጄር ወንዝ ነው የተወሰደው። ናይጄሪያ በአፍሪካ በሕዝብ ቁጥር አንደኛ ስትሆን ከዓለም ደግሞ ሰባተኛ ናት። የናይጄሪያ ኢኮኖሚ በዓለም ላይ በፍጥነት በማደግ ላይ ካሉት ኢኮኖሚዎች ይመደባል። የዓለም አቀፍ ገንዘብ ፈንድ እንደሚገምተው የናይጄሪያ ኢኮኖሚ በ2011 እ.ኤ.አ. በ8% ያድጋል። \n \nጥያቄ: ናይጄሪያ የምትገኘው በየት አህጉር ውስጥ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አፍሪቃ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nስብሐት ገብረ እግዚአብሔር ስብሐት (ስብሐት ለአብ) ገብረ እግዚአብሔር (ሚያዝያ 27 [1928]ዓ.ም. - ሰኞ፣ ቀን ትግራይ ጠቅላይ ግዛት፣ አድዋ አውራጃ፣ እርባ ገረድ በተባለች መንደር ከአባቱ ከቄስ ገብረ እግዚአብሔር ዮሐንስ እና ከወይዘሮ መአዛ ወልደ መድኅን ተወለደ። ትምህርቱን በስዊድን ሚሲዮን፣ እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተከታትሎ በትምህርት አስተዳደር የመጀመሪያ ዲግሪውን ተቀብሏል። በአስፋ ወሰን ትምህርት ቤት በእንግሊዝኛ መምህርነት ለ2 ዓመት አገልግሏል። በመቀጠልም ከየተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፤ ሳየንስ እና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ባገኘው የትምህርት እድል አማካይነት ወደ ፈረንሳይ (ኤክስ አን ፕሮቫንስ) በመሄድ ከ1962-1964 ቆይቷል። የሄደበትን ትምህርት አጠናቆ ምስክር ወረቀት ባይቀበልም ቆይታው ከአውሮፓ ባህል እና ስነ-ጽሁፍ እንዲተዋወቅ በጣም እንደረዳው ይናገራል። ወደ ፈረንሳይኛ «Les Nuits d'Addis-Abeba» ተብሎ በፍራንሲስ ፋልሴቶ የተተረጎመውን የልብ-ወለድ ድርስቱን «ሌቱም አይነጋልኝ»ን ብዙውን ለመጻፍ የበቃው እዚያው በፈረንሳይ እንደሆነም ይናገራል። ይኸው ድርሰቱም ወደ ፈረንሳይኛ ቋንቋ የተተረጎመ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ልብ-ወለድ ነው። ስብሐት ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በኋላ በመነን መጽሄት የዝግጅት ክፍል ውስጥ ሰርቷል። በ1966 ዓ.ም. ወታደራዊው ደርግ ስልጣን ከያዘ በኋላ ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ሲቋቋም በአርታኢነት ተቀጥሮ ሰርቷል። በመንግሥት ትእዛዝም ከሌሎች ሰዎች ጋር በመሆን የካርል ማርክስ ሥራ የሆነውን ካፒታልን ከእንግሊዝኛ ወደ አማርኛ በመመለስ ሥራ ላይ ተሳትፏል። ብዙዎቹ የስብሐት ሥራዎች በተጻፉበት ጊዜ ለመታተም ባይታደሉም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን የህትመትን ብርሃን ለማየት በቅተዋል። ጽሁፎቹ ረዘም ላለ ጊዜ ሳይታተሙ ለመቆየታቸው ዋነኛው ምክንያቱ ስብሐት በመጽሐፉ የሚጠቀማቸው ቃላት ብዙዎቹ በኢትዮጵያ ባህል ያደገ አንባቢን አይን የሚያስፈጥጡ፣ ጆሮ የሚያስይዙ በመሆናቸው ነው። በገበያ ላይ በቅርብ የወጡት ድርሰቶቹ ከመጀመሪያ ቅጂያቸው ብዙ ለውጥ እና የአርትኦት ሥራ የተደረገባቸው እንደሆኑ ይነገራል። ስለዚሁ ጉዳይ ለአዲስ ላይቭ በሰጠው ቃለመጠይቅ ላይ ሲናገር «በጨለማ ያልተደረገውን ነገር አንድም የጻፍኩት የለም... ያለውን እንዳለ ነው የምጽፈው» ብሏል። ይህንኑም ከኤሚል ዞላ የአጻጻፍ ዘይቤ የወሰደው እንደሆነ ይናገራል። ስብሐት ገብረእግዚአብሔር ደራሲ፣ አርታኢ፣ ጋዜጠኛ ብቻ አይደለም - የልብ-ወለድ ድርሰት ገጸባህርይም ነው። ደራሲው የተሰኘው የበአሉ ግርማ ልብ-ወለድ በስብሐት ህይወት ላይ ተመስርቶ የተጻፈ ነው። ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር የ2 ወንዶች እና የ3 ሴቶች አባት ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ ነው። \n \nጥያቄ: ወደ ፈረንሳይኛ ቋንቋ ለመጀመሪያ ጊዜ የተተረጎመ ኢትዮጵያዊ ልብ-ወለድ መጽሐፍ ደራሲው ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nፀሐይ ፀሓይ በምድር ሥርዐተ-ፈለክ መኻል ያለች ኮከብ ናት። ምድር ሞላላ ቀለበት በሚመስል የዑደት ምሕዋር እየተጓዘች ፀሓይን ትዞራታለች። ሌሎች ሰማያዊ አካላትም፣ ፈለኮች፣ ፈለክ-አስተኔዎች፣ ጅራታም ከዋክብት እና ኅዋዊ ብናኞች በፀሓይ ዙሪያ ይዞራሉ። ምድር በፀሓይ ዙሪያ የምታደርገውን አንድ ዙር ጉዞ ለመጨረስ አንድ ዓመት ይፈጅባታል፤ ይህን ጉዞ ስታደርግም በገዛ ራሷ ዘንጎ ወይም ምሽዋር ዙሪያ እየሾረች ነው። ምድር በፀሓይ ዙሪያ የምታደርገው ዙረት ወቅቶች በዓመታዊ ዑደት እንዲለዋወጡ ከሚያደርጉት ምክንያቶች አንዱ ሲኾን፣ በራሷ ዘንጎ ዙሪያ የምታደርገው ሹረት ደግሞ በዕለታዊ ዑደት መዓልት (ቀን) እና ሌሊት ለሚያደርጉት መፈራረቅ ምክንያት ነው። ፀሓይ ለሥርዐተ-ፈለካችን በጣም ብሩህ የኾነ ብርሃን ትሰጣለች። ያለ ፀሓይ ብርሃን ሙቀትም ኾነ ሕይወት በምድር አይኖርም ነበር። ለምሳሌ አረንጓዴ ዕፅዋት ያለ ፀሓይ ብርሃን ሊኖሩ አይችሉም፤ ለህልውናቸው የሚያስፈልጓቸውን ካርቦን ዳይኦክሳይድ እና አልሚ ምግቦች ለማስተጻመር የሚችሉት በፀሓይ ብርሃን ብቻ ነውና። ከምድር ይልቅ ለፀሓይ ይበልጥ ቅርብ የኾኑ ፈለኮች ለከፍተኛ ጨረር እና ግለት የተጋለጡ በመኾናቸው በምድር ላይ ላለው ዐይነት ሕይወት ተስማሚ አይደሉም። ከምድር ጋር ሲነጻጸር ከፀሓይ በጣም ርቀው ያሉ ፈለኮችም ለሕይወት መኖር ምቹ ኹኔታዎች የሏቸውም፤ በቂ ብርሃን እና ሙቀት ካለማግኘታቸው የተነሣ። \n \nጥያቄ: መሬት በጸሐይ ዙሪያ የምታደርገው ዑደት ምን ያህል ጊዜ ይወስዳል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አንድ ዓመት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዶናልድ ጆን ትራምፕ ዶናልድ ጆን ትራምፕ (ጁን 14 ቀን 1946 እ.ኤ.አ. ተወለደ) አሜሪካዊ ነጋዴ ፣ ፖለቲከኛ ፣ በቴሌቪዥን ፕሮግራሞቹ ታዋቂ እና 45ኛው የዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ ፕሬዚደንት ነው። ሥልጣኑንም እ.ኤ.አ. በጃኑዌሪ 20 ቀን 2017 ተረክቧል። በክዊንስ ኒው ዮርክ ከተማ የተወለደው አቶ ትራምፕ በሪል እስቴት ሥራ ላይ ተሰማርቶ የነበረው የፍሬድ ትራምፕ ልጅ ነው። በኮሌጅ እያለም ኤሊዛቤት ትራምፕ ኤንድ ሰንስ በተባለው ድርጅት ይሠራ ነበር። በእ.ኤ.አ. 1968 ከኮሌጅ ከተመረቀ በኋላ ያንን ድርጅት ተቀላቀለ። በእ.ኤ.አ. 1971 ደግሞ ሙሉ ሥልጣን ከተሠጠው በኋላ የድርጅቱን ስም ወደ \"ዘ ትራምፕ ኦርጋናይዜሽን\" ለወጠው። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ካሲኖዎችን ፣ የጎልፍ ሜዳዎችን ፣ ሆቴሎችን እና ሌሎች በእርሱ ስም የሚጠሩ ንብረቶችን አፍርቷል። እ.ኤ.አ. ከ2005 እስከ 2015 ድረስ ዘ አፕሬንቲስ የተባለ ፕሮግራምን በኤን ቢ ሲ ላይ ያቀርብ ነበር። እ.ኤ.አ. በ2000 ላይ፣ ትራምፕ ለመጀመሪያ ጊዜ ለዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንትነት ተወዳድሮ ሁለት የሪፎርም ፓርቲ እጩነትን አሸንፎ ነበር። በእ.ኤ.አ. ጁን 16 2015 ላይ ደግሞ ለፕሬዚደንትነት እንደሚወዳደር አሳወቀ። ይህን ጊዜ ግን የሪፐብሊካን ፓርቲን በመወከል ነው። በስደት፣ በነፃ ገበያ እና በጦር ጣልቃ ገብነት ላይ ባለው ተቃውሞ ምክንያት ታዋቂ ሆኗል። በእነኚህ አነጋጋሪ አስተያየቶቹ በመላው ዩናይትድ ስቴትስ የተቃውሞ እና የድጋፍ ሰልፎች እንዲካሄዱ ምክንያት ሆኗል። በእ.ኤ.አ. ሜይ 2016 ከሪፐብሊካን የፕሬዚደንታዊ እጩነት ውድድሮች ውስጥ 28ቱን ውድድሮች ካሸነፈ በኋላ እና የተቀሩት ተቀናቃኞቹ እነ ቴድ ክሩዝ እና ጆን ካሲች ከውድድሩ ራሳቸውን ስላገለሉ፥ ትራምፕ ለሪፐብሊካን ፓርቲ እጩ መሆኑ የተረጋገጠ ሆኗል። በእ.ኤ.አ. ከጁላይ 18 እስከ 21 በተካሄደው የ2016ቱ የሪፐብሊካኖች አገር አቀፍ ስብሰባ ላይ እጩ መሆኑ በይፋ ታወጀ። በእ.ኤ.አ. ኖቬምበር 8 ቀን 2016 ላይ የፕሬዚደንትነት ምርጫውን አሸነፈ። ማሸነፉንም ተከትሎ ብዙ የተቃውሞ ሠልፎች በተለያዩ የአሜሪካ ከተሞች ውስጥ ተካሂዶ ነበር። በ70 ዓመቱም ሥልጣን ላይ በመውጣቱ ከእርሱ በፊት ከነበሩት ፕሬዚደንቶች ሁሉ በዕድሜ ትልቁ ያደርገዋል። \n \nጥያቄ: 45ኛው የዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ ፕሬዚደንት ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ዶናልድ ጆን ትራምፕ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nፐርል በክ ፐርል በክ በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ (1938) ለመሆን የበቃች አሜሪካዊት ደራሲ ናት። በክ ጁን 26 ቀን 1982 ዓ.ም በምእራብ ቨርጂኒያ ሂልዝቦሮ በተባለ ቦታ ተወለደች። ወላጆቿ ፕሬስብቴርያዊ ሚሲዮኖች የነበሩ ሲሆን ብዙውን የሚሲዮን ስራቸውን በቻይና ነው ያሳለፉት። በዚሁ የተነሳ በክ ከልጅነቷ ጀምሮ እንግሊዝኛን ብቻ ሳይሆን ቻይንኛንም አቀላጥፋ ትናገር ነበር። ትምህርቷን በ1914 እንዳጠናቀቀች ወደ ቻይና ነው ያቀናችው። በ1915 የወደፊት ባሏ ከሚሆነውን ከጆን ሎሲንግ በክ ጋር ተገናነች። በ1917 ጋብቻቸውን ከፈጸሙ በኋላ ኑሯቸውን ናንሹ በተባለችው የገጠራማዋ አንህዌ ግዛት አደረጉ። በዚሁ ቆይታዋ ነው ወደፊት የሥነ-ጽሁፍ ስራዋ ጉልላት ለመሆን የበቃውን ስሙር መሬት (The Good Earth) ለተባለው መጽሃፏ የሚሆናትን መረጃ የሰበሰበችው። በክ ጽሁፎቿን ማሳተም የጀመረችው ከ1920ዎቹ ጀምራ ሲሆን አጫጭር ስራዎቿ \"The Nation\"፣ \"The Chinese Recorder\"፣ \"Asia\" እና \"The Atlantic Monthly\" በተሰኙ መጽሄቶች ታትመውላታል። የመጀመሪያው ወጥ ልብ-ወለድ ድርሰቷ (East Wind, West Wind) በ1930 በጆን ዴይ ኩባንያ ታትሟል። የጆን ዴይ ኩባንያ አሳታሚ የነበረው ሪቻርድ ዋልሽ ኋላ ላይ (1935) የፐርል በክ ሁለተኛ ባሏ ለመሆን በቅቷል። በ1931 ጆን ዴይ ኩባንያ የፐርል በክን ሁለተኛ ወጥ ልብ-ወለድ ድርስት የሆነውን ስሙር መሬትን አሳተመ። ይኸው ሥራዋ በተከታታይ በ1931 እና በ1932 ዓ.ም በገበያ ላይ አንደኛ ተፈላጊ ሆኖ ለመዝለቅ የቻለ ሲሆን ለሷም በ1935 ዓ.ም የፑሊትዘር ሽልማት እና የሃዌልስ ሜዳልያ አስገኝቶላታል። ስሙር መሬት በ1937 ዓ.ም በኤም.ጂ.ኤም አማካይነት በፊልም መልክ ተቀናብሮ ለተመልካች ቀርቧል። ከዛ በተከታታይ ሌሎች ድርሰቶችን ለአንባቢ አቅርባለች። በክ በ1938 ዓ.ም በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን በመቀበል የመጀመሪያዋ (ሴት) አሜሪካዊት ሆናለች። ፐርል በክ በ1973 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ስትለይ ከ70 በላይ ስራዎቿ ታትመውላታል። መቃብሯም ፔንሲልቬንያ ውስጥ በክስ በተባለው ቀበሌ ይገኛል። \n \nጥያቄ: አሜሪካዊት ደራሲ ፐርል በክ በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ የሆነችው በስንት ዓመተ ምህረት ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 1938 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nፓርጦሎን ፓርጦሎን በአየርላንድ ልማዳዊ አፈ ታሪክ ዘንድ ከማየ አይኅ ጥቂት ክፍለ ዘመናት ቀጥሎ መጀመርያው በአይርላንድ ደሴት ላይ የደረሱት ሰፈረኞች መሪ ወይም ንጉሥ ነበር። የፓርጦሎን ስም በታሪክ መጻሕፍት መጀመርያው የሚታወቅ በ820 ዓ.ም. አካባቢ በሮማይስጥ በተጻፈው ሂስቶሪያ ብሪቶኑም («የብሪታንያውያን ታሪክ») ሊገኝ ይችላል። በዚሁ ጽሁፍ መሠረት፣ «ፓርጦሎሙስ» ከ1 ሺህ ሠፈረኞች (ወንዶችና ሴቶች) ጋር ደረሰ፣ እስከ 4 ሺህም ድረስ ቶሎ ተባዙ፣ ነገር ግን ድንገት በአንድ ሳምንት ውስጥ ሁላቸው ከቸነፈር ሞተዋልና አገሩ እንደገና ባዶ ሆነ። ይኸው መጽሐፍ በአየርላንድኛ ትርጉም ደግሞ ቸነፈሩ በፓርጦሎን ሕዝብ ላይ የመጣበት ጠንቅ ፓርጦሎን ከኗሪ አገሩ ገና ሳይወጣ ወላጆቹን ገድሎአቸው ስለ ነበር የአምላክ ፍርድ ነው በማለት ይጨምራል። ከዚህ በላይ የፓርጦሎን መነሻ አገር እስኩቴስ እንደ ነበር፣ የማጎግ ተወላጅ እንደ ነበር ይታመን ነበር። የስኮት (በስኮትላንድና ቀድሞ በአይርላንድ የተገኘ) ብሔር ስም ከዚህ እስኩቴስ እንደ መጣ በድሮው መጻሕፍት በሰፊው ይጻፍ ነበር። \n \nጥያቄ: ሂስቶሪያ ብሪቶኑም የብሪታንያውያን ታሪክ መቼ ተጻፈ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ820 ዓ.ም. ነው።" } ]